አትሮኖስ
286K subscribers
120 photos
3 videos
41 files
570 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
መጠየቄ '
እኔስ ፡ የት'ዐውቃለሁ፡ትወደኝ' አትወደኝ
ይህንን • ከድፍረት' ቆጥረህ 'አትፍረደኝ "
ካፌ፡ በመውጣቱ ፡ እንደዚህ ፡ ያለ ፡ ቃል ፡
እንዳትገምተው ፡ ጠባዬን ፡ በቀላል ፥
ከልብህ ፡ እንደሆን ፡ መንፈሴ ፡ ይረጋል ፤
መሠረት ፡ ከሌለው ፡ ፍቅር ፡ ምን ፡ ያደርጋል ።

#ሮሜዎ
እንደ ኣልማዝ እንደ ፡ዕንቍ ውበቷ' በጠራ'
በመስክ ፡ በሸለቆ ፡ በዱር ፡ በተራራ ፡
ብርሃን ፡ በዘረጋች ፡ መሬት ፡ ላይ ፡ ፈንጥቃ ፡
እምልልሻለሁ ፡ በዚች ፡ በጨረቃ ።

#ዝልዬት
ተው ፡ አስብ ፡ ተመልከት ፡ አንድ ፡ ነገር ፡ ፍራ ፤
ፍቅርህ ፡ ተለዋዋጭ ፡ እንዳይሆን ፡ አደራ
በጨረቃ ' አትማል ፡ በዚች ፡ ወረተኛ፤
ሁሉ ፡ ቀን ፡ አትገኝ ፡ ዘወትር ፡ መንገደኛ ፡
ወር፡አይሞላምና ፡ ይህ ፡ የሷ ፡ ግሥገሳ፤
ምን ፡ ጊዜም ፡ ያስታውሰው ፥ ልቡናህ ፡ አይርሳ '
አለች ፡ ስንል ፡ ኰርተን ፡ በብርሃን ፡ ሞገሷ፡
ለጨለማ ፡ ትታን ፡ ትጠፋለች ፡ እሷ ።

#ሮሜዎ

በምን 'ልማልልሽ ንገሪኝ' ዥልዬት !

💫ይቀጥላል💫
#ያልተቋጨ


#ክፍል_አራት


#በክፍለማርያም

...ስተት ብሎ ገባ ህሊና ጥግ ላይ ወሬ እያወራች ነበር ስታየዉ በትንሹ ደንገጥ ብላ አፈጠጠችበት
ትንሳኤ ፊት ለፊቷ ቆሞ እጁን ወደ ኋላ ማረጉን ሲያስተዉል አሁን የመጣሁት ልለምናት እንዳይመስላት አለና እጆቹን አፍታቶ የእስዋ ዴስክን አሰደግፏቸዉ ጎንበስ ብሎ ቆመ
ህሊና ምን ሆኖ ነዉ እያለች በመገረም ታየዋለች

"ምን ሆነሽ ነዉ ግን"
አላት ቆጣ ብሎ

"ምን ሆንኩ"

አለችዉ ለስለስ ባለ ዜማ ባለዉ አነጋገር
ትንሳኤ ለአፍታ የጎዋደኞቿ ግልምጫ የእሷ መደባበቅ የእሱ የፍቅር ጥያቄ አለመሳካት ከጠጣዉ መጠጥ ጋር ተደራርቦ
"የወደድኩሽ መስሎሽ ነዉ እንደዚህ የሚያረግሽ አልወድሽም እሺ አልወድሽም"
ጮክ ብሎ ተናገረ ጉዋደኛዉ እዮብ ደርሶ እንዳይመታት ይሄ እብድ እያለ ይዞት ሊወጣ ሲሞክር
ትንሳኤ አስቸገረ አፉ
"አልወድሽም አልወድሽም "
ይበልእንጂ አሁንም ልቡ ዉስጥ ናት
ህሊና ምን ነካዉ በሚል አስተያየት እያየችዉ ትንሳኤ በጉዋደኛዉ እየተጎተተ ወጣ።
ከዛን ቡሀላ ህሊና ጭራሽ ከአይኑም እየራቀች መጣች
ሁሌ ሲገባ ግን በእሷ ክፍል እያለፈ አንገቱን ሰገግ አርግ በአይኖቹ ሳይፈልጋት ክፍሉ አይገባም
የጉዋደኞቿም አይን አፈር ከመሬት የሚያበላ ነበር
በዛ ሁሉ መሀል ግን ጉዋደኞቹ ሲያስባት እና ሲያስታዉሳት በቀልድ እያሳቁ እያስረሱት በተለይ ጠጥቶ
"አልወድሽም አልወድሽም"
ብሎ የጮሀዉን እያነሱ እሱንም ሲያፅናኑት በአይን ብቻ ጠዋት እና ከትምህርት ቤት ሲለቀቁ ስትወጣ ተደብቆ እያያት አመቱ አልቆ ክረምት ሲገባ በልቡ ብቻ ይዞ እያሰባት ተቀመጠ
በዛን ክረምት ትንሳኤ ብዙ አይነት መፅሀፍቶችን ሲያነብ ከጉዋደኞቹም ጋር ሲያዝግ ከሴቶች ጋር መቀራረብ መነጋገር የመሳሰሉት ፍርሀቶቹ ዘበት ሆነዉ ጠፍተዉ
በሚቀጥለዉ አመት ትምህርት ሲጀምሩ ምላስ አርዝሞ ከትምህርቱ ቀንሶ ሌላ ሰዉ ሆኖ ገባ
ያልተቀየረዉ የህሊና ፍቅር ግን አሁንም ልቡ ዉስጥ ነበር ትምህርት ቤት ውስጥ መጀመርያ ከህሊና ጋር ሲተያዩ በረንዳ ላይ ቆማ ነበር
እንዳያት ደስ አለዉ ፈገግ እያለ ተጠጋትና
"እዚህ ምን ትሰርያለሽ ገብተሽ አትማሪም"
አላት ህሊና አይኖቿን ወደ ላይ አርጋ
"ምን አገባህ"
አለችዉ
"ዋ ስትፎርፊ እንዳላይሽ"
እያለ ቆመዉ ወደሚጠብቁት ጉዋደኞቹ አመራ።
የሆነቀን ምሳ ሰአት ናፍቃዉ ወደሷ ክፍል አመራ
አሁንም ቢሆን ግን ከሌላ ሴት ልጅ ጋር ሲሆን እንደሚያወራዉ ከበፊቱ ፍርሀቱ ቀንሷል እንጂ እሷ ጋር ሲደርስ ቃላት ይጠፉበታል ሲገባ ነጭ ወረቀት ላይ ስዕል እየሳለች አገኛት
"ቆይ እኔ ልሳልልሽ"
እያለ እስራሱን ከእሷ እጅ ተቀበላት ከጎኗ ያሉት ገዋደኞቿ እሷ እርሳሱን ለማስመለስ ስትሞክር እያዩ ይስቃሉ
ትንሳኤ በቆመበት ሳያስበዉ አፍንጫውን ሲነካ የደረቀ ን ጥ ከአፍንጫዉ ወድቆ ወረቀቱ ላይ አረፈ ህሊና
"እእይይይይይ"
እያለች ወረቀቱን አራገፈችዉ።
ትንሳኤ ጀርባዉን ሲያልበዉ ይታወቀዋል
ከአጠገቧ ገፋ አርጓት አይኑን በጨዉ አጥቦ ተቀመጠ።

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
👍1
አትሮኖስ pinned «#ያልተቋጨ ፡ ፡ #ክፍል_አራት ፡ ፡ #በክፍለማርያም ...ስተት ብሎ ገባ ህሊና ጥግ ላይ ወሬ እያወራች ነበር ስታየዉ በትንሹ ደንገጥ ብላ አፈጠጠችበት ትንሳኤ ፊት ለፊቷ ቆሞ እጁን ወደ ኋላ ማረጉን ሲያስተዉል አሁን የመጣሁት ልለምናት እንዳይመስላት አለና እጆቹን አፍታቶ የእስዋ ዴስክን አሰደግፏቸዉ ጎንበስ ብሎ ቆመ ህሊና ምን ሆኖ ነዉ እያለች በመገረም ታየዋለች "ምን ሆነሽ ነዉ ግን" አላት ቆጣ…»
#ሮሜዎና_ዡልዬት

#ክፍል_አራት

#ዡልዬት
ይቅርብኝ 'አትማል በውነትም ፡ በውሸት ፡
ደግሞም ፡ ልማል ፡ ብለህ፡አሳብህ ፡ ከጸና
ምን ጊዜም ፡ ጣዖቴ ፡ ፍቅሬ ፡ አንተ ፡ ነህና
በራስህ ፡ ማልልኝ ፡ የኔ ፡ ሁለንተና ።

#ሮሜዎ
እንግዲያውስ ፡ ስሚ ፡ እኔ ፡ አንቺን ፡ መውደዴ ፡

#ዡልዬት
ይቅር ፡ በቃ ፡ አትማል ፤ ተናወጠ ፡ ሆዴ ፡
ፈጥነህ ፡ ብትምልልኝ ፡ አሁን ፡ ዛሬ ፡ ማታ
ምንም ፡ አይሰማኝ ፡ ለልቤ ፡ ደስታ ፡
እንደዚህ ፡ በድንገት ፡ እንዲህ ፡ በችኰላ ፡
እንደዚህ ፡ በቶሎ ፡ የሆነ ፡ መሓላ ፡
መሠረት ፡ የለውም ፡ ይጠፋል ፡ ባንዳፍታ፤
አላፊ ፡ ነፋስ ፡ ነው ፡ የሰማይ ፡ ብልጭታ
የፍቅሩ፡ ቡቃያ ፡ ከዛሬ ፡ ጀምሮ ፡
ለምልሞ ፡ ይጠንክር ፡ በልባችን ፡ አድሮ ፡
እኛም ፡ እዚያ ፡ ድረስ ፡ሆነን ፡ ትዕግሥተኛ
ወደየቤታችን ፡ ገብተን ፡ እንተኛ ።

#ሮሜዎ
ልትሄጂ ፡ ነወይ ፡ ትተሽኝ ፡ በከንቱ ?

#ዥልየት
ይበቃል ፡ ለዛሬ ፡ መሽብን ፡ ሰዓቱ ።

#ሮሜዎ
ስጭኝ ፡ የሚያጠግብ፡አንድ ፡ ቃል ፡ የበቃ

#ዡልዬት
አንተ ፡ ሳትጠይቅ ፡ በፊት፡ዡልዬት ፡ዐውቃ
ሰጥታህ፡ወስደኸዋል፡የፍቅሯን፡ቃል ኪዳን
የተረፈው ፡ ይደር ፡ ለነገ ፡ እንዲረዳን ።

#ሮሜዎ
መልሰሽ ወስደሺው ፡'መልካሙን ፡ ስጦታ

#ዡልዬት
ቃሌን ፡ እሰጣለሁ ፡ ላንተ ፡ በችሮታ
የልቤ ፡ ደግነት ፡ ባሕር ፡ ነው ፡ ስፋቱ ፤
ፍቅሬም ፡ እንደዚሁ፡ ጥልቅ ፡ ነው ፡ ርቀቱ
መልካም ፡ ጠባዮቼ ፡ እነዚህ ፡ ሁለቱ ፡
ሰፊ ፡ ሀብት ፡ናቸው፡ ከሁሉም ፡ የላቁ ፤
ብሰጥህ ፡ ብሰጥህ ፡ ምን ፡ ጊዜም ፡ አያልቁ ።
(#ሞግዚቷ' #ጠራቻት ) ።
ጠሩኝ ፡ ድምፅ ፡ ሰማሁ ፡ በል ፡ ሄድኩኝ፡ደኅኖ፡እደር።
ሞግዚቴ ፡ እሺ ፡ መጣሁ ፤ ሮሜዎ ፡ አንድ ነገር ፡ አለ ፡ የምነግርህ፡አትሂድ፡ጠብቀኝ ፣ (ወደቤት'ግባች) »

#ሮሜዎ : (ብቻውን) "
የዛሬው ፡ ደስታ ፡ ምንኛ ፡ ደነቀኝ ።
ሕልም ፡ ነው ፡ ራእይ፡ ወይስ ' ደግሞ ቅዠት አልችልም ፡ ይህ ፡ ነገር ፡ ከቶ'ልደርስበት ፤
ፀሓዬ ፡ ጠለቀች ፡ ገባች ፡ ወደ ፡ ቤቷ ።
አሁን ፡ ተመልሳ ፡ ዳግም ፡ በመስኮቷ ፡
ብቅ ፡ እስክትል ፡ ድረስ ፡ ሆነብኝ ፡ ጨለማ ፡
ይኸው ፡ ተመለሰ ፡ የብርሃኗ ፡ ግርማ ።

#ዡልዬት ፡(ተመልሳ • መጣች
ሮሜዎ ፡ ልንገርህ ፡ የመጨረሻ ፡ ቃል ፤
እንደምታፈቅረኝ ፡ ዐወቅሁት ፡ ይበቃል ፡
ዳሩ ፡ ግን ፡ ፍቅራችን ፡ መሠረት ፡ አግኝቶ
በተክሊል ፡ ጋብቻ ፡ እንዲፈጸም ፡ ጸንቶ ፡
ትፈቅድ ፡ እንደ ፡ ሆነ ፡ እልካለሁና ፥
ነገ ፡ ሰው ፡ ወዳንተ ፡ ጒዳዩን ፡ ካጠናህ ፡
ካሰበ ፡ በኋላ ፡ መንፈስህ ፡ መርምሮ ፡
የተክሊሉ ፡ ሰዓት ፡ ይሁን ፡ በቀጠር ።
ወስነህ ፡ ላክብኝ ፤ ከዚያ ፡ በኋላ ፡ ግን ፡
ማመንታት ፡ ሳይኖረው ፡ ልቤ ፡ ሳይገነግን
ችግር ፡ ሳያግደኝ ፡ አደጋና ፡ ሞትም ፡
አንተን ፡ ተከትዬ ፡ እሄዳለሁ ፡ የትም ።
ነገር ግን ፡ ያንተ ፡አሳብ ከሌለው ፡ ንጽሕና
የማይሄድ ፡ ከሆነ ፡ እንደኔ ፡ ኅሊና ፡
አትምጣ፡ ወደኔ ፡ አትድከም ፡ በከንቱ
እንግዴህ ፡ ደኅና ፡ ሁን ፡ አለፈ ፡ ሰዓቱ '
ግባ ፡ ወደ ፡ ቤትህ ፡ ፍጠን ፡ አታመንታ ፤
ሊነጋ ፡ ነውና ፡ ይታያል ፡ ወገግታ ፡
ጨለማ ፡ ለቀቀ ፡ ብርሃን ፡ ተከፈተ ፡
ስንት ፡ ሰዓት ፡ ሲሆን ፡ ሰው ፡ ልላክ ፡ ወዳንተ ?

#ሮሜዎ
ሦስት ፡ ሰዓት ሲሆን መልክተኛሽ ፡ ይምጣ

#ዡልዬት
እንግዴህ ፡ ደኅና ፡ ሁን ፡ ፀሓይ ፡ ሳትወጣ
እንግባ ፡ ቤታችን ። (ሄደች)•

#ሮሜዎ
ዡልዬት ፡ ደኅና ፡ ሁኝ፤
ልቤ ፡ ካንቺ ፡ ጋራ ፡ መቅረቱን ፡ እመኝ ። (ሄዴ) •

#ሮሜዎና #ኣባ_ሎራ ፡ (ባባ ' ሎራ' ቤት)

#ሮሜዎ
እንደምን ፡ አድረዋል፡ አባቴ ፡ አባ ፡ ሎራ ?

#አባ_ሎራ
ከምሥራቅ ፡ ሳይታይ ፡ የፀሓይዋ ፡ ሥራ ፡
ማነህ ፡ በማለዳ ፡ የመጣህ ፡ ከቤቴ ?
በጣፋጩ ፡ ድምፅህ ፡ የምትል ፡ አባቴ ።
እረግ ! አንተ ፡ ነህ ፡ ወይ ፡ሮሜዎ ፡ ጐበዙ
ዐይኔ ፡ ደከመና ፡ አላየም ፡ በብዙ ፡
እንደ ፡ ምን ፡ አድረሃል ፡ የምወድህ ፡ ልጄ
ዐይንህ፡በጣም፡ቀልቷል፡ምን ነካህ ወዳጄ ?
አንድ ፡ ሰው ፡ እንደዚህ ፡ በጧት ፡ የሚነሣ
ነገር ፡ ሲያገኘው ፡ ነው ፡ እንቅልፍ ፡ የሚነሳ ፡
አሳብ ፡ የምንለው ፡ የሰላም ፡ መጋኛ ፡
መንፈሱን ፡ ሰፍሮበት ፡ እንቅልፍ ፡ የማይተኛ ፡
ሽማግሌ ፡ ሰው ፡ ነው ፤ ወጣት ፡ ግን ፡ በውኑ ፡
ከእንግዲህ ፡ ያለ ፡ ነገር ፡ ነጻ ፡ በመሆኑ ፡
ተኝቶ ፡ ያነጋል ፡ እንቅልፉን ፡ በሰላም ፤
ስለዚህ ፡ ይህ ፡ ዐይንህ ፡ በደኅናው ፡ አልቀላም ፡
ሮሜዎ ፡ ምን ፡ ሆኖ ፡ ሳይተኛ ፡ ያደረ ?
አለመተኛቱን ፡ ዐይኑ ፡ መሰከረ ።

#ሮሜዎ
እውነት ፡ ነው ፡ ነገር ፡ ግን ፡አርፌያለሁ ፡ በጣም

#አባ_ሎራ
ብታርፍማ ፡ ኖሮ ፡ በሌሊት ፡ አትመጣም ፡
ንገረኝ ፡ አትደብቅ ፡ ወዴት ፡ ነው ፡ ያደርከው ?

