አትሮኖስ
286K subscribers
120 photos
3 videos
41 files
573 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#መልስልኝ

ይቅር አይመቸው አይድላው ሥጋዬን
ከፍቶት ኅሊናዬን
አልመር አልታይ አጊጬ አብለጭልጩ
ማንነቴን ሸጬ
አልሻም ከእንግዲህ ይሄው ግሳንግስህ
ቅራቅንቦ ቁስህ
ልስማው ውስጠ ድምጹን
ላዳምጠው ሕመሜን
ንብረት ሐብቴን መልስ
ደስታና ሰላሜን፡፡
#ሸክም


#ክፍል_ሁለት (የመጨረሻ ክፍል)


#በእየሩስአሌም_ነጋ

ጥሩሰውም አሻግራ ሸክም ወደምታይበት ተመለከተችና ዐይኗን ሳታቆይ መለሰችው ሰው ያለበት ጨለማ ቦታ አሁን ባዶ መሰላትና ሸክም አፍጥጣ ወደ ጨለማው ተመለከተች።

“የጥሩሰው ባል ከሞተ በኋላ አንድ ሰው በድብቅ ወደ ጥሩሰው ቤት ሲገባ በተደጋጋሚ ታይቷል፡፡” የሚል ወሬ ስለነበር “ምናልባት በድንገት በመድረሴ በድንጋጤ ተደብቆ ይሆናል፡፡ ስትል
አሰበች፡፡ ደግሞ በዚህ ሀሳቧ እንዳትረጋ ያደረጋት ነገር የጥሩሰው መረጋጋትና ጨዋነት ነበር፡፡ እንደዚያ ቢሆን ኖሮ ጥሩሰውም እንዲህ ተረጋግታ አትጫወትም።

አሁን ዐይኗን አፍጣ ወደ ጨለማው በድፍረት ተመለከተች።
ጥሩሰው “ምነውሳ ወደዚያ አፈጠጥሽ?” አለች፡፡
“አይ እንደው ሰው ያየሁ መስሎኝ ነበር፤ ዞር ስል ደግሞ የለም፡፡” አለች በፍርሃት እየተመለከተቻት።
“ቅዠትሽን ሳትጨርሺ በጠዋቱ ተነስተሸ እዚሁ መቃዠት ጀመርሽ? ለመሆኑ ምን አይነት ሰው ነው ያየሽው? ጋኔል ይሆን?”
አሾፈችባት፡፡
“አይ እንግዲህ ወደ ጓዳ ጎራ ያለ ሰው ሊኖር ይችላል።” ብላ ፈገግ አለች፡፡

ጥሩሰው ሸክምን እንደመገላመጥ አድርጋ በገበቴ ላይ ያለውን እቃ ማጠብ ጀመረች፡፡ ወዲያው ሳቂታና ገራገር ፊቷ
ጨለማ አጠላበትና ዝም አለች፡፡

ሸክም ጥሩሰው ጥሩ ስሜት ውስጥ እንዳልሆነች ቢገባትም ምንም እንዳልተፈጠረ ጨዋታዋን ልትቀጥል ፈለገችና ምን ማውራት እንዳለባት ስታስብ፣ ጥሩሰው ቀና ብላ አፍጥጣባት
ቀረች፡፡

“ምነው?”
“እንዴት?”
“አፈጠጥሽሳ?”
“እንዲያው ገርመሽኝ ነውይ፡፡ እንደው ደርሰሽ ሰው አየሁ ስትይ...”
“ምን ላርግ እናት አለም? ያየሁትን ማለፍ አልወድ. አንቺስ አመሌን ታውቂው የለ?”
“ምን ታደርጊ አንቺማ ሲያወሩ የሰማሽውን ነው፡፡”
“ምኑን?” አለች ሸክም ደንገጥ ብላና መስማቷ ግምባሯ ላይ የሚታይ ይመስል አንገቷን ቀብራ፡፡
“እስቲ ይሁን፣ የወደቀ እንጨት ምሳር ይበዛበታል አሉ።ይሁን ግዴለም፡፡ እውነቱን ግዜ ያወጣዋል።” አለች በዐይኗ ሙሉ የሞላው እምባ እንዳይወርድ ወደ ላይ እያንጋጠጠች፡፡
“እና ለሰው ወሬ ብለሽ ልታለቅሺ ነው እናት አለሜ? ራስሽን የምታውቂው ራስሽ እንጂ ሌላ ሰው አይደለም፣” አለች የጠጣችበትን ዋርማ ቦታ እያስያዘች።
“ይሁና እንግዲህ ምን አድርጋለሁ? ያሉትን ይበሉ። የባሌ ሐዘን ከሆዴ ሳይወጣ አፋቸውን አልቻልኩትም፡፡ በነሱ ቤት ማጽናናታቸው ይሆን?” ጥሩሰው በረጅሙ ተነፈሰችና፣
“ይኸውልሽ ባለፈው ሰንበት ያቺ ምህዶ አፍ ያለችኝ ከሆዴም አይጠፋ። ያንን ሸውራራ ዐይኗን ይበልጥ አንሽዋራና
ድምጿን ጮክ አድርጋ እኔ እንድሰማላት ጓደኛዋን አሻግራ እያየች
ስሚ! ባልሽን ጠበቅ አድርገሽ ያዢ! ዛሬ ባልሽን ገድሎ አብሮሽ የሚተኛ ጎረቤትሽ ነው!' አለች። ሰምተሻታል አይደል?”
“በእርግጥ ሰምቻለሁ። ግን ገና ለገና አሽሙር ተናገረች ብለሽ መገመትሽ ጥሩ አይደለም።”
“እስቲ ይሁን ግዴለም” ብላ እንዳቀረቀረች ወደ ጓዳ ገብታ
አነስ ያለችውን የእንጨት መስኮት ከፍታ ዞር ስትል ባየችው ነገር
በድንጋጤ ደርቃ ቀረች፡፡
ፊት ለፊቷ እንደ ጅብራ ግርግዳውን ተደግፎ የቆመው ሰው አፉን እየተመተመ ዝም እንድትል ለመናት፡፡ ዝም ማለት
አልቻለችም፡፡
“ኧረግ ያባቴ አምላክ!” አለች፡፡
ሸክም የጠረጠረችው ሰው እውነት እንደሆነ አውቃ ወደ ጓዳ
ዘው ብላ ገባች፡፡

የቆመው ሰው ሸክምን በድንጋጤ እያየ፣ “አንቺ ቅንዳሻም! መተሽ የምታወሪውን ልሰማ ጥሩስው በረት እያለች ነው ቀድሜሽ መጥቸ የተሸሽኩኝ፡፡ እንዲያው የባለጌ ጓደኛ ያደረገሽ ምን ይሆን
አያ? ሞተሽ ባረፍሽ! አጅሪት አንቺንም ላንዱ ጎረቤት እንድትድርሽ ነው?” ዐይኑን እያጉረጠረጠ ሽመሉን እየወዘወዘ ወጣ፡፡

ጥሩሰው፣ “የተደፈርኩት ባሌ ሲሞት ነው ወይኔ!” አለችና ተስፋ ቆርጣና የሚብረከረክ ጉልበቷን በእጇ ይዛ ዐይኖቿን በመዳፏ እንደሸፈነች ከመደቧ ላይ ቁጭ አለች።

ሸክም ባለችበት ቆማ ተምዘግዝጎ እየዋጣ ያለውን ባሏን ግቢዉን ለቆ እስኪወጣ ተመለከተችና ጥሩሰውን ዞራ አየቻት። ጥሩሰው፣ ሸክም ወደ እርሷ እየተመለከተች እንደሆነ ገብቷት ፊቷን
ሸክም ከቆመችበት በተቃራኒው አቅጣጫ እያየች የሚወርደውን
እንባዋን ደጋግማ ትጠርጋለች፡፡
“አሁን ለምን እንደምታለቅሺ ብቻ ንገሪኝ?” አለቻት ሸክም፡፡
ለጠየቀቻት ጥያቄ መልስ ባለመስጠቷ ወደጥሩ ሰው ሄዳ በአንድ ጉልበቷ በርከክ አለችና፣
“ፊትሽ ምን እንደመሰለ ባየሽ? አታልቅሽ በቃ! ማንን ይመቸው ብለሽ ነው የምታለቅሽው? አንቺንም አውቅሻለሁ፣
ባሌንም አውቀዋለሁ።” አለቻት፡፡
ጥሩ ሰው ሸክም የምትለው አልገባ ብሏት ዐይን ዐይኗን በፍርሃት ስታያት፣ “ከዚህ በፊት ባሌ ሲያናግርሽና ደጋግመሽ
ስታመናጭቂው አይቻለሁ። ያንን ባላይ እንኳን ጨዋይቱን ጓደኛየን አምንሻለሁ... እመዬ አይክፋሽ... ተይው እናቴነሽ... ተይው አታልቅሽ ይሄ ድራሸ ቢስ ሁለተኝ ቀና ብሎም አያይሽ።እንኳንም እጄ ላይ ጣለልሽ”

ጥሩሰው ከሃዘኗ መኸከል አምልጦ የወጣውን ፈገግታዋን ለሸክም እየለገሰች እጇን ይዛ ከተንበረከከችበት እነድትነሳ
አደረገችና እንድትቀመጥ መደቡ ላይ ያለውን አጎዛ አራገፈችላት፡፡

