#የቀበቶ_ቅኔ
እንደ ብዙ ወንደች
ከብዙ ሴቶች ጋር ፥ ለዝሙት ተኝቶ
እንዲ እርኩ ማለት
ጀብዱ የሚመስለኝ ፥ እንጎለ ቀበቶ
ለስሜቴ ሳድር ፥ ነፍሴን አዝረክርኬ
ከቀበቶዬ ላይ
ተፅፎ አየሁት ፥ የህይወት ታሪክ።
እዩት ቀበቶዬን
በሴቶች ምሳሌ ፥ ቀዳዳ ተከቦ
እኔ ማለት ያ ነኝ
በቀዳዶች ውስጥ
ገብቶ የሚወጣ ; የቀበቶው ሽቦ፡፡
የማሰቤ ወገብ ፥ ሲቀጥን ሲወፍር
ካንዷ ቀዳዳ ጎን ፥ አንዷን የምቀይር፡፡
የማሰቤ ወገብ ፥ ሲከሳ ሲሰባ
ቀዳዶቹን ትቼ
ሌላ አዲስ ቀዳዳ ፥ ፈልጌ ምገባ።
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
(መነሻ ሀሳብ ገጣሚ ደስታ ነጋሽ)
እንደ ብዙ ወንደች
ከብዙ ሴቶች ጋር ፥ ለዝሙት ተኝቶ
እንዲ እርኩ ማለት
ጀብዱ የሚመስለኝ ፥ እንጎለ ቀበቶ
ለስሜቴ ሳድር ፥ ነፍሴን አዝረክርኬ
ከቀበቶዬ ላይ
ተፅፎ አየሁት ፥ የህይወት ታሪክ።
እዩት ቀበቶዬን
በሴቶች ምሳሌ ፥ ቀዳዳ ተከቦ
እኔ ማለት ያ ነኝ
በቀዳዶች ውስጥ
ገብቶ የሚወጣ ; የቀበቶው ሽቦ፡፡
የማሰቤ ወገብ ፥ ሲቀጥን ሲወፍር
ካንዷ ቀዳዳ ጎን ፥ አንዷን የምቀይር፡፡
የማሰቤ ወገብ ፥ ሲከሳ ሲሰባ
ቀዳዶቹን ትቼ
ሌላ አዲስ ቀዳዳ ፥ ፈልጌ ምገባ።
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
(መነሻ ሀሳብ ገጣሚ ደስታ ነጋሽ)
#ይህችን_አታሳጣኝ
የአዳም ዘር በሞላ ታድሞ ከእልፍኝ
ባለው ላይ ሲያተርፍ ካለው እጥፍ ሲመኝ
ከማዶ ሲያማትር አርቆ ከራሱ
ለልጅ ልጅ ሲለፋ ጠግባ አንድ ነፍሱ
ግራ ቀኝ ብፈልግ ውስጤ ፈጥሮ ቅናት
ሀበሻ ወገኔም ካፉ ሲል በአይኔ ልመለከት
መአዱን ሊቋደስ ተራው ከመድረሱ
እፍኝ ቆንጠር አርጎ ባዶ ሆኖ ኪሱ
ሊያመስግን'ሮጠ ሊቆም ከመቅደሱ።
🔘ፋሲል ሃይሉ🔘
የአዳም ዘር በሞላ ታድሞ ከእልፍኝ
ባለው ላይ ሲያተርፍ ካለው እጥፍ ሲመኝ
ከማዶ ሲያማትር አርቆ ከራሱ
ለልጅ ልጅ ሲለፋ ጠግባ አንድ ነፍሱ
ግራ ቀኝ ብፈልግ ውስጤ ፈጥሮ ቅናት
ሀበሻ ወገኔም ካፉ ሲል በአይኔ ልመለከት
መአዱን ሊቋደስ ተራው ከመድረሱ
እፍኝ ቆንጠር አርጎ ባዶ ሆኖ ኪሱ
ሊያመስግን'ሮጠ ሊቆም ከመቅደሱ።
🔘ፋሲል ሃይሉ🔘
#አረፍተ_ሀገር
“አበበ” ምንለው ፥ በሶ የሚበላ
ጩቤ እንደጨበጠ ፥ ለምናውቀው ጫላ
ጣሳ እያጠበ ፥ ለሚኖር ጨቡዴ
ሀገርሽ ሀገሬ
አረፍተ ነገርን ፥ ትመስላለች ውዴ።
*
ስልኬ አበበ ነው
በሶ ደሞ ካርዴ ፥ ስትገባኝ ሀገሬ
“ቴሌ ካርድ በላ።”
የሚል ትርጉም አለው ፣ አረፍተ ነገሬ።
*
ጫላ ባለ ስልጣን ፥ ስልጣን ደሞ ጩቤ
የጨበጡት ሁሉ
ሲያቆስሉት የኖሩ ፥ ስጋዬን ከልቤ።
***
ጨቡዴ ሙስና ፥ ጣሳ ደሞ ህዝቡ
እርቃን የሚያስቀሩት
በየ መሥሪያ ቤቱ ፥ ኪሱን እያሰቡ።
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
“አበበ” ምንለው ፥ በሶ የሚበላ
ጩቤ እንደጨበጠ ፥ ለምናውቀው ጫላ
ጣሳ እያጠበ ፥ ለሚኖር ጨቡዴ
ሀገርሽ ሀገሬ
አረፍተ ነገርን ፥ ትመስላለች ውዴ።
*
ስልኬ አበበ ነው
በሶ ደሞ ካርዴ ፥ ስትገባኝ ሀገሬ
“ቴሌ ካርድ በላ።”
የሚል ትርጉም አለው ፣ አረፍተ ነገሬ።
*
ጫላ ባለ ስልጣን ፥ ስልጣን ደሞ ጩቤ
የጨበጡት ሁሉ
ሲያቆስሉት የኖሩ ፥ ስጋዬን ከልቤ።
***
ጨቡዴ ሙስና ፥ ጣሳ ደሞ ህዝቡ
እርቃን የሚያስቀሩት
በየ መሥሪያ ቤቱ ፥ ኪሱን እያሰቡ።
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
#ለመንጋዎች_መንጋ_ግጥም
እኔ ሰው ስለሆንኩ
የግል አእምሮዬን ፥ አሳልፌ አልሰጥም
በመንጋ አስተሳሰብ ፥ ሀሳቤ አይዋጥም
ለመንጋዎችና
ለመንጋ አሳቢዎች ፥ አለኝ መንጋ ግጥም።
#መንጋ_1
ብዙዎች ተስማምተው
በሔዱበት መንገድ
ትክክል ነው ብሎ ፥ አይነሳም እግሬ
ብዙዎች በህብረት
በጠሉት ነገር ላይ ፥ አይቀንስም ፍቅሬ
አመዛዝናለሁ
አስተሳስራለሁ
የግል አእምሮዬን ፥ ከደም ዝውውሬ።
ብዙዎች ሚወዱት
በጥላቻዬ ላይ ፥ ለውጥ አያመጡም
መንጋ አእምሮዎች
ሀሳብን አይወልዱም ፥ በግል አያምጡም
አንዱ የወለደውን
ይዘው ይጮሀሉ ፥ አይደማመጡም።
#መንጋ_2
መንጋ አሳቢዎች
በምላስ ነው እንጂ ፥ በአእምሮ አይቆሙም
ከእረኛቸው እንጂ
በራሳቸው መንገድ ፥ በድፍረት አይተሙም
በቀቀኖች ናቸው ፥ የገደል ማሚቶ
ተቀብሎ መጮህ
ያውቃል ምላሳቸው ፥ አእምሯቸው ሞቶ።
#መንጋ_3
አብሮ መኖር እንጂ
አብሮ ማሰብ ማላው ፥ ሀሳብን አውጠንጣኝ
አእምሮ የቸረኝ ፥ በምላስ ያልቀጣኝ
ፈጣሪ ይመሥገን!
ከባርነት በፊት
ከመንጋ አስተሳሰብ ፥ ነፃ ስላወጣኝ !!!
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
እኔ ሰው ስለሆንኩ
የግል አእምሮዬን ፥ አሳልፌ አልሰጥም
በመንጋ አስተሳሰብ ፥ ሀሳቤ አይዋጥም
ለመንጋዎችና
ለመንጋ አሳቢዎች ፥ አለኝ መንጋ ግጥም።
#መንጋ_1
ብዙዎች ተስማምተው
በሔዱበት መንገድ
ትክክል ነው ብሎ ፥ አይነሳም እግሬ
ብዙዎች በህብረት
በጠሉት ነገር ላይ ፥ አይቀንስም ፍቅሬ
አመዛዝናለሁ
አስተሳስራለሁ
የግል አእምሮዬን ፥ ከደም ዝውውሬ።
ብዙዎች ሚወዱት
በጥላቻዬ ላይ ፥ ለውጥ አያመጡም
መንጋ አእምሮዎች
ሀሳብን አይወልዱም ፥ በግል አያምጡም
አንዱ የወለደውን
ይዘው ይጮሀሉ ፥ አይደማመጡም።
#መንጋ_2
መንጋ አሳቢዎች
በምላስ ነው እንጂ ፥ በአእምሮ አይቆሙም
ከእረኛቸው እንጂ
በራሳቸው መንገድ ፥ በድፍረት አይተሙም
በቀቀኖች ናቸው ፥ የገደል ማሚቶ
ተቀብሎ መጮህ
ያውቃል ምላሳቸው ፥ አእምሯቸው ሞቶ።
#መንጋ_3
አብሮ መኖር እንጂ
አብሮ ማሰብ ማላው ፥ ሀሳብን አውጠንጣኝ
አእምሮ የቸረኝ ፥ በምላስ ያልቀጣኝ
ፈጣሪ ይመሥገን!
ከባርነት በፊት
ከመንጋ አስተሳሰብ ፥ ነፃ ስላወጣኝ !!!
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በክፍለማርያም
መስከረም መጀመሪያ ላይ ነው
ፍፁም ይባላል ወጣት ነዉ ለማስተማር ከተቀጠረበት ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ሊደርስ ጥቂት እርምጃወች ሲቀሩት ወደ ትምህርት ቤቱ የሚገቡ ተማሪዎች ብዛት እና ጫጫታ ለአፍታ አስቆመው።
የመጀመሪያ ቅጥሩ እንደመሆኑ ትንሽ ልቡ የተረበሸ ይመስላል።
''ይቅርታ ሰአትክ ይሰራል?''
አንዲት ዩኒፎርም የለበሰች የደስደስ ያላት ልጅ እጁ ላይ የታሰረዉን ሰአት በአይንዋ እየቃኘች ጠየቀችዉ።
''ሁለት ሰአት''አፉ እየተሳሰረ መለሰላት
''አናቱ ላይ?''
አዎ ለማለት ግንባሩን ከላይ ወደ ታች ሲነቀንቅ
ልጅቷ ''አፍክ አይሰራም!!''እያለች ቆመው ወደ ሚጠብቁዋት
ጉዋደኞችዋ እሮጠች።
እየተገረመ በልቡ"አስተማሪ አልመሰልኳትም" እያለ
መራመዱን ቀጠለ።
ወደ በሩ እየገባ አሁንም ሌላ ልጅ እየሮጠች መጥታ
''ጉዋደኛዬ ካስቀየመችህ ይቅርታ ትንሽ ወሰድ መለስ ስለሚያረጋት ነዉ''
ሌባ ጣትዋን ከአይንዋ አጠገብ ካለው ራስ ቅል
ዙርያ እያሽከረከረች አሳየችዉ
''ምንም አደል''እያለ ጥሏት ወደ ዉስጥ ዘለቀ።
ከመምህራን ማረፍያ ገብቶ የያዘውን ቦርሳ እቃ ማስቀመጫ
ዉስጥ ከቶ ከሌሎች መምህራን ጋር መተዋወቅ ጀመረ ትውውቁን
እንደጨረሰ ከመምህራን ሀላፊዉ ጋር የየእለት አለት የማስተማርያ
መመርያ ለመቀበል ወደ ሀላፊዉ በር ተጠግቶ አንኩዋኩዋ፡፡
''ይግቡ!"
ከዉስጥ ወደ ዉጪ በሰማው ድምፅ መሰረት በሩን ከፍቶ ገባ፡፡
ቢሮዉ ውስጥ ሌላ አንድ መምህር እና ሀላፊዉ
ተቀምጠዋል አስተማሪዉ
''ፍቃዱ እባላለሁ አማርኛ አስተማሪ ነኝ"
ከወንበሩ እንደመነሳት እያለ እጁን ዘረጋለት
"ፍፁም ሂስትሪ መምህር "ሰላም ተባባሉ
የመምህራን ሀላፊዉም
"አረፍ በል ልጅ ፍፁም ከኔ ጋር በቀደም ተዋዉቀናል...ይሄ
ወረቀት ያንተን የማስተማርያ ሰአት እና የምታስተምራቸውን
ክፍሎች የያዘ ነዉ ሌላ የምትጠይቀዉ ነገር ከሌለ
ጨርሰሀል..መልካሙን አመኝልሀለው::"
ከመምህር ፍቃዱ ጋር አንዳንድ ነገር እያወሩ በዛውም
ግቢዉን እና ክፍሎቹን እያስጎበኘዉ ወደ መጀመርያ ትምህርት
ወደ ሚሰጥበት ክፍል ሲደርሱ ቡሀላ ለመገናኘት ተቀጣጥረውተለያዩ፡፡
ወደ ክፍሉ ውስጥ ገብቶ መሀል ላይ ቆመ
በእርስ በእርስ ወሬ ደፍርሶ የነበረው
ክፍል ፀጥ ረጭ አለ ተማሪወቹ በሙሉ አይናቸዉን ተከሉበት
ላለመደናገጥ ልቡን አያደፋፈረ
"ፍፁም ደምሴ እባላለሁ ሂስትሪ ነው
የማስተምራችሁ እንደመጀመራችን ለመተዋወቅ እንዲረዳን
እናንተም በየተራ ስማችሁን ታስተዋዉቁኛላችሁ"
ሁሉም እየተነሳ ስሙን ለፈፁም ማስተዋወቅ ጀመረ
ተራዋ ደርሶ አንዷ
"ቤዛ"አለች ከወንበርዋ ተነስታ
ፍፁም እንዳያያት አንገትዋን ደፍታ
"እንደሌሎቹ ሙሉ ስምሽን ብትነግሪን?"
"ቤዛዊት መለሰ"ቀና ስትል ፊትዋን ለማየት ቻለ
የደሰደስ ያላት ቆንጇ ልጅ ናት ልቡ መምታት ጀመረች
"ከዚህ በፊት አዉቃታለሁ....?እራሱን ጠየቀ
ብዙ ለማሰብ ሞከረ ሲያስታዉስ
ጠዋት ሰአት ጠይቃ የሰደበችዉ ልጅ ናት፡፡
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በክፍለማርያም
መስከረም መጀመሪያ ላይ ነው
ፍፁም ይባላል ወጣት ነዉ ለማስተማር ከተቀጠረበት ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ሊደርስ ጥቂት እርምጃወች ሲቀሩት ወደ ትምህርት ቤቱ የሚገቡ ተማሪዎች ብዛት እና ጫጫታ ለአፍታ አስቆመው።
የመጀመሪያ ቅጥሩ እንደመሆኑ ትንሽ ልቡ የተረበሸ ይመስላል።
''ይቅርታ ሰአትክ ይሰራል?''
አንዲት ዩኒፎርም የለበሰች የደስደስ ያላት ልጅ እጁ ላይ የታሰረዉን ሰአት በአይንዋ እየቃኘች ጠየቀችዉ።
''ሁለት ሰአት''አፉ እየተሳሰረ መለሰላት
''አናቱ ላይ?''
አዎ ለማለት ግንባሩን ከላይ ወደ ታች ሲነቀንቅ
ልጅቷ ''አፍክ አይሰራም!!''እያለች ቆመው ወደ ሚጠብቁዋት
ጉዋደኞችዋ እሮጠች።
እየተገረመ በልቡ"አስተማሪ አልመሰልኳትም" እያለ
መራመዱን ቀጠለ።
ወደ በሩ እየገባ አሁንም ሌላ ልጅ እየሮጠች መጥታ
''ጉዋደኛዬ ካስቀየመችህ ይቅርታ ትንሽ ወሰድ መለስ ስለሚያረጋት ነዉ''
ሌባ ጣትዋን ከአይንዋ አጠገብ ካለው ራስ ቅል
ዙርያ እያሽከረከረች አሳየችዉ
''ምንም አደል''እያለ ጥሏት ወደ ዉስጥ ዘለቀ።
ከመምህራን ማረፍያ ገብቶ የያዘውን ቦርሳ እቃ ማስቀመጫ
ዉስጥ ከቶ ከሌሎች መምህራን ጋር መተዋወቅ ጀመረ ትውውቁን
እንደጨረሰ ከመምህራን ሀላፊዉ ጋር የየእለት አለት የማስተማርያ
መመርያ ለመቀበል ወደ ሀላፊዉ በር ተጠግቶ አንኩዋኩዋ፡፡
''ይግቡ!"
ከዉስጥ ወደ ዉጪ በሰማው ድምፅ መሰረት በሩን ከፍቶ ገባ፡፡
ቢሮዉ ውስጥ ሌላ አንድ መምህር እና ሀላፊዉ
ተቀምጠዋል አስተማሪዉ
''ፍቃዱ እባላለሁ አማርኛ አስተማሪ ነኝ"
ከወንበሩ እንደመነሳት እያለ እጁን ዘረጋለት
"ፍፁም ሂስትሪ መምህር "ሰላም ተባባሉ
የመምህራን ሀላፊዉም
"አረፍ በል ልጅ ፍፁም ከኔ ጋር በቀደም ተዋዉቀናል...ይሄ
ወረቀት ያንተን የማስተማርያ ሰአት እና የምታስተምራቸውን
ክፍሎች የያዘ ነዉ ሌላ የምትጠይቀዉ ነገር ከሌለ
ጨርሰሀል..መልካሙን አመኝልሀለው::"
ከመምህር ፍቃዱ ጋር አንዳንድ ነገር እያወሩ በዛውም
ግቢዉን እና ክፍሎቹን እያስጎበኘዉ ወደ መጀመርያ ትምህርት
ወደ ሚሰጥበት ክፍል ሲደርሱ ቡሀላ ለመገናኘት ተቀጣጥረውተለያዩ፡፡
ወደ ክፍሉ ውስጥ ገብቶ መሀል ላይ ቆመ
በእርስ በእርስ ወሬ ደፍርሶ የነበረው
ክፍል ፀጥ ረጭ አለ ተማሪወቹ በሙሉ አይናቸዉን ተከሉበት
ላለመደናገጥ ልቡን አያደፋፈረ
"ፍፁም ደምሴ እባላለሁ ሂስትሪ ነው
የማስተምራችሁ እንደመጀመራችን ለመተዋወቅ እንዲረዳን
እናንተም በየተራ ስማችሁን ታስተዋዉቁኛላችሁ"
ሁሉም እየተነሳ ስሙን ለፈፁም ማስተዋወቅ ጀመረ
ተራዋ ደርሶ አንዷ
"ቤዛ"አለች ከወንበርዋ ተነስታ
ፍፁም እንዳያያት አንገትዋን ደፍታ
"እንደሌሎቹ ሙሉ ስምሽን ብትነግሪን?"
"ቤዛዊት መለሰ"ቀና ስትል ፊትዋን ለማየት ቻለ
የደሰደስ ያላት ቆንጇ ልጅ ናት ልቡ መምታት ጀመረች
"ከዚህ በፊት አዉቃታለሁ....?እራሱን ጠየቀ
ብዙ ለማሰብ ሞከረ ሲያስታዉስ
ጠዋት ሰአት ጠይቃ የሰደበችዉ ልጅ ናት፡፡
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍5
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#በክፍለማርያም
ፍፁም ከመምህር ፍቃዱ ጋር በሻይ ሰዓት ቁጭ ቡለዉ እያወሩ መምህር ፍቃዱ
"እዚህ ግቢ ዉስጥ ደግሞ ከወጣት ሴት ተማሪወች ጋር እንዳትታይ"
ፈገግ እያለ እና ፍፁምን ጀርባዉን መታ መታ እያረገ ነገረዉ
"ለትምህርት ቤቱም ለኛም ስም መጥፍያ ነዉ እንደማይክእዚህች ከሚማሩት ተማሪወች ጥቂት የእድሜ ልዩነት
ቢኖርህ ነዉ"
እንደ ምክርም እንደ ተግሳፅም እየቃጣዉ።
ፍፁምም በንግግሩ ቢከፋም ላለማስቀየም የዉሸት ፈገግ አለለት መስማማቱን ለመግለፅ በሚመስል መልኩ።
ቤዛዊት ጎበዝ ከሚባሉት ተማሪወች ተርታ አትመደብም
መሀል ላይ ያለች ቢሆንም በወሬ እና በመረበሽ የሚስተካከላት የለም ግን የፍፁም ክፍለ ጊዜ ደርሶ
ሲያስተምር ፀጥ ረጭ ብላ ትኩረትዋን ሰብስባ
ትቀመጣለች ጉዋደኞችዋ ሁሉ ታዝበዋታል በተለይ ትዕግሥት
"አረ የኛ ጎበዝ ተማሪ ከትምህርቱ ነዉ ከአስተማሪዉ ፍቅር የያዘሽ "
እያለች ትስቅባታለች።
ቤዛዊትም ጉዋደኛዋ ስታሾፍባት ኮስተር ብላ
"ምን አገባሽ"
ከማለት ዉጪ ሌላ መልስ አትመልስላትም
የልቧን ስሜት ግን ትሰማዋለች ፍፁምን ሰዓት ሳትጠይቀዉ
በፊት ገና የትምህርት ቤቱ በር አካባቢ ተማርካ ነበር።
ምኑ እንደሳባት ባታዉቅም ፀጉሩ በስርአት የተከረከመ
ጠይም መልኩ ላይ ለሰዉ የማይታይ ለእስዋ ግን የታያት
እና የተነበበላት የሆነ ነገር አለ ግን አስተማሪዬ ይሆናል
ብላ አላሰበችም ሰዓት የጠየቀችዉም ሆን ብላ ነበር።
መምህር ፍፁም እያስተማረ ተማሪወችን በአይኑ
ይከታተላል በመሀል ለእሱ በድንገት እስዋ ግን ሆን ብላ
የቤዛዊት አይኖች ቀጥታ ከአይኖቹ ጋር ተገናኙ የቤዛ አይኖች ሁለቱም ገርበብ ብለዉ እያዩት ቢሆንም
ቀኝ አይንዋ ብቻዉን ተዘግቶ ተከፈተ ቤዛዊት የምታረገዉን እያየ
"ምን መሆንዋ ነዉ" አለ በልቡ
ማስተማሩን ግን ቀጠለ ድጋሜም በድንገት ሲተያዩ ጠቀሰችዉ
ያልጠበቀዉ ነገር ስለሆነ ሁለት አይነት ስሜት ተሰማዉ
የመ'ፈለግ ስሜት በተቃራኒዉ የመናቅ መፈለጉን ሲያስብ
ከሙያዉ ስነ ምግባር ጋር የሚጋጭ መሰለዉ መናቁን
ሲያስብ ቤዛን እንደ ጋጠ ወጥ ተመለከታት ክፍለጊዜዉ
ሲያልቅ ለብቻዋ ጠርቶ ሊቆጣት እና ሊያስጠነቅቃት አስቦ ነበር ።
ግን እንደ አስተማሪ መሆን አቃተዉ ተወዉ ምንም አላላትም።
ከትምህርት ቤቱ እንደወጣ ቀጥታ ወደ ቤቱ አመራ ተከራይቶ የሚኖርበት ቤት ጠባብ ብትሆንመ ዉበት አላት
አልጋዉ በስርዓት ተነጥፎዋል መደርደርያዉ ዉስጥ
ያሉት መፅሀፎቹ በወግ በወጉ ተቀምጠዋል
ለማብሰያነት የሚጠቀምባቸዉ እቃወች ታጥበዉ
በአንድ እረድፍ ተስተካክለዉ ተቀምጠዋል በአጠቃላይ
ቤቱን በፅዳት ይዞታል።
ጥቂት ጋደም ካለ ብኃላ ማንበብ ያለበት መፅሀፍ
እንዳለ ሲያስታዉስ መተኛት ፈልጎ ስለ ነበር
ቅፍፍ እያለዉ ከአልጋዉ ተነስቶ ከመደርደርያዉ
የሚፈልገዉን መፅሀፍ መርጦ ወንበር ላይ ተቀመጠ።
እያነበበ ሳያቀዉ ሀሳቡ ወደ ሌላ ቦታ ሄደ አይን ይታየዋል
አይኑን ሲከተል የቤዛዊት ፊት ታየዉ እየጠቀሰችዉ ነዉ
አንድ አይንዋን ብቻ ጭፍን አርጋ ስታበራዉ አፍዋ በትንሹ ተከፍቶ ከፊት ያሉት የሚያምሩት ጥርሶቿ ይታያሉ ጉንጮ ላይ
ሳትስቅ እራሱ ፈገግታ አለ ሁሉ ነገርዋ ደስ ይላል
ይሄንን እያሰበ በድንገት ማንበብን እንደረሳዉ ሲገባዉ
"ምን ነካኝ!!ምን ሆኜ ነዉ ስለሷ የማስበዉ
ከአሁኑ ማስቆም አለብኝ" ብሎ መፅሀፉን ዘጋዉ።
"ቤዛዊትን ነገ ስርዓት እንድትይዝ እነግራታለሁ" እያለ
ብቻዉን እያወራ በዛዉ እንቅልፍ አሸንፎት ወደ አልጋዉ አመራ ለነገ ቀጠሮ እየያዘ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#በክፍለማርያም
ፍፁም ከመምህር ፍቃዱ ጋር በሻይ ሰዓት ቁጭ ቡለዉ እያወሩ መምህር ፍቃዱ
"እዚህ ግቢ ዉስጥ ደግሞ ከወጣት ሴት ተማሪወች ጋር እንዳትታይ"
ፈገግ እያለ እና ፍፁምን ጀርባዉን መታ መታ እያረገ ነገረዉ
"ለትምህርት ቤቱም ለኛም ስም መጥፍያ ነዉ እንደማይክእዚህች ከሚማሩት ተማሪወች ጥቂት የእድሜ ልዩነት
ቢኖርህ ነዉ"
እንደ ምክርም እንደ ተግሳፅም እየቃጣዉ።
ፍፁምም በንግግሩ ቢከፋም ላለማስቀየም የዉሸት ፈገግ አለለት መስማማቱን ለመግለፅ በሚመስል መልኩ።
ቤዛዊት ጎበዝ ከሚባሉት ተማሪወች ተርታ አትመደብም
መሀል ላይ ያለች ቢሆንም በወሬ እና በመረበሽ የሚስተካከላት የለም ግን የፍፁም ክፍለ ጊዜ ደርሶ
ሲያስተምር ፀጥ ረጭ ብላ ትኩረትዋን ሰብስባ
ትቀመጣለች ጉዋደኞችዋ ሁሉ ታዝበዋታል በተለይ ትዕግሥት
"አረ የኛ ጎበዝ ተማሪ ከትምህርቱ ነዉ ከአስተማሪዉ ፍቅር የያዘሽ "
እያለች ትስቅባታለች።
ቤዛዊትም ጉዋደኛዋ ስታሾፍባት ኮስተር ብላ
"ምን አገባሽ"
ከማለት ዉጪ ሌላ መልስ አትመልስላትም
የልቧን ስሜት ግን ትሰማዋለች ፍፁምን ሰዓት ሳትጠይቀዉ
በፊት ገና የትምህርት ቤቱ በር አካባቢ ተማርካ ነበር።
ምኑ እንደሳባት ባታዉቅም ፀጉሩ በስርአት የተከረከመ
ጠይም መልኩ ላይ ለሰዉ የማይታይ ለእስዋ ግን የታያት
እና የተነበበላት የሆነ ነገር አለ ግን አስተማሪዬ ይሆናል
ብላ አላሰበችም ሰዓት የጠየቀችዉም ሆን ብላ ነበር።
መምህር ፍፁም እያስተማረ ተማሪወችን በአይኑ
ይከታተላል በመሀል ለእሱ በድንገት እስዋ ግን ሆን ብላ
የቤዛዊት አይኖች ቀጥታ ከአይኖቹ ጋር ተገናኙ የቤዛ አይኖች ሁለቱም ገርበብ ብለዉ እያዩት ቢሆንም
ቀኝ አይንዋ ብቻዉን ተዘግቶ ተከፈተ ቤዛዊት የምታረገዉን እያየ
"ምን መሆንዋ ነዉ" አለ በልቡ
ማስተማሩን ግን ቀጠለ ድጋሜም በድንገት ሲተያዩ ጠቀሰችዉ
ያልጠበቀዉ ነገር ስለሆነ ሁለት አይነት ስሜት ተሰማዉ
የመ'ፈለግ ስሜት በተቃራኒዉ የመናቅ መፈለጉን ሲያስብ
ከሙያዉ ስነ ምግባር ጋር የሚጋጭ መሰለዉ መናቁን
ሲያስብ ቤዛን እንደ ጋጠ ወጥ ተመለከታት ክፍለጊዜዉ
ሲያልቅ ለብቻዋ ጠርቶ ሊቆጣት እና ሊያስጠነቅቃት አስቦ ነበር ።
ግን እንደ አስተማሪ መሆን አቃተዉ ተወዉ ምንም አላላትም።
ከትምህርት ቤቱ እንደወጣ ቀጥታ ወደ ቤቱ አመራ ተከራይቶ የሚኖርበት ቤት ጠባብ ብትሆንመ ዉበት አላት
አልጋዉ በስርዓት ተነጥፎዋል መደርደርያዉ ዉስጥ
ያሉት መፅሀፎቹ በወግ በወጉ ተቀምጠዋል
ለማብሰያነት የሚጠቀምባቸዉ እቃወች ታጥበዉ
በአንድ እረድፍ ተስተካክለዉ ተቀምጠዋል በአጠቃላይ
ቤቱን በፅዳት ይዞታል።
ጥቂት ጋደም ካለ ብኃላ ማንበብ ያለበት መፅሀፍ
እንዳለ ሲያስታዉስ መተኛት ፈልጎ ስለ ነበር
ቅፍፍ እያለዉ ከአልጋዉ ተነስቶ ከመደርደርያዉ
የሚፈልገዉን መፅሀፍ መርጦ ወንበር ላይ ተቀመጠ።
እያነበበ ሳያቀዉ ሀሳቡ ወደ ሌላ ቦታ ሄደ አይን ይታየዋል
አይኑን ሲከተል የቤዛዊት ፊት ታየዉ እየጠቀሰችዉ ነዉ
አንድ አይንዋን ብቻ ጭፍን አርጋ ስታበራዉ አፍዋ በትንሹ ተከፍቶ ከፊት ያሉት የሚያምሩት ጥርሶቿ ይታያሉ ጉንጮ ላይ
ሳትስቅ እራሱ ፈገግታ አለ ሁሉ ነገርዋ ደስ ይላል
ይሄንን እያሰበ በድንገት ማንበብን እንደረሳዉ ሲገባዉ
"ምን ነካኝ!!ምን ሆኜ ነዉ ስለሷ የማስበዉ
ከአሁኑ ማስቆም አለብኝ" ብሎ መፅሀፉን ዘጋዉ።
"ቤዛዊትን ነገ ስርዓት እንድትይዝ እነግራታለሁ" እያለ
ብቻዉን እያወራ በዛዉ እንቅልፍ አሸንፎት ወደ አልጋዉ አመራ ለነገ ቀጠሮ እየያዘ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍1
#የአባይ_ልጅ_አይጥማው
መሰረት የሚሆን ቢጠፋ እንኳ ድንጋይ
ሀገር ጥሎ ሽሽት እንዲቀር ከአባይ
እያንዳንዱ አካሌ ተነስቶ ከኔ ላይ
አጥንቴ ተለቅሞ ካፈሩ ተማግሮ
ጅማቴ ተመዞ እሱን አጠንክሮ
በቀጠነው ደሜ ስጋዬ ተቦክቶ
ካጥንቴ ማገር ላይ ልስኑ ተመትቶ
ነፍሴም ተሰውቶ ከጦር ከዘመቻ
“ የአባይን ልጅ ጠማው " አያሰማኝ ብቻ !!!
🔘ፋሲል ሃይሉ🔘
መሰረት የሚሆን ቢጠፋ እንኳ ድንጋይ
ሀገር ጥሎ ሽሽት እንዲቀር ከአባይ
እያንዳንዱ አካሌ ተነስቶ ከኔ ላይ
አጥንቴ ተለቅሞ ካፈሩ ተማግሮ
ጅማቴ ተመዞ እሱን አጠንክሮ
በቀጠነው ደሜ ስጋዬ ተቦክቶ
ካጥንቴ ማገር ላይ ልስኑ ተመትቶ
ነፍሴም ተሰውቶ ከጦር ከዘመቻ
“ የአባይን ልጅ ጠማው " አያሰማኝ ብቻ !!!
🔘ፋሲል ሃይሉ🔘
#ፍቅርን_በትወና
በየትያትር ቤቱ
በየፊልሙ ደጃፍ
ምስላችን ባይኖርም
ስማችን ባይጻፍ
በየ ቲቪው መስኮት
ኑ እዩን ! ባንልም
ፊልማችን ሲመረቅ
ታዳሚ ባይኖርም
እኛው ብንገኝም
ፍቅርን እንድንተውን
ድርሰቱን ሲሰጠን
ከሆሊውድ ደጃፍ
ከቦሊውድ ጓሮ
በጠፍ በጨረቃ
ዞሮ ተዟዙሮ
የተሻሊተዋኝ
ቢያጣ ተቸግሮ
ነበር የመረጠን
አንቺን ከኔ ጋራ
ገቢሩ እንዲፈጸም
ፍቅርን እንድንሰራ፡፡
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
በየትያትር ቤቱ
በየፊልሙ ደጃፍ
ምስላችን ባይኖርም
ስማችን ባይጻፍ
በየ ቲቪው መስኮት
ኑ እዩን ! ባንልም
ፊልማችን ሲመረቅ
ታዳሚ ባይኖርም
እኛው ብንገኝም
ፍቅርን እንድንተውን
ድርሰቱን ሲሰጠን
ከሆሊውድ ደጃፍ
ከቦሊውድ ጓሮ
በጠፍ በጨረቃ
ዞሮ ተዟዙሮ
የተሻሊተዋኝ
ቢያጣ ተቸግሮ
ነበር የመረጠን
አንቺን ከኔ ጋራ
ገቢሩ እንዲፈጸም
ፍቅርን እንድንሰራ፡፡
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#በክፍለማርያም
በነጋታዉ ፍፁም ማስተማሩን እንደጨረሰ
ቤዛዊትን የመምህራን ቢሮ እንድትመጣ አዟት ከክፍል ወጣ ከበሩ ወጥቶ ጥቂት እርምጃወች እንደተራመደ።
"ቲቸር" የሚል ድምፅ የሰማ ስለመሰለዉ ዞረ ቤዛዊት ናት
"ፈለግከኝ ነበር"
ፈጠን ፈጠን እያለች ስታወራ ትንፋሽዋም ቁርጥ ቁርጥ ይላል።
ፊትዋ ላይ ምንም የጥፋተኝነት ስሜት የለም እንደዉም ምን ሊለኝ ይሆን የሚል ጉጉት አድሮባታል
"ትላንት ምንም ያረግሽዉ ነገር የለም?"
መቆጣት ፈልጎ ቢኮሳተርም አልቻለበትም
ቤዛዊት ለማስታወስ ሌባ ጣትዋን አፍዋ ላይ አስቀምጣዉ የአይኖችዋን ብሌኖች ወደ ቅንድብዋ ላከቻቸዉ
"እ ምንም አላስታዉስም .......የጠቀስኩክ ግን"
አለችና አንጠልጥላ ተወቸዉ
ፍፁም እስዋ ይሄን ስትል ድፍረትዋ ገርሞት
ለይምሰል ተኮሳትሮ እያያት ነዉ ቤዛዊት ካቆመችበት ቀጠለች
"ስለ ጠቀስኩኩ ተናደክ ከሆነ ይቅርታ ቲቸር አይለመደኝም
ለርዕሰ መምህሩ አሳልፈህ ከሰጠሀኝ ቀጥታ ነዉ
የሚያባርረኝ ሌላ ጥፋትም አለብኝ እባክህ እዉነት አይለመደኝም ቲቸር ሳላስበዉ በስህተት ነዉ"
እያለች እንደ መለመን እጆችዋን እያርገበገበች ተጠጋችዉ
"ቆይ ቆይ" አለና ፍፁም እንደ ማሰብ ብሎ
ድጋሜ በደንብ ተመለከታት
እድሜዋን ሲገምት 20 አመት ቢሆናት ነዉ ግን
ቁመት ስላላት ትልቅ ትመስላለች የለበሰችዉ የዬኒፎርም
ቀሚስ በጣም አሳጥራዉ ከጉልበትዋ ከፍ ብሎ ታፋዋን
በከፊል ያሳያል ሰዉነትዋም ሞላ ያለ ነዉ ትከሻዋ ላይ በቅርብ የተተኮሰ የሚመስለዉ ፀጉርዋ ተመችቶት ተኝቷል
ጆሮዋ ፍፁም የሚላትን ለመስማት ቀስራቸዋለች
አይኖችዋ እንዲያዝንላት እየተለማመጡት ነዉ።
ድምፁን ጎርነን አርጎ
"ሁለተኛ እንዳይለመድሽ እኔ አስተማሪሽ እንጂ እኩያሽ አደለሁም!.."
አዉርቶ ሳይጨርስ ይቅርታ እንዳረገላት ስታዉቅ
ደስ ብሎዋት አቀፈችዉ ወድያዉ
"በጣም ይቅርታ ቲቸር"
ብላዉ እየሳቀች ወደ ክፍልዋ እየተመለሰች
ስታቅፈዉ ሳያስበዉ ስለሆነ ደንግጦ ነበር
ግልፅነትዋን ግን ስለወደደላት ዝም አላት
ጥቂት እንደተራመደች ግንስሟን እንደማያዉቀዉ እየሆነ
"ማን ነሽ ቤዛዊት?"
"አቤት"
አለችዉ በቅርብ እርቀት ላይ ሆና
"ይሄ ያረግሽዉን ቀሚስ ቀይሪዉ ላንቺ ሳይሆን
ገና ለተወለደ ህፃን ልጅ ነዉ የሚሆነዉ"
ፈገግ እያለ ነበር የነገራት
"እሺ ፍፄ"
ብላዉ ከፊቱ እርቃ ሄደች
እስዋን ቆሞ ለየት ያለ ባህሪ ነዉ ያላት ብሎ ስትሄድ
በተመስጦ እየተመለከታት መምህር ፍቃዱ ከጀርባዉ መጥቶ
"ከዚች ቀዉስ ጋር ደግሞ ምን አነካካክ?"አለዉ
"ቀዉስ?ምን ለማለት ነዉ ያዉ አስተማሪዋ አደለሁ እንዴ" መለሰለት በልቡ እንዴትቀዉስ ይላታል እያለ።
ፍቃዱ ስለ ቤዛዊት የሚያዉቀዉን መናገር ቢፈልግም
ክፍል የሚገባበት ሰአት ስለደረሰ
"ዛሬ አርብ አደል ማታ አንድ ሁለት እያልን እነግርሀለዉ ስለልጅቷ"
ብሎት ተለያዬ
ከተቀጣጠሩበት ሆቴል ስለ ቤዛዊት መስማትም ስለፈለገ
ቀድሞ የተገኘዉ ፍፁም ነበር።
ፍቃዱ እንደመጣ ወድያዉ ምግብ አዘዙ
ምግቡ ቀርቦ በልተዉ ከጨረሱ በኋላ ቢራ አዘዉ እየጠጡ
ፍቃዱ አዲስ ስለገዛዉ መፀሀፉ ማዉራት ጀመረ።ፍፁም አቁዋርጦት ስለ ቤዛዊት ሊጠይቀዉ አለና
"ምን ይለኛል ቡኀላ ወደዳት ብሎ ከስራ ቢያስተጎጉለኝስ
ደግሞ እኔ እራሴ ምን ሆኜ ነዉ ትኩረት የምሰጣት
መቼስ አልወደድኩዋትም"
ሳይታሰበዉ ድምፅ አዉጥቶ ሳቀ
"ምን የሚያስቅ ነገር ተገኘ ጃል ብቻህን የምትፍነከነከዉ
ለኛም አካፍለና እንወቀዉ"
ብሎ ፍቃዱ ሲያፋጥጠዉ
"መጠጥ ስለማልችል ነዉ ሁለት ጠጣሁ በቃ መሳቅ ነዉ"
የኔ ተፈጥሮ ብሎ መለሰለት ድጋሜ እየሳቀ።
ትንሽ የፍቃዱን የማያልቅ ወሬ ከሰሙ በኃላ ፍፁም
"እየመሸ ስለሆነ ወደየ ቤታችን እንሂድ ሌላዉ ደግሞ
ቅድሞ እነግርሀለዉ ያልከኝን ሳትነግረኝ....?
አለዉ ምን ይለኝ ይሆን በሚል ስሜት እያየዉ
ፍቃዱም ሰአቱን አይቶ
"ሳናስበዉ መሸ እዉነትህን ነዉ እንንቀሳቀስ
ሂሳብ በኔ ግብዣ ነዉ "
ብሎ ከፍሎ ተነሳ ሳይመልስለት
ከሆቴሉ በር እንደወጡ ሊለያዬ ቻዉ ተባብለዉ
በየ መንገዳቸዉ ሊሄዱ ሲሉ ፍቃዱ ማዉራት ጀመረ።
"ቤዛ ነዉ ቤዛዊት የሚሎት የታወቀ የሀብታም ልጅ ናት
ግን የሚያሳዝነዉ ትንሽ አይምሮዋ ደህና አይመስለኝም
አንድ አመት አቋርጣ ነበር ዘንድሮ ትንሽ አገግማ ነዉ እንጂ መማር የጀመረችዉ"አለዉና
"ቤት መግባትህን ደዉለህ አሳዉቀኝ"ብሎት ሄደ።
ፍፁም በእግሩ ወደ ቤቱ እየሄደ ከልቡ ለቤዛ ማሰብ ጀመረ
" ምን አይነት ህመም ይሆን ምስኪን እንኩዋንም ጠዋት
ክፉ ነገር አልተናገርኩዋት ግን እኮ ምንም የሚያማት
አትመስልም "
እያለ ቤቱ ደረሰ።
ለሊቱን በአብዛኛዉ እንቅልፍ እስኪወስደዉ ድረስ
ቤዛዊትን ከጭንቅላቱ አላወጣትም ስለስዋ በጣም ሲያስብ እና ስለስዋ የማወቅ ጉጉት አድሮበት ሲገላበጥ
ለሊቱ እንደምንም ነጋለት።
በጠዋት ተነስቶ ተጣጥቦ ቁርሱን በልቶ ከጨረሰ በኃላ መፅሀፍቶቹን ቦርሳ ዉስጥ ከቶ አነገበዉ እና በሩን ቆልፍ ወጣ
የግቢዉ መዉጫ በር ጋር ሲደርስ ሰዉ አይቶ ቆመ
ቤዛዊት የእግር ጥፍርዋ ድረስ የሚደርስ ዩኒፎርም ቀሚስ ለብሳ ቆማ እየጠበቀችዉ ነበር ቀይሪ ስላላት አዲስ መግዛትዋን ልታሳየዉ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#በክፍለማርያም
በነጋታዉ ፍፁም ማስተማሩን እንደጨረሰ
ቤዛዊትን የመምህራን ቢሮ እንድትመጣ አዟት ከክፍል ወጣ ከበሩ ወጥቶ ጥቂት እርምጃወች እንደተራመደ።
"ቲቸር" የሚል ድምፅ የሰማ ስለመሰለዉ ዞረ ቤዛዊት ናት
"ፈለግከኝ ነበር"
ፈጠን ፈጠን እያለች ስታወራ ትንፋሽዋም ቁርጥ ቁርጥ ይላል።
ፊትዋ ላይ ምንም የጥፋተኝነት ስሜት የለም እንደዉም ምን ሊለኝ ይሆን የሚል ጉጉት አድሮባታል
"ትላንት ምንም ያረግሽዉ ነገር የለም?"
መቆጣት ፈልጎ ቢኮሳተርም አልቻለበትም
ቤዛዊት ለማስታወስ ሌባ ጣትዋን አፍዋ ላይ አስቀምጣዉ የአይኖችዋን ብሌኖች ወደ ቅንድብዋ ላከቻቸዉ
"እ ምንም አላስታዉስም .......የጠቀስኩክ ግን"
አለችና አንጠልጥላ ተወቸዉ
ፍፁም እስዋ ይሄን ስትል ድፍረትዋ ገርሞት
ለይምሰል ተኮሳትሮ እያያት ነዉ ቤዛዊት ካቆመችበት ቀጠለች
"ስለ ጠቀስኩኩ ተናደክ ከሆነ ይቅርታ ቲቸር አይለመደኝም
ለርዕሰ መምህሩ አሳልፈህ ከሰጠሀኝ ቀጥታ ነዉ
የሚያባርረኝ ሌላ ጥፋትም አለብኝ እባክህ እዉነት አይለመደኝም ቲቸር ሳላስበዉ በስህተት ነዉ"
እያለች እንደ መለመን እጆችዋን እያርገበገበች ተጠጋችዉ
"ቆይ ቆይ" አለና ፍፁም እንደ ማሰብ ብሎ
ድጋሜ በደንብ ተመለከታት
እድሜዋን ሲገምት 20 አመት ቢሆናት ነዉ ግን
ቁመት ስላላት ትልቅ ትመስላለች የለበሰችዉ የዬኒፎርም
ቀሚስ በጣም አሳጥራዉ ከጉልበትዋ ከፍ ብሎ ታፋዋን
በከፊል ያሳያል ሰዉነትዋም ሞላ ያለ ነዉ ትከሻዋ ላይ በቅርብ የተተኮሰ የሚመስለዉ ፀጉርዋ ተመችቶት ተኝቷል
ጆሮዋ ፍፁም የሚላትን ለመስማት ቀስራቸዋለች
አይኖችዋ እንዲያዝንላት እየተለማመጡት ነዉ።
ድምፁን ጎርነን አርጎ
"ሁለተኛ እንዳይለመድሽ እኔ አስተማሪሽ እንጂ እኩያሽ አደለሁም!.."
አዉርቶ ሳይጨርስ ይቅርታ እንዳረገላት ስታዉቅ
ደስ ብሎዋት አቀፈችዉ ወድያዉ
"በጣም ይቅርታ ቲቸር"
ብላዉ እየሳቀች ወደ ክፍልዋ እየተመለሰች
ስታቅፈዉ ሳያስበዉ ስለሆነ ደንግጦ ነበር
ግልፅነትዋን ግን ስለወደደላት ዝም አላት
ጥቂት እንደተራመደች ግንስሟን እንደማያዉቀዉ እየሆነ
"ማን ነሽ ቤዛዊት?"
"አቤት"
አለችዉ በቅርብ እርቀት ላይ ሆና
"ይሄ ያረግሽዉን ቀሚስ ቀይሪዉ ላንቺ ሳይሆን
ገና ለተወለደ ህፃን ልጅ ነዉ የሚሆነዉ"
ፈገግ እያለ ነበር የነገራት
"እሺ ፍፄ"
ብላዉ ከፊቱ እርቃ ሄደች
እስዋን ቆሞ ለየት ያለ ባህሪ ነዉ ያላት ብሎ ስትሄድ
በተመስጦ እየተመለከታት መምህር ፍቃዱ ከጀርባዉ መጥቶ
"ከዚች ቀዉስ ጋር ደግሞ ምን አነካካክ?"አለዉ
"ቀዉስ?ምን ለማለት ነዉ ያዉ አስተማሪዋ አደለሁ እንዴ" መለሰለት በልቡ እንዴትቀዉስ ይላታል እያለ።
ፍቃዱ ስለ ቤዛዊት የሚያዉቀዉን መናገር ቢፈልግም
ክፍል የሚገባበት ሰአት ስለደረሰ
"ዛሬ አርብ አደል ማታ አንድ ሁለት እያልን እነግርሀለዉ ስለልጅቷ"
ብሎት ተለያዬ
ከተቀጣጠሩበት ሆቴል ስለ ቤዛዊት መስማትም ስለፈለገ
ቀድሞ የተገኘዉ ፍፁም ነበር።
ፍቃዱ እንደመጣ ወድያዉ ምግብ አዘዙ
ምግቡ ቀርቦ በልተዉ ከጨረሱ በኋላ ቢራ አዘዉ እየጠጡ
ፍቃዱ አዲስ ስለገዛዉ መፀሀፉ ማዉራት ጀመረ።ፍፁም አቁዋርጦት ስለ ቤዛዊት ሊጠይቀዉ አለና
"ምን ይለኛል ቡኀላ ወደዳት ብሎ ከስራ ቢያስተጎጉለኝስ
ደግሞ እኔ እራሴ ምን ሆኜ ነዉ ትኩረት የምሰጣት
መቼስ አልወደድኩዋትም"
ሳይታሰበዉ ድምፅ አዉጥቶ ሳቀ
"ምን የሚያስቅ ነገር ተገኘ ጃል ብቻህን የምትፍነከነከዉ
ለኛም አካፍለና እንወቀዉ"
ብሎ ፍቃዱ ሲያፋጥጠዉ
"መጠጥ ስለማልችል ነዉ ሁለት ጠጣሁ በቃ መሳቅ ነዉ"
የኔ ተፈጥሮ ብሎ መለሰለት ድጋሜ እየሳቀ።
ትንሽ የፍቃዱን የማያልቅ ወሬ ከሰሙ በኃላ ፍፁም
"እየመሸ ስለሆነ ወደየ ቤታችን እንሂድ ሌላዉ ደግሞ
ቅድሞ እነግርሀለዉ ያልከኝን ሳትነግረኝ....?
አለዉ ምን ይለኝ ይሆን በሚል ስሜት እያየዉ
ፍቃዱም ሰአቱን አይቶ
"ሳናስበዉ መሸ እዉነትህን ነዉ እንንቀሳቀስ
ሂሳብ በኔ ግብዣ ነዉ "
ብሎ ከፍሎ ተነሳ ሳይመልስለት
ከሆቴሉ በር እንደወጡ ሊለያዬ ቻዉ ተባብለዉ
በየ መንገዳቸዉ ሊሄዱ ሲሉ ፍቃዱ ማዉራት ጀመረ።
"ቤዛ ነዉ ቤዛዊት የሚሎት የታወቀ የሀብታም ልጅ ናት
ግን የሚያሳዝነዉ ትንሽ አይምሮዋ ደህና አይመስለኝም
አንድ አመት አቋርጣ ነበር ዘንድሮ ትንሽ አገግማ ነዉ እንጂ መማር የጀመረችዉ"አለዉና
"ቤት መግባትህን ደዉለህ አሳዉቀኝ"ብሎት ሄደ።
ፍፁም በእግሩ ወደ ቤቱ እየሄደ ከልቡ ለቤዛ ማሰብ ጀመረ
" ምን አይነት ህመም ይሆን ምስኪን እንኩዋንም ጠዋት
ክፉ ነገር አልተናገርኩዋት ግን እኮ ምንም የሚያማት
አትመስልም "
እያለ ቤቱ ደረሰ።
ለሊቱን በአብዛኛዉ እንቅልፍ እስኪወስደዉ ድረስ
ቤዛዊትን ከጭንቅላቱ አላወጣትም ስለስዋ በጣም ሲያስብ እና ስለስዋ የማወቅ ጉጉት አድሮበት ሲገላበጥ
ለሊቱ እንደምንም ነጋለት።
በጠዋት ተነስቶ ተጣጥቦ ቁርሱን በልቶ ከጨረሰ በኃላ መፅሀፍቶቹን ቦርሳ ዉስጥ ከቶ አነገበዉ እና በሩን ቆልፍ ወጣ
የግቢዉ መዉጫ በር ጋር ሲደርስ ሰዉ አይቶ ቆመ
ቤዛዊት የእግር ጥፍርዋ ድረስ የሚደርስ ዩኒፎርም ቀሚስ ለብሳ ቆማ እየጠበቀችዉ ነበር ቀይሪ ስላላት አዲስ መግዛትዋን ልታሳየዉ።
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍4
#አውቃለሁ_አታውቂም!
ክንፉ የተሰበረ፣ የታከተው መንፈስ፣
እንደ ክረምት ስማይ ፣ በእጦት ብልጭታ፣ ሲታረስ፣
.............................ሲመታ፣
ልብሽ ጽኑ ድጋፍ፣ እንዳጠነከረኝ፤
ፍቅርሽ አዲስ ምእራፍ፣ ገልቦ እንዳስጀመረኝ!
ታውቂለሽ?! ..
ድፍን ባል ለሊት፣
የብርሀን ሸማ፤
ጭር ባላ ውድቅት፣
ያሬዳዊ ዜማ፤
መሆንሽን
..............ታውቂያለሽ?!
አውቃለሁ አታውቂም!
🔘በድሉ ዋቅጅራ🔘
የካቲት፣ 2011፤ አዲስ አበባ፡፡
ክንፉ የተሰበረ፣ የታከተው መንፈስ፣
እንደ ክረምት ስማይ ፣ በእጦት ብልጭታ፣ ሲታረስ፣
.............................ሲመታ፣
ልብሽ ጽኑ ድጋፍ፣ እንዳጠነከረኝ፤
ፍቅርሽ አዲስ ምእራፍ፣ ገልቦ እንዳስጀመረኝ!
ታውቂለሽ?! ..
ድፍን ባል ለሊት፣
የብርሀን ሸማ፤
ጭር ባላ ውድቅት፣
ያሬዳዊ ዜማ፤
መሆንሽን
..............ታውቂያለሽ?!
አውቃለሁ አታውቂም!
🔘በድሉ ዋቅጅራ🔘
የካቲት፣ 2011፤ አዲስ አበባ፡፡