#የኔ_ቢጤ
ከሰዎች መካከል ተሸሎክልካ መጥታ
ፊት ለፊቴ ቆማ እጆቿን ዘርግታ
“ስለ እግዚአብሔር!” ብላ
ምፅዋት ጠየቀችኝ ፍፁም በሐዘኔታ፡፡
ብሰጣት ደስ ባለኝ ባይፀድቅ እንኳ ነፍሴ
ነገር ግን እውነቱ
ባዶ ነው ወና ነው ምንም የለም ኪሴ ፤
“እግዜር ይስጥሽ!" አልኳት አዝኜ ለራሴ፡፡
በብርሐን ፍጥነት ከአፊ ተቀብላ
“አብሮ ይስጠን!” ብላ
ሔደች ከአጠገቤ እኔን ለሐሳብ ጥላ፡፡
እጅግ ገረመችኝ!.. እጅግ ደነቀችኝ!
የለኝም አላልኳት እንዴት እንዲ አለችኝ?!?
“ኪሴ ባዶ እንደሆን
በምን አወቀችው?” እያልኩኝ በውስጤ፤
በዓይኔ ተከተልኳት ይችን የኔ ቢጤ፡፡
ሁሉም አጥቶ ነጥቶ
የልመና ባሕል ጨርሶ ሳይውጠን፤
እውነቷን ነው አሜን ፈጣሪ አብሮ ይስጠን፡፡
🔘በፋሲል🔘
ከሰዎች መካከል ተሸሎክልካ መጥታ
ፊት ለፊቴ ቆማ እጆቿን ዘርግታ
“ስለ እግዚአብሔር!” ብላ
ምፅዋት ጠየቀችኝ ፍፁም በሐዘኔታ፡፡
ብሰጣት ደስ ባለኝ ባይፀድቅ እንኳ ነፍሴ
ነገር ግን እውነቱ
ባዶ ነው ወና ነው ምንም የለም ኪሴ ፤
“እግዜር ይስጥሽ!" አልኳት አዝኜ ለራሴ፡፡
በብርሐን ፍጥነት ከአፊ ተቀብላ
“አብሮ ይስጠን!” ብላ
ሔደች ከአጠገቤ እኔን ለሐሳብ ጥላ፡፡
እጅግ ገረመችኝ!.. እጅግ ደነቀችኝ!
የለኝም አላልኳት እንዴት እንዲ አለችኝ?!?
“ኪሴ ባዶ እንደሆን
በምን አወቀችው?” እያልኩኝ በውስጤ፤
በዓይኔ ተከተልኳት ይችን የኔ ቢጤ፡፡
ሁሉም አጥቶ ነጥቶ
የልመና ባሕል ጨርሶ ሳይውጠን፤
እውነቷን ነው አሜን ፈጣሪ አብሮ ይስጠን፡፡
🔘በፋሲል🔘
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...እየተጣደፈች ወጣች
መንገድ ላይ በደስታ ብዛት ፊቷ ላይ ጤነኛ የሆነ ፈገግታ እየታየባት ወደ ማረምያ ቤቱ ከመግባቷ በፊት ከለመደችዉ ምግብ ቤት ምግብ አስቋጥራ
አዲስ ህይወት አዲስ ጅማሬ እንዳገኘ ሰዉ መንፈሷ ብሩህ ሆኖ ስትከንፍ ደርሳ ፍፁምን አስጠርታዉ በሽቦ በታጠረዉ ክልል አሻግራ የፍፁምንን መምጣት መጠባበቅ ጀመረች።
ፍፁም የጀመረዉን የህይወቱን መፅሀፍ እየፃፈ የእሱ መታሰር ከቤዛዊት በአካል እርቋ ተስፋዉ ጨልሞ ፍቅራቸዉ ያሰበዉ ሳይሆን በጅምር ቀርቶ እሱም እሷም በየራሳቸዉ መንገድ ላይ ተራርቀዉ መቅረታቸዉን ፅፎ እስከዛሬ ቀን ያለዉን የህይወቱን ምስቅልቅል ወረቀቱ ላይ ካሰፈረ በኋላ ወደ ፊት የሚፈጠረዉ ስለማይታወቅ የታሪኩን ፍፃሜ ገና እያየ የሚቀጥለዉ ስለሆነ
በተቀመጠበት እየተከዘ የስሙን መጠራት ገና እንደሰማ ተስፈንጥሮ ቆሞ በደስታ ልቡ ጮቤ እየረገጠ እየጨፈረ መራመድ ጀመረ።
ከቤዛዊት ዉጪ ማንም ሊጠይቀዉ እንደማይመጣ ልቡ ስለዋቀዉ ነዉ መደሰቱ
ካስከፋት ቀን ጀምሮ የእሷን መምጣል በጉጉት በልመና ሲጠብቅ ስለነበር
አይኖቿ እየናፈቁት አየተደሰተ ወደ ዘመድ መጠየቅያዉ ስፍራ ደረሰ።
አይን ለአይን በርቀት ሲተያዩ ሁለቱም ፊት ላይ ብልጭ ብሎ የጠፋ ፈገግታ ታየ
አይናቸዉ ሳይነቀል ተጠጋጉ በተወሰነ እርቀት ተጠጋግተዉ አቅራቢያቸዉ ያለች የማረምያ ቤቱ ፖሊስ ቤዛዊት የያዘችዉን ምግብ ለፍፁም ጎርሳ እንድታቀብለዉ በማንክያ ውስጡን ነካ ነካ ካረገች በኋላ ነገረቻት ቤዛዊት መጠነኛ ጉርሻ በአፍዋ እያኘከች
"እንዴት ነህ ፍፄ"
እያለች ምግቡን አቀበለችዉ አፏ ላይ የያዘችዉ ምግብ አላስወራ ስላላት ተረጋግታ አኝካ እዋጠችዉ
ፍፁም በደስታና በፍቅር እያያት ነበር ፊቷ ላይ የማይነበብ ፍፁም ሰላም ይነበብባታል ጤናዋ እንደተስተካከለ ገምቶ በልቡ ተመስጌን እያለ የአፍ አመል ስለሆነ
"ደህና ነኝ አንቺስ እንዴት ነሽ?"
ተነፋፍቀዋል መሀላቸዉ ላይ ግን የሚያስተያይ ነገር ግን የማያገኛኝ አጥር አለ
እስርም እንደዚህ ነዉ
"ልጅ ልወልድልህ ነዉ"
እያለች እጆቿን ወደ ሆዷ ሰዳቸዉ ሆዷን በቀስታ መዳበስ ጀመረች
ፍፁም መልስ ሳይሰጣት አብረዉ ያደሩበትን ቀን አስታወሰ ተሽሎት ከሆስፒታል የወጣቀን
አሰላዉ አንድ ወር ከሳምንት አካባቢ
"እርግጠኛ ነሽ ሀኪም ቤት ሄደሽ ነበር? "
ጠየቃት በማመን እና ባለ ማመን መሀል ባለ ግር የማለት ስሜት ዉስጥ ሆኖ
ቤዛዊት ፊቷን ከላይ ወደ ታች እየነቀነቀች
"አዎ የአንድ ወር ከሰባት ቀን ልጅ ሆዴ ዉስጥ አለ"
ፍፁም ጥርጣሬዉ እነደጉም በኖ ጠፋ በቤዛዊት እና በእሱ አንድ አምሳል እንዳለ ልቡ አሰየነገረዉ ፊቱ በደስታ እየፈካ ጣቶቹን በአጥሩ ላይ እደገፈ ባይነካኩም እሷም በሱ ትይዩ እጆቿን ዘረጋች
"እወድሻለሁ "
ሲል በቀስታ አወራ
"እኔም እወድሃለሁ "
የእሷ ድምፅ ከሱ በጣም ቀንሶ በዉስጡ አብረሀኝ ከጎኔ ብትሆን ልጃችንን አብረን እናሳድግ የሚል አስተያየት አብሮት ነበረ።
💫ይቀጥላል 💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...እየተጣደፈች ወጣች
መንገድ ላይ በደስታ ብዛት ፊቷ ላይ ጤነኛ የሆነ ፈገግታ እየታየባት ወደ ማረምያ ቤቱ ከመግባቷ በፊት ከለመደችዉ ምግብ ቤት ምግብ አስቋጥራ
አዲስ ህይወት አዲስ ጅማሬ እንዳገኘ ሰዉ መንፈሷ ብሩህ ሆኖ ስትከንፍ ደርሳ ፍፁምን አስጠርታዉ በሽቦ በታጠረዉ ክልል አሻግራ የፍፁምንን መምጣት መጠባበቅ ጀመረች።
ፍፁም የጀመረዉን የህይወቱን መፅሀፍ እየፃፈ የእሱ መታሰር ከቤዛዊት በአካል እርቋ ተስፋዉ ጨልሞ ፍቅራቸዉ ያሰበዉ ሳይሆን በጅምር ቀርቶ እሱም እሷም በየራሳቸዉ መንገድ ላይ ተራርቀዉ መቅረታቸዉን ፅፎ እስከዛሬ ቀን ያለዉን የህይወቱን ምስቅልቅል ወረቀቱ ላይ ካሰፈረ በኋላ ወደ ፊት የሚፈጠረዉ ስለማይታወቅ የታሪኩን ፍፃሜ ገና እያየ የሚቀጥለዉ ስለሆነ
በተቀመጠበት እየተከዘ የስሙን መጠራት ገና እንደሰማ ተስፈንጥሮ ቆሞ በደስታ ልቡ ጮቤ እየረገጠ እየጨፈረ መራመድ ጀመረ።
ከቤዛዊት ዉጪ ማንም ሊጠይቀዉ እንደማይመጣ ልቡ ስለዋቀዉ ነዉ መደሰቱ
ካስከፋት ቀን ጀምሮ የእሷን መምጣል በጉጉት በልመና ሲጠብቅ ስለነበር
አይኖቿ እየናፈቁት አየተደሰተ ወደ ዘመድ መጠየቅያዉ ስፍራ ደረሰ።
አይን ለአይን በርቀት ሲተያዩ ሁለቱም ፊት ላይ ብልጭ ብሎ የጠፋ ፈገግታ ታየ
አይናቸዉ ሳይነቀል ተጠጋጉ በተወሰነ እርቀት ተጠጋግተዉ አቅራቢያቸዉ ያለች የማረምያ ቤቱ ፖሊስ ቤዛዊት የያዘችዉን ምግብ ለፍፁም ጎርሳ እንድታቀብለዉ በማንክያ ውስጡን ነካ ነካ ካረገች በኋላ ነገረቻት ቤዛዊት መጠነኛ ጉርሻ በአፍዋ እያኘከች
"እንዴት ነህ ፍፄ"
እያለች ምግቡን አቀበለችዉ አፏ ላይ የያዘችዉ ምግብ አላስወራ ስላላት ተረጋግታ አኝካ እዋጠችዉ
ፍፁም በደስታና በፍቅር እያያት ነበር ፊቷ ላይ የማይነበብ ፍፁም ሰላም ይነበብባታል ጤናዋ እንደተስተካከለ ገምቶ በልቡ ተመስጌን እያለ የአፍ አመል ስለሆነ
"ደህና ነኝ አንቺስ እንዴት ነሽ?"
ተነፋፍቀዋል መሀላቸዉ ላይ ግን የሚያስተያይ ነገር ግን የማያገኛኝ አጥር አለ
እስርም እንደዚህ ነዉ
"ልጅ ልወልድልህ ነዉ"
እያለች እጆቿን ወደ ሆዷ ሰዳቸዉ ሆዷን በቀስታ መዳበስ ጀመረች
ፍፁም መልስ ሳይሰጣት አብረዉ ያደሩበትን ቀን አስታወሰ ተሽሎት ከሆስፒታል የወጣቀን
አሰላዉ አንድ ወር ከሳምንት አካባቢ
"እርግጠኛ ነሽ ሀኪም ቤት ሄደሽ ነበር? "
ጠየቃት በማመን እና ባለ ማመን መሀል ባለ ግር የማለት ስሜት ዉስጥ ሆኖ
ቤዛዊት ፊቷን ከላይ ወደ ታች እየነቀነቀች
"አዎ የአንድ ወር ከሰባት ቀን ልጅ ሆዴ ዉስጥ አለ"
ፍፁም ጥርጣሬዉ እነደጉም በኖ ጠፋ በቤዛዊት እና በእሱ አንድ አምሳል እንዳለ ልቡ አሰየነገረዉ ፊቱ በደስታ እየፈካ ጣቶቹን በአጥሩ ላይ እደገፈ ባይነካኩም እሷም በሱ ትይዩ እጆቿን ዘረጋች
"እወድሻለሁ "
ሲል በቀስታ አወራ
"እኔም እወድሃለሁ "
የእሷ ድምፅ ከሱ በጣም ቀንሶ በዉስጡ አብረሀኝ ከጎኔ ብትሆን ልጃችንን አብረን እናሳድግ የሚል አስተያየት አብሮት ነበረ።
💫ይቀጥላል 💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍1
#ሮሜዎና_ዡልዬት
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሶስት
#በአባ_ሎራ_ቤት ።
አባ ፡ ዮሐንስ ፡ (ከውጭ ፡ መጣ) ።
ወዴት ፡ ነው ፡ ያለኸው ፡ አባቴ ፡ አባ ፡ ሎራ ?
#አባ_ሎራ ።
ተሳሳትኩ ፡ ብዬ ፡ በልቤ ፡ ባልፈራ ፡
በድምፅህ ፡ መሰልከኝ ፡ የኛ ፡ አባ ፡ ዮሐንስ ።
#አባ_ዮሐንስ ።
ዐውቀሃል ፡ እኔ ፡ ነኝ ።
#አባ_ሎራ ።
አንተ ፡ እስክትመለስ ፡
እጠብቅህ ፡ ነበር ፡ ቸኩዬ ፡ ባሳቤ ፡
ፈጥነህ ፡ ደረስክልኝ ፡ ስሥጋ ፡ በልቤ ፡
መልሱን ፡ ከሮሜዎ ፡ ለጻፍኩት ፡ ደብዳቤ አመጣህልኝ ፡ ወይ ?እስቲ ቶሎ ፡ ስጠኝ፤
#አባ_ዮሐንስ ።
የሆንኩትን ፡ ነገር ፡ ልንገርህ ፡ አድምጠኝ
ደብዳቤህን ፡ ቶሎ ፡ ለመስጠት ፡ ወስጄ
አንዱን ፡ የኛ ፡ ካህን ፡ ልፈልገው ፡ ሄጄ ፡
ወደ ፡ ሮሜዎ ቤት፡ እንዲወስድኝ መርቶ :
እሱም ፡ እሺ ፡ ብሎ ፡ ሊወስደኝ ፡ ተነሥቶ
ዘበኞች ፡ መጡና ፡ ከቤት ፡ እንዳንወጣ ፡
ዘግተውብን ፡ ሄዱ፤ ከውጭ ፡ የመጣ ፡
በሽታ ፡ ስላለ ማንም ፡ ከሌላ ፡ አገር፡
ሲመጣ ፡ አስቀድሞ ፡ ለካ ፡ እስቲመረመር
ለብቻው ፡ እንዲሆን ፡ የመጣው ፡ ሥራቱ፡
የሚያስገድድ ፡ ኖሮ ፡ ሳልሄድ ወደ ፡ማንቱ
ሮሜዎን ፡ ሳላገኝ ፡ ሳላየው ፡ ደርሼ
ያንተንም ፡ ደብዳቤ ፡ አመጣሁ ፡ መልሼ
ልልከው ፡ አስቤ ፡ ብሞክር ፡ ብለፋ:
ብጠይቅ ባስጠይቅ የሚላክ ሰው ፡ ጠፋ፡
አልሆንልህ ፡ አለኝ ፡ ነገር ፡ አልሳካ ፤
ይቅርታ ፡ አድሮግልኝ ፡ ደብዳቤህን፡እንካ ። (ሰጠው)
#አባ_ሎራ ።
ምንኛ ፡ መጥፎ ፡ ነው ፡ያመጣኸው ወሬ !
አይ ፡ አባ ፡ ዮሐንስ ፡ ጉድ ሰራኸኝ ፡ ዛሬ ።
መልክቴ ፡ በውነቱ፡ ትልቅ ጕዳይ ፡ ነበር ፤
በጣም ፡ የከበደ ፡ ከፍ ያለ'ቁም ፡ ነገር ፡
ባለመፈጸሙ ፡ የመልክቴ ፡ አደራ ፡
እጅግ ፡ የሚያሳዝን በጣም የሚያስፈራ፡
ነገር ፡ ለማስከተል ፡ ይችላል ፡ ወዳጄ ፤
ጽፌ ፡ የሰጠሁህ ፡ ያ ፡ ወረቀት ፡ በእጄ ፡
ለሮሜዎ ፡ ቶሎ ፡ መድረስ ፡ ነበረበት ፤
አይ ፡አባ ዮሐንስ ጕድ ሠራኸኝ በውነት !
እባክህ ፡ አሁንም ፡ ቶሎ ፡ እንረዳዳ ፤
ጕጠት ፡ ፈልግና ፡ አምጣልኝ ፡ ከጓዳ ።
#አባ_ዮሐንስ ።
ሳልችል ፡ ቀርቼ ፡ ነው ፡ በጣም ፡ ተቸግሬ ፡
ምን ፡ ሁን ፡ ትለኛለህ ፡ ስቀመጥ ፡ ታስሬ ፡
እንዴት ፡ ብዬ ፡ ልሂድ እንደ ፡ ምን ፡ አድርጌ
መልካም ነው ጕጠቱን ላምጣልህ ፡ ፈልጌ
(አባ ፡ ዮሐንስ ፡ ወደ ፡ ጓዳ ፡ ገባ) ።
#አባ_ሎራ ፡ (ብቻውን) ።
ከዡልዬት ፡ መቃብር ፡ ብቻዬን ፡ ገሥግሼ ፡
መዝጊያውን ፡ ልከፍተው ፡ በቶሎ ፡ ደርሼ
መድረስ ፡ ይገባኛል ፡ በቶሎ ፡ በቅጽበት
ጊዜው ፡ ደርሷልና ፡ የምትነሣበት ።
በተነሣች ፡ ጊዜ ፡ ሮሜዎን ፡ ስታጣ ፡
እንደ ፡ ምን ፡ ትረግመኝ ፡ በንዴት ፡ በቍጣ
አምጥቼ ፡ ላስቀምጣት ፡ በቤቴ ፡ ሸሽጌ ፤
ከዚያም ፡ እንደ ፡ ገና ፡ አንድ ፡ሰው ፡ ፈልጌ
ደግሞ ፡ ለሮሜዎ ፡ ሲሆን ፡ ዛሬ ፡ ማታ ፡
ጽፌለት ፡ ይመጣል ፡ ሁሉንም ፡ ሐተታ ።
(ፓሪስ ፡ ካሽከሩ ፡ ጋር ፡ አበባና 'መብራት ፡ ይዞ ፡ ወደ ፡ ዡልዬት ፡መቃብር ፡ መጣ) "
#ፓሪስ ።
መብራቱን አጥፋው እንግዲህ ይበቃል
ሰው የመጣ፡እንደሆን ምናልባት ማን ያውቃል
እዚህ ፡ ሰው ፡ እንዲያየኝ ፡ አልፈልግምና
በል ፡ ቅረብ ፡ተጠጋ ፡ አንተም ወደዚህ ፡ና።
ጀሮህን ፡ አቁመህ ፡ ተጠንቅቀህ ፡ ስማ ፤
ኰሽታ ፡ ስትሰማ ፡ ወይም ፡ የሰው ፡ ጫማ
ምልክት እንዲሆን አፏጭተህ አስታውቀኝ ፡
አስቀድሜ ፡ እንዳውቀው ፡ ፈጥነህ ፡ አስጠንቅቀኝ፤
በል ፡ እንግዲህ ፡ አሁን ፡ አበባውን ፡ ስጠኝ ።
(ፓሪስ ፡ ሄደ) ።
#አሽከር ፡ (ብቻውን) ።
የተሻለ ፡ ስፍራ ፡ ባገኝ ፡ ደግ ፡ ነበር ፤
ይህ ፡ ቦታ ፡ ቀፈፈኝ ፡አልወድም ፡ መቃብር
(እልፍ ፡ ብሎ ፡ ሄደ ) ።
#ፓሪስ ። (በዥልዬት ፡ መቃብር ፡ ላይ) ።
ይህንን ፡ አበባ ፡ መርጨ፡ ፈልጌ ፡
ላቀርብልሽ ፡ መጣሁ ፡ በረከት ፡ አድርጌ
ገጸ ፡ በረከቴ ፡ ጸጸት ፡ ነው ፥ አበባ ፤
ሐዘን ፡ ነው ፡ ለቅሶ ፡ ነው ፡ የመረረ ፡ እንባ
ትተሽኝ ፡ ብትሄጂ ፡ ብቻዬን ፡ ቀርቼ ፡
ልጐበኝሽ ፡ መጣሁ ፡ ሌሊት ፡ ተነሥቼ ።
(አሽከሩ ፡ አፏጨ) ።
እንሆ ፡ አፏጨ ፡ ሰማሁት ፡ አሽከሬ ፤
አሁን የሚመጣ ሰው፡ ነው ወይስ አውሬ ?
ሰላም ፡ የሚነሳኝ ማነው፡ ባሁን ፡ ሰዓት ?
እንዴት ? ደግሞ ፡ ያውም፡ይዟል ፡ በእጁ ፡ መብራት!
እስክረዳው ፡ ድረስ ፡ ምስጢሩን ፡ ዐውቄ ፡
ከለላ፡ፈልጌ፡ልየው ፡ተደብቄ (እልፍ፡ ብሎ ተደበቀ)
(ሮሜዎና ፡ ቤልሻጥር ፡ መብራትና ጉጠት ፡ ይዘው ፡ መጡ) ።
#ሮሜዎ ።
በል መብራቱን ስጠኝ፤ አንተ ግን ተመለስ
እገባለሁ ፡ እኔ ፡ መቃብሯ ፡ ድረስ ፤
አንተ ፡ ከዚህ ፡ ቦታ ፡ እንዳትንቀሳቀስ ፡
ዦሮህን ፡ አቁመህ ፡ ሰው ፡ ሲመጣ ፡ ስማ
ተደብቀህ ፡ ጠብቅ ፡ እዚህ ፡ በጨለማ ።
ያየህ ፡ እንደ ፡ ሆነ ፡ ሰው ወዲህ ሲመጣ፡
ከተደበቅህበት ፡ ቦታ ፡ ሳትወጣ ፡
በፉጨት ፡ ምልክት ፡ እኔን ፡ አስጠንቅቀኝ
ምናልባት ፡ ሰው ደርሶ ድንገት ፡ እንዳያየኝ
የዡልዬት ፡ ሬሳ ፡ ካለበት ፡ ገብቼ ፡
በመቃብሯ ፡ ውስጥ ፡ እሷን ፡ ተመልክቼ ፡
ካየኋት ፡ በኋላ ፡ ከልቤ ፡ አልቅሼ ፡
አንብቼ ፡ ሲያበቃኝ ፡ ሐዘኔን ፡ ጨርሼ ፡
የጣቷን ፡ ቀለበት ፡ አውልቄ ፡ ከሷ ፡ ላይ ፡
ልወስድ ፡አስቤያለሁ ላንድ ብርቱ ጕዳይ
ከወጣሁ ፡ በኋላ ፡ እኔ ፡ ከዚህ ፡ ቦታ ፡
ይህንን ፡ ደብዳቤ ፡ ጨምረህ ፡ ሰላምታ ፡
ላባቴ ፡ ስጥልኝ ፡ ነገር ፡ ግን ፡ ተጠንቀቅ ፤
ምን ፡ ይሠራል ፡ ብለህ፡ አሳቤን ፡ ለማወቅ
መሰለል ፡ አስበህ ፡ ወደ ፡ እኔ ፡ አትጠጋ ፤
ያገኝሃልና ፡ የመሞት፡ አደጋ ፡
በውነቱ ፡ ባገኝህ ፡ ይህንን ፡ ስትሠራ ፡
እጄም ፡ አያዝንልህ ፡ መንፈሴም ፡ አይራራ
ልብ ፡ በል ፥ተጠንቀቅ ለሕይወትህ ፡ ፍራ
#ቤልሻጥር ።
እኔ ፡ ከዚህ ፡ ቦታ ፡ አልንቀሳቀስም !
ስታስጠነቅቀኝ፡ትእዛዝ ፡ አላፈርህም። (ሮሜዎ'ሄደ)።
#ሮሜዎ ፡ (የዡልዩትን መቃብርዋን ' በር
ሊከፍት ፡ ይታገላል) ።
ከጥንት ፡ ጀምረህ ፡ ብትበላ ፡ ብትበላ ፡
ጠገብኩኝ ፡ የማትል ፡ ሆድህ ፡ የማይሞላ
መቃብር ፡የሚሉህ አንተ መጥፎ ከርሣም
ለወጣት ፡ አታዝን ፥ ለቆንዦ ፡ አትሣሣም
ዡልዬትን ፡ ከጥርስህ ፡ ፈልቅቄ ፡ ላወጣ ፡
መጥቻለሁና ፡ የዋጥከውን ፡ አምጣ ፡
አንዴ ፡ ልያትና ፡ እንባዬን ፡ አፍስሼ ፡
እርሜንም ፡ አውጥቼ ፡ ተራዬን ፡ አልቅሼ ፡
ሐዘኔን ፡ ገልጬ ፡ ከበቃኝ ፡ በኋላ ፡
እኔንም ፡ ከሷ ፡ ጋር ፡ አብረህ ፡ እንድትበላ
#ፓሪስ ።
መብራት ፡ በጁ ፡ ይዞ ፡ የመጣው ፡ ከደጅ
ሮሜዎ ፡ ይመስላል ፡ ያ የሞንታግ ፡ ልጅ፡
ጐበዙን ፡ ቲባልትን ፡ የዡልዬትን ፡ ዘመድ ፡
አሁን ፡ በቅርብ ፡ቀን ተጣልቶት ፡ በመንገድ
ገድሎ ፡ ተፈርዶበት ፡ ተሰዶ ፡ የወጣ ፡
አሁን ፡ ደግሞ ፡ እዚህ ፡ ምን ፡ ሊፈጥር፡ መጣ?
💫ይቀጥላል💫
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሶስት
#በአባ_ሎራ_ቤት ።
አባ ፡ ዮሐንስ ፡ (ከውጭ ፡ መጣ) ።
ወዴት ፡ ነው ፡ ያለኸው ፡ አባቴ ፡ አባ ፡ ሎራ ?
#አባ_ሎራ ።
ተሳሳትኩ ፡ ብዬ ፡ በልቤ ፡ ባልፈራ ፡
በድምፅህ ፡ መሰልከኝ ፡ የኛ ፡ አባ ፡ ዮሐንስ ።
#አባ_ዮሐንስ ።
ዐውቀሃል ፡ እኔ ፡ ነኝ ።
#አባ_ሎራ ።
አንተ ፡ እስክትመለስ ፡
እጠብቅህ ፡ ነበር ፡ ቸኩዬ ፡ ባሳቤ ፡
ፈጥነህ ፡ ደረስክልኝ ፡ ስሥጋ ፡ በልቤ ፡
መልሱን ፡ ከሮሜዎ ፡ ለጻፍኩት ፡ ደብዳቤ አመጣህልኝ ፡ ወይ ?እስቲ ቶሎ ፡ ስጠኝ፤
#አባ_ዮሐንስ ።
የሆንኩትን ፡ ነገር ፡ ልንገርህ ፡ አድምጠኝ
ደብዳቤህን ፡ ቶሎ ፡ ለመስጠት ፡ ወስጄ
አንዱን ፡ የኛ ፡ ካህን ፡ ልፈልገው ፡ ሄጄ ፡
ወደ ፡ ሮሜዎ ቤት፡ እንዲወስድኝ መርቶ :
እሱም ፡ እሺ ፡ ብሎ ፡ ሊወስደኝ ፡ ተነሥቶ
ዘበኞች ፡ መጡና ፡ ከቤት ፡ እንዳንወጣ ፡
ዘግተውብን ፡ ሄዱ፤ ከውጭ ፡ የመጣ ፡
በሽታ ፡ ስላለ ማንም ፡ ከሌላ ፡ አገር፡
ሲመጣ ፡ አስቀድሞ ፡ ለካ ፡ እስቲመረመር
ለብቻው ፡ እንዲሆን ፡ የመጣው ፡ ሥራቱ፡
የሚያስገድድ ፡ ኖሮ ፡ ሳልሄድ ወደ ፡ማንቱ
ሮሜዎን ፡ ሳላገኝ ፡ ሳላየው ፡ ደርሼ
ያንተንም ፡ ደብዳቤ ፡ አመጣሁ ፡ መልሼ
ልልከው ፡ አስቤ ፡ ብሞክር ፡ ብለፋ:
ብጠይቅ ባስጠይቅ የሚላክ ሰው ፡ ጠፋ፡
አልሆንልህ ፡ አለኝ ፡ ነገር ፡ አልሳካ ፤
ይቅርታ ፡ አድሮግልኝ ፡ ደብዳቤህን፡እንካ ። (ሰጠው)
#አባ_ሎራ ።
ምንኛ ፡ መጥፎ ፡ ነው ፡ያመጣኸው ወሬ !
