አትሮኖስ
286K subscribers
120 photos
3 videos
41 files
575 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
​​ከጀርባዬ ኮቴ ሳያሰማ ማጅራቴ አከባቢ

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
​​#ልጩህበት!!


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#ድርሰት_በጥላሁን

ተነስተህ በቦክስ ወደ ጀርባው ዘርረውና ልጅቷን ይዘኃት ውጣ ውጣ አለኝ።
መሲ ተነስታ ወደ ሽንት ቤት ስትሄድ ከጀርባ ተከተልኳት ! እሷ ከፊት እኔ ከኋላ ወደ ሽንት ቤት እምትወስደው ቀጭን መንገድ መሀል ላይ እንደደረስን ከጀርብዬ ኮቴ ሳያሰማ ማጅራቴ አከባቢ •••
ኮሌታዬን ቀብ ሲያደርገኝ በድንጋጤ መንጭቄው በፍጥነት ዞርኩ!
"ክክክ አንተ ምነው ? ሊያጠቃኝ ይችላል ብለህ የምታስበው ጠላት አለህ እንዴ?
ተፈናጠርክ እኮ ካካካ•••!"

ኮንትራት የያዘኝ ሰውዬ ነበር። የሚገርመው እራሴ አምጥቼው ሳበቃ እዛ ጭፈራ ቤት የውስጠኛው ክፍል ውስጥ መኖሩን ጭራሽ ረስቼዋለሁ!
ወደ ወንዶች ሽንት ቤት ጎን ለጎን እየሄድን •••
"ደሞ ደክሞኛል ገብቼ ተኛለሁ ባጃጅ ከፈለክ ብለህ ሌላ ስልክ ሰጥተከኝ አልነበር እንዴ የሄድከው ነው ወይስ ሞባይሉን ሰጠኸኝ ስትወጣ አንዷ ጠልፋህ ነው? መሆን አለበት ! እዚ ቤት ያሉ ሴቶች እኮ ልዩ ናቸው እንኳን
እዚህ ድረስ እራሱ የመጣውን ሰው በአየር ላይ ፖይለቱን አማሎ አውሮፕላን ለመጥለፍ ወደኋላ የማይል ውበት ነው ያላቸው ቆይ የጭፈራ ቤቱ ባለቤት የቁንጅና ውድድር አዘጋጅቶ ከአንድ እስከ አምስት የሚወጡትን ነው እንዴ የሚቀጥረው! ካካካ!"
ኧረ መቆለል አልኩና በሆዴ !
ኧረ አይደለም ባጋጣሚ ነው አልኩት ሸንተን ስንመለስ•••
"ምኑ ነው አጋጣሚ ቆንጆዎች መሆናቸው?"
አይ የኔ እዚህ መከሰት!
"እና ብቻህን ነህ ብቻህን ከሆንክ ለምን ውስጥ እኔጋ አለመጣህም " እያለ አቁሞ ሲነዘንዘኝ መሲ ከሽንት ቤት ወጥታ እየተውረገረገች ባጠገባችን አለፈች። አፈጠጥኩባት ።
እሱም በሚስቁት አይኖቹ እኔ ላይ አፈጠጠብኝ ።
"ተመለስክ?!"
ኬት ?
"ከልጅቷ ላይ ነዋ!"
አዎ አልኩት ፈገግ ብዬ !
በል ና እሄንን እማ እየጠጣን ነው መስማት የምፈልገው ናናናና !" እያለ እጄን እንደያዘ ወደ ውስጥ ገባን።
እዛ የተገኘሁበትን እውነት ልንገረው? አልንገው ? ብነግረውስ ምን ብዬ ልንገረው? ምናልባት ጥሬ እውነቱን እንደወረደ ስነግረው ምናልባት እኔን የተሰማኝ ስሜት ካልተሰማው•••
"ቆይ ከልጅቷ ጋር ዘመድ ናችሁ?"
ኧረ አይደለንም ።
"ትውውቅ አላችሁ ማለት ታውቃታለህ ?"
አይ!
"እሺ ቆይ ልጅቷን ወደሀታል?'
ኧረ በጭራሽ!
"ታድያ ምን አግብቶህ ነው እዚህ ሁሉ ፈተና ውስጥ እራስህን የምትከተው?!" ቢለኝስ!
እኔ የሴቶች እህቶቼ ጉዳትና ጥቃት እንደሚያገባኝ አምናለሁ ይሄ የሚያገባቸው የማይመስላቸው እሄን ምን አገባኝ እያሉ ነገር ግን በማያገባቸው ብዙ ነገሮች ውስጥ እጃቸውን የሚያስገቡ ሰዎች በዙርያችን ብዙ ናቸው።
የሴት ጥቃት አይመለከተኝም እያሉ የአርሰናል መጠቃት የሚያደባድባቸው በሞሉባት ሀገራችን
አላውቃትም!
ዝምድናም የለንም!
አልወደድኳትም!
እያልክ ለሷ መቆም እንቆቅልሽ የሚሆንበትና ምን አገባህ የሚልህ ቢያጋጥምህ ምን ይገርማል?!
ምንም!።
ስለዚህ ምን ልበለው? በቀላሉ የሚፋታኝ አይመስለኝም ።
"ምናገባህ!" እንዳይለኝ ትንሽ ቀየር አድርጌ ልነግረው ወሰንኩና•••
ይሄውልህ ቅድም ሞባይሉን ሰጥቼህ ስወጣ የአንደኛ አመት የዩንቨርስቲ ተማሪ የሆነችውን የአክስቴን ልጅ ከማይሆን ሰው ጋር አየኋት!
ከኔ ጋር ከተጣላን አመት ሆኖናል። ተኮራርፈናል። አንነጋገርም ግን ብንጣላም ስለሰውየው በደንብ ስለማውቅ ጥያት በጭራሽ አልገባም ልጅቷ እንደዚህ አይነት አመል የላትም እርግጠኛ ነኝ ቅድም የገላመጥኳት ልጅ በሆነ መንገድ ሸውዳ አምጥታለት ነው •••
አልኩና ስለመሲና ስለሰውየው በዝርዝር ነገርኩት።
እሄን ግዜ ሰውየው ከኔ በላይ የተቆጣ ነብር ሆኖ ቁጭ አለ። ፊቱ ተለዋወጠ።
"በቃ ይሄን ጉዳይ ለኔ ተወው አንተ ዝምበልና ቁጭ ብለህ ጠጣ!"
ማለት ምን ልታደርግ ነው?!
"ዝም ብለህ ጠጣ! ብዬሀለሁ ዝም ብለህ ጠጣ!" አለኝ ክርድድ ባለ ድምፅ።
ድሮም ነገረ ስራው ግራ ነበር የሚገባኝ አሁን ደግሞ ባንዴ ሲለዋወጥብኝ እኔ እራሴ ፈራሁት ።
ካጠገቤ ሄዶ እነመሲን ከሩቁ አይቷቸው ተመለሰ።
ከደቂቃዎች በኋላ ከነመሲ ጋር ያለው ሰውዬ ቦርጩን እያሻሸ ወደ ሽንት ቤት ሲያልፍ እኩል እየነው! ተያየን••ኀ
"እሄ አሁን ያለፈው ነው አደለ?
"አዎ ግን ምን ልታደርግ ነው?
"አቢቲ አማርኛዬ አልገባ ካለህ የፈለከውን የሚገባህን ቋንቋ ንገረኝና በሱ ላስረዳህ ከዚህ በኋላ ለኔ ተወው የትም እንዳትንቀሳቀስ እዚሁ ቁጭ ብለህ እየጠጣህ ጠብቀኝ !"
ብሎኝ ሰውየውን ተከትሎ ወደ ሽንት ቤት ሄደ።
ብዙም ሳይቆይ ተመልሶ መጣና ምንም ሳይለኝ መጠጣት ጀመረ
ወደሽንት ቤት የሄደውን ሰውዬ ካሁን ካሁን ይመለሳል ብዬ ብጠብቅም አልተመለሰም ጨነቀኝ እንዴ ምን አርጎት መጣ? ግራ ገባኝ
ምን አልከው ሰውየው እኮ ብር ያጠገበው ባለጌ ነው ምን አለህ? ስለው•••
መልስ ሳይሰጠኝ እሄን ውስኪ እንደውሃ እየጠጣ •••
"ጠጣ ጠጣ ያቺን አየሀት ዝም ብላ እያየችህ ነው አብረካት መደነስ ትፈልጋለህ ልጥራት እንዴ?"
አለኝ ጥግ ኮርነር ላይ ካሉት ሴቶች መሀል ወደኛ እያየች ወደምትናጠው ሴት እያመለከተኝ
ወይ መደነስ እኔ ሰውየው እምጥ ይግባ ስምጥ ሄዶ ካናገረው በኋላ ከሽንት ቤት ባለመመለሱ ምን አርጎት ነው የመጣው እያልኩ ግራ ተጋብቻለሁ ጭራሽ ደንስ ይለኛል ምን አይነት ባህሪ ያለው ሰው ነው እሄ ደግሞ ቢያንስ እንኳን የኔ ጭንቀት ለምን አይገባውም እንዴ በራሴ ጉዳይ ዝም በል ጠጣ ደንስ ስላለኝ ዝም የምል ይመስለዋል?!
ወደ ሽንት ቤት ሌላ ሰው በሄደ እና በወጣ ቁጥር እያየሁ በጭንቀት ከመፈንዳቴ በፊት እራሴ ሄጄ ለማረጋገጥ ስለፈለኩ•••
••• እሺ መጣሁ አንዴ ስመለስ አብሪያት እደንሳለሁ አልኩትና ሄድኩ መጀመሪያ ወደነመሲ ገልመጥ ሳደርግ ሁለቱ ብቻ ናቸው እነሱም እንደኔ ሰውየው የት ሄደ ብለው ግራ ተጋብተዋል መሰለኝ ግራና ቀኝ ይገላመጣሉ ።
ወደ ወንዶች ሽንት ቤት በፍጥነት ሄድኩና ከአምስቱ ሽንት ቤቶች መሀከል ክፍት የሆኑትን ሁለቱን አየት አድርጌ በማለፍ ሶስተኛውን ስበረግደው•••

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍1
​​#ልጩህበት!!


