#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በክፍለማርያም
....መግለጥ ጀመረ..ወረቀቱ ላይ በጥቁር እስኪርቢቶ የተሳለ የልብ ቅርፅ
ምልክት ይታያል መሀሉ ላይ ልቡን አቁዋርጦ የሚያልፍ የጦር
ምልክት በቀይ እስኪርቢቶ የተንጠባጠበ የሚመስል የሚፈስ ደም
የሚመስል ነጠብጣብ ጨምራበታለች ወደታች ማየቱን ሲቀጥል
በትልቁ የተፃፈ
"ልቤን ሰጥቼሀለዉ አትጉዳኝ"
ፍፁም ደነገጠ
"ምን አስባነዉ"
ገና ተዋወቅን እንጂ መጎዳዳት ዉስጥ መች ደረስን ደሞ በወረቀት
ስዕል መሳል ምን የሚሉት ነዉ ሲል እያሰበ ከጀርባዉ መምህር ፍቃዱ ሲመጣ ወረቀቱን ጨምድዶ ኪሱ ዉስጥ ከተተዉ።
ፍቃዱም
"አቶ ፍፁም ዉሎ እንዴት ይዞሀል"
ብሎ አጠገቡ ወንበር ስቦ ተቀመጠ።
ፍፁም ደፈር ብሎ
"ባለፈዉ ስለጀመርክልኝ ስለ ቤዛዊት ታሪክ ቀጥልልኝ"
አለዉ ለመስማት ሰፍ ብሎ
"ቤዛዊት የምታሳዝን ልጅ ናት ዉበትዋን እንደምታየዉ
ቆንጆ ናት ቤተሰቦቿም ከተማዉ ዉስጥ በንግድ ስራ ።የታወቁ ከበርቴወች ናቸዉ "
ፍቃዱ አየር እየሳበ ማዉራቱን ቀጠለ
"ለቤተሰቧ ሁለተኛ ልጅ ስትሆን አንድ ታላቅ እህት አላት
እኔ እስከማዉቀዉ የታወቀ ሳይኸኮሎጂስት ጋር
ህክምና ስታረግ እንደነበር ከዚህ ቀደም አብራት ከምትማር
ተማሪ ጋር ተጣልታ ወላጅ አምጪ ብለናት
ከወላጆችዋ እንደሰማሁት ከሆነ ካደገች በሆላ
በምን እንደጀመራት በማይታወቅ የአይምሮ መታወክ
እና የስሜት መለዋወጥ እንዳለባት
እንደ ተስተካከለች ነግረዉን እና ከሀኪሙ የተሰጠ
ወረቀትም አሳይተዉ ነዉ ትምህርትም የጀመረችዉ
እና በሀሪዋ እንደምታየዉ ለየት ያለ ነዉ ከዚህ በላይ አላዉቅም"
ብሎት ወደ ሌላ እርዕስ ገባ።
ፍፁም ባላወቀዉ ታሪኳ በሰዉ ወሬ ብቻ ቤዛዊትን ማራቅ አልፈለገም እንደዉም ስለስዋ በሰማ ቁጥር
ቀስ በቀስ ፍቅሩ እየጨመረበት ነዉ።
ቁጭ ባለበት የቤዛ መልክ አይምሮዉ ላይ ታየዉ
ፊትዋ አነስ ያለ የቆንጆ ህፃን ልጅ መልክ ነዉ
ፊትዋ ላይ ጠዋት ስትናደድ ካየዉ አስተያየት ዉጪ
ፈገግታ አይለያትም ስትስቅ በሁለቱም ጉንጯ
ጎርጎድ የሚሉ የዉበት ማድመቅያወች የብይ ጉሬ የሚመስሉ ይታያሉ
ከንፈርዋ ጎበዝ ሰዓሊ የሳላቸዉ ነዉ የሚመስሉት
ጥርሷቿ ንጣታቸዉ ብርሀን የማንፀባረቅ ሀይል አሏቸዉ
ቁመቷ በጣም እረጅም ባትባልም ከሱ ቁመት ብዙም አታጥርም
ሰዉነትዋ ሞላ ያለ ነዉ በየመንገዲ አብረዉ ሲመጡ
አንገቱን እያዞረ ሲያያት የነበረ ብዙ ሰዉን ተመልክቷል
ይህን እያሰበ ምንም ይፈጠር ከጎንዋ ሆኜ የሚመጣዉን በፀጋ እቀበላለሁ ሲል ለራሱ ቃል ገባ።
ፍቅር የሰዉን ችግር አይቶ አይርቅም ይረዳል እንጂ
ፍቅር በሰዉ ህመም አይስቅም ያስታምማል እንጂ
ፍፁም ከተቀጣጠሩበት ቦታ ቆማ ከጠበቀችዉ
የቤቱ መግቢያ በር ፊት ለፊትተ ቆሞ እየጠበቃት ነዉ።
ሰዓቱን አስሬ ያያል ቀረችበት መንቆራጠጥ ጀመረ
አጠገቡ የሚገኝ ድንጋይ ላይ ቁጭ አለ
ቤዛዊትን መዉደዱ እርግጥ መሆኑ አሁን ገባዉ
"ምን ሆና ይሆን የቀረችዉ "
እያለ መጨነቅ ጀመረ ሰአቱን ሲመለከት እየመሸ ነዉ
ብዙ ተቀምጦ ከተጨነቀ በኃላ እያሰበ እና እያዘነ ወደ ቤቱ ገባ።
ቤት ገብቶ መፅሀፍ ለማንበብ ገፅ እየገለጠ የቤቱ በር ተንኳኳ
የቤት ኪራይ ለካ ደርሷል እረስቼዉ እያለ ኪሱ ዉስጥ
ያሉትን ብሮች ለአከራዩ ለመክፈል እየቆጠረ በሩን ከፈተዉ።
ቤዛዊት ፊትዋ በእንባ እረጥቦ ፊት ለፊቱ ቆማለች
"ምን ሆነሽ ነዉ የምታለቅሽዉ"
እየተንተባተበ ጠየቃት
መልስ ሳትሰጠዉ ገፍትራዉ እንደራስዋ ቤት ወደ ዉስጥ ገባች
እና የሱ አልጋ ላይ ቁጭ አለች።
ምን እንደሆነች ለመስማት አጠገቡዋ ተቀምጦ አቀፋት
"አትነግሪኝም ቤዚ"
"ከቤት አንተ ጋር ልመጣ ስል አትወጪም ብለዉኝ ተጣልቼ
አሁን እራሱ ተደብቄ ጠፍቼ ነዉ የመጣሁት ቀጠሮህን ለማክበር"
ስታወራ አሁንም እንባዋ እየፈሰሰ ስለሆነ የእሱም አንጀት አልቻለም
በሀዘን ተላወሰ በሁለቱም እጇቹ ጉንጯቿን
አቁዋርጠዉ የሚፈሱትን የእንባ ዘለላወቿን እየጠረገ
አባ'በላት ወድያዉ ማልቀስዋን አቁማ
"ናፍቀሀኝ ነበር"
አለችዉ
ከአልጋዉ ተነስቶ ዉሀ እንድትጠጣ እየሰጣት
"እንዴት በጥቂት ቀን ወደድሽኝ"
አላት አይኖችዋን በፍቅር እያያቸዉ
"ገና መጀመርያ ትምህርት ቤት በር ጋ ቆመክ ነዉ
አይኔን የሳብከዉ ልቤን ደሞ..."
አለችና ሳትጨርሰዉ ሳቀች አጠገቧ ቁጭ ብሎ አሱም ሳቀ
ትንሽ የሆድ የሆዳቸዉን ካወሩ በኃላ ሰዓቱን ሲያይ በጣም
እየመሸ ስለሆነ የእስዋ ቤተሰቦች እንዳይጨነቁ በማሰብ
ፍፁም እንዉጣ ብሏት እጅ ለእጅ ተያይዘዉ ሊሸኛት ወጡ።
መንገዱ ጨለም ያለ ስለነበር ትከሻዋን በእጆቹ አቀፋቸዉ
የየሷም እጇች ወገቡን አቅፈዉት እያወሩ ወደሷ ቤት አመሩ
ቤቷ በር ጋር ደርሰዉ መለያየት ከብዷቸዉ እየተያዩ
የእነ ቤዛዊት ቤት በር ተከፍቶ የቤዛዊት አባት ወጥተዉ
አይናቸዉን በቤዛዊት እና ፍፁም ላይ ተከሉት።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በክፍለማርያም
....መግለጥ ጀመረ..ወረቀቱ ላይ በጥቁር እስኪርቢቶ የተሳለ የልብ ቅርፅ
ምልክት ይታያል መሀሉ ላይ ልቡን አቁዋርጦ የሚያልፍ የጦር
ምልክት በቀይ እስኪርቢቶ የተንጠባጠበ የሚመስል የሚፈስ ደም
የሚመስል ነጠብጣብ ጨምራበታለች ወደታች ማየቱን ሲቀጥል
በትልቁ የተፃፈ
"ልቤን ሰጥቼሀለዉ አትጉዳኝ"
ፍፁም ደነገጠ
"ምን አስባነዉ"
ገና ተዋወቅን እንጂ መጎዳዳት ዉስጥ መች ደረስን ደሞ በወረቀት
ስዕል መሳል ምን የሚሉት ነዉ ሲል እያሰበ ከጀርባዉ መምህር ፍቃዱ ሲመጣ ወረቀቱን ጨምድዶ ኪሱ ዉስጥ ከተተዉ።
ፍቃዱም
"አቶ ፍፁም ዉሎ እንዴት ይዞሀል"
ብሎ አጠገቡ ወንበር ስቦ ተቀመጠ።
ፍፁም ደፈር ብሎ
"ባለፈዉ ስለጀመርክልኝ ስለ ቤዛዊት ታሪክ ቀጥልልኝ"
አለዉ ለመስማት ሰፍ ብሎ
"ቤዛዊት የምታሳዝን ልጅ ናት ዉበትዋን እንደምታየዉ
ቆንጆ ናት ቤተሰቦቿም ከተማዉ ዉስጥ በንግድ ስራ ።የታወቁ ከበርቴወች ናቸዉ "
ፍቃዱ አየር እየሳበ ማዉራቱን ቀጠለ
"ለቤተሰቧ ሁለተኛ ልጅ ስትሆን አንድ ታላቅ እህት አላት
እኔ እስከማዉቀዉ የታወቀ ሳይኸኮሎጂስት ጋር
ህክምና ስታረግ እንደነበር ከዚህ ቀደም አብራት ከምትማር
ተማሪ ጋር ተጣልታ ወላጅ አምጪ ብለናት
ከወላጆችዋ እንደሰማሁት ከሆነ ካደገች በሆላ
በምን እንደጀመራት በማይታወቅ የአይምሮ መታወክ
እና የስሜት መለዋወጥ እንዳለባት
እንደ ተስተካከለች ነግረዉን እና ከሀኪሙ የተሰጠ
ወረቀትም አሳይተዉ ነዉ ትምህርትም የጀመረችዉ
እና በሀሪዋ እንደምታየዉ ለየት ያለ ነዉ ከዚህ በላይ አላዉቅም"
ብሎት ወደ ሌላ እርዕስ ገባ።
ፍፁም ባላወቀዉ ታሪኳ በሰዉ ወሬ ብቻ ቤዛዊትን ማራቅ አልፈለገም እንደዉም ስለስዋ በሰማ ቁጥር
ቀስ በቀስ ፍቅሩ እየጨመረበት ነዉ።
ቁጭ ባለበት የቤዛ መልክ አይምሮዉ ላይ ታየዉ
ፊትዋ አነስ ያለ የቆንጆ ህፃን ልጅ መልክ ነዉ
ፊትዋ ላይ ጠዋት ስትናደድ ካየዉ አስተያየት ዉጪ
ፈገግታ አይለያትም ስትስቅ በሁለቱም ጉንጯ
ጎርጎድ የሚሉ የዉበት ማድመቅያወች የብይ ጉሬ የሚመስሉ ይታያሉ
ከንፈርዋ ጎበዝ ሰዓሊ የሳላቸዉ ነዉ የሚመስሉት
ጥርሷቿ ንጣታቸዉ ብርሀን የማንፀባረቅ ሀይል አሏቸዉ
ቁመቷ በጣም እረጅም ባትባልም ከሱ ቁመት ብዙም አታጥርም
ሰዉነትዋ ሞላ ያለ ነዉ በየመንገዲ አብረዉ ሲመጡ
አንገቱን እያዞረ ሲያያት የነበረ ብዙ ሰዉን ተመልክቷል
ይህን እያሰበ ምንም ይፈጠር ከጎንዋ ሆኜ የሚመጣዉን በፀጋ እቀበላለሁ ሲል ለራሱ ቃል ገባ።
ፍቅር የሰዉን ችግር አይቶ አይርቅም ይረዳል እንጂ
ፍቅር በሰዉ ህመም አይስቅም ያስታምማል እንጂ
ፍፁም ከተቀጣጠሩበት ቦታ ቆማ ከጠበቀችዉ
የቤቱ መግቢያ በር ፊት ለፊትተ ቆሞ እየጠበቃት ነዉ።
ሰዓቱን አስሬ ያያል ቀረችበት መንቆራጠጥ ጀመረ
አጠገቡ የሚገኝ ድንጋይ ላይ ቁጭ አለ
ቤዛዊትን መዉደዱ እርግጥ መሆኑ አሁን ገባዉ
"ምን ሆና ይሆን የቀረችዉ "
እያለ መጨነቅ ጀመረ ሰአቱን ሲመለከት እየመሸ ነዉ
ብዙ ተቀምጦ ከተጨነቀ በኃላ እያሰበ እና እያዘነ ወደ ቤቱ ገባ።
ቤት ገብቶ መፅሀፍ ለማንበብ ገፅ እየገለጠ የቤቱ በር ተንኳኳ
የቤት ኪራይ ለካ ደርሷል እረስቼዉ እያለ ኪሱ ዉስጥ
ያሉትን ብሮች ለአከራዩ ለመክፈል እየቆጠረ በሩን ከፈተዉ።
ቤዛዊት ፊትዋ በእንባ እረጥቦ ፊት ለፊቱ ቆማለች
"ምን ሆነሽ ነዉ የምታለቅሽዉ"
እየተንተባተበ ጠየቃት
መልስ ሳትሰጠዉ ገፍትራዉ እንደራስዋ ቤት ወደ ዉስጥ ገባች
እና የሱ አልጋ ላይ ቁጭ አለች።
ምን እንደሆነች ለመስማት አጠገቡዋ ተቀምጦ አቀፋት
"አትነግሪኝም ቤዚ"
"ከቤት አንተ ጋር ልመጣ ስል አትወጪም ብለዉኝ ተጣልቼ
አሁን እራሱ ተደብቄ ጠፍቼ ነዉ የመጣሁት ቀጠሮህን ለማክበር"
ስታወራ አሁንም እንባዋ እየፈሰሰ ስለሆነ የእሱም አንጀት አልቻለም
በሀዘን ተላወሰ በሁለቱም እጇቹ ጉንጯቿን
አቁዋርጠዉ የሚፈሱትን የእንባ ዘለላወቿን እየጠረገ
አባ'በላት ወድያዉ ማልቀስዋን አቁማ
"ናፍቀሀኝ ነበር"
አለችዉ
ከአልጋዉ ተነስቶ ዉሀ እንድትጠጣ እየሰጣት
"እንዴት በጥቂት ቀን ወደድሽኝ"
አላት አይኖችዋን በፍቅር እያያቸዉ
"ገና መጀመርያ ትምህርት ቤት በር ጋ ቆመክ ነዉ
አይኔን የሳብከዉ ልቤን ደሞ..."
አለችና ሳትጨርሰዉ ሳቀች አጠገቧ ቁጭ ብሎ አሱም ሳቀ
ትንሽ የሆድ የሆዳቸዉን ካወሩ በኃላ ሰዓቱን ሲያይ በጣም
እየመሸ ስለሆነ የእስዋ ቤተሰቦች እንዳይጨነቁ በማሰብ
ፍፁም እንዉጣ ብሏት እጅ ለእጅ ተያይዘዉ ሊሸኛት ወጡ።
መንገዱ ጨለም ያለ ስለነበር ትከሻዋን በእጆቹ አቀፋቸዉ
የየሷም እጇች ወገቡን አቅፈዉት እያወሩ ወደሷ ቤት አመሩ
ቤቷ በር ጋር ደርሰዉ መለያየት ከብዷቸዉ እየተያዩ
የእነ ቤዛዊት ቤት በር ተከፍቶ የቤዛዊት አባት ወጥተዉ
አይናቸዉን በቤዛዊት እና ፍፁም ላይ ተከሉት።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍3
#አራዳ_ላይ_ብቻ
ሰባ ነገስታትን ፥ ሲያስጨንቅ የነበር
ሰማዕቱ ጊዮርጊስ
“ፒያሳ" በሚሏት ፥ በአራዶች ሀገር
የቢራ ቆርኪ ላይ ፥ ምስሉ ታትሞ
የጠርሙስ ልብ ላይ
ድራጎኑን ሲገል ፥ እያየሁት ቆሞ
“አራዳነት ማለት
አፅድቆ ማርከስ ነው” ፥ እላለሁ ባ'ርምሞ፡፡
ደግሞ
ደግሞ
ደግሞ
እዛው አራዳ ላይ
ፒያሳ አደባባይ
ሚሔድ የሚመስል ፥ የማይሔድ ፈረሱ
ሁሌ እዛው ቦታ….
ስሔድ የማላጣው ፥ ሚኒሊክ ንጉሡ
ሀውልቱ ታትሞ
ከፈረሱ ጋራ ፥ እያየሁት ቆሞ
“አራዳነት ማለት
“ሲሔዱ መቆም ነው” ፥ እላለሁ ባ'ርምሞ።
ደግሞ
ደግሞ
ደግሞ
እዛው አራዳ ላይ
ፒያሳ ላይ ያለ ፥ ሌላው አደባባይ
ነቅለው የተከሉት ፥ የእምነት አቡኑ
“አትገዙ” ብሎ!
ገዝቶን ያለፈ ፥ ጴጥሮስ ካህኑ
በሰንሰለት ታስሮ
ከመትረየስ ጋራ ፥ እያየሁት ቆሞ
“አራዳነት ማለት…
ፈቺውን ማሰር ነው” ; እላለሁ ባ'ርምሞ፡፡
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
ሰባ ነገስታትን ፥ ሲያስጨንቅ የነበር
ሰማዕቱ ጊዮርጊስ
“ፒያሳ" በሚሏት ፥ በአራዶች ሀገር
የቢራ ቆርኪ ላይ ፥ ምስሉ ታትሞ
የጠርሙስ ልብ ላይ
ድራጎኑን ሲገል ፥ እያየሁት ቆሞ
“አራዳነት ማለት
አፅድቆ ማርከስ ነው” ፥ እላለሁ ባ'ርምሞ፡፡
ደግሞ
ደግሞ
ደግሞ
እዛው አራዳ ላይ
ፒያሳ አደባባይ
ሚሔድ የሚመስል ፥ የማይሔድ ፈረሱ
ሁሌ እዛው ቦታ….
ስሔድ የማላጣው ፥ ሚኒሊክ ንጉሡ
ሀውልቱ ታትሞ
ከፈረሱ ጋራ ፥ እያየሁት ቆሞ
“አራዳነት ማለት
“ሲሔዱ መቆም ነው” ፥ እላለሁ ባ'ርምሞ።
ደግሞ
ደግሞ
ደግሞ
እዛው አራዳ ላይ
ፒያሳ ላይ ያለ ፥ ሌላው አደባባይ
ነቅለው የተከሉት ፥ የእምነት አቡኑ
“አትገዙ” ብሎ!
ገዝቶን ያለፈ ፥ ጴጥሮስ ካህኑ
በሰንሰለት ታስሮ
ከመትረየስ ጋራ ፥ እያየሁት ቆሞ
“አራዳነት ማለት…
ፈቺውን ማሰር ነው” ; እላለሁ ባ'ርምሞ፡፡
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...አይናቸዉን ቤዛዊት እና ፍፁም ላይ ተከሉት ፍፁም አባትዋ እንደሆኑ ደመ-ነብሱ ነግሮታል
ልቡ ትንሽ መምታት ጀምራለች አቅም አጊንቶ ቢሮጥ
ደስተኛ ነበር እንዴት
"በሯ ድረስ አብሬያት መጣሁ ከመጣሁስ
ለምን እስዋን አስገብቼ አልተመለስኩም"
እያለ እራሱን እየወቀሰ ደርቆ ቀረ።
ቤዛዊት አባትዋን ስታይ ምንም አልመሰላትም
እንደዉም እንደሌሉ ቆጥራቸዉ ፍፁምን ለከንፈሩ የቀረበ ቦታ ስማዉ
"ደህና እደር"
ብላዉ አባትዋን ከቁብ ሳትቆጥር ገፍትራቸዉ ወደ ቤትዋ ገባች።
ፍፁም ከቆመበት ወደ ቤቱ ለመመለስ ጥቂት እንደተራመደ
ኮቴ ስለሰማ አንገቱን በቀስታ አዞረዉ የቤዛዊት አባት
በራቸዉን ዘጋ አርገዉ እየተጠጉት ነዉ።
"ስማ ማነህ አንዴ ቁም"
ድምፃቸዉ እንደ አካላቸዉ ወፈር ያለ ነዉ ያስፈራል።
"እንዴት ብትደፍረኝ ነዉ ልጄን ከቤትዋ አስጠፍተህ
ወዳንተ ማምጣትህ ሳያንስ ቤቴ በር ጋ የምትስማት ውሻ ይመስል"
ቀጠሉ ማዉራት
"ማን እንደሆንኩ አላወከኝም የማንም ወጠጤ
መቀለጃ አደለሁም"
እያሉ ፊቱን በአትኩሮት አዩት።
እሱም ፍርሀት እና የወንድነት ወኔ እየታገለዉ አያቸዉ
አባትዋ ወፍራም አጠር ያሉ ሲሆኑ ሆዳቸዉ በምቾት
ከሰዉነታቸዉ ገዝፎ ይታያል ፀጉራቸዉ ሉጫ ሲሆን
ዉበታቸዉ እሱ ብቻ ነዉ።
አይናቸዉ ድፍርስርስ ያለ ነዉ ያስፈራል
የአፍንጫቸዉ ስፋት የከንፈራቸዉ ዉፍረት
የጥርሳቸዉ መበለዝ ከጉንጫቸዉ እና ከአካላቸዉ
ዉፍረት ጋር የሚያስፈራ ነገር ግን ግርማ ሞገስም አላቸዉ።
በጣም ተጠግተዉ ካዩት በኃላ
"ዉርጋጥ ሁለተኛ ከልጄ ጋር እንዳላይህ"
ብለዉ የለበሱትን ገዋን በግራ እጃቸዉ ገለጥ አርገዉ
ለሱ ያልታየዉን ነገር ለማሳየት ሞክረዉ መልሰዉ እያስተካከሉት
እየተበሳጩ ጥለዉት ወደቤታቸዉ ገቡ።
ፍፁም ቤቱ ገብቶ ማንበብ አልቻለም ተቁነጠነጠ
የሚያረገዉ ሲጠፋዉ አልጋዉ ላይ በጀርባዉ ተዘረረ።
አባትዋ ያሉትን ነገር በንዴት ማብሰልሰል ጀመረ
እኔን ዉርጋጥ ለነገሩ ዱርዬ መስያቸዉ ይሆናል
ሁሉም አባት ለልጁ ጥሩ ሰዉ ነዉ የሚመርጠዉ
እያለ እያሰበ ገልጠዉ ያሳዩት ነገር አሁን ታየዉ
የቤዛዊት አባት በግራ ታፋቸዉ ሽጉጥ ይዘዉ ነበር።
ፍርሀት ወድያዉ ወረረዉ
ስለ ቤዛዊት ግልፅነት የዋህነት እና ፍቅር ሲያስብ ግን
ቀስ እያለ ፍርሀቱ እየለቀቀዉ ልቡ በድፍረት ወኔ ተሞላ
ወድጃታለሁ ወዳኛለች ከኔ እና ከእስዋ ዉጪ የሚያገባዉ
ማንም የለም ብሎ እየተገላበጠ እንቅልፍ አሸለበዉ።
ጠዋት የትምህት ጊቢዉ ዉስጥ ገብቶ
ቤዛዊትን አይንዋን ለማየት እያሰበ ክፍለ ጊዜዉ ሳይደርስ
ወደ እነቤዛዊት ክፍል ገብቶ አየት አርጎት ሌሎች
ተማሪወችም ሲያፈጡበት
"ይቅርታ ለካ ክፍለጊዜዬ አደለም "
ብሎ ሲወጣ
ቤዛዊት እና ጉዋደኛዋ ትዕግሥት ተያይዘዉ ወጡ
አጠገቡ ደርሰዉ ቤዛዊት በቅፅበት ጉንጩን ስማዉ
"ተዋወቃት ትዕግሥት ትባላለች ጉዋደኛዩ ናት"
አለችዉ ቤዛዊት ወደ ጉዋደኛዋ እያሳየችዉ።
በልቡ እኔም ላያት መሄድ አልነበረብኝም
እስዋም እኔን ትምህርት ቤት ዉስጥ ልትስመኝ አይገባም
ደሞ ለጉዋደኛዋ ስለኔ እና ስለእስዋ ማን ንገሪ አላት
እንዴት አታገናዝብም እያለ በጣም እየተናደደ
የተዘረጋዉን የትዕግስት እጅ ጨብጦ ወደ ቢሮዉ አመራ።
ቢሮዉ ሊደርስ ጥቂት እርምጃ ሲቀረዉ ወፍራም አጠር ያሉ ሰዉዬ
አብሯቸዉ ጠብደል ያለ ወጣት ከጎናቸዉ በተጠንቀቅ ቆሞ
ከመምህር ፍቃዱ ቆመዉ እያወሩ ነዉ ።
እንደመደበቅ እየቃጣዉ ጥጉን ያዘ የሚያያቸዉ
የቤዛዊትን አባት መሆኑን እየተጠራጠረ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...አይናቸዉን ቤዛዊት እና ፍፁም ላይ ተከሉት ፍፁም አባትዋ እንደሆኑ ደመ-ነብሱ ነግሮታል
ልቡ ትንሽ መምታት ጀምራለች አቅም አጊንቶ ቢሮጥ
ደስተኛ ነበር እንዴት
"በሯ ድረስ አብሬያት መጣሁ ከመጣሁስ
ለምን እስዋን አስገብቼ አልተመለስኩም"
እያለ እራሱን እየወቀሰ ደርቆ ቀረ።
ቤዛዊት አባትዋን ስታይ ምንም አልመሰላትም
እንደዉም እንደሌሉ ቆጥራቸዉ ፍፁምን ለከንፈሩ የቀረበ ቦታ ስማዉ
"ደህና እደር"
ብላዉ አባትዋን ከቁብ ሳትቆጥር ገፍትራቸዉ ወደ ቤትዋ ገባች።
ፍፁም ከቆመበት ወደ ቤቱ ለመመለስ ጥቂት እንደተራመደ
ኮቴ ስለሰማ አንገቱን በቀስታ አዞረዉ የቤዛዊት አባት
በራቸዉን ዘጋ አርገዉ እየተጠጉት ነዉ።
"ስማ ማነህ አንዴ ቁም"
ድምፃቸዉ እንደ አካላቸዉ ወፈር ያለ ነዉ ያስፈራል።
"እንዴት ብትደፍረኝ ነዉ ልጄን ከቤትዋ አስጠፍተህ
ወዳንተ ማምጣትህ ሳያንስ ቤቴ በር ጋ የምትስማት ውሻ ይመስል"
ቀጠሉ ማዉራት
"ማን እንደሆንኩ አላወከኝም የማንም ወጠጤ
መቀለጃ አደለሁም"
እያሉ ፊቱን በአትኩሮት አዩት።
እሱም ፍርሀት እና የወንድነት ወኔ እየታገለዉ አያቸዉ
አባትዋ ወፍራም አጠር ያሉ ሲሆኑ ሆዳቸዉ በምቾት
ከሰዉነታቸዉ ገዝፎ ይታያል ፀጉራቸዉ ሉጫ ሲሆን
ዉበታቸዉ እሱ ብቻ ነዉ።
አይናቸዉ ድፍርስርስ ያለ ነዉ ያስፈራል
የአፍንጫቸዉ ስፋት የከንፈራቸዉ ዉፍረት
የጥርሳቸዉ መበለዝ ከጉንጫቸዉ እና ከአካላቸዉ
ዉፍረት ጋር የሚያስፈራ ነገር ግን ግርማ ሞገስም አላቸዉ።
በጣም ተጠግተዉ ካዩት በኃላ
"ዉርጋጥ ሁለተኛ ከልጄ ጋር እንዳላይህ"
ብለዉ የለበሱትን ገዋን በግራ እጃቸዉ ገለጥ አርገዉ
ለሱ ያልታየዉን ነገር ለማሳየት ሞክረዉ መልሰዉ እያስተካከሉት
እየተበሳጩ ጥለዉት ወደቤታቸዉ ገቡ።
ፍፁም ቤቱ ገብቶ ማንበብ አልቻለም ተቁነጠነጠ
የሚያረገዉ ሲጠፋዉ አልጋዉ ላይ በጀርባዉ ተዘረረ።
አባትዋ ያሉትን ነገር በንዴት ማብሰልሰል ጀመረ
እኔን ዉርጋጥ ለነገሩ ዱርዬ መስያቸዉ ይሆናል
ሁሉም አባት ለልጁ ጥሩ ሰዉ ነዉ የሚመርጠዉ
እያለ እያሰበ ገልጠዉ ያሳዩት ነገር አሁን ታየዉ
የቤዛዊት አባት በግራ ታፋቸዉ ሽጉጥ ይዘዉ ነበር።
ፍርሀት ወድያዉ ወረረዉ
ስለ ቤዛዊት ግልፅነት የዋህነት እና ፍቅር ሲያስብ ግን
ቀስ እያለ ፍርሀቱ እየለቀቀዉ ልቡ በድፍረት ወኔ ተሞላ
ወድጃታለሁ ወዳኛለች ከኔ እና ከእስዋ ዉጪ የሚያገባዉ
ማንም የለም ብሎ እየተገላበጠ እንቅልፍ አሸለበዉ።
ጠዋት የትምህት ጊቢዉ ዉስጥ ገብቶ
ቤዛዊትን አይንዋን ለማየት እያሰበ ክፍለ ጊዜዉ ሳይደርስ
ወደ እነቤዛዊት ክፍል ገብቶ አየት አርጎት ሌሎች
ተማሪወችም ሲያፈጡበት
"ይቅርታ ለካ ክፍለጊዜዬ አደለም "
ብሎ ሲወጣ
ቤዛዊት እና ጉዋደኛዋ ትዕግሥት ተያይዘዉ ወጡ
አጠገቡ ደርሰዉ ቤዛዊት በቅፅበት ጉንጩን ስማዉ
"ተዋወቃት ትዕግሥት ትባላለች ጉዋደኛዩ ናት"
አለችዉ ቤዛዊት ወደ ጉዋደኛዋ እያሳየችዉ።
በልቡ እኔም ላያት መሄድ አልነበረብኝም
እስዋም እኔን ትምህርት ቤት ዉስጥ ልትስመኝ አይገባም
ደሞ ለጉዋደኛዋ ስለኔ እና ስለእስዋ ማን ንገሪ አላት
እንዴት አታገናዝብም እያለ በጣም እየተናደደ
የተዘረጋዉን የትዕግስት እጅ ጨብጦ ወደ ቢሮዉ አመራ።
ቢሮዉ ሊደርስ ጥቂት እርምጃ ሲቀረዉ ወፍራም አጠር ያሉ ሰዉዬ
አብሯቸዉ ጠብደል ያለ ወጣት ከጎናቸዉ በተጠንቀቅ ቆሞ
ከመምህር ፍቃዱ ቆመዉ እያወሩ ነዉ ።
እንደመደበቅ እየቃጣዉ ጥጉን ያዘ የሚያያቸዉ
የቤዛዊትን አባት መሆኑን እየተጠራጠረ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍1
#የትውልዴ_ድርሳን - 2
ለየመፈክሩ - እንደወነጨፈ፤
ለየነጋሪቱ - እንደተሰለፈ ፤
ባንዲራ ሲያዳውር - ባንዲራ ሲፈትል፤
ባንዲራ አውርዶ - ባንድራ ሲሰቅል ፤
ሰንደቁን ታቅፎ፣ ከጎጡ ጫፍ ሰቅሎ ፤
የሌላውን ሰንደቅ፣ እረግጦ - አቀጣጥሎ ፤
እንደተቆላ ዘር - በየወደቀበት እየበሰበሰ፣ ማጎንቆል ተስኖት፣
ፍሬውን ሳይተካ፤
አያጸድቅ - አያድን፣ የንፉግ ድርጎውን - መብቱን ሲያለካካ ፤
በ‹‹እኔ ይበልጥ ፣ የ«እኔ ይበልጥ እየተፋጠጠ ፤
በገዢው መዳፍ ላይ፣ ሙዝ ሆኖ ተላጠ፡፡
🔘በድሉ ዋቅጅራ🔘
ጥቅንት፣ 2012 ፤
ለየመፈክሩ - እንደወነጨፈ፤
ለየነጋሪቱ - እንደተሰለፈ ፤
ባንዲራ ሲያዳውር - ባንዲራ ሲፈትል፤
ባንዲራ አውርዶ - ባንድራ ሲሰቅል ፤
ሰንደቁን ታቅፎ፣ ከጎጡ ጫፍ ሰቅሎ ፤
የሌላውን ሰንደቅ፣ እረግጦ - አቀጣጥሎ ፤
እንደተቆላ ዘር - በየወደቀበት እየበሰበሰ፣ ማጎንቆል ተስኖት፣
ፍሬውን ሳይተካ፤
አያጸድቅ - አያድን፣ የንፉግ ድርጎውን - መብቱን ሲያለካካ ፤
በ‹‹እኔ ይበልጥ ፣ የ«እኔ ይበልጥ እየተፋጠጠ ፤
በገዢው መዳፍ ላይ፣ ሙዝ ሆኖ ተላጠ፡፡
🔘በድሉ ዋቅጅራ🔘
ጥቅንት፣ 2012 ፤
#የትውልዱ_ድርሳን - 3
ቀረርቶው ጥላቻ ፣
ፉከራው ጭካኔ፣ ሽለላው ድንፋታ፤
መንፈሱ የታሰረ፣ አካሉ የተፈታ::
ልቦናን አስሮ፣ ለወስፋቱ ፈራጅ ፣
የገዛ ወንድሙን ፣ እንደሙክት አራጅ::
ፍቅሩ ያንዳፍታ፣
ህብረቱ ያንዳፍታ፣ የሳፋ ላይ ብቅል፤
መጽኛ ስር የነሳው ፣ መለምላሚያ ቅጠል፡፡
እድሩ የፈረሰ፣
አሟሟቱ ምጸት፣ መሾ ያነወረው ፤
በቁሙ የሞታ፣ ቀባሪ የቸገረው ፤
በጅምላ አሳቢ፣
በመንጋ ተዋጊ፣
የ'ራሱ ባላንጣ፣ ተስፋ የቆረጠ ፤
ሰብኣዊ ሚዛኑን፣ ለጎሳው የሸጠ፡፡
🔘በድሉ ዋቅጅራ🔘
የካቲት፣ 2011፣ አዲስ አበባ፡፡
ቀረርቶው ጥላቻ ፣
ፉከራው ጭካኔ፣ ሽለላው ድንፋታ፤
መንፈሱ የታሰረ፣ አካሉ የተፈታ::
ልቦናን አስሮ፣ ለወስፋቱ ፈራጅ ፣
የገዛ ወንድሙን ፣ እንደሙክት አራጅ::
ፍቅሩ ያንዳፍታ፣
ህብረቱ ያንዳፍታ፣ የሳፋ ላይ ብቅል፤
መጽኛ ስር የነሳው ፣ መለምላሚያ ቅጠል፡፡
እድሩ የፈረሰ፣
አሟሟቱ ምጸት፣ መሾ ያነወረው ፤
በቁሙ የሞታ፣ ቀባሪ የቸገረው ፤
በጅምላ አሳቢ፣
በመንጋ ተዋጊ፣
የ'ራሱ ባላንጣ፣ ተስፋ የቆረጠ ፤
ሰብኣዊ ሚዛኑን፣ ለጎሳው የሸጠ፡፡
🔘በድሉ ዋቅጅራ🔘
የካቲት፣ 2011፣ አዲስ አበባ፡፡
#የተከፈተ_በር
የቤታችን በሩ፣
ከፍተሽው እንደሄድሽ፣ ዛሬም አልተዘጋም
የነበረኝ የለም፣ ለቀማኛ አልሰጋም
እምቢ ካልሽ እምቢ ነው፣ ፅኑ ነው ያንች ቃል
እንደማትመለሽ፣ አእምሮየ ያውቃል።
ግን አልፈርድበትም፣ ልቤ ቢያመነታ
ምኞት በሞላው ቤት፣ እውቀት የለው ቦታ።
ተስፋ አይቆርጥም ደግሞ
ልቤ ህልሙን ያምናል
ይለኛል ደጋግሞ፣
“ትመለስ ይሆናል
ትመለስ ይሆናል
ትመለስ ይሆናል።”
እኔም በምላሹ፣ ልቤን ፊት ሳልሰጠው
እንዲህ እለዋለሁ፣ ተስፋ ላስቆርጠው
“ጠጠር ላይቀቀል፣ አልማዝ ላይከለስ
በደመና ራስጌ፣ ጎጆ ላይቀለስ
እኔም አልሻሻል፣ እሷም ኣትመለስ።
ሰማይ ሰም ይመስል፣ ሲንጠባጠብ ቀልጦ
የረር ፈልሶ ቢሸሽ፣ ቢከተል እንጦጦ
ባሕሮች ቢከስሙ፣ ምድር ብትናወጥ
እሷም አትመለስ፣ እኔም አልለወጥ።
በዙሪያየ ያለው ጸጋ ብዙ ነበር
ግና ክንፍ አብቅሎ
ፍቅርሽ ጥሎኝ ሲበር
ከኔ ጋር የቀረው
የተቆለፈ ልብ፣ የተከፈተ በር።
🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
የቤታችን በሩ፣
ከፍተሽው እንደሄድሽ፣ ዛሬም አልተዘጋም
የነበረኝ የለም፣ ለቀማኛ አልሰጋም
እምቢ ካልሽ እምቢ ነው፣ ፅኑ ነው ያንች ቃል
እንደማትመለሽ፣ አእምሮየ ያውቃል።
ግን አልፈርድበትም፣ ልቤ ቢያመነታ
ምኞት በሞላው ቤት፣ እውቀት የለው ቦታ።
ተስፋ አይቆርጥም ደግሞ
ልቤ ህልሙን ያምናል
ይለኛል ደጋግሞ፣
“ትመለስ ይሆናል
ትመለስ ይሆናል
ትመለስ ይሆናል።”
እኔም በምላሹ፣ ልቤን ፊት ሳልሰጠው
እንዲህ እለዋለሁ፣ ተስፋ ላስቆርጠው
“ጠጠር ላይቀቀል፣ አልማዝ ላይከለስ
በደመና ራስጌ፣ ጎጆ ላይቀለስ
እኔም አልሻሻል፣ እሷም ኣትመለስ።
ሰማይ ሰም ይመስል፣ ሲንጠባጠብ ቀልጦ
የረር ፈልሶ ቢሸሽ፣ ቢከተል እንጦጦ
ባሕሮች ቢከስሙ፣ ምድር ብትናወጥ
እሷም አትመለስ፣ እኔም አልለወጥ።
በዙሪያየ ያለው ጸጋ ብዙ ነበር
ግና ክንፍ አብቅሎ
ፍቅርሽ ጥሎኝ ሲበር
ከኔ ጋር የቀረው
የተቆለፈ ልብ፣ የተከፈተ በር።
🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...የቤዛዊት አባት መሆናቸዉን እየተጠራጠረ።
ፍፁም እየተደናገጠ ፊቱን እንዳያዩት እየተሳቀቀ ወደ
መፀዳጃ ቤት ገብቶ ፊቱን ዉሀ አስነካዉ
ከዚህ በኃላ የሚፈጠረዉን የሱን እና የቤዛዊትን እጣ ፋንታ በአይነ ህሊናዉ እያሰበ።
ከማስተማሩ ሲታገድ የቤዛዊት አባት ተኩሰዉ ሲገሉት
ሲያይ በፍጥነት ፊቱን ድጋሜ ዉሀ አስነክቶት
የቤዛዊት አባት መሄድ አለመሄዳቸዉን
ለማረጋገጥ አንገቱን አጮልቆ ተመለከተ የሉም ሄደዋል።
እኔ እዚህ ማስተማሬን አዉቀዉ እንዳይሆን እያለ
ወደ መምህራን ማረፍያ ገብቶ ፍቃዱን ፈልጎ አገኘዉ።
"እሺ ፍቄ አብረዉክ የነበሩት ማናቸዉ"
የእጆቹን ጣቶች ያልበላዉን ፀጉሩን እንደማከክ እያረገ
"የቤዛዊት አባት ናቸዉ ስለልጃቸዉ ሁኔታ ለመጠየቅ ነዉ"
ቀለል አርጎ መለሰለት
የእፎይታ ተንፍሶ ለማስተማር ወደ ሌላ ክፍል አመራ።
ጊዜዉ እየገፋ ነዉ መስከረም አልፎ ለጥቅምት
ቦታዉን ለቋል ፍፁም እና ቤዛዊት በድብቅ
የፍፁም ቤት ዉስጥ ይገናኛሉ
አብረዉ የፍቅር ጊዜ ማሳለፍ ከጀመሩ ሰነባብተዋል
ስለ ቤዛዊት በፊት እንደሰማዉ እንደሰማዉ ወሬ
ምንም የአይምሮ ህመም አይታይባትም ጤነኛ ነበረች።
አንድ ቀን ፍፁም ከሌላ ሴት ተማሪ ጋር ቆሞ ስለ ትምህርት ጉዳይ እያወሩ ቤዛዊት አይታዉ
አዉርቶ ሲጨርስ የተጠቀለለ ወረቀት
ሰጥታዉ ሄደች።
ፍፁም ወረቀቱን ገልጦ አነበበዉ
"ከትምህርት በኃላ ቤትክ ቀስ ብለክ ና ስጦታ አለክ"
ደስ እያለዉ ወረቀቱን ኪሱ ከቶ ዛሬ ቤቱ ሲገባ
ምን አይነት አስደሳች የፍቅር ጊዜ እንደሚጠብቀዉ
አያሰበ ደስ አለዉ።
የቀኑ ትምህርት አልቆ ተማሪወች ወደ እየቤታቸዉ
መሄድ ጀምረዋል እሱም ቤዛዊት እንዳለችዉ
ትንሽ ስዓት ለመግደል አስቦ ወደ ላይብረሪ አመራ።
መንገድ ላይ ወደ ዉጪ በመዉጣት ላይ ያሉ ተማሪወች
ጮክ ብለዉ ያወራሉ
"ቤዛዊት"
የሚባል ስም ስለሰማ ከመሀል አንዱን ተማሪ ጠርቶ
"ምን ተፈጥሮ ነዉ"
አለዉ አንገቱን ከታች ወደ ላይ እየነቀነቀ
የጠየቀዉ ተማሪ እንደ ትወና እያረገዉ
እንዴት አይነት ድብድብ መሆኑን ለማሳወቅ እጆቹን እያወናጨፈ
"በለዉ ቲቸር ቤዛዊት እና ህሊና የሚገርም ፀብ ተጣሉ"
አለዉ በወኔ ድምፁን ከፍ አርጎ።
ፍፁም ማሰብ አቃተዉ ህሊና ቅድም ስለ ትምህርት
ሲያዋራት የነበረችዋ ልጅ ናት።
ወደ ቤቱ ሊደርስ ሲል አከራዩ ይዘዉ አስቆሙት
"አቶ ፍፁም እጮኛህ ምን ሆና ነዉ ብቻዋን የምታወራዉ
ዉስጥ ገብታለች ተጣልታችሁ ነዉ እንዴ "
አሉት ለማስታረቅ እንደ እናት እያዩት
አከራዩ ደርባባ የቤት እመቤት ናቸዉ ፊታቸዉ ደግነታቸዉን
እና አዛኝነታቸዉን ይናገራል ቤት ኪራይ እራሱ እሱ አስቦ ካልሰጣቸዉ ጠይቀዉት አያዉቁም
የዉሸት
"ትንሽ ተጋጭተን ነዉ "
እያለ ትላንት ኪሱ ውስጥ አስቀምጦት የነበረዉን
የቤት ኪራይ ብር ሰጥቷቸዉ ወደ ቤቱ አመራ።
ወደ ዉስጥ ሲዘልቅ አንጀት የሚያላዉስ የምግብ ሽታ
እየሸተተዉ ጠረጴዛው ላይ በሚስብ አቀራረብ
ምግብ ቀርቦ ከጎኑ ሁለት
ብርጭቆ ቀርቦ አንደኛዉ የተጋመሰ የተጠጣ ቢራ
በዉስጡ ይዞል እና የተደረደሩ የቢራ ጠርሙሶች ይታየዋል።
ቤዛዊት ስታየዉ አቅፋዉ ትንሽ ከቆየች በኃላ
እንዲቀመጥ ወንበር ሳበችለት ፍፁም ተቀምጦ
ለምን ተጣላሽ ሊላት አለና የምታረገዉን ነገር ሲያይ ደስ እንዲላት ዝምታን መረጠ።
ቤዛዊት ምግቡን በልተዉ ቢራዉን ጠጥተዉ ከጨረሱ በኃላ
አልጋ ላይ እንዲቀመጥ እና ልብሱን እንዲያወልቅ አዘዘችዉ
ማዉለቅ አልፈለገም ግራ የተጋባ ስሜት ውስጥ
ገብቷል አለማዉለቁን ስታይ ቀስ ብላ
በፍቅር እየተጠጋችዉ የሸሚዙን ቁልፍ ፈታታት
ሙሉ ለሙሉ ሸሚዙን አወለቀችዉ ቀጥላም
እስዋ የለበሰችዉን ቀሚስ አዉልቃ ፊቱ ቆመች።
ፍፁም ከጠጣዉ መጠጥ ጋ ተያይዞ አይኖቹ ፈዘዝ ብለዉ
ፊትዋን አየዉ አይኖቿ ደፍርሰዋል ፊትዋ ተለዋዉጧል
"ምን ሆንሽ ቤዚ"
አላት በለሰለሰ ድምፅ
ቤዛዊት የፍፁምን አይን እያየች የፊዝ ሳቅ ከሳቀች በኃላ ።
ከእሷ ይወጣል ብሎ በማያስበዉ ድምፅ
ጩሀቷን አቀለጠችዉ ...
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...የቤዛዊት አባት መሆናቸዉን እየተጠራጠረ።
ፍፁም እየተደናገጠ ፊቱን እንዳያዩት እየተሳቀቀ ወደ
መፀዳጃ ቤት ገብቶ ፊቱን ዉሀ አስነካዉ
ከዚህ በኃላ የሚፈጠረዉን የሱን እና የቤዛዊትን እጣ ፋንታ በአይነ ህሊናዉ እያሰበ።
ከማስተማሩ ሲታገድ የቤዛዊት አባት ተኩሰዉ ሲገሉት
ሲያይ በፍጥነት ፊቱን ድጋሜ ዉሀ አስነክቶት
የቤዛዊት አባት መሄድ አለመሄዳቸዉን
ለማረጋገጥ አንገቱን አጮልቆ ተመለከተ የሉም ሄደዋል።
እኔ እዚህ ማስተማሬን አዉቀዉ እንዳይሆን እያለ
ወደ መምህራን ማረፍያ ገብቶ ፍቃዱን ፈልጎ አገኘዉ።
"እሺ ፍቄ አብረዉክ የነበሩት ማናቸዉ"
የእጆቹን ጣቶች ያልበላዉን ፀጉሩን እንደማከክ እያረገ
"የቤዛዊት አባት ናቸዉ ስለልጃቸዉ ሁኔታ ለመጠየቅ ነዉ"
ቀለል አርጎ መለሰለት
የእፎይታ ተንፍሶ ለማስተማር ወደ ሌላ ክፍል አመራ።
ጊዜዉ እየገፋ ነዉ መስከረም አልፎ ለጥቅምት
ቦታዉን ለቋል ፍፁም እና ቤዛዊት በድብቅ
የፍፁም ቤት ዉስጥ ይገናኛሉ
አብረዉ የፍቅር ጊዜ ማሳለፍ ከጀመሩ ሰነባብተዋል
ስለ ቤዛዊት በፊት እንደሰማዉ እንደሰማዉ ወሬ
ምንም የአይምሮ ህመም አይታይባትም ጤነኛ ነበረች።
አንድ ቀን ፍፁም ከሌላ ሴት ተማሪ ጋር ቆሞ ስለ ትምህርት ጉዳይ እያወሩ ቤዛዊት አይታዉ
አዉርቶ ሲጨርስ የተጠቀለለ ወረቀት
ሰጥታዉ ሄደች።
ፍፁም ወረቀቱን ገልጦ አነበበዉ
"ከትምህርት በኃላ ቤትክ ቀስ ብለክ ና ስጦታ አለክ"
ደስ እያለዉ ወረቀቱን ኪሱ ከቶ ዛሬ ቤቱ ሲገባ
ምን አይነት አስደሳች የፍቅር ጊዜ እንደሚጠብቀዉ
አያሰበ ደስ አለዉ።
የቀኑ ትምህርት አልቆ ተማሪወች ወደ እየቤታቸዉ
መሄድ ጀምረዋል እሱም ቤዛዊት እንዳለችዉ
ትንሽ ስዓት ለመግደል አስቦ ወደ ላይብረሪ አመራ።
መንገድ ላይ ወደ ዉጪ በመዉጣት ላይ ያሉ ተማሪወች
ጮክ ብለዉ ያወራሉ
"ቤዛዊት"
የሚባል ስም ስለሰማ ከመሀል አንዱን ተማሪ ጠርቶ
"ምን ተፈጥሮ ነዉ"
አለዉ አንገቱን ከታች ወደ ላይ እየነቀነቀ
የጠየቀዉ ተማሪ እንደ ትወና እያረገዉ
እንዴት አይነት ድብድብ መሆኑን ለማሳወቅ እጆቹን እያወናጨፈ
"በለዉ ቲቸር ቤዛዊት እና ህሊና የሚገርም ፀብ ተጣሉ"
አለዉ በወኔ ድምፁን ከፍ አርጎ።
ፍፁም ማሰብ አቃተዉ ህሊና ቅድም ስለ ትምህርት
ሲያዋራት የነበረችዋ ልጅ ናት።
ወደ ቤቱ ሊደርስ ሲል አከራዩ ይዘዉ አስቆሙት
"አቶ ፍፁም እጮኛህ ምን ሆና ነዉ ብቻዋን የምታወራዉ
ዉስጥ ገብታለች ተጣልታችሁ ነዉ እንዴ "
አሉት ለማስታረቅ እንደ እናት እያዩት
አከራዩ ደርባባ የቤት እመቤት ናቸዉ ፊታቸዉ ደግነታቸዉን
እና አዛኝነታቸዉን ይናገራል ቤት ኪራይ እራሱ እሱ አስቦ ካልሰጣቸዉ ጠይቀዉት አያዉቁም
የዉሸት
"ትንሽ ተጋጭተን ነዉ "
እያለ ትላንት ኪሱ ውስጥ አስቀምጦት የነበረዉን
የቤት ኪራይ ብር ሰጥቷቸዉ ወደ ቤቱ አመራ።
ወደ ዉስጥ ሲዘልቅ አንጀት የሚያላዉስ የምግብ ሽታ
እየሸተተዉ ጠረጴዛው ላይ በሚስብ አቀራረብ
ምግብ ቀርቦ ከጎኑ ሁለት
ብርጭቆ ቀርቦ አንደኛዉ የተጋመሰ የተጠጣ ቢራ
በዉስጡ ይዞል እና የተደረደሩ የቢራ ጠርሙሶች ይታየዋል።
ቤዛዊት ስታየዉ አቅፋዉ ትንሽ ከቆየች በኃላ
እንዲቀመጥ ወንበር ሳበችለት ፍፁም ተቀምጦ
ለምን ተጣላሽ ሊላት አለና የምታረገዉን ነገር ሲያይ ደስ እንዲላት ዝምታን መረጠ።
ቤዛዊት ምግቡን በልተዉ ቢራዉን ጠጥተዉ ከጨረሱ በኃላ
አልጋ ላይ እንዲቀመጥ እና ልብሱን እንዲያወልቅ አዘዘችዉ
ማዉለቅ አልፈለገም ግራ የተጋባ ስሜት ውስጥ
ገብቷል አለማዉለቁን ስታይ ቀስ ብላ
በፍቅር እየተጠጋችዉ የሸሚዙን ቁልፍ ፈታታት
ሙሉ ለሙሉ ሸሚዙን አወለቀችዉ ቀጥላም
እስዋ የለበሰችዉን ቀሚስ አዉልቃ ፊቱ ቆመች።
ፍፁም ከጠጣዉ መጠጥ ጋ ተያይዞ አይኖቹ ፈዘዝ ብለዉ
ፊትዋን አየዉ አይኖቿ ደፍርሰዋል ፊትዋ ተለዋዉጧል
"ምን ሆንሽ ቤዚ"
አላት በለሰለሰ ድምፅ
ቤዛዊት የፍፁምን አይን እያየች የፊዝ ሳቅ ከሳቀች በኃላ ።
ከእሷ ይወጣል ብሎ በማያስበዉ ድምፅ
ጩሀቷን አቀለጠችዉ ...
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
❤1👍1
#ለልደቴ
እጣ ፈንታ
ባልመረጥሁት ዘመን፣ ባልመረጥኩት ቦታ
ጎዳና ላይ አውጥቶኝ
እንቅፋት በየርምጃው፣ ተለክቶ ተሰጥቶኝ
ሲሻኝ እየሸሸሁ፣ ሲሻኝ እየተዋጋሁ
እንቅፋቴን በባዶ እግሬ፣ እንደ እንቧይ እየለጋሁ
ሕምምን እየሸወድኩ፣ ሞትን እያዘናጋሁ።
መኖር ሳልጠላ
ግና ለመኖር ብዬ፤ የግብር እንጀራን ሳልበላ
አሜን የሚል ቃል ሳይወጣኝ
በጌቶች ፊት በፍርሃት፣ ጎንበስ ጎንበስ ሳያቃጣኝ
ነፃነቴን ከጥልቁ ሥር፣ እንደ ብርቅ አሳ አስግሬ
ያሻኝን ተናግሬ
ተጨብጭቦልኝ
አንዳንዴም ተወግሬ
ያለ አጀብ ያለጋሻ ጃግሬ
ባሻኝ እየገሰገስኩ
እንደ ወፍ በነፃነት፣ አገር ምድሩን እያዳረስኩ
በመረጥሁት ዛፍ ስር ተኝቼ
በጅሎች ካብ ስር ሸንቼ
እያወጋሁ፣ እየገጠምኩ፣ እያለመጥሁ፣ እያላገጥሁ
እንባዎቼን በቃል ምትሐት፣ ወደ ሣቅ እየለወጥሁ፡
እየጣልኩ እየወደቅሁ፤ እየማቀቅሁ እየደላኝ
እንሆ አርባ አመት ሞላኝ!
🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
እጣ ፈንታ
ባልመረጥሁት ዘመን፣ ባልመረጥኩት ቦታ
ጎዳና ላይ አውጥቶኝ
እንቅፋት በየርምጃው፣ ተለክቶ ተሰጥቶኝ
ሲሻኝ እየሸሸሁ፣ ሲሻኝ እየተዋጋሁ
እንቅፋቴን በባዶ እግሬ፣ እንደ እንቧይ እየለጋሁ
ሕምምን እየሸወድኩ፣ ሞትን እያዘናጋሁ።
መኖር ሳልጠላ
ግና ለመኖር ብዬ፤ የግብር እንጀራን ሳልበላ
አሜን የሚል ቃል ሳይወጣኝ
በጌቶች ፊት በፍርሃት፣ ጎንበስ ጎንበስ ሳያቃጣኝ
ነፃነቴን ከጥልቁ ሥር፣ እንደ ብርቅ አሳ አስግሬ
ያሻኝን ተናግሬ
ተጨብጭቦልኝ
አንዳንዴም ተወግሬ
ያለ አጀብ ያለጋሻ ጃግሬ
ባሻኝ እየገሰገስኩ
እንደ ወፍ በነፃነት፣ አገር ምድሩን እያዳረስኩ
በመረጥሁት ዛፍ ስር ተኝቼ
በጅሎች ካብ ስር ሸንቼ
እያወጋሁ፣ እየገጠምኩ፣ እያለመጥሁ፣ እያላገጥሁ
እንባዎቼን በቃል ምትሐት፣ ወደ ሣቅ እየለወጥሁ፡
እየጣልኩ እየወደቅሁ፤ እየማቀቅሁ እየደላኝ
እንሆ አርባ አመት ሞላኝ!
🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...ጩሀቷን አቀለጠችዉ
ፍፁም ያልጠበቀዉ እና ያላሰበዉ ነገር ስለተፈጠረ ዉሀ ሆኖ ቀረ እግሮቹ መንቀጥቀጥ ጀምረዋል
የቤዛዊት መታመም አሁን ሁሉ ነገር ግልፅ ሆነለት
ነገር ግን ከረፈደ በኃላ ነዉ ምንም ማረግ አልቻለም።
በተቀመጠበት አልጋ የቤዛዊት ጩሀት ጆሮዉ ላይ ያስተጋባል
ጭ ዉ የሚል ስሜት ጆሮዉን አልፎ አይምሮዉ
ዉስጥ ያለማቋረጥ ይዞራል።
"ደፈረኝ"
የሚሉ ቃላት ከጩሀቱ ገዝፈዉ ይሰሙታል ነገር ግን
ከአልጋዉ ተነስቶ እንኳን ለመቆም አቅም አጣ።
የቤዛዊትን ጩሀት የሰሙ የፍፁም አከራዮች ከነሱ አልፎ
የሰፈሩ ነዋሪወች ጠባቡን የፍፁምን ቤት
በርግደዉ ሲገቡ ጩሀቱን የሰሙ በአቅራቢያዉ የነበሩ
የፖሊስ አባሎችም ተከታትለዉ ገቡ።
ቤዛዊት በፍጥነት ልብሷን ለባብሳ የፍፁም ቤት አከራይ
ሴትዮ ላይ ተጠመጠመችባቸዉ።
ፍፁምን የተከራየበት አካባቢ የነበሩ ወጣቶች እንደ በ'ዳይ በጥያቄ እያዋከቡት ነዉ።
ከፓሊሶቹ አንዱ
"ልብስ ደርብ እና ለጥያቄ ጣብያ እንሄድ"
ስላለዉ ፍፁም በሀፍረት እና በድንጋጤ አጠገቡ
ወልቆ የተቀመጠዉን ሸሚዙን እየለበሰ ቤዛዊትን ለመፈለግ አይኖቹን ቤቱ ዉስጥ ወሬ ለማድመቅ የቆሙትን
ሰወች ማየት ጀመረ የሁሉም ሰዉ ፊት እሱን በንቀት አስተያየት እያዩት ነዉ አከራዩም ሳይቀሩ
ተለወጡበት እየገላመጡት ነዉ።
ቤዛዊት ግን ከሰወቹ መሀል የለችም በግርግሩ ወሀል ወጥታ ሄዳለች።
ፍፁም በምሽት ፖሊስ ጣብያ አግዳሚ ላይ ቁጭ ብሎ
ማሰብ ተስኖት ትካዜ ዉስጥ ገብቶ የመርማሪዉ ፖሊስ ድምፅ አባነነዉ።
ለመርማሪዉ የተጠየቀዉን ሀሉ መመለስ ጀመረ ወደ መጨረሻ ለተጠየቀዉ መልስ ቤዛዊት ፍቅረኛዉ እንደሆነች
እና በጊዜያዊ ፀብ ከሌላ ሴት ጋ አይታዉ በስህተት ተርጉማዉ እንደተጋጩ አርጎ ነግሯቸዉ ከሳሽ ከመጣ
ብለዉ እዛዉ አሳድረዉት በነጋታዉ ከረፋፈደ በኃላ ለቀቁት።
ከፖሊስ ጣብያዉ እንደወጣ በተስፋ መቁረጥ ዉስጥ ሆኖ ቤዛዊትን እየረገማት እንባ እየተናነቀዉ ላለማልቀስ
ከራሱ ጋር እየታገለ ከተከራየበት ቤት ደረሰ።
ገና የግቢዉን በር ሲገባ በፊት በፈገግታ እና በፍቅር የሚያዩት አከራዩ እሳት ጎርሰዉ እና ተኮሳትረዉ ጠበቁት
"ዛሬዉኑ ቤቴን ለቀህ እንድትወጣ"
ፍፁም ንፁህነቱን ሊያወራ ሲሞክር ጉሮሮዉ ደረቀበት
ቃላቶች ከአፉ ማዉጣት አቃተዉ
"እ እ ማዘር..."
"ምንም ወሬ አልፈልግም ዉልቅ በል"
ሁለት ቦታ የታጠፈ ወረቀት በእጁ እየሰጡት ።
ወደ ቤታቸዉ
"እንዲህ ነችና"እያሉ ገቡ።
ቤቱ ክፍት አድሮ ነዉ የዋለዉ እንደዛ የተስተካከለ እና
ዉበት ያለዉ ቤት ምንቅርቅሩ ወጥቷል በቆመበት እጁ ላይ
ያለዉ ወረቀት የማን እንደሆነና ምን እንደሚል ለማንበብ ገለጠዉ።
የቤዛዊት እጅ ፅሁፍ ነዉ እስዋ ናት በወረቀት አየፃፈች መስጠት ያስለመደችዉ ገና ሳያነበዉ እንባዉ ወረቀቱ ላይ ዱ ብ ዱብ ማለት ጀመረ አይኖቹ በእንባዉ ጭጋግ
ስለተሸፈኑ ማንበብ አልቻለም።
ቤዛዊትን ከልቡ ወዷት ነበር "ፍቅር ይሄ ነዉ" እያለ
ለራሱ የማይመልሰዉ ጥያቄ እየጠየቀ እንባዉን
በቀኝ እጁ እየጠረገ ወረቀቱን ድጋሜ አየዉ።
"ፍፁም ምን እንደሆንኩ...ምን እንዳረኩ አላዉቅም..
ማጥፋቴ ጠዋት ነዉ የገባኝ
እወድሃለሁ
ይቅርታ አርግልኝ
አንተን አጥቼ ግን መኖር አልችልም እራሴን አጠፋለሁ"
እየቀለደችበት መሰለዉ ስለሚያማት ይሆናልም ብሎ አሰበ
ነገር ግን ንዴቱ ስለበለጠበት ወረቀቱን ቅድድድ አርጎ መሬት ላይ ወርዉሮት ሌላ ቤት ለመፈለግ ቤቱ እንኳን
ሳይዘጋ ወደ ደጅ ወጣ።
ደላሎች ወደ ሚቆሙበት መንገድ እየተጎዘ
በሀሳብ ብቻዉን እያሰበ ሲጎዝ ከጀርባዉ
የሆነ ነገር ዉርር አረገዉ እየተጫጫነዉ ዞረ
ቤዛዊት ነጭ የሀበሻ ቀሚስ ለብሳ
በእጇ ቀይ አበባ ይዛ እየተከተለችዉ ነበር.....
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#በክፍለማርያም
...ጩሀቷን አቀለጠችዉ
ፍፁም ያልጠበቀዉ እና ያላሰበዉ ነገር ስለተፈጠረ ዉሀ ሆኖ ቀረ እግሮቹ መንቀጥቀጥ ጀምረዋል
የቤዛዊት መታመም አሁን ሁሉ ነገር ግልፅ ሆነለት
ነገር ግን ከረፈደ በኃላ ነዉ ምንም ማረግ አልቻለም።
በተቀመጠበት አልጋ የቤዛዊት ጩሀት ጆሮዉ ላይ ያስተጋባል
ጭ ዉ የሚል ስሜት ጆሮዉን አልፎ አይምሮዉ
ዉስጥ ያለማቋረጥ ይዞራል።
"ደፈረኝ"
የሚሉ ቃላት ከጩሀቱ ገዝፈዉ ይሰሙታል ነገር ግን
ከአልጋዉ ተነስቶ እንኳን ለመቆም አቅም አጣ።
የቤዛዊትን ጩሀት የሰሙ የፍፁም አከራዮች ከነሱ አልፎ
የሰፈሩ ነዋሪወች ጠባቡን የፍፁምን ቤት
በርግደዉ ሲገቡ ጩሀቱን የሰሙ በአቅራቢያዉ የነበሩ
የፖሊስ አባሎችም ተከታትለዉ ገቡ።
ቤዛዊት በፍጥነት ልብሷን ለባብሳ የፍፁም ቤት አከራይ
ሴትዮ ላይ ተጠመጠመችባቸዉ።
ፍፁምን የተከራየበት አካባቢ የነበሩ ወጣቶች እንደ በ'ዳይ በጥያቄ እያዋከቡት ነዉ።
ከፓሊሶቹ አንዱ
"ልብስ ደርብ እና ለጥያቄ ጣብያ እንሄድ"
ስላለዉ ፍፁም በሀፍረት እና በድንጋጤ አጠገቡ
ወልቆ የተቀመጠዉን ሸሚዙን እየለበሰ ቤዛዊትን ለመፈለግ አይኖቹን ቤቱ ዉስጥ ወሬ ለማድመቅ የቆሙትን
ሰወች ማየት ጀመረ የሁሉም ሰዉ ፊት እሱን በንቀት አስተያየት እያዩት ነዉ አከራዩም ሳይቀሩ
ተለወጡበት እየገላመጡት ነዉ።
ቤዛዊት ግን ከሰወቹ መሀል የለችም በግርግሩ ወሀል ወጥታ ሄዳለች።
ፍፁም በምሽት ፖሊስ ጣብያ አግዳሚ ላይ ቁጭ ብሎ
ማሰብ ተስኖት ትካዜ ዉስጥ ገብቶ የመርማሪዉ ፖሊስ ድምፅ አባነነዉ።
ለመርማሪዉ የተጠየቀዉን ሀሉ መመለስ ጀመረ ወደ መጨረሻ ለተጠየቀዉ መልስ ቤዛዊት ፍቅረኛዉ እንደሆነች
እና በጊዜያዊ ፀብ ከሌላ ሴት ጋ አይታዉ በስህተት ተርጉማዉ እንደተጋጩ አርጎ ነግሯቸዉ ከሳሽ ከመጣ
ብለዉ እዛዉ አሳድረዉት በነጋታዉ ከረፋፈደ በኃላ ለቀቁት።
ከፖሊስ ጣብያዉ እንደወጣ በተስፋ መቁረጥ ዉስጥ ሆኖ ቤዛዊትን እየረገማት እንባ እየተናነቀዉ ላለማልቀስ
ከራሱ ጋር እየታገለ ከተከራየበት ቤት ደረሰ።
ገና የግቢዉን በር ሲገባ በፊት በፈገግታ እና በፍቅር የሚያዩት አከራዩ እሳት ጎርሰዉ እና ተኮሳትረዉ ጠበቁት
"ዛሬዉኑ ቤቴን ለቀህ እንድትወጣ"
ፍፁም ንፁህነቱን ሊያወራ ሲሞክር ጉሮሮዉ ደረቀበት
ቃላቶች ከአፉ ማዉጣት አቃተዉ
"እ እ ማዘር..."
"ምንም ወሬ አልፈልግም ዉልቅ በል"
ሁለት ቦታ የታጠፈ ወረቀት በእጁ እየሰጡት ።
ወደ ቤታቸዉ
"እንዲህ ነችና"እያሉ ገቡ።
ቤቱ ክፍት አድሮ ነዉ የዋለዉ እንደዛ የተስተካከለ እና
ዉበት ያለዉ ቤት ምንቅርቅሩ ወጥቷል በቆመበት እጁ ላይ
ያለዉ ወረቀት የማን እንደሆነና ምን እንደሚል ለማንበብ ገለጠዉ።
የቤዛዊት እጅ ፅሁፍ ነዉ እስዋ ናት በወረቀት አየፃፈች መስጠት ያስለመደችዉ ገና ሳያነበዉ እንባዉ ወረቀቱ ላይ ዱ ብ ዱብ ማለት ጀመረ አይኖቹ በእንባዉ ጭጋግ
ስለተሸፈኑ ማንበብ አልቻለም።
ቤዛዊትን ከልቡ ወዷት ነበር "ፍቅር ይሄ ነዉ" እያለ
ለራሱ የማይመልሰዉ ጥያቄ እየጠየቀ እንባዉን
በቀኝ እጁ እየጠረገ ወረቀቱን ድጋሜ አየዉ።
"ፍፁም ምን እንደሆንኩ...ምን እንዳረኩ አላዉቅም..
ማጥፋቴ ጠዋት ነዉ የገባኝ
እወድሃለሁ
ይቅርታ አርግልኝ
አንተን አጥቼ ግን መኖር አልችልም እራሴን አጠፋለሁ"
እየቀለደችበት መሰለዉ ስለሚያማት ይሆናልም ብሎ አሰበ
ነገር ግን ንዴቱ ስለበለጠበት ወረቀቱን ቅድድድ አርጎ መሬት ላይ ወርዉሮት ሌላ ቤት ለመፈለግ ቤቱ እንኳን
ሳይዘጋ ወደ ደጅ ወጣ።
ደላሎች ወደ ሚቆሙበት መንገድ እየተጎዘ
በሀሳብ ብቻዉን እያሰበ ሲጎዝ ከጀርባዉ
የሆነ ነገር ዉርር አረገዉ እየተጫጫነዉ ዞረ
ቤዛዊት ነጭ የሀበሻ ቀሚስ ለብሳ
በእጇ ቀይ አበባ ይዛ እየተከተለችዉ ነበር.....
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍4
#ሀዘንን_በደስታ
ማልቀሴ ቢረዝም
መቋጫው ቢጠፋኝ
ማልቀስና መሳቅ
ማልቀስ ቢሆንብኝ
ራሴን ጠየኩኝ
ለቅሶዬን በሳቅ መልክ
አርጎ እንዲቆጥርልኝ
ሜዳ ነው ገደሉ
ከዛማ ይሻለኛል
በቀሪው ዘመኔም
ደስታ ይሰጠኛል
ውስጤ ያልቅስ እንጂ
እኔ ምን ገዶኛል፡፡
🔘ፋሲል ሃይሉ🔘
ማልቀሴ ቢረዝም
መቋጫው ቢጠፋኝ
ማልቀስና መሳቅ
ማልቀስ ቢሆንብኝ
ራሴን ጠየኩኝ
ለቅሶዬን በሳቅ መልክ
አርጎ እንዲቆጥርልኝ
ሜዳ ነው ገደሉ
ከዛማ ይሻለኛል
በቀሪው ዘመኔም
ደስታ ይሰጠኛል
ውስጤ ያልቅስ እንጂ
እኔ ምን ገዶኛል፡፡
🔘ፋሲል ሃይሉ🔘
Forwarded from አትሮኖስ via @Qualitymovbot
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#በክፍለማርያም
...አበባ ይዛ እየተከተለችዉ ነበር
ፍፁም ገና እንዳያት እንደ ሁል ጊዜዉ ዝም ሊላት አቅም ስላጣ።
"ምን ፈልገሽ መጣሽ!!"
ሲል እየጮሀ ፊት ለፊትዋ ቆመ
ግንባሩ ላይ ያሉት የደም ስሮች ፊቱ ላይ ገዝፈዉ ይታያሉ
በጥፊ መምታት አስቦ እጃቹን ካወራጨ በኃላ ፊትዋ ላይ ያለዉ የልመና አስተያየት
ከእንባዋ ጋ ተጨምሮ አላረገዉም የዘረጋዉን እጅ ኪሱ ዉስጥ ከቶ
"እባክሽ ተይኝ ልለምንሽ ተይኝ"
ድምፁ ሳይታወቀዉ ጮክ ብሎ ስለነበር
መንገዱ ላይ የሚያልፋ የሚያገድመዉ እየዞረ ሲያዩዋቸዉ
ቤዛዊትን በቆመችበት ጥሏት ሄደ።
ፍፁም አሁን ስለቤዛዊት ላለማሰብ እና ላለማስታወስ እየታገለ
አነስተኛ መኪና እቃዉን የሚጭንበት አናግሮ
አዲስ ደላላዉ ወዳገኘለት ቤት ለመግባት
እቃዉን ማስተካከል ጀመረ።
ቤዛዊት አበባዉን እንደያዘች እያለቀሰች ወደ ቤቷ ገባች ቤትዋ ዉስጥ ወደ ሳሎን እንደገባች እናትዋ እና እህቷ
ተቀምጠዉ ጠበቋት።
"ምን ሆንሽ ልጄ"
እያሉ በልጃቸው የማይጨክን እናትዋ ሮጠዉ ፊትዋን ለመደባበስ ሲሞክሩ
"እንዳትነኪኝ እንደዉም እሞትላችሁዋለሁ"
እያለች ወደ መኝታ ክፍሎ እየሮጠች ሄደች።
እናትዋ ቤዛዊት እንደዚህ አይነት ቃላት ሲያማት ሲያማት ስለምትናገር ብዙም አልተደናገጡም ግን የዛሬዉ
የተለየ የመሰላቸዉ አበባ በእጇ ይዛ ስላዩ ተጨንቀዉ ተከትለዋት እሮጡ
"ልጄ ልግባ?"
አሏት ሆዳቸዉ ስፍስፍ እያለ
"ማንንም ማናገር አልፈልግም"
አለች ቤዛዊት እያለቀሰች ስለሆነ ሳግዋ እየተናነቃት
በመሀል ታላቅ እህቷ እናታቸዉን ቀነስ ባለ ድምፅ
"እኔ አዋራታለሁ እማ አንቺ አትጨነቂ"
ብላ የቤዛዊትን የመኝታ ቤት በር ከፍታ ገባች
መልሳ ዘግታዉ በዝግታ ትራስ ታቅፋ
የምታለቅሰዉ እህቷ ጎን ተቀመጠች።
"ቤዚ ምን ሆነሽ ነዉ"
ዝም አለቻት
"ንገሪኝ እኔ እህትሽ አደለሁ ምንም ይሁን እረዳሻለሁ"
"ለነ አባቢ" አትናገሪም እያለች ቀና አለች
"አዎ ቃል እገባለሁ ማልቀስ አሁን አቁሚና ንገሪኝ"
አለቻት በእጇ እየደባበሰቻት።
ቤዛዊት አንድ ሳታስቀር እዉነቱን ነገረቻት ፍፁምን እንደምትወደዉ
አስተማሪዋ እንደሆነ ሌላዉ ደሞ በፊት ስትክደዉ የነበረዉ
እንደሚያማት እርግጠኛ እንደሆነች እና
ፍፁምንም እንዳስከፋችዉ አንድ ሳታስቀር ሁሉንም ነገረቻት።
እህቷም ቀለል አርጋ
"በቃ ለዚህ ነዉ ዋናዉ አንቻ ጥፋትሽን ማመንሽ ነዉ
ስለ ህመምሽ ደሞ አትጨነቂ ህክምና ታገኛለሽ
ትድኛለሽ ማሰብ የለብሽም ፍፁምን ደሞ ነገ ትምህር ቤታችሁ ሄጄ አዋራዋለሁ"
አለቻት
ቤዛዊት አይሆንም አሁኑኑ አዋሪዉ ተናዶብኛል ይጠላኛል
ብላ ስላስቸገረቻት የቤቱን አድራሻ ተቀብላ
ፍፁምን ለማዋራት ታላቅ እህቷ ወጣች።
በሰወች ጥቆማ የፍፁምን ግቢ አገኘችዉ
በሩጋ እቃ የተጫነበት መኪና ቆሞል ወደ ሹፌሩ ጠጋ ብላ
"ፍፁም የሚባል ሰዉ ታዉቃለህ"
እያለችዉ
ፍፁም እራሱ ፍራሹን ተሸክሞ መኪናዉ ላይ ከጫነዉ በኋላ
"እኔ ነኝ"
አላት በጥርጣሬ ማን ናት ምን ፈልጋ ነዉ እያለ
"ይቅርታ አታዉቀኝም ትርሲት እባላለሁ"
እጇን ዘረጋችለት
ፍፁም እያለ የዘረጋችለትን እጇች ጨበጣቸዉ
"ማዉራት ትችላለህ ቁጭ ብለን?"
ጠየቀችዉ
አንዴ ወደ መኪናዉ አንዴ ቤት ዉስጥ ስለቀሩት እቃወች እያሰበ
"እዚሁ ማዉራት አንችልም"
አላት ያለበት ሁኔታ ተቀምጦ ለማዉረራት እንደማይመች
በአይኑ እያሳያት
"እሺ የቤዛዊት እህትነኝ ስለሷ ላዋራክ ነበር"
ፍፁም የቤዛዊት ስም ሲነሳ ፍቅሩ አገረሸበት
ቅድም ያለችዉን ሲያስታዉስ ደንግጦ
"ምን ሆነች"
አላት ሰፍ ብሎ ትርሲት የእህቷን ስም ስትነግረዉ ባየችዉ ነገር
ይወዳታል ያስብላታል እያለች ነበር ስልኳ ሲጠራም ልብ አላለችም
"ተረጋጋ ምንም አልሆነችም ይቅርታ ስልኩን ላንሳዉ ማዘር ናት" ብላ የስልኩን ማንሻ ጫር አድርጋ ወደ ጆሮዋ አሰጠጋችዉ
እናትዋ እየጮሁ እያለቀሱ ነዉ
ስልኩን ይዛ መንቀጥቀጥ ጀመረች።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#በክፍለማርያም
...አበባ ይዛ እየተከተለችዉ ነበር
ፍፁም ገና እንዳያት እንደ ሁል ጊዜዉ ዝም ሊላት አቅም ስላጣ።
"ምን ፈልገሽ መጣሽ!!"
ሲል እየጮሀ ፊት ለፊትዋ ቆመ
ግንባሩ ላይ ያሉት የደም ስሮች ፊቱ ላይ ገዝፈዉ ይታያሉ
በጥፊ መምታት አስቦ እጃቹን ካወራጨ በኃላ ፊትዋ ላይ ያለዉ የልመና አስተያየት
ከእንባዋ ጋ ተጨምሮ አላረገዉም የዘረጋዉን እጅ ኪሱ ዉስጥ ከቶ
"እባክሽ ተይኝ ልለምንሽ ተይኝ"
ድምፁ ሳይታወቀዉ ጮክ ብሎ ስለነበር
መንገዱ ላይ የሚያልፋ የሚያገድመዉ እየዞረ ሲያዩዋቸዉ
ቤዛዊትን በቆመችበት ጥሏት ሄደ።
ፍፁም አሁን ስለቤዛዊት ላለማሰብ እና ላለማስታወስ እየታገለ
አነስተኛ መኪና እቃዉን የሚጭንበት አናግሮ
አዲስ ደላላዉ ወዳገኘለት ቤት ለመግባት
እቃዉን ማስተካከል ጀመረ።
ቤዛዊት አበባዉን እንደያዘች እያለቀሰች ወደ ቤቷ ገባች ቤትዋ ዉስጥ ወደ ሳሎን እንደገባች እናትዋ እና እህቷ
ተቀምጠዉ ጠበቋት።
"ምን ሆንሽ ልጄ"
እያሉ በልጃቸው የማይጨክን እናትዋ ሮጠዉ ፊትዋን ለመደባበስ ሲሞክሩ
"እንዳትነኪኝ እንደዉም እሞትላችሁዋለሁ"
እያለች ወደ መኝታ ክፍሎ እየሮጠች ሄደች።
እናትዋ ቤዛዊት እንደዚህ አይነት ቃላት ሲያማት ሲያማት ስለምትናገር ብዙም አልተደናገጡም ግን የዛሬዉ
የተለየ የመሰላቸዉ አበባ በእጇ ይዛ ስላዩ ተጨንቀዉ ተከትለዋት እሮጡ
"ልጄ ልግባ?"
አሏት ሆዳቸዉ ስፍስፍ እያለ
"ማንንም ማናገር አልፈልግም"
አለች ቤዛዊት እያለቀሰች ስለሆነ ሳግዋ እየተናነቃት
በመሀል ታላቅ እህቷ እናታቸዉን ቀነስ ባለ ድምፅ
"እኔ አዋራታለሁ እማ አንቺ አትጨነቂ"
ብላ የቤዛዊትን የመኝታ ቤት በር ከፍታ ገባች
መልሳ ዘግታዉ በዝግታ ትራስ ታቅፋ
የምታለቅሰዉ እህቷ ጎን ተቀመጠች።
"ቤዚ ምን ሆነሽ ነዉ"
ዝም አለቻት
"ንገሪኝ እኔ እህትሽ አደለሁ ምንም ይሁን እረዳሻለሁ"
"ለነ አባቢ" አትናገሪም እያለች ቀና አለች
"አዎ ቃል እገባለሁ ማልቀስ አሁን አቁሚና ንገሪኝ"
አለቻት በእጇ እየደባበሰቻት።
ቤዛዊት አንድ ሳታስቀር እዉነቱን ነገረቻት ፍፁምን እንደምትወደዉ
አስተማሪዋ እንደሆነ ሌላዉ ደሞ በፊት ስትክደዉ የነበረዉ
እንደሚያማት እርግጠኛ እንደሆነች እና
ፍፁምንም እንዳስከፋችዉ አንድ ሳታስቀር ሁሉንም ነገረቻት።
እህቷም ቀለል አርጋ
"በቃ ለዚህ ነዉ ዋናዉ አንቻ ጥፋትሽን ማመንሽ ነዉ
ስለ ህመምሽ ደሞ አትጨነቂ ህክምና ታገኛለሽ
ትድኛለሽ ማሰብ የለብሽም ፍፁምን ደሞ ነገ ትምህር ቤታችሁ ሄጄ አዋራዋለሁ"
አለቻት
ቤዛዊት አይሆንም አሁኑኑ አዋሪዉ ተናዶብኛል ይጠላኛል
ብላ ስላስቸገረቻት የቤቱን አድራሻ ተቀብላ
ፍፁምን ለማዋራት ታላቅ እህቷ ወጣች።
በሰወች ጥቆማ የፍፁምን ግቢ አገኘችዉ
በሩጋ እቃ የተጫነበት መኪና ቆሞል ወደ ሹፌሩ ጠጋ ብላ
"ፍፁም የሚባል ሰዉ ታዉቃለህ"
እያለችዉ
ፍፁም እራሱ ፍራሹን ተሸክሞ መኪናዉ ላይ ከጫነዉ በኋላ
"እኔ ነኝ"
አላት በጥርጣሬ ማን ናት ምን ፈልጋ ነዉ እያለ
"ይቅርታ አታዉቀኝም ትርሲት እባላለሁ"
እጇን ዘረጋችለት
ፍፁም እያለ የዘረጋችለትን እጇች ጨበጣቸዉ
"ማዉራት ትችላለህ ቁጭ ብለን?"
ጠየቀችዉ
አንዴ ወደ መኪናዉ አንዴ ቤት ዉስጥ ስለቀሩት እቃወች እያሰበ
"እዚሁ ማዉራት አንችልም"
አላት ያለበት ሁኔታ ተቀምጦ ለማዉረራት እንደማይመች
በአይኑ እያሳያት
"እሺ የቤዛዊት እህትነኝ ስለሷ ላዋራክ ነበር"
ፍፁም የቤዛዊት ስም ሲነሳ ፍቅሩ አገረሸበት
ቅድም ያለችዉን ሲያስታዉስ ደንግጦ
"ምን ሆነች"
አላት ሰፍ ብሎ ትርሲት የእህቷን ስም ስትነግረዉ ባየችዉ ነገር
ይወዳታል ያስብላታል እያለች ነበር ስልኳ ሲጠራም ልብ አላለችም
"ተረጋጋ ምንም አልሆነችም ይቅርታ ስልኩን ላንሳዉ ማዘር ናት" ብላ የስልኩን ማንሻ ጫር አድርጋ ወደ ጆሮዋ አሰጠጋችዉ
እናትዋ እየጮሁ እያለቀሱ ነዉ
ስልኩን ይዛ መንቀጥቀጥ ጀመረች።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በክፍለማርያም
...መንቀጥቀጥ ጀመረች
ወድያዉ ስልኳን ወደ ቦርሳዋ በድንጋጤ እየከተተች
"ቤዛዊት ስለሚያማት ነዉ ተረዳት ደሞም ትወድሀለች"
ድምፅዋም በፍርሀት እየተንቀጠቀጠ ነዉ።
ፍፁም የፊትዋን መለዋወጥ አይቶ
"ምን ሰምተሽ ነዉ?"
አላት ለአመል የመስማትም ያለመስማትም ፍላጎት አጥቶ
"ምን እንደተፈጠረ አላወኩም ግን ቤዛዊት ሆስፒታል ናት
እኔም መሄድ አለብኝ በቅርቡ ተገናኝተን ግን ማዉራት አለብን"
ብላዉ የሱን መልስ ሳትጠብቅ
ጥላዉ ወደ እህቷ መሮጥ ጀመረች
ፍፁምን በቆመበት ሳትሰናበተዉ።
(ቀደምት ታሪክ)
ቤዛዊት እህቷ አዋርታት ፍፁምን ልታናግርላት ስትወጣ
እራስዋን ስላመማት ህመሙን ቀለል እንዲያረግላት
መድሀኒት ዉጣ አልጋዋ ላይ ትራሷን አቅፋ በጎኗ አረፍ አለች።
ደግማ ደጋግማ ስለፍፁም ታስባለች
ልቧ ለሁለት ተከፍሎ ፍፁም እኔን ይቅርታ ያረግልኛል
ብላ ታስባለች በተቃራኒዉ አንቺ ጤነኛ ሰዉ አደለሽም
ፍፁም እብድ አይፈልግም ይላታል።
ህመሙ ግን ሊለቃት አልቻለም
በተኛችበት ሀሳቧ ፍፁምን ከሩቁ ሙሉ ሱፍ ለብሷ
አሳያት እየቀረበችዉ ስትመጣ ብቻዉን አደለም
ነጭ ቬሎ የለበሰች ሴት ታየቻት
የደበደበቻት ህሊና ናት።
ሀሳብዋን እዉነት አርጋ ተቀበለችዉ
በንዴት ግላ ከተኛችበት ቀና ብላ እግሮቿን መሬት
አስነካቻቸዉ አሁንም አይኗ ፍፁም እና ህሊና ላይ ነዉ
ዉስጧ አንቺን ትቶ ሌላ አገባ ይላታል
"እንዴት እያለች?"
እስዋ አፍዋን እያንቀሳቀሰች ታወራለች
"ግደይዉ!!"
ብሎ ሹክ አላት አንገራገረች
"አንቺን በሌላ ቀይሮሽማ አትዘኚለት ተነሽ ግደይዉ!!"
ደገመላት
በባዶ እግሯ ቆማ መራመድ ጀመረች
ታማለች እራሷን አደለችም ነገር ግን ለእሷ አይታወቃትም
የመኝታ ቤቷን በር ከፍታ ወደ ማዕድ ቤት
በደመነፍስ ተጓዘች ከመክተፍያ አጠገብ ያገኘችዉን
ስል ቢለዋ አንስታ ፊት ለፊትዋ የቆሙት ሙሽሮችን
ለመዉጋት እጇን ቀስ አርጋ ዘረጋች
ዉሸት አጥፊዉ ሁለቱንም ግደያቸዉ ይላታል
እዉነት ማረግ የለብሽም እያለ ሲሞግታት
በባዶ ሜዳ የዘረጋችዉን ቢለዋ የራሷ አንገት ላይ አሳረፈችዉ እጇን ማንቀሳቀስ ስትጀምር
ህመም እና የሚፈሳት ደም ተቀላቅሎ
የሲቃ ድምፅ አወጣች ድምፁን የሰሙት እናቷ እና
ሰራተኛቸዉ ማዕድ ቤት በፍጥነት ሲደርሱ
ቤዛዊት በደም እርሳለች ቢላ የያዘ እጇን ከአንገቷ
እየጮሁ ቢለዋዉን መነተፏት እስዋ አቅም እያነሳት ተዝለፍልፋ ወደቀች።
የቤዛዊት እናት አንፑላንስ ጠርተዉ
ልጃቸዉን ሆስፒታል አሰገብተዉ ትንሽ ሲረጋጉ
ድንጋጤ ሲለቃቸዉ ነገር ግን የቤዛዊትን የመጨረሻ
ዉጤት ስላልሰሙ አብራቸዉ ያለችዉ
ሰራተኛቸዉ እየጮኸች እሳቸዉ እያለቀሱ
ቅድምያ ለባለቤታቸዉ ቀጥለዉ ለእህቷ ደወሉ
ሆስፒታል ቶሎ እንዲመጡ።
ፍፁም አዲስ የተከራየዉ ቤት እቃወቹን እንደነገሩ
ካራገፈ በኃላ ልቡ እርብሽ ስላለበት በቆመበት ወለሉ ላይ
ቀስ ብሎ ቁጭ አለ።
እህቷ ሆስፒታል ያለችዉን ሲያስታዉስ
ቤዛዊት እንዳለችዉ እራሷን አጥፍታ ቢሆንስ እያለ
እያሰበ ያላሰበዉ እንባዉ ቀድሞት መፍሰስ ጀምሮ ነበር
"አይሆንም አታረጊዉም ይቅርታ አረግልሻለሁ"
ሊደዉልላት ሆስፒታል በሞት እና በህይወት መሀል
ወዳለችዉ ቤዛዊት ስልኩን ከኪሱ አወጣ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በክፍለማርያም
...መንቀጥቀጥ ጀመረች
ወድያዉ ስልኳን ወደ ቦርሳዋ በድንጋጤ እየከተተች
"ቤዛዊት ስለሚያማት ነዉ ተረዳት ደሞም ትወድሀለች"
ድምፅዋም በፍርሀት እየተንቀጠቀጠ ነዉ።
ፍፁም የፊትዋን መለዋወጥ አይቶ
"ምን ሰምተሽ ነዉ?"
አላት ለአመል የመስማትም ያለመስማትም ፍላጎት አጥቶ
"ምን እንደተፈጠረ አላወኩም ግን ቤዛዊት ሆስፒታል ናት
እኔም መሄድ አለብኝ በቅርቡ ተገናኝተን ግን ማዉራት አለብን"
ብላዉ የሱን መልስ ሳትጠብቅ
ጥላዉ ወደ እህቷ መሮጥ ጀመረች
ፍፁምን በቆመበት ሳትሰናበተዉ።
(ቀደምት ታሪክ)
ቤዛዊት እህቷ አዋርታት ፍፁምን ልታናግርላት ስትወጣ
እራስዋን ስላመማት ህመሙን ቀለል እንዲያረግላት
መድሀኒት ዉጣ አልጋዋ ላይ ትራሷን አቅፋ በጎኗ አረፍ አለች።
ደግማ ደጋግማ ስለፍፁም ታስባለች
ልቧ ለሁለት ተከፍሎ ፍፁም እኔን ይቅርታ ያረግልኛል
ብላ ታስባለች በተቃራኒዉ አንቺ ጤነኛ ሰዉ አደለሽም
ፍፁም እብድ አይፈልግም ይላታል።
ህመሙ ግን ሊለቃት አልቻለም
በተኛችበት ሀሳቧ ፍፁምን ከሩቁ ሙሉ ሱፍ ለብሷ
አሳያት እየቀረበችዉ ስትመጣ ብቻዉን አደለም
ነጭ ቬሎ የለበሰች ሴት ታየቻት
የደበደበቻት ህሊና ናት።
ሀሳብዋን እዉነት አርጋ ተቀበለችዉ
በንዴት ግላ ከተኛችበት ቀና ብላ እግሮቿን መሬት
አስነካቻቸዉ አሁንም አይኗ ፍፁም እና ህሊና ላይ ነዉ
ዉስጧ አንቺን ትቶ ሌላ አገባ ይላታል
"እንዴት እያለች?"
እስዋ አፍዋን እያንቀሳቀሰች ታወራለች
"ግደይዉ!!"
ብሎ ሹክ አላት አንገራገረች
"አንቺን በሌላ ቀይሮሽማ አትዘኚለት ተነሽ ግደይዉ!!"
ደገመላት
በባዶ እግሯ ቆማ መራመድ ጀመረች
ታማለች እራሷን አደለችም ነገር ግን ለእሷ አይታወቃትም
የመኝታ ቤቷን በር ከፍታ ወደ ማዕድ ቤት
በደመነፍስ ተጓዘች ከመክተፍያ አጠገብ ያገኘችዉን
ስል ቢለዋ አንስታ ፊት ለፊትዋ የቆሙት ሙሽሮችን
ለመዉጋት እጇን ቀስ አርጋ ዘረጋች
ዉሸት አጥፊዉ ሁለቱንም ግደያቸዉ ይላታል
እዉነት ማረግ የለብሽም እያለ ሲሞግታት
በባዶ ሜዳ የዘረጋችዉን ቢለዋ የራሷ አንገት ላይ አሳረፈችዉ እጇን ማንቀሳቀስ ስትጀምር
ህመም እና የሚፈሳት ደም ተቀላቅሎ
የሲቃ ድምፅ አወጣች ድምፁን የሰሙት እናቷ እና
ሰራተኛቸዉ ማዕድ ቤት በፍጥነት ሲደርሱ
ቤዛዊት በደም እርሳለች ቢላ የያዘ እጇን ከአንገቷ
እየጮሁ ቢለዋዉን መነተፏት እስዋ አቅም እያነሳት ተዝለፍልፋ ወደቀች።
የቤዛዊት እናት አንፑላንስ ጠርተዉ
ልጃቸዉን ሆስፒታል አሰገብተዉ ትንሽ ሲረጋጉ
ድንጋጤ ሲለቃቸዉ ነገር ግን የቤዛዊትን የመጨረሻ
ዉጤት ስላልሰሙ አብራቸዉ ያለችዉ
ሰራተኛቸዉ እየጮኸች እሳቸዉ እያለቀሱ
ቅድምያ ለባለቤታቸዉ ቀጥለዉ ለእህቷ ደወሉ
ሆስፒታል ቶሎ እንዲመጡ።
ፍፁም አዲስ የተከራየዉ ቤት እቃወቹን እንደነገሩ
ካራገፈ በኃላ ልቡ እርብሽ ስላለበት በቆመበት ወለሉ ላይ
ቀስ ብሎ ቁጭ አለ።
እህቷ ሆስፒታል ያለችዉን ሲያስታዉስ
ቤዛዊት እንዳለችዉ እራሷን አጥፍታ ቢሆንስ እያለ
እያሰበ ያላሰበዉ እንባዉ ቀድሞት መፍሰስ ጀምሮ ነበር
"አይሆንም አታረጊዉም ይቅርታ አረግልሻለሁ"
ሊደዉልላት ሆስፒታል በሞት እና በህይወት መሀል
ወዳለችዉ ቤዛዊት ስልኩን ከኪሱ አወጣ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
❤1