አይ ፡ አባ ፡ ዮሐንስ ፡ ጉድ ሰራኸኝ ፡ ዛሬ ።
መልክቴ ፡ በውነቱ፡ ትልቅ ጕዳይ ፡ ነበር ፤
በጣም ፡ የከበደ ፡ ከፍ ያለ'ቁም ፡ ነገር ፡
ባለመፈጸሙ ፡ የመልክቴ ፡ አደራ ፡
እጅግ ፡ የሚያሳዝን በጣም የሚያስፈራ፡
ነገር ፡ ለማስከተል ፡ ይችላል ፡ ወዳጄ ፤
ጽፌ ፡ የሰጠሁህ ፡ ያ ፡ ወረቀት ፡ በእጄ ፡
ለሮሜዎ ፡ ቶሎ ፡ መድረስ ፡ ነበረበት ፤
አይ ፡አባ ዮሐንስ ጕድ ሠራኸኝ በውነት !
እባክህ ፡ አሁንም ፡ ቶሎ ፡ እንረዳዳ ፤
ጕጠት ፡ ፈልግና ፡ አምጣልኝ ፡ ከጓዳ ።
#አባ_ዮሐንስ ።
ሳልችል ፡ ቀርቼ ፡ ነው ፡ በጣም ፡ ተቸግሬ ፡
ምን ፡ ሁን ፡ ትለኛለህ ፡ ስቀመጥ ፡ ታስሬ ፡
እንዴት ፡ ብዬ ፡ ልሂድ እንደ ፡ ምን ፡ አድርጌ
መልካም ነው ጕጠቱን ላምጣልህ ፡ ፈልጌ
(አባ ፡ ዮሐንስ ፡ ወደ ፡ ጓዳ ፡ ገባ) ።
#አባ_ሎራ ፡ (ብቻውን) ።
ከዡልዬት ፡ መቃብር ፡ ብቻዬን ፡ ገሥግሼ ፡
መዝጊያውን ፡ ልከፍተው ፡ በቶሎ ፡ ደርሼ
መድረስ ፡ ይገባኛል ፡ በቶሎ ፡ በቅጽበት
ጊዜው ፡ ደርሷልና ፡ የምትነሣበት ።
በተነሣች ፡ ጊዜ ፡ ሮሜዎን ፡ ስታጣ ፡
እንደ ፡ ምን ፡ ትረግመኝ ፡ በንዴት ፡ በቍጣ
አምጥቼ ፡ ላስቀምጣት ፡ በቤቴ ፡ ሸሽጌ ፤
ከዚያም ፡ እንደ ፡ ገና ፡ አንድ ፡ሰው ፡ ፈልጌ
ደግሞ ፡ ለሮሜዎ ፡ ሲሆን ፡ ዛሬ ፡ ማታ ፡
ጽፌለት ፡ ይመጣል ፡ ሁሉንም ፡ ሐተታ ።
(ፓሪስ ፡ ካሽከሩ ፡ ጋር ፡ አበባና 'መብራት ፡ ይዞ ፡ ወደ ፡ ዡልዬት ፡መቃብር ፡ መጣ) "
#ፓሪስ ።
መብራቱን አጥፋው እንግዲህ ይበቃል
ሰው የመጣ፡እንደሆን ምናልባት ማን ያውቃል
እዚህ ፡ ሰው ፡ እንዲያየኝ ፡ አልፈልግምና
በል ፡ ቅረብ ፡ተጠጋ ፡ አንተም ወደዚህ ፡ና።
ጀሮህን ፡ አቁመህ ፡ ተጠንቅቀህ ፡ ስማ ፤
ኰሽታ ፡ ስትሰማ ፡ ወይም ፡ የሰው ፡ ጫማ
ምልክት እንዲሆን አፏጭተህ አስታውቀኝ ፡
አስቀድሜ ፡ እንዳውቀው ፡ ፈጥነህ ፡ አስጠንቅቀኝ፤
በል ፡ እንግዲህ ፡ አሁን ፡ አበባውን ፡ ስጠኝ ።
(ፓሪስ ፡ ሄደ) ።
#አሽከር ፡ (ብቻውን) ።
የተሻለ ፡ ስፍራ ፡ ባገኝ ፡ ደግ ፡ ነበር ፤
ይህ ፡ ቦታ ፡ ቀፈፈኝ ፡አልወድም ፡ መቃብር
(እልፍ ፡ ብሎ ፡ ሄደ ) ።
#ፓሪስ ። (በዥልዬት ፡ መቃብር ፡ ላይ) ።
ይህንን ፡ አበባ ፡ መርጨ፡ ፈልጌ ፡
ላቀርብልሽ ፡ መጣሁ ፡ በረከት ፡ አድርጌ
ገጸ ፡ በረከቴ ፡ ጸጸት ፡ ነው ፥ አበባ ፤
ሐዘን ፡ ነው ፡ ለቅሶ ፡ ነው ፡ የመረረ ፡ እንባ
ትተሽኝ ፡ ብትሄጂ ፡ ብቻዬን ፡ ቀርቼ ፡
ልጐበኝሽ ፡ መጣሁ ፡ ሌሊት ፡ ተነሥቼ ።
(አሽከሩ ፡ አፏጨ) ።
እንሆ ፡ አፏጨ ፡ ሰማሁት ፡ አሽከሬ ፤
አሁን የሚመጣ ሰው፡ ነው ወይስ አውሬ ?
ሰላም ፡ የሚነሳኝ ማነው፡ ባሁን ፡ ሰዓት ?
እንዴት ? ደግሞ ፡ ያውም፡ይዟል ፡ በእጁ ፡ መብራት!
እስክረዳው ፡ ድረስ ፡ ምስጢሩን ፡ ዐውቄ ፡
ከለላ፡ፈልጌ፡ልየው ፡ተደብቄ (እልፍ፡ ብሎ ተደበቀ)
(ሮሜዎና ፡ ቤልሻጥር ፡ መብራትና ጉጠት ፡ ይዘው ፡ መጡ) ።
#ሮሜዎ ።
በል መብራቱን ስጠኝ፤ አንተ ግን ተመለስ
እገባለሁ ፡ እኔ ፡ መቃብሯ ፡ ድረስ ፤
አንተ ፡ ከዚህ ፡ ቦታ ፡ እንዳትንቀሳቀስ ፡
ዦሮህን ፡ አቁመህ ፡ ሰው ፡ ሲመጣ ፡ ስማ
ተደብቀህ ፡ ጠብቅ ፡ እዚህ ፡ በጨለማ ።
ያየህ ፡ እንደ ፡ ሆነ ፡ ሰው ወዲህ ሲመጣ፡
ከተደበቅህበት ፡ ቦታ ፡ ሳትወጣ ፡
በፉጨት ፡ ምልክት ፡ እኔን ፡ አስጠንቅቀኝ
ምናልባት ፡ ሰው ደርሶ ድንገት ፡ እንዳያየኝ
የዡልዬት ፡ ሬሳ ፡ ካለበት ፡ ገብቼ ፡
በመቃብሯ ፡ ውስጥ ፡ እሷን ፡ ተመልክቼ ፡
ካየኋት ፡ በኋላ ፡ ከልቤ ፡ አልቅሼ ፡
አንብቼ ፡ ሲያበቃኝ ፡ ሐዘኔን ፡ ጨርሼ ፡
የጣቷን ፡ ቀለበት ፡ አውልቄ ፡ ከሷ ፡ ላይ ፡
ልወስድ ፡አስቤያለሁ ላንድ ብርቱ ጕዳይ
ከወጣሁ ፡ በኋላ ፡ እኔ ፡ ከዚህ ፡ ቦታ ፡
ይህንን ፡ ደብዳቤ ፡ ጨምረህ ፡ ሰላምታ ፡
ላባቴ ፡ ስጥልኝ ፡ ነገር ፡ ግን ፡ ተጠንቀቅ ፤
ምን ፡ ይሠራል ፡ ብለህ፡ አሳቤን ፡ ለማወቅ
መሰለል ፡ አስበህ ፡ ወደ ፡ እኔ ፡ አትጠጋ ፤
ያገኝሃልና ፡ የመሞት፡ አደጋ ፡
በውነቱ ፡ ባገኝህ ፡ ይህንን ፡ ስትሠራ ፡
እጄም ፡ አያዝንልህ ፡ መንፈሴም ፡ አይራራ
ልብ ፡ በል ፥ተጠንቀቅ ለሕይወትህ ፡ ፍራ
#ቤልሻጥር ።
እኔ ፡ ከዚህ ፡ ቦታ ፡ አልንቀሳቀስም !
ስታስጠነቅቀኝ፡ትእዛዝ ፡ አላፈርህም። (ሮሜዎ'ሄደ)።
#ሮሜዎ ፡ (የዡልዩትን መቃብርዋን ' በር
ሊከፍት ፡ ይታገላል) ።
ከጥንት ፡ ጀምረህ ፡ ብትበላ ፡ ብትበላ ፡
ጠገብኩኝ ፡ የማትል ፡ ሆድህ ፡ የማይሞላ
መቃብር ፡የሚሉህ አንተ መጥፎ ከርሣም
ለወጣት ፡ አታዝን ፥ ለቆንዦ ፡ አትሣሣም
ዡልዬትን ፡ ከጥርስህ ፡ ፈልቅቄ ፡ ላወጣ ፡
መጥቻለሁና ፡ የዋጥከውን ፡ አምጣ ፡
አንዴ ፡ ልያትና ፡ እንባዬን ፡ አፍስሼ ፡
እርሜንም ፡ አውጥቼ ፡ ተራዬን ፡ አልቅሼ ፡
ሐዘኔን ፡ ገልጬ ፡ ከበቃኝ ፡ በኋላ ፡
እኔንም ፡ ከሷ ፡ ጋር ፡ አብረህ ፡ እንድትበላ
#ፓሪስ ።
መብራት ፡ በጁ ፡ ይዞ ፡ የመጣው ፡ ከደጅ
ሮሜዎ ፡ ይመስላል ፡ ያ የሞንታግ ፡ ልጅ፡
ጐበዙን ፡ ቲባልትን ፡ የዡልዬትን ፡ ዘመድ ፡
አሁን ፡ በቅርብ ፡ቀን ተጣልቶት ፡ በመንገድ
ገድሎ ፡ ተፈርዶበት ፡ ተሰዶ ፡ የወጣ ፡
አሁን ፡ ደግሞ ፡ እዚህ ፡ ምን ፡ ሊፈጥር፡ መጣ?
💫ይቀጥላል💫
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...አብረን እናሳድግ በሚል አስተያየት
ቤዛዊት እና ፍፁም ለደቂቃዎች ቃላት ሳያወጡ ማሃላቸዉ ባለዉ ሽቦ በአይኖቻቸው እየተያዩ ነገር ግን ሁለቱም ልቦቻቸዉ ተጨንቀዉ ሀዘን የተበረዘበት ፍንጣቂ ደስታን ተሸክመዉ በአይኖቻቸዉ ፍቅርን አብሮ መሆንን ተርበዉ ጥቂት ከተያዩ በኋላ
"ልጃችንን ወልጄ በፍቅር አሳድገዋለሁ"
ቤዛዊት ይሄን ስታወራ የእንባ ሳግ አፍዋ ዉስጥ እንቅ እያረጋት ለማልቀስ እያኮበኮበች ነበር
ፍፁም ከእስር የመፈቻ ጊዜዉ በጣም እሩቅ ስለሆነ ያለእሱ የምታሳለፍቻዉ አመታት እየታያት
በተለይ ያ ጠይም መጀመርያ የትምህርት ቤቱ በር ላይ አይታዉ ደስ ብሏት ሰአት የጠየቀችዉ
ነገሮችን ያስተማራት የመከራት ህመሟን ችሎ እያስታመማት ስታጠፋ ስትበድለዉ ከጎኗ ያልራቃት ሁሉ ነገሯ የሆነዉ ፍፁም በእሷ ህይወት በተያያዘ ጉዳይ በድንገተኛ ፀብ የሰዉ ነብስ አጥፍቶ ለእስር ተዳርጎ ፊት ለፊቷ ቆሞ ስታየዉ ልጅ ከእሱ ማርገዟን የደስታ ዜና ይዛ እንኳን ደስታዋ ሙሉ ሊሆን አልቻለላትም
የሆነ የጎደለ ነገር እንዳለ ልቦናዋ ያዉቀዋል የጎደለዉ
ፊት ለፊቷ የቆመዉ የቀድሞዉ አስተማሪ ፍፁም ደምሴ ነበር።
"የምታለቅሺ ከሆነ እቀየምሻለሁ"
ፍፁም ቆጣ ሲልባት ማልቀሷን ተወችዉ
ከቤዛዊት ጋር እንደተለያየ ፍፁም ልጁን መዉለዷ መልካም ነዉ ወይ ሲል እራሱን ጠየቀ
ባትወልደዉ እና ወደ ፊት ሌላ ጥሩ አሳቢ መልካም ባል አግብታ ከእሱ ብትወልድ እያለ አስቦ ነበር ቤዛዊት ወልጄ በፍቅር አሳድገዋለሁ ያለችውን ሲያስታዉስ ሀሳቡን በምንም ተአምር እንደማትቀበለዉ ሲገባዉ ያሻዋን ታርግ ሲል ማሰቡን እርግፍ አርጎ ተወዉ።
መታሰር ከማሰብ ባያግድም ከተግባር ግን ስለሚያግድ ከጎኗ ሆኖ ምንም ሊያረግላት ስለማይችል ለመምከር ይሞክራል እንጂ እሷ የፈቀደችዉን ሁሉ እንድታረግ ከልቡ ፈቅዶላት ነበር
ቤዛዊት ፍፁምን ጠይቃዉ እየተመለሰች መንገድ ላይ ለፍፁም የነገረችዉን የምስራች ለቤተሰቦቿም መናገር እንዳለባት ገምታ የሚሰጡዋትን መልስ ለመስማት ጉዋጉታ ወደ ቤቷ አመረች ።
ቤት ዉስጥ ሁሉም ተሰብስበዉ ምግብ ቀርቦ ከተመገቡ በኋላ ማእዱ ተነስቶ ቡና ለመጠጣት አየጠበቁ ቤዛዊት
"የምነግራችሁ ትልቅ ጉዳይ አለ"
የሁሉም ሰዉ ጆሮ እና ቀልብ እሷ ላይ አረፈ።
ቤዛዊት በሽታዋ የተነሳባት አሁን ደሞ ምን ልትለን ይሆን እያሉ ነበር ቤተሰቦቿ
ቤዛዊት ወሬዉን ከመጀመሯ በፊት ኮስታራዉን አባቷን በቀስታ አይታቸዉ
"ይሄን የምነግራችሁ እናንተ የኔ የምወዳችሁ ቤተሰቦቼ ስለሆናችሁ ስለማከብራችሁም ነዉ
ነገር ግን የራሴን ዉሳኔ እንድትጋፉኝ አልፈልግም.."
ትንፋሽ ለመሳብ ንግግሯን ገታ አረገች
እናት እና አባቷ እየተያዩ ነበር ቀጥላ የምትለዉ ለመስማት ወደ ዋና ሀሳቧ እንድትገባ አስበዉ ምን ልትላቸዉ እንደ ሆነ ለመገመት እንኳን ስላልቻሉ ታላቅ እህቷ ከተቀመጠችበት ተነስታ ከቤዛዊት አጠገብ ቆማ እህቷን እያቀፈቻት
"ምን ለመናገር ፈልገሽ ነዉ ምንም ይሁን ግን እኔ ሁሌም ከጎንሽ አለሁ"
ድጋፏን አቅፋ ገለፀችላት
ቤዛዊት ካቆመችበት አንገቷን ወደ መሬት አቀርቅራ
"እኔና ፍፁም ልጅ ልንወልድ ነዉ"
ይህንን እንዳለች አባቷ ከተቀመጡበት ተነስተዉ ቆመዉ
"እየቀለድሽ መሆን አለበት ከነብሰ ገዳይ አርግዣለሁ እያልሽን ባልሆነ"
የፌዝ ሳቅ እየሳቁ
ቤዛዊት ካቀረቀረችበት አንገቷን ቀና እያረገች አባቷን እያየቻቸዉ
"አባ አብጄ ታምሜ እኔን ማየት ካልወደድክ የኔን ተስፋ የኔን ፍላጓትን ለማሙዋላት ምን
የሚይዝህ ነገር አለ ነዉ የኔ ሀዘን እንጂ ደስታዬ ትርጉም አይሰጥህም"
ቤዛዊት አባቷን እንዴት ታስረዳቸዉ በምንም ሊረዷት አይችሉም በቆመችበት ልብሶቿን እያወላለቀች
"ይሄ ከሆነ የሚያስደስትህ ኡ ኡ እያልኩ ከዚህ ቤት አወጣለሁ"
ቤዛዊት ሆን ብላ የአባቷን ልብ ለማየት ነበር ይሄንን ማረግ የጀመረችዉ ያሰበችዉም ተሳካላት አባቷ ልብስ እያወላለቀች ሲያይዋት ተጠግተዉ ያወለቀችዉን ልብስ እንድትለብስ እየረዷት
"ያንቺን ደስታ እነጂ ሀዘንሽን መቼም አስቤ አላዉቅም"
ሲሏት ቤዛዊት የጀመሩትን ወሬ ሳታስጨርስ አቀፈቻቸዉ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...አብረን እናሳድግ በሚል አስተያየት
ቤዛዊት እና ፍፁም ለደቂቃዎች ቃላት ሳያወጡ ማሃላቸዉ ባለዉ ሽቦ በአይኖቻቸው እየተያዩ ነገር ግን ሁለቱም ልቦቻቸዉ ተጨንቀዉ ሀዘን የተበረዘበት ፍንጣቂ ደስታን ተሸክመዉ በአይኖቻቸዉ ፍቅርን አብሮ መሆንን ተርበዉ ጥቂት ከተያዩ በኋላ
"ልጃችንን ወልጄ በፍቅር አሳድገዋለሁ"
ቤዛዊት ይሄን ስታወራ የእንባ ሳግ አፍዋ ዉስጥ እንቅ እያረጋት ለማልቀስ እያኮበኮበች ነበር
ፍፁም ከእስር የመፈቻ ጊዜዉ በጣም እሩቅ ስለሆነ ያለእሱ የምታሳለፍቻዉ አመታት እየታያት
በተለይ ያ ጠይም መጀመርያ የትምህርት ቤቱ በር ላይ አይታዉ ደስ ብሏት ሰአት የጠየቀችዉ
ነገሮችን ያስተማራት የመከራት ህመሟን ችሎ እያስታመማት ስታጠፋ ስትበድለዉ ከጎኗ ያልራቃት ሁሉ ነገሯ የሆነዉ ፍፁም በእሷ ህይወት በተያያዘ ጉዳይ በድንገተኛ ፀብ የሰዉ ነብስ አጥፍቶ ለእስር ተዳርጎ ፊት ለፊቷ ቆሞ ስታየዉ ልጅ ከእሱ ማርገዟን የደስታ ዜና ይዛ እንኳን ደስታዋ ሙሉ ሊሆን አልቻለላትም
የሆነ የጎደለ ነገር እንዳለ ልቦናዋ ያዉቀዋል የጎደለዉ
ፊት ለፊቷ የቆመዉ የቀድሞዉ አስተማሪ ፍፁም ደምሴ ነበር።
"የምታለቅሺ ከሆነ እቀየምሻለሁ"
ፍፁም ቆጣ ሲልባት ማልቀሷን ተወችዉ
ከቤዛዊት ጋር እንደተለያየ ፍፁም ልጁን መዉለዷ መልካም ነዉ ወይ ሲል እራሱን ጠየቀ
ባትወልደዉ እና ወደ ፊት ሌላ ጥሩ አሳቢ መልካም ባል አግብታ ከእሱ ብትወልድ እያለ አስቦ ነበር ቤዛዊት ወልጄ በፍቅር አሳድገዋለሁ ያለችውን ሲያስታዉስ ሀሳቡን በምንም ተአምር እንደማትቀበለዉ ሲገባዉ ያሻዋን ታርግ ሲል ማሰቡን እርግፍ አርጎ ተወዉ።
መታሰር ከማሰብ ባያግድም ከተግባር ግን ስለሚያግድ ከጎኗ ሆኖ ምንም ሊያረግላት ስለማይችል ለመምከር ይሞክራል እንጂ እሷ የፈቀደችዉን ሁሉ እንድታረግ ከልቡ ፈቅዶላት ነበር
ቤዛዊት ፍፁምን ጠይቃዉ እየተመለሰች መንገድ ላይ ለፍፁም የነገረችዉን የምስራች ለቤተሰቦቿም መናገር እንዳለባት ገምታ የሚሰጡዋትን መልስ ለመስማት ጉዋጉታ ወደ ቤቷ አመረች ።
ቤት ዉስጥ ሁሉም ተሰብስበዉ ምግብ ቀርቦ ከተመገቡ በኋላ ማእዱ ተነስቶ ቡና ለመጠጣት አየጠበቁ ቤዛዊት
"የምነግራችሁ ትልቅ ጉዳይ አለ"
የሁሉም ሰዉ ጆሮ እና ቀልብ እሷ ላይ አረፈ።
ቤዛዊት በሽታዋ የተነሳባት አሁን ደሞ ምን ልትለን ይሆን እያሉ ነበር ቤተሰቦቿ
ቤዛዊት ወሬዉን ከመጀመሯ በፊት ኮስታራዉን አባቷን በቀስታ አይታቸዉ
"ይሄን የምነግራችሁ እናንተ የኔ የምወዳችሁ ቤተሰቦቼ ስለሆናችሁ ስለማከብራችሁም ነዉ
ነገር ግን የራሴን ዉሳኔ እንድትጋፉኝ አልፈልግም.."