#ክፍል_አስራ_አራት


#ድርሰት_በጥላሁን

ወይ መደነስ እኔ ሰውየው እምጥ ይግባ ስምጥ ሄዶ ካናገረው በኋ ላ ከሽንት ቤት ባለመመለሱ ምን አርጎት ነው የመጣው እያልኩ ግራ ተጋብቻለሁ ጭራሽ ደንስ ይለኛል ምን አይነት ባህሪ ያለው ሰው ነው እሄ ደግሞ ቢያንስ እንኳን የኔ ጭንቀት ለምን አይገባውም እንዴ በራሴ ጉዳይ ዝም በል ጠጣ ደንስ ስላለኝ ዝም የምል ይመስለዋል?!
ወደ ሽንት ቤት ሌላ ሰው በሄደ እና በወጣ ቁጥር እያየሁ በጭንቀት ከመፈንዳቴ በፊት እራሴ ሄጄ ለማረጋገጥ ስለፈለኩ•••
••• እሺ መጣሁ አንዴ ስመለስ አብሪያት እደንሳለሁ አልኩትና ሄድኩ መጀመሪያ ወደነመሲ ገልመጥ ሳደርግ ሁለቱ ብቻ ናቸው እነሱም እንደኔ ሰውየው የት ሄደ ብለው ግራ ተጋብተዋል መሰለኝ ግራና ቀኝ ይገላመጣሉ ።
ወደ ወንዶች ሽንት ቤት በፍጥነት ሄድኩና ከአምስቱ ሽንት ቤቶች መሀከል ክፍት የሆኑትን ሁለቱን አየት አድርጌ በማለፍ ሶስተኛውን ስበረግደው•••
----------
"ምን አይነት ሰው ነህ በናትህ! ምሽግ ውስጥ ነው እንዴ ያደከው? አታንኳኳም!" አለኝ በብስጭት አንድ የማላውቀው ሰው።
ይቅርታ ይቅርታ አልኩት ቆሌዬ ተገፎ!።
"ባክህ የምናባህ ይቅርታ ነው ይቅርታ ይላል እንዴ ደሞ የልቡን አድርሶ!" አለኝ።
ንግግሩ ሳቅ ጫረብኝ ።
አይይ ስካር ደጉ ታየኝ እኮ እሱን ሽንት ቤት ተቀምጦ በማየቴ የልቤ ሲደርስ እያልኩ ቀሪ ሁለቱ ክፍሎች ውስጥ ሰውየውን መፈለጌን ቀጠልኩ•••
ሰውየው ድራሹ የለም ። ግራ ተጋብቼ በቆምኩበት ሽንትቤቱን ድንገት ከፍቼበት የተበሳጨው ሰውዬ ቆየት እያለ ሲሳደብ ሰማሁት•••
እንዴ! እሄ ደሞ እያረፈ ነው እንዴ እሚሳደበው!
አልኩና ከውስጥ ዘግተህ አትቀመጥም ነበር ሰካራም! ብየው ወደ ቦታዬ ስመለስ የኮንትራት ደንበኛዬ (ዝም ብለህ ጠጣ ሲለኝ የነበረውን ሰው ) ቦታው ላይ አጣሁት።
የክፍሉን ዙርያ ገባ ቃኘት አደረኩ ። እክፍሉ ውስጥም የለም።
እየተደነባበርኩ እነመሲ ወዳሉበት ክፍል በር ስጠጋ •••
አይኔን ተጠራጠርኩት ! ሽንት ቤት ሰውየውን ፍለጋ ደርሼ እስክመጣ ከምኔው ሄዶ ከምኔው ተዋውቋቸው እና ተግባብቷቸው መሳሳቅ እንደጀመሩ ለማመን በሚከብድ ሁኔታ•••
እሱ ያወራል እነመሲ ይስቃሉ አሁንም ያወራል እነሱ ተያይተው ያሽካካሉ አፌን ከፍቼ ስመለከታቸው ቆየሁና እየሆነ ያለው ነገር ከመጠጡ ጋር ተደምሮ ትርምስምስ እንዳለብኝ ወደ ቦታዬ ተመለስኩ።
ትንሽ ቆየሁና እሱ አልመጣ ሲለኝ መኖር አለመኖራቸውን ላረጋግጥ ድጋሚ ሄድኩ።
ጭራሽ እሱና መሲ ተጣብቀው እየደነሱ ነው። ጀርባዋን ሰጥታው እላዩ ላይ ተጣብቃለች ወገቧን አቅፎ ማጅራቷ አከባቢ እንደመሳም እየቃጣው ለስለስ ባለው ሙዚቃ ይወዛወዛሉ ።
ልጅቷ ቦታዎ ላይ ተቀምጣ ትቁለጨለጫለች ።
ምናልባት አስጠማጇን እራሷን መሲን አጥምዶ ልጅቷን ሊያፋታት አስቦ ይሆን እንዴ?
ብዬ አሰብኩና የሆነ የደስታ ስሜት ውስጤን ሲነዝረው ታውቀኝ።
ሰውየውን ምን አድርጎት ነው? የሚለው ጥያቄ ስላልተመለሰልኝና ዝም ብለህ ጠጣ ከማለት ውጪ ምን እንዳደረገ? እና ምን ሊያደርግ እንዳሰበ በግልፅ ሊነግረኝ ፍቃደኛ ባለመሆኑ ግን ደስታዬ ብርዝ ሆነብኝ!!
በዳንሳችው መሀል ድንገት ተያየን ጠቀሰኝ እኔ ግን ግራ ተጋብቶ ያፈጠጠ እንጂ የሚጨፈን አይን አልነበረኝም እና ምኑም ላልገባኝ ጥቅሻው መልስ ነፈኩት ዝም ብዬው ከራሴ ጋር እያልጎመጎምኩ•••
ግራ አጋባኝ እኮ እሚገርም ሰው ነው እሄ ሰውዬ እያልኩ ወደ ቦታዩ ተመለስኩ ።
በተመለስኩ በደቂቃዎች ውስጥ ወደኔ በመምጣ
"ፈታ በል አቢቲ ዝም ብለህ አትጨናነቅ እኔ አንድ ነገር ላደርግ ካሰብኩ ውጤቱን እንጂ ጅማሬው ማውራት አልወድም! ለምን መሰለህ?••• መጀመራችንን እንጂ መጨረሳችንን የሚያውቀው ፈጣሪ ብቻ ስለሆነ በርግጥ አሁን ያሰብኩትን ነገር ፈጣሪ ሳይሆን ሰይጣን ነው አጨራረሱን የሚያሳምረው አየህ አንዳንዴ ጥሩ ነገር ለመስራት መጥፎ ነገር ውስጥ መግባቱ ግድ ይልሀል የስራህ ውጤት ከፊሉ የፈጣሪ ከፊሉ የሰይጣን ይሆናል ድብልቅ!
ነገር ግን ፈጣሪ ልብን ሰይጣን ስራን ይመረምራል ብዬ ስለማምን እሱ አያሳስበኝም ! ለማንኛውም ስጨርስ ሁሉንም ነገር እነግርሀለሁ አሁን አንተ አታስፈልገኝም ከሀያ ደቂቃ ቡሀላ በር ላይ ሁለት ባጃጅ እፈልጋለሁ ካንተ ጋር ካሁን ቡሀላ ምናልባት ነገ ካልሄድኩ እንገናኝ ይሆናል ብሎኝ ከኔ መልስ ሳይጠብቅ ጥሎኝ ሄደ ።
እንኳን ምን ለማለት እንደፈለገ ሊገባኝ ያለውን መልሼ ማስታወስ አልቻልኩም።
አንዳንድ ሰዎችን ትንሽ ግዜ አብረሀቸው በቆየህ ቁጥር ወይ በደንብ ታውቃቸዋለህ ወይ ጭራሽ እንደማታውቃቸው ይገባሀል የሚለው የጆሲ ጋደኛ ትዝ አለኝ።
ያለኝ አማራጭ መወዛገቤን ትቼ እስከመጨረሻው የሚሆነውን ነገር መመልከት ብቻ ሆነ።
ካስር ደቂቃ ቡሀላ ኮፍያዬን አዘቅዝቄ አንገቴን አቀርቅሬ ከጭፈራ ቤቱ በፍጥነት ወጣሁ ።
ከማውቃቸው በዛ ሰአት ስራ ላይ ይሆናሉ ብዬ ወዳሰበኳቸው ሁለት የባጃጅ ሹፌሮች ደወልኩና በር ላይ እንዲጠብቁአቸው ነግሬ እኔ ራቅ ብዬ ባጃጄ ውስጥ እንዳደፈጥኩ ስጠባበቅ ልክ ባለው ሰአት መሲ እና እሱ ተቃቅፈው ግራና ቀኝ እየትወዛወዙ እና እየተሳሳቁ ልጅቷም በሁኔታቸው አብራ ፈገግ እያለች ወደ ጎን ተደርድረው ከጭፈራ ቤቱ ሲቅወጡ ተመለከትኩ።
ባጃጆቹ ጋር እንደደረሱ ሰውየው ያቀፋትን መሲን ለቅቅ አድርጎ ወደ ልጅታ ተጠጋና አናገራት። ጨብጣው ከፉት ያለው ባጃጅ ውስጥ ጥልቅ አለች እሱና መሲ ሌላኛው ባጃጅ ውስጥ ገቡና ፊትና ኋላ ሆነው ተፈተለኩ እኔም ተከትያቸው ተፈተለኩ ።
በቅርብ እየተከተልኳቸው ልጅቷን ወደ ያዘው የባጃጅ ሹፌር ደወልኩ ። አነሳው።
ምን አለህ? ስለው•••
"ግቢ አድርሳት አለኝ ወደ ግቢ እየወሰድኳት ነው " አለኝ ። በረጅሙ ተነፈስኩ እና ጀግና አቦ አልኩት ግራ ያጋባኝን ሰው።
ወደ ግቢ የሚሄደው ባጃጅና እነመሲን የያዘው ባጃጅ የሚለያዩበት ቦታ ላይ ደረሱ ልጅቷን የያዘው በዲፖ በኩል ሽቅብ ወደ ሰይዶ ሲሸመጥጠው እነመሲን የያዘው ባጃጅ በፀሀይ ሆቴል በኩል ቁልቁል ቆሰቆሰው•••
ወደያዘው ክፍል ይዟት እየሄደ መሆኑን ብረዳም ልጅቷን ትቼ የመሲን መጨረሻ ለማየት ተከተልኳቸው ።
ደረሱ ። ከባጇጃ ወርደው የሰከረችውን መሲን ከመሸከም በማይተናነስ ሀኔታ ደግፎ ወደያዘው ክፍል አስገባት ።
ለሰው ያጠመድሽው እራስሽ ላይ ባርቆ ሊዘርርሽ ነው አይ መሲ !
እያልኩ ወደ ቤቴ ገብቼ ተዘረርኩ ጥዋት ሶስት ሰአት ላይ የቀሰቀሰኝ የስልኬ ጥሪ ነበር ሰውየው ነው በፍጥነት አንስቼው ሀሎ ስል•••
" ደና አደርክ አቢቲ ተመልሼ ወደመጣሁበት እየሄድኩ ነው ምናልባት ከስድስት ወር ቡሀላ እመጣ ይሆናል የማታውን ሙሉ ትያትር ለማየት እና ለመስማት እንደምትፈልግ አውቃለሁ ቴሌግራምህን ክፈት ሶስት መልእክቶች አሉህ በድምፅ! በፅሁፍና; በምስል! ቻው !!"ብቻ ብሎኝ ስልኩን ዘጋው•••
በፍጥነት ቴሌግራም አካውንቴን ስበረግደው ቀድሞ የታየኝ የመሲ ልብስ አልባ ገላ የሚያሳየው ቪድዬ ነበር ከስር የመሲን ስልክ ቁጥር አስቀምጦ
"አቢቲ በዚህ ቁጥሯ የተከፈተ ቴሌግራም አካውንቷ ላይ ቪድዬዋን ልከህ ካሁን ቡሀላ በሴት ተማሪዎች ሂወት መነገዷን እንድታቆም ያለ በለዚያ ግን ቪድዮዋን እንደምትለቀው ነግረህ አስጠንቅቃት!" ይላል በርግጌ ከፍራሼ ላይ ተነሳሁ።
ቪድዮውን ስከፍተው ••

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍2
አትሮኖስ pinned «​​#ልጩህበት!! ፡ ፡ #ክፍል_አስራ_አራት ፡ ፡ #ድርሰት_በጥላሁን ወይ መደነስ እኔ ሰውየው እምጥ ይግባ ስምጥ ሄዶ ካናገረው በኋ ላ ከሽንት ቤት ባለመመለሱ ምን አርጎት ነው የመጣው እያልኩ ግራ ተጋብቻለሁ ጭራሽ ደንስ ይለኛል ምን አይነት ባህሪ ያለው ሰው ነው እሄ ደግሞ ቢያንስ እንኳን የኔ ጭንቀት ለምን አይገባውም እንዴ በራሴ ጉዳይ ዝም በል ጠጣ ደንስ ስላለኝ ዝም የምል ይመስለዋል?! ወደ ሽንት…»
#ነበር

ምርት እንዲበረክት አፈሩ ለም ሆኖ
ሠላሳና ስድሳ መቶም እንዲያፈራ
ቡቃያው እንዲያምር ላዩ እንዲጎመራ
እንዲታጨድበት የሰላም አዝሠራ
እንደው ከሆነ አይቀር ከተነሳ ልማት
ሰብል የሚያመክነው ተንኮልና ክፋት
ማፈራረስ ነበር ከምድረ-ገጽ ማጥፋት።

🔘በሰላም ዘውዴ🔘
#ቃል

ሰማይን ያቆመ
ምድርን ያጸና
ቃል አይደለም እንዴ ሁሉን የፈጠረ
በሁሉ የኖረ
ቃል ምነው ቀለለ?
ቦታ ክብሩን አጣ ያለስፍራው ዋለ።

🔘በሰላም ዘውዴ🔘
​​#ልጩህበት!!


