አትሮኖስ
286K subscribers
120 photos
3 videos
41 files
573 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ጥላቻ_እና_ፍቅር

ከጥላቻሽ ብዛት
አቃጥለሽ ብትገዪኝ አርከፍክፈሽ “ቤንዚን”
ይስ ይልሽ ነበረ ፤
ኖሮሽ መርዘሽኝ ብትገዪኝ በ"ራይዚን”
ደስ ይልሽ ነበረ፤
እሳተ ጐመራ በድንገት ፈንድቶ
ወዲያው ቢጠፋልሽ እኔን ብቻ አጥፍቶ
ደስ ይልሽ ነበረ፤
ሰማይ ቢያዝንብልሽ ቀላቅሉ በረዶ
ጐጆዬ እንዲገለኝ ላዬ ላይ ተንዶ
ምኞትሽ ነበረ
ደስታሽም ነበረ
በ “ነበረ” ቀረ፡፡
ወይ ነዶ!... ወይ ነዶ!... ይኸው እኖራለሁ
ወይ ወዶ!... ወይ ወዶ!... ውዴ አፈቅርሻለሁ::
ጥላቻሽን ፋቂው
እውነቱን እወቂው፡፡
ከፍቅሬ የተነሳ
ይጨንቃል ማሰቡ ኑሮዬን ያላንቺ
ከዚህ ዓለም ብጠፋ የኔ ውድ ብትሞቺ
ከፍቅሬ የተነሳ
አዕምሮዬ አምኖ እንዴት ይቀበላል?!?
እንዴት እሆናለሁ?!? ሞትሽ ከፍቶ ያይላል፡፡
ጨርቄን ያስጥለኛል እርቃን ያስቀረኛል
የኔ ውድ ብትሞቺ የማብድ ይመስለኛል፡፡
ሞትሽ ይቅርና
ካይዬ ሦር ሰሸትርቂ ላንዲት ቅፅበት እንኳን
ሐዘኔ ይከፋና
በፍጥነት ልቤ ውስጥ ይተከላል ድንኳን
ከፍቅሬ የተነሣ
ያለአንቺ አልኖርም ሕይወቴ ጣዕም ያጣል
ይኼውልሽ እንዲ ነው
ፍቅር ከጥላቻ ሺ ጊዜ ይበልጣል።

🔘ፋሲል ተካልኝ🔘
#ማምሻ


#ክፍል_ሦስት


#በአሌክስ_አብርሃም


ጀብድ ሠርቶ እንዳመለጠ የግፍ እስረኛ፣ በአድናቆትና እንኳን ተሳካላቸው ሰሚል ስሜት
የተሞላ ነበር፡፡

እማማ ዓምድነሽ፣ ልጃቸውን ማምሻን አይገቡ ገብተው አሳደጓት: ሰው ቤት ልብስ እያጠቡ፣ ጉሊት እየቸረቸሩ ትምህርቷን ሊያስተምሯት ጣሩ፡፡ ማምሻ ግን ትምህርቱም ብዙ አልሆነላትም፡፡ የሰፈሩ ማንጓጠጥ ትምህርት ቤትም ተከትሏት ነበር፡፡ እየወደቀች እየተነሳች እንደምንም ዘጠነኛ ክፍል ደርሳ አቆመች:: የሻይ ቤት አስተናጋጅነት ሥራ እንዲያፈላልግላት ደላላውን በሽርን ብትጠይቀው፣ ያንን ጫት የተለሰነበት ጥርሱን
እየገለፈጠ “ማምሻ! በዚህ ፊት አስተናጋጅነት!?…”አላት አሉ፡፡ ይህም አንድ ሰሞን
ተሳቀበት…በኋላ በወር ሰማንያ ብር እየተካፈላት የሰፈራችን ቦኖ ውሀ አስቀጅ ሆነች::
ውሀ አታፍስሱ ያለቻቸው የመንደሩ ሴቶች ያንኑ ቁሰሏን በሽሙጥ ስንጥር እየነካኩ፣
በመልከጥፉነቷ እያሸሞሩ ቁጡ አደረጓት፡፡
“ቆጥባ መልከ ጥፉነቷን ልታጥብብት ነው?
እያሉ:: በነጋ በጠባ ጸብ ሆነ፡፡

አንድ ቀን ማምሻ አንዷን አሽሙረኛ እንደ ነብር ዘልላ ተከመረችባት፡፡ ማን ያላቅቃት?
የዘመናት ብሶቷን እዚያች ዕጣው እወደቀባት ሴት ላይ አራገፈችው፡፡ በትርምሱ የውሀ
መቅጃ እንስራም አልተረፈ፣ ተከለከከለ፡፡ ከዚያቹም ሥራ ተባረረች፡፡ ደግሞ የማባረሪያ
ምክንያቱ ግነት! “ሕዝብ እንድታገልገል በተቀመጠችበት ቦታ፣ ሥልጣኗን ተገን
በማድረግ፣ ተጠቃሚውን ኅብረተሰብ በመደብደብና ንብረት በማውደም ቦንብ ጣይ
አውሮፕላን እያበረረች አንድ ከተማ ሕዝብ የደበደበች ዓይነት! ኅብረተሰቡን
በመደብደብ እና ንብረት በማውደም!”

ተራ ፌዝና ስላቃችን አንገት ያስደፋት ማምሻ፣ ሁሉንም እርግፍ አድርጋ ትታ፣ ባልቴት
እናቷ በየሰው ቤት ሠርተው በሚያመጧት ሳንቲም ኑሮዋን እየገፋች የወጣት ጡረተኛ ሆና እቤት ተቀመጠች፡፡ ይኼ መገፋት አጉብጧት እንዳቀረቀረች፤ እንጀራዋን እዚያው ባቀረቀረችበት አገኘችው፡፡ ልክ እንዲሰምጥ ወደ ባሕር የገፈተሩት ሰው የሚያስጎመዥ ዓሣ ይዞ የመውጣት ዓይነት ነበር ነገሩ፡፡ ማምሻ እንዳቀረቀረች ኪሮሽና ክር አነሳች፡፡እንዳቀረቀረች መርፌና ክር ታጥቃ በመራሩ ድህነት ላይ ዘመተች፡፡ በሰፊው የድህንትጥቁር ሸማ ላይ ውበትን ዘራችለት፡፡ ከዚያ የተገፋ ልብ፣ ያ ውበት እንዴት ወጣ?እላለሁ አንዳንዴ፡፡
ውበታቸው የመንደሩን ብቻ ሳይሆን፣ ከየትና የት ድረስ የሚመጡ የከተማውን ሴቶችን የሚያሻማ፣ ከምሶብ ዳንቴል እስከ ኤልጋ ልብስ፣ ከኩርሲ እስከሶፋ ልብስ፣ ከመጋረጃ እስከ ሐበሻ ቀሚስ ድረስ የጥልፍ ማጎተሟን አሳረፈች፡፡ ሰፈራችን በሙሉ በማምሻ የእጅ ሥራዎቿ ተጥለቀለቀ፡፡ የማምሻ ጥልፍ ያረፈባቸው መጋረጃወች በየመስኮቱ ተሰቅለው ሲታዩ፣ ማምሻ ገፊዎቿን በእጁ ጥበብ ድል ነስታ፣ ባንዲራዋን በድል
እድራጊነት በየቤቱ የሰቀለች ይመስል ነበር፡፡

በመቋጨት ይሁን በመጥለፍ፣ የማምሻ እጅ ያረፈበትን የባህል ቀሚስ ይሁን ነጠላ ለብሳ
ያልተውረገረገች፣ አንድ የመንደሩ ሴት ብትኖር፣ ማምሻ ራሷ ብቻ ነበረች። እንዲህ እያገባኝ ገብቼ የማምሻን የእጅ ሥራዎች ስመለከት፣ ከሌሎች ጥልፎች የተለዩ ይሆኑብኝ ነበር። ፍዝዝ ያለ ቀለም ባላቸው ክሮች፣ ደማቅ መደብ ላይ የምትጠልፋቸው አበቦች የራሷን ምስል የምትስል ሠዓሊ እስክትመስለኝ፣ አንዳች የሚያሳዝን ስሜት ውስጥ የሚያስገቡ ነበሩ:: በዚህም ሥራዋ እራሷን ባልቴት እናቷን በክር ጎትታ፣አንገታቸው
ከድህነት አዘቅት ብቅ እንዲል አደረገች፡፡ እናቷ በየሰው ቤት መንከራተት አቁመው እቤታቸው አረፉ፡፡ መንደርተኛውም ከማምሻ መልክ ይልቅ የእጅ ሥራዎቿ ዓይኖቹን ጋርደውት ከመዝለፍ ይልቅ ወደማድነቅ እና ማክበር የተሸጋገረ መሰለ፡፡ በእርግጥም ማምሻ መልከጥፉ ፊቷን በብርቱ እጆቿ ሽፍናው ነበር፡፡

ስም ውስጥ ሟርት አለ፡፡ ማምሻ እንደስሟ ማምሻ ሆነች: ሁሉም ነገር የተቀያየረው ድንገት ነበር፡፡ የእጅ ሥራዎቿን ሙሉ ለሙሉ ከገበያ ውጭ የሚያደርግ አጋጣሚ። ፈጣን እና በኤሌክትሪክ የሚሠሩ የጥልፍ መኪኖች በከተማው ውስጥ እንደ አሸን ፈሉ።
በአንድ ጀምበር ድፍን መንደር የሚያለብሱ፣ በደማቅ ከሮች ፎቶ የመሳሰሉ አበቦችን
የሚጠልፉ የ “ሲንጀር መኪኖች፡፡ የማምሻ ተስፋ ሟሸሽ! ጥበቧም ከምንም እስከ ሲንጀር መኪና ባለው ክፍተት መሀል ማምሻ መሸጋገሪያ ሆነ። በኑሮ አድማሷ ላይ ድንገት ብቅ ያለች ጀምበሯ፣ ሙቀትና ብርሃኗን በቅጡ ሳታጣጥማት ድርግም ብላ ጠፍታ፣ ዳግም የድህነትና የማንጓጠጥ ዝናብ ያዘለ ደመና በላይዋ ላይ ያንዣብብ
ጀመረ፡፡ ዳግም ወደ ማቀርቀር፣ ዳግም አንገት ወደ መድፋት ተመለሰች፡፡ ግና ምንም ያልተነኩ ቱባ ክሮችን ሰብስሳ ወስዳ ለባለሱቁ ከድሩ በርካሽ ሸጠችለት ተባለ፡፡ ያም የማምሻ የጥልፍ ሥራ ማብቂያ ሆኖ በጎረቤቱ ዘንድ ተወራ፡፡ በዚህም ተቀለደ፡፡ “ማምሻ ኪሮሽ ሰቀለችተባለ፡፡ የእግር ኳስ ተጫዋቾች መጫወት ሲያቆሙ
ጫማ ስቀሉ” እንደሚባለው መሆኑ ነው፡፡ቀስ በቀስ እናቷ ወደ ሰው ቤት ሥራ ተመለሱ፣ ማምሻም እናቷን ለማገዝ እንጀራ መጋርና መሸጥ ጀመረች፡፡ ታዲያ በዚህ መሃል ትንሽ በጎነት ያሳየቻት ሴት ብትኖር፣ ሎዛ ነበረች፡፡ ከአባቷ ጣውላ ቤት የእንጀራ መጋገሪያ ሳጋቱራ በነፃ እንድትወስድ አስፈቅዳላት ነበር፡፡

ባልገባኝ ምክንያት የሎዛ ዓይኖች ሁልጊዜ ማምሻ ላይ ነበሩ፡፡ የሰፈሩ ሰው ርግፍ አድርጎ
በተዋቸው ሰዓት እንኳን የማምሻ እጅ ስራ የተጠለፈባቸው ልብሶችን ትለብስ የነበረች
ሴት ሎዛ ብቻ ነበረች፡፡ እንደውም ለእኔም ከማምሻ የገዛችውን አንድ የባህል ልብስ
ስጦታ ሰጥታኝ ነበር…ለብሸው ግን አላውቅም፡፡
።።።።።።።።።።።
ሎዛ ደውላ ሄይ አብርሽ… ከሥራ ስትወጣ እቤት እመጣለሁ፣ ጠብቀኝ አለችኝ፡፡
ከሥራ ስመለስ ቀድማኝ እኛ ቤት ደርሳ፣ የምትወደውን የጦስኝ ሻይ እየጠጣች ከእናቴ
ጋር ሲያወሩ ደረስኩ፡፡ እናቴ ፊት ብትስቅም ገና ሳያት እንዳኮረፈች ገብቶኝ ነበር፡፡
"ሙሽሪት” አልኩና በትከሻዬ ገፋ አድረጊያት ገባሁ፡፡ እናቴን ተሰናብታ ተያይዘን እንደወጣን፣ “ማምሻ ጋ አካሂደኝ አለችኝ፡፡

ለምን?

“ሚዜነቷ እንደቀረ ልነግራት!”

ቀረ እንዴ?” ዞር ብላ በብስጭት አይታኝ፣

“ደስ አለህ?” አለችኝ፡፡

“ለምን ደስ ይለኛል? …ግን አለ አይደል …”

በውስጤ ግን ደስ ብሎኝ ነበር፡፡ በትዝብት አይታኝ፣

በቃ ቀርቷል፡፡ አባባ ተዪው አለኝ፡፡ ማሚ አሳምናው መሆን አለበት፡፡ማንም ሰው ከጎኔ
አልቆመም፣ ደከመኝ” አለች፡፡ ስልችት ያላት ትመስል ነበር፡፡ ተያይዘን እነማምሻ ቤት
ስንደርስ፣ ማምሻ የዘመመችው የጭቃ ቤታቸው ጋር ተያይዛ ከላስቲክ እና ከቆርቆሮ
ተሠራች ማድ ቤት ውስጥ ከጭስ ጋር እየታገለች እንጀራ ስትጋግር አገኘናት፡፡
ከማድ ቤቷ አጎንብሳ ስትወጣና አይታን ፈገግ ስትል ዓይኔን ማሳረፊያ ሌላ ቦታ ፈለግሁ፡፡
የማይለመድ መልከ ጥፉነት ነው ያላት፡፡ መልከ ጥፉ ብቻ አይደለችም… የሆነ በቀለኛ አጋንንት
ፊቷን በአጉሊ መነጽር እያየ ትንሽ ሰው ሊስብ ይችላል ያለውን ነገር ሁሉ እየለቀመ ያፈራረሰው ነበር የሚመስለው፡፡ እኔ ነኝ ያለ ደራሲ ይቅርና ፎቶ አንሺ እራሱ የማምሻን መልከ ጥፉነት በበቂ ሁኔታ አሳይቶ መጨረስ የሚችል እስከማይመስለኝ፣ ፊታ እንደ አዲስ አስገረመኝ፡፡ ምን ይሳነዋል ልሥራው ካለ ይሠረዋል፤ ላበላሸው ካለ ያበላሸዋል እላለሁ ለራሴ::

ወደ ቤታቸው እየመራች አስገባችን፣ የቤቷ ውስጥ ካሰብኩት በላይ እጅግ ንጹሕና በሥርዓት የተዘጋጀ ነበር የማምሻ ዘመን ያለፈባቸው ጥልፎች እንደሙዚየም ከአልጋ እስከ ኩርሲ በሥርዓት ለብሰው ተቀምጠዋል
👍3
እንደገባን “ትኩስ እንጀራ በበርበሬ ላቅርብላችሁ” አለችን፡፡ እኔ “አይ!” ስል ሎዛ ግን እሺ እንዲያውም ርቦኛል” አለች።

እንጀራ በበርበሬ እየበላን፣ በመሃል ሎዛ መብላቷን አቁማ ማምሻ ብላ ተጣራች፡

“የመጣሁት ሚዜነትሽ እንደቀረ ልነግርሽ ነው፤ እኔ እንኳን ሚዜዬ እንድትሆኚ ነበር የፈለከት፣ ግን ሁሉም ሰው አይሆንም አለ ሰርጉ የእኔ ቢሆንም የደገስኩት ግን እኔ አይደለሁም!… ሚዜ ሆንሽም አልሆንሽም እኔ እወድሻለሁ፣ ጓደኛዬ ነሽ” ብላ ተነስታ አቀፈቻትና እንባዋ ተዘረገፈ፡፡

ማምሻ ግን ፈገግ ለማለት እየሞከረች “ሎዛዬ አታልቅሽ የኔ ቆንጆ! ሙሽራ እያለቅስም
ነግሬሽ ነበርኮ…እኔ ከሕፃንነቴ ጀምሮ የለመድኩት ነው፡፡ መቼም ሰርግሽ ላይ እትገኚ አይሉኝ እህቴ ስታገቢ መጥቼ አቀውጠዋለሁ” አለች፡፡ ሎዛ እንባዋን እየጠረገች በቅሬታ ፈገግ አለች፡፡ ግን እንደገና አቅፋት ማልቀስ ጀመረች …ለቅሶዋ ውስጥ እልህና መሸነፍ ነበር፡፡
ከነማምሻ ቤት ስንወጣ ሎዛን ለማጽናናት ክንዷን ያዝኳት፡፡ እጇን መንጭቃኝ ሂድ! አንዲት ቆንጆ ነርስ ሚዜ አምጥተውልሃል፤ እንዲያውም የአእምሮ ሐኪም ብትሆንልህ ይሻል ነበር፡፡ ሂድ አብረሃት ዳንስ ተለማመድያ ከተሳካልህም አብረሃት ተጋደም፡፡ እምቢ የምትል ዓይነት አይደለችም ብላኝ እዚያው የቆምኲባት ትታኝ ወደቤቷ ሄደች፡፡እንዴI እኔ ምን ላድርጋት ታዲያ? ይቺ ልጅማ ችግር አለባት፡፡ አሁን የሰርጓ ቀን ነው፤
ይለፍና እንነጋገራለን” ብዬ ወደ ቤቴ ለመመለስ ካሰብኩ በኋላ ሀሳቤን ቀይሬ
ተከተልከኳት የሆነ ሆኖ የማምሻም የሎዛም ነገር ከአእምሮዬ ወዲያው ወጥቶ የቆንጆዋ ነርስ ነገር አጓጓኝ፡፡ እቤት ስንደርስ ልብ ስንጥቅ የምታደርግ የጠይም ቆንጆ በፍኖት እየተመራች ወደእኔ መጥታ እየተሸኮረመመች ተዋወቀችኝ … “ፌበን" አለችኝ፡፡ ስትናገር አንገቷን ትሰብቃለች፡፡ ለስላሳና ውብ እጆቿን ጨብጨ አብርሃም” አልኩ! ተያየን፡፡
ዓይኖቿ ያምራሉ፡፡ ፈገግታዋ አዙሮ ይደፋል፡፡ የጎረስኩት የማምሻ እንጀራ በበርበሬ አፌ
ውስጥ ማቃጠሉ ይሰማኛል “ከፍትፍቱ ፊቱ” ብዬ ተረትኩ ለራሴ፡፡ ዞር ስል ከሎዛ እህት ከፍኖት ጋር ዓይን ለዓይን ተገጣጠምን እና ጠቀሰችኝ፡፡ ወደ ፌበን ዞሬ “ከዚህ በፊት ሚዜ ሆነሽ ታውቂያለሽ” አልኳት፣

የመጀመሪያዬ ነው…አንተስ?”

እኔም እንዳንች ዓይነት ቆንጆ ሳይ የመጀመሪያዬ ነው”

“ወሬኛ” ብላ በወዳጅነት ትከሻዬን ቸብ አደረገችኝ፡፡ በኋላ ፍኖት፣ ስለዚህ “ቸብታ ሎዛ
እንዳትሰማ በሹክሹክታ ስትቀልድ እንዲህ አለች፣

ይኼ ቸብ ያረህ እጅ የማምሻ ቢሆን ኑሮ፣ መፍለጫ እንዳረፈበት ጕቶ ለሁለት
ተሰንጥቀህ ወለል ላይ ትበታተን ነበር፡፡ ዕድሜ ለኔም የታፈነ ሳቃችን ቀልዱን በሚስጥር አጀበው

የሎዛ ሰርግ ከሙሸራ እስከሚዜ ፣ከምግብ እስከ አዳራሽ እስደማሚ ሁኖ እለፈ፡፡ ማታ ሙሽሮች ሲወጡ፣ ታዳሚው ቆሞ እያጨበጨበ እትሸኟትም ወይ” ሲባል፣ ፌበንን ከጎኔ እድርጌ ከሙሽሮች ኋላ በዝግታ ስንጓዝ… ሎዛ ድንገት የመውጫውን በር ትታ ግራ በኩል ቬሎዋን እየጎተተች ሄደች፤ ባሏም ሚዜዎቹም ግራ ተጋብተን እንደቆምን፣ በውድ የሐበሻ ቀሚስና በወርቅ የተንቆጠቆጡትን አክስቶቿን አልፋ፣…እንደነገሩ የለበሱትና ትንሽ ነጠል ብለው የቆሙትን፣ ማምሻና እናቷ ቁመው ወደሚያጨበጭቡበት መቀመጫ ሄዳ
፣ ተራ በተራ አቀፈቻቸው፡፡ ማምሻ ከዘፈኑና ከጭብጨባው በላይ በሚሰማ ሳግ
በተቀቀለበት ድምፅ ስቅስቅ ብላ አለቀሰች፡፡ ሎዛ ግን ፊቷ በእልህና በቁጣ ክርር እንዳለ፣ ሰላም ሊሏት የሚሻሙ እኮስቶቿን እንዳላየች አልፋ ተመልሳ መንዷን ቀጠለች። ዓይኔን ወደፌበን መለሰኩ፣ ያ ውብ ጥርሷ አንጀት በሚያርስ ፈገግታ ተቀበለኝ፡፡ በእውነት ይቺ ልጅ ቦታዋ ሚዜነት ብቻ አይደለም እስከምል በውስጤ፡፡

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍2
አትሮኖስ pinned «#ማምሻ ፡ ፡ #ክፍል_ሦስት ፡ ፡ #በአሌክስ_አብርሃም ጀብድ ሠርቶ እንዳመለጠ የግፍ እስረኛ፣ በአድናቆትና እንኳን ተሳካላቸው ሰሚል ስሜት የተሞላ ነበር፡፡ እማማ ዓምድነሽ፣ ልጃቸውን ማምሻን አይገቡ ገብተው አሳደጓት: ሰው ቤት ልብስ እያጠቡ፣ ጉሊት እየቸረቸሩ ትምህርቷን ሊያስተምሯት ጣሩ፡፡ ማምሻ ግን ትምህርቱም ብዙ አልሆነላትም፡፡ የሰፈሩ ማንጓጠጥ ትምህርት ቤትም ተከትሏት ነበር፡፡ እየወደቀች…»
#እውነቱ

" የፍቅር ታሪኬ ደምቆ
ሳቢና ማራኪ ይሆናል
የኑሮዬ ገድል ልቆ
ከሰው ተለይቶ ይገናል”
ብዬ እንኳን ለሀገር
ለሰው ሁሉ ልናገር
ለአንዲቷም ቅፅበት
እንደዋዛ እንደዘበት
ለራሴው ተንፍሼ አላውቅም
ከነፍስሽ ይነጥለኝ!
መቼም ካንቺ አልደብቅም።
እውነት እውነት
መከራው ገዝፎ የታየ
ከስው ሁሉ የተለየ
ገድል አለኝ ብዬ ራሴን ከሰው ተራ አላርቅም
ታሪክ አለኝ ብዬ አልንቀባረርም አልመፃድቅም፡፡
ካንቺ ጋር ለዘላለም ምኖረው
እንደነፍሴ አንቺኑ ማፈቅረው
ታሪኬና ገድሌ
በሥመጥር ፀሐፍት እንዲፃፍ ለዓለም
በዕውቅ ሠዓሊያን እንዲሳል በቀለም
ፈልጌ እኮ አይደለም፡፡
አይደለም! አይደለም
ካንቺ ጋር ለዘላለም ምኖረው
እንደነፍሴ አንቺኑ ማፈቅረው
ከላይ ታች ምለው
ሠርክ ምባትለው ሠርክ ምባዝነው
ጀንበር ስትፈነጥቅ ስታዘቀዝቅም
ከጐንሽ ሳልጠፋ በሐዘን በደስታ አብሬሽ ምሆነው
ከአገር ሁሉ ከሰው ተለይቶ ስሜም የገነነው ፤
በሌላ እኮ አይደለም ይኸውልሽ እውነቱ ስለ ማፈቅርሽ ነው::
እያረፉ ይጣሉት እያረፉ ያንሱት እንዳሻቸው ስሜን
እኔ አፈቅርሻሁ ዕድሜ ዘላለሜን አሜን!
አሜን! አሜን!..

🔘ፋሲል ተካልኝ🔘
#ቸግሮኝ_እኮ_ነው

ቃልኪዳን አጉድዬ
እምነትን ገድዬ
ፍቅርንም በድዬ
ባሕል ልማድ ጥሼ
ሕግም ተላልፌ
በነፍሴ ቆርጬ
ሞገድ አሳብሬ
ፅልመቱን ገፍፌ
ይቅርታን አዝዬ
ምሕረትን ታቅፌ
እንደ ወፍ ከንፌ
እንደ ወፍ በርሬ
ትናንቱን ዘንግቼ
የመጣሁት ዛሬ
እህል ተቸግሬ
አጥቼ አይደለም
እልሰው እቀምሰው
ታርዤም አይደለም
አጥቼ እምለብሰው
ልሞላም አይደለም
ባዶ አቁማዳዬን
በእግዜር ስም ለምኜ
እደጅሽ ላይ ሆኜ
እምልከሰከሰው
ችግሮኝ እኮ ነው
እንዳንቺ ያለ ሰው።
ከቆዳሽ ውስጥ ዘልቆ
ከነፍስሽ ሥር ጠልቆ
ይስማሽ ችግሬ
ታውቂዋለሽና
ፍቅር ምን እንደሆን
ቀድሞውኑ ፍቅሬ፡፡
ፍቅር ይገባዋል
ልብሽ ለመረዳት መቸም አይሳነው
አይችሉትን ችዬ አይሆኑ ምሆነው ፧
ከቸገረኝ ሰው ውስጥ ፍቅርን ፍለጋ ነው።

🔘ፋሲል ተካልኝ🔘
#ድምጽ_አልባ_ዝምታ

ድምጽ አልባ ዝምታ
ሲበየን ሲፈታ ምን ትርጉም ይሰጣል?
እንዴትስ ተደርጐ በቃል ይገለጣል?!?
ድምጽ አልባ ዝምታ
በትግል ሲፈታ
ከአመጽ ማህፀን
አይሎ ሲወጣ ልብን ያሸብራል
በእጅጉ ያስፈራል
የራሱን ዝምታ በጩኸት ይሰብራል
ጫጫታን ሁካታን በድንገት ይፈጥራል::
ድምጽ አልባ ዝምታ ቋንቋ አለው ያወራል!!
ድምጽ አልባ ቢሆንም ዝምታ ይናገራል
ለገባው ቋንቋ ነው
“ውሃ” ሲቀዘቅዝ “በረዶ” እኮ ይስራል::
ተራራ አክሎ ተከምሮ ኖሮ
ድንገት ሳይታሰብ በማመጽ አምርሮ
ድምጹ ይደመጣል
ጩኸቱ ያናውጣል
የበረዶ አለት
የፈራረሰ ዕለት!!
ሰምና ወርቅ ያለው
ቅኔው እንደሆነ ውሃ የተቀኘለት
ሁሉም ጫኺ ሆኖ
የቋዋንቋውን ፍቺ ማን ይተርጉምለት?!?
በማን ነው እሚፈታ?
በምን ነው እሚፈታ?
ድምጽ አልባ ዝምታ!!!

🔘ፋሲል ተካልኝ🔘
👍1
#Re_post

#ያመት_በአል_ማግስት_ትእይንቶች!!

- የተመጠጠ ቤት
የሞላ ሽንትቤት
ጭር ያለ ቤተሰብ
የተጠረገ ድስት -ድርቅ የመታው ሞሰብ!!
-ያደፈ ቄጤማ
በበግ በሰው እግር- የተደቀደቀ
ወዙ ባንድ ሌሊት -ተመጦ ያለቀ
መጥረጊያ ሚጠብቅ -ወድቆ ተበታትኖ
ትናንት ጌጥ የነበር- ዛሬ ጉድፍ ሆኖ!!
-የተወቀጠ ፊት -የነጋበት ድንገት
በዳንኪራ ብዛት-ወለም ያለው አንገት
የዞረበት ናላ -ጌሾ ያበከተው
እንኳንስ መገንዘብ -መጀዘብ ያቃተው
የወለቀ ወገብ -የዛለ ትከሻ
መኪና ይመስል -ብየዳ የሚሻ
-የጠጅና የጢስ- ድብልቅ እስትንፋስ
ከሆድ ሸለቆ ውስጥ -የታፈነ ነፋስ
ባንጀት የታሰረው
እንደተከበበ አመፀኛ ሽፍታ
መውጫ የቸገረው!
-የማይፈካ ሰማይ -የማይዘንብ ደመና
በላባና በፈርስ -ያደፈ ጎዳና
በበግ ራስ ምላስ -የተልከሰከሰ
የጠገበ ውሻ-
በመንፈቅ አንድ ጊዜ አጥንት የቀመሰ::
ሀንጎቨር ያዛገው-መሂና አሽከርካሪ
እግረኛ አስደንባሪ
በከፊል የነቃ -በከፊል የተኛ
ከሱ የማይሻል- የመኪና እረኛ
ካውራ ጎዳናው ዳር -ቁሞ ሚያንቀላፋ
ድብርትን ባናቱ -እንደ ቆብ የደፋ!!
The moral of the story :
የተድላ ማገዶ!!
ላጭር ጊዜ ነዶ
ላጭር ጊዜ ደምቆ
ላጭር ጊዜ ሙቆ
አመዱ ብዙ ነው: አያልቅም ተዝቆ!!

🔘በውቀቱ ስዩም🔘
👍1
#በልጅነቴ_ይሄን_ተማርኩ

ልጅ ሆኜ...
የአባቴ ዘመዶች እማዬ በሌለችበት ሲመጡ ፤ እሷ ዘመዶቿ ሲመጡ እንደምታደርገው ቤት ውስጥ ያለውን፣ እንቁክ ሁኩ ጠብሼ ፣ በብዙ ዳቦ
አቀረብኩላቸው ።ማይዬ መጥታ የሆነውን፣ ስታውቅ ክፉኛ ገረፈችኝ።

ደግነት፥ ወገንተኝነት መሆኑን ያወኩት ያኔ ነው : :

ሁሌም ከኪሱ ብሮች የማይጠፋው ጓደኛኔ ጋር እየሄድን ነበር ፡ : አንድ ጉስቁልቁል ያለ ልጅ ፣
"ዳቦ ግዙልኝ” በርሃብ እያዛጋ ጠየቀኝ ።
ሁኔታውን ዐይቼ አላስችል ቢለኝ፤ ያለችኝን አንድ ብር ልሰጠው ከኪሴ ሳወጣ ፣ ጓደኛዬ እጄን ያዘና፣ “ለእሱ ከሰጠሽው ለአንቺ፣ አይኖርሽም”
አለኝ ።

ለጋስነት የድህነት መንስኤ መሆኑን፣ የተማርኩት ያኔ ነው ።

ሌላ ቀን ታላቅ እህቴ ፣ “እወደዋለሁ” እያለች፤ ከጋደኞቿ ጋር ቀን በቅን የምታነሳው ጎርምሳ ፣ ከታናሽ እህቱ ጋር ሰኞ ማክሰኞ ስጫወት መጣና
“እህትሽ ግን ለምንድነው የምትጠላኝ?” ሲለኝ፤ “አረ እንደውም እሷ በጣም ትወድሃለች ፤ ለጓደኞቿ ሁሌ እወደዋለሁ እንዳለች ነው” አልኩት። ብዙም ሳይቆይ ነገሩን የደረሰችበት እህቴ፣ በንዴት እሳት ጎርሳ በርበሬ አጠነችኝ።

ምስጢርን በመጠበቅ ሽፋን፣ ውሸት መናገርን የተማርኩት ያኔ ነው።

አምስተኛ ክፍል ሆኜ አስተማሪያችን ጥያቄ ጠይቆ፣ የሚመልስ ቢጠፋ እጄን አውጥቼ የመሰለኝን ተናገርኩ ፡ : መሳሳቴ፣ “አንቺ ደነዝ!”
ብሎ ሲነገረኝ የክፍሉ ተማሪ ሁሉ በአንድነት አውካካ።

ጥያቄን፤ መመለስ መሳለቅያ እንደሚያደረግ የተማርኩት ያኔ ነው : :

በኅብረተሰብ ክፍለ ጊዜ መምህራችን፣ “ሁላችሁም የአፍሪካ ካርታ ከመፀሀፍ ላይ እያያቹ
ደብተራችሁ ላይ ሳሉ" ብሎ አዘዘን ሁሉም ተማሪዎች ደብተራቸውን የጽሁፍ ስዕል ላይ አስደግፈው ፤የዋናውን ስዕል ጥላ እየተከተሉ ልክ እንደ መጽሐፉ አድርገው ስለው ሲመጡ ፤ እኔ ግን ፣ “እያያቹ ሳሉ” በተባለው መሰረት የመፅሐፉን ስዕል እያየሁ ሳላስደግፍ ደብተሬ ላይ ፣ “የኔን አፍሪካ” ስዬ መጣሁ : :
አስተማሪዬ አስደግፈው ለሳሉት ልጆች በሙሉ “እ...በ....ጥ...”እያሉ ፅፎ እኔ ጋር ሲደርስ ፣ እንደ ሌሎቹ ልጆች አስደግፈሽ ብትስይ ኖሮ እኝዲህ
አይጣመምብሽም ነበር ። ይሄ ምኑም አፍሪካን አይመስል!” ብሎ ዜሮ ከአስር ሰጠኝ : :

ቀድሞ የተሰራን ነገር፤ መቅዳት ሲያስሞግስ ፤ አዲስ ፈጠራና ሙከራ እንደሚያስቀጣ የተማርኩት ያኔ ነው : :

ደግሞ በሌላ አመት የህብረተሰብ ትምህርት ክፍለ ጊዜ ስለ ዘጠኙ ፕላኔቶች ስንማር እጄን አወጣሁና ፣ “ቲቸር ፣ ለመሆኑ ከመሬታችን
ውጪ ሌሎች ፕላኔቶች ውስጥ ሰዎች ይኖራሉ?” ብዬ ጠየቅኩ : :

ቲቸር "ምን እዚህ...! ደብተራችሁን፣ እንኳን በቅጡ አታነቡም : :ስለ ሌላ ፕላኔት አስበን እንራቀቅ ትላላችሁ" በሚል ውረፋ ክፉኛ አሸማቀቀኝ።

አርቆ ማሰብና መመራመር እደሚያስኮንን የተማርኩት ያኔ ነው : :

አድጌ ፤ መስሪያ ቤቴ ያጸደቀው መሪ ዕቅድ ፣ ገንዘብ እደሚያባክን ሲገባኝ ፤ ቅዳሜና እሁዴን ሰውቼ አዲስ መሪ ዕቅድ አርቀቅኩና ሰኞ
ላይ ለአመራሩ አቀረብኩ : :

“የመስርያ ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች ከስድስት ወር በላይ ፈጅተውና ለፍተው ያዘጋጁትን ዕቅድ በመናቅና ባስመታዘዝ” ጥርስ ተነክሶብኝ
ተገመገምኩ ። እሱን ተከትሎም የደረጃና የደሞዝ እድገት ታለፍኩ ፡ ፡

ቀናነት ከባድ ዋጋ እኝደሚያስከፍል የተረዳሁት ያኔ ነው : :

አሁን ታድያ በእድሜዬ ቶና ላይ ሆኜ ፤ ከጊዜና ኑሮ በተማርኩት መሠረት....

አዳልቼ ስሰጥ “ደግ ሰው” እየተባልኩ ፤

ከድሀ ነፍጌ ባስጠጋ እየሆንኩ፤

በአውራ ዋሾነቴ ሚስጥር ጠባቂ እየተባልኩ ፤

ጥያቄ ሳልመልስ “ምሁሯ” እየተባልኩ ፤

የተሰራን ገልብኩ “ፈጠረች” እየተባልኩ ፤

ቀና ባለመሆን ሽልማት እያፈስስ ፣

ደልቶኝ እኖራhሁ : :

🔘ጨረስኩ🔘
#የጥበብ_ፈተና

ለአንድ ነብስሽ እንኳ ለራስሽ ሳታቂ ለሌላ እመተርፊ
ሰው ሆነሽ ተፈጥረሽ ከሰው እምትልቂ ከሰው እምትገዝፊ
ሀ) በድምፅ ብትወከይ
ለ) ጆሮ ማያዳምጥሽ እማይለይ ውስጥሽ
ሐ)ቢቀርፁሽ ብትሳይ
መ)ለተመልካች ባዳ
ለእይታ እንግዳ
ሠ)በቃል ብትፃፊ
ረ)ለአንባቢ እማትገቢ።
እምትጋነኚ
እማትታመኚ
ከሰዓሊው እርቀሽ ከመስመር የወጣሽ ማየሸገልፅሽ ቀለም
ነፍስ ሚያለመልም ድምፅ አልባ ሙዚቃ ዜማ እንዳንቺ የለም
በመላው ምድረረ ዓለም።
ከገጣሚው ይልቅ አይረሴ ግጥም መንፈስ የሚያፀና
ከባለቅኔው ይበልጥ ተለይቶ ሚታይ የላቀ ልእልና
ከድርሰት በላይ ነሽ የደራሲ አሳር የጥበብ ፈተና።
አክሱም አይወክልሽ ላሊበላ አይሆንም ዕውነትሽን ማሳያ
ዘመን ተሻጋሪ ሕያው ለዝንታለም የሌለሽ አምሳያ
የሰማይ መቀነት ቀስተ ደመና ነው ሰንደቅሽ መታያ።
ሀገሬ ኢትዮጵያ ሆገሬ ኢትዮጵያ!
ስሜት ቢነ ቃቃ ስሜት ቢነሳሳ ሐሳብ ቢሰበሰብ
በረቀቀ ምናብ በጠሊቅ ልቡና ሺ ጊዜ ቢታሰብ
በቅርፅና ይዘት
መቼም አይፈጠር እንዳንቺ ገፀሀገር እንዳንቺ ገፀ ሰብ፡፡
👍2
#ማምሻ


#ክፍል_አራት


#በአሌክስ_አብርሃም


....አገሩ የበጎች ነው፤ ግን የበጎች ታሪክ ቦታ የለውም! በጎች ራሳቸው የሚተርኩት
የአንበሶችን የጀግንነት ጀብዱ ነው፡፡ ምናልባት ታሪኩ የበጎችን ስም ካነሳ፣ በጎች በአንበሶች እንዴት እንደተበሉ ከመተረክ አያልፍም፡፡ የበግ ቆዳ የለበሱ አንበሶች፣ ጠላታቸው የለበሰው ቆዳቸው ነው፤ ስለዚህ ይህን ቆዳ እንዲገፉትና ታሪካቸው እንዲጻፍ ትንሽ መርዳት አለብን፡፡ ብዙ አይደለም…ትንሽ! ለምሳሌ የራሳቸውን ቆዳ የሚገፉበት ቢላ ማቀበል፤ ሕመሙን ችለው የራሳቸውን ቆዳ መግፈፍና የራሳቸው ጉዳይ ነው፡፡ ሌሎች ቆዳቸውን እንግፈፍላችሁ ሲሏቸው አይገባም፡፡ ማንም የማንንም ሕመም አያውቅም፡፡ቆዳ ለመግፈፍ በሰነዘሩት ቢላ፣ ሥጋቸውን ቦጭቀው የዕድሜ ልክ ጠባሳና ሕመም ሊተውብቻው ይችላሉ

እንግዲህ ልትፈላሰሚብኝ ነው ሎዛ” አልኩ እየሳቅሁ…ከእናቷ ኮርጄ ነው አባባሉን፡፡
ከተጋቡ በኋላ ባሏ ዳግም ወደ አውሮፓ ተመልሶ ነበር፡፡ አልፎ አልፎ ታዲያ ያው እንደሰፊታችን እየተገናኘን ሻይ ቡና እንላለን፡፡ ዛሬም እፈልግሃለሁ ብላ፣ ተገናኝተን ገና
ከመቀመጣችን፣ የአንበሳእና የበግ ተረኳን አዘነበችብኝ፡፡ ታዲያ ልቀልድ እንጂ በቁም
ነገር እያዳመጥኳት ነበር፡፡ ሎዛ ውስጧ የሆነ ነገር አስቦ እየተቁነጠነጠች እንደነበር
ታዝቤያለሁ ያሰበችው ምንም ይሁን ምን ካላደረገችው እንደማታርፍ አውቃለሁ።
እናም እየሰማኋት ነው፡፡

“ትላንት ማምሻ ደውላልኝ ነበር” አለች፡፡

ሎዛ! በቃ "ሶሪ" ብያለሁ፣ አጥፍቻለሁ፥ በሰዓቱ ከጎንሽ አልቆምኩም… እንደገና ስለዚያ ሚዜነት እንዳታነሽብኝ በፈጠረሽ በቃ!” አልኩ ምርር ብሎኝ ማምሻ ሚዜ እንዳትሆን ተባብረሃል እያለች በስልክም በአካልም ስትነተርከኝ ነው የከረመችው።

“ዝም ብለህ ስማኝ፣ እሱ ውስጥህ ስለሚጮህብህ ነው ራስህ ቀድመህ የምታነሳው፡፡አሁን የምለውን ስማኝ፣ ሌሊቱን ሳስብ ነበር፡፡ ስደሰት ነበር…የማወራህ ስለ ማምሻ አይደለም፡፡ ስለ እኔ፣ ስለ አንተ፣ ስለ እናትህ፣ ስለ ምናልባትም ነገ ስለምትወልዳት ሴት
ልጅ…ስለ ማኅበረሰቡ ነው፡፡ ስማኝ አብርሽ፣ ቢያንስ መስማት እንዴት ነው ያቃተህ?…ስማኝ' ተነጫነጨች!

ኦ ኬ እየሰማሁ ነው፣ አትጨቅጭቂኝ፣ አውሪኝ፣ እኔን ካልወቀስሽ ማውራት አትችይም

እየሰማህ አይደለም! ገና “ማምሻ ስል፣ የምናገረውን ቀድመህ ገምተህ፣ የራስህን ግምት
ነው እየሰማህ ያለኸው ይኼ ወሬ ቶሎ አልቆ ሌላ ርዕስ እንድንጀምር ነው የምትፈልገው፡፡ ሌላ ርእስ የለም …ስማኝ …”
"
"እንደዛ አላሰብኩም!"

አስበሀል! …” ተፋጠጥን እና ሳቅሁኝ፡ በቃ እንደዚህ ናት:: እና ደግሞ ልክ ስለነበረች ሳቄ
እፍረት የተቀላቀለበት ነበር፡፡

ተመስጣ ወሬዋን ቀጠለች፡፡ ማምሻ ወደ ጣውላ ቤታቸው በየቀኑ እየሄደች፣ ሳጋቱራ ሰብስባና ጣውላ ቤቱን አጽድታላቸው ትመለሳለች፡፡ የምትሄደው ሳጋቱራ በነፃ ለመውሰድ” ቢሆንም፣ በገንዘብ ሲመነዘር የሳጋቱራውን አምሰትናስድስት እጥፍ የሚሆን የፅዳት ስራ ሰርታላቸው ነበር የምትመለሰው፡፡ ይኼን ለረዥም ጊዜ ነው ያደረገችው::የዚያን ሰሞን ግን ሳጋቱራ ስትጠርግ አንድ ነገር ተፈጠረ፡፡ አንድ ሠራተኛ የዛፍ ግንድ
መሰንጠቂያ ማሽኑ ላይ ለማስቀመጥ ይታገላል፡፡ ግንዱ ከባድ ስለነበር አልቻለም፡፡ማሽኑን አስደግፎ የሚያግዘው ሰው ለመጥራት ወደ ውጭ ወጣ፡፡ ማምሻ እዚያው ቁማለች፣ ግን አግዥኝ አላላትም፣ ምክንያቱም ሴት ናት! ልጁ የሚያግዘው ሰው ይዞ
ሲመለስ ግን፣ ያ ከባድ ግንድ በትካከል መሰንጠቂያው ላይ ተቀምጦ አገኘው፡፡ ዙሪያውን
ተመለከተ፡፡ ሰው የለም ማምሻ ፈገግ ብላ “ላግዝህ ብዬ ነው” አለችው፡፡ አንዲት ሴት
ለወንድ ያቃተ ግንድን ገፍታ ማሽን ላይ ማስቀመጧ የሚዋጥላቸው አልሆነም፡፡ ቢሆንም
በነገሩ ተሳስቀውና ቀልደው አለፉት፡፡ ማምሻ ግን ሐሰቧ በዚያ አልቆመም፡፡ ሎዛን ቃል በቃል እንዲህ አለቻት፡፡

አስቀያሚ ነኝ፡ ግን ጤነኛ ነኝ! እጆቼ ቆንጆና ለስላሳ አይደሉም፤ ግን ጠንካራ ናቸው
ጸጉሬ ቁጭራ ነው፤ ጸጉሬ የበቀለበት ጭንቅላቴ ግን ያስባል… ይማራል፤ ይረዳል! እዚህ
አልጋና ቁምሣጥን፣ ሶፋና በር የሚሠሩት ወንዶች፣ ከእጅ፣ ከአእምሮና ከጥንካሬ ውጭ
ከእኔ የተለየ ምንድን ነው ያላቸው?.ምናልባት ልምድ፡ እሱንም ቢሆን እዚሁ ስለቆዩ ነው፡፡ ስለዚህ እኔ ለምን ሳጋቱራ እጠርጋለሁ? እነሱ ለምን ይኼን ሁሉ ነገር በጥሩ ክፍያ
ያመርታሉ?ለምን…?”

ሎዛ ትክ ብላ አየችኝና ንገረኝ እስቲ፥ ወንዶቹ ምንድነው የተለየ ነገር ያላቸው”ትከሻዬን ወደላይ ሰብቄ “ምንም” አልኳት።

“ምንም! ብላ ደገመችውና፣ ማምሻ አባባን እንዳስፈቅድላትና እንደ ኣንድ ሠራተኛ
እንዲያሰለጥናት እና እንዲያሠራት ነገረችኝ፡፡ ለረዥም ጊዜ ሠራተኞቹ የሚሠሩትን
ስትመለከት እና መስራት እንደምትችል ስታስብ እንደነበር፣ ትንሽ ካለማመዷት እሷም
መሥራት እንደምትችል ነገረችኝ፡፡ ውስጤ እንዴት እንደተደሰተ አትጠይቀኝ፡፡ ለአንዲት ሴት በተለይ “ቆንጆ ሴት” ነን ብለን ለምናስብ ሴቶች፣ አቅማችንን እንዳንጠቀም እስር ቤት የሚሆንብን የራሳችን ቁንጅና ነው፡፡ የራሳችን ቆዳ የራሳችን እስር ቤት ነው!

በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ሴትነት እና ቁንጅና የሚባል የእስር ፍርግርጋችንን እያስዋብን ተሟሙቀን የወንዶችን ጭብጨባና አድናቆት እየጠበቅን እንድንኖር ሆነናል ሁሉም እስር ሰንሰለቱ ፈጦ አይታይም እንደውም አንዳንዱ እስራት ለታሳሪው ለራሱ ጭምር አይታይም፡፡ ማኅበረሰቡ አንዲትን ሴት የብረት መዝጊያ የሚሆን አማች የምታመጣ እንጂ፤ የብረት መዝጊያ መሆን የምትችል አድርጎ አያስብም! ስለዚህ የእነሱን የምኞት ስር የሚዘጋ የብረት መዝጊያ ለማምጣት፣ አንዲት ሴት ዓይኗንም አእምሮዋንም ሳይሆን እግሯን እንድትከፍት ከሕፃንነቷ ጀምሮ ሲያዘጋጃት ይኖራል”
እግር የተፈጠረበት የመጀመሪያ ዓላማው መራመድ ነው፤ ለሴት ልጅ ግን ከመራመድ በላይ
እግር ውበት እንደሆነ እንድታስብ በሥነጽሑፉ፣ በፊልሙ አእምሮዋ ውስጥ ስታጭቅባት ኑራለች፡፡ ለዚያም ነው ከፊታቸው የተነጠፈውን እሾህም ይሁን ጠጠር ረግጠውና ዋጋ ከፍለው ወዳሰቡበት ከሚራመዱ ሴቶች ይልቅ፤ ከየትም ባገኟት ሳንቲም በየውበት ሳሎኑ ተጎልተው፣ እግራቸውን የጥፍር ቀለም ሊያስቀቡና ተረከዛቸውን ሲያስፈገፍጉ የሚውሉ ዘመነኞች የሚበዙት እግራቸው ከለሰለሰ በኋላ፣ አዝሎ
የሚያሻግር ወንድ ሲጠብቁ ቁጭ ብለው ይኖራሉ፡፡

እጅ የተፈጠረበት የመጀመሪያ ዓላማው መሥራት ነው ብዙ የፋሽን እና ዘመናዊውን የውበት ሚዛን የሚደፉ 'ዘመናዊ ሴቶች እጃቸው ከሚበላሽ ስማቸውም ሕይዎታቸውም ቢበላሽ እና እጃቸው እንደለሰለሰ ቢኖር ይመርጣሉ፡፡ ልስላሴ ሳይሆን በንጽሕናና ራስን ችሎ መቆም እንጨባበጥ ከተባለ ማንናት ደፍራ እጇን የምትዘረጋ?! ለብዙኃኑ ወንዶች ጠንካራ የሴት እጅ አገርን ያቆመ ሳይሆን፣ ሴትነትን የገፋ መስሎ ነው የሚታያቸው ለዚያ ነው በሥራ ስለደደረ የሴት መዳፍ፣ ዘፋኙም መዝፈን፣ገጣሚውም መግጠም
የማይወደው፡፡ድንጋይ ፈልፍሎና እምነበረድ ጠርቦ ውብ የእጅ ጣት ያላት ሴት ሐውልት
የሚያቆመውን ቀራጺ እጅ ግን ተመልከተው፣ በሥራ የጎለዴፈ ሆኖ ታገኘዋለህ ከግማሽ
በላይ የሚሆነው ሕዝብ ሴት በሆነበት አገር፣ ሴቶች እጃቸውን አስውበው መደርደሪያ
ላይ እንዲያስቀም ጡት በማድረግ፣ ለውጥ ጠብ አይልም፤ እንዲሩ ማደፋፈር እጅ ወደተፈጠረበት የመጀመሪያ ዓላማ እንዲመለስ መሰበክ አለበት!

ማምሻ ቆንጆ አይደለችም ዕጣ ፋንታዋ ዓይንና ጥርሷ ላይ ሳይሆን፣ እጆቿ ላይ እንዳለ
ግን ተገልጦላታል ወንድ በእግሮቿ መሃል ካላለፈ የሚያልፍላት
👍1
ፍላት የማይመስላት ሴት አይደለችም፡፡ አዎ! እንዲያልፍላት የግድ ወንድ በእግሮቿ መሃል ማለፍ የለበትም ጠንካራ ሰውነት ነው ያላት፡፡አንተን ጨምሮ እዚህ ሰፈር ያላችሁ ወንዶች፡ አብራችኋት መተኛት ይቅርና፣ አብራችኋት ፎቶ መነሳትን እንኳን እንደትልቅ ውለታ ልትቆጥሩት
ቆንጆ አይደለችም! ሲኒማ ጋብዛችኋት ታውቃላችሁ? አታውቁም፡ ምክንያቱም ቆንጆ
ትፈልጋላችሁ፡፡ የፍቅር ደብዳቤ ጽፋችሁላት ታውቃላችሁ?አታውቁም! ምክንያቱም ቆንጆ
ኣይደለችም! ሌላው ይቅር፣ አንድ ቀን እንኳን የለበሰችውን ልብስ አምሮብሻል ብላችኋት
ታውቃላችሁ? ያው ሚዜ ሆነህ አየሁህኮ፣ ለእኔ ቤተሰቦች ምከንያቱ ምንም ይሁን፣
ለአንተና ለመሰሎችህ ግን፣ ጕዳዩ የፎቶም የእኔ ሰርግ መድመቅና አለመድመቅም አይደለም፣ ወሲብ ነበር! ዋናው ፉከተር ወሲብ ነው! ብትችሉ አንሶላ ለመጋፈፍ፣ካልተሳካም በየትኛውም አጋጣሚ የምታገኟትን አብራችሁ የምትቆም ቆንጆ ሴት… ጡትና እግር እያያችሁ፣ በሽተኛ ምኞታችሁን ታስታምማላችሁ! ማምሻን በተለሳለሰ ብልግና ገፍተህ፤ ከእዚያች ነርስ ጋር ጨዋ ጨዋ ስትጫወት፣ በገባች በወጣች ቁጥር ዘመናዊ ለመሳል ወንበር ስትጎትት አበሳጭተኸኛል እሷም ስትገለፍጥልህ ነበር፡፡ ምናልባትም አብረኻት ተኝተህ ይሆናል። ሁለታችሁም ገደል ግቡ…” ይውጣላት ብየ ዝም አልኳት፡፡

“ማምሻ ተገፍቶ ተገፍቶ ግድግዳ ጋ የተጣጋ፣ ልሽሽ ብትልም መሸሻ በሌለው የመገፋት
ጥግ ላይ ነው ያለችው::ማኅበረሰቡ ግን አሁንም መግፋቱን አላቆመም፣ ያላት አማራጭ፣
ወይ በገፊ ማኅበረሰብና በማትገፋው የእድል ግድግዳዋ መሃል ተጨፍልቃ መሞት
አልያም በእነዚህ ብርቱ እጆቿ መልሳ የገፋትን የድሀነት እጅ መግፋትና እንደገና
መንገዷን መጀመር ነው፡፡ እኔ፣ አንተ፣ ሁላችንም ከምናየው ማንም በስለታም ምላሱ ከሚያርደውና ከሚሸልተው የበግ ቆዳዋ ሥር ያለውን የአንበሳ ቆዳ ለማውጣት ቢያምም፣ ራሷ ቆዳዋን ለመግፈፍ ወስናለች፡፡ የመጀመሪያው ጉዳይ የተቀመጠልህን የባርነትና የአትችልም መስመር በአእምሮህ ማለፍ ነው፡፡

ለአካላዊ ጥንካሬውማ ዕድሜዋን ሙሉ በጉልበት ሥራ ስትደከም የፈረጠመ ክንድ አዳብራለች፣ ያውም ወንድን የሚያስንቅ…”

አባባን ማታ ቢራ ጋብዤ ቁጭ እድርጌ ነገርኩት መንገር ከማለት ለመንኩት ብል ይሻላል) ሥራው ለሴት አይከብድም ብለሽ ነው? አለኝ፡፡ “ሞከራት ለእኔ ስትል ሞከራት ብዬ ለመንኩት፡፡ ተስማምቷል፡፡ዛሬ ትጀምራለች፡፡ አባባን እሱ ለሠራተኞቹ የሚከፍለውን፣ እኔ እንደምከፍላት ስነግረው ሳቀብኝ፤ ችግር የለም፣ እኔ እሰጣታለሁ
አለኝ፡፡ እስካሁንም ለሰራችበት እንደሚከፍላት ሳይሆን እንደሚመጸውታት ነው የሚያስበው፡፡ አውቃለሁ፣ እሷን ተማምኖባት አይደለም፤ ለእኔ ሲል ነው፡፡ ዋት ኤቨር ከትንሽ ወራት በኋላ፣ ለእኔ ሲል ሳይሆን ለራሱ ሲል ይከፍላታል፡፡ ምክንያቱም በሥጋም በመንፈስም እዚያ ከሚሠሩት ብትሻል እንጂ አታንስም! ጠንካራ ናት! በማንም ተራ የወንድ አድናቆት የተገነባ የሴትነት ሞራል ሳይሆን፤ መገፋትን ተቋቁሞ በቆመ ብርቱ መንፈስ ትክክለኛ ማንነቷን የተረዳች ልጅ ናት።ዞሮ ዞሮ አባባም ወንድ ያሳደገው ወንድ ነው ይሄንን አትርሳ።

"ማክያቶ ልዘዝልሽ?ሳትጠጪው ቀዘቀዘ"አልኳት!

"አብርሽ..."

"እ.."

"እናትክን! አንተም ሁላችሁም እናታችሁን!..ይሄ ድንጋይ ወንድነትህ ያልኩትን ሁሉ አንጥሮ ሲመልሰውና ፣ ወሬዬን ሁሉ ተራ "የፌሚኒዚም" ልፍለፋ አድርጎ ሲመለከተው ፤ አይንህ ላይ እያየሁት ነው።በእኔ ቦታ ሆነህ ብትመለከተው እኮ፣ እናንተ ወንዶች እንዴት እንድምትደክሙ? ብላኝ ቦርሳዋን አንስጣ ወጣች።አውቃለሁ ነገ በሌላ የንዝንዝ ርዕስ እንደምንገናኝ።

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
አትሮኖስ pinned «#ማምሻ ፡ ፡ #ክፍል_አራት ፡ ፡ #በአሌክስ_አብርሃም ....አገሩ የበጎች ነው፤ ግን የበጎች ታሪክ ቦታ የለውም! በጎች ራሳቸው የሚተርኩት የአንበሶችን የጀግንነት ጀብዱ ነው፡፡ ምናልባት ታሪኩ የበጎችን ስም ካነሳ፣ በጎች በአንበሶች እንዴት እንደተበሉ ከመተረክ አያልፍም፡፡ የበግ ቆዳ የለበሱ አንበሶች፣ ጠላታቸው የለበሰው ቆዳቸው ነው፤ ስለዚህ ይህን ቆዳ እንዲገፉትና ታሪካቸው እንዲጻፍ ትንሽ መርዳት…»
በአንድ ሰሞን፣ ያነበብኩት “የታሪክ መጽሐፍ” መሳጭ ልብወለድ ነው : :

መቼም በዘመናችን የታሪክ “ደራሲያን" በዝተዋል ሃይ ባይ እስከሌለ ድረስ ማስርጃና ማጣቀሻ የሌላቸው ፣ “የታሪክ ልቧለዶች” በገፍ እየታተሙ
ነው።

አንድ የማላስታውሰው ወዳጄ እንዳው በአብዮቱ ጊዜ በቤተ መንግሥት ወጥ ወጥዋጭ የነበረ ሰው ሳይቀር ፣ “ረጅሙና እልህ አስጨራሹ
የቤተመንግስት ሕይወቴ እና ድብልቅልቁ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ሂደት" እያለ የሚፅፍበት ጊዜ ላይ እንገኛለን : :

ተቆጪ በሌለበት ዘመን ሁሉም የሆነውን ያሻውን እውነት በወገንተኛ አርትዖት እየከረከመ ፣
ጋሻውን፤ እውነት በትልቅ እመጫት እያስገባ ፣
የቆረቆረውን፣ እየሰረዘ የፈለገውን ይፅፋል ታሪክን ይደርሳል።

ይህ ነገር የሚከተለውን፣ የኤዞፕን ተረት አስታወሰኝ ።

አንበሳና ሰው ከባድ ክርክር ላይ ናቸው : :

“አንበሳው ከሰው ጉልበት የአንበሳ ጉልበት ይበልጣል" ሲል ፤ ሰውየው ደግሞ ፣ “የለም ፤ የሰው ልጅ ከአንበሳ እጅግ ያይላል” ይላል።

በዚህ ሁኔታ ክርክሩ ከቀጠለ በኋካ ሰውየው ፣ “ቆይ እንደውም ሰው አንበሳን፣ በጉልበት እንደሚያስከነዳ የሚያሳይ መረጃ ላሳይህ መLካሳ ይ” ይልና አንበሳውን አንድ ሐውልት ከቆመበት ቦታ ይወስደዋል ።

ሐውልቱ አንድ ሰው እጅግ ግዙፍ የሆነን አንበሳን ጉሮሮ እንቅ አድርጎ ይዞ ያሳያል ሐውልቱን ሲያይ የቆየው አንበሳም ፣ ይህ ሐውልት የሰው ልጅ ከአንበሳ የሚበልጥ ጉልበት እንዳለው ሊያሳምን አይችልም” ይላል።

ሰውየውም ፣ “እንዴ ... እያየኸው ምን ማለትህ ነው?” ብሎ ሲጠይቅ ፤ አንበሳው ቀበል አደረገና ፣ “ማየቱንስ አየሁት ... ግን ሐውልቱን ያነጸው ማን ሆነና? ” ብሎ መለሰለት አሉ።

እኛም ከእንግዲህ እንደዚህ ዓይነቶቹን፣ መጽሐፍት ስናነብ "ዝም ብለን" በማመን ፈንታ ፣ “የጻፈው ማን ሆነና” በማለት ሚዛን ላይ ማስቀመጥ ብንለምድ አይከፋም : :

🔘ሕይወት እምሻው🔘
#በትንሳኤ_ማግስት

ጾም ስግደቱ ሲቆም ጸሎቱም ተረሣ
እኛ መሞት ጀመርን አንተ ስትነሣ።

🔘 ዲያቆን ሄኖክ ኅይሌ🔘
#የበላይ

አየሽው አለሜ
ማንም ሰው የሰውን ፥ ህይወት ቢቀለጥም፤
ስሜት ቢያሰክረው ነው ፤ የበላይነት ጥም!

እንጂማ.....

የበላይነት ጥም
ስሜትን ቆንጥጦ፤እኛን ድል ባይነሳ፤
ቃዬን በአቤል ላይ፥ ድንጋይ ባላነሳ!

🔘በአብርሃም🔘
“ቀድመውኝ አይደለም፤ ዘግይቼም አይደለም።
ተቀድሜም አይደለም፤ ወይም እነሱ ዘግይተው።

ትክክለኛው ሰዓት ላይ ነኝ።” በል!
:
ምናልባት አንዱ በ20 ዓመቱ ያገባ ይሆናል፤ ለመውለድ አስር አመታትን ይወስዳል።

አንዱ በ30 ዓመቱ ያገባል፤ በዓመቱ ይወልዳል።

አንዷ በ22 ዓመቷ ታገባለች፤ ጥሩ ባል አይደለም።

ሌላኛዋ በ34 ዓመቷ ታገባለች፤ ደስተኛ ትዳርንም ትመራለች።

ከፊሉ በ22 ዓመቱ ይመረቃል፤ ስራ ለማግኘት 5 ዓመታ ይፈጅበታል።

ከፊሉ በ27 ዓመቱ ይመረቃል፤ ከመውጣቱ ስራን ያገኛል።

ሌላው በ25 ዓመቱ የድርጅት ስራ አስኪያጅ ይሆናል፤ በ40 ዓመቱ ይሞታል።

ሌላኛው በ50 ዓመቱ የድርጅት አስኪያጅ ይሆናል፤ በ90 ዓመቱ ይሞታል።
:

ጊዜህን ብቻ ተከተል።

የቀደሙህ ወይም የዘገየህ አድርገው ይስሉሀል።

አንተ ከማንም አልተቀደምክም፤ ከማንም አልዘገየህም።

ፈጣሪ በፈቀልህ ጊዜ ብቻ እየሄድክ ነው።

ይህንን እወቅ።

የአዕምሮ ረፍትና እርጋታህን ይዘህ ኑር።
:
ጊዜ በፈጣሪ እጅ ያለ መንገድ ነው። እንደፈለገ ያስኬደዋል። የፈለገውን ላንተ በፈለገልህ
ሰዓት ያደርግልሀል።
«ነገሩም ሁሉ በእርሱ ዘንድ በልክ የተወሰነ ነው።»

"ትክክለኛው ሰዓት ላይ ነኝ በል።”

🔘ከ FB🔘
#ጥበቃ

ጐጆዬን ትቼ ወጥቼ አስጠልቶኝ ምቹ አልጋዬ
ከባቡሩ መንገድ ላይ እየታየሁ በጀርባዬ ተንጋልዬ
“ምን ሆነህ ነው?” የሚል አዝኖ እሚጠይቀኝ
አንድ ሰው አጥቼ አንድ ሰው ናፈቀኝ፡፡
የባቡሩ ሒዲድ ሥር የድንጋይ ጠጠሮች
ሐዲዱን ያሰሩት ትናንሽ ብሎኖች
ምቾት የሌላቸው እየቆረቆሩኝ የተኛሁባቸው
የጐረበጥኳቸው ያልተመቸዋቸው
ቁሳቁሶቹ እንኳን ባለቤት አላቸው፡፡
ከሐዲዱ ባሻገር የሚታየው ሻንጣ
ከራስጌዬ ኃላ
ያለውም ጃንጥላ
ትራሴ ሥር ያለው አሻንጉሊትና
ፊቴን የሸፈነው ትልቁ ባርኔጣ
ከሥሬ ያነጠፍኩት
ከላይ የለበስኩት ረዥም ካፖርታ
በጠራራው ፀሐይ አብሮኝ የተሰጣ
ከግርጌዬ ያለው ቀዩም ዕጌረዳ
ሁሉም የኔ አይደለም
የእኔ እምለው የለም፡፡
በሥጋዬ መሐል እምትኖረው ነፍሴ
እሷም የሌላ ነች አይደለች የራሴ፡፡
ነፍሴን ይዛዋለች
ነፍሴ ርቃኛለች፡፡
እንደ እሳት ቢፋጅም ቢግልም ሐዲዱ
ንቅንቅ አልላትም ከባቡር መንገዱ፡፡
ጥላኝ ብትሔድም ብትወኝም ንቃ
ከዕቃዎቿ መሐል ሆኜ የሰው ዕቃ
በብርድ ስጠበስ በፀሐይ ስንቃቃ
እኔ ውዬ አድራለሁ
እምትመጣበትን ባቡሩን ጥበቃ።
እንዴት ናፍቃኛለች?!!

🔘ፋሲል ተካልኝ🔘
👍1
#ማምሻ


#ክፍል_አምስት(የመጨረሻ ክፍል)


#በአሌክስ_አብርሃም


ሎዛ ከዓመት በኋላ ባሏ ጋ ጠቅልላ አውሮፓ ገባች፡፡ ያው እዚህ እንደነበረው ቶሎ ቶሎ
ባንገናኝም አልፎ አልፎ ትደውልና ተጨቃጭቀን፣ ተሰዳድበን፣ አኩርፋ ጆሮዬ ላይ ዘግታብኝ፤ ከሆነ ጊዜ በኋላ መልሳ ደውላ፣ ምንም እንዳልተፈጠረ እናወራለን፡፡ በመሃል ሰፈራችን ከላይ እስከታች ፈራርሶ ጎረቤቱ ሁሉ ተበታተነ፡፡ ሰፈራችን ሲፈርስ አብሮ ያልፈረሰ ነገራችን አልነበረም፡፡ ስንድህ፣ ዳዴ ስንለማመድ የትንንሽ መዳፎቻችን አሻራ
የታተመበት ደጅ ከታሪክ ገጽ ተሰረዘ፣ የተላለፍንባቸው መንገዶች ዳናችንን እንደያዙ
ጠፉ፣ የቆምንባቸው ጥጎች ላይመለሱ ከሰሙ፣ ከየት መጣችሁ? ቢሉን ዙረን የምነጠቁመው ነገር እስከናጣ ሰፈራችን… ትንሽ አገራችን ፈረሰች!! ማንም ሰው የመጀመሪያ አገሩ ሰፈሩ ነው፡፡ አገራችን ፈረሰች!! ከሎዛም ጋር እንዲሁ መደዋወላችን እየተቀዛቀዘ ሂዶ ሙሉ ለሙሉ ተጠፋፋን!! ጭራሽ እኔ የስልክ ቁጥሬን ከቀየርኩ በኋላ ፊት የሚያውቁኝ የሰፈር ልጆች ጋር ሁሉ ተጠፋፋሁ፡፡ ዓመታት ነጎዱ፡፡ ትላንታችን
ወደ ኋላ ሮጠ፡፡ አዲስ ሕይዎት አዳዲስ ጓደኞች ረብርበን ባለፉ ቀናቶች ላይ ከፍ ብለን ቆመን፡፡ በቆምንበት ከፍታ ትላንታችንን ረስተን ነገን ልናይ ተንጠራራን፡፡
።።።።።።።።።።።
ከሰባት ወይም ስምንት ዓመት በኋላ ይመስለኛል፣ የጓደኛችን እናት አርፈው፣ የአስከሬን ሣጥን ልንገዛ ሁለት ሁነን ወደ ፒያሳ ሄድን፡፡ ከተደረደሩት ሱቆች ከአንዱ ወደ ሌላው እያልን ዋጋ ስናወዳድር ቆይተን፣ ወደ እንዱ መሸጫ ጎራ አልን፤ ገና ከመግባታችን ሁለት ወጣት ልጆች አጣደፉን፡፡ እየተቀባባሉ ስለ አስክሬን ሣጥኑ ጥንካሬ፣ ስፋት፣ ምቾት ሳይቀር እየነገሩ አግለበለቡን፡፡ ዋጋ ቀንሱ አትቀንሱ ስንከራከር፣ ድንገት ከውስጥ
ቀንሱላቸው የሚል የሴት ድምፅ ሰምተን ዞር አልን፡፡ጠቆር ያለ አጭር ጋውን የለበሰች
ሴት፣ እጅና እጁን ጋውኑ ኪስ ከትታ ከኋላችን ከነበረ ከፍል ብቅ አለች፡፡ በግርምት ፈጥጨ ቀረሁ፡፡ ይሄን ፊት ማን ይረሳል …ማምሻ ነበረች፡፡

“ማምሻ” አልኳት ፈገግ ብዬ፣

እንዴ! አብርሽ ባልሆንክ…ትልቅ ሰው! ትልቅ ሰው…” ጮኸች መጀመሪያ ለማጣራት
ብላም እንደሆን እንጃ፣ ግርምቷን ቆም አድርጋ፣
“ምነው? ማን ሙቶባችሁ ነው?” አለችኝ፡፡

“የጓደኛችን እናት ናቸው

የባጥ የቆጡን እያወራን፣ እንትና ደህና ነው? እነ አትናስ? እየተባባልን የአስከሬን ሣጥኑን ራሷ መረጠችልን፡፡ ልጆቹ ሳጥኑን እስኪያዘጋጁልንና እስኪጭኑት ድረስ፣ ወደ ውስጥ አስገብታን በግራና በቀኝ የአስክሬን ሣጥን በተከመረበት ሰፋ ያለ ቢሮዋ ውስጥ፡ ሻይ ጋበዘችን፡፡ በጣም ጎበዝ ጣውላ ሠራተኛ ከመሆን አልፋ፣ የራሷን ትንሽ ጣውላ ቤት ከፍታ ነበር፡፡ እዚህ ሥራ ላይ “ምን እግር ጣለሽ” አልኳት የከበቡንን የአስከሬን
ሣጥኖች እያየሁ፣

ሳቀችና እማማ ስታርፍ ራሴ ነኝ የአስክሬን ሣጥኗን የሠራሁላት….. አልጋ፣ ሶፋ፣ ቁም
ሳጥን እንሠራለን፡፡ ለምን እንደሆን እንጂ ከዚያ በኋላ የአስክሬን ሣጥን ስሠራ ደስ ነው
የሚለኝ፡፡ ወደድኩት! ሳጥኖቹን ስሠራ ሰላም ይሰጠኛል፡፡ ጨርቆቹ ላይ ያሉትን ጥልፎች የምሰራው ራሴ ነኝ፤ ሰዎች ሲሞቱ ከነሣጥናቸው ወደ እግዚአብሔር የሚያርጉ ይመስለኛል …" እግዚአብሔር ሣጥኖቹ ብቻ ሳይሆን በጥልፎቹም የሚደመም ይመስለኛል ብላ ሳቀችና “ይኼውልህ ይችን ሱቅ ተከራይቼ በዚሁ ሥራ ቀጠልኩ፡፡
ማምረቻትን ከኋላ በኩል ነው፡፡ ወይ አብርሽ ትልቅ ሰው ሆንክ ብላ በመደመም እጇን እፏ ላይ ስትጭን የጋብቻ ቀለበት ማድረጓን አየሁ፡፡ ግን ምንም አላልኩ፡፡

እማማ መቼ አረፉ” አልኳት፣

ትንሽ ዝም ብላ ቆየችና “አራት ዓመት ሆናት” አለችኝ፡፡

ሶሪ…" ዝም ተባብለን ቆየን! እንዲሁ ዝምታውን ለማስወገድ

የሰፈር ሰዎችን አግኝተሻቸው ታውቂያለሽ?» አልኳት፣

እዎ ተራ በተራ እየሞቱ ነው፣ ከዚሁ ነው ሣጥን የሚወስዱት፣ ደንበኛ ሁነናል…”አለችና
የአሽሙር የሚመስል ፈገግታ ፈገግ ብላ ከጠረጴዛዋ መሳቢያ ውስጥ ካርድ አውጥታ
ሰጠችኝ፡፡ “ማምሻ የጣውላ ሥራ አልጋ፣ ሶፋ፣ በሮች እንሠራለን እንዲሁም የተለያዩ
የአስከሬን ሣጥኖችን እናቀርባለን ይላል።

ሳጥኑ ተጭኖልን ስንወጣ፣ ማምሻ ፈገግ ብላ ጨበጠችኝና “ሎዛ የዛሬ ሁለት ዓመት አካባቢ መጥታ በእግር በፈረስ ብታስፈልግህ አጣችህ..ፖስታ ስጭው ብላ እኔ ጋር
አስቀምጣልህ ነበር፤ እቤት ነው ያለው፡፡ ያለህበትን ንገረኝና የሆነ ቀን አቀብልሃለሁ
ወይም መጥተህ ውሰድ አለችኝ፡፡ የእጇ ጥንካሬ እጄን የቆረጠመኝ እስኪመስለኝ አጥብቃ ጨበጠችኝ

ሰንመለስ፣ አብሮኝ የነበረው ጓደኛዬ “ማናት?” አለኝ፡፡

“ማምሻ ትባላለች የሰፈራችን አንደኛ አስቀያሚ ልጅ ነበረች…” ብዬ ከመጀመሬ፣

“አሁንም'ኮ በጣም አስቀያሚ ናት! ጭራሽ ይኼን መልክ በአስክሬን ሣጥን ተከቦ ማየት፣ አስበኸዋል!?” አለኝና በራሱ ቀለድ ከትከት ብሎ ሳቀ፡፡ እውነቱን ለመናገር የማምሻን መልክ ነገሬ ብዬ አላስተዋልኩትም ነበር፡፡

ከሳምንት በኋላ ለማምሻ ደወልኩላትና ሎዛ የተወችልኝን ፖስታ ልትሰጠኝ አንድ ካፌ
ተገናኘን፡፡ ቡና ጋብዣት እያወራን በወሬ ወሬ “አላገባህም?” ከሚል ጥያቄ ተነስቶ ነገሩ
ወደ እሷው ዞረና ማግባቷን ነገረችኝ ፤ ልጅ መውለዷንም ጭምር ፡፡ “እንኳን ደስ ያለሽ?
ከማለት ባለፈ ምንም ነገር ለመጠየቅ ፈራሁ፡፡ “ማንን አገባሽ” አልል ነገር “ማነው አንችን ያግባ!” ይመስልብኛል ብዬ …..ዝምታ ዓይኔን እዛና እዚህ ሳንከራትት ራሷ እግዚእብሔር ጥሩ ሰው ሰጠኝ …የሎዛ አባት ቤት ሶፋ የሚሰራ፣ ዳንኤል የሚባል ልጅ ታስታውሳለህ ? አለችኝ አላስታወስኩትም፡፡ የሎዛ መልክ ራሱ ደብዝዞብኛል፡፡

እሱ ጋር ተጋባን :-እጄን ይዞ ነው ጣውላ ስራ ያስተማረኝ፡፡እንጋባ ሲለኝ እየቀለደ ነበር
የመሰለኝ

ለምን?” አልኳት፡፡ የራሌ እንዳላወቀ መምሰል እያስጠላኝ::

ሳቀች እያወከው አብርሽ እኔን በዚህ መልኬ፣ እንኳን ማግባት አብሮኝ የሚቆም ወንድ አልነበረም ሃሃሃሃሃ ብላ ሳቀች፡፡

“ይሄን ያህልማ አታካብጅው አልኩ፣ ጅብ ከሄደ ውሻ ጮኸ በሆነ ማጽናናት፡፡

ፈገግ ብላ ስንተዋወቅ” በሚል አስተያየት አየችኝ “እንደተሳቀስክሁ ነው የኖርኩት…ከሰው
እንደራቅሁ፡፡ ስወልድ እንኳን አስብ የነበረው እንደ እናት ስለ ልጄ ደህንነትም ሆነ ስለ ምጡ ስቃይ አልነበረም፡፡ ከምጡ በላይ ሐሳብ የሆነብኝ የልጄ መልክ ምን ይመስል ይሆን? የሚል ጭንቀት ነበር፡፡ አምጥተው ሲያሳቅፉኝ፣ገና ሳትታጠብ በፊት…ፍከት ባለ ቆዳዋ ከእኔ ዕጣ ማምለጧን ስመለከት በደስታ አለቀስኩ፡፡ ማንም ኤልገባውም! እናት መሆን ብቻውን ያስለቀሰኝ መስሏቸው ነበር፡፡

ዘጠኝ ወር ያረገዝኩት ጭንቀት እንደ መንታ በማሕጸኔ ከልጄ ጋር እያደገ ነበር፡፡
ተገላገልኩት፡፡ ልጄ ምኗም እኔን ባለመምሰሉ ፈጣሪን አመሰገንኩ፡፡ ሁልጊዜ የሚገርመኝ
ምን እንደሆነ ታውቃለህ? ባለቤቴ አንቺን የምትመስል ልጅ ነው የምፈልገው ያለኝን
ነገር! እኔን ለማጽናናት ብሎ ይናገረውም አልያም ከልቡ ይሁን እንጃ! ብቻ ይሄ ንግግር ውስጤ ቀረ፡፡ ሰዎች “ቁርጥ አባቷን ሲሉ ነፍሴ ሐሤት ታደርጋለች አባቷ እኔን ከጥላቻ… ልጃችንንም እኔን ከመምሰል ሳያውቀው አድኖናል፡፡ በሄድኩበት ሁሉ ሎዛየንና ባለቤቴን ስማቸውን አንስቸ አልጠግብም፡፡ ነፍሴ ታከብራቸዋለች አሁንም ግን እንደገና ልጅ መውለድ እፈራለሁ፤ እኔን ብትመስልስ እያልኩ፡፡ አሁንም እሰጋለሁ… አንድ ቀን ባሌ እኔንም ልጄንም ጥሎን ቢሄድስ እያልኩ፡፡ እንጃ ከዚህ በሽታ እንዴት እንደምፈወስ!

የሎዛን ፖስታ ስከፍተው
👍5
አንድ ባለቀለም ጉርድ ፎቶግራፍ ብቻ ነበር ውስጡ ያኘሁት፤አንዲት እድሜዋ ሦስት ዓመት የሚሆናት ቆንጅዬ ሕጻን ልጅ ፎቶ፡፡ከፎቶው ጀርባ
በእንግሊዝኛና አማርኛ ቅልቅል እንዲህ የሚል ጽሁፍ ተጽፏል የሎዛ የእጅ ጽሁፍ ነው፡፡
hello,uncle! guess what ...My name is "ማምሻ ዳግማዊ!!

ሟርት ነው አልኩ ለራሴ፡፡ ግን ደግም አይገርምም፣ ሎዛ እብድ ናት እብድ ቤተሰብ
መመስረትም ትችላለች፡፡ እናም ዓለም ፈውሷን ለመቀበል የሎዛ ዓይነት ብዙ እብዶች ሳያስፈልጓት አይቀም፡፡

ጨረስን

አረ ተዉ #MUTE ያደረጋቹ #UNMUTE አድርጉ ምንም አልሰማም አላችሁ እኮ😡 ምን ይሻለኛል ወይ እስቲ ስለድርሰቱ አስተያየት ስሰጡ #UNMUTE የማታደርጉበትን ምክንያት ምንድን ነው??? እባካችሁ ንገሩኝ..Post የሚደረጉትን ብዙ ሰው የማያነበው ከሆነ ማዘጋጀቱም ይደብራል..ሌላ ድርሰት ለመጀመር ወይም ለማቆም አስተያየታችሁን (ምክንያታችሁን) እፈልጋለው...በዛሬው ቀን ብቻ እንኳን #381 ሰው ቻናሉን #MUTE አድርጓል አስተያየት ይስጡ

@atronosebot ን ይጠቀሙ
#ስንቶች_ናቸው

ሰቅለው ሁለት ባላ
ሲሰበርባቸው አንዱ
በአንዱ 'ሚንጠለጠሉ
ነፍስና ሥጋቸው እየተጣላ
አልስማማው ሲላቸው
ወሰን ሲያልፍባቸው ሲጥስባቸው ኬላ
በስመ ፍቅር ከለላ ይዘው የነፍስ ምህላ
ዕለተ ልቡናቸውን አክብረው
ሽፍነው በትዕግሥት ጥላ
ሳይፈቀሩ አፍቅረው
ዘመናቸውን ሲፈጁ ኖረው ኖረው ኖረው
መግቢያ መውጫ ሲቸግራቸው
የፍቅረ ረቂቅ ኃይል ውስብስቡ ውጥንቅጡ
መስመራቸውን ሲያስታቸው ሲጠፋባቸው መላቅጡ
ሌላ አማራጭ ሲያጡ
በፅልመት ውስጥ ሲዋጡ ቶሎ ተስፋ ሲቆርጡ
ከራሳቸው ጋር ተጣልተው ከራሳቸው ጋር ሳይታረቁ
ጀንበራቸው አዘቅዝቀው የሰውን ፀሐይ እየጠበቁ
የሚሞቁ
ልባቸውን አቀዝቅዘው የሌላን ልብ እያሞቁ
መሪር ሐዘን ውጧቸው በሰው ደስታ እየቦረቁ
የራሳቸውን ጥርስ አኑረው በሰው ጥርስ እየሳቁ
“የእኔ” ከሚሉት በቀር ማፍቀር እንደማይችሉ እያወቁ
ያፈቀሩ መስለው ሳያፈቅሩ
አኗኗሪ ሆነው እሚኖሩ
የሚቆጠሩ እያሉ እንደሌሉ
በየቤቱ ስንቶች አሉ?!?
ከሚያፈቅሩት ሰው እየሸሹ ከሚያፈቅሩት ሰው እየራቁ
ለሚጠሏቸው እጅ የሰጡ በማይፈልጉት ሰው እጅ የወደቁ
ገና የቃልኪዳነን ቀለበት በጣታቸው ላይ ሲያጠልቁ
የሚያፈቅሩትን ሰው እየናፈቁ
ስንቶች ናቸው ፍቺያቸውን በጋብቻቸው ዕለት ያፀደቁ?!?
ስንቶች ናቸው
ተለይቶ ከራሳቸው
ተቦጭቆ ከገፃቸው የነፍስና ያካላቸው ግማሹ
ከሚያፈቅሩት ጋር እንደቀረ እያወቁ እየዋሹ
የሚያፈቅሩትን ሰው እያሰቡ
ከማይወዱት ጋር የሚቆርቡ
ላይፋቱ ያለፍቅር የሚጋቡ፡፡
ስንቶች ናቸው::
ራሳቸውን በራሳቸው የቀጡ
ራሳቸውን በራሳቸው የገደሉ
የፅድቅ መንገዳቸውን ያበላሹ
ፀዓዳ መንፈሳቸውን ያቆሽሹ
ከማያፈቅሩት ጋር እየኖሩ
የሚያፈቅሩትን ሰው እሚሹ፡፡
ስንቶች ናቸው?!?

🔘ፋሲል ተካልኝ🔘