ትንፋሽ ለመሳብ ንግግሯን ገታ አረገች
እናት እና አባቷ እየተያዩ ነበር ቀጥላ የምትለዉ ለመስማት ወደ ዋና ሀሳቧ እንድትገባ አስበዉ ምን ልትላቸዉ እንደ ሆነ ለመገመት እንኳን ስላልቻሉ ታላቅ እህቷ ከተቀመጠችበት ተነስታ ከቤዛዊት አጠገብ ቆማ እህቷን እያቀፈቻት
"ምን ለመናገር ፈልገሽ ነዉ ምንም ይሁን ግን እኔ ሁሌም ከጎንሽ አለሁ"
ድጋፏን አቅፋ ገለፀችላት
ቤዛዊት ካቆመችበት አንገቷን ወደ መሬት አቀርቅራ
"እኔና ፍፁም ልጅ ልንወልድ ነዉ"
ይህንን እንዳለች አባቷ ከተቀመጡበት ተነስተዉ ቆመዉ
"እየቀለድሽ መሆን አለበት ከነብሰ ገዳይ አርግዣለሁ እያልሽን ባልሆነ"
የፌዝ ሳቅ እየሳቁ
ቤዛዊት ካቀረቀረችበት አንገቷን ቀና እያረገች አባቷን እያየቻቸዉ
"አባ አብጄ ታምሜ እኔን ማየት ካልወደድክ የኔን ተስፋ የኔን ፍላጓትን ለማሙዋላት ምን
የሚይዝህ ነገር አለ ነዉ የኔ ሀዘን እንጂ ደስታዬ ትርጉም አይሰጥህም"
ቤዛዊት አባቷን እንዴት ታስረዳቸዉ በምንም ሊረዷት አይችሉም በቆመችበት ልብሶቿን እያወላለቀች
"ይሄ ከሆነ የሚያስደስትህ ኡ ኡ እያልኩ ከዚህ ቤት አወጣለሁ"
ቤዛዊት ሆን ብላ የአባቷን ልብ ለማየት ነበር ይሄንን ማረግ የጀመረችዉ ያሰበችዉም ተሳካላት አባቷ ልብስ እያወላለቀች ሲያይዋት ተጠግተዉ ያወለቀችዉን ልብስ እንድትለብስ እየረዷት
"ያንቺን ደስታ እነጂ ሀዘንሽን መቼም አስቤ አላዉቅም"
ሲሏት ቤዛዊት የጀመሩትን ወሬ ሳታስጨርስ አቀፈቻቸዉ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
❤1
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስድስት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...አቀፈቻቸዉ
እናቷ መቼም ቢሆን የእሷን ፍላጎት ተጋፍተዉ ባያዉቁም ትምህርትን ሳትመረቅ ልጅ ለመዉለድ በመቸኮሏ ቅር ቢሰኙም አጣሁዋት አይምሮዋ ተቃዉሶ ተቀጨችብኝ ብለዉ ካዘኑበት በርካታ አመታት ጤናዋ ተመልሶ ከፊታቸዉ ቆማ የልጅ ልጅ ላሳያችሁ ነው ማለቷ ለእሳቸዉ አለም ነበር
የሚያስጨንቃቸዉ ሁሌ የልጃቸዉ ጤንነት ብቻ ስለነበር።
ትምህርት ስራ ገንዘብ ሀብት ....የህይወት መስመሮች ዉስጥ ያሉ መንገዶች ሊሆኑ ይችላሉ
ዋናዉ የህይወት ዋስትናችን ግን ጤንነታችን ላይ የተመረኮዘ ነዉ።
የቤዛዊት ሆድ ከቀን ወደ ቀን እየገፋ ፍፁም ጋር በየሳምንቱ ሳትቀር የሚያስፈልገዉን ይዛ እየጠየቀችዉ የመዉለጃዋ ስዓት ሲቃረብ የህመም ስሜትም ጀመራት።
በበፊቱ የአይምሮ ህመሟ ወቅት እሷ ሳይታወቃት ስትወድቅ ስትነሳ ሰዉነቷ ልጁን ለመቋቋም አልቻለም ነበር
ሆድዋ አካባቢ ቀላል የህመም ስሜትን እየተሰማት መራመድም እያቃታት ፍፁምን መጠየቅ እየፈለገች ነገር ግን ከአቅሟ በላይ ስለሆነ ቤት ዉስጥ እራሱ ጉድ ጉድ ማለቱ ሲያቅታት ቤተሰቧቿ ወደ ሆስፒታል ወሰዷት።
የሆስፒታሉ አልጋ ላይ ሆና ቤዛዊት እህቷን
"ወረቀት እና እስኪርቢቶ አቀብይኝ"
አለቻት
"ምን ልትፅፊ ነው ደሞ"
እያለች እስኪርቢቶ ከቦርሳዋ አዉጥታ ወረቀት ስላጣች
"ወረቀት ግን የለኝም ቤዚ"
ቤዛዊት ፊት ላይ እርግዝናዉ ይሆን ባልታወቀ ሁኔታ ተለዋዉጣለች ጉንጮቿ ቀልተዋል የአይኖቿ
ቆቦች ወፍረዉ አይኗን መግለጥ ያቃታት ነዉ የምትመስለዉ
"ለፍፁም የምፅፍለት ነገር ነበር ተይዉ በቃ ልጄን ወልጄ አንድ ላይ ከልጄ ጋር ስንሄድ እነግረዋለሁ"
አለችና በትግል ለመሳቅ እየሞከረች
"የልጄን ስም ዳግማዊት ፍፁም ብላትስ"
እህቷን እየጠየቀቻት የእንሽርት ዉሀዋ ፈሰሰ።
የማዋለጃ ክፍል ዉስጥ ሀኪሞቹ ቤዛዊትን ለማዋለድ ጥረት እያረጉ ነዉ
ቤተሰቦቿ በረንዳ ላይ ሆነዉ በጭንቀት የልጃቸውን ሁኔታ ለማወቅ ከወድያ ወዲህ ይንጓማለላሉ
ቤዛዊት የምጥ ጩሀት ተጮሀለች
"ኡ ኡፍ ኡ ኡ "
ጩሀቷን ዉጪ የሚሰሙት እናቷ መቆም ስላልቻሉ አንጀታቸዉን እስር አርገዉ ተቀመጡ
አባቷ በሀሳብ ጭልጥ ብለዉ ሄደዋል እህቷ በፍርሀት እርዳለች የቤዛዊት ሁኔታ አወራሯ አልጣማትም ነበር።
ፍፁም በየሳምንቱ መምጣት አስለምዳዉ ስትቀር ቅር ያለዉ ቢሆንም የሆዷን መግፋት
የመዉለጃዋ ቀይ እየደረሰ ስለመጣ
እየተጨነቀም ቢሆን ልጁን አቅፋ መጥታ እንደምታሳየዉ ተስፋ እያደረገ ነበር።
ዶክተሮቹ እንድትበረታ እየነገሯት ነው ኦፕራሲዮን ማረግ የፈሩ ይመስላሉ
ቤዛዊት ለመጨረሻ ጊዜ ስትጮህ ከሆዷ አዲስ ሰዉ አዲስ ፍጥረት ወደ አለም ቀላቅላ
በዛችዉ ቅፅበት የእሷ ህይወት ግን ከዚህ አለም ሾልኮ ሄዶ በድን ሆና ነበር
(ከደቂቃዎች በፊት)
ቤዛዊት በአልጋ እየተገፋች ወደ ማዋለጃ ክፍል ከመግባቷ በፊት
በተኛችበት ሆና ቀና ማለት እየከበዳት ከርታታ አይኗን ለመግለጥ እየታገለች ቤተሰቦቿን ተሰብስበዉ ለአፍታ አየቻቸዉ እናቷ እየሮጡ የሚገፋዉ አልጋ ላይ ደርሰዉ እጇን ለመሳም ሲሞክሩ ቤዛዊት ቃል ከአፏ አወጣች
"ልጄን አደራ ልጄን አ ደ ራ"
ሁሉ ነገር የታያት ይመስል ነበር።
የመጨረሻውን ክፍል ነገ 12 ሰዓት ይጠብቁ
💫ይቀጥላል 💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስድስት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...አቀፈቻቸዉ
እናቷ መቼም ቢሆን የእሷን ፍላጎት ተጋፍተዉ ባያዉቁም ትምህርትን ሳትመረቅ ልጅ ለመዉለድ በመቸኮሏ ቅር ቢሰኙም አጣሁዋት አይምሮዋ ተቃዉሶ ተቀጨችብኝ ብለዉ ካዘኑበት በርካታ አመታት ጤናዋ ተመልሶ ከፊታቸዉ ቆማ የልጅ ልጅ ላሳያችሁ ነው ማለቷ ለእሳቸዉ አለም ነበር
የሚያስጨንቃቸዉ ሁሌ የልጃቸዉ ጤንነት ብቻ ስለነበር።
ትምህርት ስራ ገንዘብ ሀብት ....የህይወት መስመሮች ዉስጥ ያሉ መንገዶች ሊሆኑ ይችላሉ
ዋናዉ የህይወት ዋስትናችን ግን ጤንነታችን ላይ የተመረኮዘ ነዉ።
የቤዛዊት ሆድ ከቀን ወደ ቀን እየገፋ ፍፁም ጋር በየሳምንቱ ሳትቀር የሚያስፈልገዉን ይዛ እየጠየቀችዉ የመዉለጃዋ ስዓት ሲቃረብ የህመም ስሜትም ጀመራት።
በበፊቱ የአይምሮ ህመሟ ወቅት እሷ ሳይታወቃት ስትወድቅ ስትነሳ ሰዉነቷ ልጁን ለመቋቋም አልቻለም ነበር
ሆድዋ አካባቢ ቀላል የህመም ስሜትን እየተሰማት መራመድም እያቃታት ፍፁምን መጠየቅ እየፈለገች ነገር ግን ከአቅሟ በላይ ስለሆነ ቤት ዉስጥ እራሱ ጉድ ጉድ ማለቱ ሲያቅታት ቤተሰቧቿ ወደ ሆስፒታል ወሰዷት።
የሆስፒታሉ አልጋ ላይ ሆና ቤዛዊት እህቷን
"ወረቀት እና እስኪርቢቶ አቀብይኝ"
አለቻት
"ምን ልትፅፊ ነው ደሞ"
እያለች እስኪርቢቶ ከቦርሳዋ አዉጥታ ወረቀት ስላጣች
"ወረቀት ግን የለኝም ቤዚ"
ቤዛዊት ፊት ላይ እርግዝናዉ ይሆን ባልታወቀ ሁኔታ ተለዋዉጣለች ጉንጮቿ ቀልተዋል የአይኖቿ
ቆቦች ወፍረዉ አይኗን መግለጥ ያቃታት ነዉ የምትመስለዉ
"ለፍፁም የምፅፍለት ነገር ነበር ተይዉ በቃ ልጄን ወልጄ አንድ ላይ ከልጄ ጋር ስንሄድ እነግረዋለሁ"
አለችና በትግል ለመሳቅ እየሞከረች
"የልጄን ስም ዳግማዊት ፍፁም ብላትስ"
እህቷን እየጠየቀቻት የእንሽርት ዉሀዋ ፈሰሰ።
የማዋለጃ ክፍል ዉስጥ ሀኪሞቹ ቤዛዊትን ለማዋለድ ጥረት እያረጉ ነዉ
ቤተሰቦቿ በረንዳ ላይ ሆነዉ በጭንቀት የልጃቸውን ሁኔታ ለማወቅ ከወድያ ወዲህ ይንጓማለላሉ
ቤዛዊት የምጥ ጩሀት ተጮሀለች
"ኡ ኡፍ ኡ ኡ "
ጩሀቷን ዉጪ የሚሰሙት እናቷ መቆም ስላልቻሉ አንጀታቸዉን እስር አርገዉ ተቀመጡ
አባቷ በሀሳብ ጭልጥ ብለዉ ሄደዋል እህቷ በፍርሀት እርዳለች የቤዛዊት ሁኔታ አወራሯ አልጣማትም ነበር።
ፍፁም በየሳምንቱ መምጣት አስለምዳዉ ስትቀር ቅር ያለዉ ቢሆንም የሆዷን መግፋት
የመዉለጃዋ ቀይ እየደረሰ ስለመጣ
እየተጨነቀም ቢሆን ልጁን አቅፋ መጥታ እንደምታሳየዉ ተስፋ እያደረገ ነበር።
ዶክተሮቹ እንድትበረታ እየነገሯት ነው ኦፕራሲዮን ማረግ የፈሩ ይመስላሉ
ቤዛዊት ለመጨረሻ ጊዜ ስትጮህ ከሆዷ አዲስ ሰዉ አዲስ ፍጥረት ወደ አለም ቀላቅላ
በዛችዉ ቅፅበት የእሷ ህይወት ግን ከዚህ አለም ሾልኮ ሄዶ በድን ሆና ነበር
(ከደቂቃዎች በፊት)
ቤዛዊት በአልጋ እየተገፋች ወደ ማዋለጃ ክፍል ከመግባቷ በፊት
በተኛችበት ሆና ቀና ማለት እየከበዳት ከርታታ አይኗን ለመግለጥ እየታገለች ቤተሰቦቿን ተሰብስበዉ ለአፍታ አየቻቸዉ እናቷ እየሮጡ የሚገፋዉ አልጋ ላይ ደርሰዉ እጇን ለመሳም ሲሞክሩ ቤዛዊት ቃል ከአፏ አወጣች
"ልጄን አደራ ልጄን አ ደ ራ"
ሁሉ ነገር የታያት ይመስል ነበር።
የመጨረሻውን ክፍል ነገ 12 ሰዓት ይጠብቁ
💫ይቀጥላል 💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍1
#ከምንም_በላይ
ያለሐሰት ብትኖሪ
ከልብ ብታፈቅሪ
ፍፁም ብትሆኚ ነፃነት ቢሰማሽ
በቅድሚያ ወስነሽ ቆመሽ ለዓላማሽ
“ከፍቅር ከእውነት
ወይም ከነፃነት
የትኛው ያዋጣል?
የትኛው ይበልጣል? "
ብለሽ ብጠይቂኝ
በነጋ በጠባ ባገኘሁሽ ቁጥር ብታጨናንቂኝ
የእውነት መኖሬ
ከልብም ማፍቀሬ
ይገባሻል ብዬ
ሁሉን ላንቺ ጥዬ
ግን ምላሽ ልስጥሽ
በሰከነ መንፈስ አጥንቼ መርምራ
በረጋ አዕምሮ ምርጫሽን በርብሬ
በትኜ እየኋቸው ለ ይ ቼ ዘርዝሬ።
ያለፍቅር ሕይወት” ትርጉም ያጣብኛል
ያለእውነት መኖር ፍርጃ ይመስለኛል
ሺ ጊዜ ቢፋቀር
ሰው ነፃ ካልሆነ እንዴት ይገናኛል?!
እንዴት ይቆራኛል?'
በእብሮ መኖር ሒደት ነፃ ሆኖ ተዋ'ዶ
በአካል በመንፈስም እያደር ተላምዶ
በሐሳብ ተግባብቶ ተስማምቶ ተዛምዶ
ከ “እውነት” ማህፀን “ፍቅር”ንም ወልዶ፡፡
ሕብር ፈጥሮ መኖር የስው ልጅ ይችላል
በ “እውነት” ይቻላል!.. በ “ፍቅር” ይቻላል
“ፍቅር” ይጣፍጣል በ”እውነት” ደስ ይላል
ከምንም በላይ ግን
“ነፃነት” ይበልጣል፤ ነፃነት” ያይላል።
በእውነት ስም-ማዪ ከንግዲህ ሞግቺኝ እሠሪኝ ገዝቺኝ
ስለፍቅር ስትዪ በፍቅር ስም 'ርቺኝ አንበርክከሽ ቅጪኝ
ስትፈልጊ ፍቺኝ ከምንም በላይ ግን ነፃነቴን ስጪኝ፡፡
🔘በፋሲል🔘
ያለሐሰት ብትኖሪ
ከልብ ብታፈቅሪ
ፍፁም ብትሆኚ ነፃነት ቢሰማሽ
በቅድሚያ ወስነሽ ቆመሽ ለዓላማሽ
“ከፍቅር ከእውነት
ወይም ከነፃነት
የትኛው ያዋጣል?
የትኛው ይበልጣል? "
ብለሽ ብጠይቂኝ
በነጋ በጠባ ባገኘሁሽ ቁጥር ብታጨናንቂኝ
የእውነት መኖሬ
ከልብም ማፍቀሬ
ይገባሻል ብዬ
ሁሉን ላንቺ ጥዬ
ግን ምላሽ ልስጥሽ
በሰከነ መንፈስ አጥንቼ መርምራ
በረጋ አዕምሮ ምርጫሽን በርብሬ
በትኜ እየኋቸው ለ ይ ቼ ዘርዝሬ።
ያለፍቅር ሕይወት” ትርጉም ያጣብኛል
ያለእውነት መኖር ፍርጃ ይመስለኛል
ሺ ጊዜ ቢፋቀር
ሰው ነፃ ካልሆነ እንዴት ይገናኛል?!
እንዴት ይቆራኛል?'
በእብሮ መኖር ሒደት ነፃ ሆኖ ተዋ'ዶ
በአካል በመንፈስም እያደር ተላምዶ
በሐሳብ ተግባብቶ ተስማምቶ ተዛምዶ
ከ “እውነት” ማህፀን “ፍቅር”ንም ወልዶ፡፡
ሕብር ፈጥሮ መኖር የስው ልጅ ይችላል
በ “እውነት” ይቻላል!.. በ “ፍቅር” ይቻላል
“ፍቅር” ይጣፍጣል በ”እውነት” ደስ ይላል
ከምንም በላይ ግን
“ነፃነት” ይበልጣል፤ ነፃነት” ያይላል።
በእውነት ስም-ማዪ ከንግዲህ ሞግቺኝ እሠሪኝ ገዝቺኝ
ስለፍቅር ስትዪ በፍቅር ስም 'ርቺኝ አንበርክከሽ ቅጪኝ
ስትፈልጊ ፍቺኝ ከምንም በላይ ግን ነፃነቴን ስጪኝ፡፡
🔘በፋሲል🔘
❤1👍1
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት(የመጨረሻ ክፍል)
፡
#በክፍለማርያም
..ልጄን አደራ እያለች ነበር
ፍፁም እስር ቤት ዉስጥ የቤዛዊትን ልጃቸዉን አቅፋ መምጣት በጉጉት ይጠብቃል ነገር ግን ቤዛዊትን በላሁ የሚል ጅብ አልጮህ አለ።
የቤዛዊት ቀብር ተፈፅሞ ልጇን ቤዛዊት ባወጣችላት ስም አየጠሩ ቤተሰቦቿ በከባድ ሀዘን ዉስጥ ሆነዉም ቢሆን በእሷ ምትክ ልጅ ሰጥታቸዉ አልፋለች እና የወለደቻትን ቆንጅዬ ሴት ልጅ እንደቤዛዊት አይተዉ እየተንከባከቧት ነበር።
እስር ቤት ቀን ወራት ነዉ አመት ዘመን ነዉ ደቂቃ እየተንቀራፈፉ ነዉ የሚጓዙት ፍፁም ጥግ ላይ ተቀምጦ ወረቀት እና እስኪቢርቶዉን ይዞ
የህይወቱን የመጨረሻ ክፍል በመፃፍ ላይ ነዉ
ቤዛዊት ምን ገጥሟት ቀረች ለሚለዉ መልስ እንኳን መልስ ማግኘት አልቻለም በልቡ ቤተሰቦቿ አስገድደዋት ልጁን አስወርዳ ሌላ ባል አግብታ ይስላል
እስር ቤቱ ዉስጥ የመጀመርያዎቹ ሳምንታት ቤዛዊት
"የምስራች ልጅ ልወልድልህ ነዉ"
ብላዉ የጠፋችበት ወቅት ለእሱ ከባድ ነበር ስሙ የተጠራ እየመሰለዉ በለሊት
"አቤት"
ይል ነበር አንዳንዴ ቤዛዊት ያስጠራችዉ እየመሰለዉ
በህልሙ ሁሌ ልጇን አቅፋ እየሳቀች ትቀርበዉና አጠገቡ ስትደርስ የዉሀ ሽታ ሆና እንደጉም ትበተናለች ይጨነቅ ይረበሽ ነበር።
ሰከንዶች እያዘገሙ ደቂቃ ይሆናሉ ደቂቃወች ወደ ሰአት ለማደግ ይንቀራፈፋሉ ሰአታት ሰአት ሆነዉ ለመቆጠር አቅም ያንሳቸዋል ቀን እና ለሊት ለመለዋወጥ በጣም አሰልቺ ጊዜን የሚወስዱ እየመሰለው ቀን በመቁጠር ተጠምዶ ሲዉል ነበር።
አመት አመትን እየተካ ፍፁምም የወጣትነት ፊቱ በጎልማሳ ፊት እየተቀየረ የጭንቀት ሀሳቦቹ ቀስ በቀስ እየቀለሉት
ቀን መቁጠሩን ትቶ የተፈረደበትን ብዙ አመታትን ወደማገባደዱ ሲደርስ ጭንቀቱ ዳግም ማገርሸት ጀመረ።
ፍፁም እድሜዉ ወደ ሀምሳወቹ እየተጠጋ ነዉ መፈቻዉ እየደረሰ ሲመጣ ወደ በፊቱ ሀሳብ ተመለሰ
"ፍቅር አያረጅም ትዝታ አያረጅም
እድሜ ቢጠወልግ ሰውነት ቢጃጅም"
ቤዛዊት እሱን ለመጠየቅ መጥታ ልጅ አርግዤልሀለዉ ያለችዉን ቀን እያስታወሰ አሁን ቤዛዊት እና ልጁ ሊኖሩ የሚችሉበትን ሁኔታ እያሰበ ይቆዝም ገባ።
የቤዛዊት ቤተሰቦች ለፍፁም ልጁን ለማሳየት ማረምያ ቤት ለመምጣት ያስቡና የተፈረደበት ፍርድ ብዙ አመታት መሆኑን ሲያዉቁ ልፋት እና ልጅቷን ማንከራተት እየመሰላቸዉ ጥቂት ጊዜያት በተግባር ባያረጉትም ያስቡት ነበር
አመት እየተለወጠ በአመት ሲተካ እረሱት የቤዛዊት አባትም በህመም ተይዘዉ ብዙም ሳይቆዩ ስለሞቱ እህቷ ባል አግብታ የራሷን ሁለት ልጆች ወልዳ ከእናቷ ጋር የቤዛዊትን ልጅም ጭምር ፍቅር ሰጥተዉ እየተንከባከቧት አሳደጓት እድሜዋም ወደ ሀያወቹ እየተጠጋ ወጣት ሆናለች
ፍፁም የመፈቻ ስሙ ተጠርቶ የነበረውን ሁሉ ታሪኩን ከፃፈበት ወረቀት ዉጪ ሁሉንም ለታሳሪወች አከፋፍሎ ሁሉንም አቅፎ ተሰናብቶ ከማረምያ ቤቱ ወጣ
የብዙ አመት መኖርያ የነበረዉን እስርቤቱን ለመጨረሻ ጊዜ ተመልክቶት ግቢዉን ለቆ ወደ ቤዛዊት እና ልጁ ገሰገሰ።
የእነ ቤዛዊት በር ጋር ደርሶ ቆመ በር ማንኳኳት አልቻለም ቆሞ ልቡ ሲመታ እና ሲጨንቀዉ የግቢያቸዉን በር ተደግፎ ለመረጋጋት እየሞከረ በሩ ተከፍቶ ወጣት ሴት ወጥታ
"ምን ሆነዉ ነዉ አሞት ነዉ ዉሀ ላምጣሎት?"
ፍፁም አንገቱን ቀና አርጓ አያት የቤዛዊትን አይን የያዘች ደግነቷም እንደሷ የሆነ ቆንጆ ልጅ
ልቡ ልጁ እንደሆነች እየነገረዉ የጥንቱ ፈገግታ ፊቱ ላይ ባይኖርም ለመሳቅ እየታገለ
"ስምሽ ማነዉ?"
ብሎ ጠየቃት
ደንግጣ የፍፁምን የተዳከመ የከፋዉ የሚመስል ፊት ለአፍታ አይታ
"ዳግማዊት"
አለችዉ
"የአባትሽን ስምም ንገሪኝ"
ፍፁም መጀመርያ የቤዛዊትን ስም ሲጠይቃትም እንደዚህ ነበር ያላት
ዳግማዊት ማን ነዉ ምን ፈልጎ ነዉ...በሚል የጥርጣሬ አይን እያየችዉ
"ዳግማዊት ፍፁም"
እያለችዉ አያቷ
"ከማን ጋር ነዉ ደሞ የምታወሪዉ"
እያሉ ወደ ደጅ ሲወጡ አብራዉ የቆመችዉን ሰዉዬ ተመለከቱት እርጅናዉ በርቀት አላሳይ እያለ ስለሚያስቸግራቸዉ በጣም ቀርበዉ ተጠግተዉ እያዩት
"ማን ነህ አንተ"
ፊቱ ዉስጥ የተደበቀ የበፊቱ ፍፁም እየታያቸዉ
"ዉይ ዉይ አፈር በበላሁ ልጄ ልጄ ልጄ"
ማልቀስ ጀመሩ ለፍፁም ሳይሆን ከሞተች አመታቶች ያለፋት ቤዛዊት ፍፁምን ሲያዩት ፊታቸዉ ላይ ድቅን ብላባቸዉ እንጂ።
ፍፁም የቤዛዊት በህይወት አለመኖር ዉስጡ እየነገረዉ ነበር ወደ ቤት ዉስጥ እያለቀሰ ገብቶ ተቀመጠ ማዉራት አቅቶት በአይኑ ዳግማዊትን አያት
አይኖቿ ላይ ለማታዉቃት ለወለደቻት እናቷ እንባወች ይታዩበታል
ከተቀመጠበት ተነስቶ ተጠጋት
"ዳግማዊት አባትሽ ነኝ"
አቀፋት ወደ ደረቱ አስጠግቶ የብዙ አመት ናፍቆቱን ሀሳቡን በለቅሶ እየተንሰቀሰቀ ልጁን አቅፎ
ማንባት ቀጠለ ቤዛዊት አለመኖሯን የሚያስረሳ ምትክ ስለሰጠችዉ ልጁን ደግሞ ደጋግሞ አቀፋት እስከ ህይወቱ ማብቅያ ለልጁ ለመኖር ቃል እየገባ።
💫ተፈፀመ💫
ስለ ድርሰቱ ያሎትን አስተያየት በ @atronosebot ላይ እንጠብቃለን መልካም ጊዜ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት(የመጨረሻ ክፍል)
፡
#በክፍለማርያም
..ልጄን አደራ እያለች ነበር
ፍፁም እስር ቤት ዉስጥ የቤዛዊትን ልጃቸዉን አቅፋ መምጣት በጉጉት ይጠብቃል ነገር ግን ቤዛዊትን በላሁ የሚል ጅብ አልጮህ አለ።
የቤዛዊት ቀብር ተፈፅሞ ልጇን ቤዛዊት ባወጣችላት ስም አየጠሩ ቤተሰቦቿ በከባድ ሀዘን ዉስጥ ሆነዉም ቢሆን በእሷ ምትክ ልጅ ሰጥታቸዉ አልፋለች እና የወለደቻትን ቆንጅዬ ሴት ልጅ እንደቤዛዊት አይተዉ እየተንከባከቧት ነበር።
እስር ቤት ቀን ወራት ነዉ አመት ዘመን ነዉ ደቂቃ እየተንቀራፈፉ ነዉ የሚጓዙት ፍፁም ጥግ ላይ ተቀምጦ ወረቀት እና እስኪቢርቶዉን ይዞ
የህይወቱን የመጨረሻ ክፍል በመፃፍ ላይ ነዉ
ቤዛዊት ምን ገጥሟት ቀረች ለሚለዉ መልስ እንኳን መልስ ማግኘት አልቻለም በልቡ ቤተሰቦቿ አስገድደዋት ልጁን አስወርዳ ሌላ ባል አግብታ ይስላል
እስር ቤቱ ዉስጥ የመጀመርያዎቹ ሳምንታት ቤዛዊት
"የምስራች ልጅ ልወልድልህ ነዉ"
ብላዉ የጠፋችበት ወቅት ለእሱ ከባድ ነበር ስሙ የተጠራ እየመሰለዉ በለሊት
"አቤት"
ይል ነበር አንዳንዴ ቤዛዊት ያስጠራችዉ እየመሰለዉ
በህልሙ ሁሌ ልጇን አቅፋ እየሳቀች ትቀርበዉና አጠገቡ ስትደርስ የዉሀ ሽታ ሆና እንደጉም ትበተናለች ይጨነቅ ይረበሽ ነበር።
ሰከንዶች እያዘገሙ ደቂቃ ይሆናሉ ደቂቃወች ወደ ሰአት ለማደግ ይንቀራፈፋሉ ሰአታት ሰአት ሆነዉ ለመቆጠር አቅም ያንሳቸዋል ቀን እና ለሊት ለመለዋወጥ በጣም አሰልቺ ጊዜን የሚወስዱ እየመሰለው ቀን በመቁጠር ተጠምዶ ሲዉል ነበር።
አመት አመትን እየተካ ፍፁምም የወጣትነት ፊቱ በጎልማሳ ፊት እየተቀየረ የጭንቀት ሀሳቦቹ ቀስ በቀስ እየቀለሉት
ቀን መቁጠሩን ትቶ የተፈረደበትን ብዙ አመታትን ወደማገባደዱ ሲደርስ ጭንቀቱ ዳግም ማገርሸት ጀመረ።
ፍፁም እድሜዉ ወደ ሀምሳወቹ እየተጠጋ ነዉ መፈቻዉ እየደረሰ ሲመጣ ወደ በፊቱ ሀሳብ ተመለሰ
"ፍቅር አያረጅም ትዝታ አያረጅም
እድሜ ቢጠወልግ ሰውነት ቢጃጅም"
ቤዛዊት እሱን ለመጠየቅ መጥታ ልጅ አርግዤልሀለዉ ያለችዉን ቀን እያስታወሰ አሁን ቤዛዊት እና ልጁ ሊኖሩ የሚችሉበትን ሁኔታ እያሰበ ይቆዝም ገባ።
የቤዛዊት ቤተሰቦች ለፍፁም ልጁን ለማሳየት ማረምያ ቤት ለመምጣት ያስቡና የተፈረደበት ፍርድ ብዙ አመታት መሆኑን ሲያዉቁ ልፋት እና ልጅቷን ማንከራተት እየመሰላቸዉ ጥቂት ጊዜያት በተግባር ባያረጉትም ያስቡት ነበር
አመት እየተለወጠ በአመት ሲተካ እረሱት የቤዛዊት አባትም በህመም ተይዘዉ ብዙም ሳይቆዩ ስለሞቱ እህቷ ባል አግብታ የራሷን ሁለት ልጆች ወልዳ ከእናቷ ጋር የቤዛዊትን ልጅም ጭምር ፍቅር ሰጥተዉ እየተንከባከቧት አሳደጓት እድሜዋም ወደ ሀያወቹ እየተጠጋ ወጣት ሆናለች
ፍፁም የመፈቻ ስሙ ተጠርቶ የነበረውን ሁሉ ታሪኩን ከፃፈበት ወረቀት ዉጪ ሁሉንም ለታሳሪወች አከፋፍሎ ሁሉንም አቅፎ ተሰናብቶ ከማረምያ ቤቱ ወጣ
የብዙ አመት መኖርያ የነበረዉን እስርቤቱን ለመጨረሻ ጊዜ ተመልክቶት ግቢዉን ለቆ ወደ ቤዛዊት እና ልጁ ገሰገሰ።
የእነ ቤዛዊት በር ጋር ደርሶ ቆመ በር ማንኳኳት አልቻለም ቆሞ ልቡ ሲመታ እና ሲጨንቀዉ የግቢያቸዉን በር ተደግፎ ለመረጋጋት እየሞከረ በሩ ተከፍቶ ወጣት ሴት ወጥታ
"ምን ሆነዉ ነዉ አሞት ነዉ ዉሀ ላምጣሎት?"
ፍፁም አንገቱን ቀና አርጓ አያት የቤዛዊትን አይን የያዘች ደግነቷም እንደሷ የሆነ ቆንጆ ልጅ
ልቡ ልጁ እንደሆነች እየነገረዉ የጥንቱ ፈገግታ ፊቱ ላይ ባይኖርም ለመሳቅ እየታገለ
"ስምሽ ማነዉ?"