#ክፍል_አስራ_አምስት


#ድርሰት_በጥላሁን

ቴሌግራምህን ክፈት ሶስት መልእክቶች አሉህ በድምፅ! በፅሁፍና; በምስል! ቻው !!"ብቻ ብሎኝ ስልኩን ዘጋው•••
በፍጥነት ቴሌግራም አካውንቴን ስበረግደው ቀድሞ የታየኝ የመሲ ልብስ አልባ ገላ የሚያሳየው ቪድዮ ነበር ከስር የመሲን ስልክ ቁጥር አስቀምጦ
"አቢቲ በዚህ ቁጥሯ የተከፈተ ቴሌግራም አካውንቷ ላይ ቪድዮዋን ልከህ ካሁን ቡኋላ በሴት ተማሪዎች ህይወት መነገዷን እንድታቆም ያለ በለዚያ ግን ቪድዮዋን እንደምትለቀው ነግረህ አስጠንቅቃት!" ይላል በርግጌ ከፍራሼ ላይ ተነሳሁ።
ቪድዮውን ስከፍተው •••
የሶስት ደቂቃ እድሜ ሲኖረው በዚች ሶስት ደቂቃ ውስጥ መሲ ያልተቀረፀ የሰውነት እካሏ አልነበረም ስካሯ ከመጠን ያለፈ ነበርና ያላትን በሙሉ እያደረገች ትስቃለች ። የሚገርመው የሰውየው አንዲት ጣት እንኳን በትይንቱ ውስጥ አለመኖሯ ነው።
ተጫወተባት እናቴ ትሙት በደንብ አርጎ ነው የተጫወተባት አልኩኝ ጮክ ብዬ መጮሄ ሳይታወቀኝ።
ለኔ በአለም ደስ የሚሉ ግን ያልተፃፉ ህግ አስከባሪም ፍርድቤትም ዳኛም ሳያስፈልጋቸው ከሚተገበሩ ተፈጥሮአዊ ህጎች አንዱ
"ሁሉም የእጁን ያገኛል "የሚለው የውስጤ እምነት ነው ማንም ቢሆን በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የዘራውን ማጨዱ የማይቀር ነው
ይዘግይም ይፍጠን፡ ይነስም ይብዛ ቅጣቱን መቀበሉ የማይቀር ነው
ስንቶቹን በክፋቷ አሳልፋ እንዳልሰጠቻቸው እሷን ከክፉ የሚጠብቃት ከሷ በብዙ ክንድ ራቀና አጋለጣት በክፋታችን ያራቅነውን የላይኛውን ጠባቂ የትኛውም የምድር ሀይል ሊተካው አይችልምና አብሯት የነበረው የሰፈራችን ሰውዬም አስረክቧት ፈረጠጠ።
ቪድዮውን ዘጋሁትና የድምፅ ቅጂ መልእክትን ከፈትኩት።
የድምፅ ቅጂው በሁለት ሰዎች መካከል የተደረገን ምልልስ ይዟል ።
የት እንደገባ እስካሁን ያልተመለሰልኝን ያንን ሽንት ቤት ድረስ ሄጄ የፈለኩት ሰውዬ ተከትሎት ሄዶ ሲያናግረው ይጀምራል•••
በቅጂው የመጀመሪያ አስር ሰከንዶች የኮቴ እና በጭፈራ ቤቱ በዛች ቅፅበት ሲዘፍን የነበረው የ ቦብ ማርሊ ዘፈን በስሱ ይሰማል ።
ልክ አስራ አንደኛው ሰከንድ ላይ •••
"ጤና ይስጥልኝ ?
ጤና ይስጥልኝ ምን ነበር እንተዋወቃለን ወንድም?
እኔ እንጃ እንተዋወቃለን መሰለኝ እንካ እስቲ እሄን ተመልከት!
ምንድን ነው እሱ ?
አይታይህም እንዴ መታወቂያ ነዋ !
ያ የሰፈራችን ሰው መታወቂያውን ካየ በኋላ መሰለኝ ድምፅ ተቀየረ።
ታድያ ም-ም-ም-ም-ም-ምን ልታዘዝ ጌታዬ? በርግጥ አላወኮትም ወይ ያጠፋሁት ነገር ይኖር ይሆን ?
ያጠፋሁት ነገር ይኖር ይሆን ትላለህ እንዴ ደሞ?
ለነገሩ ላንተም ለብዙዎቹም ለህግም ጥፋት መስሎ የማይታይ ጥፋት ስለሆነ አይታወቅህም
ማለት? እንዴት? መቼ? ምን አድርጌ ? የኔ ጌታ እስቲ ና አረፍ በልና ልጋብዝህ እየጠጣን እናውራ!
ህሊናቸውን በብራቸው ቁልል አፍነው የትውልድን አእምሮ የሚያቀንጭር ስራ ላይ ከተሰማሩ ከብቶች መሀል አንዱ ነህና ሰውን ሁሉ በብር በግብዣ ከመግዛት የሚሻገር አስተሳሰብ የለህም እንኳን እኔን ልትጋብዘኝ ከዚች ሰከንድ ጀምሮ አብረሀት ያለችውን አንድ ፍሬ ልጅ ደግመህ ሳታያት እዚሁ ቆሜ እያየሁህ በጓሮ በር ሹልክ ብለህ ጥፋ! ያለበለዚያ •••
ኧረ እሺ እሺ ጌታዬ እሄዳለሁ ግን የጓሮ በር ያለው አይመስለኝም ቤቱ!
በዛጋ ወደ ሽንት ቤቱ መጊቢያ በስተቀኝ በኩል ባለችው ቀጭን መንገድ ወደ ውስጥ ትንሽ ሄደህ ደረጃውን ቁልቁል ስትወርድ በር ታገኛለህ
እሺ ጌታዬ እሄው ያለብኝ ሂሳብ ነው!
ፍጠን!
እሺ እሄው ሄድኩኮ!"
ሰውየውን በዚህ መልኩ ቆሌውን ገፎ ማባረሩን ሳዳምጥ ከተሰማኝን ደስታ ጋር ግን እሄ ሰውዬ ማን ነው? ለምንድን ነው መታወቂያውን ሲያሳየው እንደዛ ምላሱን የዋጣት ይመስል ንግግሩ ሁሉ የተቆላለፈበት ?የሚለው ጥያቄ ገዝፎ አንቃጨለብኝ!።
ሰውየውን ለግዜው እንቆቅልሽ እንደሆነብኝ ተውኩትና ጆሲን ቀስቅሼ ከማታ ጀምሮ የተፈጠረውን ነገር ነገርኩት።
"ለማንኛውም ቪድዮውን ለመሲ ከመላክህ በፊት አስብበት ማለቴ አረጋጋው !" አለኝ።
ቅዳሜን በጣም እወዳታለሁ በዛ ላይ ዛሬ ከኤዱ ጋር ቀጠሮ አለን።
ከቀኑ ልክ 7:30 ላይ ኤዱ ደወለችና ሰፈር መድረሷንና ያለችበትን ቦታ ነገረችኝ ።
ስትነሺ ደውይልኝ መጥቼ እወስድሻለሁ ብያት ስለነበር ለምን ቀድማ እንዳልደወለችልኝ እየጠየኳት ከቤት ወጣሁና ብር ላይ, ያቆምኳትን ባጃጄን! አስነስቼ ከነፍኩ ።
እነሱ ሳያዩኝ ገና ከሩቁ እንዳየሁዋቸው ደነገጥኩ ግን ምን አስደነገጠኝ ? እኔ እንጃ!
ኤዱ ብቻዋን አልነበረም የመጣችው ሶስት ናቸው ከረድኤት አንድ ባለባበሱ ፍንድትድት ያለ ወጣት ወንድ አብሮአቸው አለ።
ማንም አብሮአቸው ቢኖር ግን ምን አገባኝ ?
ግን ለምን ሶስት ሆነው እንደሚመጡ ቀድማ አልነገረችኝም ?
ግን ማን ነው? እያልኩ መልስ በለላቸው ጥያቄዎቼ እራሴንም ባጃጇንም እያጣደፍኩ አጠገባቸው ደረስኩ።
ከሷ እና ከረድኤት ጋር በመተቃቀፍ ሞቅ ያለ የቅርብ ሰው ሰላምታ ከተለዋወጥን ብሀላ ፈንጠር ብሎ ሞባይሉን የሚነካካውን ልጅ እያመለከተችኝ ዳንዬ ተዋወቀው ባለፈው ከመሲ አስመለጠኝ ያልኩህ የክፍሌ ልጅ ፣ ጓደኛዬ እሱ ነው አለችና ደሞ እሱን
ቴዲዬ ተዋወቁ ምርጥ ወንድሜን " አለችው
ልጥጥ እንዳለ እጁን ዘርፕጋልኝ ጨበጥኩትና ግቡ እንሂድ አልኳቸው።
ባጃጅ ውስጥ ገብተው ወደቤት እየሄድን በመካከላችን ወሬ ጠፋ!።
በኔ በኩል የልጁ ሁኔታ ይሁን ሌላ ባይገባኝም የሆነ ደስ የማይል አዲስ ስሜት ውስጤ ሲላወስ እያዳመጥኩት ነበርና ዝም ማለቴንም አላስተዋልኩትም ነበር ።
እቤት እንደደረስን የውስጤ ስሜት ፊቴ ላይ እንዳይታይ እየታገልኩ ላጫውታቸው ብሞክርም ልጁ እኔ ከረድኤትም ይሁን ከኤዱ አልያም ከሁለቱን ጋር ወሬ ስጀምር እየጠበቀ በማክሸፍ ነበርና የራሱን የሚተኩሰው ሊያስወራኝ አልቻለም።
መናደድ ጀመርኩ። ልጁ እኔ ብቻ ላውራ አድምጡኝ በማለት የሚከተለውን ሙድና የኔን ንዴት በመጠኑም ቡሆን የተረዳችው ኤዱ ጀርባዋን ለሱ ሰጥታ እኔን ለማዋራት ሞከረች።
ከቆይታ በኋላ ካርድ ልግዛ በሚል ሰበብ ወጣ ብሎ ሲመለስ በፊት የነበረበትን ቦታ ትቶ እኔና ኤዱ መሀል ገብቶ ሲቀመጥ ንዴቴን መመጠንም መቆጣጠርም አቅቶኝ ጠፍቶ ድንገት ሀይል ጨምሮ እንደመጣ መብራት ሁለመናዬ ቦግ •••••

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍1
#እስቃለሁ

የውስጤን ረመጥ የልቤን ቃጠሎ
ለመሸፈን ብዬ
ይሄው እስቃለሁ እንከተከታለሁ
ከእንባ እየተናነኩ በሳቅ እወድቃለሁ
ከኀዘን እየታገልኩ ጥርሴን አሳያለሁ።

🔘በሰላም ዘውዴ🔘
#ሰላምታ

ጊዜ ጊዜን ሲወልድ
ዘመን ተቀይሮ
ወግ ባህል ተሽሮ
ሰላምታም አጠረ
መጣጥፍ ቁምጣ ሆኖ።

🔘በሰላም ዘውዴ🔘
#ልጩህበት!!


#ክፍል_አስራ_ስድስት


#ድርሰት_በጥላሁን


መናደድ ጀመርኩ። ልጁ እኔ ብቻ ላውራ አድምጡኝ በማለት የሚከተለውን ሙድና የኔን ንዴት በመጠኑም ቢሆን የተረዳችው ኤዱ ጀርባዋን ለሱ ሰጥታ እኔን ለማዋራት ሞከረች።

ከቆይታ በኋላ ካርድ ልግዛ በሚል ሰበብ ወጣ ብሎ ሲመለስ በፊት የነበረበትን ቦታ ትቶ እኔና ኤዱ መሀል ገብቶ ሲቀመጥ ንዴቴን መመጠንም መቆጣጠርም አቅቶኝ ጠፍቶ ድንገት ሀይል ጨምሮ እንደመጣ መብራት ሁለመናዬ ቦግ
••••
ቦግ አለ። ነደድኩ!፤ ፊቴ ተቀያየረ!፤ ደምስሬ ተወጣጠረ!
ልጁ ግን አየት አደረገኝና ከቁብም ሳይቆጥረኝ •••
"ኤድሻ ፌስ ቡክ ላይ የሆነ ፈን ነገር አይቼ እኮ ነው ቆይ ላሳይሽ እይውሟ እሄንን፤ እሄን አየሽው"እያለ ከሞባይሉ ላይ አይኗ እንዳይነቀል ስላደረጋት እሷም ሳታየኝ ተንጨርጭሬ እንደቀዘቀዝኩ ሆን ብሎ እኔን ለማናደድ እንደዛ እንደሚያደርግ በደንብ ያስታውቃል ብድግ አልኩና•••
እቤቴ ባትመጣ በዚህ አመት ከተጣላኋቸው ሰዎች አንዱ ትሆን ነበር ግን ምን ያረጋል
እቤቱ የመጣን ሰው ካልነከስኩ የሚለው ውሻ ብቻ ነው ውሻ ነገር ነህ አቦ! ገገማ! እያልኩ በውስጤ እየተሳደብኩ ተነስቼ ወጣሁና ግቢ ውስጥ ፊቴን መታጠብ ጀመርኩ።
ተመልሼ ስገባ እራሱ እያወራ እነሱ ሳይስቁ እራሱ ይስቃል ። የነበረን ቆይታ በልጁ ምክንያት ምኑም ሳይጥመኝ በሱ ውትወታ " በቃ እንሂድ" ብለው ተነሱ አላግደረደርካቸውም።

ከቤት እንደወጣን ግቢ ላድርሰችሁ ? አልኳቸው።
ከልቤ ነበር ከኛ ሰፈር ግቢ ድረስ ኮንትራት ካልያዙ በስተቀር ቀጥታ የሚወስዳቸው ታክሲ የለምና እንዳይቸገሩ ብዬ በማሰብ
"ስራ ትወጣለህ እንዴ ከዚህ ቡሀላ? አለችኝ ኤዱ
ስራ እንደማልወጣና እነሱን ብቻ አድርሻቸው ወደ ቤት እንደምመለስ ስነግራት•••
" አይሆንም በቃ ለኛ ብለህማ እዛ ድረስ መድከም የለብህም በትራንስፖርት እንሄዳለን!" ብላ ድርቅ አለች!
ተሰነባብተን ወደ ቤት ተመለስኩ።

አመሻሹ ላይ ጆሲ ድንገት በሩን ብርግድ አድርጎ ሲገባ ደንብሬ ተነሳሁ•••
"በለው በለው በቅዳሜ ቀን መጋደም ! ምን ሆነሀል አንተ ? እኔኮ የዳኒ እንግዳ ሄደች እንዴ ብዬ ሚሚ ባለሱቋን ስጠይቃት " ቆዩኮ ከወጡ!" ስትለኝ ገርሞኛል ቆይ ቆይ•••
በማህበር ተደራጅተው ነው እንዴ የመጡት?
እኔ እሷን ብቻ የቀጠርካት መስሎኝ አደል እንዴ የተቀየስኩት እዚሁ ደቅ ብዬ የቅዳሜ በርጫየን እንዳላጣጥም መሄድ እማልፈልግበት ቦታ ሄጄ ተጦልቤ ነው የመጣሁት ሰራህልኝ አቦ ቀጥሪያታለሁ ትመጣለች ከምትለኝ ይመጣሉ አትለኝም ወይ ምናለ ከመጡ ቡሀላስ ብትደውል መጥቼ ጀማውን እቀላቀል አልነበር እንዴ ! ግን እንዴት ነበር ውሎ?"
ኧረ ብትኖርልኝ ይሻለኝ ነበር ጆስዬ እኔም የመጨረሻ ተደውኬ ነው የዋልኩት !።

"እንዴ ለምን?" አለኝ ከበር ላይ ወደ ውስጥ ገብቶ አጠገቤ እየተቀመጠ
አላ! አብሯት የመጣው ልጅ ደዋኪ ነገር ነው ባክህ
"ማነው ልጁ ዝም ብሎ ጀለሳቸው ነው ወይስ•••?
አቦ ! ያ ነዎ! ባለፈው መሲ ልታስበላት ስትል ከጀለሶቹ ጋር ቀመር ቀምረው አስመለጣት ብዬ የነገርኩሁ የክፍሏ ልጅ
የፈራሁት ደረሰ ወይኔ ወንድሜን አንተ በህትነት ምናምን ነው እምንከባከባት እያልክ እራስህንም እኔንም ስትሸውድ በፍቅር የሚንከባከባትን አምጥታ አስተዋወቀችህ? ፍቅረኛዬ ነው ተዋወቀው ብላህ እጅ አፈችው አደል ?"
ውይይይይ ጆሲ ደግሞ እስቲ አሁን ማን እንደዛ አለ ? እንደዛ አለችኝ አልኩህ? ወጣኝ!?
"ታድያ እንደዛ ካልሆነ ምን አናደደህ? ብዬ ነዋ!"
አሃ! እኔ እምናደደው እሱ ስለጠበሳት ብቻ ነው ማለት ነው?
"ታድያ ፍላጎቱ እንደዛ መሆኑን ወይ አብሯት መሆኑን ብታውቅ እንጂ በምን ትናደዳለህ በዚ የማትናደድ ከሆነማ በምንም ልትናደድ አትችልም!"
ማለት?
"በዚህ ካልተናደድክ ሌላው ምክንያት እንዳለ ከዚህ በታች ነው ብዬ ነዋ!"
ይሆናል ብሎ ከመደምደም በምን ተናደድክ ብሎ መጠየቅ አይሻልም?
"እሺ በምን ተናደድክ?"
በቃ ልጁ እኔን ብቻ አድምጡኝ ከኔጋ ብቻ አውሩ ሙድ የሚያራምድ ነገር ነው ማለት•••አልኩና ከመጡ ጀምሮ የነበረውን ሁኔታ ነግሬው ሳበቃ••••
"ካካካካካ•••!" ሳቁን ለቀቀው!።
ምን ያስቅሀል?! አልኩት ተናድጄ!
" አይ ዳንዬ በዚህ ያልተሳቀ በምን ይሳቃል የፍቅርን አመል ስለማውቀው ነው አንድ ፈላስፋ ምን እንደሚል ታውቃለህ••••"
አላውቅምም ደሞም እንዳታወራልኝ ! ኤጭ አሁንስ አንተና ያ ጓደኛህ ወሬያችሁ ጅማሮውን በሙሉ
" አንድ ፈላስፋ ምን እንዳለ ታውቃለህ?
"እገሌ የተባለው መፅሀፍ ላይ ምን እንደሚል ታውቃለህ?
አንድ ምሁር ሰው ምን እንዳለ ልንገርህ?
በሚል እያሟሻችሁ የራሳችሁን ሀሳብ በቀላሉ ሰው እንዲቀበለው ለማድረግ የምትሄዱበት መንገድና
አለም ላይ ምን ተፈጠረ ብዬ ዜና ለማዳመጥ በተቀመጥኩ ቁጥር የሀገራችን የቲቪና ራድዬ ሚድያዎች
"ምሁራን ተናገሩ!
የህግ ባለሞያዎች ገለፁ!።
ነዎሪዎች እንዲህ አሉ !/
እገሌ እንዲህ አለ
እገሊት እንዲህ አለች" እያሉ የግልን አስተያየት ምልከታ አንድ ሰአት በሙሉ ዜና ብለው የሚያደርቁን ነገር እንዴት እንደሰለቸኝ •••
"በናትህ ይጠቅምሀል እቺን ብቻ አድምጠኝ ፈላስፋው እውቅ የግሪክ ፈላስፋ ነው ምን አለ መሰለህ ••••" ብሎ ሊቀጥል ሲል•••
በናትህ ተወኝ አልኩትና በንዴት ተነስቼ ክፍሉን ለቅቄለት ወጣሁ ። ስራ አልወጣም ያልኩት ሰውዬ ባጃጄን አስነስቼ ወደ ከተማ ከነፍኩ።
ንዴቴን በስራ ለመርሳት ተፍ ተፍ ስል አምሽቼ ልክ ከምሽቱ አራት ሰአት አከባቢ ከገንደቆሬ ወደ ሼል እየመጣሁ ብሎሰም ሆቴል ኩርባው ጋር እንደደረስኩ አንድ እድሜው በአርባዎቹ መጀመሪያ ላይ የሚሆነው ፈርጠም ያለ ጎልማሳ ሰው ሁለት እጁን በየተራ እያርገበገበ•••
"ባጃጅ ኮንትራት ኮንትራት " አለኝ ። አቆምኩና
የት? አልኩት ፊቱ ላይ እንደእሳት የሚንቀለቀለውን ንዴቱን እያስተዋልኩ
"የት እንደሆነች አላውቅም !
የገባችበት ጉድጓድ ውስጥ ገብቼ እስካገኛት ከኔ ጋር ነህ!
ያልከኝን እከፍላለሁ !"
አለኝና መጀመሪያ የምንሄድበትን ሆቴል ነገረኝ።
እየሄዱን በየመሀሉ •••
" እኔ ላይ! ለኔ እሄ ይገባኛል!" እያለ የአንዱ እጁን መዳፍ በሌላኛው እጁ ቡጢ ያጎነዋል።
ተናድጄ ብወጣ ከኔ የባሰ በንዴት የተከነ ሰው አጋጠመኝና የራሴን ንዴት ረሳሁት። ምን ሆኖ ይሆን እንዲህ ግብግብ ያለው? አልኩ ለራሴ።
ምን ሆነህ ነው ዘመዴ? አልኩት ፈራ ተባ እያልኩ•••
"ወይይይ ሴት ! አይይይ ሴት ገና ለገና ለሳምንት ያህል ለስልጠና ሀረር ሄጃለሁ ስላልኳት በከተማው የለም ብላ እግሬ ከመውጣቱ ቱ የማትረባ !
እሄማ መጀመሪያ የተቀባበለ እንጂ ሄጄ ገና ሶስት ቀን እንኳን ሳይሞላኝ ኬት ይመጣል እስካሁንም እየተጫወትሽብኝ ነበር ማለት ነው እኔ አንቺ ለማግባት ስሰናዳ በግዜ ጉድሽን ያሰማኝ!
ዛሬ ምን እንደሚውጥሽ አያለሁ "! አለ ።
ከንግግሩ ለኔ ጥያቄ መልስ እየሰጠኝ ይሁን ብሶቱን እየተነፈሰ መረዳት ተሳነኝና ግራ ተገብቼ ዝምታን መረጥኩ ። ትንሽ ቆየና •••
"የገዛ ጓደኛዬ አይቷት አይቷት እኮ ነው የደወለልኝ በአይነ ብረቱ ነው ያያት ወይኔ ደጉ ደግነቴን የዋህነቴን አይታ ነው የተጫወተችብኝ እነሱ እኮ ደግ ወንድ አይወዱም ዛሬ እጅ ከፍንጅ ስይዛት ምን እንደሚውጣት አያለሁ አጠገባ ያለውን ሰውዬ ትውጠው እንደሆነ እንተያያለን !"አለ።
ሁሉም ነገር ገባኝ። ፍቅረኛውን ከሰው ጋር ያያት ጓደኛው ደውሎለት እንደመጣ ተረዳሁ። በዚህ ሁኔታው ቢያገኛት ምን ሊፈጠር እንደሚችል ሳስበው ጨነቀኝ ።
ከሰው ጋር ታየች የተባለበት ሆቴል በር ላይ እንደደረስን በፍጥነት
👍1
​​​​በመውረድ እጁን እያወናጨፈ ወደ ሆቴሉ ቅጥር ግቢ ሲግሰግስ ወርጄ ተከተልኩት

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#የህይወት_ታሪክ

አሁን እኔ ብሞት ፥ ከኔ ምን ይቀራል?
ስኖር “ክፉ” ያለኝ
“ደግ ሰው ነበረ " ; እያለ ያወራል
“እሱ ሰው አይደለም” ፥ ሰይጣን ነው መሠሪ"
ሲለኝ የከረመ
“መልካም ሰው ነበረ ፥ መልአክ መሥሎ ኗሪ”
ብሎ ቀብሬ ላይ ፥ እንባውን ይዘራል
መቼም በዚህ ሀገር
ሲኖር የተናቀ ፥ ሲሞት ይከበራል ።
•••
የሚጠላኝ ሁላ
ተወዳጅነቴን ፥ ቀብሬ ላይ ያወሳል
መቼም በዚህ ሀገር
ሲኖር የሚነቀፍ ፥ ሲሞት ይወደሳል
ሲኖር የተረሳ ሲሞት ይታወሳል ።

🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
#እንሆ_ነፃነት 💚 💛 ❤️

“የጠላህ ይጠላ ፥ ብድሩ ይድረሰው”
ያጎደፈህ ይጉደፍ ፥ ጭቅቅት ያልብሰው።”
ብዬ አልራገምም!
ጠላትህ ጠላቴ ፥ ነፍሴን ሲያስጨንቃት
የእውነት አንገትህን
የተረት ሸምቀቆ ፥ አስገብቶ ሲያንቃት
አንተን ለሚረግሙ
አንተ እንዳስተማርከኝ ፥ እነሆ ምርቃት።
የጠላህ ይወደድ ፥ ይራቀው አመፃ
ያጨቀየ ይጥራ ያጎደፈህ ይንፃ!
ባንተ የጨቆነኝ
ቂም በቀል ጥላቻን ፥ ፈፅም አይቅመሰው
አንተ እንዳስተማርከኝ ፥ ነፃነት ላውርሰው
እነሆ ነፃነት
እነሆ አንድ እውነት
ሚኒሊክ ጥቁር ሰው!

🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
#ልጩህበት!!


#ክፍል_አስራ_ሰባት


#ድርሰት_በጥላሁን

ምን ሊፈጠር እንደሚችል ሳስበው ጨነቀኝ ።
ከሰው ጋር ታየች የተባለበት ሆቴል በር ላይ እንደደረስን በፍጥነት በመውረድ እጁን እያወናጨፈ ወደ ሆቴሉ ቅጥር ግቢ ሲግሰግስ ወርጄ ተከተልኩት•••
ወደ ውስጥ ስንዘልቅ ያን ያህልም ሰው ስላልነበረ አየት አየት አድርጎ እየወጣን•••
"የለችም ባክህ••• እዚህ መጥታ ጭር ሲል ደብሯት ቦታ እንቀይር ብላው ይሆናል አውቃታለሁ እኮ ልትዝናና ስትወጣ ግርግር ትወዳለች ሰው ከማን ጋር እንደሆነች እንዳያስተውላት ነው መሰለኝ ከኔም ጋር ስትዝናና ቦታው በሰዎች ጢም ካላለ አይመቻትም!
ወይኔ ደጉ ያኔ መች ገባኝ !
አሁን አሁን እኮ ነው ቀስ እያለ ነገረ ስራዋ በሙሉ የሚገለጥልኝ
የባጥ የቋጡን እየለፈለፈ ተመልሰን ባጃጇ ውስጥ እንደገባን
"ንዳው! ንዳው! አለኝ።
ወዴት ልንዳው? ስለው•••
"ከሶስቱ ውጪ አትሆንም!" አለና
ትኖራለች ብሎ የሚጠረጥርባቸውን ሶስት ጭፈራ እና ሆቴል ቤቶች ነግሮኝ
"ከሚቀርብህ ጀምር" አለኝ።
በቅርብ ወዳለው አዙሬ መንዳት እንደጀመርኩ ፍቅረኛውን ከሌላ ሰው ጋር ስትቀብጥ ያያት ጓደኛው ሲደውልለት ከምሽቱ ሁለት ሰአት ተኩል አልፎ እንደነበርና በብስጭት ከሀረር ብቻውን አንድ ሚኒባስ በመያዝ የሙሉ ሰው ከፍሎ እንደመጣ ነገረኝ።
አሳዘነኝ።
ምናልባት የእውነት ሆኖ ከሆነ የሆነው ሆነ የኔ ስጋት ግን በሷ መከዳቱ ሳያንስ በብስጭት ያልሆነ ፀብ ውስጥ ገብቶ መታሰር የሚሉት ሌላ ጣጣ ውስጥ እንዳይገባ ነው።

ቢረጋጋ ጥሩ ነበር ምን ብዬ ላረጋጋው ? ትንሽ አሰብ አደረኩና
ቆይ ብታገኛት••• ማለቴ እንደተባለው ከሰው ጋር ሆና ብታገኛት ምን ልታደርግ ነው?
"እኔ እንጃ ብቻ ላግኛት ያኔ የሚሆነው ይሆናል በናትህ ራቅ ስለሚል ፍጠን!
በበኩሌ ከወንድ ልጅ ጋር ተዝናናች ማለት ወሰለተች ማለት ነው ብዬ አላምንም!
ተዝናንታ ክብሯን ጠብቃ ወደ ቤቷ ልትመለስ አስባ ሊሆን እንደሚችልም ማሰቡ ጥሩ ነው ያንን ካሰብክ ቡሀላ የሚፀፅትህን ነገር ከማድረግ ትቆጠብና ቅድሚያ ቢያንስ እርግጠኛ ለመሆን ትሞክራለህ አይመስልህም ስለው
አይመስለኝም በጭራሽ አይመስለኝም እኔ የፍቅር ሂወቴን በመሰለኝ ሳይሆን ልቤ በሚለኝ በራሴ እምነት ነው የምመራው
በኔ እምነት ሴት ልጅ አንሶላ የተጋፈፈች ቀን ሳይሆን ወንዶችን ቀለል ብላ የመቅረብ ባህሪ ያላት መሆኑን ያወኩ ቀን ነው እምነቷንና እምነቴን የምታጎድለው!"
ማለት?
ቀለል ብላ የመቅረብ ስትል ጭራሽ የወንድ ዘር መቅረብ የለባትም እያልከኝ እንዳይሆን?! ስለው
"አንድ ነገር ልጠይቅህ ?" አለ ።
ጠይቀኝ
"ለግዜው የማይፈልገው ገንዘብ እንዳለው ማበደር እንደሚችል እያወክ 300 ብር አበድረኝ ስትለው የለኝም ብሎ የከለከለህን ሰው በሌላ ግዜ አንድ ሺ ብር አበድረኝ ብለህ ትጠይቀዋለህ?
ካላበድኩ በስተቀር እንኳን ሺ አንድ ብርም አልጠይቀውም ግን እሄ ከፍቅር ወይም ካነሳነው ጉዳይ ጋር ምን አገናኘው?
"ሌላ ጥያቄ ልድገምህ ያኔ በምን መልኩ እንደሚገናኝ ሳልነግርህ እራስህ ትረዳዋለህ"
እሺ ቀጥል
"ታክሲ ውስጥ ባጋጣሚ አጠገብህ የተቀመጠችውን ሴት ልታዋራት ልታጫውታት ስትሞክር ፊቷን እንዳኮማተረች ወደ አንተ አንድም ግዜ እንኳን ዞራ ሳታይ ልክ እንደሹፌሩ ፊት ለፊቷን ብቻ እየተመለከተች ጫወታህን ባጭር ባጭሩ ዝግት የሚያደርግ መልስ እየመለሰች ብታከሽፍብህ ከመለያየታችሁ በፊት ስልክ ቁጥሯን ለመጠየቅ ትደፍራለህ?"
ሰውየው ነገሮችን ቤት በኩል እያገናኛቸው እንደሆነ እያሰላሰልኩ መልስ ሳልሰጠው ስለ ዘገየሁ
"መልስልኛ! ትጠይቃታለህ?!
እንዴ ፊቷን አጨማዳው እንዴት ልጠይቃት እችላለሁ አልጠይቃትም መጀመሪያ ልግባባት ስሞክር ፊት ከነሳችኝ ከታክሲው እስክወርድ ዞሬም ሳላያት እንደምሄድ እርግጠኛ ነኝ።
" አየህ መጀመሪያ ቀለል ብላ አንተ የባጥ የቆጡን ስትቀባጥር ከገለፈጠችልህ ግን ስልክ ለመጠየቅ ቀለለህ ማለት ነው!
ስልክ ስጠይቅ በቀላሉ ከተሰጠህ ደግሞ ደውሎ እንገናኝ ልጋብዝሽ ለማለት ቀለለህ
ግብዣህን በቀላሉ ከተቀበለች ወደ ቀጣዩ ጉዳይህ ለመግባት አልጋ ባልጋ ሆነልህ ማለት ነው ስለዚህ እቺ ሴት የኔዋ ብትሆን እምነቷን የሸረሸረችው መቼ ነው? ብዬ እራሴን ብጠይቅ
በኔ እምነት አልጋ ውስጥ ሳይሆን ታክሲ ውስጥ የተገናኛችሁ ቀን ነው ያን ቀን እኔ ባጋጣሚ እሷ ሳታየኝ ከጀርባችሁ ቁጭ ብዬ ቢሆን መጨረሻችሁን አልጠብቅም እንደከዳችኝ የምቆጥረው ያኔውኑ ነው!"
ሲለኝ የእውነት ነበርና አመለካከቱ ያስደነገጠኝ
በዚህ ሀሳብህ በፍፁም አልስማማም እስቲ አንተንም አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ አንዳንድ ሴቶች
ፍቅረኛም ባልም ሳይኖራቸው ፣ ያሉበት ሁኔታ ፍቅር ለመጀመር ፈቅዶላቸው፣ ውስጣቸውም ፍቅር ለመጀመር ፍላጎት እያለው
በዛ ላይ ሽቅርቅር ብለው እየወጡ በተለያየ አጋጣሚ ከወንዶች ጋር በተገናኙ ቁጥር ወንዶቹ ሊቀርቧቸው ሲሞክሩ ኮሶ የጋቷቸው ይመስል
ፊታቸውን ከስክሰው የወንዶችን ቆሌ የሚገፉት በምን ምክንያት ነው?ስለው•••
"አይነጥላ ነው አዎ አይነ ጥላ ያለባት ሴት ካልሆነች በስተቀር በዚህ ሁኔታ ላይ ሆና በጤናዋ እንደዚህ የምትሆን ሴት ብዙ የምትኖር አይመስለኝም! ብሎኝ አረፈው። ሳይታወቀኝ እየጮህኩ
አትሳሳት ይልቅ
የተግባባች ፣ የሳቀች፣ ወንዶችን በቀላሉ የቀረበች ሴት ሁሉ ሌላ ፍላጎት አላት የተኮሳተረች ሴት ሁሉ ደግሞ ፍላጎት ስለለላት ነው ብለህ መደምደም ትልቅ ስተት መሆኑንን ብታምን የተሻለ ይመስለኛል!
አንተ ምናልባት ከፍቅረኛህ ውጪ ልክ እንደወንዶች ጓደኛችህ በጓደኝነት የምትቀርባቸው ሴቶች ከሌሉ አላቅም!
እኔም ወንድሜቼም ጋደኞቼም በዚህ መልኩ የምንቀርባቸው ሴቶች አሉ አንዳንድ ሴቶች እንደውም ሁሉም ወይም አብዛኛቹ የቅርብ ጋደኛቻቸው ወንዶች እንዲሆኑ እንደሚፈልጉና እንደሆኑም የሚናገሩ አሉ ።
በጋደኝነት ህይወታቸው ወጣ ብሎ ከመዝናናት አንስቶ ብዙ ነገሪችን በጋራ ያሳልፋሉ ያ ማለት በተገኘው አጋጣሚ በሙሉ ሌላ ጉዳይ ውስጥ ይገባሉ ማለት አይደለም!።
"እሱማ ፍቅረኛ ወይም ባል ሳይኖራቸው ሊሆን ይችላል"
ኧረ እያላችው ! እሄውልህ ማናችንም ብንሆን የምንፈልገውን ነገር ለማድረግ የሚከለክለን የፍቅር ጓደኛ መኖር ወይም አለመኖሩ ሳይሆን የውስጣችን ስብእናና የልባችን ትርታ ብቻ ነው
ምንም ነገር ለማድረግ መቀራረብ ሳይሆን መተዋወቅ በማያስፈልግበት በዚህ ዘመን ፍቅረኛህን ታሟኝ የምታደርገው ወንድ አትቅረቢ እያልክ በመጮህ ሳይሆን እራስህን ልቧ ውስጥ ማስቀመጥ ከቻልክ ብቻ ነው ያለበለዚያ ፍቅረኛ ሳይሆን እረኛ ሆነህ ትቀራለህ"! አንተን ለማለት ፈልጌ አይደለም ይቅርታ አመለካከቴን ነው ያወራሁት አልኩትና በዛው ቀጠል አድርጌ•••
ወደ ሆቴሉ እየደረስን ነው ይልቅ አሁን ወደ ጉዳያችን እንመለስና እንደታናሽ ወንድም እምመክርህ ምናልባት ከሰው ጋር ሆና ብታገኛት በኔ በኩል ኩሩና በሳል ወንድ ሆነህ ብታሳያት ደስ ይለኛል!
"ማለት?!"
የተባለው እውነት ሆኖ ከተገኘ በቃ አለ አይደል ምንም ሳትናደድ
ለሁሉም ነገር አመሰግናለሁ እንኳንም በግዜ አወኩሽ መልካሙን ሁሉ እመኝልሻለህ!" ብለህ ብቻ ብትለያት
"ምንምንምምን !? "ያልተነካ ግልግል ያውቃል" አሉ ደሞ መች በግዜ አወኳት ከዛ በፊት ያንከራተተችኝን ተወው እሺ ብላኝ አብረን ከሆንን እንኳን አንድ አመት ከስድስ ወር ሆኖናል እኮ!"
ቢሆንም ገና አልተጋባችሁም ብዬ ነዋ!
"እና ባንጋባስ?!"
ማለቴ እንደምታገባት እርግጠኛ ካልሆነች•••
አልኩና መናደዱን ከድምፁ በመረዳቴ ያሰብኩትን ሳልጨርሰው ዝም አልኩ•••
"ካልሁነች ምን?! ጨርሰዋ !
ኧረ በናትህ ተወኝና
👍2
​​ዝም ብለህ ንዳ አንተ ደሞ
ነው ወይስ አብሯት ያለው ሰውዬ አጎትህ ነው ብዙ ተከራከርክላት እኮ !"
ሲለኝ እውነትም ዝም ብዬ ብነዳስ አልኩና ዝም አልኩ ።
እንደደረስን ምንም ሳይለኝ ወርዶ ወደ ሆቴሉ ሲገባ ተከትየው ገባሁ።
በር ላይ ቆም ሲል ቆምኩ።
ወደውስጥ ገልመጥ ገልመጥ አደረገና ካጠገቤ ድንገት ተፈናጥሮ በመሄድ ቀዝቀዝ ባለው ዘፈን ጥንድ ጥንድ ሆነው ተጣብቀው ከሚወዘወዙት መሀል•••

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍1
​​#ልጩህበት!!


#ክፍል_አስራ_ስምንት


#ድርሰት_በጥላሁን

ኧረ በናትህ ተወኝና ዝም ብለህ ንዳ አንተ ደሞ
ነው ወይስ አብሯት ያለው ሰውዬ አጎትህ ነው ብዙ ተከራከርክላት እኮ !"
ሲለኝ እውነትም ዝም ብዬ ብነዳስ አልኩና ዝም አልኩ ።
እንደደረስን ምንም ሳይለኝ ወርዶ ወደ ሆቴሉ ሲገባ ተከትየው ገባሁ።
በር ላይ ቆም ሲል ቆምኩ።
ወደውስጥ ገልመጥ ገልመጥ አደረገና ካጠገቤ ድንገት ተፈናጥሮ በመሄድ ቀዝቀዝ ባለው ዘፈን ጥንድ ጥንድ ሆነው ተጣብቀው ከሚወዘወዙት መሀል•••
በስተግራዋ እስከ ባቷ መገባደጃ የተቀደደ ትከሻውን በዞሩ ሁለት ቀጫጭን ገመዶች ተንጠልጥሎ ከደረቷ ጀምሮ ቁልቁል ገላዋ ላይ ቀዳዋ እስኪመስል የተጣበቀ እሮዝ ቀለም ያለው የራት ልብስ ለብሷ አብሯት እሚደንሰው ሰው አንገት ውስጥ በፍቅር መርከብ እየተንሳፈፈች የምትደንሰውን ሴት ክንዷን ይዞ በመጎተት ከሰውየው እቅፍ ውስጥ መንጭቆ አወጣት!
እሷ ምን መጣ ብላ በድንጋጤ ስትዞር፤ እሱ ፊቷን አይቶ የሱ ፍቅር አለመሆኗን ሲረዳና አብሯት ያለው ሰው ይቅርታ የምትለውን ቃል ከፉ አውጥቶ እስኪጨርሳት እንኳን ግዜ ሳይሰጠው ተደፈርኩ በሚል ስሜት እንደነብር ተወርውሮ አንገቱን ሲያንቀው ዘልዬ መሀላቸው ገባሁ!
ይቅርታ አርግለት ባባ በስተት ነው በስተት ነው ስለው መጀመሪያውኑ ፊቷን እንዳየ ሲደነግጥ አስተውሎት ነበር መሰለኝ ከማነቅ ውጪ ቦክስ እንኳን ሳይሰነዝር•••
"እብድህን ወደዛ ይዘህልን ውጣ ባክህ ! ብሎ እሱን ገፈተረውና ሽምቅቅ ብላ ወደቆመችው ፍቅሩ ዞሮ •••
" አስደነገጠሽ አይደል የኔ ማር?!" አላት። እኛም በፍጥነት ተያይዘን ውልቅ አልን።
ባጃጅ ውስጥ ገብተን ወደሶስተኛው ቤት ጉዞ እንደጀመርን ድንጋጤው ለቀቀው መሰለኝ•••
"አይገርምም የሰይጣን ስራ ቁመቷ፣ ከለሯ፣ ፀጉራ ከነ አያያዟ እራሷን ቁጭ እኮ ነች በዛላይ የለበሰችው ልብስ ተውሳት ነው እንዴ እውነቴን ነው ሀሉንም ነገር ከፍቅረኛዬ የተዋሰችው እኮ ነው እምትመስለው ቢያንስ እንኳን በውፍረት መለያየት የለባቸውም ደባዋ እራሱ ቁጭ የኔዋን!" ሲል
ሳቄን በጭራሽ መቆጣጠር አልቻልኩም ኪኪኪኪኪ•••
"ሳቅ አንተ ምን አለብህ!"
እና በዛች ሰከንድ ውስጥ እሄን ሁሉ ደባዋን (ቂጧን ) ሳይቀር ማየትህ ቢያስቀኝ በኔ ይፈረዳል?
"ኧረ አይፈረድም"
እሄኔ ልጅቷ ከፍቅረኛህ ጋር በብዙ ነገሯ ትለያይ ይሆናል አንዳንዴ ውስጣችን የሚፈልገውን ነው አይናችን የሚያየው ለዛ ይሆናል።
አልኩትና በሆዴ ዛሬማ የከተሟዋ ሴቶች ሁሉ እሷን መስለው ነው እሚታዩህ ብዬ አከልኩበት።
ሶስተኛው ቤት ገባን እዛም አልነበረችም።
አሁን የቀረን አንድ ቦታ ብቻ ነው ወደዛው መብረር ጀመርን።
ልንደርስ ትንሽ ሲቀረን መንገድ ላይ ወዳለ ወደ አንድ ከፍንዳታዎችና ከዩንቨርስቲ ተማሪዎች ውጪ ሌላ ሰው ወደማይገባበት ቀውጢ ጭፈራ ቤት እየተገላመጥኩ መቸስ እዚህ አትኖርም አደል ስለው•••
ድንገት በሩ ላይ ኤዱን አየኋት ሊያውም ከዛ ልጅ ጋር!
በፍጥነት እየነዳ ድንገት ሰው እንደገባበት ሹፌር ልቤ ስንጥቅ ሲል ፍሬኑን ጭምቅ አደረኩት ባጃጇ ሲጢጢጢጢጢጢ ብላ ቀጥ ስትል ሰውየው ተፈናጥሮ ወደ ትከሻዬ መጣና ሳይመለስ •••
"ምነው! ሰው ገባብህ? ውሻ ገባብህ?" እያለ ወደ ፊት በማንጋጠጥ ምን እንደገባብኝ ለማየት ሲሞክር •••
ሰው አይቼ ነው።አልኩት።
"ማንን? አየሀት? እሷን ነው? የቱጋ? የታለች?" ሲል •••
ማነች እሷ አልኩት ግራ ተጋብቼ
" የኔዋ ነቻ! የኔዋ ጉድ ሌላ ማንን ታያለህ!"
ወይ ጉድ••••
"የጨነቀው እርጉዝ ያገባል ብለው ከሚተርቱ የጨነቀው የሚናገረውን አያውቀው ቢሉ ኖሮ ሳይሻል አይቀርም እስቲ አሁን የሱን ፍቅረኛ የት አውቂያት ነው የማያት ?
እንኳን ለኔ ለራሱም ሳትጠፋበት አትቀርም እያልኩ ውስጥ ጫጫታው ስላልተመቻቸው ሳይሆን አይቀርም ስልክ ለማናገር ወጥተው አንድ ስልክ እየተቀባበሉ በጋራ ከሚያውቁት ከሌላ ሰው ጋር እያወሩና እርስ በርስ እየተያዩ ወደ ሚሳሳቁት ወደ እነ ኤደን ከርቀት እንዳፈጠጥኩ •••
ወርደህ ቀጥ ብለህ ሂድላት ከዛ ኤዱ ቅድም ከቤት ስትወጡ ወደ ግቢ ነው እምንሄደው ብለሽ መዋሸቱ ለምን አስፈለገ እኔን ዋሽኝ ችግር የለውም ግን በዚህ ሰአት ሊያውም እዚህ በየቀኑ ፀብ በማያጣው ጭፈራ ቤት ውስጥ ምን ትሰሪያለሽ በላት በላት የሚል ስሜት ተሰማኝ።
ዘወር ብዬ ሰውየውን ሳየው እሱም ግራ ተጋብቶ እኔን ተከትሎ እነ ኤዱ ላይ አፍጥጧል።
መለስ አለና " ማነች? ታውቃታለህ? " አለኝ
ማነች ልበለው? አዎ ያክስቴ ልጅ ነች፤ የዩንቨርስቲ ተማሪ ነች በዚህ ሰአት ከወንድ ጋር ጭፈራ ቤት••••
አላስጨረሰኝም •••
"ታድያ ምን ችግር አለው አለው አብረው ተዝናንተው የሚለያዩ ንፁህ ጋደኛሞች ሊሆኑ ይችላሉ ። አለኝ በስላቅ ።
በንዴት •••
አዎ ችግር የለውም ይዝናኑ እኛም እንሂድ አልኩና ባጃጇን አስነስቼ ወደ መጨረሻው ቤት ጋለብኳት።
ደርሰን እሱ ከፊት እኔ ከጀርባው ተከታትለን እንደገባን
"ያቿትና"
አለኝ ፊት ለፊት ካንድ ሰው ጋር የተቀመጠች ቆንጂዬ ሴት ተመለከትኩ ።
ወደሱ ስዞር አራት ጣቶቹን ከንፈሩ ላይ ጭኖ እንዳፈጠጠባቸው ትንሽ ቆየና
"ውይ ውርዴት !
አቤት ቅሌት !
እሄ እኮ ውጪ ሀገር የነበረ ያክስቷ ልጅ ነው የሰርጋችሁን ግማሽ ወጪ እኔ እችላችሃምሀለሁ ብሎ ቃል ገብቶልናል! በቅርብ ነው የመጣው።
ጓደኛዬም ያላወቀው ለዛ ነው!
እነደመጣ አዲስ አበባ ነበር ያረፈው ሰሞኑን ወደ ድሬ ይመጣል ስትለኝ ነበር እንደዛ ሲፎክር የነበረው ሰው ጭራሽ "ደብቀኝ እንዳታየኝ ! "
እያለ እኔን ጎትቶ ከጀርባዬ ተደበቀና
"ዝም ብለህ ወደ ኋላ ና እንውጣ!" አለኝ።

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
​​#ልጩህበት!!


#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ


#ድርሰት_በጥላሁን

ደርሰን እሱ ከፊት እኔ ከጀርባው ተከታትለን እንደገባን
"ያቿትና"
አለኝ ፊት ለፊት ካንድ ሰው ጋር የተቀመጠች ቆንጂዬ ሴት ተመለከትኩ ።
ወደሱ ስዞር አራት ጣቶቹን ከንፈሩ ላይ ጭኖ እንዳፈጠጠባቸው ትንሽ ቆየና
"ውይ ውርዴት !
አቤት ቅሌት !
እሄ እኮ ውጪ ሀገር የነበረ ያክስቷ ልጅ ነው የሰርጋችሁን ግማሽ ወጪ እኔ እችላችሃምሀለሁ ብሎ ቃል ገብቴልናል! በቅርብ ነው የመጣው።
ጓደኛዬም ያላወቀው ለዛ ነው!
እነደመጣ አዲስ አበባ ነበር ያረፈው ሰሞኑን ወደ ድሬ ይመጣል ስትለኝ ነበር እንደዛ ሲፎክር የነበረው ሰው ጭራሽ "ደብቀኝ እንዳታየኝ ! "
እያለ እኔን ጎትቶ ከጀርባዬ ተደበቀና
"ዝም ብለህ ወደ ኋላ ና እንውጣ!" አለኝ።
እየተጓተትን ወጣን።
እሺ አሁን ወዴት እንሂድ? ስለው•••
"ዛሬ በቃ ካንተ ጋር የመረጥከው ቦታ ስጠጣ አድሬ ጥዋት በዛው ወደሀረር መመለስ ነው
እምፈልገው ግን ፍቃደኛ ከሆንክ ነው ?"
አለኝ እኔም በኤዱ ተከፍቼ ስለነበር መጠጣት ፈለኩ በሀሳቡ ተስማማሁና ተያይዘን ሄድን እየጠጣን ስለራሱ ብዙ እያወራልኝ ቆየና ድንገት በመሀል •••
"ቅድም ከልጁ ጋር ያየሀት ልጅ ግን እውነት ያክስትህ ልጅ ነች እንዳትዎሸኝ በናትህ እ ያክስትህ ልጅ ነች?"
ለምን ጠየከኝ ? አልኩት
"እኔ እንጃ የሆነ የፍቅር ስሜት አይንህ ውስጥ ያነበብኩ መስሎኝ ነው እ ተሳሳትኩ?!"
ኧረ በጭራሽ የፍቅር ስሜት እኔ ላይ ልታነብማ አትችልም ግን ያክስቴ ልጅ አይደለችም ብዬ ስለኤዱ በስሱ ነገርኩት ጎህ ሲቀድ ትዝ ይለኛል ግን ብዙ ከመጠጣቴ የተነሳ መች? እና እንዴት? እሱ ወደ ሀረር እኔም ወደ ቤት እንደገባሁ ትዝ አይለኝም።
በነጋታው ስድስት ሰአት አከባቢ ተነሳሁና ገላዬን ተጣጥቤ ወደ ስራ ወጣሁ።
በአከባቢያችን ባለ አንድ ምግብ ቤት ገብቼ ምሳ አዘዝኩና ከመምጣቱ በፊት ኤደንጋ ደወልኩ።
አነሳችው ድምፁዋ ስትጨፍር ማደሯን ይመሰክራል ሰላምታ ከተለዋወጥን ቡሀላ•••
የት ነሽ?
"ዶርም ነኝ ጋደም ብዬ !
ትናንት ታክሲ አገኛችሁ?
አዎ ዳንዬ ካንተ ጋር እንደወጣን ወድያው ነው ያገኘነው;"
በግዜ ገባችሁ?
አዎ ምነው?
አይ ምንም ከአንደበትሽ ልስማው ብዬ ነው!
ምኑን ዳኒ?
በቃ ተይው!
ምን ሆነሀል ዳኒ!?
ምን ሆንኩ?!
"አይ ምን እንደጠየከኝ እንኳን ሳይገባኝ በቃ ተይው ስትለኝ ግራ ገብቶኝ ነው"
በቃ እንደውም እንኳን ያልገባሽ ወሬ እንቀይር••
እሺ ካልክ!
እሺ!
"እሺ ምን!"
እሺ ምንም!
እንዴ ዳኒ ግራ አጋባከኝ እኮ ወሬ እንቀይር አላልክም እሺ ስለ ምን እናውራ?"
ምን አዲስ ነገር አለ?
"ምንም ዳኒዬ ምን አዲስ ነገር ይኖራል ብለህ ነው"
በቃ እሺ
በቃ እሺ ምን?
በቃ እሺ ቻዋ አዲስ ነገር ከሌለ!
"እሺ ቻው ግን•••" እያለች ስልኩን ዘጋሁት።
ስራው አስጠላኝ ባጃጄን ላጣቢ ሰጥቼ ገብቼ ተኛሁ።
ከትንሽ ቆይታ ቡሀላ ጆሲ እና ያ ጅምር እብድ ጓደኛው በርጫቸውን ይዘው እየተሳሳቁ ሲገቡ በሆዴ ተደፍቼ በመተኛት የተኛ ሰው መሰልኩ።
ጆሲ••••" እንዴ ዳኒ ስራ ወጥተህ አልነበር እንዴ በል ተነስ አትደብረን •••" ምናምን እያለ ሊቀሰቅሰኝ ቢሞክርም አውቆ የተኛን እንዲሉ ዝም አልኩ።
ከቆይታ ቡሀላ ከነመኖሬም ረስተውኝ ጆሲ እና ጓደኛው በራሳቸው አለም ውስጥ ገብተው የባጥ የቋጡን መዘባረቅ ጀመሩ።
የተኛሁ መስዬ ብተኛም ወሬያቸው እረፍት ነሳኝ ከአንዱ ርእስ ወደ ሌላ ለመሄድ ምንም አይነት ቅድመ ሁኔታ አይጠብቁም ወሬያቸውን ይጀምሩታል እንጂ አያልቅም።
ብስጭትጭት ብዬ በመነሳት ቤቱን ጥየላቸው ስወጣ ጆሲ•••
"ና እንጂ ዳንዬ! ወዴት ልትሄድ ነው? ረበሽንህ እንዴ! ማታ ሰክረህ ምን ስትል እንደነበር ልንገርህ ክክክክ !"
መልስ ሳልሰጠው ወጥቼ ሄድኩ።
ከዛን ቀን ቡሀላ ህይወቴ እራሱ የሰከረ ሆኖ ታየኝ ከኤዱ ጋር እንኳን ልንገናኝ ስልክ ተደዋውለን ሰላም ሰላም ከመባባል ውጪ የረባ ነገር ሳናወራ ወራቶች ተቆጠሩ የሷን ባላውቅም እኔ ግን ከራሴ ጋር ስለሷ ሳላወራ አድሬ አላውቅም ።
ጥፋተኛዋ እሷ ሆና ሳለ ስለመገናኘት አንስታብኝ ስለማታውቅ እልህ ያዘኝ ።አንድም ቀን ላግኝሽ ሳልላት አልፎ አልፎ በስልክ ድምጿን ብቻ እየሰማሁ ብቆይም ጤነኛ አለነበርኩም።
ለካ ከፍቅር ጋር እንደመጣላት ከባድ በሽታ የለም ቆይ በአለም ላይ ከፍቅር ጋር ተጣልቶ ያሸነፈ ጀግና አለመኖሩን እያወቁ ፀብ መግጠም ምን ይሉታል እኔ ማነኝ እናነው እንኳን ተራው እኔ ክርስቶስም የተረታው ለፍቅር አይደል እንዴ?! ምን እሚሉት ነው እሄ ትንቅንቅ ! እውነታውን ብረዳም ብቻየን መታመም ብቻ ሆነ ስራዬ ያለሁበትን ሁኔታ እንኳን ለሷ ለጓደኛዬ ለጆሲም አልነገርኩትም ።
ሁኔታዬን ተረድቶ ሲጠይቀኝም መልሴ ቀና አልነበረም በብስጭት እጬህበታለሁ።
"ማፍቀር እኮ መታደል ነው ዳንዬ አፍቅረሀታል በቃ ለምን አታምንም?!" ሲለኝ
ቁስሉን እንደነኩበት አንበሳ ቁጣዬ ገንፍሎ እጮሀለሁ እሱም ድርቅ ያለ ደረቅ አደል ይስቅና •••
"ጩኸትህ መሸነፍህን በደንብ በፍቅሯ መንበርከክህን ያረጋግጥልኛል እንጂ ሀሳቤን አያስቀይረኝም ይልቅ ብናወራ ይሻላል በጩኸት ዝም ልታስብለኝ አትሞክር!
ጓደኛዬ አንተኮ መፍታት ያቃተህ እራስህ ያሰርከውን ገመድ ነው አውቃለሁ እራስህ ያሰርከውን ገመድ መፍታት አለመቻል እጅግ ያበሳጫል ነገር ግን እየተበሳጨህ አልፈታ ያለህን ቋጠሮ ጎትተህ ልትበጥሰው በሞከርክ ቁጥር ጭራሽ እያጠበከው እንደምትሄድ እወቀው!!
በቃ ልትበጥሰው ልታስቀረው አለመቻልህን እመን ያኔ ቢያንስ ላትበጥሰው እየጎተትክ ከማጥበቅ ትቆጠብ ይሆናል!
ለማንም ሳትናገር ብቻህን በተብሰከሰክ ቁጥር መጨረሻህ ማበድ ይሆናል እሺ እሄን እወቀው ብሎኝ ካጠገቤ ይሄዳል!
ቤቱን ብቻውን አገኘዋለሀ!
ያኔ "" ኤዱን በናትሽ አንዴ ብቻ ልጩህ!?" ያላት ሰካራም ፊቴ ድቅን ይላል በሩን እዘጋና ልክ እንደሱ እጬሀለሁ !
በዚህ ሁኔታ ብዙ ታገልኩ ዛሬ ግን አልቻልኩም!
ለሊቱን ሙሉ በህልሜ ሳያት ስላደርኩ ነው መሰለኝ ናፍቆቴ ልኩን አለፈ ባላገኛት እንኳን ወደዛ አጥር ወደለለው ዩንቨርስቲያቸው ሄጄ ከሩቁ አይቻት ልመለስ ሄድኩ።
ደርሼ አምስት ደቂቃ ያክል እንኳን ሳልቆም ከሩቅ ኤዱን አየኋት !
ግን ብቻዋን አልነበረችም ከልጁ ጋር ነች ውስጤ ሲፈነቃቀል ታወቀኝ እዛው በቆምኩበት
ጩህ ጩህ ስሟን ከፍ አድርገህ ጥራት ጥራት አለኝ••

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍1
አትሮኖስ pinned «​​#ልጩህበት!! ፡ ፡ #ክፍል_አስራ_ዘጠኝ ፡ ፡ #ድርሰት_በጥላሁን ደርሰን እሱ ከፊት እኔ ከጀርባው ተከታትለን እንደገባን "ያቿትና" አለኝ ፊት ለፊት ካንድ ሰው ጋር የተቀመጠች ቆንጂዬ ሴት ተመለከትኩ ። ወደሱ ስዞር አራት ጣቶቹን ከንፈሩ ላይ ጭኖ እንዳፈጠጠባቸው ትንሽ ቆየና "ውይ ውርዴት ! አቤት ቅሌት ! እሄ እኮ ውጪ ሀገር የነበረ ያክስቷ ልጅ ነው የሰርጋችሁን ግማሽ ወጪ እኔ እችላችሃምሀለሁ…»
#ያ_ሞኙ_ወዳጄ

አንገበጀበችኝ ፈጀችኝ ይለኛል ያ...ሞኙ ወዳጄ
የታደለለትን እግዜር የሰጠውን አምኖ ሳይል በጄ
የኔስ አንገብግቢኝ በደንብ ይረር ቆሽቴ
ደጋግመሽ ለብልቢኝ ሳትሰለቺ በሞቴ
እሰት ሆነሽ ኑሪ ሰደዱ የከፋ
እኔን ውሃ አድርጎኝ የብቻዬ አድርጌ
ይዤሽ እንድጠፋ።
#የሸተተ_ሽቶ

ብሩ ይገማል አለኝ ቱጃሩ ወዳጄ
እንኳን ላፍንጫዬ መቼ ተርፎ ከእጄ
እንካ አሽትተው አለኝ ፊቱን አጨፍግጎ
አንዳች የብር ክምር በቃጫ ጠፍንጎ
እየተንቀ ቀጥኩ ተቀበልኩትና
በሸተው........ባሸተው
እንደ እቅፍ አበባ
ከገንዘቡ ቀድሞ ችግሬ ጠነባ።
​​#ልጩህበት!!
:
:
#ክፍል_ሀያ


#ድርሰት_በጥላሁን

በዚህ ሁኔታ ብዙ ታገልኩ ዛሬ ግን አልቻልኩም!
ለሊቱን ሙሉ በህልሜ ሳያት ስላደርኩ ነው መሰለኝ ናፍቆቴ ልኩን አለፈ ባላገኛት እንኳን ወደዛ አጥር ወደሌለው ዩንቨርስቲያቸው ሄጄ ከሩቁ አይቻት ልመለስ ሄድኩ።
ደርሼ አምስት ደቂቃ ያክል እንኳን ሳልቆም ከሩቅ ኤዱን አየኋት !
ግን ብቻዋን አልነበረችም ከልጁ ጋር ነች ውስጤ ሲፈነቃቀል ታወቀኝ እዛው በቆምኩበት
ጩህ ጩህ ስሟን ከፍ አድርገህ ጥራት ጥራት አለኝ••
ግን አልጮሆኩም ዝም ብዬ ፈዝዤ ስመለከታቸው ሁለት የማላውቃቸው ሴቶች መጥተው ተቀላቀሏቸው ወድያው ልጁ ሁለቱን እጃቸውን ጨብጦ ትከሻቸውን በመግጨት ኤዱን ግን ጉንጯን በመሳም ተሰናበታቸውና በርምጃ ከግቢው መውጣት ጀመረ ውስጤ በልጁ እና በኤዱ መካከል የሆነ ነገር እንዳለ እርግጠኛ ሆነ መሰለኝ ፍርሀት ፍርሀት ሲለው ታወቀኝ።
የቆመ ባጃጅ ውስጥ ገብቶ ሲሄድ ተከተልኩት።
ከዚራ አከባቢ ሲደርስ ወርዶ የሆነ ካፍቴርያ ውስጥ ገባ ።
ትንሽ ቆየት አልኩና እዛ ካፍቴሪያ ውስጥ ድንገት እንደተከሰተ ሰው መስዬ ገባሁ ።
ልጁና አንዲት የምታምር ሴት ጎን ለጎን ተቀምጠው ጭማቂ በስትሮ እየማጉ ያወራሉ።
ክው አልኩ እሄ ልጅ ኤዱን እያጃጃላት ባልሆነ እቺ ደሞ ማነች እያልኩ በውስጤ ፈንጠር አልኩና ጀርባዬን ሰጥቻቸው ተቀመጥኩ። ስልኬን አውጥቼ ለኤዱ ደወልኩላት•••
"ወዬ የዘጋከኝ ወንድሜ!" አለች እየሳቀኝ እቺ ልጅ ደግሞ እሄ ወንድሜ እምትለውን ነገር አፏ ላይ ነው እንዴ ያተሙባት እያልኩ ለራሴ የት እንደሆነች ጠየኳት ግቢ ከጓደኛቿ ጋር መሆኗን እንደነገረችኝ
ጓደኛሽ ደና ነው? ስላት ደህና መሆኑን ነግሯት ዛሬ እሚገርም ኳስ አለ ብሏት እኛ ሰፈር ወዳለው ድሬ ዳዋ እስታዲየም ኳስ ሊመለከት መሄዱን አከለችበት"
ተሰናብቻት ስልኩን ዘጋሁትና ። ኳስ ሜዳው ካፌ ኳሷ ደሞ ልጅቷ እንዳትሆን ብቻ አልኩና ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ወደ ልጅ በመሄድ ድንገት እንዳየሁት ሆኜ ሰላምታ ተለዋውጠን ፍቃደኛ ከሆነ አንድ ግዜ ለ አምስት ደቂቃ ላናግረው እንደምፈልግ ስነግረው ፍቃደኛ ቢሆንም ከኤዱ ጋር ምን አይነት ግኑኝነት እንዳላቸው ስጠይቀው
በጣም በሚያስጠላ ሁኔታ ምን አገባህ የሚል ስሜት ባዘለ መልኩ መልስ ሊሰጠኝ ሲሞክር አቋርጬው ቤተሰቦቿ እንዴት ሆነው እንዳስተማሯት ስለነገረችኝ እንዳትሰናከል በማሰብ እንጂ እሱ እንዳለው እንደማያገባኝና ያንንም ጠንቅቄ እንደማውቅ ነግሬው መልስ ሳይሰጠኝ በቆመበት ጥዬው ሄድኩ።
እንዲሁ እንደተወዛገብኩ ቀን ቀኖችን ቀኖች ሳምንትን ሳምንት ወርን ወሮች አመትን እያስከተሉ ነጎዱ እነኤዱም ሁለት አመት ተምረው የመጨረሻውን አንድ አመት መማር ከጀመሩ አንድ ወር ሆናቸው።
ያሁኖቹን ባላውቃቸውም መጀመርያ ላይ ጓደኛቿ ከነበሩት ትግስት ከመሲ ጋር አብሯ ስታብድ ትምህርቷን በአግባቡ ስላልተከታተለች እስከመጨረሻው ላትመለስ ከትምህርት ቤቱ ተባራ እዚሁ ድሬ ዳዋ ልዩ ስሙ ነምበር ዋን በመባል ወደ ሚታወቀው አከባቢ አንድ ሆቴል ውስጥ በአስተናጋጅነት ስትቀጠር ረድኤት ደሞ ለአንድ አመት ተቀጥታ ወደ ቤተሰቦቿ መሄዷን ነግራኛለች ።
ኤዱ ግን ልትመረቅ ወራቶች ብቻ ቀርተዋታል ልትመረቅ መሆኑን ባሰብኩ ቁጥር ጭንቀቴ ይጨምራል ስጨነቅ እንቅልፍ አጣለሁ ከጭንቀቴ ለመደበቅ እንቅልፍ ለመተኛት ስል ማታ ማታ ቋሚ ጠጪ ከሆንኩ ቆየሁ።
ሁሌም የምጠጣው ለመጀመሪያ ግዜ ኤዱን በሩ ላይ ቆማ ያየኋት ጭፈራ ቤት ውስጥ ነው ።
ወደ ውስጥ ከመግባቴ በፊት የቆመችባትን ቦታ ቆም ብዬ አያለሁ ኤዱ ግን የለችም ጠጥቼ ስወጣ ግን ወደዛ ከተመለከትኩ ቆማ ትታየኛለች እራሴንም እሷንም እየተሳደብኩ ወደ ቤት እንደምገባ ብዙ ግዜ ዳኒ ነግሮኛል ዛሬም እዛው እየጠጣሁ ነው።
በግዜ ስለገባሁ ሙዚቃው በስሱ ነው የተከፈተው ነገር ግን ከኔ በሁለት እርምጃ ርቀት እንደኔው ብቻውን የሚጠጣው ሰው ሰላሜን አሳጣኝ በሱ ምክንያት እራሴን ማዳመጥ አልቻልኩም ሰውየው አስተናጋጇን ያለ ምንም ምክንያት ይሰድባታል።
እሱ በሰደባት ቁጥር እኔ እናደዳለሁ።
የማይሆን ጥያቄ ይጠይቃትና መልስ አልሰጥ ስትለው ይሰድባታል •••
"ቆይ እሄ ቂጥሽ ሀይ ኮፒ ነው ኦርጅናል? ንገሪኝ ሀይ ኮፒ ነው ? ሳላረጋግጥ እማ ወይ ፍንክች "
ይላል እሚፈነክት ይፈንክተውና ምን ማረጋገጥ እንደፈለገ ሳስበው ደሞ ሳቄ ይመጣል ።
ትንሽ ቆይቶ ያጨበጭብና ሌላ ይዛለት እንድትመጣ ያዛል። ልክ እንዳመጣችለት ሊነካት እየሞከረ•••
" እንዴ ንገሪኛ እኛ ሀይኮፒም ዩዝድም ባንድ ላይ ጉዳት ነው ንገሪኛ በናትሽ !"
ሲል ልጅቷ ተበሳጭታ መልስ ስለሰጠችው ብድግ አለ ሊመታት ያኔ የኔም ንዴት ገነፈለና ተንደርድሬ በጥፊ ከመሬቱ ጋር አላትሜ አርፎ እንዲጠጣ አስጠነቅቄው ወደ ቦታዬ ተመለስኩ ።
ሰውየው መለፍለፉን አላቆመም ወይ እሱ ወይ እኔ ከዛ ቤት ካልወጣን ዝም እንደማይል ስለገባኝ ተነስቼ ወጣሁና ግማሽ ኪሎ ሜትር አከባቢ በግሬ ተጉዤ " ጨለማው ቤት" በመባል ወደ ሚታወቀው ሆቴል ገባሁ።
ብዙ ግዜ ጥንዶች የሚዝናኑበት ሆቴል ቢሆንም እኔ ብቻዬን ቁጭ ብዬ ስጠጣ ሁለት ቢራ ጨርሼ ሶስተኛውን እንዳገባደድኩ ከፊት ለፊቴ በቅርብ ርቀት ከተቀመጡት ሶስት ሰዎች መካከል ድንገት ቦግ ብሎ በበራው የሞባይል መብራት የመሀለኛዋን እየኋት•••

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍2