#ልጩህበት!!
:
:
#ክፍል_ሀያ
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
በዚህ ሁኔታ ብዙ ታገልኩ ዛሬ ግን አልቻልኩም!
ለሊቱን ሙሉ በህልሜ ሳያት ስላደርኩ ነው መሰለኝ ናፍቆቴ ልኩን አለፈ ባላገኛት እንኳን ወደዛ አጥር ወደሌለው ዩንቨርስቲያቸው ሄጄ ከሩቁ አይቻት ልመለስ ሄድኩ።
ደርሼ አምስት ደቂቃ ያክል እንኳን ሳልቆም ከሩቅ ኤዱን አየኋት !
ግን ብቻዋን አልነበረችም ከልጁ ጋር ነች ውስጤ ሲፈነቃቀል ታወቀኝ እዛው በቆምኩበት
ጩህ ጩህ ስሟን ከፍ አድርገህ ጥራት ጥራት አለኝ••
ግን አልጮሆኩም ዝም ብዬ ፈዝዤ ስመለከታቸው ሁለት የማላውቃቸው ሴቶች መጥተው ተቀላቀሏቸው ወድያው ልጁ ሁለቱን እጃቸውን ጨብጦ ትከሻቸውን በመግጨት ኤዱን ግን ጉንጯን በመሳም ተሰናበታቸውና በርምጃ ከግቢው መውጣት ጀመረ ውስጤ በልጁ እና በኤዱ መካከል የሆነ ነገር እንዳለ እርግጠኛ ሆነ መሰለኝ ፍርሀት ፍርሀት ሲለው ታወቀኝ።
የቆመ ባጃጅ ውስጥ ገብቶ ሲሄድ ተከተልኩት።
ከዚራ አከባቢ ሲደርስ ወርዶ የሆነ ካፍቴርያ ውስጥ ገባ ።
ትንሽ ቆየት አልኩና እዛ ካፍቴሪያ ውስጥ ድንገት እንደተከሰተ ሰው መስዬ ገባሁ ።
ልጁና አንዲት የምታምር ሴት ጎን ለጎን ተቀምጠው ጭማቂ በስትሮ እየማጉ ያወራሉ።
ክው አልኩ እሄ ልጅ ኤዱን እያጃጃላት ባልሆነ እቺ ደሞ ማነች እያልኩ በውስጤ ፈንጠር አልኩና ጀርባዬን ሰጥቻቸው ተቀመጥኩ። ስልኬን አውጥቼ ለኤዱ ደወልኩላት•••
"ወዬ የዘጋከኝ ወንድሜ!" አለች እየሳቀኝ እቺ ልጅ ደግሞ እሄ ወንድሜ እምትለውን ነገር አፏ ላይ ነው እንዴ ያተሙባት እያልኩ ለራሴ የት እንደሆነች ጠየኳት ግቢ ከጓደኛቿ ጋር መሆኗን እንደነገረችኝ
ጓደኛሽ ደና ነው? ስላት ደህና መሆኑን ነግሯት ዛሬ እሚገርም ኳስ አለ ብሏት እኛ ሰፈር ወዳለው ድሬ ዳዋ እስታዲየም ኳስ ሊመለከት መሄዱን አከለችበት"
ተሰናብቻት ስልኩን ዘጋሁትና ። ኳስ ሜዳው ካፌ ኳሷ ደሞ ልጅቷ እንዳትሆን ብቻ አልኩና ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ወደ ልጅ በመሄድ ድንገት እንዳየሁት ሆኜ ሰላምታ ተለዋውጠን ፍቃደኛ ከሆነ አንድ ግዜ ለ አምስት ደቂቃ ላናግረው እንደምፈልግ ስነግረው ፍቃደኛ ቢሆንም ከኤዱ ጋር ምን አይነት ግኑኝነት እንዳላቸው ስጠይቀው
በጣም በሚያስጠላ ሁኔታ ምን አገባህ የሚል ስሜት ባዘለ መልኩ መልስ ሊሰጠኝ ሲሞክር አቋርጬው ቤተሰቦቿ እንዴት ሆነው እንዳስተማሯት ስለነገረችኝ እንዳትሰናከል በማሰብ እንጂ እሱ እንዳለው እንደማያገባኝና ያንንም ጠንቅቄ እንደማውቅ ነግሬው መልስ ሳይሰጠኝ በቆመበት ጥዬው ሄድኩ።
እንዲሁ እንደተወዛገብኩ ቀን ቀኖችን ቀኖች ሳምንትን ሳምንት ወርን ወሮች አመትን እያስከተሉ ነጎዱ እነኤዱም ሁለት አመት ተምረው የመጨረሻውን አንድ አመት መማር ከጀመሩ አንድ ወር ሆናቸው።
ያሁኖቹን ባላውቃቸውም መጀመርያ ላይ ጓደኛቿ ከነበሩት ትግስት ከመሲ ጋር አብሯ ስታብድ ትምህርቷን በአግባቡ ስላልተከታተለች እስከመጨረሻው ላትመለስ ከትምህርት ቤቱ ተባራ እዚሁ ድሬ ዳዋ ልዩ ስሙ ነምበር ዋን በመባል ወደ ሚታወቀው አከባቢ አንድ ሆቴል ውስጥ በአስተናጋጅነት ስትቀጠር ረድኤት ደሞ ለአንድ አመት ተቀጥታ ወደ ቤተሰቦቿ መሄዷን ነግራኛለች ።
ኤዱ ግን ልትመረቅ ወራቶች ብቻ ቀርተዋታል ልትመረቅ መሆኑን ባሰብኩ ቁጥር ጭንቀቴ ይጨምራል ስጨነቅ እንቅልፍ አጣለሁ ከጭንቀቴ ለመደበቅ እንቅልፍ ለመተኛት ስል ማታ ማታ ቋሚ ጠጪ ከሆንኩ ቆየሁ።
ሁሌም የምጠጣው ለመጀመሪያ ግዜ ኤዱን በሩ ላይ ቆማ ያየኋት ጭፈራ ቤት ውስጥ ነው ።
ወደ ውስጥ ከመግባቴ በፊት የቆመችባትን ቦታ ቆም ብዬ አያለሁ ኤዱ ግን የለችም ጠጥቼ ስወጣ ግን ወደዛ ከተመለከትኩ ቆማ ትታየኛለች እራሴንም እሷንም እየተሳደብኩ ወደ ቤት እንደምገባ ብዙ ግዜ ዳኒ ነግሮኛል ዛሬም እዛው እየጠጣሁ ነው።
በግዜ ስለገባሁ ሙዚቃው በስሱ ነው የተከፈተው ነገር ግን ከኔ በሁለት እርምጃ ርቀት እንደኔው ብቻውን የሚጠጣው ሰው ሰላሜን አሳጣኝ በሱ ምክንያት እራሴን ማዳመጥ አልቻልኩም ሰውየው አስተናጋጇን ያለ ምንም ምክንያት ይሰድባታል።
እሱ በሰደባት ቁጥር እኔ እናደዳለሁ።
የማይሆን ጥያቄ ይጠይቃትና መልስ አልሰጥ ስትለው ይሰድባታል •••
"ቆይ እሄ ቂጥሽ ሀይ ኮፒ ነው ኦርጅናል? ንገሪኝ ሀይ ኮፒ ነው ? ሳላረጋግጥ እማ ወይ ፍንክች "
ይላል እሚፈነክት ይፈንክተውና ምን ማረጋገጥ እንደፈለገ ሳስበው ደሞ ሳቄ ይመጣል ።
ትንሽ ቆይቶ ያጨበጭብና ሌላ ይዛለት እንድትመጣ ያዛል። ልክ እንዳመጣችለት ሊነካት እየሞከረ•••
" እንዴ ንገሪኛ እኛ ሀይኮፒም ዩዝድም ባንድ ላይ ጉዳት ነው ንገሪኛ በናትሽ !"
ሲል ልጅቷ ተበሳጭታ መልስ ስለሰጠችው ብድግ አለ ሊመታት ያኔ የኔም ንዴት ገነፈለና ተንደርድሬ በጥፊ ከመሬቱ ጋር አላትሜ አርፎ እንዲጠጣ አስጠነቅቄው ወደ ቦታዬ ተመለስኩ ።
ሰውየው መለፍለፉን አላቆመም ወይ እሱ ወይ እኔ ከዛ ቤት ካልወጣን ዝም እንደማይል ስለገባኝ ተነስቼ ወጣሁና ግማሽ ኪሎ ሜትር አከባቢ በግሬ ተጉዤ " ጨለማው ቤት" በመባል ወደ ሚታወቀው ሆቴል ገባሁ።
ብዙ ግዜ ጥንዶች የሚዝናኑበት ሆቴል ቢሆንም እኔ ብቻዬን ቁጭ ብዬ ስጠጣ ሁለት ቢራ ጨርሼ ሶስተኛውን እንዳገባደድኩ ከፊት ለፊቴ በቅርብ ርቀት ከተቀመጡት ሶስት ሰዎች መካከል ድንገት ቦግ ብሎ በበራው የሞባይል መብራት የመሀለኛዋን እየኋት•••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
:
:
#ክፍል_ሀያ
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
በዚህ ሁኔታ ብዙ ታገልኩ ዛሬ ግን አልቻልኩም!
ለሊቱን ሙሉ በህልሜ ሳያት ስላደርኩ ነው መሰለኝ ናፍቆቴ ልኩን አለፈ ባላገኛት እንኳን ወደዛ አጥር ወደሌለው ዩንቨርስቲያቸው ሄጄ ከሩቁ አይቻት ልመለስ ሄድኩ።
ደርሼ አምስት ደቂቃ ያክል እንኳን ሳልቆም ከሩቅ ኤዱን አየኋት !
ግን ብቻዋን አልነበረችም ከልጁ ጋር ነች ውስጤ ሲፈነቃቀል ታወቀኝ እዛው በቆምኩበት
ጩህ ጩህ ስሟን ከፍ አድርገህ ጥራት ጥራት አለኝ••
ግን አልጮሆኩም ዝም ብዬ ፈዝዤ ስመለከታቸው ሁለት የማላውቃቸው ሴቶች መጥተው ተቀላቀሏቸው ወድያው ልጁ ሁለቱን እጃቸውን ጨብጦ ትከሻቸውን በመግጨት ኤዱን ግን ጉንጯን በመሳም ተሰናበታቸውና በርምጃ ከግቢው መውጣት ጀመረ ውስጤ በልጁ እና በኤዱ መካከል የሆነ ነገር እንዳለ እርግጠኛ ሆነ መሰለኝ ፍርሀት ፍርሀት ሲለው ታወቀኝ።
የቆመ ባጃጅ ውስጥ ገብቶ ሲሄድ ተከተልኩት።
ከዚራ አከባቢ ሲደርስ ወርዶ የሆነ ካፍቴርያ ውስጥ ገባ ።
ትንሽ ቆየት አልኩና እዛ ካፍቴሪያ ውስጥ ድንገት እንደተከሰተ ሰው መስዬ ገባሁ ።
ልጁና አንዲት የምታምር ሴት ጎን ለጎን ተቀምጠው ጭማቂ በስትሮ እየማጉ ያወራሉ።
ክው አልኩ እሄ ልጅ ኤዱን እያጃጃላት ባልሆነ እቺ ደሞ ማነች እያልኩ በውስጤ ፈንጠር አልኩና ጀርባዬን ሰጥቻቸው ተቀመጥኩ። ስልኬን አውጥቼ ለኤዱ ደወልኩላት•••
"ወዬ የዘጋከኝ ወንድሜ!" አለች እየሳቀኝ እቺ ልጅ ደግሞ እሄ ወንድሜ እምትለውን ነገር አፏ ላይ ነው እንዴ ያተሙባት እያልኩ ለራሴ የት እንደሆነች ጠየኳት ግቢ ከጓደኛቿ ጋር መሆኗን እንደነገረችኝ
ጓደኛሽ ደና ነው? ስላት ደህና መሆኑን ነግሯት ዛሬ እሚገርም ኳስ አለ ብሏት እኛ ሰፈር ወዳለው ድሬ ዳዋ እስታዲየም ኳስ ሊመለከት መሄዱን አከለችበት"
ተሰናብቻት ስልኩን ዘጋሁትና ። ኳስ ሜዳው ካፌ ኳሷ ደሞ ልጅቷ እንዳትሆን ብቻ አልኩና ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ወደ ልጅ በመሄድ ድንገት እንዳየሁት ሆኜ ሰላምታ ተለዋውጠን ፍቃደኛ ከሆነ አንድ ግዜ ለ አምስት ደቂቃ ላናግረው እንደምፈልግ ስነግረው ፍቃደኛ ቢሆንም ከኤዱ ጋር ምን አይነት ግኑኝነት እንዳላቸው ስጠይቀው
በጣም በሚያስጠላ ሁኔታ ምን አገባህ የሚል ስሜት ባዘለ መልኩ መልስ ሊሰጠኝ ሲሞክር አቋርጬው ቤተሰቦቿ እንዴት ሆነው እንዳስተማሯት ስለነገረችኝ እንዳትሰናከል በማሰብ እንጂ እሱ እንዳለው እንደማያገባኝና ያንንም ጠንቅቄ እንደማውቅ ነግሬው መልስ ሳይሰጠኝ በቆመበት ጥዬው ሄድኩ።
እንዲሁ እንደተወዛገብኩ ቀን ቀኖችን ቀኖች ሳምንትን ሳምንት ወርን ወሮች አመትን እያስከተሉ ነጎዱ እነኤዱም ሁለት አመት ተምረው የመጨረሻውን አንድ አመት መማር ከጀመሩ አንድ ወር ሆናቸው።
ያሁኖቹን ባላውቃቸውም መጀመርያ ላይ ጓደኛቿ ከነበሩት ትግስት ከመሲ ጋር አብሯ ስታብድ ትምህርቷን በአግባቡ ስላልተከታተለች እስከመጨረሻው ላትመለስ ከትምህርት ቤቱ ተባራ እዚሁ ድሬ ዳዋ ልዩ ስሙ ነምበር ዋን በመባል ወደ ሚታወቀው አከባቢ አንድ ሆቴል ውስጥ በአስተናጋጅነት ስትቀጠር ረድኤት ደሞ ለአንድ አመት ተቀጥታ ወደ ቤተሰቦቿ መሄዷን ነግራኛለች ።
ኤዱ ግን ልትመረቅ ወራቶች ብቻ ቀርተዋታል ልትመረቅ መሆኑን ባሰብኩ ቁጥር ጭንቀቴ ይጨምራል ስጨነቅ እንቅልፍ አጣለሁ ከጭንቀቴ ለመደበቅ እንቅልፍ ለመተኛት ስል ማታ ማታ ቋሚ ጠጪ ከሆንኩ ቆየሁ።
ሁሌም የምጠጣው ለመጀመሪያ ግዜ ኤዱን በሩ ላይ ቆማ ያየኋት ጭፈራ ቤት ውስጥ ነው ።
ወደ ውስጥ ከመግባቴ በፊት የቆመችባትን ቦታ ቆም ብዬ አያለሁ ኤዱ ግን የለችም ጠጥቼ ስወጣ ግን ወደዛ ከተመለከትኩ ቆማ ትታየኛለች እራሴንም እሷንም እየተሳደብኩ ወደ ቤት እንደምገባ ብዙ ግዜ ዳኒ ነግሮኛል ዛሬም እዛው እየጠጣሁ ነው።
በግዜ ስለገባሁ ሙዚቃው በስሱ ነው የተከፈተው ነገር ግን ከኔ በሁለት እርምጃ ርቀት እንደኔው ብቻውን የሚጠጣው ሰው ሰላሜን አሳጣኝ በሱ ምክንያት እራሴን ማዳመጥ አልቻልኩም ሰውየው አስተናጋጇን ያለ ምንም ምክንያት ይሰድባታል።
እሱ በሰደባት ቁጥር እኔ እናደዳለሁ።
የማይሆን ጥያቄ ይጠይቃትና መልስ አልሰጥ ስትለው ይሰድባታል •••
"ቆይ እሄ ቂጥሽ ሀይ ኮፒ ነው ኦርጅናል? ንገሪኝ ሀይ ኮፒ ነው ? ሳላረጋግጥ እማ ወይ ፍንክች "
ይላል እሚፈነክት ይፈንክተውና ምን ማረጋገጥ እንደፈለገ ሳስበው ደሞ ሳቄ ይመጣል ።
ትንሽ ቆይቶ ያጨበጭብና ሌላ ይዛለት እንድትመጣ ያዛል። ልክ እንዳመጣችለት ሊነካት እየሞከረ•••
" እንዴ ንገሪኛ እኛ ሀይኮፒም ዩዝድም ባንድ ላይ ጉዳት ነው ንገሪኛ በናትሽ !"
ሲል ልጅቷ ተበሳጭታ መልስ ስለሰጠችው ብድግ አለ ሊመታት ያኔ የኔም ንዴት ገነፈለና ተንደርድሬ በጥፊ ከመሬቱ ጋር አላትሜ አርፎ እንዲጠጣ አስጠነቅቄው ወደ ቦታዬ ተመለስኩ ።
ሰውየው መለፍለፉን አላቆመም ወይ እሱ ወይ እኔ ከዛ ቤት ካልወጣን ዝም እንደማይል ስለገባኝ ተነስቼ ወጣሁና ግማሽ ኪሎ ሜትር አከባቢ በግሬ ተጉዤ " ጨለማው ቤት" በመባል ወደ ሚታወቀው ሆቴል ገባሁ።
ብዙ ግዜ ጥንዶች የሚዝናኑበት ሆቴል ቢሆንም እኔ ብቻዬን ቁጭ ብዬ ስጠጣ ሁለት ቢራ ጨርሼ ሶስተኛውን እንዳገባደድኩ ከፊት ለፊቴ በቅርብ ርቀት ከተቀመጡት ሶስት ሰዎች መካከል ድንገት ቦግ ብሎ በበራው የሞባይል መብራት የመሀለኛዋን እየኋት•••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍2
#ልጩህበት!!
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ሰውየው መለፍለፉን አላቆመም ወይ እሱ ወይ እኔ ከዛ ቤት ካልወጣን ዝም እንደማይል ስለገባኝ ተነስቼ ወጣሁና ግማሽ ኪሎ ሜትር አከባቢ በግሬ ተጉዤ " ጨለማው ቤት" በመባል ወደ ሚታወቀው ሆቴል ገባሁ።
ብዙ ግዜ ጥንዶች የሚዝናኑበት ሆቴል ቢሆንም እኔ ብቻዬን ቁጭ ብዬ ስጠጣ ሁለት ቢራ ጨርሼ ሶስተኛውን እንዳገባደድኩ ከፊት ለፊቴ በቅርብ ርቀት ከተቀመጡት ሶስት ሰዎች መካከል ድንገት ቦግ ብሎ በበራው የሞባይል መብራት የመሀለኛዋን እየኋት•••
ያቺን እርኩስ አየኋት እስከዛሬ ሳያት ከሚሰማኝ የንዴት ስሜት በተለየ ሁኔታ ጠላቴ መስላ ታየችኝ የግቢ ሴቶች ላይ ብቻ ሳይሆን እኔ ሂወት ላይም የተጫወተች መስሎ ተሰማኝ።
አዎ እሷ ነች ለኔ እና ለኤዱ መተዋወቅ ምክንያት ሆና እዚህ የማልወጣው የፍቅር ገደል ውስጥ ወድቄ የመንፈስ ስብራት እንዲያጋጥመኝ የሞራል የደስታ ባጠቃላይ የኑሮ ጣእምና ለዛዋ ሁሉ እንዲጠፋብኝ ቀንደኛዋ ተዋናይ እሷ ነች ብዬ አሰብኩኝ ።
አዋ! እሷ ነች ያን ቀን ኤዱን አታላ ለዛ ፀያፍ ስራዋ አመቻችታ ይዛት ባትወጣ ኖሮ እኔና ኤዱ ባልተዋወቅን ባላየኋት ባላየችኝ እህቴ ብዬ ስቀርባት ዉንድሟ አርጋኝ ባላረፈችው ነበር
እሷ እስከዛሬም እንደወንድሟ እያየችኝ የኔ ግን ምን እንደገለበጠው ባይገባኝም ወደማላውቀውና ለኔ አዲስ ወደሆነ ከባድ የፍቅር ስሜት ተገልብጦ እንዲህ ቀንና ለሊቱ ባልተገለባበጠብኝ ነበር።
አንዳንዴ ኧረ የምን አንዳንዴ ሁሌም ቢሆን በተለይ ከራሴ ጋር የሚያላትመኝ ፍቅር ከያዘኝ ወዲህ ምነው ባላወኳት እላለሁ ።
ደሞ መልሼ በተለይ ከተዋወቅን ጀምሮ በቃሌ መሰረት እንዳትሳቀቅ በማሰብ ያሰፈልገኛል ብላ ጠየቀችኝም አልጠየቀችኝም በየወሩ አቅሜ የፈቀደውን ያህል በባንክ አካውንቷ ሳስገባላት ወድያው ትደውልና•••
"በመጀመሪያ አንተን ሳይሆን ከናት እና አባቴ ባትወለድም አንተን የመሰለ ወንድም በስጦታ የሰጠኝ ፈጣዬን ሁሌም አመሰግናለሁ በመቀጠል ደሞ አንተንም እመሰግናለሁ እሺ ወንድሜ "
የምትለኝ ሁሌም የማይቀየር ንግግሯ
ሀሳቤን ያስቀይረኝና መተዋወቃችንን ሳይሆን ማፍቀሬን በመኮነን ከራሴ ጋር እጣላለሁ
ሆነም ቀረ ከብዙ ግዜ ቡሀላ ያጋጠመችኝን አሁን ከፊቴ ሶስት ደረጃ ከፍ ብላ ከአንድ ክልስ ከሚመስል ሰውና ከሌላ አዲስ እንቡጥ ሴት ጋር ተቀምጣ የምታስካካውን መሲን በጭራሽ እንደማላልፋት ወሰንኩ!
ሞባይሌን አወጣሁ!
በሁለተኛው ሲም ካርድ ስም ቀይሬ በከፈትኩት ቴሌግራም•••
ካሁን ቡሀላ የግቢ ሴቶችን እያወጣሽ እንደእቃ ስትቸረችሪ ቢያጋጥመኝ ወይ ብሰማ እሄን ጉድሽን በሁሉም ማህበራዊ ሚድያ ለቅቄ መደበቂያ እንደማሳጣሽ እወቂ!
አሁንም አብራሽ ያለችውን ልጅ ቶሎ ወደ ግቢ መልሻት ከሚል አጭር ትእዛዝ ጋር ያ ሰውዬ የላከልኝን የራሷን ቪድዮ ወደ ቴሌግራም አካውንቷ ላኩላትና ወድያው ሞባይሌን ኪሴ ከትቼ እምትሆነውን መጠባበቅ ጀመርኩ።
የቴሌግራም ማሳወቂያውን (notification) አጥፍታዋለች መሰለኝ አዲስ መልክት እንዳላት ስላልነገራት ጭራሽ ሞባይሏን ከፍታ ሳታየው ቆየች።
ስልኳ ላይ መልክት መላክ ግድ ሆነብኝ ቴሌግራም አካውንትሽ ላይ መልክት አለሽ ገብተሽ ተመልከችው ብዬ ላኩ።
ወድያው ሞባይሏ ብልጭ ብሎ ድርግም ሲል አየሁት።
ከፍታ እየተመለከተችው ነው
ቪድዮውን አይታው ነው መሰለኝ በርግጋ ከመቀመጫዋ ተነሳች ፀጉሯን እንደመንጨት እያደረጋት ቪድዮውን የላከልሽ ሰው ውጪ በር ላይ ነው ያሏት ይመስል ያደረገችው ተረከዘ ረጅም ጫማ መሆኑን ረስታ እየተውረገረገች በፍጥነት ደረጃውን ለመውረድ ስትሞክር ባየር ላይ ተበረጋግዳ መሬት ተሰጣች ።
ፈገግ አልኩ አናቴ ላይ ያለውን ኮፍያ ዝቅ እያደረኩ።
ሁሉም ተደነጋግጦ ወደሷ ሲሮጥ ለቅሶ በተናነቀው ድምፅ
"ምንም አልሆንኩም እንዳትጠጉኝ!" ብላ በእልህ ተነሳችና የተጎዳ እግሯን እየጎተተች እና እስከባቷ የተሰነጠቀውን ሮዝ የራት ልብሷን ለማራገፍ እየሞከረች በደመነፍስ የሆቴሉ የውጪ በር ላይ ደረሳ ወደላይና ወደ ታች እየተገላመጠች የጠረጠረችውን ሰው መፈለግ ጀመረች።
ምንም ማየት ባለመቻሏ ተስፋ ቆረጠች ያኔ ስትወድቅ የተመታችበት ቦታ ህመመ ተሰማት ጎኗ አከባቢ ይዛ እያቃሰተች መቆም ስላቃታት ቁጭ ብላ ማልቀስ ጀመረች።
ሰውየውና አብራት የነበረችው ልጅ አጠገቧ እንደደረሱ ልጅቷ በጣም ተጨንቃ ዝቅ ብላ ልታናግራት ልታባብላት በምትሞክርበት ሰአት መሲ ተቀየረችባት•••
"ዞወር በይልኝ ወደዛ ያንቺ ገዳፋ ነው እሄ ሁሉ መጀመሪያም ምንሽም አልጣመኝም ነበር ካሁን ቡሀላ ላይሽ አልፈልግም አሁኑኑ ባጃጅ ያዢና ቀጥ ብለሽ ወደ ግቢ ሂጂ !" በማለት ስታምባርቅባት ልጅቷ ሽምቅቅ ብላ ዘወር አለች ሄደች ወደግቢ ።
"ጎበዝ መሲ ትዛዝ ታከብሪያለሽ ማለት ነው!" ብዬ መልክት ላኩላትና ስልኬን አጥፍቼ ኪሴ ውስጥ ከተትኩ እሄን ግዜ እንደ እብድ አደረጋት መልክቱ እየደረሳት ያለው እዛው ሆቴል ውስጥ እየተዝናና ካለ በቅርብ ርቀት ከሚያያት ሰው መሆኑን እርግጠኛ ሆነች ።
እንደምንም ተነስታ ስልክ መደወል ጀመረች ወደኔ እምትሞክር መስሎኝ ነበር ጎረምሶቿን እየጠራች እንደሆነ የገባኝ ሶስት
ክብደት ገፊ ፣ደረተ ሰፋፊ ፣ ባስተሳሰብ ደሞ ቀፋፊ የሆኑ በጭንቅላታቸው ሳይሆን በተከመረው ጡንቻቸው የሚያስቡ ወጣቶች ከመቅስፈት ደርሰው መሲን በመክበብ ምን እንደፈጠረ ሲጠይቋት እንደተመለከትኩ ነው ።
በመሲ ጥሪ በዛ ፍጥነት ሰው ሊደበድቡ መምጣታቸውን ሳስበው ለህሊናቸው ሳይሆን ለሆዳቸው የሚኖሩ አሳሞች መስለው ታዩኝ
መሲ ማነች ? ምንድን ነች? ስራዋ ምንድን ነው ማንን ነው የምታስደበድበን ? ለምን?
አያገባቸውም ብቻ ትክፈላቸው እንጂ እንደ እንስሳ ወደፈለገችበት ትነዳቸዋለች ። ገልቱዎች ።
ዘበኛውን ሰው እንዳይወጣ አስጠነቀቁትና
መሀላቸው አድርገዋት ግቢ ውስጥ መዟዟር ጀመሩ ብዙ ሰው የለም ያሉትም ጥንድ ጥንድ ሆነው ነው የተቀመጡት ብቻዬን ቁጭ ያልኩት እኔ ብቻ ነኝ ።
ደረታቸውን ገልብጠው እየተሽከረከሩ የሚዝናኑትን ሰዎች ምን እንደሚሏቸው ባላውቅም አንዳንዶቹን ጠጋ ብለው እያናገሩ ያንዳንዶቹን ሞባይላቸውን ተቀብለው እየመለሱላቸው እኔ ወዳለሁበት ቦታ መጠጋት ጀመሩ።
ሂሳብ ዘጋሁ።
እነዚህን ዱባ ጭንቅላቶች ፈርቼ ሳይሆን የሰው ሆቴል ውስጥ ብጥብጥ ተፈጥሮ ላለመታሰር ስል ተነስቼ ወደ መውጫው በር ስጠጋ•••
" እንዳታስወጣው! ጥበቃ እንዳታስወጣው !"
የሚለው የመሲ ጩኸት ጆሮዬ ላይ አንቃጨለብኝ ዘወር ስል እሷ ከጀርባቸው ቆማ ሶስቱም ወደኔ ሲመጡ እየኋቸው•••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ሰውየው መለፍለፉን አላቆመም ወይ እሱ ወይ እኔ ከዛ ቤት ካልወጣን ዝም እንደማይል ስለገባኝ ተነስቼ ወጣሁና ግማሽ ኪሎ ሜትር አከባቢ በግሬ ተጉዤ " ጨለማው ቤት" በመባል ወደ ሚታወቀው ሆቴል ገባሁ።
ብዙ ግዜ ጥንዶች የሚዝናኑበት ሆቴል ቢሆንም እኔ ብቻዬን ቁጭ ብዬ ስጠጣ ሁለት ቢራ ጨርሼ ሶስተኛውን እንዳገባደድኩ ከፊት ለፊቴ በቅርብ ርቀት ከተቀመጡት ሶስት ሰዎች መካከል ድንገት ቦግ ብሎ በበራው የሞባይል መብራት የመሀለኛዋን እየኋት•••
ያቺን እርኩስ አየኋት እስከዛሬ ሳያት ከሚሰማኝ የንዴት ስሜት በተለየ ሁኔታ ጠላቴ መስላ ታየችኝ የግቢ ሴቶች ላይ ብቻ ሳይሆን እኔ ሂወት ላይም የተጫወተች መስሎ ተሰማኝ።
አዎ እሷ ነች ለኔ እና ለኤዱ መተዋወቅ ምክንያት ሆና እዚህ የማልወጣው የፍቅር ገደል ውስጥ ወድቄ የመንፈስ ስብራት እንዲያጋጥመኝ የሞራል የደስታ ባጠቃላይ የኑሮ ጣእምና ለዛዋ ሁሉ እንዲጠፋብኝ ቀንደኛዋ ተዋናይ እሷ ነች ብዬ አሰብኩኝ ።
አዋ! እሷ ነች ያን ቀን ኤዱን አታላ ለዛ ፀያፍ ስራዋ አመቻችታ ይዛት ባትወጣ ኖሮ እኔና ኤዱ ባልተዋወቅን ባላየኋት ባላየችኝ እህቴ ብዬ ስቀርባት ዉንድሟ አርጋኝ ባላረፈችው ነበር
እሷ እስከዛሬም እንደወንድሟ እያየችኝ የኔ ግን ምን እንደገለበጠው ባይገባኝም ወደማላውቀውና ለኔ አዲስ ወደሆነ ከባድ የፍቅር ስሜት ተገልብጦ እንዲህ ቀንና ለሊቱ ባልተገለባበጠብኝ ነበር።
አንዳንዴ ኧረ የምን አንዳንዴ ሁሌም ቢሆን በተለይ ከራሴ ጋር የሚያላትመኝ ፍቅር ከያዘኝ ወዲህ ምነው ባላወኳት እላለሁ ።
ደሞ መልሼ በተለይ ከተዋወቅን ጀምሮ በቃሌ መሰረት እንዳትሳቀቅ በማሰብ ያሰፈልገኛል ብላ ጠየቀችኝም አልጠየቀችኝም በየወሩ አቅሜ የፈቀደውን ያህል በባንክ አካውንቷ ሳስገባላት ወድያው ትደውልና•••
"በመጀመሪያ አንተን ሳይሆን ከናት እና አባቴ ባትወለድም አንተን የመሰለ ወንድም በስጦታ የሰጠኝ ፈጣዬን ሁሌም አመሰግናለሁ በመቀጠል ደሞ አንተንም እመሰግናለሁ እሺ ወንድሜ "
የምትለኝ ሁሌም የማይቀየር ንግግሯ
ሀሳቤን ያስቀይረኝና መተዋወቃችንን ሳይሆን ማፍቀሬን በመኮነን ከራሴ ጋር እጣላለሁ
ሆነም ቀረ ከብዙ ግዜ ቡሀላ ያጋጠመችኝን አሁን ከፊቴ ሶስት ደረጃ ከፍ ብላ ከአንድ ክልስ ከሚመስል ሰውና ከሌላ አዲስ እንቡጥ ሴት ጋር ተቀምጣ የምታስካካውን መሲን በጭራሽ እንደማላልፋት ወሰንኩ!
ሞባይሌን አወጣሁ!
በሁለተኛው ሲም ካርድ ስም ቀይሬ በከፈትኩት ቴሌግራም•••
ካሁን ቡሀላ የግቢ ሴቶችን እያወጣሽ እንደእቃ ስትቸረችሪ ቢያጋጥመኝ ወይ ብሰማ እሄን ጉድሽን በሁሉም ማህበራዊ ሚድያ ለቅቄ መደበቂያ እንደማሳጣሽ እወቂ!
አሁንም አብራሽ ያለችውን ልጅ ቶሎ ወደ ግቢ መልሻት ከሚል አጭር ትእዛዝ ጋር ያ ሰውዬ የላከልኝን የራሷን ቪድዮ ወደ ቴሌግራም አካውንቷ ላኩላትና ወድያው ሞባይሌን ኪሴ ከትቼ እምትሆነውን መጠባበቅ ጀመርኩ።
የቴሌግራም ማሳወቂያውን (notification) አጥፍታዋለች መሰለኝ አዲስ መልክት እንዳላት ስላልነገራት ጭራሽ ሞባይሏን ከፍታ ሳታየው ቆየች።
ስልኳ ላይ መልክት መላክ ግድ ሆነብኝ ቴሌግራም አካውንትሽ ላይ መልክት አለሽ ገብተሽ ተመልከችው ብዬ ላኩ።
ወድያው ሞባይሏ ብልጭ ብሎ ድርግም ሲል አየሁት።
ከፍታ እየተመለከተችው ነው
ቪድዮውን አይታው ነው መሰለኝ በርግጋ ከመቀመጫዋ ተነሳች ፀጉሯን እንደመንጨት እያደረጋት ቪድዮውን የላከልሽ ሰው ውጪ በር ላይ ነው ያሏት ይመስል ያደረገችው ተረከዘ ረጅም ጫማ መሆኑን ረስታ እየተውረገረገች በፍጥነት ደረጃውን ለመውረድ ስትሞክር ባየር ላይ ተበረጋግዳ መሬት ተሰጣች ።
ፈገግ አልኩ አናቴ ላይ ያለውን ኮፍያ ዝቅ እያደረኩ።
ሁሉም ተደነጋግጦ ወደሷ ሲሮጥ ለቅሶ በተናነቀው ድምፅ
"ምንም አልሆንኩም እንዳትጠጉኝ!" ብላ በእልህ ተነሳችና የተጎዳ እግሯን እየጎተተች እና እስከባቷ የተሰነጠቀውን ሮዝ የራት ልብሷን ለማራገፍ እየሞከረች በደመነፍስ የሆቴሉ የውጪ በር ላይ ደረሳ ወደላይና ወደ ታች እየተገላመጠች የጠረጠረችውን ሰው መፈለግ ጀመረች።
ምንም ማየት ባለመቻሏ ተስፋ ቆረጠች ያኔ ስትወድቅ የተመታችበት ቦታ ህመመ ተሰማት ጎኗ አከባቢ ይዛ እያቃሰተች መቆም ስላቃታት ቁጭ ብላ ማልቀስ ጀመረች።
ሰውየውና አብራት የነበረችው ልጅ አጠገቧ እንደደረሱ ልጅቷ በጣም ተጨንቃ ዝቅ ብላ ልታናግራት ልታባብላት በምትሞክርበት ሰአት መሲ ተቀየረችባት•••
"ዞወር በይልኝ ወደዛ ያንቺ ገዳፋ ነው እሄ ሁሉ መጀመሪያም ምንሽም አልጣመኝም ነበር ካሁን ቡሀላ ላይሽ አልፈልግም አሁኑኑ ባጃጅ ያዢና ቀጥ ብለሽ ወደ ግቢ ሂጂ !" በማለት ስታምባርቅባት ልጅቷ ሽምቅቅ ብላ ዘወር አለች ሄደች ወደግቢ ።
"ጎበዝ መሲ ትዛዝ ታከብሪያለሽ ማለት ነው!" ብዬ መልክት ላኩላትና ስልኬን አጥፍቼ ኪሴ ውስጥ ከተትኩ እሄን ግዜ እንደ እብድ አደረጋት መልክቱ እየደረሳት ያለው እዛው ሆቴል ውስጥ እየተዝናና ካለ በቅርብ ርቀት ከሚያያት ሰው መሆኑን እርግጠኛ ሆነች ።
እንደምንም ተነስታ ስልክ መደወል ጀመረች ወደኔ እምትሞክር መስሎኝ ነበር ጎረምሶቿን እየጠራች እንደሆነ የገባኝ ሶስት
ክብደት ገፊ ፣ደረተ ሰፋፊ ፣ ባስተሳሰብ ደሞ ቀፋፊ የሆኑ በጭንቅላታቸው ሳይሆን በተከመረው ጡንቻቸው የሚያስቡ ወጣቶች ከመቅስፈት ደርሰው መሲን በመክበብ ምን እንደፈጠረ ሲጠይቋት እንደተመለከትኩ ነው ።
በመሲ ጥሪ በዛ ፍጥነት ሰው ሊደበድቡ መምጣታቸውን ሳስበው ለህሊናቸው ሳይሆን ለሆዳቸው የሚኖሩ አሳሞች መስለው ታዩኝ
መሲ ማነች ? ምንድን ነች? ስራዋ ምንድን ነው ማንን ነው የምታስደበድበን ? ለምን?
አያገባቸውም ብቻ ትክፈላቸው እንጂ እንደ እንስሳ ወደፈለገችበት ትነዳቸዋለች ። ገልቱዎች ።
ዘበኛውን ሰው እንዳይወጣ አስጠነቀቁትና
መሀላቸው አድርገዋት ግቢ ውስጥ መዟዟር ጀመሩ ብዙ ሰው የለም ያሉትም ጥንድ ጥንድ ሆነው ነው የተቀመጡት ብቻዬን ቁጭ ያልኩት እኔ ብቻ ነኝ ።
ደረታቸውን ገልብጠው እየተሽከረከሩ የሚዝናኑትን ሰዎች ምን እንደሚሏቸው ባላውቅም አንዳንዶቹን ጠጋ ብለው እያናገሩ ያንዳንዶቹን ሞባይላቸውን ተቀብለው እየመለሱላቸው እኔ ወዳለሁበት ቦታ መጠጋት ጀመሩ።
ሂሳብ ዘጋሁ።
እነዚህን ዱባ ጭንቅላቶች ፈርቼ ሳይሆን የሰው ሆቴል ውስጥ ብጥብጥ ተፈጥሮ ላለመታሰር ስል ተነስቼ ወደ መውጫው በር ስጠጋ•••
" እንዳታስወጣው! ጥበቃ እንዳታስወጣው !"
የሚለው የመሲ ጩኸት ጆሮዬ ላይ አንቃጨለብኝ ዘወር ስል እሷ ከጀርባቸው ቆማ ሶስቱም ወደኔ ሲመጡ እየኋቸው•••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍1
#ልጩህበት!!
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
በመሲ ጥሪ በዛ ፍጥነት ሰው ሊደበድቡ መምጣታቸውን ሳስበው ለህሊናቸው ሳይሆን ለሆዳቸው የሚኖሩ አሳሞች መስለው ታዩኝ መሲ ማነች ? ምንድን ነች? አያገባቸውም ብቻ ትክፈላቸው እንጂ እንደ እንስሳ ወደፈለገችበት ትነዳቸዋለች ። ገልቱዎች ።
ጥበቃውን ሰው እንዳይወጣ አስጠነቀቁትና
መሀላቸው አድርገዋት ግቢ ውስጥ መዟዟር ጀመሩ ብዙ ሰው የለም ያሉትም ጥንድ ጥንድ ሆነው ነው የተቀመጡት ብቻዬን ቁጭ ያልኩት እኔ ብቻ ነኝ ።
ደረታቸውን ገልብጠው እየተሽከረከሩ የሚዝናኑትን ሰዎች ምን እንደሚሏቸው ባላውቅም አንዳንዶቹን ጠጋ ብለው እያናገሩ ያንዳንዶቹን ሞባይላቸውን ተቀብለው እየመለሱላቸው እኔ ወዳለሁበት ቦታ መጠጋት ጀመሩ።
ሂሳብ ዘጋሁ።
እነዚህን ዱባ ጭንቅላቶች ፈርቼ ሳይሆን የሰው ሆቴል ውስጥ ብጥብጥ ተፈጥሮ ላለመታሰር ስል ተነስቼ ወደ መውጫው በር ስጠጋ•••
" እንዳታስወጣው! ጥበቃ እንዳታስወጣው !"
የሚለው የመሲ ጩኸት ጆሮዬ ላይ አንቃጨለብኝ ዘወር ስል እሷ ከጀርባቸው ቆማ ሶስቱም ወደኔ ሲመጡ እየኋቸው•••
ጥበቃው ወደኔ ተጠግቶ አየት አደረገኝና ጠቀስ አርጎኝ ሳቁ ልገንፍልብህ እንዳለው ሰው በእጁ አፉን ይዞ ወደነሱ ዞረና
" ማንን ዳኒን?" አላቸው በአመልካች ጣቱ ወደኔ እያመላከታቸው •••
" እሱን ነው እንዳይወጣ ያልሽው አንቺ ልጅ? "የቀበጡ ለት•••"
አለ የሀገር ሰው ትሰሚያለሽ እሱን እንኳን እኔ ታንክ አያቆመውም ቅድም ስትፎክሪ የነበረው እሱን ለማስመታት ነው እንዴ ?
ቆይ ዛሬ ነው ድሬ የገባችሁት? እንግዶች ናችሁ እንዴ?
ዳኒኮ በካራቴ ትምህርት ጥቁሩን ቀበቶ እንደ አባቶቹ ዝናር ደጋግሞ ወገቡ ላይ የጠመጠመ የድሬ ዥግና ነው !
ቆይ ቆይ ቆይ በወፈረ መስሎሽ ነው እነኝህን ይዘሽ የመጣሽው ምነው "ለሀምሳ ጋን አንድ አሎሎ ይበቃል " ብለው ቲተርቱ ውልእንኳ ብሎብሽ አያውቅም?
ታይነኩት አይነካም ምላሳችሁንም እግራችሁንም ሰብስባችሁ ሂዱ ዳንዬ በል አንተም ሂድ ምን ይደረግ
አንዳንዱ ተማን ጋር እንደተጣላ የሚገባው ተተወቀጠ ቡሀላ ነው !
ቢያውቁህማ እንኳንስ ለጠብ አስቁመው ሊሉኝ ሰአት ጠይቀው ለማለትም ባልደፈሩ ነበር በል ሂድ መሽቷል!"
ሲለኝ ገለማምጫቸው ሁለት እጄን ኪሴ ውስጥ ከትቼ ብወጣም ከወጣሁ ቡሀላ ካልወጣሁ እያለ ከሚታገልኝ ሳቅ ጋር መታገል ፈተና እንደሆነብኝ ጉንጬን ነፍቼ ትንሽ ራቅ እንዳልኩ ሳቄን ለቀኩት!
ወይ ጥቁር ቀበቶ! ኬት አምጥቶት ነው?
የባጃጇ ነው እንዳልል ባጃጄ ቀበቶ የላትም ።
ከጥበቃው ጋር የምንተዋወቀው በስራ ነው
አልፎ አልፎ ቀን ቀን በብዛት ደሞ ማታ ማታ ሆቴሉ ውስጥ የሚዝናኑ ብሎም እዛው አልጋ ይዘው ድሬ ሰንበትበት ብለው የሚሄዱ ደንበኞቻቸው ታክሲ እንዲጠራላቸው ሲነግሩት ደውሎ ይጠራኛል የተወሰነ ኮምሽን አስብለታለሁ እሄን እማደርገው ከብዙ ሆቴል ጥበቃዎች ጋር ነው አንድ ሁለቴ እዛ ስጠቀም ጋብዤዋለሁ አለቀ ከዚህ ያለፈ ቅርርብ አልነበረንም ።
ባንድ ግዜ የከተማው አክተር አድርጎኝ ቁጭ ሲል እንኳን እነመሲ እኔ እራሴ እራሴን ሳልፈራው አልቀረሁም ወይ የሰው ነገር እራሴን ታዘብኩት እሱ በካበኝ ቁጥር ፍታቸው ሁለት እግሬን ከፈት አድርጌ ፊቴን አጨፍግጌ በመቆም በለለኝ ደረት ስወጣጠር ፈንድቼ ነበርኮ እያልኩ በራሴው ንግግር እኔው እየሳኩ ወደቤት ስገባ ደንግጦ ከንቅልፉ የባነነው ጆሲ ቀና ብሎ አየኝና •••
"ወይኔ ወንድሜን ለየልህ በቃ!?"አለኝ።
ስማ ጆስዬ በዚህ ሰአት ቢለይልኝማ በምን እድሌ እየውልህ ጆስዬ ሁሉንም ነገር ስንፈልግ የምንሆነው ሳንፈልግ የማንሆነው ቢሆን ኤዱን እስክረሳት ብቻ ባብድ ደስ ይለኝ ነበር!
"ከዚህ በላይ! በል ተኛ አሁን ጥዋት እናወራለን" ሲለኝ ተኛሁ።
ረፋድ አራት ሰአት አከባቢ ከንቅልፌ ነቃሁ።
ማታ የዘጋሁትን ስልኬን ስክፍተው መሲ ሶስት መልክቶችን በተከታታይ ስልኬ ላይ ልካልኛለች ።
ከፍቼ ማንበብ ጀመርኩ•••
የመጀመሪያው መልከት እባክህ ወንድሜ እንደዛ እንዳታረግ ትንሽ አላሳዝንህም ? ቆይ እህት የለህም ?" ይላል
ሁለተኛው መልክቷ" ያንን ቪድዬ እንዳልከው እምትለቀው ከሆነ እራሴን እንደማጠፋ እወቅ! ይፀፅትሀል!" ይላል
ሶስተኛው መልክቷ" ጨነቀኝ ኧረ በናትህ መልስ እንኳን ስጠኝ!" ይላል ።
አሳዘነችኝ ልበል ኧረ አልልም !።
መልስ መፃፍ ጀመርኩ•••
አንቺ ክፉ ልታደርጊባቸው ስለቻልሽ ሌሎች ላይ ክፉ ስታደርጊ አንቺ ላይ ክፉ የማረግ አቅም ያለው ሌላ ሰው እንዳለ አትርሺ ቢሆንም ከስተትሽ ተምረሽ ክፋትሽን ካቆምሽ አንቺን በመጉዳቴ ሳይሆን በማስተማሬ ብዙ አተርፋለሁና በጭራሽ አልጎዳሽም!
መልክቱን ልክ እንደላኩት ስራ ሄዷኩ ያለው ጆሲ ተመልሶ መጣ ።
ምነው ጆሲ ስራ የለም እንዴ ለምን መጣህ?
"አንተን ላናግር መነጋገር አለብን ዳኒ!"
ስለምን?
"ስላንተ ነዋ!"
ስለኔ ምን ?
"ቆይ ዳኒ ለምን እኔንስ ታስጨንቀኛለህ እንደወንድሜ እማይህ ጓደኛዬ ነህ ያንተ እንዲህ መሆን የሚያስደስተኝ ይመስልሀል እንዴ?
ምን ሆንኩ?
ምን ያልሆንከው አለ! ስራህን በአግባቡ እየሰራህ
አይደለም ፣ ማታ ማታ አዘውትረህ ትጠጣለህ ከኔ ጋር እንኳን ማውራት አስጠልቶካል የኔስ ችግር የለውም ቤተሰብጋም እኮ ሄደህ አታውቅም እናትህ ሳያዩህ ሲያድሩ ምን ያህል እንደሚጨነቁ ታውቃለህ አንተን ፍለጋ እዚህ ድረስ መምጣት አለባቸው ዳኒ! ቆይ እስከመቼ እውነቱን ልንገርህ እኔ ወስኛለሁ ይቺ ኤደን የምትላትን ልጅ ሄጄ አናግራታለሁ!"
ብሎኝ ከቤት ሲወጣ ተከትዬው ወጥቼ አንገቱን አነኩትና
አታደርገውም ዳኒ አልኩት
"ቆይ ለምን" አለኝ እጄን እያስለቀቀ
ለምን እንደሆነ እነግርሀለሁ።
እሺ ወይ ያቺ የምትወድህን የኔን ሲስተር ጓደኛ ጀምራትና ይቺን ኤደን ተብዬዋን እርሳታ በቃ ዳኒ !"
ካካካካካ ኤዱን ነው በሷ እምረሳት አልኩት ከልቤ ነበር የሳኩበት!
አትሳቅ ዳኒ እንድትስቅብኝ አደለም ስራ አስፈቅጄ የመጣሁት ሁለት አማራጭ አለህ አንዱን ካልመረጥክ ከኔጋም ትጣላለህ!
ምኑን ከምኑ ነው እምመርጠው?
"ወይ ኤደንን እኔ ሄጄ እንዳናግራት መፍቀድ ካልሆነ ከልጅቷ ጋር ፍቅር ጀምረህ ኤደንን መርሳት!"
ጆሲ አምርሯል ግራ ገባኝ ። ኤዱን እንዲያናግራት በጭራሽ እንደማልፈልግ አውቃለሁ ሁለተኛው ምርጫ ደግሞ ጡጫ ሆነብኝ ቢሆንም•••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
በመሲ ጥሪ በዛ ፍጥነት ሰው ሊደበድቡ መምጣታቸውን ሳስበው ለህሊናቸው ሳይሆን ለሆዳቸው የሚኖሩ አሳሞች መስለው ታዩኝ መሲ ማነች ? ምንድን ነች? አያገባቸውም ብቻ ትክፈላቸው እንጂ እንደ እንስሳ ወደፈለገችበት ትነዳቸዋለች ። ገልቱዎች ።
ጥበቃውን ሰው እንዳይወጣ አስጠነቀቁትና
መሀላቸው አድርገዋት ግቢ ውስጥ መዟዟር ጀመሩ ብዙ ሰው የለም ያሉትም ጥንድ ጥንድ ሆነው ነው የተቀመጡት ብቻዬን ቁጭ ያልኩት እኔ ብቻ ነኝ ።
ደረታቸውን ገልብጠው እየተሽከረከሩ የሚዝናኑትን ሰዎች ምን እንደሚሏቸው ባላውቅም አንዳንዶቹን ጠጋ ብለው እያናገሩ ያንዳንዶቹን ሞባይላቸውን ተቀብለው እየመለሱላቸው እኔ ወዳለሁበት ቦታ መጠጋት ጀመሩ።
ሂሳብ ዘጋሁ።
እነዚህን ዱባ ጭንቅላቶች ፈርቼ ሳይሆን የሰው ሆቴል ውስጥ ብጥብጥ ተፈጥሮ ላለመታሰር ስል ተነስቼ ወደ መውጫው በር ስጠጋ•••
" እንዳታስወጣው! ጥበቃ እንዳታስወጣው !"
የሚለው የመሲ ጩኸት ጆሮዬ ላይ አንቃጨለብኝ ዘወር ስል እሷ ከጀርባቸው ቆማ ሶስቱም ወደኔ ሲመጡ እየኋቸው•••
ጥበቃው ወደኔ ተጠግቶ አየት አደረገኝና ጠቀስ አርጎኝ ሳቁ ልገንፍልብህ እንዳለው ሰው በእጁ አፉን ይዞ ወደነሱ ዞረና
" ማንን ዳኒን?" አላቸው በአመልካች ጣቱ ወደኔ እያመላከታቸው •••
" እሱን ነው እንዳይወጣ ያልሽው አንቺ ልጅ? "የቀበጡ ለት•••"
አለ የሀገር ሰው ትሰሚያለሽ እሱን እንኳን እኔ ታንክ አያቆመውም ቅድም ስትፎክሪ የነበረው እሱን ለማስመታት ነው እንዴ ?
ቆይ ዛሬ ነው ድሬ የገባችሁት? እንግዶች ናችሁ እንዴ?
ዳኒኮ በካራቴ ትምህርት ጥቁሩን ቀበቶ እንደ አባቶቹ ዝናር ደጋግሞ ወገቡ ላይ የጠመጠመ የድሬ ዥግና ነው !
ቆይ ቆይ ቆይ በወፈረ መስሎሽ ነው እነኝህን ይዘሽ የመጣሽው ምነው "ለሀምሳ ጋን አንድ አሎሎ ይበቃል " ብለው ቲተርቱ ውልእንኳ ብሎብሽ አያውቅም?
ታይነኩት አይነካም ምላሳችሁንም እግራችሁንም ሰብስባችሁ ሂዱ ዳንዬ በል አንተም ሂድ ምን ይደረግ
አንዳንዱ ተማን ጋር እንደተጣላ የሚገባው ተተወቀጠ ቡሀላ ነው !
ቢያውቁህማ እንኳንስ ለጠብ አስቁመው ሊሉኝ ሰአት ጠይቀው ለማለትም ባልደፈሩ ነበር በል ሂድ መሽቷል!"
ሲለኝ ገለማምጫቸው ሁለት እጄን ኪሴ ውስጥ ከትቼ ብወጣም ከወጣሁ ቡሀላ ካልወጣሁ እያለ ከሚታገልኝ ሳቅ ጋር መታገል ፈተና እንደሆነብኝ ጉንጬን ነፍቼ ትንሽ ራቅ እንዳልኩ ሳቄን ለቀኩት!
ወይ ጥቁር ቀበቶ! ኬት አምጥቶት ነው?
የባጃጇ ነው እንዳልል ባጃጄ ቀበቶ የላትም ።
ከጥበቃው ጋር የምንተዋወቀው በስራ ነው
አልፎ አልፎ ቀን ቀን በብዛት ደሞ ማታ ማታ ሆቴሉ ውስጥ የሚዝናኑ ብሎም እዛው አልጋ ይዘው ድሬ ሰንበትበት ብለው የሚሄዱ ደንበኞቻቸው ታክሲ እንዲጠራላቸው ሲነግሩት ደውሎ ይጠራኛል የተወሰነ ኮምሽን አስብለታለሁ እሄን እማደርገው ከብዙ ሆቴል ጥበቃዎች ጋር ነው አንድ ሁለቴ እዛ ስጠቀም ጋብዤዋለሁ አለቀ ከዚህ ያለፈ ቅርርብ አልነበረንም ።
ባንድ ግዜ የከተማው አክተር አድርጎኝ ቁጭ ሲል እንኳን እነመሲ እኔ እራሴ እራሴን ሳልፈራው አልቀረሁም ወይ የሰው ነገር እራሴን ታዘብኩት እሱ በካበኝ ቁጥር ፍታቸው ሁለት እግሬን ከፈት አድርጌ ፊቴን አጨፍግጌ በመቆም በለለኝ ደረት ስወጣጠር ፈንድቼ ነበርኮ እያልኩ በራሴው ንግግር እኔው እየሳኩ ወደቤት ስገባ ደንግጦ ከንቅልፉ የባነነው ጆሲ ቀና ብሎ አየኝና •••
"ወይኔ ወንድሜን ለየልህ በቃ!?"አለኝ።
ስማ ጆስዬ በዚህ ሰአት ቢለይልኝማ በምን እድሌ እየውልህ ጆስዬ ሁሉንም ነገር ስንፈልግ የምንሆነው ሳንፈልግ የማንሆነው ቢሆን ኤዱን እስክረሳት ብቻ ባብድ ደስ ይለኝ ነበር!
"ከዚህ በላይ! በል ተኛ አሁን ጥዋት እናወራለን" ሲለኝ ተኛሁ።
ረፋድ አራት ሰአት አከባቢ ከንቅልፌ ነቃሁ።
ማታ የዘጋሁትን ስልኬን ስክፍተው መሲ ሶስት መልክቶችን በተከታታይ ስልኬ ላይ ልካልኛለች ።
ከፍቼ ማንበብ ጀመርኩ•••
የመጀመሪያው መልከት እባክህ ወንድሜ እንደዛ እንዳታረግ ትንሽ አላሳዝንህም ? ቆይ እህት የለህም ?" ይላል
ሁለተኛው መልክቷ" ያንን ቪድዬ እንዳልከው እምትለቀው ከሆነ እራሴን እንደማጠፋ እወቅ! ይፀፅትሀል!" ይላል
ሶስተኛው መልክቷ" ጨነቀኝ ኧረ በናትህ መልስ እንኳን ስጠኝ!" ይላል ።
አሳዘነችኝ ልበል ኧረ አልልም !።
መልስ መፃፍ ጀመርኩ•••
አንቺ ክፉ ልታደርጊባቸው ስለቻልሽ ሌሎች ላይ ክፉ ስታደርጊ አንቺ ላይ ክፉ የማረግ አቅም ያለው ሌላ ሰው እንዳለ አትርሺ ቢሆንም ከስተትሽ ተምረሽ ክፋትሽን ካቆምሽ አንቺን በመጉዳቴ ሳይሆን በማስተማሬ ብዙ አተርፋለሁና በጭራሽ አልጎዳሽም!
መልክቱን ልክ እንደላኩት ስራ ሄዷኩ ያለው ጆሲ ተመልሶ መጣ ።
ምነው ጆሲ ስራ የለም እንዴ ለምን መጣህ?
"አንተን ላናግር መነጋገር አለብን ዳኒ!"
ስለምን?
"ስላንተ ነዋ!"
ስለኔ ምን ?
"ቆይ ዳኒ ለምን እኔንስ ታስጨንቀኛለህ እንደወንድሜ እማይህ ጓደኛዬ ነህ ያንተ እንዲህ መሆን የሚያስደስተኝ ይመስልሀል እንዴ?
ምን ሆንኩ?
ምን ያልሆንከው አለ! ስራህን በአግባቡ እየሰራህ
አይደለም ፣ ማታ ማታ አዘውትረህ ትጠጣለህ ከኔ ጋር እንኳን ማውራት አስጠልቶካል የኔስ ችግር የለውም ቤተሰብጋም እኮ ሄደህ አታውቅም እናትህ ሳያዩህ ሲያድሩ ምን ያህል እንደሚጨነቁ ታውቃለህ አንተን ፍለጋ እዚህ ድረስ መምጣት አለባቸው ዳኒ! ቆይ እስከመቼ እውነቱን ልንገርህ እኔ ወስኛለሁ ይቺ ኤደን የምትላትን ልጅ ሄጄ አናግራታለሁ!"
ብሎኝ ከቤት ሲወጣ ተከትዬው ወጥቼ አንገቱን አነኩትና
አታደርገውም ዳኒ አልኩት
"ቆይ ለምን" አለኝ እጄን እያስለቀቀ
ለምን እንደሆነ እነግርሀለሁ።
እሺ ወይ ያቺ የምትወድህን የኔን ሲስተር ጓደኛ ጀምራትና ይቺን ኤደን ተብዬዋን እርሳታ በቃ ዳኒ !"
ካካካካካ ኤዱን ነው በሷ እምረሳት አልኩት ከልቤ ነበር የሳኩበት!
አትሳቅ ዳኒ እንድትስቅብኝ አደለም ስራ አስፈቅጄ የመጣሁት ሁለት አማራጭ አለህ አንዱን ካልመረጥክ ከኔጋም ትጣላለህ!
ምኑን ከምኑ ነው እምመርጠው?
"ወይ ኤደንን እኔ ሄጄ እንዳናግራት መፍቀድ ካልሆነ ከልጅቷ ጋር ፍቅር ጀምረህ ኤደንን መርሳት!"
ጆሲ አምርሯል ግራ ገባኝ ። ኤዱን እንዲያናግራት በጭራሽ እንደማልፈልግ አውቃለሁ ሁለተኛው ምርጫ ደግሞ ጡጫ ሆነብኝ ቢሆንም•••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍1
#ልጩህበት!!
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ምኑን ከምኑ ነው እምመርጠው?
"ወይ ኤደንን እኔ ሄጄ እንዳናግራት መፍቀድ ካልሆነ ከልጅቷ ጋር ፍቅር ጀምረህ ኤደንን መርሳት!"
ጆሲ አምርሯል ግራ ገባኝ ። ኤዱን እንዲያናግራት በጭራሽ እንደማልፈልግ አውቃለሁ ሁለተኛው ምርጫ ደግሞ ጡጫ ሆነብኝ ቢሆንም•••
ውስጤ እንደማይሆን እያወቀው ከዳኒ ጭቅጭቅ ለመገላገል ስል •እሺ አልኩት
በቃ እሺ!
"በቃ እሺ ምን በየትኛው ሀሳብ?"
"በቃ ካልካት ልጅ ጋር እንቀራረባለና!"
አዋ ዳንዬ አንዳንዴ እንኳን እንደዚህ እሺ በለኝ እስቲ ዳንዬ ዋናው መቀራረባችሁ ነው ከዛ ቡሀላ ሌላው ይከተላል ኤዱንስ ቢሆን ሳትቀርባት አላፈቀርካት!"
እሺ አልኩህ እኮ በቃ አልኩት። ከዛች ሰአት ጀምሮ ጆሲ ስራውን ጀመረ ።
ልጅቷን እቤት ያመጣትና መጣሁ ብሎ በመውጣት ጥሎን ይጠፋል።
መቀራረብ ብንጀምርም እውነቱን ለመናገር እሷን ለብቻዋ ከማገኛት ይልቅ ኤዱን ከልጁ ጋር ሆና ባገኛት እመርጥ ነበር።
ለሶስት ወር ልጅቷ እና ጆሲ ስራ አደረጉኝ የተቀየረ ስሜት አልነበረም በመሀል ድንገት ለተከታታይ ቀናት ጥፍት አለች።
ለስድስት ቀን ያህል ድምጿንም ስልኳንም አጥፍታ ከተሰወረች ቡሀላ በሰባተኛው ቀን እኔና ጆሲ ሰፈር ውስጥ ቁጭ ባልንበት እራሷ ጆሲ ስልክ ላይ ደወለች።
ስልኩን ለሁለታችንም እንዲሰማ አደረገና •••
" ምን ሆነሽ ነው የጠፋሽው?" የጆሲ ጥያቄ ነበር
" ምን ላድርግ ጓደኛህ ኤደን የምትባል ሰይጣን አጠናፍራዋለች መሰለኝ በተገናኘን ቁጥር ወሬው ሁሉ ከሷ አያልፍም እንዴ እኔ ልጅቷን ሳላውቃት ሁላ እንድጠላት ነው ያደርገኝ በጣም ነው የተጎዳሁት ጆሲ ከቻልክ ጓደኛህን ወይ አሳክመው ወይ ፀበል ውሰደው " ብላው እርፍ አለች ።
ጆሲ ዘወር ብሎ ሲያፈጥምኝ ተነስቼ ካጠገቡ ሄድኩ።
ከዛን ቀን ቡሀላ ከጆሲ ጋር ስለምንም ነገር ሳናወራ የኤዱ ምርቃት ሰባት ቀን( ሳምንት) ቀረው ።
ስድስት ቀን ሲቀረው ደውላ ቤተሰቦቿ ለምርቃቷ ከሁለት ቀን ቡሀላ እንደሚመጡ እና ከምርቃቷ ቡሀላ አብራቸው ወደ አዲስ አበባ እንደምትሄድ ነገረችኝ ።
ይህ ንግግሯ መብረቅ በሉት ለኔ ።ጨነቀኝ ።
ያን ቀን ጠጥቼ ብገባም እንቅልፍ እንቢ አለኝ እኩለ ለሊት ላይ አንድ ሀሰብ መጣልኝ።
ተነስቼ ለኤዱ ደብዳቤ መፃፍ ጀመርኩ•••
••••• ለኤደን
ኤዱዬ ህይወትን መራራም ጣፋጭም እንድትሆን ካደረጓት ምክንያቶች አንዱ ምን እንደሆነ ታውቂያለሽ?
እኛ ሰዎች ስላለፈው እና ስለ አሁኑ እንጂ ነገ ምን እንደሚፈጠር እለማወቃችን ነው ።
ነገን አለማወቅ የራሱ የሆነ ብዙ ጥሩም መጥፎም ገፅታዎች አሉት።
ነገ የሚከሰተውን መጥፎ ነገር ቀድመን ስናውቅ እና ነገ የሚከሰተውን ጥሩ ነገር ቀድመን ስናውቅ የሚሰሙን ሁለት ተቃራኒ ስሜቶች ናቸው።
እንዲህ ያልኩሽ አሁን የሆንኩትን ነገር ያኔ በዛ በብርድ እዛ ሆቴል በር ላይ ቆመሽ ባየሁሽ ሰአት ቀድሜ ባውቀው ምን እወስን ነበር ብዬ ሁሌም እራሴን ስለምጠይቀው ነው
"አሁን ምን ሆንክ? ትይ ይሆኖል። ምንም አታውቂምና ጥያቄሽ ልክ ነው የኔ ስስት ያኔ ካሁን ቡሀላ ወንድምሽ ነኝ ስልሽ አንቺም ተቀብለሽ የእውነት ወንድም አድርገሽኛልና ምን ሆንክ ብትይኝ ባንቺ አይፈረድም እኔ ግን ብዙ ሆኛለሁ አንቺን በማፍቀሬ እንኳን አንቺ እኔ እንኳን የማላውቀው ሌላ ዳኒ እንደሆኑኩ አውቃለሁ።
ኤዱዬ አፈቅርሻለሁ!
ይህን ስታነቢ ምን ትይኝ ይሆን?
በቃሌ የማልገኝ እራስ ወዳድ ነኝ አደል ኤዱዬ?
በጣም ይቅርታ።
ከግዜ ቡሀላ ለኔም ባልገባኝ መንገድ ውስጤ ተቀያይሮ ካቅሜ በላይ ሆኖብኝ እንጂ ያኔ ወንድም እሆንሻለሁ ከጎንሽ ነኝ እንደወንድምሽ እይኝ ያልኩሽ ግን ከልቤ ነበር!።
ሁሌም ቃሌን ያጠፍኩ መስሎ ይሰማኛል ላንቺ ስላልነገርኩሽ ምንም ባትይኝም ብታውቅ ምን ትለኛለች እያልኩ ከመሸማቀቅ አልዳንኩም።
ፍቅር የሻቱትን ማግኘት ብቻ አይደለምና የኔ እንደማትሆኚ እያሰብኩም አፈቅርሻለሁ።
ከምንም ነገር በላይ አንቺን በእውኔም በህልሜም ማየት፣ ስላንቺ ማሰብ ፣ ስላንቺ ማውራት ያስደስተኛል ። ካንቺ ውጪ ሁሉ ነገር አልጥምህ ካለኝ ወራቶች ተቆጥረዋል።
"ታድያ በነበረን ግዜ በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ውስጥ ከነበርክ እንዴት አልነገርከኝም?
ወይም እንዴት ከፊትህ መረዳት አልቻልኩም? " ትይኝ ይሆናል
በፍቅር ንዳድ ከመለብለብ በላይ በልብ ውስጥ ያለውን የፍቅር እሳት አውጥቶ ላፈቀሩት ሰው ንዳዱን ማሳየት ለብዙ አፍቃሪዎች ከባድ ነው።
እኔን ግን አውጥቶ ከመናገሩም በላይ ከባድ የሆነብኝ ብነግርሽ የሚሰማሽን ስሜት ማሰብ ነው።
ፍቅረኛሽ ሆኜ ቢሆን አሁን ወንድምሽ በመሆኔ የተደሰትሽውን ያክል እምትደሰቺ መስሎ አይታየኝም ።
ካፌ ሻይ ቡና እያልን ፊት ለፊቴ ቁጭ ብለሽ ከናት ካባቴ ባትወለድም አንተን የመሰለ ወንድም በስጦታ ስለሰጠኝ እያልሽ ፈጣሪን ስታመሰግኚ ስሰማ እንኳን ልነግርሽ ማፍቀሬን የምታውቂብኝ እየመሰለኝ ምክንያት ፈጥሬ ካጠገብሽ እሽሻለሁ ።
ጆሲ ጓደኛዬ ምን እንደሚለኝ ታውቂያለሽ ኤዱዬ?
••••" አንተኮ መፍታት ያቃተህ መጀመሪያ ላይ እራስህ አጥብቀህ ያሰርከውን ቋጠሮ ነው አልፈታ ባለህ ቁጥር ደግሞ በንዴት ለመበጠስ እየሞከርክ የበለጠ ታጠብቀዋለህ!" ይለኛል
እውነቱን ነው ትዝ ይልሻል እዱዬ?
ስለመሲ ስናወራ አንድ ሰው ውለታ ውሎልሽ ውለታውን በመንተራስ ከፍላጎትሽ ውጪ የሚጫንሽ ከሆነ ውለታ ሳያስቀድም ተመሳሳይ ጥያቄ ከሚጠይቅሽ ሰው በላይ እርኩስ ነው ብዬሽ ነበር ።
እኔም የፍቅር ጥያቄዬ ካደረኩልሽ ትንሽ ውለታ ጋር እንዳይያያዝብኝ ፈራሁ።
አንቺንም እኔን ወንድም እንጂ ፍቅረኛ የማድረግ ፍላጎት ውስጥሽ ሳይኖር የምጫንሽ ጥያቄዬን ባለመቀበልና እኔን ባለማስከፋት መሀል ሆነሽ የምትጨነቂ መስሎ ታየኝ ።
በዚህ መሀል እናንተ ባታዩኝም ከልጁ ጋር ሆኖችሁ ብዙ ቦታዎች ታጋጥሙኝ ጀመር።
ያኔ በሱም ባንቺም ሳይሆን በራሴ ይበልጥ መናደድ ጀመርኩ ።
ህመምህ መድሀኒት የለውም አትድንም እንደተባለ በሽተኛ የፍቅር ህመሜ ፈውስ የሆንሽውን አንቺን የኔ እንደማላደርግሽ ተረዳሁ ።
ኤዱዬ በመመረቅሽ እንኳን ደስ አለሽ!
በመመረቅሽ የተሰማሽን ደስታ ትንሽ ሳታጣጥሚውና ከድሬ ሳትወጪ አንብበሽው ሌላ ስሜት ውስጥ እንድትገቢ ስላልፈለኩ ነው ይህን ደብዳቤ በእጅሽ ሳልሰጥሽ ከምርቃቷ ቡሀላ ወደ አዲስ አባባ ስሸኛት ሳታየኝ የልብስ ሻንጣዋ ውስጥ አስቀምጥላታለሁ ባየችው ግዜ ትየው ብዬ የወሰንኩት።
በነበረን ስሜት ወንድምሽ ሆኜ ልሸኝሽ ቀናቶች ቀርተዋል ለዛም ተዘጋጅቻለሁ ።
የኔ ኤደን ዛሬም ቢሆን ስላወኩሽ ደስተኛ ነኝ።
የማንም ሁኚ እኔ ግን አፈቅርሻለሁ። መቼም ቢሆን አረሳሽም። ዝምምምም ብዬ ሳፈቅርሽ እኖራለሁ።
ሰላም ሁኚ!
ዳኒ ነኝ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ምኑን ከምኑ ነው እምመርጠው?
"ወይ ኤደንን እኔ ሄጄ እንዳናግራት መፍቀድ ካልሆነ ከልጅቷ ጋር ፍቅር ጀምረህ ኤደንን መርሳት!"
ጆሲ አምርሯል ግራ ገባኝ ። ኤዱን እንዲያናግራት በጭራሽ እንደማልፈልግ አውቃለሁ ሁለተኛው ምርጫ ደግሞ ጡጫ ሆነብኝ ቢሆንም•••
ውስጤ እንደማይሆን እያወቀው ከዳኒ ጭቅጭቅ ለመገላገል ስል •እሺ አልኩት
በቃ እሺ!
"በቃ እሺ ምን በየትኛው ሀሳብ?"
"በቃ ካልካት ልጅ ጋር እንቀራረባለና!"
አዋ ዳንዬ አንዳንዴ እንኳን እንደዚህ እሺ በለኝ እስቲ ዳንዬ ዋናው መቀራረባችሁ ነው ከዛ ቡሀላ ሌላው ይከተላል ኤዱንስ ቢሆን ሳትቀርባት አላፈቀርካት!"
እሺ አልኩህ እኮ በቃ አልኩት። ከዛች ሰአት ጀምሮ ጆሲ ስራውን ጀመረ ።
ልጅቷን እቤት ያመጣትና መጣሁ ብሎ በመውጣት ጥሎን ይጠፋል።
መቀራረብ ብንጀምርም እውነቱን ለመናገር እሷን ለብቻዋ ከማገኛት ይልቅ ኤዱን ከልጁ ጋር ሆና ባገኛት እመርጥ ነበር።
ለሶስት ወር ልጅቷ እና ጆሲ ስራ አደረጉኝ የተቀየረ ስሜት አልነበረም በመሀል ድንገት ለተከታታይ ቀናት ጥፍት አለች።
ለስድስት ቀን ያህል ድምጿንም ስልኳንም አጥፍታ ከተሰወረች ቡሀላ በሰባተኛው ቀን እኔና ጆሲ ሰፈር ውስጥ ቁጭ ባልንበት እራሷ ጆሲ ስልክ ላይ ደወለች።
ስልኩን ለሁለታችንም እንዲሰማ አደረገና •••
" ምን ሆነሽ ነው የጠፋሽው?" የጆሲ ጥያቄ ነበር
" ምን ላድርግ ጓደኛህ ኤደን የምትባል ሰይጣን አጠናፍራዋለች መሰለኝ በተገናኘን ቁጥር ወሬው ሁሉ ከሷ አያልፍም እንዴ እኔ ልጅቷን ሳላውቃት ሁላ እንድጠላት ነው ያደርገኝ በጣም ነው የተጎዳሁት ጆሲ ከቻልክ ጓደኛህን ወይ አሳክመው ወይ ፀበል ውሰደው " ብላው እርፍ አለች ።
ጆሲ ዘወር ብሎ ሲያፈጥምኝ ተነስቼ ካጠገቡ ሄድኩ።
ከዛን ቀን ቡሀላ ከጆሲ ጋር ስለምንም ነገር ሳናወራ የኤዱ ምርቃት ሰባት ቀን( ሳምንት) ቀረው ።
ስድስት ቀን ሲቀረው ደውላ ቤተሰቦቿ ለምርቃቷ ከሁለት ቀን ቡሀላ እንደሚመጡ እና ከምርቃቷ ቡሀላ አብራቸው ወደ አዲስ አበባ እንደምትሄድ ነገረችኝ ።
ይህ ንግግሯ መብረቅ በሉት ለኔ ።ጨነቀኝ ።
ያን ቀን ጠጥቼ ብገባም እንቅልፍ እንቢ አለኝ እኩለ ለሊት ላይ አንድ ሀሰብ መጣልኝ።
ተነስቼ ለኤዱ ደብዳቤ መፃፍ ጀመርኩ•••
••••• ለኤደን
ኤዱዬ ህይወትን መራራም ጣፋጭም እንድትሆን ካደረጓት ምክንያቶች አንዱ ምን እንደሆነ ታውቂያለሽ?
እኛ ሰዎች ስላለፈው እና ስለ አሁኑ እንጂ ነገ ምን እንደሚፈጠር እለማወቃችን ነው ።
ነገን አለማወቅ የራሱ የሆነ ብዙ ጥሩም መጥፎም ገፅታዎች አሉት።
ነገ የሚከሰተውን መጥፎ ነገር ቀድመን ስናውቅ እና ነገ የሚከሰተውን ጥሩ ነገር ቀድመን ስናውቅ የሚሰሙን ሁለት ተቃራኒ ስሜቶች ናቸው።
እንዲህ ያልኩሽ አሁን የሆንኩትን ነገር ያኔ በዛ በብርድ እዛ ሆቴል በር ላይ ቆመሽ ባየሁሽ ሰአት ቀድሜ ባውቀው ምን እወስን ነበር ብዬ ሁሌም እራሴን ስለምጠይቀው ነው
"አሁን ምን ሆንክ? ትይ ይሆኖል። ምንም አታውቂምና ጥያቄሽ ልክ ነው የኔ ስስት ያኔ ካሁን ቡሀላ ወንድምሽ ነኝ ስልሽ አንቺም ተቀብለሽ የእውነት ወንድም አድርገሽኛልና ምን ሆንክ ብትይኝ ባንቺ አይፈረድም እኔ ግን ብዙ ሆኛለሁ አንቺን በማፍቀሬ እንኳን አንቺ እኔ እንኳን የማላውቀው ሌላ ዳኒ እንደሆኑኩ አውቃለሁ።
ኤዱዬ አፈቅርሻለሁ!
ይህን ስታነቢ ምን ትይኝ ይሆን?
በቃሌ የማልገኝ እራስ ወዳድ ነኝ አደል ኤዱዬ?
በጣም ይቅርታ።
ከግዜ ቡሀላ ለኔም ባልገባኝ መንገድ ውስጤ ተቀያይሮ ካቅሜ በላይ ሆኖብኝ እንጂ ያኔ ወንድም እሆንሻለሁ ከጎንሽ ነኝ እንደወንድምሽ እይኝ ያልኩሽ ግን ከልቤ ነበር!።
ሁሌም ቃሌን ያጠፍኩ መስሎ ይሰማኛል ላንቺ ስላልነገርኩሽ ምንም ባትይኝም ብታውቅ ምን ትለኛለች እያልኩ ከመሸማቀቅ አልዳንኩም።
ፍቅር የሻቱትን ማግኘት ብቻ አይደለምና የኔ እንደማትሆኚ እያሰብኩም አፈቅርሻለሁ።
ከምንም ነገር በላይ አንቺን በእውኔም በህልሜም ማየት፣ ስላንቺ ማሰብ ፣ ስላንቺ ማውራት ያስደስተኛል ። ካንቺ ውጪ ሁሉ ነገር አልጥምህ ካለኝ ወራቶች ተቆጥረዋል።
"ታድያ በነበረን ግዜ በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ውስጥ ከነበርክ እንዴት አልነገርከኝም?
ወይም እንዴት ከፊትህ መረዳት አልቻልኩም? " ትይኝ ይሆናል
በፍቅር ንዳድ ከመለብለብ በላይ በልብ ውስጥ ያለውን የፍቅር እሳት አውጥቶ ላፈቀሩት ሰው ንዳዱን ማሳየት ለብዙ አፍቃሪዎች ከባድ ነው።
እኔን ግን አውጥቶ ከመናገሩም በላይ ከባድ የሆነብኝ ብነግርሽ የሚሰማሽን ስሜት ማሰብ ነው።
ፍቅረኛሽ ሆኜ ቢሆን አሁን ወንድምሽ በመሆኔ የተደሰትሽውን ያክል እምትደሰቺ መስሎ አይታየኝም ።
ካፌ ሻይ ቡና እያልን ፊት ለፊቴ ቁጭ ብለሽ ከናት ካባቴ ባትወለድም አንተን የመሰለ ወንድም በስጦታ ስለሰጠኝ እያልሽ ፈጣሪን ስታመሰግኚ ስሰማ እንኳን ልነግርሽ ማፍቀሬን የምታውቂብኝ እየመሰለኝ ምክንያት ፈጥሬ ካጠገብሽ እሽሻለሁ ።
ጆሲ ጓደኛዬ ምን እንደሚለኝ ታውቂያለሽ ኤዱዬ?
••••" አንተኮ መፍታት ያቃተህ መጀመሪያ ላይ እራስህ አጥብቀህ ያሰርከውን ቋጠሮ ነው አልፈታ ባለህ ቁጥር ደግሞ በንዴት ለመበጠስ እየሞከርክ የበለጠ ታጠብቀዋለህ!" ይለኛል
እውነቱን ነው ትዝ ይልሻል እዱዬ?
ስለመሲ ስናወራ አንድ ሰው ውለታ ውሎልሽ ውለታውን በመንተራስ ከፍላጎትሽ ውጪ የሚጫንሽ ከሆነ ውለታ ሳያስቀድም ተመሳሳይ ጥያቄ ከሚጠይቅሽ ሰው በላይ እርኩስ ነው ብዬሽ ነበር ።
እኔም የፍቅር ጥያቄዬ ካደረኩልሽ ትንሽ ውለታ ጋር እንዳይያያዝብኝ ፈራሁ።
አንቺንም እኔን ወንድም እንጂ ፍቅረኛ የማድረግ ፍላጎት ውስጥሽ ሳይኖር የምጫንሽ ጥያቄዬን ባለመቀበልና እኔን ባለማስከፋት መሀል ሆነሽ የምትጨነቂ መስሎ ታየኝ ።
በዚህ መሀል እናንተ ባታዩኝም ከልጁ ጋር ሆኖችሁ ብዙ ቦታዎች ታጋጥሙኝ ጀመር።
ያኔ በሱም ባንቺም ሳይሆን በራሴ ይበልጥ መናደድ ጀመርኩ ።
ህመምህ መድሀኒት የለውም አትድንም እንደተባለ በሽተኛ የፍቅር ህመሜ ፈውስ የሆንሽውን አንቺን የኔ እንደማላደርግሽ ተረዳሁ ።
ኤዱዬ በመመረቅሽ እንኳን ደስ አለሽ!
በመመረቅሽ የተሰማሽን ደስታ ትንሽ ሳታጣጥሚውና ከድሬ ሳትወጪ አንብበሽው ሌላ ስሜት ውስጥ እንድትገቢ ስላልፈለኩ ነው ይህን ደብዳቤ በእጅሽ ሳልሰጥሽ ከምርቃቷ ቡሀላ ወደ አዲስ አባባ ስሸኛት ሳታየኝ የልብስ ሻንጣዋ ውስጥ አስቀምጥላታለሁ ባየችው ግዜ ትየው ብዬ የወሰንኩት።
በነበረን ስሜት ወንድምሽ ሆኜ ልሸኝሽ ቀናቶች ቀርተዋል ለዛም ተዘጋጅቻለሁ ።
የኔ ኤደን ዛሬም ቢሆን ስላወኩሽ ደስተኛ ነኝ።
የማንም ሁኚ እኔ ግን አፈቅርሻለሁ። መቼም ቢሆን አረሳሽም። ዝምምምም ብዬ ሳፈቅርሽ እኖራለሁ።
ሰላም ሁኚ!
ዳኒ ነኝ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍3
#ልጩህበት!!
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አራት(የመጨረሻው ክፍል)
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ሌላ ስሜት ውስጥ እንድትገቢ ስላልፈለኩ ነው ይህን ደብዳቤ በእጅሽ ሳልሰጥሽ ከምርቃቷ ቡሀላ ወደ አዲስ አባባ ስሸኛት ሳታየኝ የልብስ ሻንጣዋ ውስጥ አስቀምጥላታለሁ ባየችው ግዜ ትየው ብዬ የወሰንኩት።
በነበረን ስሜት ወንድምሽ ሆኜ ልሸኝሽ ቀናቶች ቀርተዋል ለዛም ተዘጋጅቻለሁ ።
የኔ ኤደን ዛሬም ቢሆን ስላወኩሽ ደስተኛ ነኝ።
የማንም ሁኚ እኔ ግን አፈቅርሻለሁ። መቼም ቢሆን አረሳሽም። ዝምምምም ብዬ ሳፈቅርሽ እኖራለሁ።
ሰላም ሁኚ!
ዳኒ ነኝ።
ደብዳቤውን ፅፌ እንደጨረስኩ ለመውረድ ተጨማሪ ሀይል እየጠበቀ ያቀረረውን እንባዬን ከአይኖቼ ላይ ጠራረኩና ተጠቅልዬ ተኛሁ።
የውስጤን በትንሹም ቢሆን አውጥቼ ስልፃፍኩት ነው መሰለኝ ቅልል ያለኝ መስሎ ተሰማኝ ። እንቃልፍ ይዞኝ ከመሄዱ በፊት ፈጣሪዬ አንተ ያልከው ብቻ ይሁን! አልኩ ። እንቅልፍ ወሰደኝ።
ጥዋት ከንቅልፌ ስነቃ ጆሲ እክፍላችን ውስጥ መሀል ግድግዳ ላይ በሰቀላት ክብ መስታወት እየተመለከተ እርጥብ ፀጉሩን ያደራርቃል ።
በኔ ተናዶ ስለምንም ጉዳይ ከኔ ጋር ማውራት ካቆመ ቢቆይም ላወራው ፈለኩ•••
ጆሲ ለኤደን እኮ ደብዳቤ ፃፍኩላት !
"ተው ባክህ! ምነው ቁልቁል?"
ምንድነው ቁልቁል?
"በቴክኖሎጂ ተሽቀንጥሮ የተጣለውን የፍቅር ደብዳቤ መፃፃፍ ኬት ፈልገህ አገኘከው ብዬ ነዋ!"
የመረጥኩት መንገድ እሱን ስለሆነ ከወደቀበት አነሳሁት!
"ምርጫህ ከሆነ ይሁን ግን ምነው ፈጠንክ ገና ከመተዋወቃችሁ!"
እያላገጥክ ነው ጂሲ?
"እያላገጥክ ያለኸው እማ አንተ ነህ ዳንዬ እሄን ሁሉ ግዜ በፍቅሯ ፍዳህን ስታይ ቆይተህ
አንተስ ወደህ ነው ባንተ እንደዛ መሆን እኔንም ቤተሰቦችህንም በጭንቀት ስትንጠን ከርመክ አሁን ልጅቷ ትምህርቷን ጨርሳ አንተንም ሀገሩንም ጥላ ልትሄድ ቀናቶች ሲቀሯት ምን ብለህ ልትፅፍላት ነው ?
እባክሽ ጥለሽኝ አትሂጂ ወይ ተያይዘን እንሂድ ልትላት ነው?
ቆይ በዚህ ሰአት ምን ልትላት ነው!?
አፈቅርሻለሁ ነው አፈቅርሽ ነበር ?"
ጆሲ በቃህ እንግዲህ አታናደኝ !
ከተረዳኸኝ እኔ ለሷ ያለኝ ፍቅር እሷን በማግኘትና በማጣት የሚወሰን አይደለም !
የትም ትሁን የማንም ትሁን አፈቅራታለሁ!
ደሞም ደብዳቤውን የፃፍኩት አሁን ልሰጣት አይደለም!
"ምን ማለት ነው ? ከሄደች ቡሀላ በፖስታ ቤት ልትልክላት ባልሆነ!"
ለምን አይሆንም ?ቢሆንስ?
" እንዴ ታድያ ለምን መፃፉ አስፈለገህ ዝም ብልህ እንዲሁ ፍቅር ዲዳ ያረገህ ይመስል ትንፍሽ ሳትል እንደተለጎምክ ለምን አትሸኛትም?
አዋ እንደተለጎምኩ እሸኛታለሁ ከልጁ ጋር ፍቅር እንደጀመሩ እርግጠኛ ነኝ የኔ ላትሆን ላስጨንቃት አልፈልግም !
"ታድያ እንደዛ ካሰብክ ተዋታ ! እርሳታ በቃ ደብዳቤውን እዛ ደርሳስ ቢሆን ስትልክላት ማንበባቧ ይቀራል እንዴ ያኔስ አትጨነቅም ነው የድሬዳዋ እና ያዲስ አበባ ጭንቀት ይለያያል!"
ጭንቀቱ ላይለያይ ይችላል ያንን የማደርገው በሁለት ምክንያት ነው
አንድ አሁን በመመረቋ የተሰማትን ደስታ ላለመረበሽ
ሁለተኛው እና ዋናው ምክንያቴ ደግሞ ተመርቃ ከሄደች ከኔ ምንም ነገር በማትፈልግበት ሁኔታ ውስጥ ስትሆን ለመወሰን ነፃ ትሆናለች
"አየህ አሁንም ዙረህ ዙረህ ቋጠሮው ጋር ሄድክ ዳንዬ እሄን ቋጠሮ መፍታት ወይ መተው ካልቻልክ በሷ ጉዳይ ከኔ ጋር መቼም አንግባባም "
ብሎኝ ጥሎኝ ወጣ። እሱ ባይሰማኝም
እንኳን ካንተ ጋር ከራሴም መግባባት አልቻልኩም ጓደኛዬ ይቅርታ ስላስጨነኩህ አልኩ ለራሴ።
የኤዱ ቤተሰቦች ድሬ ዳዋ ከመድረሳቸው ከሰአታት በፊት ያ ከመደብደብ ያተረፈኝ ጥበቃ ወደ ሚሰራበት ሆቴል ሄድኩና አልጋ ያዝኩላቸው ስገባ አለነበረም ስወጣ ገና ከሩቅ ሲያየኝ መሳቅ ጀመረ አጠገቡ ስደርስም•••
" ካካካካ ስማ እኔ እኮ እነዛን ልጆች አውቃቸዋለሁ ያን ቀን የባጥ የቋጡን ቀባጥሬ ባላስመልጥህ ለቀብር እሚሆንም እንኳን አያስቀሩልህም ነበር
የት እንደማውቃቸው ታውቃለህ•••"
ብሎ ሊቀጥል ሲል እኔም ፈገግ እያልኩ አቦ ሌላ ግዜ በሰፊው እናወራለን እሺ ከአዲስ አበባ የሚመጣ እንግዳ ልቀበል ነው ደርሰዋል ብየው የሻሂ ሰጠሁትና ሄድኩ።
ከኤዱ ጋር ሆነን ቤተሰቦቿን እየጠበቅን ያ ልጅ በየደቂቃው ይደውል ነበር ስታናግረውም ከኔ ፈንጠር እያለች ነበር ቤተሰቦቿ ደርሰው በኔው ባጃጅ ወደ ያዝኩላቸው ማረፊያ ሄድን ።
እንደደረስን •••
"እማ ዳኒ ማለት እኮ እሱ ነው " አለች እናትና አባቷን በየተራ ልብ በሚሰውረው ፈገግታዋ እያቻቸው።
አቤት ምርቃት እናትና አቧቷ እየተቀባበሉ የመረቁኝ ምርቃት ሰምቸው ሁላ አላውቅም ካሁን ቡሀላ በሂወት ዘመኔ ማንም እኔ ነኝ ያለ ተራጋሚ የፈለገውን አይነት እርግማን ቢረግመኝ እራሱ እሄን ምርቃት አሸንፎት እንደማይደርስብኝ እርግጠኛ ነኝ።
ኤዱ በተመረቀችበት እለት መሄዷን እያሰብኩ ውስጤ ሀዘን ቢሰማውም መመረቋ በሷና በቤተሰቦቿ ፊት ላይ የማየው የደስታ ጥግ ግን ሀዘኔን ለግዜውም ቢሆን አክሽፎት ደስታቸውን ለመጋራት ተገደድኩ።
እንዳትደርስ የፈራኋት የመጨረሻዋ ሰአት ደረሰች።
እኔና ኤዱ በኔ ባጃጅ ወደ ግቢ ሄድንና ከግቢ ያመጣቻቸውን ሻንጣዋን ጨምሮ ሌሎች የግል እቃዎቿን ባጃጇ ውስጥ አስገብታ•••
"ዳኒዬ መጣሁ እሺ ጓደኛቼን ልሰናበታቸው" ብላኝ ሄደች።
ደብዳቤውን ከውሃላ ኪሴ አወጣሁና የልብስ ሻንጣዋን ከፍቼ ልብሶቿ መሀል አርቄ ቀበርኩት።
ሀሙስ ከለሊቱ 10:30 ድሬ ዳዋ የድሮ ባቡር ጣብያ ፊት ለፊት ባጃጄን ተደግፌ ቆሚያለሁ
ከኔ ፊት ለፊት እነ ኤዱን ይዞ ወደ አዲስ አበቧ የሚነጉደው ዘመናዊ አውቶብስ የተሳፋሪዎቹን እቃ ከታች ሆዱ ውስጥ ተሳፋሪዎቹን ደግሞ ከላይ ጭኖ ለመምዘግዘግ መዘጋጀቱን በሚያጓራው ድምፁ ያውጃል።
ኤዱ አንዴ ከኛ ራቅ ብለው የያዙትን እቃ ወደሚያስመዝኑት ቤተሰቦቿ አንዴ ውስጤ ትርምስምስ እንዳለ ባጃጄን ተደግፌ ወደ ቆምኩት ወደኔ ሄድ መለስ ትላለች ።
ግራ ግብት! ጭንቅ !እንዳላት ታስታውቃለች ።
ያን ስሜት የፈጠረባት የኔ ሁኔታ ሳይሆን አይቀርም ።
ምንም ማውራት ሳንችል በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች ካቅማችን በላይ ሆነና መላቀስ ጀመርን በቃ ተላቀስን እሷን እያባበልኩ እኔ አለቀስኩ።
እኔን እያባብለች እሷም አለቀሰች ።
ተለያየን ሄዱ ።
በሄደች በአራተኛው ቀን ስልኬ ላይ በማላውቀው ቁጥር ተደወለ አነሳሁት ••• ኤዱ ነች•••
"ዳንዬ ቆይ ለምን ለምን ለምን " ብቻ ብላ ማልቀስ ጀመረች ደብዳቤውን አግኝታ አንብባው እንደሆነ ገባኝ ።
በስልክም ከመላቀስ ውጩ ብዙ ማውራት አልቻልንም ነገር ግን በሷ ምክንያት በመጎዳቴ እጅግ ማዘኗንና ከልጁ ጋር በፍቅር አብራ መሆኗን ነገረችኝ ለኔ አዲስ አልነበረም በነበርኩበት ከባድ የድብርት ሂወት ቀጠልኩ።
ይህ ከሆነ አንድ አመት ከሁለት ወር እንደሆነው
እንደሁልግዜው ማታ በስካር ጥንብዝ ብዬ ገብቼ ተኝቻለሁ እዛው እንደተኛሁ ከቀኑ አምስት ሰአት አከባቢ ከተኛሁበት በሀይል ተቀሰቀስኩ ብንን ስል ጆሲ ጓደኛዬ እና የኔዋ ኤደን አጠገብ ላጠገብ ቆመዋል።
ወይ መቃዥት አልኩና አይኔን እየጠራረኩ ከተኛሁበት ብድግ ብዬ ቆምኩ አሁንም ፊት ለፊቴ ጎን ለጎን ቆመዋል።ግን ዝም ብለው ያዩኛል እንጂ ትንፍሽ አይሉም።
ያበድኩ የለየልኝ መሰለኝ።ወደ ጆሲ ተጠጋሁና ነካ አደረኩት ።ያኔ ባሰብኝ።ለራሴ አዘንኩ እንባዬ በሁለቱም አይኖቼ ግጥም አለ። የጆሲንም እንባ ያየሁት መሰለኝ።
ጆስዬ በናትህ ተንፍስ!?
ጆሲ እባክህ እውነት ነው እየቃዥህ አይደለም በለኝ ።
ህልም ነው እንዳትለኝ እሺ ጆሲ?
አጠገቤ የቆመችው ያንተዋ ኤደን ነች በለኝ
ተወርውራ አንገቴ ላይ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አራት(የመጨረሻው ክፍል)
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ሌላ ስሜት ውስጥ እንድትገቢ ስላልፈለኩ ነው ይህን ደብዳቤ በእጅሽ ሳልሰጥሽ ከምርቃቷ ቡሀላ ወደ አዲስ አባባ ስሸኛት ሳታየኝ የልብስ ሻንጣዋ ውስጥ አስቀምጥላታለሁ ባየችው ግዜ ትየው ብዬ የወሰንኩት።
በነበረን ስሜት ወንድምሽ ሆኜ ልሸኝሽ ቀናቶች ቀርተዋል ለዛም ተዘጋጅቻለሁ ።
የኔ ኤደን ዛሬም ቢሆን ስላወኩሽ ደስተኛ ነኝ።
የማንም ሁኚ እኔ ግን አፈቅርሻለሁ። መቼም ቢሆን አረሳሽም። ዝምምምም ብዬ ሳፈቅርሽ እኖራለሁ።
ሰላም ሁኚ!
ዳኒ ነኝ።
ደብዳቤውን ፅፌ እንደጨረስኩ ለመውረድ ተጨማሪ ሀይል እየጠበቀ ያቀረረውን እንባዬን ከአይኖቼ ላይ ጠራረኩና ተጠቅልዬ ተኛሁ።
የውስጤን በትንሹም ቢሆን አውጥቼ ስልፃፍኩት ነው መሰለኝ ቅልል ያለኝ መስሎ ተሰማኝ ። እንቃልፍ ይዞኝ ከመሄዱ በፊት ፈጣሪዬ አንተ ያልከው ብቻ ይሁን! አልኩ ። እንቅልፍ ወሰደኝ።
ጥዋት ከንቅልፌ ስነቃ ጆሲ እክፍላችን ውስጥ መሀል ግድግዳ ላይ በሰቀላት ክብ መስታወት እየተመለከተ እርጥብ ፀጉሩን ያደራርቃል ።
በኔ ተናዶ ስለምንም ጉዳይ ከኔ ጋር ማውራት ካቆመ ቢቆይም ላወራው ፈለኩ•••
ጆሲ ለኤደን እኮ ደብዳቤ ፃፍኩላት !
"ተው ባክህ! ምነው ቁልቁል?"
ምንድነው ቁልቁል?
"በቴክኖሎጂ ተሽቀንጥሮ የተጣለውን የፍቅር ደብዳቤ መፃፃፍ ኬት ፈልገህ አገኘከው ብዬ ነዋ!"
የመረጥኩት መንገድ እሱን ስለሆነ ከወደቀበት አነሳሁት!
"ምርጫህ ከሆነ ይሁን ግን ምነው ፈጠንክ ገና ከመተዋወቃችሁ!"
እያላገጥክ ነው ጂሲ?
"እያላገጥክ ያለኸው እማ አንተ ነህ ዳንዬ እሄን ሁሉ ግዜ በፍቅሯ ፍዳህን ስታይ ቆይተህ
አንተስ ወደህ ነው ባንተ እንደዛ መሆን እኔንም ቤተሰቦችህንም በጭንቀት ስትንጠን ከርመክ አሁን ልጅቷ ትምህርቷን ጨርሳ አንተንም ሀገሩንም ጥላ ልትሄድ ቀናቶች ሲቀሯት ምን ብለህ ልትፅፍላት ነው ?
እባክሽ ጥለሽኝ አትሂጂ ወይ ተያይዘን እንሂድ ልትላት ነው?
ቆይ በዚህ ሰአት ምን ልትላት ነው!?
አፈቅርሻለሁ ነው አፈቅርሽ ነበር ?"
ጆሲ በቃህ እንግዲህ አታናደኝ !
ከተረዳኸኝ እኔ ለሷ ያለኝ ፍቅር እሷን በማግኘትና በማጣት የሚወሰን አይደለም !
የትም ትሁን የማንም ትሁን አፈቅራታለሁ!
ደሞም ደብዳቤውን የፃፍኩት አሁን ልሰጣት አይደለም!
"ምን ማለት ነው ? ከሄደች ቡሀላ በፖስታ ቤት ልትልክላት ባልሆነ!"
ለምን አይሆንም ?ቢሆንስ?
" እንዴ ታድያ ለምን መፃፉ አስፈለገህ ዝም ብልህ እንዲሁ ፍቅር ዲዳ ያረገህ ይመስል ትንፍሽ ሳትል እንደተለጎምክ ለምን አትሸኛትም?
አዋ እንደተለጎምኩ እሸኛታለሁ ከልጁ ጋር ፍቅር እንደጀመሩ እርግጠኛ ነኝ የኔ ላትሆን ላስጨንቃት አልፈልግም !
"ታድያ እንደዛ ካሰብክ ተዋታ ! እርሳታ በቃ ደብዳቤውን እዛ ደርሳስ ቢሆን ስትልክላት ማንበባቧ ይቀራል እንዴ ያኔስ አትጨነቅም ነው የድሬዳዋ እና ያዲስ አበባ ጭንቀት ይለያያል!"
ጭንቀቱ ላይለያይ ይችላል ያንን የማደርገው በሁለት ምክንያት ነው
አንድ አሁን በመመረቋ የተሰማትን ደስታ ላለመረበሽ
ሁለተኛው እና ዋናው ምክንያቴ ደግሞ ተመርቃ ከሄደች ከኔ ምንም ነገር በማትፈልግበት ሁኔታ ውስጥ ስትሆን ለመወሰን ነፃ ትሆናለች
"አየህ አሁንም ዙረህ ዙረህ ቋጠሮው ጋር ሄድክ ዳንዬ እሄን ቋጠሮ መፍታት ወይ መተው ካልቻልክ በሷ ጉዳይ ከኔ ጋር መቼም አንግባባም "
ብሎኝ ጥሎኝ ወጣ። እሱ ባይሰማኝም
እንኳን ካንተ ጋር ከራሴም መግባባት አልቻልኩም ጓደኛዬ ይቅርታ ስላስጨነኩህ አልኩ ለራሴ።
የኤዱ ቤተሰቦች ድሬ ዳዋ ከመድረሳቸው ከሰአታት በፊት ያ ከመደብደብ ያተረፈኝ ጥበቃ ወደ ሚሰራበት ሆቴል ሄድኩና አልጋ ያዝኩላቸው ስገባ አለነበረም ስወጣ ገና ከሩቅ ሲያየኝ መሳቅ ጀመረ አጠገቡ ስደርስም•••
" ካካካካ ስማ እኔ እኮ እነዛን ልጆች አውቃቸዋለሁ ያን ቀን የባጥ የቋጡን ቀባጥሬ ባላስመልጥህ ለቀብር እሚሆንም እንኳን አያስቀሩልህም ነበር
የት እንደማውቃቸው ታውቃለህ•••"
ብሎ ሊቀጥል ሲል እኔም ፈገግ እያልኩ አቦ ሌላ ግዜ በሰፊው እናወራለን እሺ ከአዲስ አበባ የሚመጣ እንግዳ ልቀበል ነው ደርሰዋል ብየው የሻሂ ሰጠሁትና ሄድኩ።
ከኤዱ ጋር ሆነን ቤተሰቦቿን እየጠበቅን ያ ልጅ በየደቂቃው ይደውል ነበር ስታናግረውም ከኔ ፈንጠር እያለች ነበር ቤተሰቦቿ ደርሰው በኔው ባጃጅ ወደ ያዝኩላቸው ማረፊያ ሄድን ።
እንደደረስን •••
"እማ ዳኒ ማለት እኮ እሱ ነው " አለች እናትና አባቷን በየተራ ልብ በሚሰውረው ፈገግታዋ እያቻቸው።
አቤት ምርቃት እናትና አቧቷ እየተቀባበሉ የመረቁኝ ምርቃት ሰምቸው ሁላ አላውቅም ካሁን ቡሀላ በሂወት ዘመኔ ማንም እኔ ነኝ ያለ ተራጋሚ የፈለገውን አይነት እርግማን ቢረግመኝ እራሱ እሄን ምርቃት አሸንፎት እንደማይደርስብኝ እርግጠኛ ነኝ።
ኤዱ በተመረቀችበት እለት መሄዷን እያሰብኩ ውስጤ ሀዘን ቢሰማውም መመረቋ በሷና በቤተሰቦቿ ፊት ላይ የማየው የደስታ ጥግ ግን ሀዘኔን ለግዜውም ቢሆን አክሽፎት ደስታቸውን ለመጋራት ተገደድኩ።
እንዳትደርስ የፈራኋት የመጨረሻዋ ሰአት ደረሰች።
እኔና ኤዱ በኔ ባጃጅ ወደ ግቢ ሄድንና ከግቢ ያመጣቻቸውን ሻንጣዋን ጨምሮ ሌሎች የግል እቃዎቿን ባጃጇ ውስጥ አስገብታ•••
"ዳኒዬ መጣሁ እሺ ጓደኛቼን ልሰናበታቸው" ብላኝ ሄደች።
ደብዳቤውን ከውሃላ ኪሴ አወጣሁና የልብስ ሻንጣዋን ከፍቼ ልብሶቿ መሀል አርቄ ቀበርኩት።
ሀሙስ ከለሊቱ 10:30 ድሬ ዳዋ የድሮ ባቡር ጣብያ ፊት ለፊት ባጃጄን ተደግፌ ቆሚያለሁ
ከኔ ፊት ለፊት እነ ኤዱን ይዞ ወደ አዲስ አበቧ የሚነጉደው ዘመናዊ አውቶብስ የተሳፋሪዎቹን እቃ ከታች ሆዱ ውስጥ ተሳፋሪዎቹን ደግሞ ከላይ ጭኖ ለመምዘግዘግ መዘጋጀቱን በሚያጓራው ድምፁ ያውጃል።
ኤዱ አንዴ ከኛ ራቅ ብለው የያዙትን እቃ ወደሚያስመዝኑት ቤተሰቦቿ አንዴ ውስጤ ትርምስምስ እንዳለ ባጃጄን ተደግፌ ወደ ቆምኩት ወደኔ ሄድ መለስ ትላለች ።
ግራ ግብት! ጭንቅ !እንዳላት ታስታውቃለች ።
ያን ስሜት የፈጠረባት የኔ ሁኔታ ሳይሆን አይቀርም ።
ምንም ማውራት ሳንችል በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች ካቅማችን በላይ ሆነና መላቀስ ጀመርን በቃ ተላቀስን እሷን እያባበልኩ እኔ አለቀስኩ።
እኔን እያባብለች እሷም አለቀሰች ።
ተለያየን ሄዱ ።
በሄደች በአራተኛው ቀን ስልኬ ላይ በማላውቀው ቁጥር ተደወለ አነሳሁት ••• ኤዱ ነች•••
"ዳንዬ ቆይ ለምን ለምን ለምን " ብቻ ብላ ማልቀስ ጀመረች ደብዳቤውን አግኝታ አንብባው እንደሆነ ገባኝ ።
በስልክም ከመላቀስ ውጩ ብዙ ማውራት አልቻልንም ነገር ግን በሷ ምክንያት በመጎዳቴ እጅግ ማዘኗንና ከልጁ ጋር በፍቅር አብራ መሆኗን ነገረችኝ ለኔ አዲስ አልነበረም በነበርኩበት ከባድ የድብርት ሂወት ቀጠልኩ።
ይህ ከሆነ አንድ አመት ከሁለት ወር እንደሆነው
እንደሁልግዜው ማታ በስካር ጥንብዝ ብዬ ገብቼ ተኝቻለሁ እዛው እንደተኛሁ ከቀኑ አምስት ሰአት አከባቢ ከተኛሁበት በሀይል ተቀሰቀስኩ ብንን ስል ጆሲ ጓደኛዬ እና የኔዋ ኤደን አጠገብ ላጠገብ ቆመዋል።
ወይ መቃዥት አልኩና አይኔን እየጠራረኩ ከተኛሁበት ብድግ ብዬ ቆምኩ አሁንም ፊት ለፊቴ ጎን ለጎን ቆመዋል።ግን ዝም ብለው ያዩኛል እንጂ ትንፍሽ አይሉም።
ያበድኩ የለየልኝ መሰለኝ።ወደ ጆሲ ተጠጋሁና ነካ አደረኩት ።ያኔ ባሰብኝ።ለራሴ አዘንኩ እንባዬ በሁለቱም አይኖቼ ግጥም አለ። የጆሲንም እንባ ያየሁት መሰለኝ።
ጆስዬ በናትህ ተንፍስ!?
ጆሲ እባክህ እውነት ነው እየቃዥህ አይደለም በለኝ ።
ህልም ነው እንዳትለኝ እሺ ጆሲ?
አጠገቤ የቆመችው ያንተዋ ኤደን ነች በለኝ
ተወርውራ አንገቴ ላይ
👍2
ተጠመጠመች !።
"አዎ ዳንዬ ያንተዋ ኤደን ነኝ ሁሉንም ነገር ትቼ ወዳንተው መጥቻለሁ ።
እጠብቅሻለሁ ብለከኝ የለ ዳንዬ አረሳከኝም አደል? ዛሬም ታፈቅረኛለህ አይደል ዳንዬ?"
አፏን አፍኜ አቋረጥኳትና እንባዋን እየጠራረኩ ወደ ጆሮዋ በመጠጋት አንድ ጥያቄ ብቻ ልጠይቅሽ ኤዱዬ አልኳት።
እሺ አለችኝ አፋን ስላፈንኳት ጭንቅላቷን እያወዛወዘች ።
አንዴ ልጩህ በናትሽ?????
💫ተፈፀመ💫
በአጨራረሱ ዙርያ ያላችሁን ሀሳብ አስተያየት በ @atronosebot በኩል እጠብቃለሁ።
"አዎ ዳንዬ ያንተዋ ኤደን ነኝ ሁሉንም ነገር ትቼ ወዳንተው መጥቻለሁ ።
እጠብቅሻለሁ ብለከኝ የለ ዳንዬ አረሳከኝም አደል? ዛሬም ታፈቅረኛለህ አይደል ዳንዬ?"
አፏን አፍኜ አቋረጥኳትና እንባዋን እየጠራረኩ ወደ ጆሮዋ በመጠጋት አንድ ጥያቄ ብቻ ልጠይቅሽ ኤዱዬ አልኳት።
እሺ አለችኝ አፋን ስላፈንኳት ጭንቅላቷን እያወዛወዘች ።
አንዴ ልጩህ በናትሽ?????
💫ተፈፀመ💫
በአጨራረሱ ዙርያ ያላችሁን ሀሳብ አስተያየት በ @atronosebot በኩል እጠብቃለሁ።
#ሽንቁር
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
እያፈርኩ ለሰው አላወራውም እንጂ፣ ረዥም የትዝታ እጁን እየላከ፣ የዛሬ ኑሮዬን
የሚፈተፍትና ከአእምሮዬ የማይጠፋ አንድ ጉዳይ አለ፡፡ በየቀኑ በምክንያትም
ካለምክንያትም ውልብ እያለ ትዝ ሳይለኝ ውሎ አያውቅም፡፡ ቆይቷል ከዚያ ወዲህ ስንትና ስንት ነገር በዕድሜዬ ማገርና ቋሚ ላይ እንደ ጭቃ ተለስኖ፣ እንደ አሸዋና ስሚንቶ ተገርፎ፣ ደንዳና ወጣት ሆኛለሁ፡፡ ግን ያ ትዝታ ዛሬም ድረስ ከነትኩስነቱ፣ልቤን እንደ ቃልቻ ድቤ ከሚያስደልቃት ፍርሀት ከቀላቀለ ጉጉቱ ጋር በውስጤ ተዝናንቶ ተቀምጧል፡፡ ለማንም አላወራሁትም፤ እንኳንስ ለሌሎች ላወራው፣ ለራሴም እንደ ፎቶ
ካሜራ ብርሃን ብልጭ ከሚል ቅጽበት አልፎ በውስጤ ቃል ሆኖ እንዳይወለድ ፊት ነስቼው ነው የኖርኩት፡፡
ትምህርት ቤት የተዘጋበት የክረምት ወቅት ነበር፡፡ ያ ክረምት ከዚያ በፊት
እንዳሳለፍኳቸው የተለመዱ ዓይነት የክረምት ወቅቶች አልነበረም - ለእኔ፡፡ የሆነ ነገሬ ላይመለስ የተቀየረበት ክረምት ነበር፡፡ ከሰፈር ልጆች ጋር ተሰባስበን ጭቃውን ከሰማይ
እንደ ወረደ መና በጉጉት እያድበለበልን የምንወራወርበት ክረምት አልነበረም፣ በጭቃ እና በውሃ የላቆጠ ኳስ እየጠለዝን የምንጨዋወትበት ክረምት አልነበረም፡፡ በዚያ ክረምት የስምንተኛ ክፍል “ሚኒስትሪ” ፈተና ወስደን፣ ወደ ዘጠነኛ ክፍል የመሸጋገሪያ ወቅታችን ላይ ነበርን፡፡ በየክረምቱ የምናቋቁመውና በየዓመቱ እየፈረሰ እንደገና የምንመሠርተውን የእግር ኳስ ቡድን እንደገና ለመመሥረት ቸል ያልንበት ክረምት ነበር፡
ይልቅ ኳስ ተከትለው የሚቃብዙ፣ በድንጋይ መትተን የምናባርራቸውን ወፎች አንጋጠው በየዛፉና በየቤት ጣሪያ ላይ የሚፈልጉ፣ ዓይኖቻችን፤ ተልከው በሚያልፉና እኮዮቻችን በሚሆኑ ልጃገረዶች ላይ የሚንከራተቱበት፣ ከፍ ባሉና በደረሱ ሴቶች ላይ
የሚንከባለሉበት ልዩ ክረምት ነበር፡፡
እንዴት ነው ሦስት መቶ ስልሳ አምስት ቀናት ይኼን ሁሉ ለውጥ ያመጡብን!?
እንዲያውም ብዙዎቻችን በቁመትም በክብደትም ቅንጣት ታህል ጭማሬ ሳናሳይ፣ምናችን ነው እንዲህ ከውስጣችን ተቀይሮ አዲስ ዐመል ያሸከመን!? ዛሬም ድረስ የጉርምስናችን ቅኔ ለምን በዚያች ክረምት እንደተቀኜ፣ ባወጣ ባወርድ አልተገለጠልኝም ብቻ ስንጎረምስ ትዝ ይለኛል በዚያ ክረምት ነበር የጎረመስነው፡፡ ልክ ሰው ቁመቱ
ያደገባትን ቀን፣ ሰዓትና ደቂቃ ሂደቱን ሳይሆን ቅጽበቱን፣ እንደ ሬዲዮ አንቴና ድንገት ቁመቴ የተመዘዘባትን ቅጽበት አስታውሳታለሁ ቢል እንደሚገርመው፤ የጎረመስንባትን ጧት ማስታወሴ ይገርመኛል፡፡ እንግዲህ ተመልሼ ሳሰላው አሥራ ስድስት ዓመት ገደማ ሆነው ፡፡
አንድ ጧት፣ ፈተና እንደ ትላንት ጨርሰን እንደ ዛሬ፣ አባ ኃይሉ በረንዳ (አባ ኃይሉ፣
ሸገኔ ሱቅ የምትባለው ባለቤት ናቸው ... ከሱቋ ግራና ቀኝ ረዥም የግንብ ውሃ ልክ
ያላት፣ አንዳንዴ ሰው እንዳይቀመጥበት የተቃጠለ ጥቁር ነዳጅ የሚፈስበት ድድ ማስጫ ነገር) አምስት የምንሆን የሰፈር ልጆች (አዲስ ምልምል ጎረምሶች) ተቀምጠናል፡፡ አላፊ አግዳሚውን እየቃኘን ነበር፡፡ የዚያኑ ቀን ገና ዓይናችን በተአምር የበራልን ይመስል፣ሁሉን ነገር፣በተለይ ግን ሁሉን ሴት፣በተለይ ሁሉን ወጣት ሴት በጉጉት እንመለከታለን፡፡
እኛ ትምህርት ቤት ታጉረን ስንውል፣ ምን መድኃኒት ሲረጩባቸው ነው ሴቶቹ ሁሉ
እንዲህ ያማሩት!? ሳንል አልቀረንም! ... በሦስት መቶ ስልሳ አምስት ቀናት ምን የሚሉት ኬሚስትሪ በሰውነታቸው ውስጥ ቢቀናበር ነው፣ ቅልቦሽ ሲጫዎቱ የነበሩ የሰፈራችን ሴቶች እንዲህ ሙሉ ሴት ሆነው አረማመዳቸው ተቀይሮ ሽንጣቸው የሚመዘዘው?!..
ጡቶቻቸው ከፊት ቀድመው እየተንሳፈፉ አየር የሚያነፈነፉት? ለምንስ ነው የቡሄ ዳቦ ሲናጠቁን፣ ማስቲካና ከረሜላ እንድናካፍላቸው ሲለማመጡን እንዳልነበር ዓይናችንን
ማየት አፍረው በመሽኮርመም አየት የሚያደርጉንና ሳያናግሩን የሚያልፉት? በዚያ የዘነበው ዝናብ ምን ተአምር ተበጥብጦበት ነበር? ..
ያኔ ነው በማየት ሱስ ተለከፈን በበረንዳዋ ፍቅር የወደቅነው፡፡ ሕይወት ጦርነት ነው፣
አነሰም በዛም እኛም ወታደሮች፤ያች በረንዳ የወላጅና የበላዮቻችንን “አትንኩ!
አትቅመሱ!” ትእዛዝ በዓይንም ቢሆን ልንጥስ የከተምንባት ምሽጋችን ነበረች፡፡ ፀሐይ ገብታ ቀኑ ሊመሻሽ ሲል፣ ተሰባስበን በረንዳዋ ላይ እንኮለኮላለን (ኮልኮሌ ሁሉ! ይሉናል የበረንዳዋ ባለቤት አባ ሃይሌ)
ሰባተኛ ክፍል ሦስት ጊዜ ደግማ፣ “የማታ ትምርት” ቢሻላት ተብሎ የማታ ተማሪ
የሆነችው ህሊና የምትባለው የሰፈራችን ልጅ፣ አንዲት ደብተር በቄንጥ አንጠልጥላ ፣አቋሙ ከሚያምር ልጅ ጋር ወደ ትምህርት ቤት ስትሄድ አይተናል፡፡ ደግሞ ሲመሻሽ፣ሲራመድ ጎበጥ-ጎበጥ ከሚልና፣ በቁመት ከሚያንሳት ልጅ ጋር ከትምህርት ቤት ስትመለስ፣ ቀይ ብርሃን እየተፉ መንገዱን በቀይ ወጋገን በሚያጨቀዩት የመንገድ ዳር
መብራቶች የበለጠ አምራ አይተናል፡፡ በየቀኑ የሚወስዳት ሌላ፣ የሚመልሳት ሌላ ወንድ ሲንጋጋ ታዝበን “በትምህርቷ የሰነፈችው ከወንዶች ጋር እየተንዘላዘለች ነው” የሚባለውን የሰፈራችንን ሐሜት እውነት ነው ብለን አምነናል ደግሞ ሰሎሜ የምትባል ቆንጆ ቀይ ሴትዮ (ከሰፈራችን ነዋሪ ሁሉ ብቸኛ የመንግሥት ሥራ ያላትና ጉልበቷ ላይ የሚቆም
ጉርድ ቀሚስ የምትለብስ ባለትዳር ሴት) ከባሏ አስታጥቄ ጋር ከሥራ ሲመለሱ የዕለት ትዕይንታችን የዘወትር ግብአት ነበሩ! ሁልጊዜ በፌስታል የሆነ ነገር አንጠልጥለው ነበር ወደቤት የሚገቡት፡፡
ፍቅረኛሞች ከባለትዳሮች የሚለዩት፣ ወደ ቤት ሲገቡ አንዳች ነገር
በማንጠልጠል ሳይሆን አይቀርም!
ለእኔ ግን የዘወትር የዓይኖቼ ርሃብ አንዲት ሴት ነበረች፤ ፖሊስ ናት፡፡ ኢንስፔክተር
መንበረ የምትባል፡፡ ለምን እንደሆነ እንጃ፣ ያች ሴት ስታልፍ ካላየሁ፣ ቋጥኝ የሚያህል ድብርት ተጭኖኝ ነበር ወደ ቤቴ የምገባው፡፡ ደግነቱ ከሰፈራችን በላይ ከነበረው አራተኛ
ፖሊስ ጣቢያ፣ ልክ 1፡30 ሲሆን ወጥታ፣ በፈጣን እርምጃ በመንገዱ ማለፉ አይቀርም፡፡ የእግሮቿ ፍጥነት፣ ፊቷ ላይ
ሁልጊዜ የማይጠፋው ኮስታራነት እና፣ ሁልጊዜም ከሩቅ፣ዓይኔ ውስጥ ከምትገባበት ርቀት ጀምሮ፣ አልፋን ከዓይኔ እስከምትጠፋበት መታጠፊያ
ድረስ፣ የመንገዱን ግራ ይዛ ቀጥ ያለ መስመር ተከትላ መራመዷ፣ ተራማጅ ቅርፅ እንጂ ሰው መሆኗን ያጠራጥረኛል፣ሁልጊዜ መስመሯን አለመቀየሯ ይገርመኛል፡፡ አንዳንድ
ለሕዝብ ተብሎ በተሠራው መንገድ ላይ፣ ለሷ ብቻ ተብሎ ለሌሎች በማይታይ ሥውር ቀለም የተሰመረ የሐሳብ ሐዲድ ያለ እስኪመስለኝ እርምጃዋ ዝንፍ አይልም ሰዎች ሰላም ሲሏት(ሁልጊዜ ሰላም የሚሏት ሰዎች ይሽቆጠቆጣሉ) የእርምጃዋን ፍጥነት፣የፊቷንም ገጽታ ሳትቀይር፣ እጇን ብቻ በፍጥነት ከፍ አድርጋ እና አንገቷን ሰበር አድርጋ
ታልፋለች፡፡ ታዲያ ይህች ሴት እንደ ሰው እቤቷ ሄዳ አድራ የምትመጣ ሳይሆን፣
እንዲሁ በዚሁ እርምጃ ይህችኑ መስመር ተከትላ፣ ዓለም ጥግ ድረስ እየተራመደች፣ ዙራ ጧት በዚሁ የምትመለስ ዑደት ነገር ትመስለኝ ነበር፡፡
ኢንስፔክተር መንበረ ከብዙዎቹ ከማውቃቸው ሴቶች ረዘም ያለች፣ የፖሊስ ጉርድ ካኪ ቀሚስ፣ አንዳንዴም ሱሪ የምትለብስ፣ ሁለቱም የሚያምርባት፣ ቀጭን ወገቧ ላይ ሰፊ ብርማ የብረት ዘለበት ያለው የሸራ ቀበቶ የምትታጠቅ ቀበቶው ላይ በግራ በኩል( ሽጉጥ ከነማኅደሩ የሚንጠለጠልበት) ፀጉሯን ጠቅልላ ጀልባ የመሰለች የፖሊስ ኮፍያ
ጣል የምታደርግ፣ ዕድሜዋ ቢበዛ በሃያዎቹ መጨረሻ አልያም ሠላሳ የሚሆናት ሴት ነበረች መርማሪ ናት ይላሉ ለምን እንደሆነ
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
እያፈርኩ ለሰው አላወራውም እንጂ፣ ረዥም የትዝታ እጁን እየላከ፣ የዛሬ ኑሮዬን
የሚፈተፍትና ከአእምሮዬ የማይጠፋ አንድ ጉዳይ አለ፡፡ በየቀኑ በምክንያትም
ካለምክንያትም ውልብ እያለ ትዝ ሳይለኝ ውሎ አያውቅም፡፡ ቆይቷል ከዚያ ወዲህ ስንትና ስንት ነገር በዕድሜዬ ማገርና ቋሚ ላይ እንደ ጭቃ ተለስኖ፣ እንደ አሸዋና ስሚንቶ ተገርፎ፣ ደንዳና ወጣት ሆኛለሁ፡፡ ግን ያ ትዝታ ዛሬም ድረስ ከነትኩስነቱ፣ልቤን እንደ ቃልቻ ድቤ ከሚያስደልቃት ፍርሀት ከቀላቀለ ጉጉቱ ጋር በውስጤ ተዝናንቶ ተቀምጧል፡፡ ለማንም አላወራሁትም፤ እንኳንስ ለሌሎች ላወራው፣ ለራሴም እንደ ፎቶ
ካሜራ ብርሃን ብልጭ ከሚል ቅጽበት አልፎ በውስጤ ቃል ሆኖ እንዳይወለድ ፊት ነስቼው ነው የኖርኩት፡፡
ትምህርት ቤት የተዘጋበት የክረምት ወቅት ነበር፡፡ ያ ክረምት ከዚያ በፊት
እንዳሳለፍኳቸው የተለመዱ ዓይነት የክረምት ወቅቶች አልነበረም - ለእኔ፡፡ የሆነ ነገሬ ላይመለስ የተቀየረበት ክረምት ነበር፡፡ ከሰፈር ልጆች ጋር ተሰባስበን ጭቃውን ከሰማይ
እንደ ወረደ መና በጉጉት እያድበለበልን የምንወራወርበት ክረምት አልነበረም፣ በጭቃ እና በውሃ የላቆጠ ኳስ እየጠለዝን የምንጨዋወትበት ክረምት አልነበረም፡፡ በዚያ ክረምት የስምንተኛ ክፍል “ሚኒስትሪ” ፈተና ወስደን፣ ወደ ዘጠነኛ ክፍል የመሸጋገሪያ ወቅታችን ላይ ነበርን፡፡ በየክረምቱ የምናቋቁመውና በየዓመቱ እየፈረሰ እንደገና የምንመሠርተውን የእግር ኳስ ቡድን እንደገና ለመመሥረት ቸል ያልንበት ክረምት ነበር፡
ይልቅ ኳስ ተከትለው የሚቃብዙ፣ በድንጋይ መትተን የምናባርራቸውን ወፎች አንጋጠው በየዛፉና በየቤት ጣሪያ ላይ የሚፈልጉ፣ ዓይኖቻችን፤ ተልከው በሚያልፉና እኮዮቻችን በሚሆኑ ልጃገረዶች ላይ የሚንከራተቱበት፣ ከፍ ባሉና በደረሱ ሴቶች ላይ
የሚንከባለሉበት ልዩ ክረምት ነበር፡፡
እንዴት ነው ሦስት መቶ ስልሳ አምስት ቀናት ይኼን ሁሉ ለውጥ ያመጡብን!?
እንዲያውም ብዙዎቻችን በቁመትም በክብደትም ቅንጣት ታህል ጭማሬ ሳናሳይ፣ምናችን ነው እንዲህ ከውስጣችን ተቀይሮ አዲስ ዐመል ያሸከመን!? ዛሬም ድረስ የጉርምስናችን ቅኔ ለምን በዚያች ክረምት እንደተቀኜ፣ ባወጣ ባወርድ አልተገለጠልኝም ብቻ ስንጎረምስ ትዝ ይለኛል በዚያ ክረምት ነበር የጎረመስነው፡፡ ልክ ሰው ቁመቱ
ያደገባትን ቀን፣ ሰዓትና ደቂቃ ሂደቱን ሳይሆን ቅጽበቱን፣ እንደ ሬዲዮ አንቴና ድንገት ቁመቴ የተመዘዘባትን ቅጽበት አስታውሳታለሁ ቢል እንደሚገርመው፤ የጎረመስንባትን ጧት ማስታወሴ ይገርመኛል፡፡ እንግዲህ ተመልሼ ሳሰላው አሥራ ስድስት ዓመት ገደማ ሆነው ፡፡
አንድ ጧት፣ ፈተና እንደ ትላንት ጨርሰን እንደ ዛሬ፣ አባ ኃይሉ በረንዳ (አባ ኃይሉ፣
ሸገኔ ሱቅ የምትባለው ባለቤት ናቸው ... ከሱቋ ግራና ቀኝ ረዥም የግንብ ውሃ ልክ
ያላት፣ አንዳንዴ ሰው እንዳይቀመጥበት የተቃጠለ ጥቁር ነዳጅ የሚፈስበት ድድ ማስጫ ነገር) አምስት የምንሆን የሰፈር ልጆች (አዲስ ምልምል ጎረምሶች) ተቀምጠናል፡፡ አላፊ አግዳሚውን እየቃኘን ነበር፡፡ የዚያኑ ቀን ገና ዓይናችን በተአምር የበራልን ይመስል፣ሁሉን ነገር፣በተለይ ግን ሁሉን ሴት፣በተለይ ሁሉን ወጣት ሴት በጉጉት እንመለከታለን፡፡
እኛ ትምህርት ቤት ታጉረን ስንውል፣ ምን መድኃኒት ሲረጩባቸው ነው ሴቶቹ ሁሉ
እንዲህ ያማሩት!? ሳንል አልቀረንም! ... በሦስት መቶ ስልሳ አምስት ቀናት ምን የሚሉት ኬሚስትሪ በሰውነታቸው ውስጥ ቢቀናበር ነው፣ ቅልቦሽ ሲጫዎቱ የነበሩ የሰፈራችን ሴቶች እንዲህ ሙሉ ሴት ሆነው አረማመዳቸው ተቀይሮ ሽንጣቸው የሚመዘዘው?!..
ጡቶቻቸው ከፊት ቀድመው እየተንሳፈፉ አየር የሚያነፈነፉት? ለምንስ ነው የቡሄ ዳቦ ሲናጠቁን፣ ማስቲካና ከረሜላ እንድናካፍላቸው ሲለማመጡን እንዳልነበር ዓይናችንን
ማየት አፍረው በመሽኮርመም አየት የሚያደርጉንና ሳያናግሩን የሚያልፉት? በዚያ የዘነበው ዝናብ ምን ተአምር ተበጥብጦበት ነበር? ..
ያኔ ነው በማየት ሱስ ተለከፈን በበረንዳዋ ፍቅር የወደቅነው፡፡ ሕይወት ጦርነት ነው፣
አነሰም በዛም እኛም ወታደሮች፤ያች በረንዳ የወላጅና የበላዮቻችንን “አትንኩ!
አትቅመሱ!” ትእዛዝ በዓይንም ቢሆን ልንጥስ የከተምንባት ምሽጋችን ነበረች፡፡ ፀሐይ ገብታ ቀኑ ሊመሻሽ ሲል፣ ተሰባስበን በረንዳዋ ላይ እንኮለኮላለን (ኮልኮሌ ሁሉ! ይሉናል የበረንዳዋ ባለቤት አባ ሃይሌ)
ሰባተኛ ክፍል ሦስት ጊዜ ደግማ፣ “የማታ ትምርት” ቢሻላት ተብሎ የማታ ተማሪ
የሆነችው ህሊና የምትባለው የሰፈራችን ልጅ፣ አንዲት ደብተር በቄንጥ አንጠልጥላ ፣አቋሙ ከሚያምር ልጅ ጋር ወደ ትምህርት ቤት ስትሄድ አይተናል፡፡ ደግሞ ሲመሻሽ፣ሲራመድ ጎበጥ-ጎበጥ ከሚልና፣ በቁመት ከሚያንሳት ልጅ ጋር ከትምህርት ቤት ስትመለስ፣ ቀይ ብርሃን እየተፉ መንገዱን በቀይ ወጋገን በሚያጨቀዩት የመንገድ ዳር
መብራቶች የበለጠ አምራ አይተናል፡፡ በየቀኑ የሚወስዳት ሌላ፣ የሚመልሳት ሌላ ወንድ ሲንጋጋ ታዝበን “በትምህርቷ የሰነፈችው ከወንዶች ጋር እየተንዘላዘለች ነው” የሚባለውን የሰፈራችንን ሐሜት እውነት ነው ብለን አምነናል ደግሞ ሰሎሜ የምትባል ቆንጆ ቀይ ሴትዮ (ከሰፈራችን ነዋሪ ሁሉ ብቸኛ የመንግሥት ሥራ ያላትና ጉልበቷ ላይ የሚቆም
ጉርድ ቀሚስ የምትለብስ ባለትዳር ሴት) ከባሏ አስታጥቄ ጋር ከሥራ ሲመለሱ የዕለት ትዕይንታችን የዘወትር ግብአት ነበሩ! ሁልጊዜ በፌስታል የሆነ ነገር አንጠልጥለው ነበር ወደቤት የሚገቡት፡፡
ፍቅረኛሞች ከባለትዳሮች የሚለዩት፣ ወደ ቤት ሲገቡ አንዳች ነገር
በማንጠልጠል ሳይሆን አይቀርም!
ለእኔ ግን የዘወትር የዓይኖቼ ርሃብ አንዲት ሴት ነበረች፤ ፖሊስ ናት፡፡ ኢንስፔክተር
መንበረ የምትባል፡፡ ለምን እንደሆነ እንጃ፣ ያች ሴት ስታልፍ ካላየሁ፣ ቋጥኝ የሚያህል ድብርት ተጭኖኝ ነበር ወደ ቤቴ የምገባው፡፡ ደግነቱ ከሰፈራችን በላይ ከነበረው አራተኛ
ፖሊስ ጣቢያ፣ ልክ 1፡30 ሲሆን ወጥታ፣ በፈጣን እርምጃ በመንገዱ ማለፉ አይቀርም፡፡ የእግሮቿ ፍጥነት፣ ፊቷ ላይ
ሁልጊዜ የማይጠፋው ኮስታራነት እና፣ ሁልጊዜም ከሩቅ፣ዓይኔ ውስጥ ከምትገባበት ርቀት ጀምሮ፣ አልፋን ከዓይኔ እስከምትጠፋበት መታጠፊያ
ድረስ፣ የመንገዱን ግራ ይዛ ቀጥ ያለ መስመር ተከትላ መራመዷ፣ ተራማጅ ቅርፅ እንጂ ሰው መሆኗን ያጠራጥረኛል፣ሁልጊዜ መስመሯን አለመቀየሯ ይገርመኛል፡፡ አንዳንድ
ለሕዝብ ተብሎ በተሠራው መንገድ ላይ፣ ለሷ ብቻ ተብሎ ለሌሎች በማይታይ ሥውር ቀለም የተሰመረ የሐሳብ ሐዲድ ያለ እስኪመስለኝ እርምጃዋ ዝንፍ አይልም ሰዎች ሰላም ሲሏት(ሁልጊዜ ሰላም የሚሏት ሰዎች ይሽቆጠቆጣሉ) የእርምጃዋን ፍጥነት፣የፊቷንም ገጽታ ሳትቀይር፣ እጇን ብቻ በፍጥነት ከፍ አድርጋ እና አንገቷን ሰበር አድርጋ
ታልፋለች፡፡ ታዲያ ይህች ሴት እንደ ሰው እቤቷ ሄዳ አድራ የምትመጣ ሳይሆን፣
እንዲሁ በዚሁ እርምጃ ይህችኑ መስመር ተከትላ፣ ዓለም ጥግ ድረስ እየተራመደች፣ ዙራ ጧት በዚሁ የምትመለስ ዑደት ነገር ትመስለኝ ነበር፡፡
ኢንስፔክተር መንበረ ከብዙዎቹ ከማውቃቸው ሴቶች ረዘም ያለች፣ የፖሊስ ጉርድ ካኪ ቀሚስ፣ አንዳንዴም ሱሪ የምትለብስ፣ ሁለቱም የሚያምርባት፣ ቀጭን ወገቧ ላይ ሰፊ ብርማ የብረት ዘለበት ያለው የሸራ ቀበቶ የምትታጠቅ ቀበቶው ላይ በግራ በኩል( ሽጉጥ ከነማኅደሩ የሚንጠለጠልበት) ፀጉሯን ጠቅልላ ጀልባ የመሰለች የፖሊስ ኮፍያ
ጣል የምታደርግ፣ ዕድሜዋ ቢበዛ በሃያዎቹ መጨረሻ አልያም ሠላሳ የሚሆናት ሴት ነበረች መርማሪ ናት ይላሉ ለምን እንደሆነ
👍1
እንጃ፣ የእግሮቿን ጥርት ያለ ጠይምነት እና፣ የፖሊስ ዩኒፎርሟን ንጽሕና ስመለከት፣ ያውም ከነማዕረጓና ከነሽጉጧ፣ የፖሊስ
ልብስ መልበሷን እያየሁ እንኳን፣ ለእኔ ግን ነርስ ትመስለኛለች፤ የምትመረምረው
በሽተኞችን ይመስለኛል፡፡ እሷን ማየት ነበር ሱሴ፡፡
የሁላችንም ቤተሰቦች እዚያች በረንዳ ላይ መሰብሰባችንን አይወዱትም፡፡ ሂዱና የአባ
ኃይሌን በረንዳ አሙቁ” እያሉ ይነጫነጩብናል! በተለይ የእኔ እናት “ተጎርምሶ ተሞተ!
የማንም ዱርዬና ሌባ መሰብሰቢያ በረንዳ ላይ መሄድህን ተው ብያለሁ፣ ኋላ አንዲት ነገር እሰማና፣ ውርድ ከራሴ!” ትለኛለች፡፡ መልስ አልሰጣትም፡፡ ሲመሻሽ ከጓደኞቼ ጋር እዚያው ነኝ፡፡ የሱቁ ባለቤት አባ ኃይሌ አጭር፣ ክብ የቴክሳስ ኮፍያ የሚደፉና ባለቀጭን ጥለት ነጠላ የማይለያቸው ኮስታራ ሽማግሌ ናቸው፡፡ ኮስታራ ብቻ አይደሉም፣ ነጭናጫም ጭምር ናቸው፡፡ ወርቃማ እጄታ ያላትን የምታምር ከዘራቸውን ክንዳቸው ላይ አንጠልጥለው (ሁልጊዜ አይመረኮዙባትም) የሱቋን ዙሪያ ይቃኛሉ፡፡
በተለይ ከጎረቤት ጋር የምታወስነዋን ድንበር በጥንቃቄ ነው የሚመረመሯት፡፡ በዚሁ ድንበር ብዙ ዓመት ፍርድ ቤት ተመላልሰዋል፡፡ (ጉቦ ሰጥተው ነው ያሸነፉት እንጂ ሱቁ የተሠራበት ግማሽ ቦታ ጭምር የቅመም ሻጩ ጎረቤታቸው የጋሽ ውበቱ ድንበር ነበር
እየተባለ ይታማል)
ኧረ በሕግ አምላክ ወዲያ ሂዱልኝ እናንተ ልጆች!…በሩ ላይ ተኮልኩላችሁ ገበየተኛው በየት በኩል አልፎ ይገበያይ"?ይላሉ:: ድምፃቸው ከዚያች አጭር ሰውነት የሚወጣ አይመስልም፣ አስገምጋሚ ነው፡፡ ለዓይናቸው አይወዱንም፡፡ ወዲያው ከፊታቸው ዞር
እንልና በቀጣዩ ቀን ግን እዚያው ነን፡፡ በረንዳቸው ላይ መቀመጣችንን እንደማይወዱት እናውቃለን፡፡ እንዲያውም በየጊዜው የተቃጠለ ነዳጅ ከጋራዥ እያስመጡ ግንቡ ላይ ያስፈስሱበታል፡፡ ግን ምን ዋጋ አለው፣ መቀመጡ ይቀራል እንጂ እዛው ቁመን የዕለት
ሱሳችንን ማድረሳችን አይቀርም፡፡ ዛሬም ድረስ ሱቁ ፈርሶ ትልቅ ሕንጻ ተሠርቶበት፣
ከሕንጻው መስተዋቶችና መግቢያው ላይ ከሚኮለኮሉት የሀብታም መኪኖች ይልቅ፣ ያች ጉርምስናችን ተወልዳ እትብቷ የተቀበረበት፣ ነዳጅ ያጠቆራት በረንዳ ገዝፋ ትታወሰኛለች፡፡ ዛሬ ወደ ሕንጻው ጎራ ከሚሉ በመዋቢያና በውድ ልብሶች ከተሸቀረቀ ሀብታምና ውብ ሴቶች ይልቅ፣ ያኔ የሻይ ቅጠልና ቡና ሊገዙ ከመንደሮቹ ውስጥ ወደ ሸገኔ ሱቅ ብቅ የሚሉ የተፈጥሮ ለዛቸው ከዕድሜ ትኩሳታቸው ጋር ከሩቅ የሚጣራ ወጣት ሴቶች ትዝ ይሉኛል፡፡መቼስ ለትዝታ ሩቅ የሚባል ..ላለመድረስ ከፈለጉም
ቅርብ የሚባል ቦታ የለም፡፡
አንድ ምሽት እንደ ልማዳችን አባ ኃይሌ በረንዳ ላይ ተኮልኩለን የባጥ የቆጡን
እናወራለን፡፡ እያወራን፣ የሌሎቹን እንጃ፣ እኔ ግን በዓይኔ ኢንስፔክተር መንበረን
እጠብቃለሁ፡፡ ቀኑን ሙሉ የክረምት የማይመስል ኃይለኛ ፀሐይ ወጥቶ ስለነበር፣ የተቀመጥንበት ግንብ እንደወትሮው አይቀዘቅዝም፡፡ የበረንዳው ውሃ ልክ ከሰዓት በኋላ የማታ ፀሐይ ሲቀጠቅጠው ስለሚውል ሁልጊዜም ለሰስ ያለ ሙቀት ነበረው፡፡ እሱም
ይሆናል አንዱ ምቾታችን፡፡ የምናወራውን እንጃ ብቻ የሞቀ ወሬ ላይ ነበርን፡፡ ድንገት
እዚያው አጠገባችን የአንዲት ሴት ኡኡታ አካባቢውን አደበላለቀው፡፡ “ኡኡኡኡ
ተዘረፍኩ! ጉድ ሆንኩ! ሌባ ሌባ ሌባ …” የባህል ቀሚስ የለበሱ ወፍራም ሴት ነበሩ፡፡ከዛ ወፍራም ሰውነት እንደዛ ጆሮ የሚወጋ ቀጭን ድምፅ መውጣቱ ይገርማል፡፡ ደግሞ እሪታቸው መርዘሙ እልልታ ነበር የሚመስለው፡፡ ሰው የሚጮሁትን ሴትዮ ከበው በጥያቄ ያጣድፏቸው ገባ
“ምንድነው?” “ሌባውን አይተሽዋል?” ሴትዮዋ ለቅሶ በተቀላቀለበት ድምፅ እየጮሁ፣ እኛ ወደተቀመጥንበት ጠቁመው፡፡
“ቦርሳዬን ቀምቶኝ ሮጠ አይቼዋለሁ፣ ተነሱ መኻል ነው ተነስቶ የመጣው አሉ፡፡
እግዚኦ!! የተሰበሰበው ሕዝብ እንዳለ ወደኛ ዞረ፡፡ እኔ እንደ በረዶ ገግሬ ከተቀመጥኩበት እንኳን መነቃነቅ አቃተኝ፡፡
አንድ ሽበታም ሰውዬ “ያዙዋቸው! ወመኔ ሁሉ!” ብለው ፉከራ በሚመስል ድምፅ
ሲጮሁ፣ ጓደኞቼ እንደ አንዳች ነገር ከጎኔ እየተስፈነጠሩ እግራቸው ወደ መራቸው
ተፈተለኩ፡፡ አንዱ ጓደኛችን፣ እንዲያውም መንገዱን አቋርጦ ሲሮጥ፣ እየተግለበለበ የሚያልፍ ታክሲ ሊገጨው ለጥቂት ተረፈ… ሲጢጢጢ! የሚል የመኪና ጎማ ድምፅ ከሰው ጫጫታ ጋር ተዳምሮ፣ አካባቢው ባንዴ በጩኸት ተደበላለቀ፡፡
በደነዘዝኩበት አንድ ጠንካራና የሚሞቅ እጅ፣ ከእጅጌ ጉርድ “ቲሸርቴ” ሥር ራቁት ክንዴን አፈፍ ሲያደርገኝ፣ ቀና ብዬ የያዘኝን ሰው ተመለከትኩ ..ኢንስፔክተር መንበረ ነበረች።መያዜም ሳይሆን፣ ጩኸቱም ሳይሆን፣ ኢንስፔክተር መንበረ ሐዲዷን ስታ እኔ አጠገብ መቆሟ ትንግርት ሆነብኝ ….ምድር ምህዋሯን ሳተች የተባልኩ ይመስል፡፡
ማመን አልቻልኩም፡፡ ከዚያች ቀን በፊት፣ እንኳን መታሰር፣ የታሰረ ሰው ለመጠየቅ
ፖሊስ ጣቢያ ደጅ ረግጨ አላውቅም ነበር፡፡ ኢንስፔክተር መንበረ ክንዴን አጥብቃ እንደያዘችኝ ከሰፈራችን አለፍ ብሎ ወደሚገኘው አራተኛ ፖሊስ ጣቢያ ስትወስደኝ፣ ዙሬ እንኳን ላያት ፈራሁ፡፡ አቀርቅሬ ተራ በተራ በፍጥነት በአስፋልት መንገዱ ላይ የሚያርፉትን ተወልውለው የሚያንጸባርቁ ጉርድ ጥቁር ቆዳ ጫማዎቿን እያየሁ፣ ከጎኗ
ሱክ ሱክ እላለሁ፡፡ በሰፋፊው ነው የምትራመደው፡፡ ፖሊስ ጣቢያው የተመሠረተው፣አንድ ሲያዩት የሚጨንቅ፣ ሙሉውን ከድንጋይና ከሰፋፊ ጣውላ የተሠራ የድሮ ቤት ውስጥ ነበር፡፡ የአንድ ቀኝ አዝማች ይሁኑ ግራ አዝማች መኖሪያ ቤት የነበረና፣ በደርግ ዘመን የተወረሰ ነው ይባላል፡፡ ሰውዬው ይሄን ቤት ተወረስኩ ብለው፣ በደም ግፊት ይሁን በልብ ድካም እንደሞቱ ይነገራል፡፡ የልብ ምቴን ሳዳምጥ ይኼ ገፊ ቤት እኔንም እንደ ባለቤቱ ሊደፋኝ ይሆን ብዬ ሰጋሁ፡፡ ከእርጅናው ብዛት የተነሳ የወለሉ ንጣፍ..
💫ይቀጥላል💫
ልብስ መልበሷን እያየሁ እንኳን፣ ለእኔ ግን ነርስ ትመስለኛለች፤ የምትመረምረው
በሽተኞችን ይመስለኛል፡፡ እሷን ማየት ነበር ሱሴ፡፡
የሁላችንም ቤተሰቦች እዚያች በረንዳ ላይ መሰብሰባችንን አይወዱትም፡፡ ሂዱና የአባ
ኃይሌን በረንዳ አሙቁ” እያሉ ይነጫነጩብናል! በተለይ የእኔ እናት “ተጎርምሶ ተሞተ!
የማንም ዱርዬና ሌባ መሰብሰቢያ በረንዳ ላይ መሄድህን ተው ብያለሁ፣ ኋላ አንዲት ነገር እሰማና፣ ውርድ ከራሴ!” ትለኛለች፡፡ መልስ አልሰጣትም፡፡ ሲመሻሽ ከጓደኞቼ ጋር እዚያው ነኝ፡፡ የሱቁ ባለቤት አባ ኃይሌ አጭር፣ ክብ የቴክሳስ ኮፍያ የሚደፉና ባለቀጭን ጥለት ነጠላ የማይለያቸው ኮስታራ ሽማግሌ ናቸው፡፡ ኮስታራ ብቻ አይደሉም፣ ነጭናጫም ጭምር ናቸው፡፡ ወርቃማ እጄታ ያላትን የምታምር ከዘራቸውን ክንዳቸው ላይ አንጠልጥለው (ሁልጊዜ አይመረኮዙባትም) የሱቋን ዙሪያ ይቃኛሉ፡፡
በተለይ ከጎረቤት ጋር የምታወስነዋን ድንበር በጥንቃቄ ነው የሚመረመሯት፡፡ በዚሁ ድንበር ብዙ ዓመት ፍርድ ቤት ተመላልሰዋል፡፡ (ጉቦ ሰጥተው ነው ያሸነፉት እንጂ ሱቁ የተሠራበት ግማሽ ቦታ ጭምር የቅመም ሻጩ ጎረቤታቸው የጋሽ ውበቱ ድንበር ነበር
እየተባለ ይታማል)
ኧረ በሕግ አምላክ ወዲያ ሂዱልኝ እናንተ ልጆች!…በሩ ላይ ተኮልኩላችሁ ገበየተኛው በየት በኩል አልፎ ይገበያይ"?ይላሉ:: ድምፃቸው ከዚያች አጭር ሰውነት የሚወጣ አይመስልም፣ አስገምጋሚ ነው፡፡ ለዓይናቸው አይወዱንም፡፡ ወዲያው ከፊታቸው ዞር
እንልና በቀጣዩ ቀን ግን እዚያው ነን፡፡ በረንዳቸው ላይ መቀመጣችንን እንደማይወዱት እናውቃለን፡፡ እንዲያውም በየጊዜው የተቃጠለ ነዳጅ ከጋራዥ እያስመጡ ግንቡ ላይ ያስፈስሱበታል፡፡ ግን ምን ዋጋ አለው፣ መቀመጡ ይቀራል እንጂ እዛው ቁመን የዕለት
ሱሳችንን ማድረሳችን አይቀርም፡፡ ዛሬም ድረስ ሱቁ ፈርሶ ትልቅ ሕንጻ ተሠርቶበት፣
ከሕንጻው መስተዋቶችና መግቢያው ላይ ከሚኮለኮሉት የሀብታም መኪኖች ይልቅ፣ ያች ጉርምስናችን ተወልዳ እትብቷ የተቀበረበት፣ ነዳጅ ያጠቆራት በረንዳ ገዝፋ ትታወሰኛለች፡፡ ዛሬ ወደ ሕንጻው ጎራ ከሚሉ በመዋቢያና በውድ ልብሶች ከተሸቀረቀ ሀብታምና ውብ ሴቶች ይልቅ፣ ያኔ የሻይ ቅጠልና ቡና ሊገዙ ከመንደሮቹ ውስጥ ወደ ሸገኔ ሱቅ ብቅ የሚሉ የተፈጥሮ ለዛቸው ከዕድሜ ትኩሳታቸው ጋር ከሩቅ የሚጣራ ወጣት ሴቶች ትዝ ይሉኛል፡፡መቼስ ለትዝታ ሩቅ የሚባል ..ላለመድረስ ከፈለጉም
ቅርብ የሚባል ቦታ የለም፡፡
አንድ ምሽት እንደ ልማዳችን አባ ኃይሌ በረንዳ ላይ ተኮልኩለን የባጥ የቆጡን
እናወራለን፡፡ እያወራን፣ የሌሎቹን እንጃ፣ እኔ ግን በዓይኔ ኢንስፔክተር መንበረን
እጠብቃለሁ፡፡ ቀኑን ሙሉ የክረምት የማይመስል ኃይለኛ ፀሐይ ወጥቶ ስለነበር፣ የተቀመጥንበት ግንብ እንደወትሮው አይቀዘቅዝም፡፡ የበረንዳው ውሃ ልክ ከሰዓት በኋላ የማታ ፀሐይ ሲቀጠቅጠው ስለሚውል ሁልጊዜም ለሰስ ያለ ሙቀት ነበረው፡፡ እሱም
ይሆናል አንዱ ምቾታችን፡፡ የምናወራውን እንጃ ብቻ የሞቀ ወሬ ላይ ነበርን፡፡ ድንገት
እዚያው አጠገባችን የአንዲት ሴት ኡኡታ አካባቢውን አደበላለቀው፡፡ “ኡኡኡኡ
ተዘረፍኩ! ጉድ ሆንኩ! ሌባ ሌባ ሌባ …” የባህል ቀሚስ የለበሱ ወፍራም ሴት ነበሩ፡፡ከዛ ወፍራም ሰውነት እንደዛ ጆሮ የሚወጋ ቀጭን ድምፅ መውጣቱ ይገርማል፡፡ ደግሞ እሪታቸው መርዘሙ እልልታ ነበር የሚመስለው፡፡ ሰው የሚጮሁትን ሴትዮ ከበው በጥያቄ ያጣድፏቸው ገባ
“ምንድነው?” “ሌባውን አይተሽዋል?” ሴትዮዋ ለቅሶ በተቀላቀለበት ድምፅ እየጮሁ፣ እኛ ወደተቀመጥንበት ጠቁመው፡፡
“ቦርሳዬን ቀምቶኝ ሮጠ አይቼዋለሁ፣ ተነሱ መኻል ነው ተነስቶ የመጣው አሉ፡፡
እግዚኦ!! የተሰበሰበው ሕዝብ እንዳለ ወደኛ ዞረ፡፡ እኔ እንደ በረዶ ገግሬ ከተቀመጥኩበት እንኳን መነቃነቅ አቃተኝ፡፡
አንድ ሽበታም ሰውዬ “ያዙዋቸው! ወመኔ ሁሉ!” ብለው ፉከራ በሚመስል ድምፅ
ሲጮሁ፣ ጓደኞቼ እንደ አንዳች ነገር ከጎኔ እየተስፈነጠሩ እግራቸው ወደ መራቸው
ተፈተለኩ፡፡ አንዱ ጓደኛችን፣ እንዲያውም መንገዱን አቋርጦ ሲሮጥ፣ እየተግለበለበ የሚያልፍ ታክሲ ሊገጨው ለጥቂት ተረፈ… ሲጢጢጢ! የሚል የመኪና ጎማ ድምፅ ከሰው ጫጫታ ጋር ተዳምሮ፣ አካባቢው ባንዴ በጩኸት ተደበላለቀ፡፡
በደነዘዝኩበት አንድ ጠንካራና የሚሞቅ እጅ፣ ከእጅጌ ጉርድ “ቲሸርቴ” ሥር ራቁት ክንዴን አፈፍ ሲያደርገኝ፣ ቀና ብዬ የያዘኝን ሰው ተመለከትኩ ..ኢንስፔክተር መንበረ ነበረች።መያዜም ሳይሆን፣ ጩኸቱም ሳይሆን፣ ኢንስፔክተር መንበረ ሐዲዷን ስታ እኔ አጠገብ መቆሟ ትንግርት ሆነብኝ ….ምድር ምህዋሯን ሳተች የተባልኩ ይመስል፡፡
ማመን አልቻልኩም፡፡ ከዚያች ቀን በፊት፣ እንኳን መታሰር፣ የታሰረ ሰው ለመጠየቅ
ፖሊስ ጣቢያ ደጅ ረግጨ አላውቅም ነበር፡፡ ኢንስፔክተር መንበረ ክንዴን አጥብቃ እንደያዘችኝ ከሰፈራችን አለፍ ብሎ ወደሚገኘው አራተኛ ፖሊስ ጣቢያ ስትወስደኝ፣ ዙሬ እንኳን ላያት ፈራሁ፡፡ አቀርቅሬ ተራ በተራ በፍጥነት በአስፋልት መንገዱ ላይ የሚያርፉትን ተወልውለው የሚያንጸባርቁ ጉርድ ጥቁር ቆዳ ጫማዎቿን እያየሁ፣ ከጎኗ
ሱክ ሱክ እላለሁ፡፡ በሰፋፊው ነው የምትራመደው፡፡ ፖሊስ ጣቢያው የተመሠረተው፣አንድ ሲያዩት የሚጨንቅ፣ ሙሉውን ከድንጋይና ከሰፋፊ ጣውላ የተሠራ የድሮ ቤት ውስጥ ነበር፡፡ የአንድ ቀኝ አዝማች ይሁኑ ግራ አዝማች መኖሪያ ቤት የነበረና፣ በደርግ ዘመን የተወረሰ ነው ይባላል፡፡ ሰውዬው ይሄን ቤት ተወረስኩ ብለው፣ በደም ግፊት ይሁን በልብ ድካም እንደሞቱ ይነገራል፡፡ የልብ ምቴን ሳዳምጥ ይኼ ገፊ ቤት እኔንም እንደ ባለቤቱ ሊደፋኝ ይሆን ብዬ ሰጋሁ፡፡ ከእርጅናው ብዛት የተነሳ የወለሉ ንጣፍ..
💫ይቀጥላል💫
#ጨለማ_እና_ብርሐን
ተፈጥራዊውን ሐቅ በውል ሳያስሰው
ውስብስቡን ምስጢር በወግ ሳይዳስሰው
የብርሃንን ሐይል ከፅልመት ሲያረክሰው
ፋይዳ ቢስ አርጉ ዋጋ ሲያሳንሰው
ማሾ ይዞ ወጣ ሰው የቸገረው ሰው።
እውነት በሌለበት
በገበያ ሥፍራ ከሚርመሰመሰው
ሳያገኝ ቀረና እንድ እውነተኛ ሰው
እውነት የጠፋበት
እውነቱን ፈላጊ ተቆጥሮእንደዘበት
ገብያተኛው ሁሉ በሳቅ አፌዘበት ።
ከሀቅ ያለያያል
እንደቂል ያሳያል ገበያ መሐል ላይ
የማሾ ብርሐን በጠራራ ፀሐይ።
ረቂቅ እውነቱ የብርሐን ውበት
ጎልቶ የሚወጣበት ደምቆ የሚታይበት
ነፍስ የሚዘራበት የሚሰጠው ሕይወት
ጨለማው እኮ ነው ድቅድቁ መስታወት።
ተፈጥራዊውን ሐቅ በውል ሳያስሰው
ውስብስቡን ምስጢር በወግ ሳይዳስሰው
የብርሃንን ሐይል ከፅልመት ሲያረክሰው
ፋይዳ ቢስ አርጉ ዋጋ ሲያሳንሰው
ማሾ ይዞ ወጣ ሰው የቸገረው ሰው።
እውነት በሌለበት
በገበያ ሥፍራ ከሚርመሰመሰው
ሳያገኝ ቀረና እንድ እውነተኛ ሰው
እውነት የጠፋበት
እውነቱን ፈላጊ ተቆጥሮእንደዘበት
ገብያተኛው ሁሉ በሳቅ አፌዘበት ።
ከሀቅ ያለያያል
እንደቂል ያሳያል ገበያ መሐል ላይ
የማሾ ብርሐን በጠራራ ፀሐይ።
ረቂቅ እውነቱ የብርሐን ውበት
ጎልቶ የሚወጣበት ደምቆ የሚታይበት
ነፍስ የሚዘራበት የሚሰጠው ሕይወት
ጨለማው እኮ ነው ድቅድቁ መስታወት።
❤1👍1
#ሽንቁር
፡
፡
#ክፍል_ሁለት(የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
...የወለሉ ንጣፍ ጣውላ ሲረግጡት፣ እሪታው ሌላ ሰፈር ድረስ የሚሰማ ይመስላል፡፡ ኢንስፔክተር መንበረ አንድም ቃል ሳትናገር፣ ክንዴን እንደያዘችኝ ነበር ከኋላ ከነ አጀበኝ የሕዝብ አጀብ ፖሊስ ጣቢያ የደረስነው፡፡ በሩ ላይ ስንደርስ፣ ቀጥ ብሎ ቆሞ ሰላምታ ለሰጣት
ፖሊስ “አስገባቸው” አለችው።
“እሺ! አስገባቸዋለሁ ኢንስፔክተር” አለ፡፡ ድምፁ ስልል ያለና አስፈሪ ነው “እሺ! ወደ ሲኤል እወረውራቸዋለሁ!” የሚል የሲኦል በር ጠባቂ ነበር የሚመስለው፡፡ እኔ ግን አስገባቸው?” ብዬ ዞር ስል፣ ለካስ ብቻዬን አልነበርኩም፤ እስካድማስ የሚባል የሰፈሬ ልጅም ተይዟል፡፡ ፖሊሱ ከኢንስፔክተር መንበረ ተቀብሎ፣ ከሷም በጠበቀ አያያዝ ክንዳችንን ጨምድዶ እያመናጨቀ፣ በሚንቋቋው አሮጌ የጣውላ ደረጃ ቁልቁል ወሰደና ከዋናው ቤት ሥር ያለ ሰፊ ክፍል ውስጥ ገፋ አድርጎ አስገብቶ ከውጭ ቆለፈብን፡፡ ይሄ ክፍል እኒያ በደም ግፊት የሞቱ ሰውዬ ሲያሠሩት ለአንዳንድ ዕቃ ማስቀመጫ ብለው ሳይሆን አይቀርም፡፡ ጣሪያው በጣም ቅርብ ነው፡፡ እጄን ብዘረጋና ትንሽ ዘለል ብል እነካዋለሁ፡፡ እንግዲህ የታሰርንበት ክፍል ጣሪያ የዋናው ቤት የጣውላ ወለል ነው…ሰዎች ከበላያችን ሲረማመዱ የሚከነክን ልም አቧራ ይራገፍብናል፡፡ ከታሰርንበት ክፍል
በውጭ በኩል በር ላይ የተሰቀለው ፍሎረሰንት መብራት፣ ነጭ ብርሃን ከበሩ በላይባለው ክፍተት ገብቶ ቤቱን በለስላሳ ብርሃን በከፊል ሞልቶታል፡፡ ብርሃኑ ከበላያችን ባለው የጣውላ ክፍተት ሽቅብ አልፎ፣ ከላይ የሚረማመዱትን ሰዎች ያሳያል፡፡
ብዙም ሳይቆይ ከፖሊስ ጣቢያው ውጭ (በግምት በሩ አካባቢ ካለው መተላለፊያ
ይመስለኛል) የእናቴንና ተከትለዋት የመጡ ጎረቤቶቻችንን የተደበላለቀ ድምፅ ተሰማኝ፡፡
ነቃ አልኩ፡፡ “ይረጋጉ ማዘር ኢንስፔክተር
መንበረ ናት፡፡ እንዴት ነው የምረጋጋው
ልጄን እንደ ወንጀለኛ እያዳፋችሁ ስታመጡት፤ ከቤት ወቶ የማያቅ ልጅ በድንጋጤ ግጥም ብሎስ እንደሆን እንዴት ነው የምረጋጋው!? .…ልጄን! እኔ አፈር ልብላ” ትላለች
እናቴ፡፡ ሙቼ ከመቃብሬ ውስጥ ሆኜ የማዳምጣት መሰለኝ፡፡ እንደዚያ፣
እንግዲህ ንዝንዝ ጀመረችኝ!” ብዬ የምሸሸው ድምጿ ብዙ ዓመታት እንደተራራቀ ሰው ናፈቀኝ፡፡ከበላዬ ጣውላው በበርካታ ሰዎች እግር ሲረገጥ እና ሲንሲያጠጥ፣ያገር አቧራ እንደ
ዝናብ ሲዘንብ ይሰማኛል፡፡ የጣውላው ይኼን ያህል መንጓጓትና ሲጥሲጥታ የመንደሩ ሰው ከላይ የሚጨፍር ነበር ያስመስለው፡፡ “ችግር የለም ማዘር፣ ጉዳዩን አጣርተን እንለቃቸዋለን” ትላለች ኢንስፔክተር መንበረ፡፡ ይመስለኛል፣ ኢንስፔክተር መንበረ
እናቴን ጨምሮ ሁሉንም ሰዎች ወደውጭ እንዲወጡ አድርጋ፣ ተመልሳ ከአንድ ፖሊስ ጋር ዝቅ ባለ ድምፅ የሆነ ነገር ማውራት ጀመረች፡፡ የምትለውን መስማት አልቻልኩም፡፡ለማዳመጥ ጓጉቸ ከበላዬ ወዳለው የጣውላ ሽንቁር ጠጋ ብዬ ቆምኩና ሽቅብ በሽንቁ ዓይኔን ሰደድኩ፡፡
ፈጽሞ ያላሰብኩት ነገር ነበር የጠበቀኝ፡፡ ኢንስፔክተር መንበረ ጥርት ያሉ ጠይም
እግሮች፣ እስከ ታፋዋ ጥግ ከበላዬ ቆሟል፡፡ ያንን የካኪ ቀሚስ በስሱ ባለፈው የፖሊስ ጣቢያው “ፍሎረሰንት” መብራት፣ ደግሞም ከታች እኛ ከታሰርንበት ሽቅብ ባለፈ ቀጭን ብርሃን ኪነታዊ ቅንብር፣ ጠይም እግሮቿ ከጉርድ ወታደራዊ ቆዳ ጫማዋ ጀምሮ
ጉልበቷን አልፎ ታፋዋ…ብሎም የውስጥ ሱሪዋ ድረስ ቁልጭ ብለው ይታያሉ፡፡ አንድ እግሯ ከጉልበቷ ትንሽ አጠፍ ብሏል፡፡ አንዳች የማላውቀው ንዝረት መላ ሰውነቴን ሲወረው ተሰማኝ፡፡ ሕልም ነበር የሚመስለው እስር ቤት ነኝ!..ያውም እንደ መቃብር በከበደ እና በሚቀዘቅዝ ምድር ቤት ውስጥ፡፡ እንዴት ነው እንዲህ የተቀናበረ በሚመስል ተአምር፣ እንደ የእጅ ባትሪ በቀጠነ የፍሎረሰንት ብርሃን፣ ያውም በሽንቁር ሽቅብ አልፎ እንዲህ ግራ የሚጋባ ነገር የሚታየው? የኢንስፔክተር መንበረ የውስጥ ሱሪ ቀይ ነው። ደማቅ ቀይ ..ቅላቱ እንግዳ ነበር! ሕይወት ያለው ቀለም፡፡ እግሮቿ ወደ ላይ ወደ ታፋዋ ቀላ ይላሉ... በተንቀሳቀሰች ቁጥር ብርሃኑ የሚያርፍበት የሰውነቷ ክፍል፣ በጥላና ብርሃን ፍርርቆሽ እየተጫወተ በመጠየምና በመጥቆር መካከል እየተቀያየረ ይታያኛል፡፡ እግሮቿን
ስትከድን ታፋዎቿ በስሱ ተነካኩ፡፡ ዓይኖቼ ከሽንቁሩ ሊነቀሉ አልቻሉም፡፡ የማይረሳ
አንዳች ትዕይንት ነበር ንዝረት የቀላቀለ፡፡
ዛሬ ላይ ሳስበው ታዲያ፣ የደቡብ አፍሪካው የነፃነት ታጋይ ኔልሰን ማንዴላ፣ ሃያ ሰባት ዓመት በታሰሩበት ክፍል መስኮት ይሁን ፋካ፣ ተስፋቸውን የሚቀጥል ምን ነገር እያዩ እንደነበር ማን ያውቃል?! እላለሁ .…መቼስ እስር ቤትም ቢሆን ሽንቁር ይኖረዋል የሰው ልጅ ሁሉን ሽንቁር ደፍኖ አይችለውም፡፡ ሁሉም ነገር የሆነ ሽንቁር አለው ..ሕይወት
ድፍን አይደለችም፡፡ ሰው ራሱ ተስፋው በጨለማ ተከባ፣ ተጀብኖ እንደ ጥቢኛ እሳት መኻል ቢጣል፣ የከበበውን እሳት ይረሳ ዘንድ ሕይወት የተስፋ ውሃ የምታሳይበት አንዳች ሽንቁር አላት፡፡ እያጮለቅን እፎይታን ተስፋ እናደርግ ዘንድ፡፡ ይኼ ትዕይንት ካለፈ ደቂቃዎች በኋላ፣ አንድ ጥግ ቆሜ ትዕይንቱን ዕፍረት በጠላበት የውስጥ መደናገር
እየመላለስኩ ሳስብ።
አብሮኝ የታሰረው ጓደኛዬ እስካድማስ በተራው ወደ ሽንቁሩ አንጋጦ እየተመለከተ በፍርሃት በሚንቀጠቀጥ የሹክሹክታ ድምፅ “ሊያስሩን ነው መሰል ..ሊያስሩን ነው” አለ
እ?” አልኩት ከሐሳቤ ባንኜ … ከዚህ ወዲያ ምን መታሰር ሊመጣ ነው እያልኩ…
ወደ ሽንቁሩ እየጠቆመኝ “ና ና ተመልከት” አለ፡፡
ትከሻ ለትከሻ ገጥመን ወደላይ አንጋጠን ስንመለከት፣ አንድ የቆመ ፖሊስ በከፊል አንድ ጎኑ ብቻ ይታያል ... በሽንቁሩ ትክክል ሙሉ ለሙሉ የሚታየው
ግን ያንጠለጠለው የእጅ ካቴናው ነበር፡፡ ታፋውን በካቴናው መታ መታ እያደረገ፣ የሆነ ነገር የሚጠብቅ ይመስላል፡፡ ለምን እንደሆነ እንጃ አልፈራሁም! አንድ ከተማችን ውስጥ መንገድ ለመንገድ እየዞረ ወንጌል የሚሰብክ ጎልማሳ ነበር ድንገት ወደ አዕምሮዬ የመጣው፡፡
አንድ ቀን በመነበብ ብዛት የተጎሳቆለውን ባለጥቁር ሽፋን መጽሐፍ ቅዱስ ወደ ላይ ከፍ አድርጎ ሂድ ወደዛ መናፍቅ? የሚሉት ሰዎች መኻል እንደቆመ….
ወገኖቼ ይኼ ቃል ሽንቁር ነው፣ መስኮት ነው፣ ነገ ይገለጥ ዘንድ ያለውን ዓለም
በከፊል የምናይበት ሽንቁር! ሲኦልንም ገነትንም በዚህ ሽንቁር ካልሆነ አታዩትም!
አትፍሩ… ወደ መስኮቱ ተጠጉ ዓይኖቻችሁንም ግለጡ .…” እያለ የጮኸው ነገር፡፡ የዛ ሰው ንግግር ድንገት ዛሬ እንዲህ በጨለማ የተገለጠልኝ ያህል፣ ደግሞም የማይታይ
በማየቴ ሽው ከሚልብኝ የመቀሰፍ ፍርሃት በላይ ቅዱስ የሆንኩ ዓይነት፣ ቅዱስ ሆኜ
እስር ቤት የተወረወርኩ ዓይነት፣ እንዲያው እዚህ ከጎኔ በፍርሀት ከሚርበደበደው ልጅ ጋር ጮኸ ብለን ብንዘምር የእስር ቤቱ በር በተአምር እንደሚከፈት ዓይነት፣ ውስጤን
አንዳች ንፁህ ደስታ ሲሞላው ይሰማኝ ነበር፡፡
የዚያን ቀን የተባለውን እንጃ፣ ብቻ በዚያው ምሽት ተፈተን ወደ ቤታችን ሄድን፡፡ተፈትቶ መመለስ” ይለዋል ጎረቤቱ ይኼን የሥጋ መንከላወስ፣ ከፖሊስ ጣቢያ ወደ ቤት ማዝገም፡፡ ለእኔ ግን ጉዳዩ ሌላ ነበር፤ ታስሬ ነበር የተመለስኩት፡፡ የሴት ልጅ ሰውነት
በዚያ ልክ ተጋልጦ ሳይ የመጀመሪያዬ ነበር፡፡ ለስንት ዓመት ይሆን ከዚያ በኋላ
ኢንስፔክተር መንበረን ለማየት፣ አይቼም ከተሸፋፈነ እሷነቷ ሥር በድብቅ ትዕይንት
የተገለጠው ዓይኔ፣ የፖሊስ ዩኒፎርሟን ሰርስሮ እነዚያን እግሮች ሲያይ የኖረው
አላውቅም! ሱሪ ትልበስ ቀሚስ ብቻ ራቁት
፡
፡
#ክፍል_ሁለት(የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#በአሌክስ_አብርሃም
...የወለሉ ንጣፍ ጣውላ ሲረግጡት፣ እሪታው ሌላ ሰፈር ድረስ የሚሰማ ይመስላል፡፡ ኢንስፔክተር መንበረ አንድም ቃል ሳትናገር፣ ክንዴን እንደያዘችኝ ነበር ከኋላ ከነ አጀበኝ የሕዝብ አጀብ ፖሊስ ጣቢያ የደረስነው፡፡ በሩ ላይ ስንደርስ፣ ቀጥ ብሎ ቆሞ ሰላምታ ለሰጣት
ፖሊስ “አስገባቸው” አለችው።
“እሺ! አስገባቸዋለሁ ኢንስፔክተር” አለ፡፡ ድምፁ ስልል ያለና አስፈሪ ነው “እሺ! ወደ ሲኤል እወረውራቸዋለሁ!” የሚል የሲኦል በር ጠባቂ ነበር የሚመስለው፡፡ እኔ ግን አስገባቸው?” ብዬ ዞር ስል፣ ለካስ ብቻዬን አልነበርኩም፤ እስካድማስ የሚባል የሰፈሬ ልጅም ተይዟል፡፡ ፖሊሱ ከኢንስፔክተር መንበረ ተቀብሎ፣ ከሷም በጠበቀ አያያዝ ክንዳችንን ጨምድዶ እያመናጨቀ፣ በሚንቋቋው አሮጌ የጣውላ ደረጃ ቁልቁል ወሰደና ከዋናው ቤት ሥር ያለ ሰፊ ክፍል ውስጥ ገፋ አድርጎ አስገብቶ ከውጭ ቆለፈብን፡፡ ይሄ ክፍል እኒያ በደም ግፊት የሞቱ ሰውዬ ሲያሠሩት ለአንዳንድ ዕቃ ማስቀመጫ ብለው ሳይሆን አይቀርም፡፡ ጣሪያው በጣም ቅርብ ነው፡፡ እጄን ብዘረጋና ትንሽ ዘለል ብል እነካዋለሁ፡፡ እንግዲህ የታሰርንበት ክፍል ጣሪያ የዋናው ቤት የጣውላ ወለል ነው…ሰዎች ከበላያችን ሲረማመዱ የሚከነክን ልም አቧራ ይራገፍብናል፡፡ ከታሰርንበት ክፍል
በውጭ በኩል በር ላይ የተሰቀለው ፍሎረሰንት መብራት፣ ነጭ ብርሃን ከበሩ በላይባለው ክፍተት ገብቶ ቤቱን በለስላሳ ብርሃን በከፊል ሞልቶታል፡፡ ብርሃኑ ከበላያችን ባለው የጣውላ ክፍተት ሽቅብ አልፎ፣ ከላይ የሚረማመዱትን ሰዎች ያሳያል፡፡
ብዙም ሳይቆይ ከፖሊስ ጣቢያው ውጭ (በግምት በሩ አካባቢ ካለው መተላለፊያ
ይመስለኛል) የእናቴንና ተከትለዋት የመጡ ጎረቤቶቻችንን የተደበላለቀ ድምፅ ተሰማኝ፡፡
ነቃ አልኩ፡፡ “ይረጋጉ ማዘር ኢንስፔክተር
መንበረ ናት፡፡ እንዴት ነው የምረጋጋው
ልጄን እንደ ወንጀለኛ እያዳፋችሁ ስታመጡት፤ ከቤት ወቶ የማያቅ ልጅ በድንጋጤ ግጥም ብሎስ እንደሆን እንዴት ነው የምረጋጋው!? .…ልጄን! እኔ አፈር ልብላ” ትላለች
እናቴ፡፡ ሙቼ ከመቃብሬ ውስጥ ሆኜ የማዳምጣት መሰለኝ፡፡ እንደዚያ፣
እንግዲህ ንዝንዝ ጀመረችኝ!” ብዬ የምሸሸው ድምጿ ብዙ ዓመታት እንደተራራቀ ሰው ናፈቀኝ፡፡ከበላዬ ጣውላው በበርካታ ሰዎች እግር ሲረገጥ እና ሲንሲያጠጥ፣ያገር አቧራ እንደ
ዝናብ ሲዘንብ ይሰማኛል፡፡ የጣውላው ይኼን ያህል መንጓጓትና ሲጥሲጥታ የመንደሩ ሰው ከላይ የሚጨፍር ነበር ያስመስለው፡፡ “ችግር የለም ማዘር፣ ጉዳዩን አጣርተን እንለቃቸዋለን” ትላለች ኢንስፔክተር መንበረ፡፡ ይመስለኛል፣ ኢንስፔክተር መንበረ
እናቴን ጨምሮ ሁሉንም ሰዎች ወደውጭ እንዲወጡ አድርጋ፣ ተመልሳ ከአንድ ፖሊስ ጋር ዝቅ ባለ ድምፅ የሆነ ነገር ማውራት ጀመረች፡፡ የምትለውን መስማት አልቻልኩም፡፡ለማዳመጥ ጓጉቸ ከበላዬ ወዳለው የጣውላ ሽንቁር ጠጋ ብዬ ቆምኩና ሽቅብ በሽንቁ ዓይኔን ሰደድኩ፡፡
ፈጽሞ ያላሰብኩት ነገር ነበር የጠበቀኝ፡፡ ኢንስፔክተር መንበረ ጥርት ያሉ ጠይም
እግሮች፣ እስከ ታፋዋ ጥግ ከበላዬ ቆሟል፡፡ ያንን የካኪ ቀሚስ በስሱ ባለፈው የፖሊስ ጣቢያው “ፍሎረሰንት” መብራት፣ ደግሞም ከታች እኛ ከታሰርንበት ሽቅብ ባለፈ ቀጭን ብርሃን ኪነታዊ ቅንብር፣ ጠይም እግሮቿ ከጉርድ ወታደራዊ ቆዳ ጫማዋ ጀምሮ
ጉልበቷን አልፎ ታፋዋ…ብሎም የውስጥ ሱሪዋ ድረስ ቁልጭ ብለው ይታያሉ፡፡ አንድ እግሯ ከጉልበቷ ትንሽ አጠፍ ብሏል፡፡ አንዳች የማላውቀው ንዝረት መላ ሰውነቴን ሲወረው ተሰማኝ፡፡ ሕልም ነበር የሚመስለው እስር ቤት ነኝ!..ያውም እንደ መቃብር በከበደ እና በሚቀዘቅዝ ምድር ቤት ውስጥ፡፡ እንዴት ነው እንዲህ የተቀናበረ በሚመስል ተአምር፣ እንደ የእጅ ባትሪ በቀጠነ የፍሎረሰንት ብርሃን፣ ያውም በሽንቁር ሽቅብ አልፎ እንዲህ ግራ የሚጋባ ነገር የሚታየው? የኢንስፔክተር መንበረ የውስጥ ሱሪ ቀይ ነው። ደማቅ ቀይ ..ቅላቱ እንግዳ ነበር! ሕይወት ያለው ቀለም፡፡ እግሮቿ ወደ ላይ ወደ ታፋዋ ቀላ ይላሉ... በተንቀሳቀሰች ቁጥር ብርሃኑ የሚያርፍበት የሰውነቷ ክፍል፣ በጥላና ብርሃን ፍርርቆሽ እየተጫወተ በመጠየምና በመጥቆር መካከል እየተቀያየረ ይታያኛል፡፡ እግሮቿን
ስትከድን ታፋዎቿ በስሱ ተነካኩ፡፡ ዓይኖቼ ከሽንቁሩ ሊነቀሉ አልቻሉም፡፡ የማይረሳ
አንዳች ትዕይንት ነበር ንዝረት የቀላቀለ፡፡
ዛሬ ላይ ሳስበው ታዲያ፣ የደቡብ አፍሪካው የነፃነት ታጋይ ኔልሰን ማንዴላ፣ ሃያ ሰባት ዓመት በታሰሩበት ክፍል መስኮት ይሁን ፋካ፣ ተስፋቸውን የሚቀጥል ምን ነገር እያዩ እንደነበር ማን ያውቃል?! እላለሁ .…መቼስ እስር ቤትም ቢሆን ሽንቁር ይኖረዋል የሰው ልጅ ሁሉን ሽንቁር ደፍኖ አይችለውም፡፡ ሁሉም ነገር የሆነ ሽንቁር አለው ..ሕይወት
ድፍን አይደለችም፡፡ ሰው ራሱ ተስፋው በጨለማ ተከባ፣ ተጀብኖ እንደ ጥቢኛ እሳት መኻል ቢጣል፣ የከበበውን እሳት ይረሳ ዘንድ ሕይወት የተስፋ ውሃ የምታሳይበት አንዳች ሽንቁር አላት፡፡ እያጮለቅን እፎይታን ተስፋ እናደርግ ዘንድ፡፡ ይኼ ትዕይንት ካለፈ ደቂቃዎች በኋላ፣ አንድ ጥግ ቆሜ ትዕይንቱን ዕፍረት በጠላበት የውስጥ መደናገር
እየመላለስኩ ሳስብ።
አብሮኝ የታሰረው ጓደኛዬ እስካድማስ በተራው ወደ ሽንቁሩ አንጋጦ እየተመለከተ በፍርሃት በሚንቀጠቀጥ የሹክሹክታ ድምፅ “ሊያስሩን ነው መሰል ..ሊያስሩን ነው” አለ
እ?” አልኩት ከሐሳቤ ባንኜ … ከዚህ ወዲያ ምን መታሰር ሊመጣ ነው እያልኩ…
ወደ ሽንቁሩ እየጠቆመኝ “ና ና ተመልከት” አለ፡፡
ትከሻ ለትከሻ ገጥመን ወደላይ አንጋጠን ስንመለከት፣ አንድ የቆመ ፖሊስ በከፊል አንድ ጎኑ ብቻ ይታያል ... በሽንቁሩ ትክክል ሙሉ ለሙሉ የሚታየው
ግን ያንጠለጠለው የእጅ ካቴናው ነበር፡፡ ታፋውን በካቴናው መታ መታ እያደረገ፣ የሆነ ነገር የሚጠብቅ ይመስላል፡፡ ለምን እንደሆነ እንጃ አልፈራሁም! አንድ ከተማችን ውስጥ መንገድ ለመንገድ እየዞረ ወንጌል የሚሰብክ ጎልማሳ ነበር ድንገት ወደ አዕምሮዬ የመጣው፡፡
አንድ ቀን በመነበብ ብዛት የተጎሳቆለውን ባለጥቁር ሽፋን መጽሐፍ ቅዱስ ወደ ላይ ከፍ አድርጎ ሂድ ወደዛ መናፍቅ? የሚሉት ሰዎች መኻል እንደቆመ….
ወገኖቼ ይኼ ቃል ሽንቁር ነው፣ መስኮት ነው፣ ነገ ይገለጥ ዘንድ ያለውን ዓለም
በከፊል የምናይበት ሽንቁር! ሲኦልንም ገነትንም በዚህ ሽንቁር ካልሆነ አታዩትም!
አትፍሩ… ወደ መስኮቱ ተጠጉ ዓይኖቻችሁንም ግለጡ .…” እያለ የጮኸው ነገር፡፡ የዛ ሰው ንግግር ድንገት ዛሬ እንዲህ በጨለማ የተገለጠልኝ ያህል፣ ደግሞም የማይታይ
በማየቴ ሽው ከሚልብኝ የመቀሰፍ ፍርሃት በላይ ቅዱስ የሆንኩ ዓይነት፣ ቅዱስ ሆኜ
እስር ቤት የተወረወርኩ ዓይነት፣ እንዲያው እዚህ ከጎኔ በፍርሀት ከሚርበደበደው ልጅ ጋር ጮኸ ብለን ብንዘምር የእስር ቤቱ በር በተአምር እንደሚከፈት ዓይነት፣ ውስጤን
አንዳች ንፁህ ደስታ ሲሞላው ይሰማኝ ነበር፡፡
የዚያን ቀን የተባለውን እንጃ፣ ብቻ በዚያው ምሽት ተፈተን ወደ ቤታችን ሄድን፡፡ተፈትቶ መመለስ” ይለዋል ጎረቤቱ ይኼን የሥጋ መንከላወስ፣ ከፖሊስ ጣቢያ ወደ ቤት ማዝገም፡፡ ለእኔ ግን ጉዳዩ ሌላ ነበር፤ ታስሬ ነበር የተመለስኩት፡፡ የሴት ልጅ ሰውነት
በዚያ ልክ ተጋልጦ ሳይ የመጀመሪያዬ ነበር፡፡ ለስንት ዓመት ይሆን ከዚያ በኋላ
ኢንስፔክተር መንበረን ለማየት፣ አይቼም ከተሸፋፈነ እሷነቷ ሥር በድብቅ ትዕይንት
የተገለጠው ዓይኔ፣ የፖሊስ ዩኒፎርሟን ሰርስሮ እነዚያን እግሮች ሲያይ የኖረው
አላውቅም! ሱሪ ትልበስ ቀሚስ ብቻ ራቁት
👍2