ብሎ ጠየቃት
ደንግጣ የፍፁምን የተዳከመ የከፋዉ የሚመስል ፊት ለአፍታ አይታ
"ዳግማዊት"
አለችዉ
"የአባትሽን ስምም ንገሪኝ"
ፍፁም መጀመርያ የቤዛዊትን ስም ሲጠይቃትም እንደዚህ ነበር ያላት
ዳግማዊት ማን ነዉ ምን ፈልጎ ነዉ...በሚል የጥርጣሬ አይን እያየችዉ
"ዳግማዊት ፍፁም"
እያለችዉ አያቷ
"ከማን ጋር ነዉ ደሞ የምታወሪዉ"
እያሉ ወደ ደጅ ሲወጡ አብራዉ የቆመችዉን ሰዉዬ ተመለከቱት እርጅናዉ በርቀት አላሳይ እያለ ስለሚያስቸግራቸዉ በጣም ቀርበዉ ተጠግተዉ እያዩት
"ማን ነህ አንተ"
ፊቱ ዉስጥ የተደበቀ የበፊቱ ፍፁም እየታያቸዉ
"ዉይ ዉይ አፈር በበላሁ ልጄ ልጄ ልጄ"
ማልቀስ ጀመሩ ለፍፁም ሳይሆን ከሞተች አመታቶች ያለፋት ቤዛዊት ፍፁምን ሲያዩት ፊታቸዉ ላይ ድቅን ብላባቸዉ እንጂ።
ፍፁም የቤዛዊት በህይወት አለመኖር ዉስጡ እየነገረዉ ነበር ወደ ቤት ዉስጥ እያለቀሰ ገብቶ ተቀመጠ ማዉራት አቅቶት በአይኑ ዳግማዊትን አያት
አይኖቿ ላይ ለማታዉቃት ለወለደቻት እናቷ እንባወች ይታዩበታል
ከተቀመጠበት ተነስቶ ተጠጋት
"ዳግማዊት አባትሽ ነኝ"
አቀፋት ወደ ደረቱ አስጠግቶ የብዙ አመት ናፍቆቱን ሀሳቡን በለቅሶ እየተንሰቀሰቀ ልጁን አቅፎ
ማንባት ቀጠለ ቤዛዊት አለመኖሯን የሚያስረሳ ምትክ ስለሰጠችዉ ልጁን ደግሞ ደጋግሞ አቀፋት እስከ ህይወቱ ማብቅያ ለልጁ ለመኖር ቃል እየገባ።
💫ተፈፀመ💫
ስለ ድርሰቱ ያሎትን አስተያየት በ @atronosebot ላይ እንጠብቃለን መልካም ጊዜ
👍3
#ሮሜዎና_ዡልዬት
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
ለክፋት ፡ ነው ፡እንጂ አልመጣም ፡ በደኅና
እንግዴህ ፡ ልያዘው ፡ ድንገት ፡ ልድረስና ።
(ቀረበ) ።
አንተ ፡ የሞንታግ ፡ ልጅ ፡ዐመፀኛ ፡ መጥፎ
በሰላም ፡ ጸጥታ፡ የተኛውን ፡ ዐርፎ ፡
ምን ፡ ልታደርግ ፡ ነው ፡ ትኵሱን ፡ ሬሳ ፡
ከመቃብሩ ፡ ላይ ፡ በል ፡ እጅህን ፡ አንሣ ፡
ና፡ ወዲህ ፡ ልያዝህ ፡ ከዚህ ፡ ቦታ ፡ ውጣ
ኣሳልፌ ፡ ልስጥህ ፡ በሞት ፡ ለሚቀጣ ።
#ሮሜዎ
አንተ መልካም ወጣት፡ዐርፈህ ሂድ በደኅና
እኔ ፡ ሞገደኛ፡ አጥፊ ፡ ሰው ፡ ነኝና ፡
መዘዜ፡ የበዛ ፡ አሳር ፡ የጐተተኝ፡
ሕይወቴን ፡ የጠላሁ፣ ኑሮ ፡ የታከተኝ፡
ሞትና ፡ መቃብር ፡ ጥፋት ፡ የሸተተኝ ፡
የከፋው ፡ ወንድ ፡ ነኝ ፡ ወደኔ ፡ አትጠጋ ፤ .
ጠብ ፡ አትፈልገኝ' ለሕይወትህ ፡ ሥጋ ።
ቲባልት ፡ እንደዚሁ ፡ ደርሶ : ሳይቸግረው ፡
በመጥፎ፡ ንግግር ፡ ሆዴን ፡ አሳረረው ፡
ሳልፈልግ ፡ ገደልኩት እሱ ባነሣው ፡ ጠብ
አሁን ፡ ደግሞ ፡ አንተ ይብቃህ ፡ አትሳደብ
ነፍሴን ፡ የጠላሁ፡ ሰው ፡ በመሆኔ ፡ ፍራኝ
ሳልወድ ፡ በግዴታ ፡ ዐመፅ ፡ አታሠራኝ ፡
የሚወጣው ፡ ምክር ፡ አሁን ፡ ከመላሴ ፡
አልሠራሁበትም ፡ እኔ ፡ እንኳ ፡ ለራሴ ፡
ስለዚህ ፡ ከራሴ ፡ አብልጬ ፡ ስወድህ ፡
እኔን ፡ አመስግነህ ፡ ይሻላል ፡ መሄድህ ፡
አንድ፡ እብድ ፡ ሰው ዛሬ የሰጠኝን ምክር
ሰምቼ ፡ ድኛለሁ ፡ ብለህ ፡ ይልቅ ፡ ፎክር ።
#ፓሪስ ።
እኔስ ፡ ኣለቅህም ፡ ከያዝኩህ ፡ በኋላ ፤
መስጠት ፡ ትችላለህ ፡ ምክርህን ፡ ለሌላ
#ሮሜዎ
መሞት ፡ ከፈለገህ ፡ እንቢ ፡ ብለህ ፡ በጄ ፡
እንግዲያው ሞክረኝ መልካም፡ነው ወዳጄ
(ይዋጉና'ፓሪስ ፡ ይወድቃል) ።.
ቲባልትና ፣ፓሪስ ፡ እኔን እያስቆጡ ፣
እኔ ፡ ሳልነካቸው ፡ በግድ ፡ እየመጡ፡
በእጄ ፡ እየተወጉ' ክዚህ ፡ ዓለም ፡ ወጡ ።
እንዲህ ፡ መሞታቸው ፡ ተናግረውኝ ፡ ክፉ
ተፈርዶባቸው ፡ ነው ፡ በኔ' እጅ እንዲጠፉ
እንደዚህ ፡ ከሆነ ፡ ፓሪስ ፡ ያንተም ፡ ዕጣ ፡
ጥፋቱ ፡ ያንተ ፡ ነው ፡ በኔ ፡ እንዳትቈጣ ፡
የዡልዬት ፡ ቁንዥና፡ ደምቆ እንደ ፡ ብርሃን
ጽርሐ አርያም ፡ መስሎ የሰማይ ፡ ውጋጋን
እያንጸባረቀ ፡ ከኮከብ ፡ ሲያበራ ፡
ግርማ፡ተጐናጽፎ፡ በታየበት፡ ስፍራ፡
እንሙት' ወዳጄ ፡ ኣብረን ፡ ከሷ ፡ ጋራ።
(ሮሜዎበዝልዬት፡መቃብር፡ላይየሐዘን ' ንግግር ፡ ያደርጋል)።
ይህችን ፡ ውብ ፡ አበባ ፡ ፍቅር ፡ አሳማሪ ፡
ውሏን ፡ የማትረሳ ፡ ቃል ፡ ኪዳን ፡ አክባሪ ፡
ትወድ ፡ የነበረች ፡ ቁም ፡ ነገር ፡ ጨዋታ፡
እዩልኝ ፡ ከዘመድ ፡ ከሰው ፡ ተለይታ ፡
የኔ ፡ ሆደ፡ ባሻ ፡ ብቻዋን ፡ ተኝታ፡
ተመልከቱት ፡ እጅዋ ፡ ተመልከቱት ፡ ፊቷ ፤
ወዟ ፡ ገና፡ አልጠፋም ። ከሠራ፡ አካላቷ፡
ግንባሯን ፡ ከንፈራን ፡ ተመልከቱ ፡ ጣቷን ፤
ይህን ፡ አበቃቀል ፡ ተክለ ፡ ሰውነቷን ፡
ገላዋ ፡ ያበራል ፡ በደም ፡ ተሸልሞ ፤
ዡልዬት ፡ሞት የነካት፡አትመስልም ፈጽሞ
እባካችሁ ፡ ሰዎች ፡ ሐዘን፡ ተካፈሉኝ፤
ዡልዬት ፡ አልሞተችም ፡ ተኝታለች ፡ በሉኝ
ታውቂ ፡ የነበርሽው ፡ ፍቅራዊ ፡ አቀባበል ፡
ሽቍጥቀጥ ፡እመቤት ባለመልካም ዐመል
ተወዳጁ ፡ ድምፅሽ ፡ ውብ ፡እንደ ፡ ሙዚቃ
በበገናው ፡ ቃሉ ፡ መንፈስ ፡ የሚያነቃ ፡
ዛሬ ፡ ወዴት ፡ ጠፋ? የት ፡ ቦታ ፡ ደረሰ ? .
ደግሞስ ዐይንሽ ፡ ቆቡን ስለ ምን ለበሰ ?
ዡልዩት ፡ ባትሞት ኖሮ፡ በውነት ፡ ባትቀበር
ሮሜዎ ፡ እዚህ ፡ ቆሞ ዝም አትልም ነበር
ባለም ፡ ላይ ፡ ብንሻ ፡ በውነቱ ፡ የት ፡ ኣለ ፡
ጨካኝ አረመኔ ፡ ሞትን ፡ የመሰለ ፡
ጥቂት ፡ አላዘነም ፡ አልሣሣም ፡ ጨርሶ ፡
ይችን ፡ ጽጌ ፡ ረዳ ፡ ሲጥላት ፡ በጥሶ :
ይችን ፡ አሳዛኝ ፡ ልጅ ፡ ትተዋት ፡ ሲሄዱ፡
በሩን ፡ የዘጋ ፡ ሰው ፡ እንዴት ፡ ቻለ ፡ ሆዱ
እይዋት ይችን ቄንጥ እይዋት ይችን ሎጋ
በባዶ፡ አዳራሽ ፡ በመቃብር ፡ ኣልጋ ፡
ወፍ ፡ በማይዞርበት ፡ ጭር ፡ ባለ ፡ ስፍራ ፡
ብቻዋን ፡ ቀርታለች ፡ አዲሷ ፡ ሙሽራ ።
በመከራ ፡ ቅመም ፡ ባሳር ፡ ተለውሶ :
ዡልዬት፡ ሕይወታችን ፡ መሮን ፡ እንደ ፡ኮሶ
ወጣን ፡ ከዚህ ፡ ዓለም ፡ ያላንድ ፡ ደስታ .
እንግዲህ ፡ እንኑር ፡ እዚህ ፡ በጸጥታ ።
ባለም ፡ ቦታ፡ ጠፍቶ ፡ ለመኖር'ተዋደን ፡
እዚህ ፡ ተገናኘን ፡ ካለም ፡ ላይ ፡ ተሰደን
አይቈጨን እንደዚህ ካለም መውጣታችን
በጣም ፡ ደስ ፡ይበለን ፡ በዛሬው ፡ ዕጣችን
ላለሙ ፡ ደስታ ፡ ለረዥሙም ፡ ዕድሜ ፡
ያው ሞት አይደለም ወይ የሁሉ ፍጻሜ ?
ገላዬን ፡ ከገላሽ ፡ ዐፅምሽን ፡ ካዕፅሜ ፡
ሥጋዬን ፡ ከሥጋሽ ፡ ደምሽን ፡ ከደሜ ፡
ቀላቅሎ ፡ የሚያኖር፡ ከተገኘ ፡ ቦታ ፡
ዡልዬት፡ ከዚህ ፡ ወዲያ ፡ ምን አለ ፡ ደስታ
ይቅር ፡ ደኅና ፡ ይሁን ፡ ዓለም ፡ ከነቂሙ ፤
እዚህ ፡ እኔና፡ አንቺ ፡ እስከ ፡ ዘላለሙ ፡
መቃብር፡ ሆኖልን ፡ የጸጥታ ፡ ገዳም ፡
ከዛሬ ፡ ጀምሮ ፡ እንኑር ፡ በሰላም ።
ከሚወዱት፡ጋራ፡ እንዲህ ፡ ጐን ፡ ለጐን ፡
ምንኛ ፡ መልካም ፡ ነው ፡ ዐፈር ፡ ትቢያ ፡ መሆን ።
(ሮሜዎ ፡ መርዝ ፡ ጠጥቶ ፡ ሞተ ።)
#አባ_ሎራ መብራትና፡ጕጠት፡ ይዞ ፡
ወደ፡መቃብሩ፡ ቦታ፡ መጣ ።
#አባ_ሎራ ።
ስፍራው ፡ አያስኬድም ፡ ሆነና ፡ መቃብር
እያደናቀፈ ፡ ያስቸግራል ፡ ለእግር ፡
አዬ ፡ መከራዬ ፡ በዚሁ ፡ ላይ ፡ ደግሞ ፡
ምንም ፡አይታየኝ ፡ዐይኔ ፡ በጣም ፡ ደክሞ
ማነህ አንተ እዚህ የቆምከው እንደ አጥር ?
#ቤልሻጥር ።
የሚያውቁኝ ፡ወዳጅዎ ፡እኔ፡ ነኝ ቤልሻጥር ።
#አባ_ሎራ ።
እግዚአብሔር ይባርክህ በል ልጄ ንገረኝ ፤
በሩቅ ፡ አላይ ፡ ብሎ ፡ ዐይኔ ፡ አስቸገረኝ፡
እዚያ ፡ በካፑሌ ፡ የመቃብር ፡ ስፍራ ፡
መብራት አይደለም፡ ወይ የማየው ፡ ሲበራ?
#ቤልሻጥር ።
አዎን ፡ ነው ፡ አባቴ ፡ ሄዷል ፡ እዚያ ፡ ቦታ ፡
ወዳጅዎ ፡ ሮሜዎ ፡ የኔ ፡ መልካም ፡ ጌታ
#አባ_ሎራ
ማን ፡ አልከኝ ?
#ቤልሻጥር ።
ሮሜዎ ።
#አባ_ሎራ ።
አዬ ፡ የእግዜር ፡ ቀጣ
ምን ፡ ያኽል ፡ ጊዜ ፡ ነው ፡ እሱ ፡ እዚህ ፡ ከመጣ ?
#ቤልሻጥር ።
ልክ ፡ እኩል ፡ ሰዓት ፡ ነው ።
#አባ_ሎራ ።
ና፡ እንሂድ፡ ወደ ፡ እሱ
#ቤልሻጥር ።
አልችልም ፡ አባቴ ፡ አስጠንቅቆ ፡ ራሱ ፡
ወደ ፡ መቃብሩ፡ እሱ ፡ ወዳለበት ፡
ከቶ ፡ እንዳልጠጋ ፡ ሥራውን ፡ ለማየት ፡
ከልክሎኛልና ፡ በሞት ፡ አስፈራርቶ ፤
ትእዛዙን ፡ ለመጣስ ፡ እኔ ፡አልችልም ፡ ከቶ
#አባ_ሎራ ፡
በል ፡ ተወው፡ ልጄ ፡ ሆይ፡ ሠግቷልና፡ ልቤ
እስቲ ፡ ልመልከተው ፡ ብቻዬን፡ቀርቤ።(አባ፡ሎራሄደ)
#ቤልሻጥር ፡ (ብቻውን ) ።
ዛፍ ፡ ተደገፍኩና ፡ እንቅልፍ ወስዶኝ ፡ ኖሮ
በሕልማ፡ ሮሜዎ ፡ አድርጎ ፡ አምባጓሮ ፡
ውጊያ፡ገጠሙና ፡ የኔ ፡ ጌታ ፡ ሲጥል ፡
አየሁ፡ ደግሞ ፡ ዛሬ ፡ ሌላ ፡ ሰው ፡ ሲገድል
#አባ_ሎራ ፡(ብቻውን) ።
ይህ ፡ ደም ፡ ከየት ፡ መጣ ? ይህ ሻምላ ፡ ምንድነው?
እዚህ ፡ የወደቀ ፡ ባለቤት ፡ የሌለው ።
(ዡሊዬት ነቃች ፤ አባ ፡ ሎራ፡ ጥግ ፡ ይዞ ፡ ቆመ) ።
#ዡልዬት ።
ሮሜዎ ፍቅሬ ሆይ ማን አምጥቶ ጣለህ ?
ይኸ ፡ ደም ምንድነው ? ፓሪስ ፡ ማ፡ገደለህ ?
ጨርሰው ፡ አይሰሙም ፡ ሞተዋል ፡ እነሱ
ትንፋሽም ፡ የላቸው ፡ አይንቀሳቀሱ ፡
የእንቅልፍ ፡ የመኝታ ፡ የዕረፍት ፡ የጸጥታ :
መሆኑ ፡ ቀረና ፡ ሰላማዊ ፡ ቦታ ፤
ከእንቅልፌ ፡ ስነቃ ፡ አወይ ፡ መቃብሬ ፡
የጦር ፡
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
ለክፋት ፡ ነው ፡እንጂ አልመጣም ፡ በደኅና
እንግዴህ ፡ ልያዘው ፡ ድንገት ፡ ልድረስና ።
(ቀረበ) ።
አንተ ፡ የሞንታግ ፡ ልጅ ፡ዐመፀኛ ፡ መጥፎ
በሰላም ፡ ጸጥታ፡ የተኛውን ፡ ዐርፎ ፡
ምን ፡ ልታደርግ ፡ ነው ፡ ትኵሱን ፡ ሬሳ ፡
ከመቃብሩ ፡ ላይ ፡ በል ፡ እጅህን ፡ አንሣ ፡
ና፡ ወዲህ ፡ ልያዝህ ፡ ከዚህ ፡ ቦታ ፡ ውጣ
ኣሳልፌ ፡ ልስጥህ ፡ በሞት ፡ ለሚቀጣ ።
#ሮሜዎ
አንተ መልካም ወጣት፡ዐርፈህ ሂድ በደኅና
እኔ ፡ ሞገደኛ፡ አጥፊ ፡ ሰው ፡ ነኝና ፡
መዘዜ፡ የበዛ ፡ አሳር ፡ የጐተተኝ፡
ሕይወቴን ፡ የጠላሁ፣ ኑሮ ፡ የታከተኝ፡
ሞትና ፡ መቃብር ፡ ጥፋት ፡ የሸተተኝ ፡
የከፋው ፡ ወንድ ፡ ነኝ ፡ ወደኔ ፡ አትጠጋ ፤ .
ጠብ ፡ አትፈልገኝ' ለሕይወትህ ፡ ሥጋ ።
ቲባልት ፡ እንደዚሁ ፡ ደርሶ : ሳይቸግረው ፡
በመጥፎ፡ ንግግር ፡ ሆዴን ፡ አሳረረው ፡
ሳልፈልግ ፡ ገደልኩት እሱ ባነሣው ፡ ጠብ
አሁን ፡ ደግሞ ፡ አንተ ይብቃህ ፡ አትሳደብ
ነፍሴን ፡ የጠላሁ፡ ሰው ፡ በመሆኔ ፡ ፍራኝ
ሳልወድ ፡ በግዴታ ፡ ዐመፅ ፡ አታሠራኝ ፡
የሚወጣው ፡ ምክር ፡ አሁን ፡ ከመላሴ ፡
አልሠራሁበትም ፡ እኔ ፡ እንኳ ፡ ለራሴ ፡
ስለዚህ ፡ ከራሴ ፡ አብልጬ ፡ ስወድህ ፡
እኔን ፡ አመስግነህ ፡ ይሻላል ፡ መሄድህ ፡
አንድ፡ እብድ ፡ ሰው ዛሬ የሰጠኝን ምክር
ሰምቼ ፡ ድኛለሁ ፡ ብለህ ፡ ይልቅ ፡ ፎክር ።
#ፓሪስ ።
እኔስ ፡ ኣለቅህም ፡ ከያዝኩህ ፡ በኋላ ፤
መስጠት ፡ ትችላለህ ፡ ምክርህን ፡ ለሌላ
#ሮሜዎ
መሞት ፡ ከፈለገህ ፡ እንቢ ፡ ብለህ ፡ በጄ ፡
እንግዲያው ሞክረኝ መልካም፡ነው ወዳጄ
(ይዋጉና'ፓሪስ ፡ ይወድቃል) ።.
ቲባልትና ፣ፓሪስ ፡ እኔን እያስቆጡ ፣
እኔ ፡ ሳልነካቸው ፡ በግድ ፡ እየመጡ፡
በእጄ ፡ እየተወጉ' ክዚህ ፡ ዓለም ፡ ወጡ ።
እንዲህ ፡ መሞታቸው ፡ ተናግረውኝ ፡ ክፉ
ተፈርዶባቸው ፡ ነው ፡ በኔ' እጅ እንዲጠፉ
እንደዚህ ፡ ከሆነ ፡ ፓሪስ ፡ ያንተም ፡ ዕጣ ፡
ጥፋቱ ፡ ያንተ ፡ ነው ፡ በኔ ፡ እንዳትቈጣ ፡
የዡልዬት ፡ ቁንዥና፡ ደምቆ እንደ ፡ ብርሃን
ጽርሐ አርያም ፡ መስሎ የሰማይ ፡ ውጋጋን
እያንጸባረቀ ፡ ከኮከብ ፡ ሲያበራ ፡
ግርማ፡ተጐናጽፎ፡ በታየበት፡ ስፍራ፡
እንሙት' ወዳጄ ፡ ኣብረን ፡ ከሷ ፡ ጋራ።
(ሮሜዎበዝልዬት፡መቃብር፡ላይየሐዘን ' ንግግር ፡ ያደርጋል)።
ይህችን ፡ ውብ ፡ አበባ ፡ ፍቅር ፡ አሳማሪ ፡
ውሏን ፡ የማትረሳ ፡ ቃል ፡ ኪዳን ፡ አክባሪ ፡
ትወድ ፡ የነበረች ፡ ቁም ፡ ነገር ፡ ጨዋታ፡
እዩልኝ ፡ ከዘመድ ፡ ከሰው ፡ ተለይታ ፡
የኔ ፡ ሆደ፡ ባሻ ፡ ብቻዋን ፡ ተኝታ፡
ተመልከቱት ፡ እጅዋ ፡ ተመልከቱት ፡ ፊቷ ፤
ወዟ ፡ ገና፡ አልጠፋም ። ከሠራ፡ አካላቷ፡
ግንባሯን ፡ ከንፈራን ፡ ተመልከቱ ፡ ጣቷን ፤
ይህን ፡ አበቃቀል ፡ ተክለ ፡ ሰውነቷን ፡
ገላዋ ፡ ያበራል ፡ በደም ፡ ተሸልሞ ፤
ዡልዬት ፡ሞት የነካት፡አትመስልም ፈጽሞ
እባካችሁ ፡ ሰዎች ፡ ሐዘን፡ ተካፈሉኝ፤
ዡልዬት ፡ አልሞተችም ፡ ተኝታለች ፡ በሉኝ
ታውቂ ፡ የነበርሽው ፡ ፍቅራዊ ፡ አቀባበል ፡
ሽቍጥቀጥ ፡እመቤት ባለመልካም ዐመል
ተወዳጁ ፡ ድምፅሽ ፡ ውብ ፡እንደ ፡ ሙዚቃ
በበገናው ፡ ቃሉ ፡ መንፈስ ፡ የሚያነቃ ፡
ዛሬ ፡ ወዴት ፡ ጠፋ? የት ፡ ቦታ ፡ ደረሰ ? .
ደግሞስ ዐይንሽ ፡ ቆቡን ስለ ምን ለበሰ ?
ዡልዩት ፡ ባትሞት ኖሮ፡ በውነት ፡ ባትቀበር
ሮሜዎ ፡ እዚህ ፡ ቆሞ ዝም አትልም ነበር
ባለም ፡ ላይ ፡ ብንሻ ፡ በውነቱ ፡ የት ፡ ኣለ ፡
ጨካኝ አረመኔ ፡ ሞትን ፡ የመሰለ ፡
ጥቂት ፡ አላዘነም ፡ አልሣሣም ፡ ጨርሶ ፡
ይችን ፡ ጽጌ ፡ ረዳ ፡ ሲጥላት ፡ በጥሶ :
ይችን ፡ አሳዛኝ ፡ ልጅ ፡ ትተዋት ፡ ሲሄዱ፡
በሩን ፡ የዘጋ ፡ ሰው ፡ እንዴት ፡ ቻለ ፡ ሆዱ
እይዋት ይችን ቄንጥ እይዋት ይችን ሎጋ
በባዶ፡ አዳራሽ ፡ በመቃብር ፡ ኣልጋ ፡
ወፍ ፡ በማይዞርበት ፡ ጭር ፡ ባለ ፡ ስፍራ ፡
ብቻዋን ፡ ቀርታለች ፡ አዲሷ ፡ ሙሽራ ።
በመከራ ፡ ቅመም ፡ ባሳር ፡ ተለውሶ :
ዡልዬት፡ ሕይወታችን ፡ መሮን ፡ እንደ ፡ኮሶ
ወጣን ፡ ከዚህ ፡ ዓለም ፡ ያላንድ ፡ ደስታ .
እንግዲህ ፡ እንኑር ፡ እዚህ ፡ በጸጥታ ።
ባለም ፡ ቦታ፡ ጠፍቶ ፡ ለመኖር'ተዋደን ፡
እዚህ ፡ ተገናኘን ፡ ካለም ፡ ላይ ፡ ተሰደን
አይቈጨን እንደዚህ ካለም መውጣታችን
በጣም ፡ ደስ ፡ይበለን ፡ በዛሬው ፡ ዕጣችን
ላለሙ ፡ ደስታ ፡ ለረዥሙም ፡ ዕድሜ ፡
ያው ሞት አይደለም ወይ የሁሉ ፍጻሜ ?
ገላዬን ፡ ከገላሽ ፡ ዐፅምሽን ፡ ካዕፅሜ ፡
ሥጋዬን ፡ ከሥጋሽ ፡ ደምሽን ፡ ከደሜ ፡
ቀላቅሎ ፡ የሚያኖር፡ ከተገኘ ፡ ቦታ ፡
ዡልዬት፡ ከዚህ ፡ ወዲያ ፡ ምን አለ ፡ ደስታ
ይቅር ፡ ደኅና ፡ ይሁን ፡ ዓለም ፡ ከነቂሙ ፤
እዚህ ፡ እኔና፡ አንቺ ፡ እስከ ፡ ዘላለሙ ፡
መቃብር፡ ሆኖልን ፡ የጸጥታ ፡ ገዳም ፡
ከዛሬ ፡ ጀምሮ ፡ እንኑር ፡ በሰላም ።
ከሚወዱት፡ጋራ፡ እንዲህ ፡ ጐን ፡ ለጐን ፡
ምንኛ ፡ መልካም ፡ ነው ፡ ዐፈር ፡ ትቢያ ፡ መሆን ።
(ሮሜዎ ፡ መርዝ ፡ ጠጥቶ ፡ ሞተ ።)
#አባ_ሎራ መብራትና፡ጕጠት፡ ይዞ ፡
ወደ፡መቃብሩ፡ ቦታ፡ መጣ ።
#አባ_ሎራ ።
ስፍራው ፡ አያስኬድም ፡ ሆነና ፡ መቃብር
እያደናቀፈ ፡ ያስቸግራል ፡ ለእግር ፡
አዬ ፡ መከራዬ ፡ በዚሁ ፡ ላይ ፡ ደግሞ ፡
ምንም ፡አይታየኝ ፡ዐይኔ ፡ በጣም ፡ ደክሞ
ማነህ አንተ እዚህ የቆምከው እንደ አጥር ?
#ቤልሻጥር ።
የሚያውቁኝ ፡ወዳጅዎ ፡እኔ፡ ነኝ ቤልሻጥር ።
#አባ_ሎራ ።
እግዚአብሔር ይባርክህ በል ልጄ ንገረኝ ፤
በሩቅ ፡ አላይ ፡ ብሎ ፡ ዐይኔ ፡ አስቸገረኝ፡
እዚያ ፡ በካፑሌ ፡ የመቃብር ፡ ስፍራ ፡
መብራት አይደለም፡ ወይ የማየው ፡ ሲበራ?
#ቤልሻጥር ።
አዎን ፡ ነው ፡ አባቴ ፡ ሄዷል ፡ እዚያ ፡ ቦታ ፡
ወዳጅዎ ፡ ሮሜዎ ፡ የኔ ፡ መልካም ፡ ጌታ
#አባ_ሎራ
ማን ፡ አልከኝ ?
#ቤልሻጥር ።
ሮሜዎ ።
#አባ_ሎራ ።
አዬ ፡ የእግዜር ፡ ቀጣ
ምን ፡ ያኽል ፡ ጊዜ ፡ ነው ፡ እሱ ፡ እዚህ ፡ ከመጣ ?
#ቤልሻጥር ።
ልክ ፡ እኩል ፡ ሰዓት ፡ ነው ።
#አባ_ሎራ ።
ና፡ እንሂድ፡ ወደ ፡ እሱ
#ቤልሻጥር ።
አልችልም ፡ አባቴ ፡ አስጠንቅቆ ፡ ራሱ ፡
ወደ ፡ መቃብሩ፡ እሱ ፡ ወዳለበት ፡
ከቶ ፡ እንዳልጠጋ ፡ ሥራውን ፡ ለማየት ፡
ከልክሎኛልና ፡ በሞት ፡ አስፈራርቶ ፤
ትእዛዙን ፡ ለመጣስ ፡ እኔ ፡አልችልም ፡ ከቶ
#አባ_ሎራ ፡
በል ፡ ተወው፡ ልጄ ፡ ሆይ፡ ሠግቷልና፡ ልቤ
እስቲ ፡ ልመልከተው ፡ ብቻዬን፡ቀርቤ።(አባ፡ሎራሄደ)
#ቤልሻጥር ፡ (ብቻውን ) ።
ዛፍ ፡ ተደገፍኩና ፡ እንቅልፍ ወስዶኝ ፡ ኖሮ
በሕልማ፡ ሮሜዎ ፡ አድርጎ ፡ አምባጓሮ ፡
ውጊያ፡ገጠሙና ፡ የኔ ፡ ጌታ ፡ ሲጥል ፡
አየሁ፡ ደግሞ ፡ ዛሬ ፡ ሌላ ፡ ሰው ፡ ሲገድል
#አባ_ሎራ ፡(ብቻውን) ።
ይህ ፡ ደም ፡ ከየት ፡ መጣ ? ይህ ሻምላ ፡ ምንድነው?
እዚህ ፡ የወደቀ ፡ ባለቤት ፡ የሌለው ።
(ዡሊዬት ነቃች ፤ አባ ፡ ሎራ፡ ጥግ ፡ ይዞ ፡ ቆመ) ።
#ዡልዬት ።
ሮሜዎ ፍቅሬ ሆይ ማን አምጥቶ ጣለህ ?
ይኸ ፡ ደም ምንድነው ? ፓሪስ ፡ ማ፡ገደለህ ?
ጨርሰው ፡ አይሰሙም ፡ ሞተዋል ፡ እነሱ
ትንፋሽም ፡ የላቸው ፡ አይንቀሳቀሱ ፡
የእንቅልፍ ፡ የመኝታ ፡ የዕረፍት ፡ የጸጥታ :
መሆኑ ፡ ቀረና ፡ ሰላማዊ ፡ ቦታ ፤
ከእንቅልፌ ፡ ስነቃ ፡ አወይ ፡ መቃብሬ ፡
የጦር ፡
👍1
ሜዳ ፡ ሆኖ ፡ ጠብቆኛል ፡ ዛሬ ።
ሮሜዮ፡ ምን ፡ ነካው ? ፓሪስን ማ መታው ?
ይህን ፡ እንቆቅልሽ ፡ማነው ፡ የሚፈታው ?
#ኣባ_ሎራ ።
ይኸውልሽ ፡ ልጄ ፡ እግዜር ፡ አልፈቀደም
እንዳሰብኩት ፡ ሆኖ ፡ ነገሩ ፡ አልሄደም ።
ኣሁንም ፡ ቶሎ ፡ በይ ፡ ውጪ ከዚህ ፡ ቦታ
ሰዎች ፡ መጡ ፡ ከደጅ ይሰማል ፡ ጫጫታ
እንድትገቢ ፡ አድርጌ አንቺን ካንድ ገዳም
እዚያ ፡ ትኖሪያለሽ ፡ ልጄ ፡ ሆይ ፡ በሰላም ፡
እባክሽ ቶሎ በይ፡ ሰዎች ወዲህ መጡ፡
#ዡልዬት ።
ከዚህ ፡ እኔ ፡ አልሄድም ፡ እርስዎ ፡ ፈጥነው፡ይውጡ።
(ዡልዬት ፡ ብቻዋን ፡ )፣ ( አባ ' ሎራ' ሄደ)
ደግሞ ፡ ይህ ፡ ኩባያ ፡ እዚህ ፡ ምን ፡ አመጣው ?
ምን ፡ ይሆን ሮሜዎ አግኝቶ የጠጣው ?
አሁን ፡ ገና ፡ ገባኝ ፡ ዐይኔ ፡ ተከፈተ ፤
መርዝ ፡ ጠጥቶ ፡ ነው ፡ ሮሜዎ ፡ የሞተ ።
ጥንቱን ፡ ተፈጥሬ ፡ ለዬዬ ፡ ለለቅሶ ፡
እንዴት ፡ ያለው ፡ ሐዘን ፡ ቈየኝ ፡ ተደግሶ :
እኔ ፡ እሱን ፡ ስጠብቅ ፡ እዚህ ፡ ተቀብሬ ፡
በድን ፡ ሆኜ ፡ ሬሳ ፡ቆየሁ ፡ እስከ ፡ ዛሬ ፡
ወይ ፡ አለ ፡ መታደል ፡ መፈጠር፡ ላበሳ ፤
ይኸ ፡ ሁሉ ፡ ድካም ፡ይህ ሁሉ ፡ ግሥገሣ
ለማየት ፡ ኖሯል ፡ ወይ ወድቆ ያንተ ሬሳ፤
ለካ ፡ መልካም ፡ ኖሯል ፡ ብቀር ፡ ሳልነሣ ።
ወደ፡እሱ፡ብመጣ ፡ እኔ አድርጌው ዘመድ፡
እሱስ ቀድሞኝ ሄዷልባላሰብኩት መንገድ
እንዳልቀየመው ፡ የኔ ፡ ከዳተኛ ፡
መጥቶ ፡ ካጠገቤ ፡ እዩት፡እንደ፡ተኛ ።
አወይ ፡ ሮሜዎ ፡ የኔ ፡ ሆደ ፡ ባሻ ፡
አንተ፡ እኔን ፡ ስትፈልግ እኔም አንተን ፡ ስሻ
ብቻህን ፡ ሄደሃል ፡ ሰው ፡ ቀርቶኛል ፡ ሳትል
የጭንቅ ፡ ወዳጅህን ፡ እኔን ፡ ሳታስከትል ፡
አልቀርም ፡ ጠብቀኝ ፡ ባለህበት ፡ ቦታ ፤
ኩባያህ ፡ ባዶ ፡ ነው ፡ የለውም ፡ ጠብታ ፡
አንተ ፡ ቢስ ፡ ሥሥታም ፡ ንፉግ ፡ መኰንኔ
ጨልጠህ ፡ ጠጣኸው ፡ ሳታስተርፍ ፡ ለኔ
ቆየኝ ፡ ደረስኩብህ ፡ በርሬ፡ እንደ ፡ አሞራ፤
ይኸው ፡መምጣቴ ነው ፡ እኔም ካንተ፡ ጋራ
አልሠራህበትም ፡ አንተ ፡ ባለቤቱ ፡
እስቲ ፡ ልታቀፈው ፡ ይግባ ፡ በስለቱ ፡
አንጀቴ ፡ ለጩቤህ ፡ ይሁነው ፡ አፎቱ ።
(በሮሜዎ ፡ ልቤ ፡ ሆዷን ' ወግታ ፡ ሞተች)
#የመጀመሪያ_ዘበኛ ።
በልምራን ወዴት ነው መንገዱና ስፍራው ?
#የፓሪስ_አሽከር ።
ይኸው እዚህ ነበር መብራት ፡ የሚበራው
#የመጀመሪያ_ዘበኛ ።
ምድሩ ፡ ደም ፡ ብቻ፡ነው፡ምድነው፡ ነገሩ?
እስቲ ፡ ቶሎ ፡ ግቡ ፡ ወደ ፡ መቃብሩ፡
ትልቁ ፡ መኰንን ፡ ፓሪስ ፡ ይኸው ፡ ሞቶ ፡
ቀርቷል ፡ በመሬት ፡ ላይ ፡እዚህ ፡ ተዘርግቶ
ከሁለት ፡ ቀን ፡ በፊት ፡ የቀበሯት፡ ሞታ ፡
ዝልዬትም ፡ ወድቃለች በጨቤ ፡ ተወግታ፡
እዩ ፡ ተመልከቱ ፡ በደም ፡ ተለውሳ ፤
አልብሶት ፡ የለም ፡ ወይ ፡ ሜዳውን 'ሬሳ ።
ደግሞስ ፡ ሮሜዎ ፡እዚህ ፡ምን አመጣው፤
እሱም ደግሞ ሞቷል ትንፋሽም አይወጣው ።
ቶሎ ፡ ንገሯቸው ፡ መስፍኑ፡ይጠሩ፤
ደግሞም ፡ ግማሻችሁ ፡ ስፍራውን ፡ መርምሩ ፡
ይጠሩ፡ እነ ፡ ሞንታግ ፡ ይምጡ ፡ እነ ፡ ካፑሌ ፤
ፍተሻ ፡ይደረግ ፡ በዚሁ ፡ ቀበሌ ፡
ምስክር ፡ ተገኝቶ ፡ታሪኩ ፡ እስቲሰማ ፡
የተሰወረ፡ ነው፡ ምስጢሩ ፡ ጨለማ ።
💫ይቀጥላል💫
ሮሜዮ፡ ምን ፡ ነካው ? ፓሪስን ማ መታው ?
ይህን ፡ እንቆቅልሽ ፡ማነው ፡ የሚፈታው ?
#ኣባ_ሎራ ።
ይኸውልሽ ፡ ልጄ ፡ እግዜር ፡ አልፈቀደም
እንዳሰብኩት ፡ ሆኖ ፡ ነገሩ ፡ አልሄደም ።
ኣሁንም ፡ ቶሎ ፡ በይ ፡ ውጪ ከዚህ ፡ ቦታ
ሰዎች ፡ መጡ ፡ ከደጅ ይሰማል ፡ ጫጫታ
እንድትገቢ ፡ አድርጌ አንቺን ካንድ ገዳም
እዚያ ፡ ትኖሪያለሽ ፡ ልጄ ፡ ሆይ ፡ በሰላም ፡
እባክሽ ቶሎ በይ፡ ሰዎች ወዲህ መጡ፡
#ዡልዬት ።
ከዚህ ፡ እኔ ፡ አልሄድም ፡ እርስዎ ፡ ፈጥነው፡ይውጡ።
(ዡልዬት ፡ ብቻዋን ፡ )፣ ( አባ ' ሎራ' ሄደ)
ደግሞ ፡ ይህ ፡ ኩባያ ፡ እዚህ ፡ ምን ፡ አመጣው ?
ምን ፡ ይሆን ሮሜዎ አግኝቶ የጠጣው ?
አሁን ፡ ገና ፡ ገባኝ ፡ ዐይኔ ፡ ተከፈተ ፤
መርዝ ፡ ጠጥቶ ፡ ነው ፡ ሮሜዎ ፡ የሞተ ።
ጥንቱን ፡ ተፈጥሬ ፡ ለዬዬ ፡ ለለቅሶ ፡
እንዴት ፡ ያለው ፡ ሐዘን ፡ ቈየኝ ፡ ተደግሶ :
እኔ ፡ እሱን ፡ ስጠብቅ ፡ እዚህ ፡ ተቀብሬ ፡
በድን ፡ ሆኜ ፡ ሬሳ ፡ቆየሁ ፡ እስከ ፡ ዛሬ ፡
ወይ ፡ አለ ፡ መታደል ፡ መፈጠር፡ ላበሳ ፤
ይኸ ፡ ሁሉ ፡ ድካም ፡ይህ ሁሉ ፡ ግሥገሣ
ለማየት ፡ ኖሯል ፡ ወይ ወድቆ ያንተ ሬሳ፤
ለካ ፡ መልካም ፡ ኖሯል ፡ ብቀር ፡ ሳልነሣ ።
ወደ፡እሱ፡ብመጣ ፡ እኔ አድርጌው ዘመድ፡
እሱስ ቀድሞኝ ሄዷልባላሰብኩት መንገድ
እንዳልቀየመው ፡ የኔ ፡ ከዳተኛ ፡
መጥቶ ፡ ካጠገቤ ፡ እዩት፡እንደ፡ተኛ ።
አወይ ፡ ሮሜዎ ፡ የኔ ፡ ሆደ ፡ ባሻ ፡
አንተ፡ እኔን ፡ ስትፈልግ እኔም አንተን ፡ ስሻ
ብቻህን ፡ ሄደሃል ፡ ሰው ፡ ቀርቶኛል ፡ ሳትል
የጭንቅ ፡ ወዳጅህን ፡ እኔን ፡ ሳታስከትል ፡
አልቀርም ፡ ጠብቀኝ ፡ ባለህበት ፡ ቦታ ፤
ኩባያህ ፡ ባዶ ፡ ነው ፡ የለውም ፡ ጠብታ ፡
አንተ ፡ ቢስ ፡ ሥሥታም ፡ ንፉግ ፡ መኰንኔ
ጨልጠህ ፡ ጠጣኸው ፡ ሳታስተርፍ ፡ ለኔ
ቆየኝ ፡ ደረስኩብህ ፡ በርሬ፡ እንደ ፡ አሞራ፤
ይኸው ፡መምጣቴ ነው ፡ እኔም ካንተ፡ ጋራ
አልሠራህበትም ፡ አንተ ፡ ባለቤቱ ፡
እስቲ ፡ ልታቀፈው ፡ ይግባ ፡ በስለቱ ፡
አንጀቴ ፡ ለጩቤህ ፡ ይሁነው ፡ አፎቱ ።
(በሮሜዎ ፡ ልቤ ፡ ሆዷን ' ወግታ ፡ ሞተች)
#የመጀመሪያ_ዘበኛ ።
በልምራን ወዴት ነው መንገዱና ስፍራው ?
#የፓሪስ_አሽከር ።
ይኸው እዚህ ነበር መብራት ፡ የሚበራው
#የመጀመሪያ_ዘበኛ ።
ምድሩ ፡ ደም ፡ ብቻ፡ነው፡ምድነው፡ ነገሩ?
እስቲ ፡ ቶሎ ፡ ግቡ ፡ ወደ ፡ መቃብሩ፡
ትልቁ ፡ መኰንን ፡ ፓሪስ ፡ ይኸው ፡ ሞቶ ፡
ቀርቷል ፡ በመሬት ፡ ላይ ፡እዚህ ፡ ተዘርግቶ
ከሁለት ፡ ቀን ፡ በፊት ፡ የቀበሯት፡ ሞታ ፡
ዝልዬትም ፡ ወድቃለች በጨቤ ፡ ተወግታ፡
እዩ ፡ ተመልከቱ ፡ በደም ፡ ተለውሳ ፤
አልብሶት ፡ የለም ፡ ወይ ፡ ሜዳውን 'ሬሳ ።
ደግሞስ ፡ ሮሜዎ ፡እዚህ ፡ምን አመጣው፤
እሱም ደግሞ ሞቷል ትንፋሽም አይወጣው ።
ቶሎ ፡ ንገሯቸው ፡ መስፍኑ፡ይጠሩ፤
ደግሞም ፡ ግማሻችሁ ፡ ስፍራውን ፡ መርምሩ ፡
ይጠሩ፡ እነ ፡ ሞንታግ ፡ ይምጡ ፡ እነ ፡ ካፑሌ ፤
ፍተሻ ፡ይደረግ ፡ በዚሁ ፡ ቀበሌ ፡
ምስክር ፡ ተገኝቶ ፡ታሪኩ ፡ እስቲሰማ ፡
የተሰወረ፡ ነው፡ ምስጢሩ ፡ ጨለማ ።
💫ይቀጥላል💫
#ሮሜዎና_ዡልዬት
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት(የመጨረሻ
ክፍል)
#ሁለተኛ_ዘበኛ ።
ይኸው ፡ አገኘነው ፡ የሮሜዎን ፡ አሽከር ።
#የመጀመሪያ_ዘበኛ ።
መስፍኑ ፡ እስቲመጡ፡ እንዳይመረመር ።
(ሦስተኛ ፡ ዘበኛ ፡ ከአባ ' ሎራ፡ጋራ፡ መጣ)
#ሦስተኛ_ዘበኛ ።
እያንቀጠቀጠው ፡ ጥግ ፡ ይዞ ፡ ሲያለቅስ
ይኸውና ፡ ደግሞ ፡ አገኘሁ ፡ አንድ ፡ ቄስ ፡
ለምን ፡ እንደ ፡ ያዘው ፡ አልታወቀም፡ ከቶ ፡
ጕጠቱን ፡ ቀማነው ፡ በእጁ ፡ ላይ ፡ተገኝቶ
#የመጀመሪያ_ዘበኛ ።
መስፍኑ ፡ እስቲመጡ ፡ እሱን ፡ አትልቀቁ ፤
የሚጠረጠር ፡ ነው ፡ ይዛችሁ ፡ ጠብቁ ።
(መስፍኑ ፡ ታጅቦ ፡ መጣ) ።
#መስፍን ።
እኔን ፡ የሚያስጠራ ፡ ሳይነጋ ፡ ሌሊቱ ፤
ምንድነው ፡ንገሩኝ ፡ እስቲ ፡ ምክንያቱ ? ..
(ካፑሌ ' ፤ ሚስቱና ሌሎች ሰዎች መጡ)
#ካፑሌ ።
ምስጢሩ ፡ ምንድነው ፡ የሰዉ ጫጫታ ?
#የካፑሌ_ሚስት ።
እረ ፡ እንዲህ ፡ አይደለም ፡ የሕዝቡ ጋጋታ ፡
ግማሹ ፡ ሮሜዎ ፡ ግማሹ ፡ ዡልዬት ፡
ግማሾቹም ፡ ፓሪስ ፡ እያሉ ፡ በጩኸት ፡
ወደ ፡ እኛ ፡ መቃብር ፡ ገቡ ፡ እየተጋፉ ።
#መስፍን ።
ነገሩን ፡ ንገሩኝ፡ ደግም ፡ ሆነ፡ ክፉ ።
#የመጀመሪያ_ዘበኛ ።
ልዑል ፡ ሆይ ፡ ያስተውሉ'ፓሪስን ፡ተገድሎ
እዩት ፡ ሮሜዎ ፡ መሬት ፡ ላይ ፡ ተንጋሎ ፡
ቀድሞ ፡ የሞተችው ፡ ዡልዬት ፡ ተመልሳ፣
እይዋት ፡ እሷ ፡ ደግሞ ፡ በደም ተለውሳ ።
#መስፍን ።
ይህ ፡ ዐመፅ ፡ እንደ፡ምን ፡ ሆኖ ፡ እንደ ፡ ተሠራ ፍጠኑ ፡ በቶሎ ፡ይደረግ ፡ ምርመራ
#የመጀመሪያ_ዘበኛ ።
የሮሜዎ ፡ ሎሌ ፥ ካንድ ፡ ካህን ፡ ጋራ ፡
እነሆ ፡ ተገኝቷል ፡ አሁን ፡ በዚህ ፡ ስፍራ ።
#ካፑሌ ።
ሚስቴ ፡ ተመልከቺ ፡ ልጃችን ፡ ተኝታ ፥
እዪው ፡ ደሟ ፡ ሲፈስ ሆዷ ላይ ፡ ተወግታ
አስተውዪው ይህ ጩቤ ከመጣበት ፡ ቦታ
ከሞንታግ ልጅ ላይ ነው ተመልከች አፎቱ
ባዶውን ፡ ይታያል ፡ ይግባሽ ፡ ምክንያቱ ።
#የካፑሌ_ሚስት ።
እባክህን ፡ ተወኝ ፡ እኔ ፡ አልችልም ፡ ማየት
ወይ፡ልጄ ፡ ወይ ልጄ ፡ ወይ፡ ልጄ ፡ ዝልዬት
ሐዘን ፡ ጨፈለቀኝ ፡ ውሃ ፡ ሆንኩኝ ፡ እኔ ፤
ይህንን ፡ ትልቅ ፡ ጕድ ፡ ይህንን ፡ ጭካኔ፡
ኣይችልም ፡ አይችልም። ሊመለከት ዐይኔ
(ሞንታግና ፡ ሌሎች ፡ ሰዎች ፡ መጡ) "
#መስፍን ።
ሞንታግ ፡ ወዲህ ፡ ቅረብ ፡ ተመልከተው ፡ አንተ ፡ልጅህን ፡ አስተውለው ፥ እየው ፡ እንደ ፡ ሞተ ።
#ሞንታግ ።
የልጅዋ ፡ መሰደድ ፡ ሆኖባት ፡ በሽታ ፡
ሚስቴ ፡ ሌሊት ፡ ሞተች በሐዘን ተጐድታ
ያሁን ፡ ሐዘኔ ፡ ግን በጣም ፡ ትልቅ መዓት
የባሰ ፡ ጐዳት፡ ነው ፡ የመጣ ፡ ለቅጣት ።
#መስፍን ።
እንባህን ፡ አግደው ፡ አትቸኵል ፡ ለማልቀስ
በፊት ፡ ምርመራውን ፡ ይገባል ፡ መጨረስ
ያመፁን ፡ ምክንያት፡ ምንጩን ፡ እንወቀው
ምርመራው ይጀመር አብረን ፡ እንዝለቀው
የተያዙት ፡ ሰዎች ፡ በፍጥነት ፡ ይቅረቡ ።
#አባ_ሎራ ።
እዚህ ፡ ያላችሁት ፡ አሁን ፡ ስታስቡ ፡
እኔ ፡ መገኘቴ ፡ በዚህ ፡ ዐመፅ ፡ ቦታ ፡
ያስጠረጥረኛል ፡ ገፍቶ ፡ በግዴታ ፡
ዳሩ ፡ ግን ፡ ነገሩን ፡ ልናገረውና ፡
ተረዱት ፡ ዕወቁት ፡ የኔን ፡ ንጽሕና ።
#መስፍን ።
ታሪኩን ፡ እንስማ ፡ በሉ ፡ ይናገሩ ።
#አባ_ሎራ ።
ሐተታ ፡ አላበዛም ፡ ልናገር ፡ ባጭሩ ፤
ረዥም ፡ አይደለም ፡ቀላል፡ ነው ምስጢሩ
መልካሙ ፡ ሮሜዎ ፡ ይህ አሁን ፡ የሞተው ለዡልዬት ፡ባሏ ነው በተክሊል ተጋብተው
ቃል ኪዳን ሞልተዋል ቈርበው እንደ ሕጉ
በሃይማኖት ሥራት ቃል፡ ኪዳን ሲያደርጉ
የተክሊሉን ፡ ሥራት ፡ ባርኮ ፡ የቀደሰው ፡
እኔው ፡ ራሴ ፡ ነኝ፤ አይደለም ፡ ሌላ ፡ ሰው
በዚያው ቀን ቲባልትን ቢገድለው ፡ ተፈርዶ
ከዚህ ፡ አገር ፡ ወጣ ፡ ሮሜዎ ፡ ተሰዶ፡
ዡልዬት ፡ ዘመዶቿ ፡ ይህንን ፡ ሳያውቁ ፡
ለፓሪስ ፡ ሊድሯት ፡ እሷን ፡ ቢያስጨንቁ ፡
በሐዘን ፡ አልቅሳ ፡ ነገረችኝ ፡ መጥታ ፤
ዘዴ ፡ ካልተገኘ ፡ በገዛ ፡ እጅዋ ፡ ሞታ ፡
ልትድን ፡ አሰበች ፡ ካገኛት ፡ ፈተና ፤
እኔም ፡ በዚህ ፡ ነገር ፡ በጣም ፡ አዘንኩና ፡
መድኀኒት ፡ ሰጠኋት ሕይወት ፡ አጠውልጎ
እንቅልፍ ፡ የሚያስተኛ እንደ ሞት ፡ አድርጎ
ከዚያም ፡ ለሮሜዎ ፡ ወረቀት ፡ ጽፌለት ፡
እንዲመጣ ፡አዘዝኩት ገሥግሦ በፍጥነት
ከእንቅልፋ፡ ስትነቃ የመርዙ ኃይል ፡ አልቆ
እንዲወስዳት ፡ ነበረ ውጭ ፡ አገር ፡ ደብቆ
የኔንም ፡ ወረቀት ፡ የወሰደልኝ ፡ ሰው ፡
የኛ ፡ ካህን ፡ ነበር ፤ እሱም ፡ ሳያደርሰው ፡
እክል፡ ስላገኘው ፡ በሄደበት ፡ ቦታ ፡
መልሶ ፡ አመጣልኝ ፡ ትናንትና ፡ ማታ ።
የዡልየት ፡ መነሻ ፡ ሌሊት ፡ ስለ ፡ ነበር ፡
እኔም ፡ በጨለማ ፡ መጣሁ ፡ ስደናበር ፡
አሳቤ ፡ ነበረ ፡ ሮሜዎ ፡እስቲመጣ ፡
ደብቄ ፡ ላቆያት ፡ ከቤት ፡ ሳላስወጣ ፡
ዳሩ፡ግን ፡ ገሥግሼ ፡ እኔ ፡ ከዚህ ፡ ስደርስ
ወድቀው ፡ አየኋቸው ፡ ሮሜዎና፡ ፓሪስ ።
እሷም ፡ ነቃችና ፡ ወዲያው ፡ ስትነሣ ፡
እግዜር ፡ ያመጣውን ፡ ብትቀበል ፡ ታግሣ
የሚሻል ፡ መሆኑን ፡ ላስረዳት ፡ ሞክሬ ፡
ከደጅ ፡ ድምፅ ሰማሁ ሳጥናናት በምክሬ
ለመንኳት ፡ እንድትሄድ ፡ እኔን ፡ ተከትላ ፥
ምክሬን ፡ አልሰማችም ቀረች እንቢ ፡ ብላ
እኔም ፡ የመጣውን ፡ ለማየት ፡ በኋላ ፤
ወጥቼ ፡ መጣሁኝ ፡ ይኸው ፡ እዚህ ፡ ቦታ
ያስረዳ፡ ነበረ ፡ የዡልዬት ፡ ሁኔታ ፡
ሐዘኗ ፡ መሆኑን ፡ በጣም ፡ የበረታ ።
ከዚያ በኋላ ፡ ግን ፡ የሆነውን ፡ ነገር ፡
አላየሁምና ፡ አልችልም ፡ መናገር ፡
ዡልዬት ፡ ሮሜዎን በተክሊል ፡ ማግባቷን
ታውቀዋለችና ፡ ጠይቁ ፡ ሞግዚቷን ፡
እንግዴህ ፡ ልቀጣ ፡ ቃሌ ፡ ቢገኝበት ፡
በውስጡ ፡ የገባ ፡ ሐሰትና፡ ውሸት
#መስፍን ።
ጻድቅ ፡ሰው ኣድርገን ፡እርስዎን ከማክበር
አቋርጠን ፡ አናውቅም የሮሜዎን ፡ አሽከር
በፍጥነት ፡ አቅርቡት ፡ ያየውን ፡ ይናገር ።
#ቤልሻጥር ።
የዡልዬትን ፡ መሞት ፡ ጌታዬ ፡ ብነግረው ፡
መርዶውን ፡ ሲሰማ ፡ ሐዘን ፡ አሰከረው ፡
ወዲያው ፡ ተነሣና ፡ እየገሠገሠ ፡
ሌሊት ፡ እዚህ ፡ ቦታ ፡ ከኔ ፡ ጋር ፡ ደረሰ ።
ይህንን ፡ ደብዳቤ ፡ ላባቴ ፡ ስጥ ፡ ብሎ ፡
እኔን ፡ እንዳልገባ ፡ በብርቱ ፡ ከልክሎ ፡
ትእዛዙን ፡ ባልፈጽም ፡ በሞት ፡ አስፈራርቶ
አየሁት ፡ ሲገባ ፡ እኔን ፡ እዚህ ፡ ትቶ ።
#መስፍን ።
ደብዳቤውን ፡ ስጠኝ እስቲ ፡ ልመልከተው
የፓሪስም ፡ አሽከር ፡ ይጠራ ወዴት ፡ ነው ?
(የፓሪስ • አሽከር ፡ ቀረበ) ።
ሌሊት ፡ በጨለማ ፡ ደግሞ ፡ ያንተ ፡ ጌታ ፡
እዚህ ፡ ለምን ፡ መጣ ፡ እመቃብር ፡ ቦታ ?