#ሮሜዎ
ድል ፡ አድራጊው : ፍቅሯ ፡ መንፈሴን ፡ ማረከው
አባቴ ፡ እጅዎ ፡ ተክሊሌን ፡ ይባርከው ።

#አባ_ሎራ
ያሰብከውን ፡ ነገር ፡ ንገረኝ ፡ አትፍራ ፤
ከመልካሟ ፡ እጮኛህ ፡ ከሮዛሊን ፡ ጋራ ፡
የተክሊል ፡ ቃል ፡ ኪዳን ፡ ዛሬ ፡ ልትሞላ ፡
የመጣህ ፡ መሰለኝ ፡ ሳስበው ፡ በመላ ።

#ሮሜዎ
ሮዛሊን ፡ ቀርታለች ፡ አያንሷት ፡ አባቴ ፡
ትናንትና ፡ ማታ ፡ ተመታ ፡ ደረቴ ፡
ባዲስ ፡ የፍቅር ፡ ጦር ፡ በሰላ ፡ ጐራዴ ፤
ከመውደዷ ፡ ጋራ ፡ ገጠመ ፡ መውደዴ፡
ስሜታችን ፡ እኩል ፡ ፍቅራችን ፡ የጋራ ፡
ሆኖ ፡ ከተገኘ ፡ አባቴ ፡ አባ ፡ ሎራ ፡
ተክሊሉን ፡ ይሙሉልን ፡ በሥልጣንዎ ፡ ባርከው ፡
እኛ ፡ ቂም ፡ የለንም ፤

#አባ_ሎራ
መንፈሴን ፡ ኣወከው
ምን ፡ አመጣህብኝ ፡ የማላውቀው ፡ ምስጢር ፥
መላ ፡ መትቶ ፡ ያውቃል ፡ ብለህ ፡ አትጠርጥር ፤
አልገባኝምና ፡ ያሁኑ ፡ ንግግር ።
ይህን ፡ እንቆቅልሽ ፡ እንደ ፡ ሾላ ፡ ድፍን ፡
ትተህ ፡ ፡ ግለጥልኝ ፡ ነገሩን ፡ ሳትሸፍን ።

#ሮሜዎ
አባቴ ፡ አልደብቅም ፡ ሁሉንም ፡ ገልጬ ፡
ለርስዎ ፡ ልነግር፡ ነው ፡ የመጣ ፡ ሮጬ፡
የነካፑሌን ፡ ልጅ ዡለየትን ፡ ወድጄ ፤
ራሴ ፡ እስቲጠፋ ፡ በፍቅር አብጄ ፡
እሷም ፡ በጣም ወዳኝ፡አድርገን ፡ መሐላ ፡
ተስማምተን ተዋደን ከቈረጥ ኋላ ፡
አሁን 'የሚቀረን'ተክሊል ፡ የሚሞላ ፡
ካህን ፡ ስለ ፡ ሆነ የሚሰጥ፡ ቡራኬ ፡
ከሷ ጋር ፡ መጥቼ ፈትዎ' ተንበርክኬ ፡
ሞልተው 'ያሰናብቱን የተክሊሉን ፡ ሥርዐት
ሰዓቱን 'ይንገሩኝ መቼ እንደምጠራት ።

#አባ_ሎራ
አይጣል፡ነው፡እናንተ፡ የወጣቶች ፡ ወረት፤
ፍቅራቸው ፡ ቃላቸው ፡ የለውም መሠረት፡
የቀድሞ ፡ እጮኛህ ፡ ሮዛሊን 'ተረስታ፡
ሌላ ፡ ልጅ ፡ አግኝተህ አሁን ትናንት ፡ ማታ
እንዴት ተለወጠ፡ ኣሳብህ ፡ ባንድ ፡ አፍታ፡
በሮዛሊን ፡ ፍቅር ፡ ልብህ ፡ እንዲያ፡ግሎ ፡
ዘላለም ፡ የማይበርድ፡እውነተኛ፡መስሎ ፡
ታጫውተኝ ፡ ነበር አሁን ፡ ይኸውና ፡
ያ ፡ ሁሉ ፡ መውደድህ 'ከመቼው 'ቀረና ፡
መጣህ ' ባዲስ ፡ ፍቅር ፡ ልብህ ፡ ተብረክርኮ ፡
ለምታያት፡ሁሉ፡መንፈስህ ፡ ተማርኮ፡

💫ይቀጥላል💫
👍1
#መስቀልና_እና_ወንበር

“ከሰይጣን እስራት
ነፃ ልትወጡ ነው "
ይለናል አንደኛው ፥ መስቀል ላይ ተሰቅሎ
“ካንባገነን ገዢ
ነፃ ልትወጡ ነው
ይለናል ሌላኛው ፣ ወንበር ላይ ቁጭ ብሎ።
እኛ ህዝቦች ግን...
በወንበዴ መሃል ፥ ለሚሰቀል እውነት
ከወንበዴ መሃል ፥ለሚታጭ ሹመት
ስለሌለን እምነት
“ውረዱልን” እያልን ፥ እንጮኻለን በጣም
እነሱም አይወርዱም
እኛም ሳንገድላቸው ፥ አርነት አንወጣም ።

🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
👍1
#ያልተቋጨ

#ክፍል_አምስት (የመጨረሻ ክፍል)

#በክፍለማርያም

ህሊና
"አይይይይይይይ" እያለች ወረቀቱን አራገፈችዉ ትንሳኤ ጀርባዉን ሲያልበዉ ይታወቀዋል
ከአጠገቧ ገፋ አርጓት አይኑን በጨዉ አጥቦ ተቀመጠ
አንዳንዴ ተዋረድ ካለህ እንደዚህ ነዉ
አጠገቧ ተቀምጦ እጆቹን ወደ ሰደርያዋ ኪስ በቀስታ ሰዶ ከኪሷ ሶፍት አወጣ
አንደኛዋ ጉዋደኛዋ አይታዉ ሳቀች ህሊናም እንደወሰደባት ስታዉቅ ተናዳ አፈጠጠችበት
ትንሳኤም በሶፍቱ አፍንጫዉን እያበሰ በመዋረዱ በልቡ በጣም እያዘነ ሲወጣ በር ላይ ዮናስ ጠበቀዉ

"ባክህ ተዋረድኩልህ"

አለዉ ትንሳኤ በንዴት ከንፈሩን ነክሶ
"ምን ተፈጠረ"
ሲል ዮናስ አፋጠጠዉ
"ደረቅ መሆኑ ጠቅሞኛል ...."
እያለ ትንሳኤ የተፈጠረዉን ነገረዉ ከዛን ቀን ጀምሮ ነገሮች በህሊናና በእሱ መሀል ሴጣን እንዳለ ተገነዘበ እየወደዳት እያፈቀራትም ቢሆን ሌላ ሌላ ነገር ዉስጥ ገባ
የሆነ ቀን ሲያገረሽበት ለጉዋደኛዉ
"ጥራልኝ ላዋራት ናፈቀችኝ"
አለዉ
"ምን ጣጣ አለዉ"
ተከተለኝ አለዉና ወደ ህሊና ክፍል አምርተዉ ትንሳኤ በረንዳ ሲቆም ደፋሩ ጉዋደኛዉ ህሊናን አቀፍ አርጎ እያዋራት ይዧት ከወጣ በኋላ
"ተነጋገሩ "
ብሏቸዉ ትንሳኤን እና ህሊናን አገናኝቷቸዉ ሄደ።
"የመጀመርያ ቀን ቦርሳ በትከሻሽ ይዘሽ እየሳቅሽ ስትገቢ ነዉ ያየሁሽ
ደሞ በግራ እጅሽ ነዉ የምትፅፊዉ አደል"
ትንሳኤ ሊያዋራት የመጣዉ ሌላ ቢሆንም የልቡን በቻለዉ ቋንቋ መናገር ቀጠለ
ነገር ግን የህሊና መልስ
"ጉዋደኛ አለኝ አንደዉም አሁን እራሱ ሰዉ አይቶኝ ካንተ ጋር መቆሜን እንዳይነግሩት"
አለችዉ
ሀሳቡ ተበታተነ እኔ ነኝ እንጂ እስዋ አትወደኝም ሲል አስቦ በልቡ እሳት እየነደደ ዉስጡ በንዴት ግሎ
"እሺ ስታገኚኝ ግን አትዝጊኝ ሰላምታ እንኳን"
"እሺ"
ብላዉ ጥላዉ ገባች
ነገር ግን አንዴ ታክሲ ስትጠብቅ ከሩቅ አይቷት በደስታ ክንፍ ብሎ ሲጠጋት እየገላመጠች እራቀችዉ
ተከትሏት ጥቂት ለማዋራት እየሞከረ ተከተላት ነገር ግን እሷ ማዋራት አልፈለገችም
ትንሳኤ አመታት አልፈዉም አሁንም እንደ መጀመርያዉ ቦርሳ ይዛ እየሳቀች ስትገባ ያለዉ ምስል አይምሮዉ ዉስጥ አለ ፍቅሯ አመታት አልፎ እንደ ትላንት ይታወሰዋል መልኳ አይኗ ሰዉነቷ አወራሯ ሁሉ ነገሯ አይረሳዉም
ማፍቀር ማለት የማያገኙትን ሰዉ በተስፋ እንደመጠበቅ ነዉ ስሜቱ ያማል ያስከፋል መንገዱ ዉስጥ ግን አይረሴ ታሪኮች አሉ
አንድ ቀን አጊንቷት ያለ ፍርሀት ያለ ሰቀቀን እንደ ጉዋደኛ እንኳን ቢያዋራት ህልሙ ነዉ አንዳንዶች ለቀልድ ተዋዉቀዉ ይጋባሉ አንዳንዶች የእዉነት አፍቅረዉ ያጣሉ አለም ትገርማለች ፍቅርም ይገርማል ይሄ ታሪክ ለትንሳኤ የህይወቱ ክፍል ለህሊና ተራ ወሬ ሊሆን ይችላል
ትንሳኤ በልቡ የያዘዉ ታሪክ ነዉ ህሊና የናቀችዉ ተራ ነገር
ትንሳኤ በህሊና መፍረድ አቁሟል ምክንያቱም ሰዉ የፍላጎቱ ዉጤት ነዉ
የእሷ ምርጫና ፍላጎት የራሷ ዉሳኔ ነዉ

💫አለቀ💫

ነገ በተለመደው ሰዓት #ህመም_ያዘለ_ፍቅርን #ምእራፍ_ሁለት እንጀምራለን እሰከዛው መልካም ቆይታ🙏
👍3
#ሮሜዎና_ዡልዬት

#ክፍል_አምስት

ከተሸንፍክማ ' በጕንጮቿ ፡ ቅላት '
በወገቧ ቅጥነት፡ በደረቷ፡ ሙላት'
አበድኩ ፡ ካልክማ፡ ለጥርሶቿ 'ንጣት '
ለባቷ፡ አቀራረጽ ለጠጕርዋ ፡ቀለም ፡
ፍቅርህ ፡ ባይንህ ፡ ላይ ፡ነው፤ በልብህ ፡ አይደለም ይቅር በለኝ፡ልጄ፡ ባሁኑ ፡ ወቀሣ
ለዚች ፡ ከንፈህላት፡ ያችን ' ስትረሳ ፡
አመዛዘንኩና' ሠጋሁ፡ ኣስተውዬ '
ይችንም ፡ እንደዚያች' ትረሳለህ ፡ ብዬ ።

#ሮሜዎ
አባቴ ፡ በፍጹም ፡ ይህን ፡ አይጠርጥሩ፤
የዚችና ፡ የዚያች ፡ ልዩ ፡ ነው ፡ ነገሩ
በምን ፡ ቃል ፡ ልናገር ፡ ይህን ፡ ለማሳመን
በግሪክ ፡ በሮማ ፡ በጥንታዊው ፡ ዘመን ፡
ያነቡ፡ እንደ'ነበር' የእንስሳውን ፡ ሞራ ፡
ይችሉ ፡ እንደ ፡ ሆነ ፡ አባቴ ፡ አባ፡ ሎራ '
እርስዎም ፡ እንደዚሁ፡ የልቤን ፡ ብራና፡
በጥበብ ፡ አውጥተው ፡ገልጠው፡ያንቡና '
የወረት ፡ ምልክት ፡ ቢያገኙ፡ በውስጡ '
ያን ፡ ጊዜ 'ይገባል ፡ ቢንቁኝ ፡ ቢቈጡ ።

#አባ_ሎራ
መልካም ነው አመንኩህ ፡ግን ከዚህ ፡ በኋላ
አንድ ፡ ነገር ፡ አለ ፡ የሚያስቸግር ፡ ሌላ ፤
ካፑሌና ፡ ሞንታግ ፡ የናንተ ፡ አባቶች ፡ .
ወገኖቻቸውን ፡ ጨምረው ፡ ጠላቶች ፡
ባላንጦች ፡ ቂመኞች ፡ ደመኞች ፡ ሲሆኑ ፤
በየመንገዱ ፡ ላይ ፡ እንዳውሬ ፡ እያደኑ ፡
አንዱ ፡ አንዱን ፡ ሲገድለው ፡ ባይኑ ፡ ሲያየው፡ብቻ
እንዴት ፡ ሊፈጸም ፡ ነው ፡ የናንተ ፡ ጋብቻ ? .
ይኖሩ ፡ የለም ፡ ወይ ፡ ዘወትር ፡ በዘመቻ ፡
ዘለዓለም ፡ ለውጊያ ፡ ለጠብ ፡ ተሰልፈው ፡
ለቄስ ፡ ላስታራቂ ፡ ለዳኛ ፡ አሸንፈው ።

#ሮሜዎ
ይኸው፡አባቴ ሆይ ይህ ነው፡ ዋናው ነገር
በዚህ ፡ ላይ ፡ ይገባል ፡ በብዙ ፡ መማከር ፡
እውነት፡ ነው ፡ ቢኖሩ፡ ዘለዓለም ፡እነሱ፡
በጠብ ፡ ባምባጓሮ ፡ ደም ፡ እያፈሰሱ ፡
ለፍርድ ፡ ቢያስቸግሩ የቄስ ፡ ቃል ፡ ባይሰሙ ፡
እኔና ፡ ዡልዬት ፡ ግን ፡ንጹሕ ፡ ነን ፡ ከቂሙ፡
አለ ፡ ወይ ፡ አባቴ ፡ በሃይማኖት ፡ መንገድ
የሚከለክል ፡ ሕግ ፡ እኛ ፡ እንዳንዋደድ ፡
እንግዲህ ፡ አባቴ ፡ ይህንን ፡ ካወቁ ፡
ዘዴውን ፡ ለማግኘት ፡ እርስዎም ፡ ይጨነቁ ፡ቤተ ሰቦቻችን ወሬውን ፡ ሳይሰሙ
ተክሊሉን ፡ በምስጢር ፡ እርስዎ፡ ይፈጽሙ ።

#አባ_ሎራ
ይህንን ፡ ታልህማ ፡ ዘዴ ፡ ጠፍቶ ፡ ለርቁ ፡
ካህንም ፡ አልቀረም ፡ አብሮ ፡ መጨነቁ ፡
ለሁለቱ ፡ ወገን ፡ ሰላምን ፡ መልሶ ፡
ያባቶቻችሁን ፡ ክፉ ፡ ቂም ፡ ደምስሶ ፡
ስለታቸው ፡ ዘወትር ፡ የሰው ፡ ደም ፡ ከማፍሰስ ፡
እንዲቆም ፡ ለማድረግ ፡ ትንሽ ፡ እንዲታገሥ ፡
ለሻምላ ፥ ለጩቤ ፥ ለሰይፍ ፡ ለጐራዴ ፡
ከዚህ ፡ የተሻለ ፡ መች ፡ ይገኛል ፡ ዘዴ ።
የናንተ ፡ ጋብቻ ፡ ይህን ፡ ቂም ፡ አብርዶ ፤
ዕርቅ ፡ ይመሠረታል ፡ ሰላምን ፡ አውርዶ ።

#ሮሜዎ
እንግዴህ፡ አባቴ ፡ እንፍጠን ፡ በቶሎ ፡
ተክሊሉ ፡ ይፈጸም ፡ በዛሬ ፡ቀን ፡ ውሎ ፡
ጊዜና ሰዓቱን ፡ ካልተሻማን ፡ በጣም :
እንዲህ ፡ ያለ ፡ ፍቅር ፡ ዕንቅፋት ፡ አያጣም

#አባ_ሎራ
እንግዲያው ፡ መልካም ፡ ነው ፡ ኑና ፡ ባሥር ፡ ሰዓት፡
ትፈጽማላችሁ ጋብቻችሁን በስራት

#የዡዬየት_ሞግዚትና #ሮሚዎ

#ሞግዚት
መልሱን ፡ ተቀብለሽ ፡ እንድትመጪ ' ብላ
ልካኝ' እመቤቴ ፡ በቶሎ ፡ አስቸኵላ '
ይኸው ፡ መጥቻለሁ፡ መልሱን ፡ ለመቀበል ፤
ቸኩያለሁና ፡ ንገረኝ፡ ቶሎ ፡ በል ።

#ሮሜዎ
ምላሴ 'ያሞግስ ፡ አፌም ፡ ያመስግናት ፤
በውነት' ያንቺ ፡ እመቤት ፡ የተባረከች ፡ ናት
ዐመሏ ' ጠባይዋ ፡ በለጠ ' ከመልኳ፤
ቃሏን ፡ ፈጸመችው ፡ አንቺን ፡ በመላኳ
ዥሮቼ ፡ ተከፍተው 'እሰማለሁና፡
እንግዴህ ፡ ንገሪኝ የዡልዬትን ፡ ዜና ።

#ሞግዚት
ለተነጋገርነው ፡ ትናንትና ፡ ማታ ፡
እንድትልክብኝ' ያሳብህን ፡ ሁኔታ ፡
በመጠበቅ ፡ ላይ ፡ ነኝ ፡ አስታውቀኝ ፡ በቶሎ ፤
በዪና፡ ንገሪው ፤እንደዚህ ፡ ነው፡ ብሎ ፡
አሳቡን ፡ ሲነግርሽ ፡ ተቀብለሽ ፡ አምጪ፡
ብላኝ ' መጥቻለሁ ።

#ሮሜዎ
መልሴን ፡ ስትሰጪ '
እንግዲያው ፡ ንገሪያት ፡ ሮሜዎ ፡ ከልቡ ፡
ይወድሻል ፡ ብለሽ ፡ መንፈሱም ፡ አሳቡ ፡
ወዳንቺ ፡ ነው ፡ በያት ፡ ንገሪያት ፡ አደራ ፤
እስቲ ፡ ልለምንሽ ፡ እባክሽ ፡ ሳልፈራ ፡
እኔ ፡ እንደምወዳት፡ እንደዚሁም ፡ እሷ'
ትወደኝ ፡ እንደሆን ፡ ዡልዬት፡ በመንፈሷ፡
ታውቂዋለሽና ፡ እባክሽ ፡ ንገሪኝ ፡
አሳቧን ፡ ጠባይዋን 'እንዳውቀው ፡
ምከሪኝ ።

#ሞግዚት
ምንም ፡ አልደብቅህ ፡ ልንገርህ ፡ ካንዠቴ
አንተን ፡ ስታፈቅር ፡ ዝልዬት ፡ እመቤቴ'
እመነኝ ፡ ልንገርህ ፡ በውነት ፡ ከልቧ' ነው
የመስፍኑ ዘመድ፡ፓሪስ የሚባለው፡
ሊያገባት፡ ፈልጎ ፡ መሞቱ ፡ ነው ፡ ደክሞ ፡
ጨርሳ ፡ አትወደውም፡ እሷ ፡ ግን ፡ ፈጽሞ
አታንሡ፡ትላለች ፡ የሱን ፡ ስም ፡ ከፊቴ ፤
ትቈጣለችና ፡ ስቈይ ፡ እመቤቴ ፡
ልመለስ ፡ እባክህ ፡ መልሱን ፡ ስጠኝና ፤

#ሮሜዎ
አቀርብልሻለሁ'በሰፊው ፡ ምስጋና ።
እንደዚህ ' በዪና ፡ መልሱንም ፡ ንገሪያት ፤
ከቀትር ፡ በኋላ ፡ ዛሬ ፡ ባሥር ፡ ሰዓት ፡
አባ 'ሎራ፡ ድረስ ፡ አስፈቅዳ ፡ ትምጣ፤
ተናዘን ፡ ተባርከን ፡ የተክሊሉን ፡ጣጣ፡
ደብቀው ፡ በሙሉ ፡ ሊፈጽሙ፡ ቄሱ ፡
ተስማምተናል ፡ በያት ፡ ዛሬ ፡ ሊጨርሱ ።

#አባ_ሎራ #ዡልዬት #ሮሜዎ

#አባ_ሎራ
የናንተ ፡ ጋብቻ ፡ ፍጻሜው ፡ እንዲያምር ፡
ፈጣሪ ፡ ጸጋውን ፡ ምሕረቱን ፡ ይጨምር ።

#ሮሜዎ
አሳቤ ' ሞላልኝ ፡ እንግዲህ ፡ አባቴ ፡
ይህ ፡ ብቻ፡ ነበረ ፡ የቀረኝ ፡ ምኞቴ ።
ከሷ'ጋራ ፡ መጥቼ ፡ ቀርበን ፡ ከመንበሩ፡
ሥራቱን ፡ ከሞላን ፡ አለቀ ፡ ነገሩ ፡
እንግዲህ ፡ ግድ ፡ የለም የመጣ ፡ ቢመጣ

#አባ_ሎራ
ልጄ ፡ ሆይ ፡ ብዙ ነው የዚህ ዓለም ፡ ጣጣ
ለደስታ ፡ ሐዘን ፡ ለማር ፡ አለው ፡ እሬት ፤
ጠፊ ፡ ካጥፊው ፡ ጋራ ፡ ይኖራል ፡ በመሬት
ስለዚህ ፡እግዚአብሔር መጥፎውን ፡ አርቆ
ልጄ ፡ ያኑራችሁ ፡ በሰላም ፡ ጠብቆ ።

(ዡልዩት ፡ መጣች) ።

ፍቅሯንና ፡ ጌጧን ፡ በልቧ ፡ ሸፍና ፡
አልማዟ ፡ ማስተዋል ፡ ወርቋ ፡ ትሕትና ፡
ምስጢሯን ፡ ባሳቧ ፡ በጥበብ ፡ ሰውራ ፡
ይኸው ፡ መጣችልን ፡ መልካሟ ፡ ሙሽራ

#ዡልዬት
ሰላም ፡ ለርስዎ ፡ ይሁን ፡ ኣባቴ ፡ አባ ሎራ

#አባ_ሎራ
ደኅና ፡ ነሽ ወይ? ልጄ። ወጣት ፡ ሴት ፡ ወይዘሮ ፤
መልካም ፡ ጊዜ ፡ መጣሽ ፡ ልክ ፡ በቀጠሮ

#ዡልዬት
አመሰግናለሁ ፡ ለኔም ፡ ለሮሜዎ ፡
አባቴ ፡ ስለ ፡ እኛ ፡ በመቸገርዎ ።

#ሮሜዎ
እንዳንቺ ፡ እንደ ፡ እኔ ፡ በፍቅር ፡ ተሳስረው
ለመጡ ፡ ወጣቶች ፡ ሥራቱን ፡ አክብረው
ፍቅራቸውን ፡ ባርኮ ፡ በእጁ ፡ ሊቀድሰው ፡
ምን ፡ ጊዜም ፡ ሥራው ፡ ነው ፡ ካህን ፡ የሆነ ፡ሰው።

#አባ_ሎራ
እጆቹን ፡ ዘርግቶ ፡ ካህን ፡ ይጠብቃል ፤
እውነት ፡ ነው ፡ ሮሜዎ ፡ የተናገረው ፡ ቃል'
ከቤተ ፡ ክርስቲያን ፡ እንግባና ፡ በሉ ፡
ሳይዘገይ ፡ በቶሎ ፡ ይፈጸም ፡ ተክሊሉ ።

(ቤተ ፡ ክርስቲያን'ገቡ)

(#በቬሮና #ከተማ' #መንገድ) •

#ሜርኩቲዎ #ቤንቮሊዎ ፡ አንድ ፡ የእልፍኝ #አሽከር

#ቤንቮሊዎ
ሜርኩቲዎ ፡ እንሂድ ፡ የካፑሌ ፡ ሰዎች ፡
ይጠፉ ፡ አይመስለኝም በነዚህ መንደሮች
ድንገት ፡ ብንገናኝ ፡ ኋላ ፡ ጠብ ፡ ይነሣል ፤
ደግሞ ፡ ጠብ ሲነሣ ፡ ጸጥታ ፡ ይፈርሳል ፡
ብንሸሽ ፡ ይሻላል ፡ ከዚህ ፡ ሁሉ ፡ ጣጣ ።

#ሜርኩቲዎ
እነሱም ፡ አስበው ፡
👍1
ነገር ፡ እንዳይመጣ ' .
እንደ እኛ ፡ ሰላም ፡ ካልተጠነቀቁ ፡
ዳኝነትን ፡ ፈርተው ፡ ሕጉን ፡ ካልጠበቁ ፡
ዕወቅ ፡ እንዳይበቃ ፡ ጠብ ፡ ብንሸሽ ፡ እኛ
ለምሳሌ ፡ መጥቶ ፡ አንዱ፡ ጥጋበኛ ፡
ያላንድ ፡ ምክንያት ፡ ከመሬት ፡ ተነሥቶ :
እንዴት ፡ ታደርጋለህ ፡ ቢጣላህ ፡ ደንፍቶ ?
ያውም ፡ ደግሞ አንተ ፡ የባስክ ፡ ነህ ፡ ከኛ
ትንሽ ፡ የሚበቃህ ፡ ቍጡ ፡ ግልፍተኛ ።

#ቤንቮሊዎ
እኔስ ፡ ቢዋጣልን ፡ እወድ ፡ ነበረ ፤
ዳሩ ፡ ምን ፡ ይሆናል ፡ ዐዋጁ ፡ አስቸገረ፡
ለጠብ ፡ ይነሣና ፡ ልቤም ፡ ሰውነቴ ፡
የመስፍኑ ፡ ቁጣ ፡ ይመጣል ፡ ከፊቴ ።

#ሜርኩቲዎ
የፈራኸው ፡ ነገር ፡ አልቀረም ፡ ደረሰ ፤
ቲባልት ፡ ይመስለኛል ፡ ጥቍር ፡ የለበሰ '
እነሱ ፡ አይደሉም ፡ ወይ ፡ ወዲህ ፡ የሚመጡት ?

#ቤንቮሊዎ
ተመልከት ፡ ካሁኑ ፡ ደሜን ፡ እንዳስቈጡት

(ቲባልት ' ለወገኖቹ ")

ነቃ ፡ ነቃ ፡ በሉ ፡ አሳዩ ፡ ጕብዝና ፤
ጠብ ፡ ቆስቋሽ ፡ ለመሆን ፡ ፈልጌያለሁና'
ይህ፡የማነው፡ሻምላ፡የዛገ፡ሳይሠራ?(ወደ 'ጠላቶቸእያየ)»

#ሜርኩቲዎ
ምነው ፡ ቢመለከት ፡ ዐይንህ ' እያጠራ'

💫ይቀጥላል💫
#ለራስ_የተፃፈ_ውዳሴ

ስላንቺ ቁንጅና
ስላንቺ ቁመና
ከንፈር እና ዳሌ
ጥርስና ተረከዝ ፥ ፀጉር ገለመሌ
ለጡት ለወገብሽ ፥ ለፀባይሽ ጭምር
በግጥም በዝርው ፥ ባድናቆት ስዘምር
እስከዛሬ ድረስ...
ውበትሽን አግንኜ ፥ ሰርክ መለፈፌ
እኔ ስለራሴ
አንዳች ቀን እንኳ ፥ ግጥም አለመፃፌ
ሲትጠዪኝ ቆጨኝ
ቢሆንም ቆንጆ ነኝ፡፡
እርግጥ ነው ብዙዎች
ስለኔ ሳወራ ፥ ድንገት ያኮርፉኛል
"ያንተን ሌሎች ያውሩ” ፥ ብለው ይነግሩኛል
እኔ ግን እላለሁ!
“እኔን ከኔ በላይ
እርግጠኛ ሆኖ ፣ ሌላ እንዴት ያውቀኛል?!”
እናም እኔ ማለት
ቁመቴ ከአክሱም ፥ በእጥፍ ይረዝማል
ጣፋጭ አንደበቴ
መስማት ለተሳነው ፥ ለስልሶ ይሰማል
ውብ አረማመዴ
እንኳን መንገደኛን ፥ መንገድን ያቆማል፡፡
የከንፈሬ ወዙ ፥ ጥፍጥናው አያልቅም
ጥርሴ ሺ ገዳይ ነው!
ሺ ሟች ላለማየት ፥ ኗሪ ፊት አልስቅም፡፡
ከዐይኖቼ ብሌን ውስጥ ፥ ብርሐን ይፈልቃል
አይኔን ያየ ሁሉ
ብርሃን እንዳይጎዳው
በእጆቹ መዳፍ ; ዐይኑን ይደብቃል።
የገላዬ ጠረን ፥ ከሽቱ እጥፍ ነው
መልካም ጠረን ሁሉ
አለ ባሉት ስፍራ ፥ እኔ አለሁ ማለት ነው፡፡
ፀባየ ትሁት ነኝ ፥ ምጡቅ ነው እውቀቴ
ግርማ ሞገሳም ነው ፥ ተክለ ሰውነቴ
ሁሉ ይወደኛል
የወደየኝ ሁሉ ፥ መቼም አይጠላኝም
ከዚ በላይ እንኳን
ብዙም ስለራሴ ፥ የማውቀው የለኝም፡፡
እንደውም እንደውም...
አልጎርርም እንጂ !
ያ'ፈር ሰውነቴን ፥ በቁንጅና አብየው
ቆንጆ ማየት ሲያምረኝ ፥ ራሴን ነው ማየው፡፡
ቢሆንም ቆንጆ ነኝ!

🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
#ህመም_ያዘለ_ፍቅርን


#ምእራፍ_ሁለት


#ክፍል_አንድ

#በክፍለማርያም

ፀሀይዋ ለመጥለቅ ጥቂት ሰዐታት ይቀራታል እስዋን እየተመለከቱ ብዛት ያላቸዉ ወንዶች ግቢዉ ዉስጥ ከወዲህ ወድያ ይንጎማለላሉ።

ፍፁም በብቸኝነት ተቆራምቶ ከተቀመጠበት ጥግ ተነስቶ ቆመና ወደ ሰፊዉ ክፍል አምርቶ ወረቀት እና እስኪርቢቶ አንስቶ መፃፍ ጀመረ።
ለመጀመርያ ጊዜ ቤዛዊትን ያገኛት ቀን ሰአት ጠይቃዉ ስትሰድበዉ ታሪኩን እየፃፈ ከታሰረ ለመጀመርያ ጊዜ ፊቱ ላይ ፈገግታ ተነበበ መፃፉን አላቋረጠም የሚያስታዉሳቸዉን የእሱን እና የቤዛዊትን ታሪክ ወረቀቱ ላይ እየከተበዉ ነዉ።
ትምህርት ቤት ዉስጥ የጠቀሰችዉን ሲያስታዉስ ድምፅ አዉጥቶ መንከትከት ጀመረ ከጎኑ የነበሩት እስረኞች እየገላመጡት ከአጠገቡ ተነስተዉ እራቁት ማንም ሰዉ ያንተን ህመም እንዳንተ አያመዉም
ማንም ሰዉ አንተ ያሳለፍከዉ ከባድ ነገር ለእሱ ክብደቱ አይታወቀዉም
መሸከም ስትችል ተቋቁመሀዉ ስታልፍ ያበረታሀል እንጂ አቅቶህ ስትወድቅ የሚያነሳህ ውስን ነዉ።

መፃፉን እየቀጠለ ነዉ ቤዛዊት ፅፋ የምትሰጠዉን ወረቀቶች አሁንም ድረስ ያስታዉሳቸዋል
ህመሟን እብደቷን ሳያዉቅ ቀሚስሽ አጥሯል ሲላት ጠልፎ የሚጥል እረጅም ቀሚስ ለብሳ ቤቱ የመጣችዉንም አልረሳዉም አሁንም እንደታመመች አዉቆ ስላልተዋት ስላልራቃት በራሱ ደስተኛ ነዉ።

ቤዛዊትን ሲያስብ ፈገግታዋ የፊቷ እንቅስቃሴ አይኑ ላይ ይታየዋል ሳቋ በጆሮወቹ ዛሬም ያስተጋባሉ
ንዴትዋን ኩርፊያዋን ህመሟን ሲያስብ ብታናድደዉም ስለተላመዳቸዉ እንደ እንከኖቿም አይቆጥርባትም
የእሱን በድንገት በአጋጣሚ ፍቃዱ የሚባልን የተረገመን ፍጥረት በንዴት ተገፋፍቶ መግደሉን ሲያስብ ፀፀት መላ ሰዉነቱን እየወረረዉ የጀመረዉን ፅሁፍ አቁዋርጦ ማልቀስ ጀመረ።

ፍፁም እስር አልተመቸዉም ለነገሩ መታሰር ለማን ይመቻል ገና አሁን ወዳለበት የእስር ግቢ እንደገባ የሬሽን መዝገብ ዉስጥ ስሙ ስላልተካተተ ደረቅ ዳቦ ብቻ ቀምሶ ትራስ እያስፈለገዉ
ፍራሽ ላይ ጋደም አለ ለማሰብ ግዜ አላገኘም እራሱን ሀይለኛ ህመም እየተሰማዉ ነዉ።
ሰዉነቱ በትኩሳት ግሎ ነገር ግን ብርድብርድ እያለዉ እየተንቀጠቀጠ ለሊቱን እንቅልፍ በአይኑ ሳይዞር ነጋ
የመከራ ለሊት ይረዝማል ከታሰረ ሳምንት ወራት የቆየ ይመስለዋል ጠዋት ለህክምና የእስር ቤቱ ግቢ ካለዉ ክሊኒክ ለመሄድ ቢሞክርም ወረፋ ስላለ እንዲታገስ
ስለተነገረዉ መራመድ እያቃተዉ በልቡ
"መሞቴ ነዉ"
እያለ እንደምንም ፍራሹ ላይ ወድቆ ለመተኛት ሞከረ።

ቤዛዊት አይምሮዋ እየተረጋጋ ሲመጣ እማማ ስንቅነሽን ለፍፁም ምግብ እንዲቋጥሩለት አርጋ በተዘበራረቀ ስሜት ዉስጥ ሆና እንባ እየተናነቃት ወደ ፍፁም አመራች
እስካሁን ፍፁም ፍቃዱን መግደሉን አላመነችም
"የማይሆን የማይታሰብ ነገር"
ትላለች ከአፏ እያመለጣት ስትራመድ
የእስር ቤቱ ግቢ መግቢያ ስትደርስ የልብ ምቷ መፍጠን ጀመረ
ፍፁምን ካየችዉ ቆይታለች በፖሊሶች ታጅቦ ሲያልፍ ካየችዉ ወድያ ምንም የምታስታዉሰዉ ነገር አልነበረም እድሜ ለእማማ ስንቅነሽ እና ለልጃቸዉ ለጌታቸዉ ስታስቸግር ስትረብሽ ተንከባክበዉ ለዛሬ እንድትበቃ ላገዟት
ዉስጥ ገብታ የምትፈልገዉን ሰዉ ስም ተናግራ ቆማ መጠበቅ ጀመረች።
ፍፁም አይኖቹ ቀልተዉ ደም መስለዋል በተኛበት ፍራሽ እንደሰመመን "ፍፁም ደምሴ"
እየተባለ ሲጠራ ይሰማዋል መነሳት ግን አልቻለም
በሞት እና በህይወት መሀል ያለ እየመሰለዉ ሲያጣጥር ቆይቶ የቤዛዊት ምስል ፊቱ ላይ ድቅን ስላለበት አይኖቹ እንባ አዝለዉ እንደምንም ተነስቶ ለመቀመጥ ሞከረ
"ፍፁም ደምሴ ጠያቂ መጥቶሎታል"
የሚል ድምፅ ስለሰማ እያቃሰተ ወደ ዘመድ ጥየቃዉ ቦታዉ ለመሄድ መታገል ጀመረ።
ቤዛዊት እንደሆነች አስቀድሞ ልቡ አዉቆታል ጥቂት እንደተራመደ ግን የማጥወልወል ስሜት
ስለተሰማዉ ለመረጋጋት አስቦ ለመቆም ሲሞክር ወደቀ ጨለማ እየታየዉ የነበረ ቢሆንም ቀስበቀስ ጨለማዉም ጠፍቶ እራሱን ስቶ ወድቆ ቀረ።

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍3
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር


#ምእራፍ_ሁለት (#ክፍል_ሁለት)


#በክፍለማርያም

...ወድቆ ቀረ
ቤዛዊት ከዘመድ መጠየቅያዉ ስፍራ ቆማ የፍፁምን መምጣት እየተጠባበቀች እንደ መለያ ከታጠረዉ ጥልፍልፍ የሽቦ አጥር መሀል ጥዉልግ ያለዉ ፍፁም እየተንቀራፈፈ ሲራመድ
እሱን እያየች ዉስጧ ስለተረበሸ በቆመችበት

"እኔን እኔን እኔን"

እያለች ለእሱ ያመጣችለትን ምግብ የያዘ ጎድጓዳ የምሳ እቃ መሬት ላይ እያስቀመጠች
በሁለቱም እጆቿ ደረቷን ለኮፍ ለኮፍ እያረገች መድቃት ጀመረች
"ምነው ለኔ ለበሽተኛዋ ባረገዉ እሱን ፈተዉ እኔን ባሰሩኝ"
ስትል ቆይታ ፍፁም መራመድ አቅቶት ሲቆም የእሷም ልብ በድንጋጤ ቆመ
መሬት ላይ ዝልፍልፍ እያለ ሲወድቅ እስዋም እንደሱ ወደ መሬት ተንበረከከች የለበሰችዉ ጥቁርበጥቁር ቀሚስ አዋራ ለበሰ ከአይኗ እንባ እንደ ዉሀ ትኩስ ሆኖ ጉንጮቿን አቁዋርጦ ይፈሳል
አጠገቧ የነበሩት እስረኛ ጠያቂዎች እና የማረምያ ቤቱ ፖሊሶች ሊያነሷት ቢጠጉም በጉልበቷ እንደተንበረከከች አንገቷን መሬቱ ላይ ደፍታ
"አስተማሪዬን አስተማሪዬን መልሱልኝ እኔ የሚያመኝን እሰሩኝና ፍፁሜን ፍቱልኝ"
ጩሀቷን የታመቀ ብሶቷን ማሰማት ጀመረች።

ፍፁምን እስረኞች በጥንቃቄ ደግፈዉ አቅፈዉ ወደ ክሊኒኩ ለመዉሰድ ሲሞክሩ ጠዋት የመለሰዉ ህክምና ወረፋ የሚያሲዘዉ ሰዉ እየተፀፀተ እና
"ምን አለ ጠዋቱኑ እንዲታከም በፈቀድኩለት"
በሚል ስሜት ዉስጥ ሆኖ ፍፁም ህክምናውን በፍጥነት እንዲያገኝ እረዳዉ
ፍፁም አይኑን ሲገልጥ ያስተዋለዉ አሁንም እስር ቤት ግቢ ዉስጥ መሆኑን ነዉ
አካባቢዉን እየቃኘ አንድ ወጣት ነጭ ገዋን የለበሰ ሀኪም መጥቶ
"ተከተለኝ"
አለዉ ፍፁምም ከተኛበት የክሊኒኩ አልጋ ቀስ እያለ ተነስቶ ተከተለዉ
ብዛት ያላቸዉ መድሀኒት ሰጥቶት ሰዐቱን ጠብቆ እንዲዉጥ ከመከረዉ በኋላ የደንብ ልብስ የለበሰ የማረምያ ቤቱ ፖሊት ወደ መታሰርያዉ ግቢ እየመለሰዉ።

መንገድ ላይ ለዘመድ ጥየቃ እንደተጠራ ሲያስታዉስ ከጎኑ ያለዉን ፖሊስ
"ዘመድ ፈልጎኝ ነበር እባክህ አንዴ ላናግራት"
አለ በተያያዘ አንደበት በህመም ቅላፄ ባለዉ አወራር
"ምንህ ናት"
ሲል ፖሊሱ ጥያቄዉን በጥያቄ መለሰለት
"ጉዋደኛዬ ፍቅረኛዬ "
እየተንተባተበ መለሰለት
"ትንሽ አስቸግራ ነበር አልወጣም ብላ ትንሽ ቆይተን ተሽሎታል ሌላ ግዜ ነይ ስንላት ተመልሳ ሄዳለች"
አለዉና ፍፁም የታሰረበት ግቢ ሲደርሱ ለሌላኛዉ ፖሊስ አስረክቦ
"ፈጣሪ ይማርህ"
ብሎ ተለየዉ።

(ከደቂቃወች በፊት)
ቤዛዊት በርቀት ፍፁምን በሽቦዉ አጮልቃ አፋፍሰዉ ሲወስዱት እየች
ሽቦዉን እየነቀነቀች መጮኋን አላቋረጠችም ነበር ፖሊሶች ሊያረጋጓት ቢሞክሩም የምትሰማበት ጆሮም ልብም አልነበራትም እናት አባት እንደተሞተበት ትኩስ ሀዘን ከልቧ አምርራ
"አረ ወገን አረ ፖሊስ አረ ወንድም አረ እህቴ"
እያለች ፊት ለፊቷ ያየችዉን ሰዉ ሁላ በለቅሶ እየለመነች
"አስፈቱልኝ አስለቅቁልኝ አስተማሪዬ እኮ ነዉ
ወደቀ እኮ ወ ደ ቀ አረ ላንሳዉ ኡኡኡኡ አረ የሰዉ ያለ..."
ልብሷ እንዳለ በአቧራ ተላዉሶ ፀጉሯን እያመነቃቀረች ደረቷን እየደቃች ስታስቸግር በሁኔታዋ ግራ የተጋቡት ፖሊሶች በስንት ልፋትና ትግል አረጋግተዋት ፍፁም ደህና እንደሆነና ህክምና እያገኘ እንደሆነ አስረድተዋት በፈለገችዉ ሌላ ቀን መጥታ ማየት እንደምትችል ነግረዋት እስከግቢዉ በር ደግፈው ሸኙዋት።

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
#ሮሜዎና_ዡልዬት


#ክፍል_ስድስት


አሁንም ፡ ፡ ይሻላል ፡ ብታየው ፡ አስተውለህ ፤

የደረቀ፡ደም፡ነው፡ዝገት፡የመሰለህ

#ቲባልት
ኧረግ ፡ እንዲህ ፡ነው ፡ ወይ ! የበግ ፡ ነው ፡ የዶሮ ?

#ቤንቮሊዎ
ፈሶ : የተገኘ ፡ ካንገቱ ፡ ጕረሮ ፡
የወገንህ ፡ ደም ፡ ነው ፡ ከበግ ፡ የማይሻል

#ቲባልት
በመሳደብ ፡ ብቻ ፡ ጊዜያችን ፡ ይመሻል ፡
እንግዲህ፡ ይቀጥል ፡ የወንዶቹ ፡ ሥራ ።
(#ሻምላ#መዘዘ)።

#ሜርኩቲዎ
ዘወትር፡ዝግጁ፡ነኝ፡ማንንም፡አልፈራ፤(#ሜርኩቲዎም #መዘዘ)
(ሮሜዎ ፡ መጣ) ።

#ቲባልት
ከናንተ ፡ ኣልዋጋም ፡ መጣ ፡ የኔ ፡ እኩያ ፤
ስማኝ ፡ ሮሜዎ ፡ ወጥቼ ፡ ገበያ ፡
አቃተኝ ፡ ለማግኘት ፡ ፈልጌ ፡ ክፉኛ ፡
አንተን ፡ የመሰለ ፡ የወንድ ፡ መናኛ ።

#ሮሜዎ
ተፍቋል ፡ ጨርሶ ፡ ቂም ፡ በቀል ፡ ከልቤ ፤
በመጥፎ ፡ ንግግር ፡ ሮሜዎን ፡ ሰድቤ ፡
ላስቈጣው ፡ በማለት ፡ ቂሙን ፡ ልቁስቀሰው ፡ ማለት በከንቱ ፡ ይደክማል ፡ የተጣጣረ ፡ ሰው' .
የፍቅሬ ፡ ምክንያት ፡ ሆኗልና ፡ ብርቱ ፡
ቲባልት ፡ የኔ ፡ ወዳጅ ፡ አትድከም ፡ በከንቱ

#ቲባልት
ኀይለኛው ፡ ቂማችን ፡ ያከማቸው ፡ ዕዳ ፡
መች ፡ እንዲህ 'ይፋቃል ፡ ይልቅ ፡ ተሰናዳ

#ሮሜዎ
ቲባልት ፡ ስማኝ ፡ እኔ ፡ ንጹሕ ፡ ነኝ፡ ከቂሙ
ካፑሌ ፡ የሚሉት ፡ የዘራችሁ ፡ ስሙ ፡
እንደ ማር፡ ጣፋጭ ነው፡አይመረኝም ለኔ
ጠባችሁ ፡ ብቻ ፡ ነው ፡ በውነቱ ፡ ሐዘኔ ።
የፍቅሬን ፡ ምክንያት ፡ ሳታውቀው ፡ መርምረህ ፤
አትድከም ፡ በከንቱ ፡ ክፉ ቃል ፡ተናግረህ፡
ቲባልት ፡ እኔና ፡ አንተ መቼም : አንጣላም
ደኅና ፡ ዋል ፡ ወዳጄ ፡ እንሂድ ፡ በሰላም ፡
ደግሞም ፡ ከዚህ በቀር ፡ የሕጉን ፡ ወቀሣ
የመስፍኑን ፡ ዐዋጅ ፡ ልብህ ፡ እንዳይረሳ ።

#ሜርኩቲዎ
ዦሮዬ ፡ አይሰማም እንዲህ ፡ ያለ ፡ ፍራት
ቲባልት ፡ እይ ፡ ሻምላዬ ፡ ሲያበራ ፡ እንደ ፡ መብራት ። (መዘዘ)።
ተመልሶ ፡ እንግዴህ ፡ ኣይገባም ፡ ካፎቱ ፡
በደም ፡ ካልታጠበ ፡ የዛገው ፡ ስለቱ ።
(አቲባልት'ጋራ ውጊያ'ገጠሙ)•

#ሮሜዎ
ፍጠን ፡ ቤንቮሊዎ ፡ እንገላግላቸው ፤
ሁለቱም አይረቡ በውነት እብዶች ፡ ናቸው
ቲባልት ! ሜርኩቲዎ ! አስቡት ፥ አትርሱ ፤
ልዑል ፡ በቀደም ፡ ለት ፡ ደም ፡ እንዳታፈሱ
ብለው ፡ የሰጡትን ፡ ዐዋጁን ፡ አስታውሱ
(ገላገላቸወ፡ ቲባልት' ከወገኖቹ'ጋራ'ሄደ)

#ሜርኩቲዎ
ቈስያለሁ ፡ እኮ ፡ በቃ ፡ የኔ ፡ ነገር ፤
ተበላሸሁ ፡ እኔ ፡ ወይ ፡ አለመመከር ።
ቤንቮሊዎ ፡(ቁስሉን'ያያል)"
ለካ ፡ ቁስለሃል ፡ ወይ ? አላየሁም ፡ እኮ !

#ሜርኩቲዎ
ሐኪም ፡ ይጠራልኝ ፡ አንድ ፡ ሰው ፡ ተልኮ
(የልፍኝ' አሽከር መሄዴ) "

#ቤንቮሊዎ
አይዞህ ፡ የኔ ፡ ወንድም፡ ትንሽ ፡ ነው ፡ቍስሉ ፤

#ሜርኩቲዎ
ምንም ፡ ትንሽ ፡ ቢሆን ፡ አይቀርም ፡ መግደሉ'ካፑሌና ፡ ሞንታግ ፡ ትውልዳቸው ፡ ይጥፋ፤
በነሱ፡ ምክንያት ፡ ስንት ፡ ሰው ፡ ተደፋ፡
በምን ፡ ኀጢአታችን ፡ እንሞታለን ፡ እኛ ፡
ለማይረባ፡ ነገር ፡ ተሳድቦ ፡ እንደ እረኛ ፡
በሰው፡እጅ፡ መሞት ፡ በሆነ ፡ ባልሆነው '
ከንቱ ፡ ሞት ይሉሃል ፡ እንደዚህ ፡ ያለ ነው
ተመቸውና ፡ ነው ፡ ይኸ ፡ ፈሪ፡ መጥፎ ፡
በሮሜዎ ፡ እጅ ፡ ሥር ፡ ታቹን ፡ አሳልፎ ፡
በድንገት ፡ የወጋኝ ፡ በቃ ፡ የኔ ፡ ነገር ፤
ባትገላግሉኝ ፡ አይነካኝም ፡ ነበር ።
(ሜርኩቲዎን'ቤንሾሊዎ 'ደግፎት ፡ አብረው ሄዱ)”

#ሮሜዎ ፡ (ወቻውን)
ወዳጄ ፡ ሜርኩቲዎ ፡ የመስፍኑ፡ ዘመድ ፡
አባቴን ፡ ወገኔን ፡ እኔንም ፡ በመውደድ
እንሆ ፡ቈሰለ ፡ ለኛ ፡ ሲል ፡ ተጣልቶ ፤
ቲባልት ፡ አዋረደኝ ፡ ከመሬት' ተነሥቶ
ዡልዬትን • ወድጄ ፡ ፍቅር ፡ መፈለጌ ፡
ስድቡንም ፡ ሸሽቼ ፡ ከጠብ ፡ ማፈግፈጌ፡
ወደ 'መለማመጥ ወገኖቼን ' መሪ
ወንድነት 'ያነሰኝ'አስመሰለኝ ' ፈሪ ።
(ቤንቮሊዎ መጣ)

#ቤንቮሊዎ
አልቅስ ፡ሮሜዎ ' እንባህን 'አፍስሰው
ሜርኩቲዎ ፡ ሞተ፡ መልካሙ 'ደጉ' ሰው ።
መልካሙ ፡ ወዳጄ ፡ ሜርኩቲዎ ' ከሞተ '
እንግዴህ ፡ መታረቅ ፡ ሰላም ፡ ተከተተ ፥
ጠባችን ፡ ነደደ ፡ በሉ ፡ የተነሣ ፤
ወደ ፡ ፊት ፡ ይወድቃል ፡ ገና ፡ ብዙ ፡ ሬሳ
(ቲባልት' ተመልሶ ፡ መጣ)

#ቤንቮሊዎ
ቲባልት ፡ ይኸ ሰይጣን መጥፎ ፡ ጥጋበኛ
እየው ተመልሶ ፡ ሲመጣ ፡ ወደ ፡ እኛ ።

#ሮሜዎ ፡ ለብቻው' ይናገራል) "
ወይ ፡ ጥሎኝ ወይ ፡ ጥዬው አንጀቴን ላርሰው ፤
ቆይ ፡ ይምጣ ፡ ግድ ፡ የለም ፡ ደም ፡ ነው፡ የመለሰው።
ዡልዬት ፡ ደግነቷ ፡ ፍቅሯ ፡ ሰላም ፡ ሆኖ ፡
ይዞህ ፡ የነበርከው ፡ በትዕግሥት ፡ ሸፍኖ ፡
በልቤ ፡ ያለኸው ፡ የቂሜ ፡ ትኵሳት ፡
ለብልበኝ ፥ ጠበሰኝ ፡ አቃጥለኝ ፡ እንደ ፡ እሳት ።
(ለቲባልት • ይናገራል) "
ቲባልት ፡ በል ስደበኝ፡ አሁን እንደ ቅድም
የሜርኩቲዎ ፡ ነፍስ ፡ ብቻዋን ፡ አትሄድም
ወይ ፡ እኔን ፡ ወይ ፡ አንተን ፡ አንዱን ፡ ሳያስተክትል፤
ሻሞላህን ፡ ምዘዘው ፡ ዛሬ ፡ ነገ ፡ ሳትል ፡
የምትሻው ፡ ቂሜ ፡ የነደደ ፡ ይሁን ።

#ቲባልት ። ..
አንተም፡ ከሱ ፡ ጋራ ፡ ትሞታለህ ፡አሁን ።
(ይዋጉና'ቲባልት 'ይወድቃል )

#ቤንቮሊዎ
ሮሜዎ ፡ አትቁም ፡ ቶሎ ፡ ከዚህ ፡ ጥፋ ፤
ቲባልት ፡ ከሞተ ፡ ምንም ፡ የለህ ፡ ተስፋ፡
መስፍኑ ፡ ሲያገኝህ ይህን ፡ነገር ፡ ሰምቶት
ዕወቅ ፡ አይምርህም ፡ ይቀጣሃል ፡ በሞት
(ሮሜዎ 'ሸሸ ፡ ሰዎች፡ መጡ)

#ወታደር
እንዴህ ፡ ያለ ነገር ዘለዓለም ፡ የማይበርድ
ነጋ ፡ ጠባ ፡ ሬሳ ፡ በየዋናው ፡ መንገድ ፡
ጠብ መሆኑን፡ሰምተው ይኸው፡ልዑል መጡ፤
ማነው ፡ የገደለው ? አሁን ፡ በቶሎ ፡ አውጡ ።

#መስፍን
አወይ ፡ ዘመዴ ፡ ሆይ፡ ሜርኩቲዎ ፡ ሞተ፤
ማነው ፡ ጠብ ፡ ሲጀመር 'የተመለከተ?

#ቤንቮሊዎ
ልዑል ሆይ፡እኔ ነኝ'ያየሁ፡ሁሉንም ፡ ነገር !
ፈቃድዎ ፡ ቢሆን' ፈጥኝ፡ ልናገር ።

#መስፍን
ንገረኝ ፡ ሁሉንም ፡ ከምንጩ ፡ ጀምሮ፤

💫ይቀጥላል💫
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር


#ምእራፍ_ሁለት (ክፍል ሶስት)


#በክፍለማርያም

ቤዛዊት ቤትዋን እነ እማማ ስንቅነሽ ቤት ካረገች ሰነባበተች ይሄ ሁሉ ምስቅልቅል ይፈጠራል ብላ አልነበረም ወደ እነ እማማ ቤት አመጣጧ ፍፁምንም የጋበዘችዉ በነፋሻዉ አየር ከሰዉ እራቅ ብለዉ የሰላም የፍቅር ጊዜ ለማሳለፍ ነበር
ነገር ግን አንዳንዴ ሀሳብ እንደ ንፋስ የማይታይ ሆኖ ይነፍከሳል ሀይል ካለዉም ነገሮችን ሳይጠበቅ እያንሳፈፈ እንደሚወስደዉ የታሰበዉ ሳይሆን ቀርቶ ያልተጠበቀ ነገር ይፈጠራል
ከእስር ቤቱ በር ጥቂት እንደወጣች ድንጋይ አጊንታ አረፍ አለች ጭንቅላቷ ዉስጥ ፍፁም ሲወድቅ ያለዉ ሁኔታ አሁንም ይታያታል አይኖቿ በለቅሶ ብዛት እንባ ማዉጣት ቢያቅታቸዉም ለአመል በቀስታ የሚፈሱ የእንባ ዘለላወች የአፍንጫዋን መስመር አቋርጠዉ አፍዋን እያራሱ በአገጯ አርገዉ ልብሷን እያረጠቡት ነዉ።

"ፍፁም ፍፁም ፍፁም"
በልቧ ይሄን ቃል ታነበንባለች እስካሁን መታሰሩ እዉነት አልመስልሽ እያላት እራሷን
"እንዴት እንዲህ ሊሆን ቻለ"
እያለች ትጠይቃለች መመለስ እና መፍታት የማትችለዉ ጥያቄ ሲሆን አይምሮዋ እየተቃወሰም ቢሆን ከተቀመጠችበት ተነስታ እንባዋን በእጆቿ እያበሰች ወደ እነ እማማ ስንቅነሽ ቤት አመራች።

ፍፁም ለመጀመሪያ ግዜ መድሀኒቱን ዉጦ የሰላም እንቅልፍ ወሰደዉ በህልሙ
ቤዛዊት ፊት ለፊቱ ተቀምጣ ስትስቅ እያያት ከጀርባዋ ጥቁር አሞራ እየበረረ ትከሻዋ ላይ ተቀምጦ የማያስፈራ ድምፅ እያወጣ ሲጮህ ባኖ ተነሳ
እየነጋጋ ነበር ከእስር ቤቱ ሚዲያ ክፍል መዝሙር ድምፁ ከፍተደርጎ ተከፍቷ ይሰማዋል እስረኞች ከእንቅልፋቸዉ እየተነሱ ወደ ዉጪ እየወጡ ነዉ ተነስቶ ለመቀመጥ ሞከረ ህመም አልተሰማዉም ተነስቶ ቆመ እራሱን ለቆታል
ፊቱ ላይ ጥልቅ ብሎ የጠፋ ፈገግታ ታይቶ እየተራመደ ወደ ዉጪ ወጣ አለ።
ቤዛዊት ከተኛችበት ስትነቃ የእማማ ስንቅነሽ ልጅ ጌታቸዉ በጥቂት ተገልጧ ወደ ሚታየዉ ባቷ ሲያፈጥ ያዘችዉ ቀሚሷን እያስተካከለች ተነሳች ጌታቸዉ ግን አሁንም በአይኑ እየተከታተላት ነዉ
"ቆንጆ እንደሆንሽ ታዉቂያለሽ"
አላት ማታ የጠጣዉ መጠጥ አሁንም አለቀቀዉም አፉን አሳስሮታል
ቤዛዊት ልብ ብላ አልሰማችዉም እማማ ስንቅነሽ ቤተክርስቲያን ለመሳለም በጠዋት ስለወጡ ሁለቱ ብቻ ናቸው ቤቱ ዉስጥ ያሉት።

(ከደቂቃ በፊት)
ቤዛዊት ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ዉስጥ ሆና እማማ ስንቅነሽ
"ልጄ ቤዛዊት ቤተስኪያን ደርሰን እንምጣ"
እያሉ ሊቀሰቅሷት ቢሞክሩም አልሰማም ስላለቻቸዉ እሳቸዉ ደጅ ወጥተዉ ልብሳቸዉን ቀያይረዉ ነጠላ ቢጤ ደርበዉ እንደወጡ በሩን ለመዝጋት ሲሞክሩ ልጃቸዉ ጌታቸዉ ከእንቅልፉ ይነቃል
ጥቂት አልጋዉ ላይ ሆኖ ስለ ቤዛዊት ቆንጅና ስለ ገላዋ ስለ ሰዉነቷ በህሊናዉ ሲስል ቆይቶ በቀስታ ከአልጋዉ ይነሳና ወደ እማማ እና ቤዛዊት ወደ ተኙበት ክፍል ያመራል
ቤዛዊት ብርድ ልብስ ተሸፋፍና ጥቅልል ብላ ተኝታለች ጌታቸዉ ፊት ለፊቷ እያያት ከቆመ በኋላ ብርድ ልብሱን ቀስ አርጎ ገለጠዉ ቤዛዊት አሁንም የእንቅልፍ ልብ ዉስጥ ናት
ቀስ ብሎ እረጅሙን ቀሚሷን እየገለጠዉ እና ታፋዋን እየተመለከተ ቤዛዊት ተገላብጣ ስትነቃ ፈንጠር ብሎ ቆሞ ማየቱን ቀጠለ።

(አሁን)
ጌታቸዉ ከቤዛዊት ጀርባ ቀስ ብሎ እየተጠጋ ሊያቅፋት ሲሞክር
"ምን መሆንህ ነዉ"
እያለች ገፍትራዉ አይኗን አጉረጠረጠችበት
እንደ መፍራት እያለ
"ምንም ምን አረኩ ደህና መሆንሽን ለማወቅ ነው "
እያለ ወደኋላ አፈገፈገ ነገር ግን በልቡ መጥፎ ሀሳብ ጠንስሶ ጠብቂ አገኝሻለሁ እያለ ነበር።

"ደህና ነኝ "
እያለችዉ ቤዛዊት ዛሬስ ፍፁምን አየዉ ይሆን እያለች እራሶን እየጠየቀች ለእራሷ
ዛሬማ አገኘዋለሁ አዋራዋለሁ እያለች ወጣች።

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
#ሮሜዎና_ዡልዬት


#ክፍል_ሰባት

#ቤንቮሊዎ
ጠቡን ፡ የጀመረው ፡ ክፉ ፡ ቃል ፡ ተናግሮ
ይኸው ፡ ቲባልት ፡ ነው ፡ ሌላ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፤
ከሱ ፡ በቀር ፡ ዛሬ ፡ ጠብ ፡ ያነሣ ፡ የለም ።
እኔና ፡ ሜርኩቲዎን ፡ ሰደበን ፡ ሳንሰድበው
ሮሜዎ ፡ ደረሰ ፡ ድንገት ፡ ሳናስበው ።
እሱም ፡ በደግነት ፡ ቃሉን ፡ አለስልሶ ፡
ልዑል ፡ የሰጡትን ያዋጅ ፡ ቃል ፡ ኣስታውሶ ፡
ቲባልትን ፡ ለመነው ፡ ጠብ ፡ እንዳያነሣ ፤
መቼም ፡ መጥቷልና ፡ እሱ ፡ ግን ፡ ላበሳ ፡
በእልህ ፡ እንቢ ፡ ብሎ ስድቡን ፡ ሲቀጥል
ከሜርኩቲዎ ፡ ጋራ ፡ ተማረሩ ፡ በጥል ፤
ሻምላ ፡ ቢማዘዙ ፡ ቶሎ ፡ መገላገል ፡
አሰብንና ፡ ገባን ፡ ከነሱ ፡ መካከል ።
እኔና ፡ ሮሜዎ ፡ ስንገላግላቸው ፡
ሜርኩቲዎን ለመውጋት ቲባልት ተመቸው
እኛም ፡ አላየንም ሜርኩቲዎን ፡ ሲወጋው
ኋላ ፡ ግን ፡ አየነው ፡ ቁስሉን ፡ ከነ አደጋው
ከሽሸ ፡ በኋላ ፡ ቲባልት ፡ እንደ ፡ ገና ፡
ቢመጣ ፡ ሮሜዎ ፡ ነዶት ፡ ነበርና ፤
ደሙን ፡ ለመበቀል ፡ በንዴት ፡ ተነሥቶ ፡
ከቲባልት ፡ ጋራ ፡ በቅጽበት ፡ ተዋግቶ ፡
ወዲያው በደቂቃ ውጊያው በጣም ሲግል
እኔም ፡ ሳያደርሰኝ ፡ ችዬ ፡ ሳልገላግል ፡
ቲባልት ፡ ቆሰለና ፡ በፍጥነት ፡ ወደቀ ፥
ሮሜዎም ፡ ሸሸና ፡ በዚሁ ፡ አለቀ ፤
ከተናገርኩትም ፡ ከውነቱ ፡ የራቀ ፡
ውሸት ፡ ቢገኝብኝ ፡ ተደርጎ ፡ ምርመራ ፡
ይድረስብኝ ፡ በኔ ፡ የቅጣት ፡ መከራ ።

የካፑሌ ፡ ሚስት (መጣች)

መሠረት ፡ የለውም ፡ ምስክርነቱ ፤
ከእውነተኛው ፡ ነገር ፡ ይበልጣል ፡ ሐሰቱ '
ይህንን ፡ ቢናገር ፡ እያስመሰለ ፡ እሱ ፡
የሞንታግ ወገን ነው ልዑል ሆይ አይርሱ!
በፍርድ ሮሜዎ ፡ ይሙት ፡ ነው ፡ የምለው

#መስፍን
ሮሜዎ ፡ ቲባልትን ፡ ወግቶ ፡ ከገደለው ፡
እናንተ ፡ ስለሱ ፡ ፍርድ ፡ ስጥ ፡ ስትሉ ፡
የሜርኩቲዎን ፡ ደም ፡ ማን ይክፈለኝ ፡ለኔ
ዘመዴ ፡ ነው ፡ እኮ ፥ ሥጋዬ ፡ወገኔ ።

#ሞንታግ
ልዑል ፡ሆይ ሜርኩቲዎን ቲባልት ገደለው
ዐዋጁ 'ቲባልትን ፡ ይሙት' ነው ' የሚለው
ስለዚህ ፡ ቢያስቡት ፡ አሁን ፡ የኔ ፡ ልጅ ፤
ቲባልትን ሲገድለው ፡ዐዋጅ ፈጸመ ፡ እንጅ
ሌላ ፡ ምን ፡ ጨመረ ፡ እስቲ ምን አጠፋ ?

#መስፍን
ሞንታግ ምሕረት አለ ብለህ ፡ እንዳትለፋ፡
ሮሜዎ ፡ በፍጥነት ፡ ዛሬ ፡ ካገር ፡ ይውጣ
ጠባችሁ ፡ በኔ ፡ ላይ ፡ ይኸው ዞሮ ፡ መጣ
በናንተ ፡ ምክንያት ፡ የሞተው ፡ ደጉ ፡ ሰው
ሥጋዬ ፡ ነው ፡ ዛሬ ፡ ደሙ ፡ የፈሰሰው ፡
በሰጠሁት ፡ ዐዋጅ ፡ ራሴ ፡ ወስኜ ፡
እገኛለሁ ፡ እኔ ፡ ጨካኝ ፡ ቀጭ ፡ ሆኜ፡
የፍርዴንም ፡ ሥራ ፡ በቅጣት ፡ ስሠራ ፡
ይቅርታ ፡ የለኝም ፡ ለማንም ፡ አልራራ ።
አማላጅ ፡ ልመና ፡ ጸጸትና ፡ ለቅሶ ፡
ፍርዴን ፡ ሊመልሱት ፡ አይችሉም ፡ ጨርሶ
ስማ ፡ ልጅህ ፡ ዛሬ ፡ የኔን ፡ ትእዛዝ ፡ ሽሮ ፡
የተገኘ ፡ እንደሆን ፡ በከተማው ፡ አድሮ ፡
ዛሬ ፡ ከቬሮና ፡ በፍጥነት ፡ ካልወጣ '
ዕወቀው ' ያለፍርድ' በሞት እንዲቀጣ ።

#ዡልዬትና#ሞግዚቷ ፡ (በቤታቸው) "

#ዡልዬት
እኔና ፡ ሮሜዎ ፡ ዕድላችን ፡ ክፉ ፤
ይደንቃል ፡ ሰርጋችን ፡ እንደዚህ ፡ ማለፉ፡
ሰርጉ አልነበረም ወይ የሰው ፡ልጅ ደስታ
እኛ ፡ ግን ፡ምስኪኖች በዚህ ፡ ሁሉ ፈንታ፡
መሥጋትና ፡ መፍራት ፡ ያባት የናት ፡ ቁጣ
ሆነና ፡ ተገኘ ፡ የተሰጠን ፡ ዕጣ ።
አልገሠግሥ ፡ አለ ፡ ጊዜና ፡ ሰዓቱ ፤
ምነው ፡ የዛሬ ፡ ቀን ፡ ደከመ ፡ ፍጥነቱ ?
ሰዓቱም ፡ ለገመ ፡ ዳተኛ ፡ መሆኑ ፡
ሮሜዎን ፡ ስጠብቅ ፡ አልመሽ ፡አለኝ ፡ ቀኑ
ደግሞ ፡ ሞግዚቴ ፡ ነች ፡ ዋና ፡ ጥፋተኛ ፤
ምነው ፡ ሆነችብኝ ፡ እንደዚህ ፡ ዳተኛ ?
በፊት ፡ ደኅንነቱን ፡ ነግራኝ ፡ ተመልሳ ፡
መሄድ ፡ ትችል ፡ ነበር ዳግም ፡ በግሥገሣ
ሌሊቱ ፡ ሲጨልም ፡ ጨረቃ ፡ ሳትወጣ ፡
ንገሪው ፡ አልኩና ፡ ሮሜዎ ፡ እንዲመጣ '
ብልካት ፡ እንሆ ፡ ቀረች ፡ እዚያው ፡ ቀልጣ
እባክህ ፡ ጨለማ ፡ ፍጠን ፡ በቶሎ ፡ ና ፤
ካልመሸ ፡ ሮሜዎ ፡ ደፍሮ ፡ አይመጣምና
ሌሊቱ' ይተካ ፡ የቀን ፡ ብርሃን ፡ ሄዶ፤
ሮሜዎን ወደ እኔ እንዲያስገባው ፡ ጋርዶ።
ቀኑ ፡ እየደከመ ፡ ብርሃን ፡ እየሸሸ ፡
ፀሓይ ፡ እየጠፋች ፡ ሰዓቱ ፡ እየመሸ ፡
አንተ ፡ ከባድ ፡ ጽልመት፡የሌሊት ፡ ጨለማ
ፈጥነህ ፡ ቶሎ ፡ ድረስ ፡ አትሁን ፡ ደካማ ።
ገሥግሠህ ፡ ሸፍናት ፡ ዓለምን ፡ በጥላ ፤
ጥላህ ፡ ለሮሜዎ ፡ ይሁነው ፡ ከለላ '
ፀሓይም ፡ ጥለቂ ፤ ብርሃንን ፡ አትስጪ ፤
ኮከብ ፡ ተሰወሪ ፡ ጨረቃም ፡ አትውጪ'
ካለም ፡ ገለል ፡ በሉ ፡ ብርሃንና ፡ ፋና ፡
ብርሃን ፡ እሱ፡ ራሱ ፡ ሮሜዎ ፡ ነውና ፡
ያቻት ወዲህ መጣች ብቅ አለች ሞግዚቴ
ደርሳ እስክትነግረኝ ፡ ወሬውን ፡ ከፊቴ ፡
ቸኩያለሁ ፡ በጣም ፡ እንዴት ፡ ያለ ፡ ወሬ ፡
ይዘሽልኝ ፡ መጣሽ ፡ ሞግዚቴ ፡ ሆይ ፡ ዛሬ ?
ምነው ፡ ምን ፡ ሆነሻል ፡ ፊትሽ ፡ ተለወጠ ?

#ሞግዚት
አዬ 'ከንቱ ፡ ነገር ፡ በቃ ፡ ተቈረጠ'
ባጭር ፡ ተቀጠፈ ' ያን ፡ መሳይ ፡ መኰንን
አዬ ፡ጉድ አዬ ፡ ጉድ! ጠላሁ ሰው መሆንን

#ዡልዬት
አሁን ፡ ባሁን 'ሄደሽ ፡ ከኔ ዘንድ ፡ ከወጣሽ'
ምን ፡ዐይነት ፡ኀዘን ነው ይዘሽው የመጣሽ

#ሞግዚት
አወይ 'ሮሜዎ 'ቲባልት ፡ መልካሙ ፡ ሰው፡
እንደ ፡ፋሲካ ፡ በግ ፡ ደሙ ፡ የፈሰሰው ።

#ዡልዬት
ሐዘኑን ' ሰምቼ ፡ ልቤ ፡ ሳይመታ፡
መናገር' አቃተሽ ፡ አፍሽ ፡ አመነታ '
ሮሜዎ ፡ ሞተ፡ ወይ ? ሞቶም ፡እንደ ፡ ሆነ
ንገሪኝ ፡ ምላስሽ ፡ እየሸፋፈነ ፡
ሳይደብቅ ፡ ገልጦልኝ ፡ መርዶውን ፡ ልረዳ
ልቤም ፡ ተሠንጥቆ ፡ በሐዘን ፡ ይፈንዳ ።

#ሞግዚት
ቍስሉንም ፡ አየሁት ፡ በጣም ፡ ያሳዝናል ፤
ሐኪም 'አይጠሩለት ፡ ሞቶ፡ ምን ፡ ይሆናል
ምንም' ትንፋሽ የለው አልፋለች ፡ ሕይወቱ፡
ደሙ ፡ ይመነጫል ፡ ቆስሎ ' ከደረቱ ፤
ከሞተ 'ቁይቷል ደርቋል ፡ ሰውነቱ "
እንዲህ ፡ ያለ ፡ ሥራ መቼም ፡ አልተሠራም
ዥልዬት ፡ የዛሬ ፡ ጉድ ፡ ይቅር ፡ አይወራም
ቲባልት ! ሮሜዎ ! አየሁ ፡ ደሙ ፡ ፈሶ :
ልብሱ ፡ ተበክሎ ፡ መሬቱም ፡ ርሶ ።

#ዡልዬት
ቲባልት ! ሮሜዎ ! ሁለቱንም ፡ ጠርተሽ ፡
ከምታስጨንቂኝ ፡ ንገሪኝ ፡ ለይተሽ '
ሮሜዎ ፡ ባሌ ፡ ነው ፡ ቲባልት ፡ ዘመዴ ፤
የቱ ፡ ነው ፡ የሞተው ፡ ተጨነቀ ፡ ሆዴ
ባለም ፡ ላይ ፡ ከሌሉ ፡ እነዚህ ፡ ሁለቱ ፡
መታከት ፡ ነውና ፡ ሁሉ ፡ ነገር ፡ ከንቱ ፡
የምጽኣት ፡ ቀን ፡ ይሁን ፡ መለከት ፡ ይነፋ ፤
አሁን ፡ ተደምስሶ ፍጥረተ ዓለም ፡ ይጥፋ፡
ባሕር ፡ ጫካ ፥ ገደል ፥ ጅረትም ፡ ተራራ ፡
ፍጡር ፡ እዬዬ ፥ በል ፡ አልቅስ ፡ ከኔ ፡ ጋራ

#ሞግዚት
ሟቹ ፡ ቲባልት ፡ ነው ፡ ካለም ፡ ላይ ፡ የሄደ
ገዳዩ ፡ ሮሜዎ ፡ ካገር ፡ተሰደደ ።

#ዡልዬት
ሮሜዎ ፡ ቲባልትን ፡ ብትዪኝ ፡ ገደለው ፡
አይችልም ፡ መንፈሴ ፡ አምኖ ፡ ሊቀበለው

💫ይቀጥላል💫
#የስህተት_ሰልፍ

አንቺም የምትስቺው
እኔም ምከተልሽ ወደ ስህተት ገደል
አዳምና ሄዋን
በአርኣያ አምሳላቸው ሰርተውን ነው መሰል።
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር


#ምእራፍ_ሁለት ( #ክፍል_አራት)


#በክፍለማርያም

..ፍፁም ወረቀቱን ገልጦ ስለቤዛዊት እና ስለሱ መከራ የበዛበት የፍቅር ታሪክ መፃፉን ተያይዞታል
ህመሙ እየተሻለዉ ስለሆነ ጥሩ ስሜት ዉስጥ ነዉ ስላለፈዉ ታሪክ እያሰበ ይፅፋል አስደሳች ጊዜወቹ ታዉሰዉት ፊቱ ላይ ደማቅ ፈገግታ እየተነበበ አእምሮዉ ላይ ያለዉን ከወረቀቱ ጋር እያዋሀደዉ ነዉ።

እንደምትወደዉ የነገረችዉን ቀን አስታወሰ ፅፋ የሰጠችዉ ወረቀት ዉል አለበት የተጣሉበትን ቀን መሀል ላይ ፍቃዱ መሀላቸዉ ገብቶ የእህቱን ፎቶ ሚስቱ ናት ብሎ ያወራ ቀን የተፈጠረዉን ሲያስታዉስ የሚፅፉት እጆቹ መንቀጥቀጥ ጀመሩ
ለቤዛዊት ሊያስረዳት ዉሸት መሆኑን ሊያብራራላት ሲጣደፍ መኪና የገጨዉን ሲያስታዉስ መፃፍ ስላልቻለ እስኪቢርቶዉን ወረቀቱላይ ጥሎ በዝምታ ተቀመጠ
ከጎኑ አብሮት የታሰረዉ ማስረሻ የተባለ ታሪሚ የፍፁምን ሁኔታ በአይኖቹ ሲከታተል ስለነበረ
"ምን እየፃፍክ ነዉ ወዳጄ?"
ሲል ለዉቀት መከላከያ ብሎ ዉሀ ዉስጥ ነክሮ አናቱ ላይ ያስቀመጠዉን ፎጣ እያወረደ
ፍፁም የጠየቀዉን ልጅ ትኩር ብሎ ተመለከተዉ ማስረሻ ቀጠን ብሎ ቀዉላላ የሚባል ወጣት ነዉ አይኖቹን ሲያስተዉላቸዉ ከተረገመዉ ፍቃዱ ጋር ተመሳሰሉበት
ለመጀመርያ ግዜ ከተቀመጠበት ተነስቶ ጮሀ
"ምን አገባት ምን አገባህ"
ደም ስሮቹ ተገታትረዉ ንዴት እያንቀጠቀጠዉ መናገሩን ተያያዘዉ
"ለምን አተወኝም ተዉኝ ተዉኝ"
እጆቹን እያወራጨ ወደ ማስረሻ ተጠጋዉ
ማስረሻ በፍፁም ሁኔታ እየተገረመ እና ጥሎት እንደመሄድ እያለ
"እብድ ድሮስ ነብሰ በላ መጨረሻዉ ማበድ ነዉ"
ብሎት ወደ ዉጪ ፍፁምን ትቶት ወጣ።
ፍፁም ግን ማስረሻ የተናገረዉ ንግግር አይምሮዉ ላይ እያቃጨለበት ነበር
"ነብሰበላ ነብሰ በላ ማበድ ማበድ"
እዉነት ነዉ የሰዉ ደም ወደ ሰማይ ይጮሀል ገዳይም የሰላም እንቅልፍ አያገኝም ማንም መጥፎ ሰው ቢሆን እንኳን የፈጠረዉ ፈጣሪ በሞት ካልወሰደዉ በቀር በሰዉ ቢገደል
ገዳዩ ሀጥያቱን ይሸከማል
ቤዛዊት መንገድ ላይ ወደ እስር ቤቱ አቅራቢያ ስትደርስ ካገኘችዉ ጥሩ ምግብ ይሰራሉ ብላ ካሰበችበት ምግብ ቤት ገብታ ለፍፁም በገዛችዉ ሰፊ የምግብ መያዣ ምግብ አስቋጠረችለት
ደስ እያላት ነው በልቧ ፍፁምን ዛሬ እንደምታገኘዉ እንደምታዋራዉ እርግጠኛ ሆናለች።
ዘመድ መጠየቅያዉ ቦታ ላይ ቆማ የፍፁምን ሙሉ ስም ተናግራ መጠበቅ ጀመረች
ፍፁም ከላይ የተጣበቀ ቲሸርት ከስር ያረጀ ቁምጣ በሲሊፐር ለብሶ ሲመጣ በርቀት ተመለከተችዉ ልቧ እየተረበሸ ነዉ አሳዘናት የሴትነት አንጀቷ ባሀሪዋም እሩሩ ስለሆነች ሆድ ብሷት እንባ ማንባት ጀምራ ሲያየኝ እሱም ይጨነቃል ብላ አስባ እንባዋን ወድያዉ ጠራረገች።
የያዘችዉን ምግብ ፖሊሶቹ ፊት ለፊታቸዉ እንድትጎርስ አዘዟት እየጎረሰች ፍፁምን በከርታታ አይኗ እያየችዉ ነዉ ፍፁም አንገቱን ደፍቶ መሬት መሬቱን እያየ ምግቡን በግዴለሽነት ተቀብሏት
መሬት ላይ አስቀምጦ በጨረፍታ እያያት
"ለምን ተቸገርሽ ለኔ ብለሽ መልፋት የለብሽም እኔ የብዙ አመት ፍርደኛ ነኝ..."
የጀመረላትን ሳታስጨርሰዉ
"ሁሌም ቢሆን እጠብቅካለሁ ሁሌም"
ቅድም ያስቆመቻቸዉ እንባወቿ መፍሰስ ጀመሩ።
"አስራ ምናምን አመት..."
አለና የፌዝ ሳቅ ሳቀ
ፍፁም እራሱ ማስረሻ ካዋራዉ ጀምሮ ፀባዩ እየተቀያየረ ነበር ዉስጡ ሰላም እየተሰማዉ አደለም
እሱ በእስር እየበሰበሰ የወጣቷን የቤዛዊትን ህይወትም የቁም እስር ዉስጥ አትክተተዉ የሚል እርኩስ መንፈስ ልቡ ዉስጥ ማደግ እየጀመረ ነበር መንፈሱ ህፃን ስለሆነም እያነጫነጨዉ ነዉ።
"እንዋደድ የለ አትወደኝም ስትል ጠየቀችው ?"
ቤዛዊት አይን አይኑን እያየች
"እወድሻለሁ"
አላትና ጥቂት አስቦ
"ነብሰ ገዳይ ሰው ግን ላንቺ አይጠቅምሽም ሌላ አዲስ ህይወት መጀመር ትችያለሽ አልቀየምሽም ባንቺ ደስተኛ ነኝ ሁለተኛ ግን እኔ ጋር እንዳትመጪ"
አላትና አይኗን ላለማየት እየተጣደፈ ሳይሰናበታት ወደ እስር ቤቱ አመራ።

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
#ሮሜዎና_ዡልዬት


#ክፍል_ስምንት


#ሞግዚት
የተሠራውን ፡ ጉድ ፡ እንግዲህ ፡ ዕወቂው
እርገሚው ፡ ሮሜዎን ፡ ከልብሽም ፡ ናቂው
በቀልሽን ፡ ቂምሽን ፡ አድርጊው ፡ የጸና ፤
በውነቱ ፡ ሮሜዎ ፡ ሰው ፡ አይደለምና ።
አብነት ፡ ይሁንሽ ፡ ይህ ፡ መጥፎ ፡ ደመኛ
ሰውን ፡ አትመኝ ፡ እንግዲህ ፡ ዳግመኛ ፡
ፍቅሩም ፡ደግነቱም ፍሬ ቢስ ፡ ነው ፡ ከንቱ
ፈጽሞ ፡ ሰው ፡ የለም መጥፎ ፡ነው ፡ ሰዓቱ
እንዲህ ፡ ያለ ፡ ነገር ፡ ሮሜዎ ፡ ሲሠራ ፡
ማነው ፡ የሚታመን ? ማነው ፡ ባለአደራ ?

#ዡልዬት
ምንም ፡ አልተገኘ ፡ የሚበጀኝ ፡ ለኔ ፤
ሁለት ፡ ስለት ፡ ያለው ፡ ሰይፍ ፡ ነው ፡ ኀዘኔ
ቲባልት ፡ ባይሞት ኖሮ ሮሜዎ ፡ ይሞታል፤
ቲባልት ፡ ባይሸነፍ ፡ ሮሜዎ ፡ ይረታል!
ሮሜዎን ፡ ከልብሽ ፡ ትይኛለሽ ፡ ጥዪው ፤
ምነው ልቤን ገብተሽ መርምረሽ ብታዪው
ለኔም ፡ገዳይ ፡ ቢሆን ፡ ለናቴም ፡ ላባቴ ፡
ሮሜዎን ፡ ለመጥላት አይችልም ፡አንጀቴ
ቲባልትም ፡መጥፎ ነህ ፡ሮሜዎም አትረባ
መሪር ፡ ነው ፡ ከናንተ ፡ የሚተርፈኝ ፡ እንባ
ባሌ ፡ ካገር' ወጣ ፤ቲባልት ፡ ሞተ ፡ በፊት፤
ሐዘኔ ፡ ዐጓጕል ፡ የሌለው ፡ መድኀኒት ፡
እንደ ምን ፡ አድርጌ ደግሞስ ፡ እስከ መቼ
እኖራለሁ ፡ እኔ ፡ እናንተን ፡ አጥቼ ፡
ከቲባልት ፡ መሞት ፡ ሮሜዎ ፡ ስደቱ ፡
ከሮሜዎ ፡ ስደት ፡ ቲባልት ፡ መሞቱ ፡
ቢሆን ፡ ምን ፡ ቸግረው ፡ ሐዘኔ ፡ በተራ ፤
ለማንኛው ፡ ላልቅስ ፡ ወይ ፡ የኔ ፡ መከራ !
ዛሬ ፡ በሠርጌ ፡ ቀን ፡ ደስ ፡ብሎኝ ፡ መዋሌ
ቀረና ፡ ሰው ፡ ገድሎ ፡ እንዲሰደድ ፡ ባሌ '
ቲባልትም ፡ እንዲሞት ፡ አድርጎ ፡ ዕድሌ ፡
ሐዘን ፡ ከሆነ ፡ ለኔ ፡ የደገሰው ፡
ልቤ ፡ ሳያደላ ፡ እንባዬን ፡ ላፍስሰው ።

#ሞግዚት
በእውነት፡ሴት ልጅ ባሏን፡ከወደደች አይቀር
እንዳንች ፡ አድርጎ ፡ ነው ከልቡና ማፍቀር
ከልብ ፡ አዘንኩልሽ ፡ በጣሙን ፡ አድርጌ ፤
አለበት ፡ ገብቼ ፡ ሮሜዎን ፡ ፈልጌ ፡ .
እኔ ፡ አመጣዋለሁ ፡ እንባሽን ፡ አድርቂው
እመኝታ ፡ ቤትሽ ፡ ግቢና ፡ ጠብቂው ።
በስደተኛነት ፡ ሳይሄድ ፡ ነገ ፡ ርቆ ፡
ተሰነባበቱ ፡ ይምጣ ፡ ተደብቆ ።

#ዡልዬት
መልካም ፡ ነው ፡ ሞግዚቴ ፡ሙሽራ ፡ ሲገባ
አጊጦ ፡ ታጅቦ ፡ በዘፈን ፡ ባበባ ፡
በወግ ፡ በማዕርግ ፡ ባለም ፡ በደስታ ፡
በክብር ፡ ነበረ ፡ በብዙ ፡ እልልታ ፤
ሌሊት ፡ ጨለማውን ፡ ከለላው ፡ አድርጎ ፡
የኔ ፡ ሙሽራ ፡ ግን ፡ ይግባ ፡ ተሸሽጎ ።
እንቢ ፡ ብሎ ፡ እንዳይቀር ፡ጠርተሽ ፡ ስታመጪው
እንቺ ፡ ለምልክት ፡ቀለበቴን ፡ ስጪው ፡
(ቀለበቷን ፡ ሰጠቻት)

#አባ_ሎራ (ባባ ሎራ ፡ ቤት)
ሮሜዎ ፡ ብቅ ፡ በል ፡ውጣ ፡ ከጨለማ ፤
የፍርዱን ፡ ቃል ፡ ይዤ ፡ መጣሁ ልጄ ስማ

#ሮሜዎ
ሳልሰማው ፡ ቢዘገይ ፡ ይሻለኝ ፡ ነበረ ፤
ፍርዱ ፡ ምን ፡ ዐይነት ነው ? ልቤ ፡ ተሸበረ

#አባ_ሎራ
መስፍኑ ፡ ፈቀደ ፡ በቀላል ፡ ሊቀጣ ፤
የሞት ፡ ፍርድ ፡ ቀርቶ ፡ካገር ፡ እንድትወጣ

#ሮሜዎ
ጨካኝ ፡ ቅጣት ፡ እንጂ ፡ ከሞትም ፡ የከፋ
ይህ ፍርድ መሪር ነው ያስቈርጣል ፡ ተስፋ
ዥልዬት ፡ ካለችበት ፡ ከተማ ፡ ወጥቼ ፡
ስደተኛ ፡ ሆኜ ፡ አገሬንም ፡ ትቼ ፡
የምኖረው ፡ ኑሮ ፡ እንደ ፡ ምን ፡ ይገፋል ፣
ቀኑና ፡ ሰዓቱ ፡ ደቂቃው ፡ መች ፡ ያልፋል ፡
እንዴት ፡ እችላለሁ ፡ ዡልዬትን ፡ ለመርሳት
ሲኦል ፡ ነው ፡ ኵነኔ ፡ ሞት ፡ገሃነመ ፡ እሳት

#አባ_ሎራ
ደስታህ ፡ ቀረና ፡ በማመስገን ፡ ፈንታ ፡
ለምን ፡ ትረሳለህ ፡ የእግዜርን ፡ ውለታ ፡
ዐዋጁ ፡ የሚያዘው ፡ የሞት፡ ቅጣት ፡ ነበር'
ለምን ፡ አታስብም ፡ ይህን ፡ ትልቅ ፡ ነገር ፡
ሄደህ ፡ ብትቀመጥ ፡ በማንቱ ፡ ከተማ ፡
አገሩ ፡ ጥሩ ፡ ነው ፡ በጣም ፡ የሚስማማ
ልጄ ሆይ ፡ ቅጣቱ ፡ በጣም ፡ የቀለለ ፡
ጥሩ ፡ ነው ፡ ሺ ፡ ጊዜ ፡ ከሞት ፡ የተሻለ ።

#ሮሜዎ
ያስቡት ፡ አባቴ ፡ ነገሩን ፡ ያስተውሉት ፤
ምኑን ፡ ነው እርስዎ ቀላል ነው ፡ የሚሉት

#አባ_ሎራ
ብስጭት ፡ አታብዛ ፡ በጣም ፡ አትናደድ ፤
ከመሞት ፡ ይሻላል ፡ ሺ ፡ ጊዜ ፡ መሰደድ
ልጄ ፡ ዓለም ፡ሰፊ ፡ ነች ወጥተህ ከቬሮና
የትም ፡ ሄደህ ፡ መኖር ፡ ትችላለህና ።

#ሮሜዎ
ወጥቼ ፡ ከሄድኩኝ ፡ እኔ ፡ ከቬሮና ፡
ውሸት ፡ ነው ፡ አባቴ ፡ ምን ፡ዓለም ፡ አለና፡
ሕይወት ፡ ነው ፡ አይበሉት የምኖረው ኑሮ
ዓለም ፡ እዚህ ፡ ቀረ ፡ ከሚስቴ ጋር አብሮ'
ሰው ነህ እንስሳ ዕንጨት አበባና ፡ቅጠል ፡
ፀሐይ ፡ ተከልሎ ፡ አየር ፡ ሳይቀበል ፡
የኖረ ፡ እንደ ፡ ሆነ ፡ ይሞታል ፡ ይደርቃል፤
ለኔም ፡ እንደዚህ ነው ፡ ስደት የሚሉ፡ ቃል
አገሬ ፡ ንብረቴ ፡ አየሬ ፡ ፀሓዬ ፡
ዓለሜ ፡ ትንፋሼ ፡ ሕይወቴ ፡ ሰማዬ ፡
የነበረችውን ፡ ዝልዬትን ፡ አጥቼ ፡
እሷ ፡ ካለችበት ፡ ከተማ ፡ ወጥቼ ፡
መሄዴ ፡ ከሆነ ፡ እሷም ፡ ከኔ ፡ ርቃ ፡
ነጣጥለው ፡ ከለዩን ፡ የኔ ፡ ነገር ፡ በቃ ።
ሕይወቴም ፡ ኑሮዬም ፡ ሞተ ፡ ተበላሸ ፤
ደስታ ፡ ተለየኝ ፡ ከኔ ፡ ርቆ ፡ ሸሸ ፡
እንግዲህ ፡ መቆሜ ፡ ለምንም ፡ አይበጅ ፤
ይህን ፡ኑሮ ፡አይበሉት መናወዝ ነው እንጅ
ፍርድ ፡ ማሻሻያ ፡ የተባለው ፡ ዘዴ ፡
ከመርዝም ፡ ይብሳል ፡ ከጦር ፡ ከጐራዴ '
ስደት ፡ የሚሉ ፡ ቃል ፡ ጨለማ ነው ፡ ገደል
እኔን ፡ አስጨንቆ ፡ መጣ ፡ ለመግደል ።

#አባ_ሎራ
እረ ፡ ስማኝ ፡ ልጄ ፡ ምክሬንም ፡ ተቀበል ፡
ሞትና ፡ መሰደድ ፡ እኩል ፡ ነው ፡ አትበል

#ሮሜዎ
ተመልሰው ፡ ስደት ፡ ወደሚባለው ፡ ቃል ፡
ሊመጡ ፡ ነውና ፡ አባቴ ፡ ይበቃል ፡
ምን ፡ አደከመዎት ፡ በቃ በዚህ ፡ ዓለም ፡
እኔን ፡ የሚያጥናና ፡ ምንም ፡ ነገር ፡ የለም
ከሞት ፡ የባሰ ፡ ነው ፡ የመከራ ፡ ጭቃ ፤
የሮሜዎ ፡ ነገር ፡ ተከተተ ፡ በቃ ።

#አባ_ሎራ
ዐውቃለሁ ፡ እንዲሆን ፡ ስደትህ ፡ መራራ ፤
ግን ፡ መድኀኒት ፡ አለው ለዚህ ፡ ለመከራ'
ዕረፍት ፡ እንድታገኝ ፡ ባሳብ ፡ በኅሊና ፡
የደረሰብህን ፡ ጭንቅህን ፡ እርሳና ፡
ልብህን ፡ መልሰው ፡ ወደ ፡ ፍልስፍና ።

#ሮሜዎ
ዡልዬትን ፡ ፈጥሮልኝ ካልሰጠኝ ፡ አምጥቶ
የመስፍኑን ፡ ብይን ፡ በጥበብ ፡ አጥፍቶ ፡
እኔን ፡ ካላዳነኝ ፡ የርስዎ ፡ ፍልስፍና ፡
ለምንም ፡ አይበጀኝ ፤ የለውም ፡ ርባና ።
(የዡልዬት'ሞግዚት'ከደጅ'ሆና'በር መታች)

#አባ_ሎራ
ተነሣ ፡ ሮሜዎ ፡ ግባ ፡ ወደ ፡ ጓዳ ፤
ስማ ፡ በር ፡ ይመታል ፡ መጣብን ፡ እንግዳ
ተደበቅ ፡ በቶሎ ፡ ጥግ ፡ ይዘህ ወደ ፡ ጐን
ይይዙሃልና ፡ ያገኙህ ፡ እንደሆን ።
(በሩ ይመታል)

#ሮሜዎ
በስደት ፡ ከሆነ ፡ እኔ ፡ የምቀጣ ፡
ምን ፡ ያስጨንቀኛል ፡ የፈቀደው ፡ ይምጣ

#አባ ፡ ሎራ ።
ለምን ፡ ትሆናለህ ፡ አንተ ፡እንደዚህ ፡ ደረቅ
እባክህ ፡ ግባና ፡ በቶሎ ፡ ተደበቅ ፡ (ሮሜዎ ሄደ)
እንዲህ ፡ ባሁን ፡ ሰዓት ፡ የመጣ ፡ በማታ ፡
ማነው ፡ በጨለማ ፡ በሬን ፡ የሚመታ ?

#ሞግዚት
መጥቻለሁና ፡ ልካኝ ፡ እመቤቴ ፤
የዡልዬት ፡ ሞግዚት ፡ ነኝ ያስገቡኝ ፡ አባቴ

#አባ ፡ ሎራ ።
እንኳን ፡ ደኅና መጣሽ ፡ ነይ ግቢ ወዳጄ፤
(ከፍተውላት ገባች)

#ሞግዚት
ሮሜዎን ፡ አጣሁት ፡ ብፈልገው ፡ ሄጄ ።
ይንገሩኝ ፡ አባቴ ፡ ከመሸ ፡ አሁን ፡ ማታ
አይተው ፡ እንደ ፡ ሆነ ፡ ያለበትን ፡ ቦታ ፡

#አባ ፡ ሎራ ።
በሐዘኑ ፡ ሰክሮ ፡ ያለቅሳል
👍1
፡ ተጨንቆ ፤
ያውልሽ ፡ ከጓዳ ፡ እመሬት ፡ ላይ ፡ ወድቆ

#ሞግዚት
ዠልዬት ፡ እመቤቴም ፡ በዚሁ ፡ ሁኔታ ፡
ስታለቅስ ፡ ዋለች ፡ ይኸው ፡ እስከ ፡ ማታ ፡
ጥሩልኝ ፡ አባቴ ፡ መልክቴን ፡ ልንገረው ።
ሮሜዎ ፡ (ከጓዳ ' ወጣ) ።
ዡልዬት ፡ እንደ ፡ ምን ፡ ነች?መልካም ፡ የነበረው
ልቧ ፡ ተለውጦ ፡ ባደረግሁት ፡ ነገር ፡
አልጠላችኝም ፡ ወይ ? ምላስሽ ፡ ይናገር ፡
ልብሽ ፡ አይደብቀኝ ፡ ንገሪኝ ፡ አትፍሪ ፤
ያየሽውን ፡ ሁሉ ፡ አስተካክለሽ ፡ አውሪ ።
በሠራሁት ፡ ሥራ ፡ ፍቅራችን ፡ መጥፋቱ ፡
እንግዴህ ፡ ወደ ፡ ፊት ፡ ተቀብሮ ፡ መቅረቱ
እርግጥ፡አይደለም ፡ ወይ ? እንዴት፡ ነው ፡መንፈሷ ፤
እኔን ፡ ስታነሣ ፡ ምን ፡ ትላለች ፡ እሷ ።

#ሞግዚት
በሐዘን ፡ ተጨንቃ ፡ ከማልቀስ ፡ በስተቀር ፡
ክፉም ፡ ሆነ ፡ በጎ ፡ ምንም ፡ አትናገር ፡
ቲባልት ሮሜዎ ! አዬ ፡ ጕድ ፡ እያለች ፡
እንባዋን ፡ በማፍሰስ ፡ ቀኑን ፡ሙሉ ፡ ዋለች
ሐዘኗ ፡ ግን ፡ ሆኗል፡ አለመጠን ፡ ብርቱ ፥
ከመሄድህ ፡ በፊት ፡ ተሰነባበቱ ፤
እንሂድ ፡ በቶሎ ፡ መሸብን ፡ ሰዓቱ ።

#ሮሜዎ
ገላዬን ፡ ብወጋ ፡ እስቲ ፡ ከምን ፡ ቦታ ፡
መሞት እንደምችል በቅጽበት ፡ አንዳፍታ
ብልኅ ፡ ነዎትና ፡ ጥበብን ፡ መርማሪ ፤
ተምረው ፡ እንደሆን ፡ ያከላትን ፡ ባሕሪ ፡
በፍጥነት ፡ ይንገሩኝ ፡ አባቴ ፡ አባ ፡ ሎራ ፤
የት ፡ ነው የሰው ነፍሱ ያለችበት ፡ ስፍራ ?
አድርጊያለሁና ፡ ጸጸቷን ፡ መራራ '
ሐዘኔ ፡ጥልቅ ፡ ነው ፡ አልችልም ፡ ልጥናና
በገዛ ፡ እጄ ፡ ልሞት ፡ ቁርጫለሁና ። (ሰይፉን መዘዘ።)

💫ይቀጥላል💫
#እንዲያው_ዝም

ወድሻለሁ ፡ ማለት ፡ አይጠቅም፤አይበቃ
ፍቅሬ ነሽ ማለትም አይጠቅም አይበቃ !
ነፍሴ ፡ ነሽ ፡ ማለትም ፡ ልቤን ፡ አያርሰው

የፍቅራችን ፡ነገር ፡ ዝም፡ ነው ፤ ዝም ፡ ነው

ምን ፡ላርገው፡መውደዴን ፡ለመግለጽ በሙሉ ?
ልሳምሽ ልቀፍሽ ፡ ላልቅስ ወይ ላመሉ ?
እግርሽን ልሳም ወይ ልስገድልሽ ፡ ወይ ?
ዓዋጅ ፡ ልናገረው ፡ በያደባባይ ?
ወረቀት ልጻፍ ወይ ፤ ልላክ ወይ ደብዳቤ
እያንዳንዱን ፡ ቃላት ፡ ወልጄ ፡ ከልቤ ፤?
ገንዘቤን ልስጥሽ ወይ ሳይቆጨኝ መክሰሬ ?
ልታረድ ፡ ልሰዋ ፤ ለፍቅርሽ ፡ ለፍቅሬ ?

ይህ ፡ ሁሉ ፡ ከንቱ ፡ ነው
የልብ ፡ አያደርስም ።
በቃል ፡ ወይ ፡ በሥራ ፡ ፍቅር ፡ አይገለጽም
ይሻላል ፡መሰለኝ፡ እንዲያው ፡ ዝም ፡ እንዲያው ፡ ዝም፤
እንዲያው ፡ በደፈና ፡ ፤ እንደ ፡ ሃይማኖት ፤
ፍቅሬን ፡ ማወቅሽን ፡ ማመን ፡ መረዳት ።

🔘መንግስቱ ለማ🔘
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር


#ክፍል_አምስት


#በክፍለማርያም

....ወደ እስር ቤቱ አመራ
ከጀርባው በህይወቴ አጊንቼ አጣሁዋት ብሎ በትዝታ በናፍቆት እስሩን እስኪጨርስ ከልቡ የማያወጣትን ቤዛዊትን ጨክኖባት ትቷት ጀርባውን ሰጥቷት ከእይታዋ እየራቀ ሄደ
እየተራመደ ዞረህ ተመለስ ዞረህ አዋራት ተስፋ ስጣት ስወጣ ተጋብተን ልጆች ወልደን በፍቅር እንኖራለን በላይ የሚለዉ ስሜት ቢኖርም
መጥፎዉ ስሜት በተቃራኒዉ የምን ተስፋ ነዉ የምታስበዉ ልጅቷም ህይወት አላት አንተ ህይወትህ አበቃ ታሰርክ እና እስዋ ሌላ ህይወት የላትም የሚለዉ ስሜት አሸንፎ ወደ ኋላም ሳይዞር እየተንቀራፈፈ እየተጎተተ መራመዱን ቀጠለ።

ህይወት ግን እስትንፋስ ይዛ እስከቀጠለች ድረስ የሚፈጠረው አይታወቅም አበቃ ተዘጋ ተደመደመ የተባለዉ አንድ ቀን ጊዜዉን ጠብቆ ይጀምራል ይከፈታል
ተጀመረ ተከፈተ የተባለዉም በድንገት ሊዘጋ ይችላል
ህይወትንም ዉስብስብ የሚያረጋት ገፅታ ይሄ ነዉ የተዘጋዉ በር ሲከፈት የሚገኘዉ ደስታ እና የተከፈተዉ በር ሲዘጋ የሚገኘዉ ሀዘን ሲፈራረቅ የህይወት መስመርም ከዚህ ጋር ተቆራኝቶ ይሄዳል።

ቤዛዊት ከአይኗ እየራቀ ያለዉን ከቤተሰብ ከአባት ከእናት ከእህቷ ያስበለጠችዉ ፍቅርን በእሱ የጀመረችዉ ሰዉ እርቋት ሲሄድ በቆመችበት ምንም ሳትንቀሳቀስ ከአይኗ እስኪርቅ ካየችዉ በኋላ በጥልቅ ዝምታ ዉስጥ ሆና መራመድ ጀመረች።

ትላንት ስትጮህ ስታለቅስ ያዩዋት የማረምያ ቤቱ ፖሊሶች
"እንዴት ነሽ እህት..."
እያሉ ሊያዋሯት ሊያፅናኗት ቢሞከሩም ልትመልስላቸዉ ልታዋራቸዉ ይቅርና በዙርያዋ ምን እንደሚፈጠር ሁሉ የምታዉቅ አትመስልም
የቀኝ እጇን የሌባ ጣት ጥፍር አፍዋ ዉስጥ ከታ እየቆረጠች ቢመስላትም በሀሳብ ግን ጀርባዉን ሰጥቷት የሄደዉን ፍፁምን እያሰበች
ህመሞም መጣሁ መጣሁ እያለ አይኖቿ ፍዝዝ እያሉ ትራንስፖርት ይዛ ከኋላ ወንበር ተቀምጣ መጉዋዝ ጀመረች።

"እናቱ ሂሳብ"

በተደጋጋሚ ይጮሀል የታክሲዉ ረዳት ቤዛዊት የፈዘዙት አይኖቿ እየቀሉ ታክሲዉ ላይ ከተለጠፈዉ ጥቅስ ላይ አይኖቿን ተክላ እየሰማችዉ አደለም
ከጎኗ የተቀመጠችዉ ተሳፋሪ ቤዛዊት የምታየውን ጥቅስ አየችዉ
"ቀን ሲጥል ፈራጁ ብዙ ነዉ"
የቤዛዊትን አይኖች ስታይ የሆነ ችግር ዉስጥ ያለች ስለመሰለቻት
"ከኔ ላይ ቁረጥ"
ብላ ለእረዳቱ እየነገረችዉ ወደ ቤዛዊት ተመልሳ ዞራ
"ደህና ነሽ ?"
ስትል ጠየቀቻት የቤዛዊትን ትከሻ ነካ ነካ እያረገች
ቤዛዊት አጠገቧ እያዋራቻት ያለችዉን ልጅ በሚንከራተቱት አይኖቿ እያየቻት
"እ ኔ እንጃ "
ስትል መለሰችላት
"እና አሁን ወዴት እየሄድሽ ነዉ?"
ለቤዛዊት አዝናላት አሟት ይሆን ስትል እያሰበች ልትረዳት ፈልጋ
አለም ላይ ብዙ የሰዉን መጥፎ ማየት የሚፈልጉ ለሰው መልካም የማያስቡ የተረገሙ ሰወች ቢኖሩም ሌሎች ለቁጥር የሚታክቱም ደግ እና መልካም ሰወችም አሉ።
"እማማ ስንቅነሽ ቤት እየሄድኩ ነዉ"
ቤዛዊት አፏ እየተሳሰረ ነገረቻት
ተሳፉሪዋ ከቤዛዊት ጋር አብራት ወርዳ የምትሄድበትን ቀጠሮ ሰርዛ ለመራመድ አቅም ያጣችዉን
ለህመሞ መነሳት ቋፍ ላይ ያለችውን ቤዛዊትን እያታለለች በዘዴ የእማማ ስንቅነሽን ቤት አቅጣጫ እያወጣጣቻት በእግር መጉዋዝ ጀመሩ።

"እማማ ስንቅነሽ እርሶ ኖት አደል"
አለች ተሳፋሪዋ የእማማን ግቢ ቆርቆሮ አጥር አልፈዉ ሲገቡ ቤዛዊትን ገብታ እንድትተኛ እየነገረቻት በእድሜ ገፋ ያሉ ሴትዮ ስታይ እማማ ስንቅነሽ መሆናቸዉን ለማረጋገጥ ብላ
እማማ ለልጅቷ መልስ አልመለሱላትም ፈዛ ነዉልላ የቆመችዉን ቤዛዊትን እሮጠዉ አጠገቧ ደርሰዉ በእጃቸዉ ፊቷን እየደባበሱ
"ምን ሆንሽብኝ ምትኬ ምን ነካብኝ "
እያሉ ደግፈዋት ወደ ዉስጥ ካስገቧት በኋላ አልጋ ላይ እንድትተኛ ነግረዋት ልጅቷን
"የተባረክሽ ልጅ ፈጣሪ ከክፉ ሁሉ ይጠብቅሽ ግቢና ሻይ ጠጪ"
እያሉ እየመረቁ እንድትገባ ቢለምኗትም
"ሌላ ግዜ እመጣለሁ"
እያለች
"ልጆትን ፈጣሪ ይማርሎት"
ብላ ተሰናብታ ወጣች።
ቤዛዊት የአልጋዉን ፍራሽ እየነጨች መሬት ላይ እንደ ቄጤማ እየጎዘጎዘችዉ ነበረ።

💫ይቀጥላል...💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍2
#ሮሜዎና_ዡልዬት


#ክፍል_ዘጠኝ


#አባ_ሎራ
ለምን ፡ ታስባለህ ፡ እንዲህ ፡ ያለ ፡ ነገር ፤
ብላሽ ፡ ሰው ፡ አትሁን ፡ ሲመክሩህ ፡ ተመከር ,እንደ ፡ ሴት ፡ አታልቅስ ፡ እንዳውሬ ፡ አትቈጣ
እንደ፡እብድ፡አትበሳጭ ፥ ከሰው፡ ግብር፡ አትውጣ
ትመስለኝ ፡ ነበረ ፡ በውነቱ ፡ ጠንካራ ፤
ሰው ፡ ለምን ፡ ይረባል ፡ ካልቻለ ፡ መከራ
መቀጣት ፡ ከወደድህ ፡ በገዛ ፡ እጅህ ፡ ሞተህ ፡
ስለምን ፡ ገደልከው ፡ ቲባልትን ፡ ተዋግተህ ?
በገዛ ፡ እጅህ ፡ ብትሞት ፡ ባለማመዛዘን ፡
መግደልህ ፡ እኮ ፡ ነው ሚስትህን ፡ በሐዘን '
ለዚህ ፡ ነው ፡ ልጄ ፡ ሆይ ፡ ኅሊናና ፡ አእምሮ ፡
ከእግዜር ፡ የተሰጠ ፡ ለሰው ፡ ልጅ ፡ ተፈጥሮ'
ዡልዬት ፡ ጠልታኛለች ፡ ብለህ ፡ ስትሠጋ፡
ሰው ፡ ልካ ፡ ጠራችህ ምሕረትን ፡ አድርጋ
ቲባልት ፡ ሊገድልህ ፡ ቢመጣ ፡ ደንፍቶ ፡
በገዛ ፡ ጥጋቡ ፡ ወደቀ ፡ ተወግቶ "
ባንተም የሞት ቅጣት ሊወድቅ የነበረው
በስደት ፡ ለውጦ ፡ መስፍናችን ፡ ሻረው '
ብትመለከተው : በውነቱ ፡ የት ፡ አለ ፤
እንዳንተ ፡ የቀናው ፡ በጣም ፡ የታደለ ፡
ተጠንቀቅ ፡ በውነቱ ፡ ልጄ ፡ በጣም ፡ ሥጋ
ሳታውቀው ፡ ብትቀር ፡ የደስታን ፡ ዋጋ ፡
ኑሮህ ፡ይበላሻል ፡ አለመጠን ፡ ፍራ ፡
ምን ፡ጊዜም ፡ አይለቅህ ፡ ጭንቅና ፡ መከራ ።
ሚስትህን ምከራት ፡ እንዳትሞት ፡ አልቅሳ
መምሸቱ፡ነውና፡ በል ቶሎ ፡ ተነሣ፡
ነገ ፡ ግን ፡ ለመሄድ ፡ ልብህ ፡ይሰናዳ ፤
ውጣ ፡ ከቬሮና ፡ ሌሊት ፡ በማለዳ
ተዛውረህ ተቀመጥ ፡ ሄደህ ፡ ወደ ፡ ማንቱ
እኛ ፡ ጊዜ ፡ አግኝተን ፡ ሲመቸን ፡ ሰዓቱ ፡
ወገኖቻችሁን ፡ በምክር ፡ አስታርቀን ፡
ጋብቻችሁንም ፡ በገሃድ ፡ ኣስታውቀን ፡ .
ላንተም ፡ ከመስፍኑ ፡ ምሕረትን ፡ ጠይቀን
እንጣጣራለን ፡ ቶሎ ፡ እንድትመለስ
እግዜር ፡ይጠብቅህ በል እስከዚያ ፡ ድረስ
አሁን ፡ ወደ ፡ ዡልዬት ፡ በቶሎ ሂድ ፡ ተነሥ

የካፑሌ ሚስት #ካፑሌ #ፓሪስ

#ፓሪስ
ጉዳዩ ዘገየ ፡ በመዋል' በማደር ፤
ታዲያስ እንዴት ፡ ሆነ ፡የጋብቻው ፡ ነገር ?

#ካፑሌ
ነገሩን ፡ ለዡልዬት ፡ ሳልነግር ፡ መቅረቴ ፡
ወድጄን ፡ አይደለም ፡ እንዲህ ፡ መዘግየቴ
በቲባልት ፡ መሞት ፡ አዝናለች ፡ በብርቱ ፤
ታፈቅረው ፡ ነበረ ፡ ከልቧ ፡ በውነቱ ፡
ስለዚህ ፡ ሐዘኑ ፡ ጥቂት ፡ ሳይረሳ ፡
አልቻልኩም ፡ ጕዳዩን ፡ ለጊዜው ፡ ላነሣ ፡
አድርግልኝና ፡ ከልብህ ፡ ይቅርታ ፤
እኔ ፡ እጨርሳለሁ ፡ ነገሩን ፡ አንድ ፡ አፍታ

#ፓሪስ
እውነት ፡ ነው ሐዘኑ ፈጽሞ ፡ አልተመቸም
ተስማምተንበታል ይህን ጕዳይ ፡ መቼም
እሷም እንቢ እንዳትል ፡ እናንተ ፡ አስቡበት

#የካፑሌሚስት _ ።
ግድ የለም ሠርጋችሁ ይሆናል በፍጥነት

#ካፑሌ
ፓሪስ ሆይ አትሥጋ አይዞህ ይህን ጕዳይ
መሄድ ፡ ትችላለህ ፡ ጥለኸው ፡ በኔ ፡ ላይ
እንዴት ፡ ትወጣለች ፡ ከኔ ፡ ፈቃድ ፡ ልጄ ፤
ያቀረብኩላትን ፡ መርጬ ፡ ወድጄ
ያላንድ ፡ ቅሬታ ፡ አለባት ፡ መቀበል ፤
እንዲያውም ፡ እንፍጠን ፡ ዛሬ ነገ ፡ አንበል
በይ ፡ ፍጠኝ ፡ ሚስቴ ፡ ወደ ፡ ልጅሽ ፡ ሂጂ
በዘዴ ፡ በርጋታ፡ነገሩን አስረጂ ፡
መልካሙ ፡ ልጃችን 'ፓሪስ ፡ አንቺን ፡ ወዶ ፡
እኔም ፡ ደስ ፡ ብሎኝ ፡ አባትሽም ፡ ፈቅዶ ፡
ይኸው ፡ በዚህ መሰሞን ሊያገባሽ ፡ ነውና
ተዘጋጂ፡ በያት ፡ በሙሉ ፡ ልቡና '
በል ፡ አንተም ፡ ንገረኝ ፡ እንደምትፈልገው
ሰርጉ ፡ እንዲፈጸም ለመቼ እናድርገው ?

#ፓሪስ
እንደ ፡ እኔ ፡ ሰርጋችን ፡ የራቀ ፡ ከሚሆን ፡
ቢፈጸም ፡ ይሻላል ፡ አሁን ፡ በዚህ ፡ ሰሞን

#ካፑሌ
እንግዲያው መልካም ነው ባጭር እንደግስ
ተክሊሉም ፡ ይፈጸም ፡ በሚመጣው ፡ ኀሙስ ፡
ጃጃታ ፡ አላበዛም ብዙም ፡ ሰው ፡ አልጠራ ፤
ልጄን ፡ እድራለሁ ፡ ብዬም ፡ አላወራ ፡
ሐዘን ፡ ስለ ፡ ሆነ ፡ቲባልት፡ በመሞቱ ፡
ቅር ፡ ያሰኛልና ፤ ዘመድ ፡ በጥቂቱ ፡
በድብቅ ፡ እንጥራ ፡ ነገር ሳናበዛ ፤
እንደዚህ 'ብናደርግ ፡ ወሬው ፡ ሳይነዛ ፡
ጉዳያችን'ያልቃል፡ያግር፡ ሰው ፡ ሳይሰማ ፤
እንግዲህ ፡ መልካም ፡ ነው ፤ በዚሁ 'እንስማማ ።

#ፓሪስ
እኔም ፡ እስማማለሁ ፡ ይሁን ፡ በዚሁ ፡ ቀን
በሉ ፡ እስከዚያው፡ድረስ፡እግዜር፡ይጠብቀን ። (ሄዳ).

#ካፑሌ ፡ (ለሚስቱ )
እንደዚህ ፡ ያለ ፡ ባል ፡ ትልቅ ፡ ሰው ፡ የበቃ
ቢሄዱ ፡ አይገኝም ፡ እግር ፡ እስቲነቃ ፡
በይ ፡ ቶሎ ፡ ፍጠኚ ፡ ወደ ፡ ልጅሽ ፡ ሂጂ ፤
ነገ ፡ ጧት ፡ አሳቧን ፡ ልቧን ፡ አዘጋጂ ።

#ሮሜዎና #ዡልዬት ፡ (በዥልዬት ' መኝታ ፡ ቤት) ።

#ዡልዬት
አይዞህ፡አትቸኵል ፡ አልነጋም ፡ ሌሊቱ ፤
ቁጭ ፡ በል ፡እናውጋ ፡ ገና ፡ ነው ፡ ሰዓቱ ፡
ተመልከት ጨለማ መሬቱን
ሲሸፍን ፡
የሰማናትም ፡ ወፍ ፡ አሁን ፡ ስትዘፍን ፡
ዞትር ፡ ልማዴ ፡ ነው ፡ ሌሊቱ ፡ ሳይነጋ ፡
መጮህ ፡ ትወዳለች ፡ እመነኝ ፡ አትሥጋ

#ሮሜዎ
ይህች ፡ የንጋት ፡ ወፍ ፡ ነች ፡ አሁን ፡ የጮኸችው ፤
ትክክል ፡ ይታያል ፡ ዡልዬት ፡ ተመልከችው
ሰማይ ወገግ፡ አለ ፡ ያው በምሥራቅ በኩል ፤
ሰዓቱ ፡ ደረሰ ፡ እንግዴህ ፡ ልቸኵል ፡
በቬሮና ፡ አድሬ ፡ ቢያገኙኝ ፡ ሳልወጣ ፡
መስፍኑ ፡ ፈርደዋል ፡ በሞት ፡ እንድቀጣ ፡
ልዳን ፡ ያልኩ ፡ እንደሆን ፡ ሕይወቴን ፡ ወድጄ ፡
መሄድ ፡ ይገባኛል ፡ አሁን ፡ ተሰድጄ ።

#ዡልዬት
እኔ ፡ መች ፡ አጣሁት ፡ ይህ ፡ ያሁኑ ፡ ብርሃን ፡
የሰማይ ፡ ፋና ፡ ነው ፡ የኮከብ ፡ ውጋጋን
ሌሊት ፡ በጨለማ ፡ ሳይነጋ ፡ ሌሊቱ ፡
ለምን ፡ ትሄዳለህ ፡ አሁን ፡ ወደ ፡ ማንቱ ፡
አይዞህ ፡ እንጫወት ሌቱ ፡ አልነጋም ፡ ገና
ጊዜ ፡ አለን ፡ እስኪታይ ፡ የንጋቱ ፡ ፋና ።

#ሮሜዎ
ዘፈኑ ፡ ሲወጣ ፡ አልሰማንም ፡ ካፍ
አልነጋም ፡ ሌሊቱ ፡ አልጮኸችም ፡ ወፍ፡
ይህም ፡ በሰማይ ላይ የሚታይ ፡ ውጋጋን አይደለም ፡ የመጣ ፡ ከፀሓይዋ ፡ ብርሃን ፡
ብለን ፡ እንካደው ፤ አምኜ፡ ልቀበል !
ሳልወጣ ፡ ይያዙኝ ፡ ተይዤም ፡ ልገደል "
ካንቺ ፡ ተለይቼ ፡ የሐዘን ፡ ኵነኔ ፡
ከሚያገኘኝ፡ መሞት ፡ እመርጣለሁ ፡ እኔ ።
አልፈራም ፡ ፈጽሞ ፡ በሞት ልቀጣ
ዡልዬት ፡ ከፈቀደች ፡ የፈለገው ፡ ይምጣ ፡
ወፎች አልተንጫጩም ሌሊቱም ፡ አልነጋ
ዡልዬት ጨዋታ አምጪ እንግዴህ እናውጋ፡

#ዡልዬት
እኔ ፡ ብዬ ፡ ነበር ፡ ገና ፡ ነው ፡ ሌሊቱ፤
አሁን ፡ ገና ፡ታየኝ ፡ ትክክል ፡ መንጋቱ ፡
ንጋት ፡ ነው ፡ የመጣው ፡ ሂድ ፡ ቶሎ ፡ ተነሣ፤
አምልጠህ ፡ ሽሽ ፡ ቶሎ ፡ ብረር ፡ በግሥገሣ ፡
እየው ፡ ተመልከተው ፡ የንጋት ፡ ወገግታ፤
ጨለማውን ቀዶ፡ ሄደ ፡ እየበረታ ፡
አስተውለው ፡ መሬቱ ፡ ሲታየን ፡ ተገልጦ ፤
አሞኘችኝ፡ ወፏ ድምፅዋ ፡ ተለውጦ ፡
ፍጠን ፡ ቶሎ ውጣ እየው፡እንደ፡ ነጋ ፤
ተነሥ ፡ ቶሎ ፡ ጥፋ፤ አይንካህ ፡ አደጋ ።

#ሞግዚት
እናትሽ ፡ ነቅተዋል' እመቤቴ ፡ ዕወቂ፤
መንጋቱ ፡ ነውና ' በጣም' ተጠንቀቂ "
ደኅና ሰንብት ፡ ልበል ፡ እኔው ፡ አስቀድሜ
እንግዴህ ፡ ደኅና'ሁን'ሮሜዎ ፡ ወንድሜ ።

#ሮሜዎ
ዡልዬት ደኅና ሁኝ ፡ ደኅና ሰንብች ፡ ፍቅሬ

#ዡልዬት
አደራ ፡ እንዳገኘው ፡ እኔ ፡ ያንተን ፡ ወሬ ፡
ሁል ፡ ጊዜ ጻፍልኝ ፡ መሆንህን ፡ ጤና ፤
መቼ ፡ እንደማገኝህ ፡ አላውቀውምና ።

#ሮሜዎ
መቼም ፡ ቢሆን ፡ ካንቺ ፡ አይለይም ፡ ልቤ
እጽፍልሻለሁ ፡ ሁል ፡ ጊዜ ፡