💫አለቀ💫
👍1👎1
#ዋጋ

ቢበር በሰማይ ላይ ቢሽከረከር በምድር
ድንጋይ ቢደራረብ ቢሰበሰብ ሀብቱ
ሁሉን የሚገዛ ቢሆንም ንብረቱ
ምንም ቢባል አንቱ
አጀባው ቢበዛ ቢከተለው መንጋ
ሁሉም ሥጋዊ ነው አይሆንም የነፍስ ዋጋ።

🔘ሰላም ዘውዴ🔘
#ለቤ

ካሳ ጠቋቆረ ወየበብኝ ነጣ
ልቤ የልቡን ሲያጣ
ከእንግዲህ ምን ይሁን
በቅባት አይወዛም በፍቅር የገረጣ።

🔘ሰላም ዘውዴ🔘
#ከየትኞቹ_መደብከኝ

አምላኬ ሆይ ንገረኝ ?
ከየትኞቹ መደብከኝ
መንገዴስ ወዴት ይሆን
ቀኔ ሳይደርስ እድባንን
ከየቱ ነኝ ?
ትዕዛዛትህን ከረሱ
ራሳቸውን ካነገሱ
በፈቃድህ ከማይኖሩ
በስሜት ከሚበሩ
ህሊናቸውን ከሸጡ
ፍጡራንህን ከሸቀጡ
ከየቱ ነኝ?
አምላኬ ሆይ ንገረኝ
በስልጣናችው ከሚመኩ
ባዕዳንን ከሚያመልኩ
ሕዝብህን ከሚበድሉ
ከማይኖሩ በቃሉ
ከውስጠ ጭቃ አብለጭላጮች
ካስመሳይ ቀላዋጮች
ከየቱ ነኝ?
ለእኔ የማይታወቅ ላንተ ግልጽ ነውና
አሳውቀኝ ለየኝና፡፡

🔘ሰላም ዘውዴ🔘
👍1
#እማማ_ዣ


#ክፍል_አንድ


#በአሌክስ_አብርሃም

“አ…ቡ.…ቹ…ኡ…” ይላሉ፣ ከቤታችን ፊት ለፊት ያለ ባለ ግንብ አጥር ቤታቸውን የብረት በር ገርበብ አድርገው፡፡

“አቤት! እማማ !” እላለሁ፡፡ ሁልጊዜም ሲጠሩኝ ስለምጮህ እናቴ ትበሳጫለች፡፡
የእርሳቸውን ጥሪ ሳትሰማ፣ ድንገት እኔ ስጮኽ ደንግጣ በቁሟ የለቀቀችው የሸክላ ሰሃን ተንኮታኩቶ ያውቃል፡፡ ብዙ ጊዜ “ሲጠሩህ ወጣ ብለህ አቤት በል እሰው ጆሮ ግንድ ስር አታንባርቅ?” እያለች በቁጣ ብትመክረኝም፣ እማማ ዣ ሲጠሩኝ ግን ምክሯን እረስቼ መጮኼን ልቆጣጠረው አልቻልኩም፡፡ መጮህ ብቻ አይደለም …የቤት ሥራ እየሰራሁ ከሆነ እስክርቢቶና ደብተሬን፣ እየበላሁም ከነበር ያዘጋጀሁትን ጉርሻ ከእጄ ላይ ርግፍ
አድርጌ፣ወደቤታቸው ሮጣለሁ። እናቴ ታዲያ “ወታደርም እንዲህ በተጠንቀቅ አይቆምም” ትላለች፡፡

በርሬ ሄጄ “አቤት! እማማ ዣ” እላለሁ በሕፃንነቴ ያንዣቡ የሚል ስማቸው አልያዝልኝ ብሎ “ዣ” አልኳቸው፡፡ካደኩም በኋላ “ዣ" ብያቸው ቀረሁ።

“ናማ! ቶሎ በል… ወሞ ገዝተህልኝ ና …ቱ! ይች ምራቅ ሳትደርቅ!”

“ያባባ ጃንሆይን ታሪክ ከነገሩኝ ነዋ?!”

“ና! ዝም ብለህ ሂድ .…ወተፈናም !… የጃንሆይ ታሪክ ለማንም ተላላኪ የሚሰጥ ድርጎ አረከው እንዴ? ሻይና ዳቦ ካገኘህ ምን አነሰህ?! ለባሪያ ነብስ አባት፣ ዲያቆን ምን አነሰው አሉ.ሆሆሆ ግዛ ያሉኝን ኦሞ የተባለ የዱቄት ሳሙና ለመግዛት፣ ወደ ዘመናይ ሱቅ ቁልቁል እበራለሁ…

ዘመናይ ማርየ
ዘመናይ፣ ገበያ ለመሳብ አጉል ወሬና ሽንገላ ስለምታበዛ ብትሰለቸኝም፣ ሱቋ ግን ትልቅና በብዙ መብራት የተንቆጠቆጠ ስለሆነ ደስ ይለኛል፡፡ በነጭ “ፍሎረሰንት” አምፑሎች
የተንቆጠቆጡትና በተንሸራታች መስተዋት የሚዘጉት መደርደሪያዎች፣ የተለያዩ ቀለማት ካላቸው የሱቅ ዕቃዎች ጋር ተዳምረው፣ ተልኬ በሄድኩ ቁጥር ከሱቁ ውጣ ውጣ አይለኝም:: በዚያ ላይ ዘመናይ ራሷ ዘናጭ የሃያ አምስት ዓመት ሴት ነበረች፡፡(እንደቀልድ ሃያ አምስት ሞላኝ ስትል ሰምቻታለሁ) የምትቀባው ሽቶ ብቻ በመንገድ የሚያልፍ ሰው
የሚጠራ ፤ ሲበዛ ንጹሕ ሴት፡፡ በተለይ ጣቶቿ! ሸቀጣሸቀጥ መኻል እየዋለች እንዴት ጣቶቿ እንደዚያ ንጹሕና የሚያንጸባርቁ እንደሚሆኑ ይገርመኛል፡፡ ደግሞ ሱቁ ውስጥ ሁልጊዜ ደስ የሚሉ ሙዚቃዎች ይከፈታሉ፡፡ ራሷ ዘመናይ ድምጿ ደስ ይላል፤ ሳቋንና የምትናገረውን ነገር ግን አልወደውም፡፡ በተለይ ሳቋን! አንዳንዴ ታዲያ ድምጿ የሚሽከከው አማርኛ አስተማሪያችን የምታወራልን አጓጊ ተረቶች፣ በዚች ዘመናይ በተባለች ባለ ሱቅ ድምፅ ሲተረክ እያልኩ አስባለሁ፡፡

ገና ወደ ሱቁ ስገባ፣ “አቡቹ ማሬ! …ምን ልስጥሽ?” አለችኝ፡፡ የአፍ መብለጥለጥ
ይደክመኛል! በተለይ “አንች!” እያሉ የሚያናግሩኝ ሰዎች ጤነኛ አይመስሉኝም እንዲህ ዓይነት ሰዎች ጠበል ቢወሰዱ ይኼ ነገራቸው ሰባት ጊዜ ጩኾ የሚወጣ አጋንት ነው የሚመስለኝ፡፡ ሁልጊዜ ስትፈጥንብኝና በማያባራ ፈጣን ልፍለፋዋ ስታጣድፈኝ፣ የተላኩት ነገር ይጠፋብኛል፡፡ ስንት ቀን ያልታዘዝኩትን ነገር አንጠልጥዬ ሄጄ መልስ ተብያለሁ! (ገና ካሁኑ ልቡ የት ሂዷል!? ከሚል ወቀሳ ጋር) የተገዛ ዕቃ እንደመመለስ
ደግሞ የሚያሳፍረኝ ነገር የለም! ዘመናይ ግን ዕቃ ልመልሰም፣ ልመልስ መሄዴን
እስከምረሳው፣ በዚያ ምላሷ ትንቀለቀልብኛለች፡፡ “እቡቹ ነፍስ ነገር፣ ችግር የለውም ይመለሳል…ግን ፍቅር ያዘሽ እንዴ? መርሳት አብዝተሻል ...ከእኔ እንዳይሆን ብቻ
…ባረገው ካካካካካካካካካ !!”

“እ… ኦሞ ስጭኝ አልኳት የጨበጥኳትን ብር ባንኮኒው መስተዋት ላይ እያስቀመጥኩ፡፡

ይሰጥሃላ! እንደሱማ በግንባርህ አታየኝም! ካካካካካ…” እያለች ፈጽሞ ያላዘዝኳትንና ከዚያ በፊት አይቼው የማላውቀውን፣ በቢጫ ላስቲክ የታሸገ የዱቄት ሳሙና አንስታ
“ይኼን ውሰድና እቤት ይሞክሩት ..እዲስ ነው፣ ቆሻሻን ድራሽ አባቱን የሚያጠፋው” ብላ ብር ያስቀመጥኩበት መስተዋት ላይ ወረወረችው፡፡ ተሽከርክር . እፊቴ ሲደርስ ቆመ፡፡ ዕቃዎችን ከሩቅ ወርውሮ ደንበኞቿ ፊት ባለው መስተዋት ላይ ማሽከርከርን እንደሆነ አራዳነት ነው የምታየው! አንዳንዴ ዕቃ ልታወርድ
ከተንጠላጠለችበት መሰላል ላይ እንደ ቆመች፣ ገዥው የፈለገውን ዕቃ ወርውራ
መስተዋቱ መኻል ላይ ቁጭ ታደርገዋለች

በእርግጥ እኔም ቤታችን መኻል ላስቲክ ለብሳ በምትቀመጥ የምግብ ጠረጴዛ ላይ ዕቃ እየወረወርኩ፣ ዘመናይ እንደምታደርገው ተሸከርክሮ እንዲቆም ለማድረግ ብዙ ጊዜ ሞክሪያለሁ፤ ግን አሪፍ ለመሆን ብዬ አይደለም፡፡ በቃ እንዲሁ ለመሞከር፤ አንድም ጊዜ
ግን የምወረውረው ዕቃ ተረጋግቶ ጠረጴዛዋ ላይ ቁሞልኝ አያውቅም፤ ተምዘግዝጎ መሬት ላይ ይወድቃል፡፡ ምናልባት የጠረጴዛችን እግሮች ጤነኛ ስላልሆኑና፣ አንዴ ወደ ሰሜን አንዴ ወደ ደቡብ ትንሽ ዘመም ስለምትል ይሆናል።

“አይ ኦሞ ነው የተባልኩት ኦሞ ስጭኝ!” አልኳት የምፈልገው የዱቄት ሳሙና ወደ
ተደረደረበት እየጠቆምኩ…

“ወ...ይም ይኼንኛውን ውሰድላቸው ዋጋው እኩል ነው!.…ኦሞኮ ፋሽኑ አልፎበታል አቡችዬ ..እያለች ሌላ ድርፉጭ ያለ ካርቶን ከመደርደሪያው ላይ አወረደች፤የመወርወር ትርኢቷን ሳታሳይ በፊት፣ በብስጭት መስተዋቱ ላይ ያስቀመጥኩትን ብር አፈፍ አድርጌ፣
ሱቋን ትቸላት በሩጫ ወጣሁ፡፡ ከኋላየ ዴጋግማ ስትጠራኝ እሰማታለሁ፡፡ በሷ እልህ (ኦሞ ያለው እሷ ሱቅ ብቻ መሰላት እንዴ? እያልኩ) ወለኔ ወደሚባለው በበሩ እንኳን ሳልፍ ወደሚቀፈኝ ሱቅ ተጣደፍኩ!

#ነገረ_ወለኔ
እውነቱን ለመናገር ይኼን ወለኔ የሚባል ሱቅ፣ እንኳን ውስጡ ገብቼ፣ እንዲሁ በዛ
በኩል እያለፍኩ ሳየው ራሱ የምቆሸሽ ነው የሚመስለኝ፡፡ እዚህ ሱቅ በረንዳ ላይ ናፍጣ ስለሚሸጥ፣ ከሁሉም ነገር ቀድሞ የሚቀረና የናፍጣ ሽታ ነው ከስር ላይ የሚቀበለው፡፡የዚያ ቤት ዕቃ ሁሉ ጋዝ ጋዝ ይሸታል፡፡ በውጩ የጭቃ ግድግዳ ላይ “ምንትስ አለ”
የሚሉና በተለያዩ ቀለማት በወልገድጋዳ የእጅ ጽሑፎች የተጻፉ ብዙ ማስታወቂያዎች ተለጥፈዋል፡፡ ማስታወቂያዎቹ ያስቃሉ ...

የአይጥ መርዝ አለ!

የአይጥ ወጥመድ አለ ...

አይጥ የማይበላው የእህል ጆንያ አለ (ደግሞ ይኼ ምንድነው?) “አይጥ አለ” ብለው መለጠፍ ነው የቀራቸው ...(መኖርም አለበት! ይኼን ሁሉ አይጥ ነክ ነገር በምን ሞክረው ለገበያ አቀረቡት ታዲያ?!) የተነጠረ ቅቤ አለ ..ትንባሆ አለ ..የኑግ ዘይት አለ...

ከትልቅ የቆሸሽ ሰማያዊ በርሜል እየቀነሱ የሚሸጡት የኑግ ዘይት፣ እዚያና እዚህ ተነካክቶ፣ ከመደርደሪያው እስከ ሱቁ ወለል ድረስ ወዛም እድፍ ተለድፎ
አጠቋቁሮታል፡፡ ሁልጊዜ ደግሞ እዚያ ሱቅ የሚነጠር ቅቤ ይሸተኛል፤ ሱቁ የናፍጣ፣ የእጣን፣ የቅቤና የሲጋራ ሽታ ተቀላቅሎበት የሚያቅለሸልሽ ስሜት ይፈጥራል…ደግሞ የት እንደተቀመጠች የማትታይ ሬዲዮ እዚህ ሱቅ በገባሁ ቁጥር ሽሽሽሽሽ የሚል ድምፅ ጋር
የተቀላቀለ ዜና ስታሰማ ነው የምደርሰው ብዙውን ጊዜ የዚህ ሱቅ ደንበኞች፣ በወረቀት የሚጠቀለል ነገር የሚያጨሱ የገጠር ሰዎች ናቸው፤ ለዚያም ሳይሆን አይቀርም፣ በተለይ ጠዋት ጠዋት…ፊት ለፊት የበረንዳው ቋሚ እንጨት ላይ ታስሮ የሚቆም፣ የዝንብ ሰርገኛ የሚጨፍርበት፣ ገጣባ አህያ በሩ ላይ አይጠፋም፡፡ ቢሆንም እንደ ዘመናይ በአጉል አራዳነትና አብረቅራቂ ውበት ታጅቦ ያልፈለጉትን አስገድዶ ከሚያስገዛ ብልጣብልጥ
ይልቅ፣ ቃል ሳይተነፍስ የጠየቁትን የሚሰጠው የዚህ ሱቅ ባለቤት ይሻላል! ስሙ አይያዝልኝም፣ ምናልባትም ከመጀመሪያውም አላውቀውም ይሆናል! ..ሱቁ በልምድ “ዘይት ቤቱ” ነው የሚባለው!
👍2
ጮክ ብዬ “ባለሱቅ ኦሞ አለ …” አልኩ፡፡ ከውጭ ስገባ ውስጡ ጨለማ ሆኖብኝ ስለነበር፣ ሰውዬው አጠገቤ ቁሞ እንደነበር እንኳን አላየሁትም፤ያንን በሚያክል በመዓት"ኮተት የተሞላ ሱቅ ውስጥ፣ አንዲት ፍዝዝ ያለችና እንደ ሰካራም ዓይን የቀላች፣ ዙሪያዋን
የሸረሪት ድር የከበባት አምፑል ብቻ ናት ያለችው፡፡ ጉንጩ በጫት የተወጠረው ባለሱቅ
“ቀስ! ዘይት እንዳትደፋ!” ብሎ ካስደነበረኝ በኋላ፣ አለመድፋቴን ተንጠራርቶ ተመልክቶ የምፈልገውን ኦሞ፣ ከሆነ ጨለማ መደርደሪያ ውስጥ አውጥቶ ሰጠኝ፡፡ ወደ በረንዳው ወጥቼ ስመለከት፣ የግራ እጄን መዳፍ ዘይት ነክቶት ነበር! የመልስ ሳንቲሞቹ ዘይት ያስነኩኝ! ሳያቸው እርስ በእርስ ተጣብቀዋል እኪሴ ጨምሪያቸው የበረንዳው ቋሚ ግንድ ላይ ጠረግሁ፡፡ ትንሽ እንደ ሄድኩ አፍንጫዬን ልጠርግ ስሞክር እጄ ናፍጣ ናፍጣ ይሸታል የሚያሳብድ ሱቅ...

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
👍2
አትሮኖስ pinned «#እማማ_ዣ ፡ ፡ #ክፍል_አንድ ፡ ፡ #በአሌክስ_አብርሃም “አ…ቡ.…ቹ…ኡ…” ይላሉ፣ ከቤታችን ፊት ለፊት ያለ ባለ ግንብ አጥር ቤታቸውን የብረት በር ገርበብ አድርገው፡፡ “አቤት! እማማ !” እላለሁ፡፡ ሁልጊዜም ሲጠሩኝ ስለምጮህ እናቴ ትበሳጫለች፡፡ የእርሳቸውን ጥሪ ሳትሰማ፣ ድንገት እኔ ስጮኽ ደንግጣ በቁሟ የለቀቀችው የሸክላ ሰሃን ተንኮታኩቶ ያውቃል፡፡ ብዙ ጊዜ “ሲጠሩህ ወጣ ብለህ አቤት በል…»
#ዘማይቱ

ኃጥያተኛ ብትሉኝ
አውጥታቹ ብትጥሉኝ
መርከሴን ብታወሩ
ድንጋይ ብትወረውሩ
ብትሸሹኝ ብትጠየፉኝ
እርሱ እንደሁ ድሮም ከጥንቱ
የሞተው ያለሃጥያቱ
ለእኔው ነው ለዘማይቱ

🔘ሰላም ዘውዴ🔘
#ዞር_በል

ህመሜን ካልታመምክ
ችግሬ ካልገባክ
ውስጤን ካልተረዳህ
ዐይኔን ካላነበብክ
ኀዘን ደስተዬን አብረክ ካልተካፈልክ
ካልገባክ ችግሬ
እኔው ለኔ ልኑር
ዞር በል ከስሬ።

🔘ሰላም ዘውዴ🔘
#ምልክት

ያሁሉ ሽንገላ
የቃላት ድርድርህ
ውዳሴ ከምርህ
ከወዴት ተነነ
ከመቼ አለቀብህ ?
ከምን ደረሰብህ ?
ንገረኝ አንተ ሰው እስኪ ልጠይቅህ ?
ምን አገኘህና ጠፋብህ ተረቱ ?
ውዴ፣ ሆዴ አንጀቴ ሕይወቴ ማለቱ
በሁሉ መማረር ማንነትን መርሳት
በዋሉበት ማደር በብዙ መሳሳት
ደርሶ ቱግ ማለት በትንሽ ትልቁ
ምልክት ነው እንዴ የፍቅርህ ማለቁ ?
#እማማ_ዣ


#ክፍል_ሁለት


#በአሌክስ_አብርሃም

#ትንሽ_ወሰድ
ይኼን ሁሉ ውጣ ውረድ አሳልፌ ለእማማ ዣ የገዛሁትን ኦሞ “ይኼው” ስላቸው፣

“ምኑ!?” ይሉኛል ...ኦሞ ግዛ ብለው መላካቸውን ረስተውታል፡፡ አንዳንዴ እንዲ
“ልባቸውን ወሰድ የሚያደርገው ነገር አለ” እያለ የሰፈሩ ሰው ያማቸዋል፡፡ በእርግጥ
የመንደሩ ሰው እንደሚያወራው አይጋነን እንጂ አልፎ አልፎ ነገር ይረሳሉ። ይኼ ደግሞ ማንም ሰው ሊያጋጥመው የሚችል ነገር ነው። እኔ ራሴ ብዙ ነገር እረሳ የለ እንዴ?! ስንት ጊዜ ነው እናቴ የተጣደ ነገር ጠብቅ ብላኝ የረሳሁት? እዚያው እንደ አሻሮ ከስሎ፣ ቤቱ በጭስ ከታፈነ በኋላ አይደል እንዴ፣ ትዝ የሚለኝ?! …ማንም ሰው ይረሳል …ምን ሰው ብቻ …የሰፈራችን ትልልቅ ሰዎች ራሳቸው በሬዲዮ የድርቅና የወረርሽኝ ምናምን ዜና በሰሙ ቁጥር፣ ስንት ጊዜ ነው “ምነው እግዚሐር ኢትዮጵያን ረሰሃት!?” የሚሉት?! እንግዲህ እግዚሐርም ቢረሳ ይሆናላ፤ ያውም ስንት ሚሊየን ሕዝብ በየቀኑ ቤተክርስቲያን እየሄደ አትርሳኝ እያለው፤ ጎረቤቱ እማማ ዣ ላይ ለምን እንደሚያጋንነው
አይገባኝም! እማማ ዣ ሽቅርቅር! ባል ነበራቸው እየተባለ ይወራል፡፡ (ሽቅርቅር ቃሉ ስለሚገርመኝ አልረሳውም!) ታዲያ ያ ባላቸው ይኼን ሆንኩ ሳይል ድንገት ከቤት እንደወጣ ሳይመለስ ቀረ፡፡ መጀመሪያ አንዱ ዘራፊ ገድሎ ጥሎት ይሆናል ብለው ያላመለከቱበት ፖሊስ
ጣቢያ አልነበረም አሉ፡፡ ጎረቤቶቻችን ሲያወሩ ነው እንግዲህ የሰማሁት:: ብዙ ቀን ስለ እማማ ዣ ሲያወሩ ሰምቻቸዋለሁ የኛ ሰፈር ሰው ከሥጋ ቅርጫ ቀጥሎ የሚወደው ነገር፣ እማማ ን ማማት ይመስለኛል።
እናቴ እራሷ ታወራለች! በእርግጥ እናቴ ያወራችው እማማ ዣን ለማማት አልነበረም አልፎ አልፎ እቤታችን የምትመጣውን የአክስቴን ልጅ ስትመክር እንደ ምሳሌ ነው ያነሳቻቸው።የአክስቴ ልጅ ሔለን (ሳይሞቅ ፈላ ነው እናቴ የምትላት) አንድ ቅዳሜ ቀን እኛ ቤት አደርኩ ብላ፣ ሌላ ቦታ ማደሯ ታወቀ:: ከማን ጋር እንዳደረች ባላውቅም፣
ከእናቴ አወራር ግን፣ ከሆነ ወንድ ጋር አድራ መምጣቷን ጠርጥሪያለሁ.……. የዚያን ቀን እናቴ እማማ ዣን ምሳሌ አድርጋ ስትመክራት እንዲህ አለች “ይችን የኛን ጎረቤት ያንዣብን ታውቂያቸው የለም ?…. ይኼውልሽ እሳቸው እንዲህ ነካ አድርጓቸው የቀሩት በወንድ ነው…” ካለች በኋላ፣ እማማ ዣ ለባላቸው ያደረጉለትን ውለታ…ከአመድ አንስተው ሰው እንዳደረጉት፣ በሕልሙ እንኳን አይቶት የማያውቀውን ኑሮ እንዳሳዩት
ብዙ ብዙ ነገር እንዳደረጉለት አውርታ በቁጭት እንዲህ አለች…

“ያን ሁሉ አርገውለት፣ አፈር አይንካህ ብለውት አፈር ያስበላውና! ..ሌላ ሴት በላያቸው ላይ ወዶ፣ ባዶ ቤት አስታቅፏቸው ሄደ። የጠፋ ሰሞን ...እሳቸው ምን ሆነብኝ ብለው
ፊታቸውን እየነጩ በየፖሊስ ጣቢያው፣ በየሆስፒታሉ ሲዞሩ ከረሙ …ምን መዞር ብቻ፣ በየሜዳው ሞቶ የተገኘውን ዘመድ ያጣ የስንት ቀን ሬሳ እያገላበጡ ሲያዩ ከርመው በኋላ ባልሽ ተገኝቷል' ሲባሉ ከቤታቸው የጀመሩ እልልል… እያሉ ፖሊስ ጣቢያ መሄድ! የምስራች ሰምተው በደስታ ፖሊስ ጣቢያ የደረሱት ሴትዮ፣ ሌላ መርዶ ጠበቃቸዋ!”

“ምን ሆነ? ሞተ?” አለች የአክስቴ ልጅ፡፡

“በምን ዕድሉ! …ባለጌ ይሞታል እንዴ?! …ፖሊሶቹ አርፈሽ ተቀመጭ! እሱ አንዲት ሴት ወዶ ጠቅልሎ ገብቶልሻል
አሏቸው እንጂ! እንግዲህ ያኔ እዛ ፖሊስ ጣቢያ ሲደነግጡ ያግኛቸው፣ አልያ የማንንም ሬሳ ሲያገላብጡ ሰይጣን ይስፈርባቸው እንጃ .. ይኼው ስንት ዘመን አይምሯቸው ተቃውሶባቸው ቀሩ!”
“ሚስኪን! ታዲያ ምናደረጉ?” አለች የአክስቴ ልጅ ማስቲካ እያላመጠች ስትናገር እንደ መሞላቀቅ ያደርጋታል!
“…ምን ያደርጋሉ ... እየፈነጠዙ የሄዱት ሴትዮ፣ የመንደሩን ዓይን ለማየት ተሸማቀው ጥፍር አክለው ወደ ቤታቸው ተመለሱ፤ ቤታቸውን ዘግተው ከርመው በስንተኛው የባላቸውን ልብስ ነሽ፣ ፎቶ ነሽ፤ ሁልጊዜ የሚቀመጥበትን ሶፋ ሳይቀር፣ ከሌላው ሶፋ ነጥለው ግቢያቸው ውስጥ ከመሩና እሳት
ለቀቁበት ... ቤታቸውን ታውቂው የለም? …እሳቱ ያንን ረዥም ግንብ አልፎ ሲንቀለቀል ደመራ መሰለ ...

ከዚያ ወዲህ ወንድ የሚባል ነገር አታንሱብኝ አሉ፣ በቃ… ማንም አጠገባቸው ስለሌ ትንፍሽ ብሎ አያውቅም:: ይኼው ስንት ዘመናቸው እንደ ባህታዊ ቤታቸውን ዘግተው
ልብስ ሲለኩና ሲያወልቁ ...በየቀኑ ኦሞ እየገዙ ምኝታ ቤታቸውን ሲያጥቡ ይውላሉ...አንድ ቀን ምኝታ ቤታቸውን በኦሞ ሳያጥቡ ውለው አያውቁም!! እና ምን ልልሽ ነው
….ወንድ አምነሽ እማይሆን ነገር ውስጥ እንዲች ብለሽ እንዳትገቢ… እንኳን ባዶ እጅሽን እየተወዘወሽ ቤታቸው ሂደሽ ቀርቶ፤ ወንዶች ከየትም አንስተው ወርቅ ላይ ቢያስተኟቸው፣ ልባቸው የማያርፍ ሰላቢዎች ናቸው ..” አለች።

የመጨረሻዋ ስድብ አባቴ ላይ ያነጣጠረች መሆኗን ከልምድ አውቃታለሁ..እናቴ “ሰላቢ” የሚል ቃል የምትጠቀመው፣ እኔን በወለደች በሁለት ዓመቷ የፈታትን አባቴን ስታነሳ ነው፡፡ ለፍቻቸው ዋናው መንሥኤ የአባቴ ቤተሰቦች “ልጁ ምኑም ምኑም አንተን
አይመስልም” ብለውት ነው አሉ፤ ታዲያ የአባቴን ፎቶ ባየሁ ቁጥር እንኳንም እሱን
ያልመሰልኩ እላለሁ፡፡ ..ሰው ልጄ እንደኔ መልከ ጥፉ ካልሆነ ብሎ እንዴት ሚስቱን
ይፈታል?!

ይህ የእማማ ዣ ታሪክ እኔን እንባዬ እስኪመጣ አሳዘነኝ እንጂ ላክስቴ ልጅ እንደሆነ ምንም አልጠቀማት፡፤ እንደ ቆንጆ የሬዲዮ ትረካ ማስቲካዋን እያላመጠች ይኼን ሁሉ የክህደት ታሪክ በኮመኮመች ልክ በአስራ አምስተኛው ቀን፣ ከአንድ ጉጉት ከመሰለ ልጅ
ጋር (እናቴ ናት ያለችው) ተያይዛ ጠፋች፡፡ እንዲያውም አብረው መኖር መጀመራቸውን ለእናቴ ደውላ ነገረቻት:: አክስቴ በሷ ምክንያት ታማ ስንት ወር ጠበል ለጠበል ዞራለች፡፡ በዓመቱ የአክስቴ ልጅ ሔለን ፊቷ አባብጦ፣ የግራ ክንዷ ተሰብሮ፣ ወደ ጤና ጣቢያ
የምትመጣ ይመስል እየተንከረፈፈች እቤታችን መጣች፡፡ “በትንሽ ትልቁ መቅናት ነው! መደብደብ! ..ነጋ ጠባ በጥፊ ጆሮ ግንዴን እየጠረቀመኝ፣ ይኼው የቀኝ ጆሮዬን ያዝ ያደርገኝ ጀምሯል ...” ብላ ተነፋረቀች፡፡

እናቴ ታዲያ እሱ እንኳ ድሮም ጆሮሽ ምክር አይሰማ! ዋናው ነገር እንኳን ነፍስሽ ተረፈ" ብላ ተቀበለቻት። ምስኪን የአክስቴ ልጅ! እንደማማ ዣ አቃጥላ እልኋን የምትወጣበት ልብስ እንኳን ሳይሰጣት፣ ተከትላው የሄደችው ወንድ ቀጥቅጦ ቀጥቅጦ መለመላዋን አባረራት፡፡ እናቴም ለወንዶች ባላት ጥላቻ ላይ፣ የአንድ ሰላቢ ወንድ ታሪክ ተጨመረላት። ታዲያ አንዳንዴ፣ ከአክስቴ ጋር እያወሩ እናቴ፣ “ያ! ሰላቢ…” ስትል
“የትኛው?” ትላታለች አክስቴ! አክስቴም ትንሽ ወሰድ ያደርጋታል!

#ከፈረሱ_አፍ
አንዳንዴ፣ “ይኼን የእማማ ዣ ታሪክ፣ እናቴ የአክስቴን ልጅ ለማስፈራራት የፈጠረችው ቢሆንስ!?” እያልኩ መጠራጠሬ አልቀረም! በእርግጥ የኦሞው ታሪክ እውነት ነበር፡፡በየቀኑ ከሱቅ የምገዛው እኔ ራሴ ስለነበርኩ ለዚህ ምስክር ነኝ፡፡ የተጠራጠርኩት
በባላቸው አጠፋፍ ላይ ነበር፤ምክንያቱም ከብዙ ጊዜ በኋላ ራሳቸው እማማ ዣ ፈፅሞ እናቴ ካወራችው የተለየ ታሪክ ሲያወሩ ስለሰማሁ ነበር፡፡ ዞሮ ዞሮ እናቴም ሆነች እማማ ዣ፣ አልያም ጎረቤቱ የሚስማሙበት ነገር ሴትዮዋ ባላቸው ሄደ መጣ፣ ምንም ኤልጎደለባቸውም! እራሳቸውም “እኔ ያንዣቡ ምን ጎደለብኝ… ባቄላ አለቀ ..ምን ቀለለ አሉ!” እያሉ ከፍ ባለ ኩራት ይናገራሉ.ኩራትን መቸም እሳቸው ይኩሯት!

አንድ እሁድ ቀን ታዲያ እማማ ዣ ታጥቦ የተከመረ ልብስ እያዘጋጁ፣ እግረ መንገዳቸውን ብዙ ጊዜ ጀምረው
1
ያቋረጡትን የአባባ ጃንሆይን ታሪክ ያወሩልኛል፡፡እኔም ከሥር ከሥራቸው እየተከተልኩ አዳምጣለሁ፡፡ እያወሩ እየተከተልኳቸው፣ ኦሞ-ኦሞ ወደሚሸተው መኝታ ክፍላቸው ተከታትለን ገባን፡፡ በወሬው መሃል የታጠፈ ልብስ
ሊያስገቡ በልብስ ከተሞላው ትልቅ የድሮ ቁምሣጥናቸው ጋር ሲታገሉ፣ ድንገት
ከላይኛው መደርደሪያ፣ ከልብሶቹ መሃል የሆነ ነገር ዱብ ብሎ ወደቀ፡፡ በብርማ የብረት ክፈፍ የተከበበ፣ የእንቁላል ቅርጽ ያለው፣ ባለ ጥቁርና ነጭ ጉርድ ፎቶ ግራፍ ነበር፤ የሆነ ጎፈሬ ሰውዬ ፎቶ፡፡ እማማ ዣ ቤት ሥዕልም ይሁን ፎቶ የሚባል ነገር ለምልክት እንኳ ስላልነበረ፣ እንደ ተአምር ከሰማይ የወረደ ነበር የመሰለኝ፡፡የተሸከሙትን ልብስ አልጋቸው ላይ ወርውረው ፎቶውን ሊያነሱ ሲደነባበሩ፣ ቀድሚያቸው አፈፍ አድርጌ
እንዳነሳሁት፣ ከእጄ ነጥቀው ቁም ሣጥኑ ውስጥ፣ ልብስ መኻል ፈልፍለው ቀበሩና
ያጣጠፉትን ልብስ ሁሉ ሳያስገቡ ቁም ሣጥኑን ቆለፉት፡፡

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
አትሮኖስ pinned «#እማማ_ዣ ፡ ፡ #ክፍል_ሁለት ፡ ፡ #በአሌክስ_አብርሃም #ትንሽ_ወሰድ ይኼን ሁሉ ውጣ ውረድ አሳልፌ ለእማማ ዣ የገዛሁትን ኦሞ “ይኼው” ስላቸው፣ “ምኑ!?” ይሉኛል ...ኦሞ ግዛ ብለው መላካቸውን ረስተውታል፡፡ አንዳንዴ እንዲ “ልባቸውን ወሰድ የሚያደርገው ነገር አለ” እያለ የሰፈሩ ሰው ያማቸዋል፡፡ በእርግጥ የመንደሩ ሰው እንደሚያወራው አይጋነን እንጂ አልፎ አልፎ ነገር ይረሳሉ። ይኼ ደግሞ ማንም…»
#ሌላ_ቀን

ሲከፋህ እልል በል
ስታዝን ተጽናና
ስትወድቅ ተፍጨርጨር
ለመነሳት ሞክር
ነገን በሌላ አስብ
ከራስህ ጋር ምከር
ይሄንን ሳታደርግ
ፋይል ዶሴ ከፍተህ
ለአለዎ ካስነበብካት
የቆምኩበት መንገድ
ፍጻሜ ነው ካልካት
ያን ጊዜ አበቃልህ
ደስታዋን አበስርካት
ዋጋ ቢስ መሆንክን
ራስህ ነገርካት
ይልቅስ ቀና ስል
ቀን አለ በልና
ወድቀው የተነሱትን
ፈርጦች አስብና
ያኔ ነው ዓለምን
ረግጠህ የምትጥላት
በራስህ ዛቢያ ሥር ምታሽከረክራት፡

🔘ሰላም ዘውዴ🔘
#እማማ_ዣ


#ክፍል_ሶስት


#በአሌክስ_አብርሃም

አልጋቸው ላይ ወርውረው ፎቶውን ሊያነሱ ሲደነባበሩ፣ ቀድሚያቸው አፈፍ እንዳነሳሁት፣ ከእጄ ነጥቀው ቁም ሣጥኑ ውስጥ፣ ልብስ መኻል ፈልፍለው ቀብሩና
ያጣጠፉትን ልብስ ሁሉ ሳያስገቡ ቁም ሣጥኑን ቆለፉት፡፡
“የማነው ፎቶ?” አልኳቸው፡፡

“የማነው ፎቶ?” አልኳቸው፡፡

“የቱ?”
ቁምሣጥኑ ውስጥ ያስገቡት ፎቶዎ

“እ…እሱማ የሞተው አጎቴ ነው” ብለው ኮስተር አሉ!

“ምን ሁኖ ነው የሞተው?”

“አላርፍ ብሎ!……ምን የመሰለ የንጉሥ ፈረሱን እቤት አስሮ፣ አንዲት በቅሎ ሲጋልብ ይዛው ገደል ገባች ..በቅሎ ታቃለህ?!” ብለው ጠየቁኝና መልሴንም ሳይጠብቁ፣
“…ተያይዘው አመድ ሆኑ! አጥንታቸውም አልተገኘ፤ አመድ ነፋስ አበነናቸው…ብን…! ብለው በአራት ጣታቸው የታችኛውን ከንፈራቸውን ከታች ወደላይ መንጨር አደረጉት!
“አጥንታቸውና አመዳቸው ካልተገኘ …አጎትዎትና ፈረሳቸው መሞታቸውን በምን
አወቁ?”

“ፈረስ አላልኩም… እያጣራህ አእድምጥ ..በቅሎ .…”

“እኮ ...በቅሎ .……..

በረዥሙ ተንፍሰው ዝም አሉ:: የሚሠሩት ግራ እንደገባቸው ዓይነት፣ ፀጉራቸውን እንደ ማከክ እያደረጉ መኝታ ቤታቸውን ኮስተር ብለው ዙሪያውን ቃኙትና፣ በረዥሙ ተንፍሰው ከዚያ በፊት ሲያወሩኝ የነበረውን የአባባ ጃንሆይንም ወሬ ሳይጨርሱልኝ “አቡቹ .እራሴን አመም አርጎኛል ጋደም ልበል ሂድ” ብለው ወደ አልጋቸው ሄዱ፡፡

እኔም የጓጓሁለት ታሪክ በመቋረጡ ቅር እያለኝ ወደ ቤቴ አዘገምኩ። ሁለት ቀን ሙሉ ጠርተው ኦሞ ግዛ ሳይሉኝ፣ ጎረቤትም ቡና ሲጠራቸው ሳይሄዱ፣ ቤታቸውን ዘግተው ጠፉ “ተነሳባቸው” ተባለ፡፡በሦስተኛው ቀን ግን፣ በሐበሻ ቀሚስ ሽክ ብለው ዘንጠው፡ የወርቅ አምባርና ሐብላቸውን ከትልልቅ የጆሮ ጉትቻ ጋር እያንቦገቦጉ ብቅ አሉ፡፡ የሆነ
ቦታ ሊሄዱ መስሎኝ ነበር …ግን እንደዚያ ዘንጠው የትም አልሄዱ… ዝም ብለው
ይወጡና፡ የግቢውን የብረት በር ገርበብ አድርገው፣ ዙሪያውን ቃኝተው መልሰው
ይገባሉ፡፡ እሴታቸው ይገቡና ተመልሰው ይወጣሉ፡፡ በመጨረሻ ቀጥ ብለው እኛ ቤት መጡ፡፡ እናቴን ሰላምም ሳይሏት እስቲ ቆንጆ ቡና አፍሊ አቡቹ ናማ ቡና ግዛ” ብለው ከምታምር ቦርሳቸው ውስጥ ድፍን አምስት ብር አውጥተው ሰጡኝ:ወደ ዘመናይ ሱቅ በረርኩ፡፡

“አቡቹ ነፍሴ -ማታ የገባ የጅማ ቡና አለ - ብላ በዜማ አቦል ጀባ ብላ ቡናዎን
ብቀምሰው፣ እግሬ ወደ ጅማ ሱስ አመላለሰው ካካካካ” ስትዘፍን ድምጿ ያምራል፡፡

#ዳቦና\ሻይን_ተገን_በማድረግ
የእኔ ይለይ እንጂ፤ እማማ ያንዣቡን የመንደሩ ልጆች ሁሉ እንደ ነፍሳችን ነው
የምንወዳቸው፡፡ ቤታቸው ሻይ እይጠፋም፡፡ ልከውን ስንመለስ ዳቦ በሻይ የማይቀር ሐቃችን ነበር እስካሁንም ድረስ መሥሪያ ቤቶች ውስጥ 'ተላላኪ' የሚባሉ ሰዎች ደመወዛቸው ዳቦ በሻይ የሚመስለኝ ለዚያ ነው መሰል፡፡ ያኔ በሬዲዮ ተላላኪዎች አገር ለማፍረስ …ምናምን ሲባል ምናይነት አገር ናት በዳቦና በሻይ የምትፈርሰ እያልኩ አስብ
ነበር! እማማ ዣ ምንም እንኳን አፈ ታሪክ ከሚመስል ታሪካቸው ጋር በብቸኝነት ይኑሩ እንጂ፣ ኩራታቸው እና ለራሳቸው ያላቸው ከብር፡ በድፍን መንደሩ የታወቀላቸው ሴት ናቸው።

ሳውቃቸው ጀምሮ ቋሚ ሠራተኛ እንኳን ኖሯቸው አያውቅም። ከበድ ያለ ሥራ
ሲገጥማቸው፣ የቀን ሠራተኛ ቀጥረው ያሠራሉ፣ ዘመድ ጓደኛ የሚባል ነገር እቤታቸው ሲመጣ አላይም። እንደዚያም ሆኖ “ተነሰቶባቸዋልያ ከሚባሉባቸው እና ቤታቸውን ዘጋግተው ከሚቀመጡባቸው ቀናት ዉጭ ትልቁ የግቢያቸው በር ከጧት ጀምሮ እስከ ምሽቱ ሁለት ሰዓት እንዲሁ ከመዘጋት ውጭ ተቆልፎ አያውቅም፡፡ ብዙ ጊዜ እናቴ በራቸውን እንዲቆልፉ ትመክራቸዋለች…

እንዱ ይኼን ወርቅሁን ያየ ሌባ ዘሎ ይገባብኋል ያንዣብ” እያለች፡፡

አይ አንች…ሌባው ገብቶ ከወጣ ወዲያ…” ብለው ንግግራቸውን ሳይጨርስ አንጠልጥለው ይተውታል

ሌላ ጊዜ መኝታ ቤታቸውን እያጠቡ ድክም ብሏቸው፣ እናቴ አገኘቻቸውና “ያንዣብ እንደው አንዲት ልጅ እግር የዘመድም ልጅ ብትሆን ለምን አታስመጡም? …ማነጋገሩም ቢሆን ቀላል ነው እንዴ!?” አለቻቸው፡፡

“ኤዲያ! ..እኔ ያንዣቡ የማንንም መገረናም አምጥቼ እሷን ላንዘፋዝፍ እንዴ? …ጥጋብ አይችሉም ልጄ ..ገና የተረከዛቸው ንቃቃት ሳይገጥም፣ አፋቸውን ይከፍታሉ ..ምን ዘመድ አለ? የጨዋው ልጅ ሁሉ አልቆ!” ብለው በማናናቅ እጃቸውን አወናጨፉት!

ሲያጥቡና ሲያስተካክሉ የሚውሉት ያበሻ ቀሚሳቸው ሲቆጠር አያልቅም፡፡ በወርቃማ ክር የተጠለፈ ጥቁር ካባ ሳይቀር ቁምሳጥናቸው ውስጥ አይቻለሁ፡፡ ሲለብሱት ግን አይቻቸው አላውቅም:: የአንገታቸው የወርቅ ሐብል ከነጉባጉቡ ልብ ያስደነግጣል፡፡
የጆሯቸውን ወርቅ አድርገውት ሲወጡ፣ ጆሮዋቸው ላይ የበቀለ የኮረዳ ጡት ነው
የሚያክለው! በተለይ ጉዳይ ኑሯቸው ወጣ ያሉ ቀን፣ ቀይ ገላቸው ላይ የወርቅ
ጌጣጌጣቸው ለጉድ ይንቦገቦጋል፡፡ ብዙ ጊዜ የሚወጡት የቤት ኪራይ ለመቀበል ነው፡፡አውቶብስ መናኸሪያው አካባቢ የሚከራይ አራት የግንብ ሱቅ አላቸው ይባላል።
መተዳደሪያቸው የሱቆቹ ኪራይ ሳይሆን አይቀርም።

ሀብታም ናቸው፤ ግን ያሳዝኑኛል:: ኩራታቸውና ሥነ-ሥርዓታቸው ቤተ-መንግሥት እንደምትኖር ልዕልት ዓይነት ነበር፡፡ ቢሆኑም ጎዳና ላይ እንደምትኖር አቅመ ቢስ እናት ውስጤ ይንሰፈሰፋል…የሚልስ የሚቀምሰው ያጣ ደሃ እንኳን እንደሳቸው አንጄቴን አይበላውም:: እናቴን ጨምሮ ጎረቤቱ ሁሉ ለዚያች ለሚሰጡኝ ሻይና ዳቦ ስል፣ ከሥር ከሥራቸው የምሮጥ ይመስላቸዋል፡፡ እንደማማ ዣ አይሁን እንጂ እኔም ኩሩ ነኝ፡፡
ማንም ቤት ብሞት ቁራሽ ቀምሸ አላውቅም! “የያንዣቡን ሞሰብ ለምዶ!” ይሉኛል፡፡

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
1
#ሠርጌ

እምቢልታው ይነፋ ከበሮ ይመታ
ይጨፈር ዳንኪራ
ይድመቅ ቤቴ ይድራ
ይምጣ ዘመድ አዝማድ
ይሰብሰብ አጃቢ
በሉኝ ሙሽራዬ የወይን አበባዬ
ብሩህ አርጉት ቀኔን በእልልታ በሆታ
ያኔ ነው ሠርጌ
እኔ የሞትኩ ለታ፡፡
#የሴት_ልጅ

የሴት ልጅ ይለኛል ያዋረደኝ መስሎት
ስድብ እና ሙገሳ መለየት ተስኖት
አው የሴት ልጅ ነኝ ያውም የጀግናዋ
ጉንበስ ቀና ብላ ለልጅዋ ኗሪዋ
ዘጠኝ ወር ሳልከፍል በሆድዋ ተኝቼ
በጀርባዋ አዝላኝ እሰክሄድ በእግሮቼ
ተደፍታ ስታነድ ምግቡን ለማብሰል
እንጀራ ስትጋግር ፊትዋ መስሎ ከሰል
ሳጠፋ ገስፃ እንዳልኩራ መክራ
በርታ እያለችኝ ሁሌም እንዳልፈራ
አይዞህ አልከፋም ሴት ያሳደገኝ ነኝ
ስድብ ከመሰለህ ደጋግመህ ስደበኝ
አልቀየምህም በስምዋ ስትጠራኝ
እውነቱን ልንገርህ አዎ የሴት ልጅ ነኝ

"መታሰቢያነቱ እናቱን ለሚወድ በሙሉ።"

🔘ሎሬት ፀጋዬ ገ/ መድህን🔘
#የሴትነት_ክብር

ከእውነታው ድግስ በሀቅ እንዲታደም
ከሴቶች ቀን በፊት ሴትን ማክበር ይቅደም።

🔘ኢዛና መስፍን🔘
#እማማ_ዣ


#ክፍል_አራት


#በአሌክስ_አብርሃም

ከእኛ ቀይ ወጥ የእማማ "ዣ" ሻይ እና ዳቦ በለጠበት ማለት መሸነፍ መስሏቸው ነው እንጂ፣ እማማ "ዣ" ቤት ከሻይ እና ዳቦ በስተቀር ሌላ ነገር ቀምሸ አላውቅም! ሻይ እና ዳቦ የሌለበት ቤት አለ? ከፈለግ እቤቴ ለማኅበርተኛ ጠላ በሚቀዳበት ማንቆርቆሪያ ሙሉ
አፍልቼ ስጠጣ መዋል እችላለሁ! እውነቴን ነው! እናቴ በሌላ ሌላው ነገር ነጭናጫ ትሁን እንጂ ለሚበላና ለሚጠጣ ነገር፣ እያፈስኩ ብበትነው ግድ የሚሰጣት ሴት አይደለችም። ሻይ በዳቦን ተገን ያደረገ ለራሴም የማይገባኝ ሐዘን ነብሴን በረዥም ክር አስሮ ወደዚያ ግቢ ይስባታል፡፡

እማማ ዣም ይኼን ባህሪዬን ሳያውቁት አይቀሩም፡፡ የሆነ ጊዜ ታመው ማታ አብሪያቸው አምሽቼ ወደ ቤቴ ተመለስኩና፣ በቀጣዩ ቀን በጧት እቤታቸው ሄድኩ …ተጨንቄ ነበር፡፡

“ቁርስ በልተሃል?” አሉኝ፡፡

"እዎ”

ሻይ ላፍላልህ?”

“አይ አልፈልግም…ልጠይቅሁ ነው
የመጣሁት” ትክ ብለው ሲያዩኝ ቆዩና “ይችን ዳቦ እና ሻይ ተገን አርገህ እየመጣህ ባታጫውተኝ ምናባቴ ይውጠኝ ነበር” ብለው ወደ ግቢያቸው አበቦች ዓይናቸውን በትካዜ ላኩ!

እማማ ዣ፣ ለኔ ነፍስ ያላቸው ተረት ነበሩ አንድ ቀን ከትምህርት ቤት ስመለስ፣
አልያም ተኝቼ ስነሳ ቤታቸውም እሳቸውም ብን ብለው ጠፍተው፣ ቤታቸው በነበረበት ቦታ ላይ ከበቀለ ጫካ መሃል፣ አንድ ባለነጭ ጢም ሽማግሌ ብቅ ብሎ “ተረት ነበሩ፣ ሲኖሩ ሲኖሩ… ሞቱ” የሚለኝ ይመስለኛል! ቆየት ብሏል እንጂ እንደዚያ ዓይነት ሕልም አይቻለሁ፡፡ በሰበብ አስባቡ ከቤታቸው አልጠፋም:: እቤት ሲደብረኝ አልያም የእናቴ ጭቅጭቅ ሲያማርረኝ፣ ደብተሬን ሰብስቤ በረንዳቸው ላይ ባለው የቀርቀሃ ወንበር ላይ፣የቤት ሥራየን ሥሰራ እውላለሁ እማማ ዣ አልፎ አልፎ ካልሆነ አያወሩም ብዙ ጊዜ
የሚያሳልፉት ወይ ልብስና ጌጣጌጦቻቸውን ሲያዘጋጁ፣ አልያም ቁጭ ብለው የግቢያቸውን ዙሪያ በመመልከት ነበር፡፡
እናቴ ታዲያ “አንተ ልጅ እዚች ሴትዮ ሥር ሥር እያልክ የተነሳባቸው ቀን፣ ሬሳህ ነው
ከዛ ግቢ የሚወጣው” ትለኛለች፡፡ ቀጠል አርጋ “ ደሞ እንዲህ አለችኝ በልና ከድሮ
ጎረቤቴ አጣላኝ…”

“ምኑ ነው የሚነሳባቸው?” እላታለሁ። ቢገባኝም ቢያንስ እብድ ናቸው መባሉን በመካድ የሰፈሩን ሰው ላለመተባበር! እናቴ ቆጣ ብላ፣

“ወሬ አትውደድ!” ትላለች: እናቴ ማውራት እንጂ ጥያቄ ስትጠየቅ አትወድም፤ በተለይ ጠያቂው እኔ ከሆንኩ።

“እስካሁን አልተነሳባቸውም?” ስላት ትበሳጫለች! ትክ ብላ ታየኝና

“ጅል” ብላኝ ወደ ሥራዋ ትዞራለች ታዲያ እንዲህ ትበል እንጂ እማማ ዣ ጋር ሽርክ
ናቸው እሷም በክፉ በደጉ ከሥራቸው አትጠፋም ሥራ በዝቶባት ሳታያቸው ከዋለች “ጉድ! ይችን ሴትዮ ቀኑን ሙሉ ሳላያቸው… እስቲ ሂድና አይተሃቸው ና!” ትለኛለች ገና ከአፉ ከመውጣቱ ምንጥቅ ብዬ ስነሳ፣

“ለዚህ ሲሉህማ ወፍ አይቀድምህም!” ትላለች: የእናቴ ባሕሪ ግራ ያጋባኛል፡፡ ትንሽ እናትነቷን የተሻሟት እየመሰላት ትቀናለች መሰል?!

#ኩርሲ
እናቴና እማማ ዣ ለአንድ ሳምንት ተኳርፈው፤ እናቴ ራሷ እግራቸው ሥር ወድቃ ይቅርታ ከጠየቀቻቸውና ከታረቁ በኋላ፣ በጥንቃቄ ነበር የምትይዛቸው የፀባቸው መነሻ እስካሁንም እናቴን እየገረማት “ልጅ እኮ ናቸው” ብትልም፣እኔ ግን ወደ እማማ ዣ ያደላ
“ግንኮ እውነት አላቸው” የሚል የማልናገረው ጥብቅና ውስጤ አለ፡፡ ከነገሩ ልክ መሆንና አለመሆን በላይ እማማ ዣ አለመሳሳታቸውን በመደገፍ ከእናቴ “ ልጅኮ ናቸው” ንግግር
ጀርባ ያለውን (ባትናገረውም) ለንክነታቸው እውቅና የሚሰጥ ፈገግታዋን ዋጋ ማሳጣት እፈልጋለሁ! ያን ፈገግታዋን አልወደውም! “የሆነ ቀንማ ልብሳቸውን ጥለው ማበዳቸው
አይቀርም” የሚል ሟርት ይመስለኛል፡፡
ፀቡ እኛ ቤት የመድኃኒያለም ዝክር የተደረገ ቀን ነበር የተፈጠረው፤ ከቅርብና ከሩቅ ያለ ዘመድና ማኅበርተኛ መጥቶ ስለነበር፣ ቤታችን ካፍ እስከገደፉ በሰው ተሞልቶ ነበር ...እማማ ዣ አዲስ የሐበሻ ቀሚሳቸውን ለብሰውና በወርቅ ተንቆጥቁጠው መጡ፡፡ ቤቱን የሞላው ሰው በሙሉ በአክብሮት ተነስቶ ቆመ፡፡ ሁሉም ወንበር ተይዞ ስለነበር እናቴ
ያኘቻትን ኩርሲ እበሩ አጠገብ እያመቻቸች “ እዚህ ያንዣብ.” አለቻቸው፡፡ እማማ "ዣ" አንዴ እናቴን አንዴ ኩርሲውን አየት አደጉና፣

የለ! የለ! …ይንፈስብኝ እውጭ እሆናለሁ” ብለው ወጡ፡፡ እናቴ ዳቦና ጠላ ይዛ
ስትወጣ እማማ ዣ የሉም፡፡ ወደ ቤታቸው ሄደዋል:: ግራ ገብቷት ብቅ ብላ ወደ
ግቢያቸው ብታይ ጭር ብሏል፡፡

“አቡቹ ያንዣብ ወደየት ሄዱ”

“እኔጃ ወደ ቤታቸው ብል ማኅበርተኛው እብድ ሊላቸው አይደል

“ጅል! ….እዚሁ ተገትረህ እኔጃ ትላለህ?!” ብላ ከተነጫነጨች በኋላ ግራ እንደተጋባች ወደ ውስጥ ተመለሰች:: የዚያን ቀን እናቴ እንግዳ ስለበዛባት፣ እኔም ዕቃ ሳነሳሳና የመጣ የሄደው ናስቲ ሳመኝ? ሲለኝ ስለዋለ፣ መንገድ ላይ እያዩኝ የሚያልፉኝ ሁሉ እቤታችን
ድግስ ሲደገስ ካልሳምንህ የሚሉት ነገር ያበሳጨኛል) ...እማማ ዣን የዛን ቀን ሳናያቸው አድረን በነጋታው እቤታቸው ሄድን፡፡ ያው እናቴ ስትሄድ ከኋላ ኋላዋ ተከትያት እንጂ እንሂድ አላለችኝም:: እማማ ዣ በረንዳቸው ላይ ተቀምጠው፣ የጥርስ ብሩሽ ሳሙና እያስነኩ ጉልበታቸው ላይ ከዘረጉት የሐበሻ ቀሚስ ላይ ጠብ ያለ ነገር ሊያስለቅቁ ይፈገፍጋሉ

እናቴ እንደ ወትሮው “ያንዣብ እንዴት አደሩ?” ብትላቸው ጠርዘዝ ብለው፣

ይመስገነው!” አሉና፣ ተቀመጭም ሳይሏት ልብሱን መፈግፈጋቸውን ቀጠሉ: እናቴ ገብቷት ትንሽ ቆመችና፣ እንዴት አደርኩ ልበልሁ ብየ ነው፣ ወደኋላ ብቅ እላለሁ..ያደረ እንግዳ አለብኝ” ብላ ስትወጣ “ አትድከሚ! እንግዶችሽን ሸኝ” ብለው ኮስተር አሉ! እናቴ የግንባሯን ቆዳ ወደ ላይ ሰብሰብ አድርጋ ወደ ቤት ተመለሰች:: አውቃለሁ በውስጧ°ዛሬ ተነስቶባቸዋል" እንደምትል:: ከደቂቃዎች በኋላ አቀርቅረው ሲፈገፍጉ ከቆዩበት ድንገት ቀና ቢሉ፣ እፊታቸው ቆሚያለሁ “እያሱ ድረስ?” ብለው |
ጣሉት:: እኔም በድንጋጤ ደነበርኩ “አቡቹ! ምነው አለሁም አይባል እንዴ? በድንጋጤ ግጥም ብል ምን ትጠቀማለህ ልጄ?” ብለው ደጋግመው አማተቡና፣ ወዲያው ከት ብለው ሳቁ!….

“ና! ቁጭ በል እዚህ! ምን ይገትርሃል አለሁ ይባላል. ወይ ጉሮሮህን እህ እህ .
እንዲያ ነው ደንቡ ክስት ሰይጣን ይመሰል ..ሆሆ አጠገባቸው ሄጀ ረዥሙ
መደገፊያ የቀርቀሃ አግዳሚ ላይ እግሬን አንጠልጥዬ ተቀመጥኩ:: ትንሽ ዝም ብለው ወደ በሩ ሲመለከቱ ቆዩና፣ ልክ የሌላ ሰው እናት እንደሚያሙ ሁሉ፣ እናቴን ያሙልኝ ጀመር

“አየሃት ይችን እናትህን?…አወኩሽ ናኩሽ እኮ ነው…. እኔ ያንዣቡ ጠሪ አክባሪ ብዬ ሄድኩ እንጂ በእንተ ስመ ለማርያም…. ብዬ ቁራሽ ፍለጋ የሄድኩ መሰላት እንዴ. በተከበርኩ በታፈርኩበት መንደር፣ ኩርሲ አንከርፍፋ እንደውሻ በር ሥር ተቀመጭ _
የምትለኝ? ሆሆ (ወደው አይስቁ አሉ! …ጥንት ገረዶቼም ኩርሲ ላይ አልተቀመጡ
እንኳን እኔ ልጅት! ይበለኝ እኔው ነኝ ካለኩያየ ገጥሜ ራሴን ያሰደብኩ!”

ዝም ብዬ ሰማኋቸው… ሥራቸውንም ወሪያቸውንም ቆም አድርገው አየት አደረጉኝና…

“ምን ይለጉምሃል? ከናትህ ጋር አብረህ መስደብህ ነው?” ብለው ተቆጡ! ቁጣቸው ድንገተኛና ምርር ያለ ስለነበር በውስጤ ዛሬ የእናቴ ሟርት መድረሱ ነው!” አልኩ። ከዚህ ቤት ሬሳዬ …”

“ኧረ እኔ .…” ከማለቴ ሳያስጨርሱኝ ….

“ኤዲያ! የቅል ዘሩ አንድ ነው እኔ ያንዣቡ እንኳን አንድ ቋቁቻም፣ አገር ቢያኮርፍ
ምንተዳዬ…
👍3
ጃንሆይ ወደቁ፣ ዙፋኑ ተንኮታኮተ ብሎ፣ ባላባቱ ሁሉ የበላበትን ወጭት እየሰበረ፣ ከዛ መንግሥቱ ከሚባል ጥላቢስ ጋር አብሮ አንዴ ወዛደር አንዴ ላብ አደር እያለ ዘጭ ዘጭ ሲል.. እኔይቱ ልጅት ባደባባይ ደረቴን ነፍቼ “ኃይለሥላሴ ይሙት!” እያልኩ ስምል ነው የኖርኩት:: ብረት ያንጠለጠለ ምንደኛ አብዮት ጠባቂ፣ የጃንሆይን
ስም በሰማ ቁጥር በስመአብ እንዳሉበት ሰይጣን ሲበረግግና ዓይኑን ሲያጉረጠርጥብኝ እንኳ ተርበትብቸ አላቅም… ለምን!?… ጨዋ፣ የጨዋ ልጅ፤ በጨዋነት ያደኩ ነኛ! ጨዋ አይበረግግም

የሰው ልጅ፣ ሞቱ ታፈር መግባቱ አይደለም …. እሱንማ ደሃውም፣ ባሪያውም ቀጣፊውም… ሴት አውሉም ይሞተዋል …የጨዋ ልጅ ሞቱ ክብሩን እንካችሁ ብሎ ሲሰጥነው! ነው ይሁን ግዴለም እንኳን የኔ፣ የአገሪቱም ክብር
በማንም ብጣሻም ተንኮታኩቶ ወድቋል
ንጉሷን የበላች አገር ያንዣቡን ልትምር
ነበር ድሮስ?…. አይ አገር እቴ.…….
በሄደችበት እንደኔ ቢጤ ኩርሲ ላይ አስቀምጠው፣ ስንዴና ዘይት የሚወረውሩላት አዝነው መሰለህ?…ሰጭ ቁራሽ እህል እየሰጠ፣ ሙሉ ክብር ይወስዳል! በደጉ ንጉሥ ዘመንማ በሄዱበት ዙፋኑ ተዘፍኖ፣ ምንጣፉ ተነጥፎ መኳንንትና መሳፍንቱ ጎንበስ
ቀና ጠብ እርግፍ ብሎ ነበር የሚቀበላቸውን ያ ሁሉ ሽር ጉድ ለአንድ ተፈሪ እንዳይመስልህ፤ ተፈሪማ ምኑ? እንዲሁ እንደኔ ሥጋና ደም ነው…ላገር ነበር ክብሩ… ንጉሥ ራስ ነው ሁሉም በደረጃው በመዓረጉ ሲሆን ያምራል... ንፍሮ ነው ተቀላቅሎ የሚቀቀል የነፈረ ዘመን ! ብለው ለረዥም ጊዜ ዝም ብለው ቆዩና

“አቡቹ” አሉኝ።

“እ!”

“ባሪያ ይመስል ባፍንጫህ አታልጎምጉም… አቤት በል በወጉ!”

“አቤት”

እንደሱ ነው …ቁርስ በልተሃል?”

አይይይ ..” ቦርሳቸውን ያኖሩበት ጠፍቷቸው ዙሪያቸውን ሲፈልጉ ቆዩና፣ድንገት ትዝ ሲላቸው የቀሚሳቸውን አንገት ጎትተው ከጡታቸው መሃል ትንሿን የብር መያዣ ቦርሳ መዘው አወጡ…አዳዲስ ሁለት ብሮች ለይተው

ሂድ ዳቦ ገዝተህ ና” አሉኝ:: ወደ ዘመናይ ሱቅ በረርኩ፡፡

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
👍3