#የፓሪስ_አሽከር ።
አበባ ፡ ሊያስቀምጥ ፡ እመቃብሯ ፡ ላይ ፡
መጣና ፡ እኔንም ፡ እዚሁ ፡ ሁኜ ፡ እንዳይ ፡
አዞኝ ፡ እንድጠብቅ ፡ እዚህ ፡ እንድቀመጥ
ሰው ፡የመጣ እንደሆን ምልክት እንድሰጥ
ስጠብቅ አንድ፡ ሰው፡ መብራት ይዞ መጣ
አፍጨሁ ፡ ጌታዬም ፡ ከመቃብር ፡ ወጣ ።
ሁለቱ ፡ ሲዋጉ ፡ ይኸው ፡ እዚህ ፡ ስፍራ ፡
ቶሎ ፡ ሮጬ ፡ ወጣሁ ፡ ዘበኛ ፡ ልጠራ ።
#መስፍን ።
አምነን ፡ ለመቀበል ፡ እኛ ፡ የቄሱን ፡ ቃል ፡
ተመልክቼዋለሁ ፥ ደብዳቤው ፡ ይበቃል ።
የፍቅራቸው ፡ ነገር ፡ የዡልዬትም ፡ መሞት
ይኸው ፡ ይነበባል ፡ በደብዳቤው ፡ ጽፎት
ሁሉንም ፡ ገልጦታል ፤ ከዡልዬትም ፡ ጋራ
ለመሞት መምጣቱን ይኸው እዚህ ስፍራ
መድኀኒት የሚሸጥ ድኻ ሰው ፡ አግኝቶ
መርዝ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት(የመጨረሻ
ክፍል)
#ሁለተኛ_ዘበኛ ።
ይኸው ፡ አገኘነው ፡ የሮሜዎን ፡ አሽከር ።
#የመጀመሪያ_ዘበኛ ።
መስፍኑ ፡ እስቲመጡ፡ እንዳይመረመር ።
(ሦስተኛ ፡ ዘበኛ ፡ ከአባ ' ሎራ፡ጋራ፡ መጣ)
#ሦስተኛ_ዘበኛ ።
እያንቀጠቀጠው ፡ ጥግ ፡ ይዞ ፡ ሲያለቅስ
ይኸውና ፡ ደግሞ ፡ አገኘሁ ፡ አንድ ፡ ቄስ ፡
ለምን ፡ እንደ ፡ ያዘው ፡ አልታወቀም፡ ከቶ ፡
ጕጠቱን ፡ ቀማነው ፡ በእጁ ፡ ላይ ፡ተገኝቶ
#የመጀመሪያ_ዘበኛ ።
መስፍኑ ፡ እስቲመጡ ፡ እሱን ፡ አትልቀቁ ፤
የሚጠረጠር ፡ ነው ፡ ይዛችሁ ፡ ጠብቁ ።
(መስፍኑ ፡ ታጅቦ ፡ መጣ) ።
#መስፍን ።
እኔን ፡ የሚያስጠራ ፡ ሳይነጋ ፡ ሌሊቱ ፤
ምንድነው ፡ንገሩኝ ፡ እስቲ ፡ ምክንያቱ ? ..
(ካፑሌ ' ፤ ሚስቱና ሌሎች ሰዎች መጡ)
#ካፑሌ ።
ምስጢሩ ፡ ምንድነው ፡ የሰዉ ጫጫታ ?
#የካፑሌ_ሚስት ።
እረ ፡ እንዲህ ፡ አይደለም ፡ የሕዝቡ ጋጋታ ፡
ግማሹ ፡ ሮሜዎ ፡ ግማሹ ፡ ዡልዬት ፡
ግማሾቹም ፡ ፓሪስ ፡ እያሉ ፡ በጩኸት ፡
ወደ ፡ እኛ ፡ መቃብር ፡ ገቡ ፡ እየተጋፉ ።
#መስፍን ።
ነገሩን ፡ ንገሩኝ፡ ደግም ፡ ሆነ፡ ክፉ ።
#የመጀመሪያ_ዘበኛ ።
ልዑል ፡ ሆይ ፡ ያስተውሉ'ፓሪስን ፡ተገድሎ
እዩት ፡ ሮሜዎ ፡ መሬት ፡ ላይ ፡ ተንጋሎ ፡
ቀድሞ ፡ የሞተችው ፡ ዡልዬት ፡ ተመልሳ፣
እይዋት ፡ እሷ ፡ ደግሞ ፡ በደም ተለውሳ ።
#መስፍን ።
ይህ ፡ ዐመፅ ፡ እንደ፡ምን ፡ ሆኖ ፡ እንደ ፡ ተሠራ ፍጠኑ ፡ በቶሎ ፡ይደረግ ፡ ምርመራ
#የመጀመሪያ_ዘበኛ ።
የሮሜዎ ፡ ሎሌ ፥ ካንድ ፡ ካህን ፡ ጋራ ፡
እነሆ ፡ ተገኝቷል ፡ አሁን ፡ በዚህ ፡ ስፍራ ።
#ካፑሌ ።
ሚስቴ ፡ ተመልከቺ ፡ ልጃችን ፡ ተኝታ ፥
እዪው ፡ ደሟ ፡ ሲፈስ ሆዷ ላይ ፡ ተወግታ
አስተውዪው ይህ ጩቤ ከመጣበት ፡ ቦታ
ከሞንታግ ልጅ ላይ ነው ተመልከች አፎቱ
ባዶውን ፡ ይታያል ፡ ይግባሽ ፡ ምክንያቱ ።
#የካፑሌ_ሚስት ።
እባክህን ፡ ተወኝ ፡ እኔ ፡ አልችልም ፡ ማየት
ወይ፡ልጄ ፡ ወይ ልጄ ፡ ወይ፡ ልጄ ፡ ዝልዬት
ሐዘን ፡ ጨፈለቀኝ ፡ ውሃ ፡ ሆንኩኝ ፡ እኔ ፤
ይህንን ፡ ትልቅ ፡ ጕድ ፡ ይህንን ፡ ጭካኔ፡
ኣይችልም ፡ አይችልም። ሊመለከት ዐይኔ
(ሞንታግና ፡ ሌሎች ፡ ሰዎች ፡ መጡ) "
#መስፍን ።
ሞንታግ ፡ ወዲህ ፡ ቅረብ ፡ ተመልከተው ፡ አንተ ፡ልጅህን ፡ አስተውለው ፥ እየው ፡ እንደ ፡ ሞተ ።
#ሞንታግ ።
የልጅዋ ፡ መሰደድ ፡ ሆኖባት ፡ በሽታ ፡
ሚስቴ ፡ ሌሊት ፡ ሞተች በሐዘን ተጐድታ
ያሁን ፡ ሐዘኔ ፡ ግን በጣም ፡ ትልቅ መዓት
የባሰ ፡ ጐዳት፡ ነው ፡ የመጣ ፡ ለቅጣት ።
#መስፍን ።
እንባህን ፡ አግደው ፡ አትቸኵል ፡ ለማልቀስ
በፊት ፡ ምርመራውን ፡ ይገባል ፡ መጨረስ
ያመፁን ፡ ምክንያት፡ ምንጩን ፡ እንወቀው
ምርመራው ይጀመር አብረን ፡ እንዝለቀው
የተያዙት ፡ ሰዎች ፡ በፍጥነት ፡ ይቅረቡ ።
#አባ_ሎራ ።
እዚህ ፡ ያላችሁት ፡ አሁን ፡ ስታስቡ ፡
እኔ ፡ መገኘቴ ፡ በዚህ ፡ ዐመፅ ፡ ቦታ ፡
ያስጠረጥረኛል ፡ ገፍቶ ፡ በግዴታ ፡
ዳሩ ፡ ግን ፡ ነገሩን ፡ ልናገረውና ፡
ተረዱት ፡ ዕወቁት ፡ የኔን ፡ ንጽሕና ።
#መስፍን ።
ታሪኩን ፡ እንስማ ፡ በሉ ፡ ይናገሩ ።
#አባ_ሎራ ።
ሐተታ ፡ አላበዛም ፡ ልናገር ፡ ባጭሩ ፤
ረዥም ፡ አይደለም ፡ቀላል፡ ነው ምስጢሩ
መልካሙ ፡ ሮሜዎ ፡ ይህ አሁን ፡ የሞተው ለዡልዬት ፡ባሏ ነው በተክሊል ተጋብተው
ቃል ኪዳን ሞልተዋል ቈርበው እንደ ሕጉ
በሃይማኖት ሥራት ቃል፡ ኪዳን ሲያደርጉ
የተክሊሉን ፡ ሥራት ፡ ባርኮ ፡ የቀደሰው ፡
እኔው ፡ ራሴ ፡ ነኝ፤ አይደለም ፡ ሌላ ፡ ሰው
በዚያው ቀን ቲባልትን ቢገድለው ፡ ተፈርዶ
ከዚህ ፡ አገር ፡ ወጣ ፡ ሮሜዎ ፡ ተሰዶ፡
ዡልዬት ፡ ዘመዶቿ ፡ ይህንን ፡ ሳያውቁ ፡
ለፓሪስ ፡ ሊድሯት ፡ እሷን ፡ ቢያስጨንቁ ፡
በሐዘን ፡ አልቅሳ ፡ ነገረችኝ ፡ መጥታ ፤
ዘዴ ፡ ካልተገኘ ፡ በገዛ ፡ እጅዋ ፡ ሞታ ፡
ልትድን ፡ አሰበች ፡ ካገኛት ፡ ፈተና ፤
እኔም ፡ በዚህ ፡ ነገር ፡ በጣም ፡ አዘንኩና ፡
መድኀኒት ፡ ሰጠኋት ሕይወት ፡ አጠውልጎ
እንቅልፍ ፡ የሚያስተኛ እንደ ሞት ፡ አድርጎ
ከዚያም ፡ ለሮሜዎ ፡ ወረቀት ፡ ጽፌለት ፡
እንዲመጣ ፡አዘዝኩት ገሥግሦ በፍጥነት
ከእንቅልፋ፡ ስትነቃ የመርዙ ኃይል ፡ አልቆ
እንዲወስዳት ፡ ነበረ ውጭ ፡ አገር ፡ ደብቆ
የኔንም ፡ ወረቀት ፡ የወሰደልኝ ፡ ሰው ፡
የኛ ፡ ካህን ፡ ነበር ፤ እሱም ፡ ሳያደርሰው ፡
እክል፡ ስላገኘው ፡ በሄደበት ፡ ቦታ ፡
መልሶ ፡ አመጣልኝ ፡ ትናንትና ፡ ማታ ።
የዡልየት ፡ መነሻ ፡ ሌሊት ፡ ስለ ፡ ነበር ፡
እኔም ፡ በጨለማ ፡ መጣሁ ፡ ስደናበር ፡
አሳቤ ፡ ነበረ ፡ ሮሜዎ ፡እስቲመጣ ፡
ደብቄ ፡ ላቆያት ፡ ከቤት ፡ ሳላስወጣ ፡
ዳሩ፡ግን ፡ ገሥግሼ ፡ እኔ ፡ ከዚህ ፡ ስደርስ
ወድቀው ፡ አየኋቸው ፡ ሮሜዎና፡ ፓሪስ ።
እሷም ፡ ነቃችና ፡ ወዲያው ፡ ስትነሣ ፡
እግዜር ፡ ያመጣውን ፡ ብትቀበል ፡ ታግሣ
የሚሻል ፡ መሆኑን ፡ ላስረዳት ፡ ሞክሬ ፡
ከደጅ ፡ ድምፅ ሰማሁ ሳጥናናት በምክሬ
ለመንኳት ፡ እንድትሄድ ፡ እኔን ፡ ተከትላ ፥
ምክሬን ፡ አልሰማችም ቀረች እንቢ ፡ ብላ
እኔም ፡ የመጣውን ፡ ለማየት ፡ በኋላ ፤
ወጥቼ ፡ መጣሁኝ ፡ ይኸው ፡ እዚህ ፡ ቦታ
ያስረዳ፡ ነበረ ፡ የዡልዬት ፡ ሁኔታ ፡
ሐዘኗ ፡ መሆኑን ፡ በጣም ፡ የበረታ ።
ከዚያ በኋላ ፡ ግን ፡ የሆነውን ፡ ነገር ፡
አላየሁምና ፡ አልችልም ፡ መናገር ፡
ዡልዬት ፡ ሮሜዎን በተክሊል ፡ ማግባቷን
ታውቀዋለችና ፡ ጠይቁ ፡ ሞግዚቷን ፡
እንግዴህ ፡ ልቀጣ ፡ ቃሌ ፡ ቢገኝበት ፡
በውስጡ ፡ የገባ ፡ ሐሰትና፡ ውሸት
#መስፍን ።
ጻድቅ ፡ሰው ኣድርገን ፡እርስዎን ከማክበር
አቋርጠን ፡ አናውቅም የሮሜዎን ፡ አሽከር
በፍጥነት ፡ አቅርቡት ፡ ያየውን ፡ ይናገር ።
#ቤልሻጥር ።
የዡልዬትን ፡ መሞት ፡ ጌታዬ ፡ ብነግረው ፡
መርዶውን ፡ ሲሰማ ፡ ሐዘን ፡ አሰከረው ፡
ወዲያው ፡ ተነሣና ፡ እየገሠገሠ ፡
ሌሊት ፡ እዚህ ፡ ቦታ ፡ ከኔ ፡ ጋር ፡ ደረሰ ።
ይህንን ፡ ደብዳቤ ፡ ላባቴ ፡ ስጥ ፡ ብሎ ፡
እኔን ፡ እንዳልገባ ፡ በብርቱ ፡ ከልክሎ ፡
ትእዛዙን ፡ ባልፈጽም ፡ በሞት ፡ አስፈራርቶ
አየሁት ፡ ሲገባ ፡ እኔን ፡ እዚህ ፡ ትቶ ።
#መስፍን ።
ደብዳቤውን ፡ ስጠኝ እስቲ ፡ ልመልከተው
የፓሪስም ፡ አሽከር ፡ ይጠራ ወዴት ፡ ነው ?
(የፓሪስ • አሽከር ፡ ቀረበ) ።
ሌሊት ፡ በጨለማ ፡ ደግሞ ፡ ያንተ ፡ ጌታ ፡
እዚህ ፡ ለምን ፡ መጣ ፡ እመቃብር ፡ ቦታ ?
#የፓሪስ_አሽከር ።
አበባ ፡ ሊያስቀምጥ ፡ እመቃብሯ ፡ ላይ ፡
መጣና ፡ እኔንም ፡ እዚሁ ፡ ሁኜ ፡ እንዳይ ፡
አዞኝ ፡ እንድጠብቅ ፡ እዚህ ፡ እንድቀመጥ
ሰው ፡የመጣ እንደሆን ምልክት እንድሰጥ
ስጠብቅ አንድ፡ ሰው፡ መብራት ይዞ መጣ
አፍጨሁ ፡ ጌታዬም ፡ ከመቃብር ፡ ወጣ ።
ሁለቱ ፡ ሲዋጉ ፡ ይኸው ፡ እዚህ ፡ ስፍራ ፡
ቶሎ ፡ ሮጬ ፡ ወጣሁ ፡ ዘበኛ ፡ ልጠራ ።
#መስፍን ።
አምነን ፡ ለመቀበል ፡ እኛ ፡ የቄሱን ፡ ቃል ፡
ተመልክቼዋለሁ ፥ ደብዳቤው ፡ ይበቃል ።
የፍቅራቸው ፡ ነገር ፡ የዡልዬትም ፡ መሞት
ይኸው ፡ ይነበባል ፡ በደብዳቤው ፡ ጽፎት
ሁሉንም ፡ ገልጦታል ፤ ከዡልዬትም ፡ ጋራ
ለመሞት መምጣቱን ይኸው እዚህ ስፍራ
መድኀኒት የሚሸጥ ድኻ ሰው ፡ አግኝቶ
መርዝ
👎1
፡ ይዞ ፡ እንደ መጣ በገንዘቡ ገዝቶ
ይኸው ፡ ተናግሮታል ፡ የሠራውን ፡ ሥራ ፤
ማስረጃው ፡ በቂ ፡ ነው ፡ ትክክል ፡ የጠራ
ካፑሌና ፡ ሞንታግ ፡ የት ናችሁ? አስተውሉ
የበቀልን ፡ ፍሬ ፡ ዛሬ ፡ ተቀበሉ ፡
እንሆ ፡ ይኸ ፡ ነው ፡ የቂማችሁ ፡ ዋጋ ፤
እዩት ፡ ይህን ፡ መዓት ፡ ይህንን ፡ አደጋ ፡
እግዚአብሔር ፡ አስቦ ፡ እናንተን ፡ ሊቀጣ ፡
እንዴት ፡ ያለ መቅሠፍት በኛ ላይ አመጣ
በኛ ፡ ላይ ፡ እላለሁ ፤ ምክንያቱም ፡ ዛሬ ፡
ይኸው ፡ ሁለተኛ ፡ ዘመዴን ፡ ቀብሬ ፡
እኔም ፡ ከናንተ ፡ ጋር ፡ ተቀጣሁ ፡ አብሬ ።
ዘላለም ፡ ቂመኞች ፡ የማትመከሩ ፡
ደም ፡ ለማፍሰስ ፡ ብቻ ፡ የምትጣጣሩ ፡
ፍቅርን ፡ የጠላችሁ ፡ ሆናችሁ ፡ ስትኖሩ ፡
ትልቅ ፡ ትምህርት ፡ ነው ፡ ብትመለከቱ ፡ .
ዛሬ ፡ ልጆቻችሁ ፡ ለፍቅር ፡ ሲሞቱ ።
ሌላ ፡ ልጅ ፡ የላችሁ ፡ አለነሱ ፡ በቀር ፤
ከዚህ ፡ በላይ ፡ ቅጣት ፡ መቼም ፡ አይፈጠር ።
#ካፑሌ ።
ይህ ፡ የወደቀብኝ ፡ የዛሬው ፡ ቅጣቴ ፡
ከሥጋዬ ፡ ዘልቆ ፡ ተሰማኝ ፡ ላጥንቴ ፡
ለኔ ፡ ሆኖ ፡ ሳለ ፡ የሚገባኝ ፡ ሞቱ ፡
ንጹኋ ፡ የኔ ፡ ልጅ ፡እንደዚህ ፡ በከንቱ ፡
ደሟን ፡ በኔ ፡ ክፋት መሬት ፡ ላይ ፡ አፍስሳ
መሥዋዕት ፡ ሆና ፡ ሞተች ፡ ለክፋቴ ፡ ካሳ
ሞንታግ ወንድሜ ሆይ በል እጅህን ስጠኝ፤
ይብቃን ' እንታረቅ ፡ በፍቅር ፡ ጨብጠኝ ።
(እጅ ፡ ለጅ ፡ ይጨባበጣሉ) ።
ደኅና ፡ አድርገን ከፈልን የኀጢአትን ዋጋ
እየው ሲያንገበግብ የእግዚአብሔር አለንጋ ፡
ክፉዎች ፡ ብንሆንበት እሱም ፡ ክፉ ፡ ሆኖ
ድብን፡ አደረገን ፡ ሳይራራ ፡ ጨክኖ ፡
በውነት ፡ ሆንኩ ዛሬ ፡ ዕርቅን የምሻ ፡ ሰው
በልጄ ፡ ንጹሕ ፡ ደም ፡ መሬት ፡ በፈሰሰው
#ሞንታግ ።
እኔም ፡ ለዡልዬት ፡ ይኸው ፡ በዚህ ፡ ስፍራ
ሐውልት ፡ አቆማለሁ ፡ በወርቅ ፡ የተሠራ :
ዜናዋ ፡ እንደ ፡ ወርቅ ፡ ያማረ ፡ ነውና ፤
ዘለዓለም ፡ እንዲኖር ፡ ስሟ' በቬሮና ፡
ከልብ ፡ ለሆነ ፡ ለእውነተኛ ፡ ፍቅር ፡
ምሳሌ ፡ ይሆናል ፡ አብነት ፡ ምስክር ።
#መስፍኑ ።
ተመልከቱት ፡ ፊቷን ፡ የዛሬ ፡ ጧት ፡ ፀሓይ
ደመና ፡ ለብሳለች ፡ ውበቷ ፡ እንዳይታይ ፤
ሆናለች ፡ ከሰው ፡ ጋር ፡ ሐዘኑን ፡ ተካፋይ ።
በሉ ፡ ሁላችሁም ፡ ሥራችሁን ፡ ሥሩ ፤
ሐዘን ፡ ያለው ፡ ያልቅስ ፡ ሙታን ፡ ይቀብሩ፡
እንደ ፡ ሙታን ፡ ሁሉ ፡ እኛን ፡ በሙቅጣቱ ፡
ነፍሳቸውን ፡ ያድን ፡ እግዜር ፡ በምሕረቱ ፡
መቼም ፡ መቼም ፡ቢሆን ታይቶ ፡ አያውቅና
እንደ ፡ እነዚህ ፡ ልጆች ፡ የሚያሳዝን ፡ ዜና
💫ተፈፀመ💫
ለደራሲው ዊሊያም ሼክስፒር ለትርጉሙ ከበደ ሚካኤል አመሰግናለው።
እንደተለመደው አስተያየታችሁን በ @atronosebot አድርሱን ትላንት በተጠናቀቀው #ህመም_ያዘለ_ፍቅር ላይ የሰጣችሁት አስተያየት ደርሶኛል በጣም ብዙ ነው ለሁሉም መመለስ አዳጋች ሆኖብኛል ግን ለሁላችሁም። እጅግ እጅግ አመሰግናለው 🙏
ይኸው ፡ ተናግሮታል ፡ የሠራውን ፡ ሥራ ፤
ማስረጃው ፡ በቂ ፡ ነው ፡ ትክክል ፡ የጠራ
ካፑሌና ፡ ሞንታግ ፡ የት ናችሁ? አስተውሉ
የበቀልን ፡ ፍሬ ፡ ዛሬ ፡ ተቀበሉ ፡
እንሆ ፡ ይኸ ፡ ነው ፡ የቂማችሁ ፡ ዋጋ ፤
እዩት ፡ ይህን ፡ መዓት ፡ ይህንን ፡ አደጋ ፡
እግዚአብሔር ፡ አስቦ ፡ እናንተን ፡ ሊቀጣ ፡
እንዴት ፡ ያለ መቅሠፍት በኛ ላይ አመጣ
በኛ ፡ ላይ ፡ እላለሁ ፤ ምክንያቱም ፡ ዛሬ ፡
ይኸው ፡ ሁለተኛ ፡ ዘመዴን ፡ ቀብሬ ፡
እኔም ፡ ከናንተ ፡ ጋር ፡ ተቀጣሁ ፡ አብሬ ።
ዘላለም ፡ ቂመኞች ፡ የማትመከሩ ፡
ደም ፡ ለማፍሰስ ፡ ብቻ ፡ የምትጣጣሩ ፡
ፍቅርን ፡ የጠላችሁ ፡ ሆናችሁ ፡ ስትኖሩ ፡
ትልቅ ፡ ትምህርት ፡ ነው ፡ ብትመለከቱ ፡ .
ዛሬ ፡ ልጆቻችሁ ፡ ለፍቅር ፡ ሲሞቱ ።
ሌላ ፡ ልጅ ፡ የላችሁ ፡ አለነሱ ፡ በቀር ፤
ከዚህ ፡ በላይ ፡ ቅጣት ፡ መቼም ፡ አይፈጠር ።
#ካፑሌ ።
ይህ ፡ የወደቀብኝ ፡ የዛሬው ፡ ቅጣቴ ፡
ከሥጋዬ ፡ ዘልቆ ፡ ተሰማኝ ፡ ላጥንቴ ፡
ለኔ ፡ ሆኖ ፡ ሳለ ፡ የሚገባኝ ፡ ሞቱ ፡
ንጹኋ ፡ የኔ ፡ ልጅ ፡እንደዚህ ፡ በከንቱ ፡
ደሟን ፡ በኔ ፡ ክፋት መሬት ፡ ላይ ፡ አፍስሳ
መሥዋዕት ፡ ሆና ፡ ሞተች ፡ ለክፋቴ ፡ ካሳ
ሞንታግ ወንድሜ ሆይ በል እጅህን ስጠኝ፤
ይብቃን ' እንታረቅ ፡ በፍቅር ፡ ጨብጠኝ ።
(እጅ ፡ ለጅ ፡ ይጨባበጣሉ) ።
ደኅና ፡ አድርገን ከፈልን የኀጢአትን ዋጋ
እየው ሲያንገበግብ የእግዚአብሔር አለንጋ ፡
ክፉዎች ፡ ብንሆንበት እሱም ፡ ክፉ ፡ ሆኖ
ድብን፡ አደረገን ፡ ሳይራራ ፡ ጨክኖ ፡
በውነት ፡ ሆንኩ ዛሬ ፡ ዕርቅን የምሻ ፡ ሰው
በልጄ ፡ ንጹሕ ፡ ደም ፡ መሬት ፡ በፈሰሰው
#ሞንታግ ።
እኔም ፡ ለዡልዬት ፡ ይኸው ፡ በዚህ ፡ ስፍራ
ሐውልት ፡ አቆማለሁ ፡ በወርቅ ፡ የተሠራ :
ዜናዋ ፡ እንደ ፡ ወርቅ ፡ ያማረ ፡ ነውና ፤
ዘለዓለም ፡ እንዲኖር ፡ ስሟ' በቬሮና ፡
ከልብ ፡ ለሆነ ፡ ለእውነተኛ ፡ ፍቅር ፡
ምሳሌ ፡ ይሆናል ፡ አብነት ፡ ምስክር ።
#መስፍኑ ።
ተመልከቱት ፡ ፊቷን ፡ የዛሬ ፡ ጧት ፡ ፀሓይ
ደመና ፡ ለብሳለች ፡ ውበቷ ፡ እንዳይታይ ፤
ሆናለች ፡ ከሰው ፡ ጋር ፡ ሐዘኑን ፡ ተካፋይ ።
በሉ ፡ ሁላችሁም ፡ ሥራችሁን ፡ ሥሩ ፤
ሐዘን ፡ ያለው ፡ ያልቅስ ፡ ሙታን ፡ ይቀብሩ፡
እንደ ፡ ሙታን ፡ ሁሉ ፡ እኛን ፡ በሙቅጣቱ ፡
ነፍሳቸውን ፡ ያድን ፡ እግዜር ፡ በምሕረቱ ፡
መቼም ፡ መቼም ፡ቢሆን ታይቶ ፡ አያውቅና
እንደ ፡ እነዚህ ፡ ልጆች ፡ የሚያሳዝን ፡ ዜና
💫ተፈፀመ💫
ለደራሲው ዊሊያም ሼክስፒር ለትርጉሙ ከበደ ሚካኤል አመሰግናለው።
እንደተለመደው አስተያየታችሁን በ @atronosebot አድርሱን ትላንት በተጠናቀቀው #ህመም_ያዘለ_ፍቅር ላይ የሰጣችሁት አስተያየት ደርሶኛል በጣም ብዙ ነው ለሁሉም መመለስ አዳጋች ሆኖብኛል ግን ለሁላችሁም። እጅግ እጅግ አመሰግናለው 🙏
#ልጩህበት !
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ስራዬን በጀመርኩ በ ሀያኛው ቀን ላይ እንደተለመደው እራቴን በልቼ ቡናዬን ጠጥቼ ከምሽቱ 3:15 ላይ ወደ ስራ ወጣሁ እስከ ምሽቱ አምስት ሰአት ድረስ ሲዝናኑ ካመሹት መሀል ከፊሉን ከመጠጥ ቤት ወደ ቤታቸው ከፊሉን ከመጠጥ ቤት አልጋ ወደያዙበት ሌላ ሆቴል ከፊሉን ከመጠጥ ቤት ወደ ሌላ መጠጥ ቤት ሳገላብጥ ቆየሁ።
ከምሽቱ 5:10 አከባቢ አንድ
ቀን ቀን ሆቴል ሆኖ ማታ ማታ ቅልጥ ወዳለ ጭፈራ ቤት ወደ ሚቀየር ሆት-ጭፈራ ቤት ከውስጥ የሚወጣ እና ትራንስፖርት መጠቀም የሚፈልግ ሰው እስኪወጣ ለመጠባበቅ ጠጋ ብዬ እንደቁምኩ አይኔ አንዲት ከራስ ፀጉሯ እስከ እግር ጥፍሯ የሚጣል ነገር የሌላት በዛው ሰአት ሰማይ ላይ እንዳለችው ጨረቃ ደስ የሚል ውበት ያላት ልጅ መግቢያ በሩ በስተቀኝ ብርዱን ለመቋቋም ከጡቶቿ በታች እጆቿን አጠላልፋ በማጣመር ቆማለች።
ሁኔታዋ ሲታይ ግራ ግብት ያላት ትመስላለች እዛው ቆማ አንዴ ቁልቁል አንዴ ሽቅብ ትገላመጣለች ።
እድሜዋ በግምት በ 19 እና በ21 መካከል ቢሆን ነው ይቺን የመሰለች ልጅ በዚህ ሳአት ሊያውም ብቻዋን እንዴት? ትልቁ የውስጤ ጥያቄ ነበር ።
አከባቢው ለኔ አዲስ ባይሆንም ልጅቷ ግን ለአከባቢው እዲስ ሳትሆን አትቀርም ከዚህ በፊት አይቻት አላውቅም ከባጃጄ ወርጄ ምነው ብቸሽን ልበላት አልበላት እያልኩ ከፍርሀቴ ጋር ስነታረክ አንዱ ስልክ ሊያናግር ከውስጥ ወደ ውጪ ወጣና ወድያው ስልኩን አናግሮ እንደጨረሰ አብረን እንግባ ብሎ ልጅቷ ላይ ሙዝዝ አለባት ከዛ በፊት እንደማይተዋወቁ ከሁኔታዋ ተረዳሁ።
ድርቅ ሲልባት ብስጭት ብላ ውዝውዝ ቅንጥስ ብጥስ እያለች ቀጥታ ወደኔ ባጃጅ መጣች ከመድረሷ በፊት ባላየ ፊቴን ወደ ፊት ለፊት አዞርኩ።
ደርሳ " ይቅርታ ወንድም ግቢ ትወስደኛለህ? ኮንትራት "
አለች ዩንቨርስቲ ማለቷ ነው ልጅቷ የዩንቨርስቲ ተማሪ እንደሆነች ለማወቅ ግዜ አላጠፋሁም ዩንቨርስቲው ደግሞ ከከተማው ትንሽ ወጣ ይላል
200 ብር ትከፍያለሽ አልኳት
ግማሽ ፊቷ ላይ ዘንፈል ብሎ ጋደም ያለውን ፀጉሯን በቀኝ እጃ ሁለት ጣቶች ወደ ጀርባዋ ብትን አደረገችና
"200 ብር ለተማሪ አይበዛም ወንድሜ ቤተሰብ በወር የሚልክልኝ እኮ 300 ብር ነው !" አለችኝ
መጀመሪያ አሳዘነችኝ !
ቆይቼ ደግሞ ታድያ አርፈሽ ትምህርትሽን አታጠኝም በዚህ ሰአት እዚህ ምን ትሰሪያለሽ ?!ልላት ፈለኩና እሷን እንዲህ ለማለት ምንም አይነት መብት እንደሌለኝ ቶሎ በማስታወሴ ምላሴን ሰበሰብኩ።
"እ ምናልክ " አለችኝ ።
በደንብ ተመለከትኳት። ውስጤ ተላወሰ ።
እሺ ግቢ እንሂድ አልኳት
"በስንት?" አለችኝ
ደስ ያለሽን ትከፍያለሽ ዘላ ገባች ። ትንሽ በዝምታ እንደተጓዝን ድንገት ዘወር አልኩና•••
•••ሂሳብም አስቀንሰሽ ዝምም ብለሽ አያዋጣኝም !
"ኦኬ እእእእእ ግን ይቅርታ በናትህ ከሚከብዱኝ ነገሮች አንዱ ጫወታ ቀድሞ መጀመር ነው" አለች እየተቁነጠነጠች
ምን አይነት ጫወታ ? አልኳት
"ያው ወሬ ነዋ ሌላ ምን አለ?"
ኧረ ብዙ አይነት ጫወታ አለ ተጫውተሽ አታውቂም እንዴ?
"እንዴ ! ክክክክክ እሱማ ብዙ አይነት ጫወታ አለ እኔ ለማለት የፈለኩት ግን ወሬውን ነው"
ሳቋ ልክ እንደ ህፃን ልጅ ሳቅ ደስ የሚል ለዛ አለው ።
ምን አይነት ጫወታ ይቀልሻል? ወይም ትወጃለሽ?
"እቃቃና እኩኩሉ ልበልህ "
ተሳሳቅን ሳቋን ወደድኩት።
ወደ ዩንቨርስቲው እየተቃረብን ነው።
እሺ እኔ ጫወታ በመጀመር ላግዝሻ?
"ከዚህ በላይ እሄው ጀመርከው እኮ! አለችኝ
እኔ ግን ጥያቄ ነበረኝ
የዩንቨርስቲ ተማሪ ሆነሽ በዚህ ሰአት ብቻሽን እዛ ጭፈራ ቤት በር ላይ ለምን ቆምሽ ወይ ገብተሽ አልተዝናናሽ
በረጁሙ ተነፈሰች ቀጠል አርጋም •••
አንድ ነገር ልንገርህ እንኳን ለኮንትራት ለምንም የሚሆን አምስት ሳንቲም ኪሴ ውስጥ የለም የፈለከውን አርገኝ!
ሲጢጢጢጢጥ ባጃጇን ከመቅፅፈት ቀጥ አድርጌ ስዞር ሽምቅቅ ብላለች
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ።
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ስራዬን በጀመርኩ በ ሀያኛው ቀን ላይ እንደተለመደው እራቴን በልቼ ቡናዬን ጠጥቼ ከምሽቱ 3:15 ላይ ወደ ስራ ወጣሁ እስከ ምሽቱ አምስት ሰአት ድረስ ሲዝናኑ ካመሹት መሀል ከፊሉን ከመጠጥ ቤት ወደ ቤታቸው ከፊሉን ከመጠጥ ቤት አልጋ ወደያዙበት ሌላ ሆቴል ከፊሉን ከመጠጥ ቤት ወደ ሌላ መጠጥ ቤት ሳገላብጥ ቆየሁ።
ከምሽቱ 5:10 አከባቢ አንድ
ቀን ቀን ሆቴል ሆኖ ማታ ማታ ቅልጥ ወዳለ ጭፈራ ቤት ወደ ሚቀየር ሆት-ጭፈራ ቤት ከውስጥ የሚወጣ እና ትራንስፖርት መጠቀም የሚፈልግ ሰው እስኪወጣ ለመጠባበቅ ጠጋ ብዬ እንደቁምኩ አይኔ አንዲት ከራስ ፀጉሯ እስከ እግር ጥፍሯ የሚጣል ነገር የሌላት በዛው ሰአት ሰማይ ላይ እንዳለችው ጨረቃ ደስ የሚል ውበት ያላት ልጅ መግቢያ በሩ በስተቀኝ ብርዱን ለመቋቋም ከጡቶቿ በታች እጆቿን አጠላልፋ በማጣመር ቆማለች።
ሁኔታዋ ሲታይ ግራ ግብት ያላት ትመስላለች እዛው ቆማ አንዴ ቁልቁል አንዴ ሽቅብ ትገላመጣለች ።
እድሜዋ በግምት በ 19 እና በ21 መካከል ቢሆን ነው ይቺን የመሰለች ልጅ በዚህ ሳአት ሊያውም ብቻዋን እንዴት? ትልቁ የውስጤ ጥያቄ ነበር ።
አከባቢው ለኔ አዲስ ባይሆንም ልጅቷ ግን ለአከባቢው እዲስ ሳትሆን አትቀርም ከዚህ በፊት አይቻት አላውቅም ከባጃጄ ወርጄ ምነው ብቸሽን ልበላት አልበላት እያልኩ ከፍርሀቴ ጋር ስነታረክ አንዱ ስልክ ሊያናግር ከውስጥ ወደ ውጪ ወጣና ወድያው ስልኩን አናግሮ እንደጨረሰ አብረን እንግባ ብሎ ልጅቷ ላይ ሙዝዝ አለባት ከዛ በፊት እንደማይተዋወቁ ከሁኔታዋ ተረዳሁ።
ድርቅ ሲልባት ብስጭት ብላ ውዝውዝ ቅንጥስ ብጥስ እያለች ቀጥታ ወደኔ ባጃጅ መጣች ከመድረሷ በፊት ባላየ ፊቴን ወደ ፊት ለፊት አዞርኩ።
ደርሳ " ይቅርታ ወንድም ግቢ ትወስደኛለህ? ኮንትራት "
አለች ዩንቨርስቲ ማለቷ ነው ልጅቷ የዩንቨርስቲ ተማሪ እንደሆነች ለማወቅ ግዜ አላጠፋሁም ዩንቨርስቲው ደግሞ ከከተማው ትንሽ ወጣ ይላል
200 ብር ትከፍያለሽ አልኳት
ግማሽ ፊቷ ላይ ዘንፈል ብሎ ጋደም ያለውን ፀጉሯን በቀኝ እጃ ሁለት ጣቶች ወደ ጀርባዋ ብትን አደረገችና
"200 ብር ለተማሪ አይበዛም ወንድሜ ቤተሰብ በወር የሚልክልኝ እኮ 300 ብር ነው !" አለችኝ
መጀመሪያ አሳዘነችኝ !
ቆይቼ ደግሞ ታድያ አርፈሽ ትምህርትሽን አታጠኝም በዚህ ሰአት እዚህ ምን ትሰሪያለሽ ?!ልላት ፈለኩና እሷን እንዲህ ለማለት ምንም አይነት መብት እንደሌለኝ ቶሎ በማስታወሴ ምላሴን ሰበሰብኩ።
"እ ምናልክ " አለችኝ ።
በደንብ ተመለከትኳት። ውስጤ ተላወሰ ።
እሺ ግቢ እንሂድ አልኳት
"በስንት?" አለችኝ
ደስ ያለሽን ትከፍያለሽ ዘላ ገባች ። ትንሽ በዝምታ እንደተጓዝን ድንገት ዘወር አልኩና•••
•••ሂሳብም አስቀንሰሽ ዝምም ብለሽ አያዋጣኝም !
"ኦኬ እእእእእ ግን ይቅርታ በናትህ ከሚከብዱኝ ነገሮች አንዱ ጫወታ ቀድሞ መጀመር ነው" አለች እየተቁነጠነጠች
ምን አይነት ጫወታ ? አልኳት
"ያው ወሬ ነዋ ሌላ ምን አለ?"
ኧረ ብዙ አይነት ጫወታ አለ ተጫውተሽ አታውቂም እንዴ?
"እንዴ ! ክክክክክ እሱማ ብዙ አይነት ጫወታ አለ እኔ ለማለት የፈለኩት ግን ወሬውን ነው"
ሳቋ ልክ እንደ ህፃን ልጅ ሳቅ ደስ የሚል ለዛ አለው ።
ምን አይነት ጫወታ ይቀልሻል? ወይም ትወጃለሽ?
"እቃቃና እኩኩሉ ልበልህ "
ተሳሳቅን ሳቋን ወደድኩት።
ወደ ዩንቨርስቲው እየተቃረብን ነው።
እሺ እኔ ጫወታ በመጀመር ላግዝሻ?
"ከዚህ በላይ እሄው ጀመርከው እኮ! አለችኝ
እኔ ግን ጥያቄ ነበረኝ
የዩንቨርስቲ ተማሪ ሆነሽ በዚህ ሰአት ብቻሽን እዛ ጭፈራ ቤት በር ላይ ለምን ቆምሽ ወይ ገብተሽ አልተዝናናሽ
በረጁሙ ተነፈሰች ቀጠል አርጋም •••
አንድ ነገር ልንገርህ እንኳን ለኮንትራት ለምንም የሚሆን አምስት ሳንቲም ኪሴ ውስጥ የለም የፈለከውን አርገኝ!
ሲጢጢጢጢጥ ባጃጇን ከመቅፅፈት ቀጥ አድርጌ ስዞር ሽምቅቅ ብላለች
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ።
#ልጩህበት !
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
...በረጁሙ ተነፈሰች ቀጠል አርጋም •••
አንድ ነገር ልንገርህ እንኳን ለኮንትራት ለምንም የሚሆን አምስት ሳንቲም ኪሴ ውስጥ የለም የፈለከውን አርገኝ!
ሲጢጢጢጢጥ ባጃጇን ከመቅፅፈት ቀጥ አድርጌ ስዞር ሽምቅቅ ብላለች••
••••
እንደፈራች ገባኝ
እኔ ሽምቅቅ ልበልልሽ አልኩ በሆዴ
ዝም ብዬ ሳያት ሳቋ መጣ ፍርሀት የተቀላቀለበት ሳቅ ሳቀች
የፈለከውን አርገኝ ስትይ?
"በቃ ብዙ ሳናወራና ሳንቀራረብ ልንገርህ ብዬ ነው "
እኮ የፈለከውን አርገኝ ስትይ ምን ለማለት ነው?
"እየተጫናነኩኝ ነበረ እኮ እይታይክም እንዴ በቃ ሲጨንቀኝ ነው እንጂ አንተ ባጃጅ ውስጥ የገባሁት ምንም ብር የለኝም ለዛ እኮ ነው ጨንቆኝ እኮ ነው ዝም ብዬ ግንቡን ተደግፌ ስቆም የነበረው"
ከጥያቄዬ እየሸሸች ስትቀበጣጥር የኔም ሳቅ መጣ ቢሆንም ለሶስተኛ ግዜ ጥያቄዬን ሰነዘርኩ
በዚህ መሀል መልሷን በጉጉት እየጠበኩ
አንድ ሰካራም ለሱ ያቆምኩ መስሎት ነው መሰለኝ ኬት መጣ ሳይባል ግራ ቀኝ እየተጋጨ ከውሃላ ገብቶ አጠገቧ ተቀመጠ።
ድንገት ስለገባ ደንግጣ •••
"እማ"
ብላ እየተጣራች ከነበረችበት መሀል ወደ ጥግ ተጠጋች ከሰውየው ራቅ ለማለት።
እሱም መደንገጧን አይቶ ዘወር አለና ወደሷ •••
በመሀል በመሀል ስቅ እያለው•••
"አይዞሽ የኔ ቆንጆ አስደነገጥኩሽ አደል ይቅርታ አንቺኮ - ሀበሻ ሴት ስለሆንሽ ብቻ በጭለማ ውስጥ ያለሽ የ-የ-የ-የ የብርሀን ጭላንጭል ነሽ አይገርምሽም"
አይገርማትም አሁን ባጃጁን ያቆምኩት ላንተ አይደለምና ውረድ አልኩት ድንገት በንዴት!።
ለኔ ንዴት ቦታም አልሰጠው •••
"ለኔማ ነው ያቆምከው! ለሌላ የቆምክ መስሎህ ነው እንዴ?
እኔን እኮ ነው እዛ ጋር ቆሜ ያየከኝ። ሌላ ሰው ቢኖር ለምን እስካሁን አልመጣም? ይልቅ አንተ ስራህን ስራ ከልጅቷ ጋር ላውራበት" ብሎ ሲመልስልኝ ልጅቷ ሳቋን ለቀቀችው።
ሰካራሙ ሰውዬ አንገቱን ከኔ ላይ መንጭቆ በፍጥነት ወደሷ ዞረና•••
"ምን ምን ምን ምን እስቲ በናትሽ ሳቅሽን ድገሚው የተኮረኮረ ህፃን ልጅ እኮ ነው እምትመስይው !
ወይኔ ልጄ ለምን እንደምጠጣ ታውቂያለሽ የልጄን ናፍቆት ለመርሳት !
ልጅ በልጅነት ሲሉ ሰምቼ ምንም ሳይኖረኝ ወልጄ ፍቅረኛዬ እኔ ላይ ጥላብኝ ስትሄድ እኔ ደግሞ አሮጊቷ እናቴ ላይ ጥየባት መጣሁ።
እናቴ ግን መጣያም ቢኖራት የሚጥል አንጀት የላትም እና እኔን ፍዳዋን በልታ ያሳደገችኝ እንዳይበቃት ላስርፋት ሲገባኝ እረፍት እምትነሳ የአንድ አመት ህፃን ልጅ ጥየባት ከመጣሁ ስድስት አመት ሞላኝ አንዴ ብቻ ነው ልጄን ያየሁዋት!!
ግን ግን በናትሽ ካላስቸገርኩሽ ያሁኑን ሳቅ አንዴ ድገሚልኝ !"
ተበሳጨሁ።
ስማ የሷ ሳቅ ስትጋት ያመሸከው ጠጅ መሰለህ እንዴ እሚደገመው አሁን እምትወርድ ከሆነ በፀባይ ውረድልኝ? አልኩት።
"ጠጅ አልጠጣሁን አረቄ ነው ጠጅ ስጠጣ አይተሀል? ነበርክ? ደሞ ሳቅ እንጂ ሌላ ነገር ድገሚኝ አላልኳት ምን አቃጠለክ ኪኪኪኪ " ብሎ ሳቀና ደሞ ወደሷ ዞሮ
"እኔኮ ተሳፋሪ መስለሽኛል ! ፍቅረኛሽ ነው እንዴ ለካ! በቅናት አንገበገብኩልሻ አንበሳ ነኝ አደል አንበሳ••••" እያለ ሳቁን ቀጠለው።
ትግስቴ አለቀ ጎትቼ ላወርደው ተፈናጥሬ ስወርድ•••
"በናትህ ተው እንዳትጣላ " ብላ ጮከች ልጅቷ እጇን እያውለበለበች እና እንዴ ወደኔ አንዴ ወደሱ እየተመለከተች
"አፌ ቁርጥ ይበልልሽ አንቺ ባትኖሪ ምን ይውጠኝ ነበር
ሆሆሆሆ ሊበላኝ ነው እንዴ?
እውነቴን ነው እድሜ ለሴቶች እንበል እናንተ ባትኖሩ እኮ እኛ ወንዶች እሄን ግዜ እንደ ዳይኖሰር እርስ በርስ ተበላልተን ከምድረገፅ በጠፋን ነበር!
አሁን እራሱ ኮረና ያላጠፋን ለምን እንደሆነ ታውቂያለሽ? አታውቂም?
እንደኔ ከሆነ ኮረና ድምጥማጣችንን ያላጠፋን ኢትዮጲያዊያን ሴቶች ጨዋዎች ስለሆናችሁ ነው
እድሜ ለናንተ!
እውነቴን ነው አሁን እኔ ልሙት እንኳን ማክስ ሱሪስ እምታስወልቁን እናንተው አደላችሁ ።
እናንተ ጨዋ ባትሆኑ ማነው ማክስ አላወልቅም የሚለው እንደ ብራዚል ሴቶች ብትሆኑ ማን ይተርፋል ? አልቆልን ነበር ሙች እውነቴን ነው!
እሱ ይለፈልፋል እሷ ትስቃለች !
ሰውየው የባጥ የቋጡን እየቀባጠረ ደሜን ቢያፈላውም ለምን እንደሆነ ባላውቅም በሱ ንግግር የምትሰቀውን ልጅቷን ማየት ስላስደሰተኝ ነው መሰለኝ ሳላስበው ብዙ ታገስኩት
አሁን ትወርዳለህ አትወርድም አልኩት ወደሱ እየተጠጋሁ
"እራስህ እኮ ነህ አቁመህ የጫንከኝ !"
ላንተ አልቆምኩም አልኩህ እኮ!
"ታድያ ለማን ነው የቆምከው?"
ለሷ!
"ለሷ ካካካ እሷኮ አብራህ ነው የመጣችው••••
እሀሀሀ ልታወርዳት ነበር እንዴ የቆምከው ገባኝ !
ታድያ ምን አጣደፈህ ቀስ ብለህ አትቆምም ብቻሽንማ አትወርጂም ነይ በይ እንውረድ!"
ሲላት•••
ሳላውቀው በንዴት ውስጥ ሆኜ ሳቄ መጣብኝ እንደምንም ላለመሳቅ እየታገልኩ ኮሌታውን ይዤ ጎትቼ ላወርደው ስል•••
"እባክህ ተወው እንደዛ አታድርግ ! ቆይ የት ነው መሄድ እምትፈልገው አንተ ?!" አለችው።
"ብዙ አርቅም እኮ እሄኛው መጠጥ ቤት ስለተዘጋብኝ እቅዴ ደሞ አዳሬን መጠጣት ስለሆነ ቤት ልቀይር ነው እዛች ጋ ያለችው ግሮሰሪ ደሞ ካልታሸገች በስተቀር አትዘጋም ወደዛ ነው እምሄደው " ሲላት
"በናትህ ጣል አርገነው እንለፍ ?" እለችኝ ባይኗ እያባበለች
ምነው በሱ ምክንያት የምታመልጪ መሰለሽ እንዴ እሱን አውርጄው የጀመርነውን እንጨርሳለን እሺ አልኳት ኮስተር ልልባት እየሞከርኩ።
ባጃጁን አስነስቼ ከነፍኩ።
"ምን አርጊ ነው እምትላት እነጨርሳለን እንጫረሳለን እያልክ ታስፈራራለህ እንዴ?" አለ
እስቲ ዝምበል ስለው ጭራሽ ባሰበት•••
"ዝም አልልም እንደውም እሱን ተይው አንቺ ብቻ ፍቀጅልኝ?"
"ምን ?"
"አንዴ ልጩህ በናትሽ ?"
"እንዴ ለምን ምን ሆንክ?" አለችው ግራ ተጋብታ ሰውየው መች ያልቅበትና እኔ በማታ ስራ ብዙ ሰካራም ጭኛለሁ እንደዚህ ሰውዬ ግራ ያጋባኝ ሰው አልገጠመኝም ቀጠለ••
"አንቺ ምን ስትሆኚ ነው እምትጮሂው?"
"ምን አይነት ጩኸት?"
"እሄውልሽ እኔ ደስ ሲለኝም እጮሀለሁ ሲጨንቀኝም እጮሀለሁ በናትሽ አሁን አንዴ ልጩህ ? ፈቀድሽልኝ አለና
በጣም በሚያስፈራ ድምፅ አቀለጠው።
እሷም ደነገጠች እኔም ባጃጁን አቁሜ በደምፍላት ወደሱ ዞርኩና
አንተ ሰውዬ እብድ ነህ እንዴ?ስለው
"የፈለከውን በለኝ ግን በናትህ ልጩህበት ተወኝ ?"
እስቲ ወንድ ነህ ድገመው አልኩት። የጉድ ቀን አይመሽም አሉ ዛሬ የጉድ ለሊት አይነጋም ሆነብኝ እሷ በኔና በሱ ሁኔታ ትስቃለች ሰውየው ቀጠለ
ልጩህበት ተወኝ ተወኝ ልጩህበት
በአፌ ቢወጣ የውስጤ እንፋሎት
ለየልኝ እሄ ሰውዬ አላበዛውም እንዴ ግጥምህንም አንተንም አልፈልግም ውረድልኝ
እቺን ግጥም ሳልጨርስልህማ አልወርድም
ታድያ ልጩህ እንጂ ሌላ ምን እላለሁ
የገዛ ጩኸቴ ለኔ እየተሰማ
ንዴቴን
ብሶቴን
ናፍቆቴን ባከስመው
እኔ እየጮህኩኝ እኔ እራሴ ልስማው!!
••••አለ። ጨረስክ አልኩት ።አፍጦ እያየኝ•••
"አዎ ግጥሜን ጨርሻለሁ ግን አንተም ዝም ብለህ አትጩህ እሺ
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
...በረጁሙ ተነፈሰች ቀጠል አርጋም •••
አንድ ነገር ልንገርህ እንኳን ለኮንትራት ለምንም የሚሆን አምስት ሳንቲም ኪሴ ውስጥ የለም የፈለከውን አርገኝ!
ሲጢጢጢጢጥ ባጃጇን ከመቅፅፈት ቀጥ አድርጌ ስዞር ሽምቅቅ ብላለች••
••••
እንደፈራች ገባኝ
እኔ ሽምቅቅ ልበልልሽ አልኩ በሆዴ
ዝም ብዬ ሳያት ሳቋ መጣ ፍርሀት የተቀላቀለበት ሳቅ ሳቀች
የፈለከውን አርገኝ ስትይ?
"በቃ ብዙ ሳናወራና ሳንቀራረብ ልንገርህ ብዬ ነው "
እኮ የፈለከውን አርገኝ ስትይ ምን ለማለት ነው?
"እየተጫናነኩኝ ነበረ እኮ እይታይክም እንዴ በቃ ሲጨንቀኝ ነው እንጂ አንተ ባጃጅ ውስጥ የገባሁት ምንም ብር የለኝም ለዛ እኮ ነው ጨንቆኝ እኮ ነው ዝም ብዬ ግንቡን ተደግፌ ስቆም የነበረው"
ከጥያቄዬ እየሸሸች ስትቀበጣጥር የኔም ሳቅ መጣ ቢሆንም ለሶስተኛ ግዜ ጥያቄዬን ሰነዘርኩ
በዚህ መሀል መልሷን በጉጉት እየጠበኩ
አንድ ሰካራም ለሱ ያቆምኩ መስሎት ነው መሰለኝ ኬት መጣ ሳይባል ግራ ቀኝ እየተጋጨ ከውሃላ ገብቶ አጠገቧ ተቀመጠ።
ድንገት ስለገባ ደንግጣ •••
"እማ"
ብላ እየተጣራች ከነበረችበት መሀል ወደ ጥግ ተጠጋች ከሰውየው ራቅ ለማለት።
እሱም መደንገጧን አይቶ ዘወር አለና ወደሷ •••
በመሀል በመሀል ስቅ እያለው•••
"አይዞሽ የኔ ቆንጆ አስደነገጥኩሽ አደል ይቅርታ አንቺኮ - ሀበሻ ሴት ስለሆንሽ ብቻ በጭለማ ውስጥ ያለሽ የ-የ-የ-የ የብርሀን ጭላንጭል ነሽ አይገርምሽም"
አይገርማትም አሁን ባጃጁን ያቆምኩት ላንተ አይደለምና ውረድ አልኩት ድንገት በንዴት!።
ለኔ ንዴት ቦታም አልሰጠው •••
"ለኔማ ነው ያቆምከው! ለሌላ የቆምክ መስሎህ ነው እንዴ?
እኔን እኮ ነው እዛ ጋር ቆሜ ያየከኝ። ሌላ ሰው ቢኖር ለምን እስካሁን አልመጣም? ይልቅ አንተ ስራህን ስራ ከልጅቷ ጋር ላውራበት" ብሎ ሲመልስልኝ ልጅቷ ሳቋን ለቀቀችው።
ሰካራሙ ሰውዬ አንገቱን ከኔ ላይ መንጭቆ በፍጥነት ወደሷ ዞረና•••
"ምን ምን ምን ምን እስቲ በናትሽ ሳቅሽን ድገሚው የተኮረኮረ ህፃን ልጅ እኮ ነው እምትመስይው !
ወይኔ ልጄ ለምን እንደምጠጣ ታውቂያለሽ የልጄን ናፍቆት ለመርሳት !
ልጅ በልጅነት ሲሉ ሰምቼ ምንም ሳይኖረኝ ወልጄ ፍቅረኛዬ እኔ ላይ ጥላብኝ ስትሄድ እኔ ደግሞ አሮጊቷ እናቴ ላይ ጥየባት መጣሁ።
እናቴ ግን መጣያም ቢኖራት የሚጥል አንጀት የላትም እና እኔን ፍዳዋን በልታ ያሳደገችኝ እንዳይበቃት ላስርፋት ሲገባኝ እረፍት እምትነሳ የአንድ አመት ህፃን ልጅ ጥየባት ከመጣሁ ስድስት አመት ሞላኝ አንዴ ብቻ ነው ልጄን ያየሁዋት!!
ግን ግን በናትሽ ካላስቸገርኩሽ ያሁኑን ሳቅ አንዴ ድገሚልኝ !"
ተበሳጨሁ።
ስማ የሷ ሳቅ ስትጋት ያመሸከው ጠጅ መሰለህ እንዴ እሚደገመው አሁን እምትወርድ ከሆነ በፀባይ ውረድልኝ? አልኩት።
"ጠጅ አልጠጣሁን አረቄ ነው ጠጅ ስጠጣ አይተሀል? ነበርክ? ደሞ ሳቅ እንጂ ሌላ ነገር ድገሚኝ አላልኳት ምን አቃጠለክ ኪኪኪኪ " ብሎ ሳቀና ደሞ ወደሷ ዞሮ
"እኔኮ ተሳፋሪ መስለሽኛል ! ፍቅረኛሽ ነው እንዴ ለካ! በቅናት አንገበገብኩልሻ አንበሳ ነኝ አደል አንበሳ••••" እያለ ሳቁን ቀጠለው።
ትግስቴ አለቀ ጎትቼ ላወርደው ተፈናጥሬ ስወርድ•••
"በናትህ ተው እንዳትጣላ " ብላ ጮከች ልጅቷ እጇን እያውለበለበች እና እንዴ ወደኔ አንዴ ወደሱ እየተመለከተች
"አፌ ቁርጥ ይበልልሽ አንቺ ባትኖሪ ምን ይውጠኝ ነበር
ሆሆሆሆ ሊበላኝ ነው እንዴ?
እውነቴን ነው እድሜ ለሴቶች እንበል እናንተ ባትኖሩ እኮ እኛ ወንዶች እሄን ግዜ እንደ ዳይኖሰር እርስ በርስ ተበላልተን ከምድረገፅ በጠፋን ነበር!
አሁን እራሱ ኮረና ያላጠፋን ለምን እንደሆነ ታውቂያለሽ? አታውቂም?
እንደኔ ከሆነ ኮረና ድምጥማጣችንን ያላጠፋን ኢትዮጲያዊያን ሴቶች ጨዋዎች ስለሆናችሁ ነው
እድሜ ለናንተ!
እውነቴን ነው አሁን እኔ ልሙት እንኳን ማክስ ሱሪስ እምታስወልቁን እናንተው አደላችሁ ።
እናንተ ጨዋ ባትሆኑ ማነው ማክስ አላወልቅም የሚለው እንደ ብራዚል ሴቶች ብትሆኑ ማን ይተርፋል ? አልቆልን ነበር ሙች እውነቴን ነው!
እሱ ይለፈልፋል እሷ ትስቃለች !
ሰውየው የባጥ የቋጡን እየቀባጠረ ደሜን ቢያፈላውም ለምን እንደሆነ ባላውቅም በሱ ንግግር የምትሰቀውን ልጅቷን ማየት ስላስደሰተኝ ነው መሰለኝ ሳላስበው ብዙ ታገስኩት
አሁን ትወርዳለህ አትወርድም አልኩት ወደሱ እየተጠጋሁ
"እራስህ እኮ ነህ አቁመህ የጫንከኝ !"
ላንተ አልቆምኩም አልኩህ እኮ!
"ታድያ ለማን ነው የቆምከው?"
ለሷ!
"ለሷ ካካካ እሷኮ አብራህ ነው የመጣችው••••
እሀሀሀ ልታወርዳት ነበር እንዴ የቆምከው ገባኝ !
ታድያ ምን አጣደፈህ ቀስ ብለህ አትቆምም ብቻሽንማ አትወርጂም ነይ በይ እንውረድ!"
ሲላት•••
ሳላውቀው በንዴት ውስጥ ሆኜ ሳቄ መጣብኝ እንደምንም ላለመሳቅ እየታገልኩ ኮሌታውን ይዤ ጎትቼ ላወርደው ስል•••
"እባክህ ተወው እንደዛ አታድርግ ! ቆይ የት ነው መሄድ እምትፈልገው አንተ ?!" አለችው።
"ብዙ አርቅም እኮ እሄኛው መጠጥ ቤት ስለተዘጋብኝ እቅዴ ደሞ አዳሬን መጠጣት ስለሆነ ቤት ልቀይር ነው እዛች ጋ ያለችው ግሮሰሪ ደሞ ካልታሸገች በስተቀር አትዘጋም ወደዛ ነው እምሄደው " ሲላት
"በናትህ ጣል አርገነው እንለፍ ?" እለችኝ ባይኗ እያባበለች
ምነው በሱ ምክንያት የምታመልጪ መሰለሽ እንዴ እሱን አውርጄው የጀመርነውን እንጨርሳለን እሺ አልኳት ኮስተር ልልባት እየሞከርኩ።
ባጃጁን አስነስቼ ከነፍኩ።
"ምን አርጊ ነው እምትላት እነጨርሳለን እንጫረሳለን እያልክ ታስፈራራለህ እንዴ?" አለ
እስቲ ዝምበል ስለው ጭራሽ ባሰበት•••
"ዝም አልልም እንደውም እሱን ተይው አንቺ ብቻ ፍቀጅልኝ?"
"ምን ?"
"አንዴ ልጩህ በናትሽ ?"
"እንዴ ለምን ምን ሆንክ?" አለችው ግራ ተጋብታ ሰውየው መች ያልቅበትና እኔ በማታ ስራ ብዙ ሰካራም ጭኛለሁ እንደዚህ ሰውዬ ግራ ያጋባኝ ሰው አልገጠመኝም ቀጠለ••
"አንቺ ምን ስትሆኚ ነው እምትጮሂው?"
"ምን አይነት ጩኸት?"
"እሄውልሽ እኔ ደስ ሲለኝም እጮሀለሁ ሲጨንቀኝም እጮሀለሁ በናትሽ አሁን አንዴ ልጩህ ? ፈቀድሽልኝ አለና
በጣም በሚያስፈራ ድምፅ አቀለጠው።
እሷም ደነገጠች እኔም ባጃጁን አቁሜ በደምፍላት ወደሱ ዞርኩና
አንተ ሰውዬ እብድ ነህ እንዴ?ስለው
"የፈለከውን በለኝ ግን በናትህ ልጩህበት ተወኝ ?"
እስቲ ወንድ ነህ ድገመው አልኩት። የጉድ ቀን አይመሽም አሉ ዛሬ የጉድ ለሊት አይነጋም ሆነብኝ እሷ በኔና በሱ ሁኔታ ትስቃለች ሰውየው ቀጠለ
ልጩህበት ተወኝ ተወኝ ልጩህበት
በአፌ ቢወጣ የውስጤ እንፋሎት
ለየልኝ እሄ ሰውዬ አላበዛውም እንዴ ግጥምህንም አንተንም አልፈልግም ውረድልኝ
እቺን ግጥም ሳልጨርስልህማ አልወርድም
ታድያ ልጩህ እንጂ ሌላ ምን እላለሁ
የገዛ ጩኸቴ ለኔ እየተሰማ
ንዴቴን
ብሶቴን
ናፍቆቴን ባከስመው
እኔ እየጮህኩኝ እኔ እራሴ ልስማው!!
••••አለ። ጨረስክ አልኩት ።አፍጦ እያየኝ•••
"አዎ ግጥሜን ጨርሻለሁ ግን አንተም ዝም ብለህ አትጩህ እሺ
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍2❤1
#የብይ_ጨዋታን_የምትወክል_ሀገር
ሃገር ገደል ስትሆን ብይ ናቸው ልጆች
ጉድጓድ የሚገቡ
ለጉድጓድ ሚቀርቡ፣ተጥለው በእጆት፡፡
እመለከታለሁ!
እንደ ብይ ጉድጓድ ፣ ተስሎ ሀገሩ
እጆች ይታዩኛል
ትውልድ ወደ ገደል ፥ የሚገፈትሩ።
እመለከታለሁ!
ብዙ ብይ ህይወቶች፧ ጉድጓዱን ሲስቱ
ብዙ ብይ ህይወቶች ፥ ጉድጓድ ሲከተቱ
እመለከታለሁ!
ከጉድጓድ የወጡት ፥ የቀረባቸውን እየፈነከቱ
ደግሞ እታዘባለሁ!
በብዮች ሀገር ላይ ፥ የብዮችን ጥፋት
ከጉድጓድ ሲወጡ
የገፋውን ሳይሆን
አብሮ ተገፊውን ፥ እንደገና መግፋት
ከክፋት ሚወርሱት ፥ ሌላ አይነት ክፋት!
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
ሃገር ገደል ስትሆን ብይ ናቸው ልጆች
ጉድጓድ የሚገቡ
ለጉድጓድ ሚቀርቡ፣ተጥለው በእጆት፡፡
እመለከታለሁ!
እንደ ብይ ጉድጓድ ፣ ተስሎ ሀገሩ
እጆች ይታዩኛል
ትውልድ ወደ ገደል ፥ የሚገፈትሩ።
እመለከታለሁ!
ብዙ ብይ ህይወቶች፧ ጉድጓዱን ሲስቱ
ብዙ ብይ ህይወቶች ፥ ጉድጓድ ሲከተቱ
እመለከታለሁ!
ከጉድጓድ የወጡት ፥ የቀረባቸውን እየፈነከቱ
ደግሞ እታዘባለሁ!
በብዮች ሀገር ላይ ፥ የብዮችን ጥፋት
ከጉድጓድ ሲወጡ
የገፋውን ሳይሆን
አብሮ ተገፊውን ፥ እንደገና መግፋት
ከክፋት ሚወርሱት ፥ ሌላ አይነት ክፋት!
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
👍1
#ዐይቶ_መጠራጠር
ሳያዩ የሚያምኑን ፥ አይተህ ተጠራጠር
ተእምር አየሁ" አትበል !
ጋንን ያህል ነገር ፥ ሲደገፍ በጠጠር
ይልቅ ተአምር ሥራ
ከሚታይ መልስ ላይ ፧ ጥያቄ በመፍጠር።
ሁሉንም አትመን ፥ ግን ሁሉን ተጠንቀቅ
“ቤትህ በሰማይ ነው”
ብሎ ለሚሰብክህ ፥ ምድርህን አትልቀቅ።
ከስጋ ፍላጎት
አርቀህ ስቀለው፥ የነፍስያህን ልክ
የቄስን ቃል ስትሰማ ፣ ቄሱን ግን አታምልክ።
ሁሉ ካህን ላይሆን
ሁሉን ፍቱኝ እያልክ ፥ ነፍስህን አታክስር
ስንቱ በካህን ለምድ
እባብ ይደብቃል በጠመጠመው ስር።
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
ሳያዩ የሚያምኑን ፥ አይተህ ተጠራጠር
ተእምር አየሁ" አትበል !
ጋንን ያህል ነገር ፥ ሲደገፍ በጠጠር
ይልቅ ተአምር ሥራ
ከሚታይ መልስ ላይ ፧ ጥያቄ በመፍጠር።
ሁሉንም አትመን ፥ ግን ሁሉን ተጠንቀቅ
“ቤትህ በሰማይ ነው”
ብሎ ለሚሰብክህ ፥ ምድርህን አትልቀቅ።
ከስጋ ፍላጎት
አርቀህ ስቀለው፥ የነፍስያህን ልክ
የቄስን ቃል ስትሰማ ፣ ቄሱን ግን አታምልክ።
ሁሉ ካህን ላይሆን
ሁሉን ፍቱኝ እያልክ ፥ ነፍስህን አታክስር
ስንቱ በካህን ለምድ
እባብ ይደብቃል በጠመጠመው ስር።
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
❤1👍1
#ልጩህበት !!
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ታድያ ልጩህ እንጂ ሌላ ምን እላለሁ
የገዛ ጩኸቴ ለኔ እየተሰማ
ንዴቴን
ብሶቴን
ናፍቆቴን ባከስመው
እኔ እየጮህኩኝ እኔ እራሴ ልስማው!!
••••አለ። ጨረስክ አልኩት ።አፍጦ እያየኝ•••
"አዎ ግጥሜን ጨርሻለሁ ግን አንተም ዝም ብለህ አትጩህ እሺ •••
እኔ ከባጃጅህ አልወረድኩ አንተ ግን ከገባሁ ጀምሮ ዝም ብለህ ትጮሀለህ ስማኝ የት እና መቼ እንደምትጮህ ካላወክ ዝም ብትል ይሻላል
ያለበለዚያ ሰሚ ሳይኖር ዝም ብለህ ብትጮህ የራስህ ጩኸት እራስህን ያደነቁርህ እንደሆን እንጂ ምንም አታመጣም !"
ብሎኝ ሲያበቃ ደሞ ወድያው ወደሷ ዞረና
"አንድ ግዜ ብቻ ልጩህ በናትሽ ?"
ሲላት ቀርታኝ የነበረችው እንጥፍጣፊ ትግስት ተሟጠጠች •••
አቦ ባባ ክብር ካልወደደልህ እንዴት እንደምትወርድ ላሳይሀ እንግዲህ ብዬ እጄን ለፀብ እያሰናዳሁ ወርጄ ስጠጋው
"ተው ተው ተው ቦክስ አታባክን ወጣቱ መጀመሪያውኑ እንደዚህ ወንድ ብትሆን ኖሮ አንተ ባጃጅ ውስጥ እስካሁን ማን ይቀመጥ ነበር ፈሪ ፈሪ ነገር ነህ !"
እያለ ከባጃጇ ሲወርድ ልጅቷ በሳቅ ፈነደቀች
ግራ ቀኝ እየተወዛወዘ ትንሽ ከባጃጇ ራቅ እንዳለ ዘወር አለና
"ሞት ይርሳኝ ቻው እሺ የኔ ልጅ ልጅ አልኩ እንዴ አንቺን እንኳን አላደርስም !
ቻው እሺ የኔ ልእልት አንቺን የመሰለች ልጅ ከዚህ አስቀያሚ ሹፌር ጋር በማየቴ ደንግጫለሁ !
ፍችው በናትሽ! " እላት።
"እሺ "አለችው በሳቋ መሀል
"ግን መች ትፈችዋለሽ በናትሽ! እ••• እ ••እ ንገሪኛ?" እያለ ሊመለስ ሲል እኔም እየሳኩ ወደሱ ስጠጋ ፊቱን አዙሮ ከቆምንበት በስተቀኝ መንገድ ዳር ወዳለችው የማትዘጋዋ መጠጥ ቤት አመራ።
ባጃጃን አስነስቼ ከዩንቨርስቲው በቅርብ ርቀት
ጨለማ ውስጥ አቆምኳትና ከመሪው ላይ ተነስቼ እሷ አጠገብ ተቀመጥኩ ። ፊቷ ተቀያየረ።
ካቆምንበት እንቀጥላ አልኳትና
ቅድም የፈለከውን አርገኝ ስትይ ምን ለማለት ፈልገሽ ነበር ?
"በቃ ከፈለክ ልትሰድበኝም ከፈልክ ልታወርደኝም ትችላለህ ሌላ ምንድን ነው?" አለችኝ የጭንቀቷን
ወደ ዩንቨርስቲው ዞሬ ተመለከትኩ አጠገባችን ነው ግቢው ከሩቅ ይታያል ሳቄ መጣ አብራኝ ሳቀች።
ሀይ ስትደርሺ ነው እንዴ ልታወርደኝ ትችላለህ እምትይው? ስላት•••
ጭንቅላቷን ወደ ግራ ሰበቀችና በዝምታ እጇን እያፍተለተለች አይን አይኔን ታየኝ ጀመር
የሆነ ስሜት ተሰማኝ
ታውቂያለሽ ሁለት ወንድሞች አሉኝ ግን እህት የለኝም ቢሆንም እናት አለኝ የማይሆን ቢሆንም እናትም ባይኖረኝ እራሱ አንቺ ላይ የሚጨክን አንጀት የለኝም
ምንም አልደርግሽምም አልሰድብሽምም አላወርድሽምም እሺ መጀመሪያውኑ ብር እንደሌለሽ ብትነግሪኝና በነፃ እንዳደርስሽ ብትጠይቂኝ ለስራ ብወጣም ከሰአቱ አንፃር ላውሬ ጥዬሽ አልሄድም ነበር ።
እያሰብኩ የነበረው ምናልባት መጥፎ ባህሪ ያለው የባጃጅ ሹፌር አጋጥሟት ቢሆን ኖሮስ እያልኩ ነው።
ግን ምን አጋጥሞሽ ነው ማለቴ
በዚህ ሰአት ብቻሽን እዛ ጭፈራ ቤት በር ላይ ለምን ቆምሽ ?ስለራስሽም ብትነግሪኝ ደስ ይለኛል
"አጋጣሚው ከብዙ ነገሮች ጋር የተያያዘ ነው ኬቱ ጋር ልጀምርልህ?
ከፈለግሽው።
"በናትህ አሁን መሽቷል ሞባይሌን ዶርም ጥዬው ወጥቼ ነው ከፈለክ ስልኬን ያዝና ነገ ወይ በሚመችህ ቀን ደውልልኝ አወራሀለሁ!"
እዚሁ ባጃጅ ውስጥ እናድራታለን እንጂ አልፋታሽም አልኳት ኮስተር ብዬ
" እያስገደድከኝ ነው ማለት ነው አለች እሷም በስሱ ከስተር ብላ
ስትስቅም ስትኮሳተርም የሚያምርባት ሴት እሷን አየሁ።
አሁን ከተለያየን ቡሀላ ልታገኝኝ ፍቃደኛ ሁኚ አትሁኝ እርግጠኛ ስላልሆንኩ አሁኑኑ እንድትነግሪኝ እየለመንኩሽ ነው! ከተጫንኩሽ ይቅር ብትነግሪኝ ግን የመጣሽበትን ሂሳብ እንደከፈልሽ እቆጥረዋለሁ አልኳትና አሁንም እኩል ሳቅን።
"ክትክትክትክት ኧረ ባክህ
እሺ ግን ባጭሩ ነው በደንብ እንድትረዳው ገባ ብዬ ብጀምርልህ ይረዝምብኛል?"
አቦ ንገሪኝኛ አታጓጊኝ!።
" እኔ
እኔ
እኔ ማለት እኔ ደሀ ከሚባል ቤተሰብ ነው የተወለድኩት ።
አባቴ አናፂ ነው እናቴ ደግሞ ሽንኩርት ቲማቲም ምናምን ነው ጉሊት ውስጥ የምትቸረችረው
ሁለቱም ፀሀይ ላይ ውለው ፊታቸው ጠቁሮ ከሚያገኙት ገቢ ውስጥ አብዛኛውን እኔን ከሰፈሬ እና ከትምህርት ቤት ጓደኛቼ እኩል ማድረግ ባይችሉ እንኳን ክፍተቱን በመጠኑ አጥብበው ብዙ ሳይሰማኝ እንዳድግ ለማድረግ አውለውታል።
ሳይለብሱ ያለብሱኛል
ለነሱ ርካሽ የተባለውን ጫማ እየተጫሙ ለኔ ውድና ሁለት ሶስት ቅያሪ ጫማ እንዲኖረኝ ለማድረግ ለነሱ የሚያስፈልጉዋቸውን ሁሉ ወደ ጎን ትተዋል !
ሳይደሰቱ እኔን ለማስደሰት የቻሉትን ሁሉ አድርገዋል!
ቢኮራረፉ እኔ ፊት ይስቃሉ!
ቢያዝኑ እኔ ፊት ደስተኛ ለመምሰል ይሞክራሉ!
በአጠቃላይ ለራሳቸው ሳይኖሩ ለኔ ደክመው ለኔ ኖረው ያስተማሩኝን ቤተሰቦቼን ለማስደሰት የምችለው በትምህርቴ ስጎብዝ ነውና ምንም ነገር ሳያታልለኝ በርትቼ በመማር ወደ ዩንቨርስቲ መግቢያ የሚሆን ውጤት አምጥቼ ባስደሰትኳቸው ማግስት ነበር አባዬ እኔ ወደዚህ ለመምጣት የሚያስፈልገኝን ነገር ለሟሟላት ከበፊቱ በተለየ ሁኔታ ያገኘውን ስራ በሙሉ እየሰራ ገንዘቡን እኔው ጋር ማጠራቀም የጀመረው •••"
አለችና ዝም አለች።
ምነው ቀጥይ እንጂ ስላት
"ስላባዬ ሳወራ ጨነቀኝ !
ትንሽ ዝምታ ተፈጠረ በመሀላችን።
ሲጨንቀኝ ደሞ ምን ትዝ እንዳለኝ ታውቃለህ?"
ምን ትዝ አለሽ ?
አንዴ ልጩህ እሚለው የቅድሙ ሰካራም ።
አንዴ ልጩህ እንዴ?"
ስትለኝ ሁለታችንም ባንድ ግዜ ከነበርንበት ሙድ ወጥተን ከባጃጇ ጣራ በላይ ሳቅን።
በናትሽ ቀጥይልኝ ? አልኳት ሳቄን ስጨርስ። ካሳቁ መልስ ደሞ ባንዴ ፊቷን ቅጭም አርጋ ቀጠለች•••
አባዬ ድካሙና እንቅልፉ ተደራርቦበት ነበር ።
ልመጣ ሁለት ሳምንት ሲቀረኝ •••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ታድያ ልጩህ እንጂ ሌላ ምን እላለሁ
የገዛ ጩኸቴ ለኔ እየተሰማ
ንዴቴን
ብሶቴን
ናፍቆቴን ባከስመው
እኔ እየጮህኩኝ እኔ እራሴ ልስማው!!
••••አለ። ጨረስክ አልኩት ።አፍጦ እያየኝ•••
"አዎ ግጥሜን ጨርሻለሁ ግን አንተም ዝም ብለህ አትጩህ እሺ •••
እኔ ከባጃጅህ አልወረድኩ አንተ ግን ከገባሁ ጀምሮ ዝም ብለህ ትጮሀለህ ስማኝ የት እና መቼ እንደምትጮህ ካላወክ ዝም ብትል ይሻላል
ያለበለዚያ ሰሚ ሳይኖር ዝም ብለህ ብትጮህ የራስህ ጩኸት እራስህን ያደነቁርህ እንደሆን እንጂ ምንም አታመጣም !"
ብሎኝ ሲያበቃ ደሞ ወድያው ወደሷ ዞረና
"አንድ ግዜ ብቻ ልጩህ በናትሽ ?"
ሲላት ቀርታኝ የነበረችው እንጥፍጣፊ ትግስት ተሟጠጠች •••
አቦ ባባ ክብር ካልወደደልህ እንዴት እንደምትወርድ ላሳይሀ እንግዲህ ብዬ እጄን ለፀብ እያሰናዳሁ ወርጄ ስጠጋው
"ተው ተው ተው ቦክስ አታባክን ወጣቱ መጀመሪያውኑ እንደዚህ ወንድ ብትሆን ኖሮ አንተ ባጃጅ ውስጥ እስካሁን ማን ይቀመጥ ነበር ፈሪ ፈሪ ነገር ነህ !"
እያለ ከባጃጇ ሲወርድ ልጅቷ በሳቅ ፈነደቀች
ግራ ቀኝ እየተወዛወዘ ትንሽ ከባጃጇ ራቅ እንዳለ ዘወር አለና
"ሞት ይርሳኝ ቻው እሺ የኔ ልጅ ልጅ አልኩ እንዴ አንቺን እንኳን አላደርስም !
ቻው እሺ የኔ ልእልት አንቺን የመሰለች ልጅ ከዚህ አስቀያሚ ሹፌር ጋር በማየቴ ደንግጫለሁ !
ፍችው በናትሽ! " እላት።
"እሺ "አለችው በሳቋ መሀል
"ግን መች ትፈችዋለሽ በናትሽ! እ••• እ ••እ ንገሪኛ?" እያለ ሊመለስ ሲል እኔም እየሳኩ ወደሱ ስጠጋ ፊቱን አዙሮ ከቆምንበት በስተቀኝ መንገድ ዳር ወዳለችው የማትዘጋዋ መጠጥ ቤት አመራ።
ባጃጃን አስነስቼ ከዩንቨርስቲው በቅርብ ርቀት
ጨለማ ውስጥ አቆምኳትና ከመሪው ላይ ተነስቼ እሷ አጠገብ ተቀመጥኩ ። ፊቷ ተቀያየረ።
ካቆምንበት እንቀጥላ አልኳትና
ቅድም የፈለከውን አርገኝ ስትይ ምን ለማለት ፈልገሽ ነበር ?
"በቃ ከፈለክ ልትሰድበኝም ከፈልክ ልታወርደኝም ትችላለህ ሌላ ምንድን ነው?" አለችኝ የጭንቀቷን
ወደ ዩንቨርስቲው ዞሬ ተመለከትኩ አጠገባችን ነው ግቢው ከሩቅ ይታያል ሳቄ መጣ አብራኝ ሳቀች።
ሀይ ስትደርሺ ነው እንዴ ልታወርደኝ ትችላለህ እምትይው? ስላት•••
ጭንቅላቷን ወደ ግራ ሰበቀችና በዝምታ እጇን እያፍተለተለች አይን አይኔን ታየኝ ጀመር
የሆነ ስሜት ተሰማኝ
ታውቂያለሽ ሁለት ወንድሞች አሉኝ ግን እህት የለኝም ቢሆንም እናት አለኝ የማይሆን ቢሆንም እናትም ባይኖረኝ እራሱ አንቺ ላይ የሚጨክን አንጀት የለኝም
ምንም አልደርግሽምም አልሰድብሽምም አላወርድሽምም እሺ መጀመሪያውኑ ብር እንደሌለሽ ብትነግሪኝና በነፃ እንዳደርስሽ ብትጠይቂኝ ለስራ ብወጣም ከሰአቱ አንፃር ላውሬ ጥዬሽ አልሄድም ነበር ።
እያሰብኩ የነበረው ምናልባት መጥፎ ባህሪ ያለው የባጃጅ ሹፌር አጋጥሟት ቢሆን ኖሮስ እያልኩ ነው።
ግን ምን አጋጥሞሽ ነው ማለቴ
በዚህ ሰአት ብቻሽን እዛ ጭፈራ ቤት በር ላይ ለምን ቆምሽ ?ስለራስሽም ብትነግሪኝ ደስ ይለኛል
"አጋጣሚው ከብዙ ነገሮች ጋር የተያያዘ ነው ኬቱ ጋር ልጀምርልህ?
ከፈለግሽው።
"በናትህ አሁን መሽቷል ሞባይሌን ዶርም ጥዬው ወጥቼ ነው ከፈለክ ስልኬን ያዝና ነገ ወይ በሚመችህ ቀን ደውልልኝ አወራሀለሁ!"
እዚሁ ባጃጅ ውስጥ እናድራታለን እንጂ አልፋታሽም አልኳት ኮስተር ብዬ
" እያስገደድከኝ ነው ማለት ነው አለች እሷም በስሱ ከስተር ብላ
ስትስቅም ስትኮሳተርም የሚያምርባት ሴት እሷን አየሁ።
አሁን ከተለያየን ቡሀላ ልታገኝኝ ፍቃደኛ ሁኚ አትሁኝ እርግጠኛ ስላልሆንኩ አሁኑኑ እንድትነግሪኝ እየለመንኩሽ ነው! ከተጫንኩሽ ይቅር ብትነግሪኝ ግን የመጣሽበትን ሂሳብ እንደከፈልሽ እቆጥረዋለሁ አልኳትና አሁንም እኩል ሳቅን።
"ክትክትክትክት ኧረ ባክህ
እሺ ግን ባጭሩ ነው በደንብ እንድትረዳው ገባ ብዬ ብጀምርልህ ይረዝምብኛል?"
አቦ ንገሪኝኛ አታጓጊኝ!።
" እኔ
እኔ
እኔ ማለት እኔ ደሀ ከሚባል ቤተሰብ ነው የተወለድኩት ።
አባቴ አናፂ ነው እናቴ ደግሞ ሽንኩርት ቲማቲም ምናምን ነው ጉሊት ውስጥ የምትቸረችረው
ሁለቱም ፀሀይ ላይ ውለው ፊታቸው ጠቁሮ ከሚያገኙት ገቢ ውስጥ አብዛኛውን እኔን ከሰፈሬ እና ከትምህርት ቤት ጓደኛቼ እኩል ማድረግ ባይችሉ እንኳን ክፍተቱን በመጠኑ አጥብበው ብዙ ሳይሰማኝ እንዳድግ ለማድረግ አውለውታል።
ሳይለብሱ ያለብሱኛል
ለነሱ ርካሽ የተባለውን ጫማ እየተጫሙ ለኔ ውድና ሁለት ሶስት ቅያሪ ጫማ እንዲኖረኝ ለማድረግ ለነሱ የሚያስፈልጉዋቸውን ሁሉ ወደ ጎን ትተዋል !
ሳይደሰቱ እኔን ለማስደሰት የቻሉትን ሁሉ አድርገዋል!
ቢኮራረፉ እኔ ፊት ይስቃሉ!
ቢያዝኑ እኔ ፊት ደስተኛ ለመምሰል ይሞክራሉ!
በአጠቃላይ ለራሳቸው ሳይኖሩ ለኔ ደክመው ለኔ ኖረው ያስተማሩኝን ቤተሰቦቼን ለማስደሰት የምችለው በትምህርቴ ስጎብዝ ነውና ምንም ነገር ሳያታልለኝ በርትቼ በመማር ወደ ዩንቨርስቲ መግቢያ የሚሆን ውጤት አምጥቼ ባስደሰትኳቸው ማግስት ነበር አባዬ እኔ ወደዚህ ለመምጣት የሚያስፈልገኝን ነገር ለሟሟላት ከበፊቱ በተለየ ሁኔታ ያገኘውን ስራ በሙሉ እየሰራ ገንዘቡን እኔው ጋር ማጠራቀም የጀመረው •••"
አለችና ዝም አለች።
ምነው ቀጥይ እንጂ ስላት
"ስላባዬ ሳወራ ጨነቀኝ !
ትንሽ ዝምታ ተፈጠረ በመሀላችን።
ሲጨንቀኝ ደሞ ምን ትዝ እንዳለኝ ታውቃለህ?"
ምን ትዝ አለሽ ?
አንዴ ልጩህ እሚለው የቅድሙ ሰካራም ።
አንዴ ልጩህ እንዴ?"
ስትለኝ ሁለታችንም ባንድ ግዜ ከነበርንበት ሙድ ወጥተን ከባጃጇ ጣራ በላይ ሳቅን።
በናትሽ ቀጥይልኝ ? አልኳት ሳቄን ስጨርስ። ካሳቁ መልስ ደሞ ባንዴ ፊቷን ቅጭም አርጋ ቀጠለች•••
አባዬ ድካሙና እንቅልፉ ተደራርቦበት ነበር ።
ልመጣ ሁለት ሳምንት ሲቀረኝ •••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍2