#ወደ_ምንም_የሚያደርሰው_መንገድ
ቸኳይ የሚመስለው
ፈጣን የሚመስለው .
በውልውል መኪና
በፋሽን መጫሚያ
ወይም በባዶ እግሩ
ሽው እልም የሚለው
ይኼ ሁሉ ምሁር፣ ይኼ ሁሉ ማይም
መንገዱን የሞላው ከታችም ከላይም
ሲመላለስ እንጂ ሲደርስ አይታይም።
🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
ቸኳይ የሚመስለው
ፈጣን የሚመስለው .
በውልውል መኪና
በፋሽን መጫሚያ
ወይም በባዶ እግሩ
ሽው እልም የሚለው
ይኼ ሁሉ ምሁር፣ ይኼ ሁሉ ማይም
መንገዱን የሞላው ከታችም ከላይም
ሲመላለስ እንጂ ሲደርስ አይታይም።
🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
👍1
#በኔ_የደረሰ•
፡
፡
#ክፍል_ሦስት
፡
፡
#በጥላሁን
...እሄ መፈላሰፍ ነው እንዴ መፈላሰፍ እራሱ ምን ማለት ነው! ወጣም ወረደም ፍቅር የያዘው ሰው ሁለመናው ማፍቀሩን ስለሚናገር ምን ልናገር ብዬ ባልጨነቅስ!
የእረፍት ሰአት ተደወለና ተያይዘን ትንሽ እንደሄድን
"ለምን ነበር እረፍት ሰአት ልታናግሪኝ የፈለከው ሶልዬ?" ስትለኝ ደንግጬ አይን አይኗን ከማየት በስተቀር ሌላው እንኳን ቢቀር ወዬ ሊሊዬ የምትለውን ቃል ለመናገር ብሞክር ኔትወርኩ እንደጠፋ ስልክ ምላሴ ላይ እየተሽከረከረች አልወርድ አለችኝ።
የስልክ ኔትወርክስ ቦታ በመቀያየር ይፈለግ ይሆናል የኔን ኔትወርክ ምኑን ቀያይሬ ላምጣው!
ቸርነቱ ብዙ አንደበቱን ሰጥቶኝ
ፍቅሬን እንዳልገልጠው ፍቅርሽ ዲዳ አረገኝ እባክሽን ማሬ ያንደበቴን ትተሽ
ውስጤን ተረጅልኝ አይኔን ተመልክተሽ!!
ብለው ዘፍነው ይሆን እንዴ ዘፋኛቹ ?
አይመስለኝም •••
መጨነቄን በማስተዋል ስታይ የነበረችው ሊሊ
"ሶልዬ አትጨነቅ በቃ እንደምትወደኝ እንኳን እኔ ጓደኛቼም ያውቃሉ!
ታፈቅረኛለህ አደል?
እሱን ልትነግረኝ ፈልገህ ነው አደል እንዲህ ፈንጅ እንደረገጠ ሰው በቆምክበት ደርቀህ ምላስህም ሰውነትህም አልንቀሳቀስ ያለው ?ስትለኝ ጆሮዬን ማመን ተሳነኝ ።
ንግግሯ ምላሴ የታሰረበትን ገመድ በጣጠሰው መሰለኝ
" ሊሊዬ አዎ አፈቅርሻለሁ ግን እንደማፈቅርሽ በምን አውቅሽ ?
ጓደኛችሽ እንዴት አወቁ ? ስላት ሳቋን ለቀቅችው
"አንተስ እንዳፈቀርከኝ በምን አወክ? ብላ ግራ የገባው ጥያቄ በመጠየቅ ግራ አጋባችኝ ቢሆንም ምላሴ ተፈቷልና ለመመለስ አልቦዘንኩም•••
እኔማ እንዴት አላውቅም ሊሊዬ
ለሰከንድ ስላንቺና አንቺን ከማሰብ ተዘናግቼ አላውቅም ።
የሚዘፈነው የፍቅር ዘፈን በሙሉ ላንቺ የተዘፈነ ይመስለኛል ።
በፍቅሯ የሆንኩትን በሙሉ ለመዘርዘር ሲዳዳኝ •••
አንገቴ ላይ ድንገት ተጠምጥማ " እኔም እወድሀለሁኮ ሶልዬ!" ስትለኝ ከደረቴ በታች የሆነ ብቻ ለመግለፅም የሚከብድ እስከዛሬ ተሰምቶኝ የማያውቅ ስሜት ተሰማኝ።
ምን አልሽኝ ሊሊዬ አልኩ እንድትደግምልኝ ፈልጌ ዝም አለች። ደግሜ ለመስማት ፈልጌ በዝምታ ጠብኳት ። ደገመችው ።ደጋገመችው። አብረን ሆንን።
እኔ ከሊሊ ጋር በፍቅር ብን ማለቴ ጨርሶ ያልተዋጠለትና ያልተመቸው ሰው ቢኖር ጓደኛዬ ነው
እሄ ጓደኛዬ ኪሩቤል ይባላል ከወንድ ጓደኛቼ በጣም የምወደውና እንደወንድሜ የማየው ከልጅነት ጀምሮ ለብዙ አመታት ተለይቼው የማላውቅ ጓደኛዬ ነው
ታድያ እንደጓደኛ የማፈቅራት ልጅ እሺ ስላለችኝ እና አብራኝ ስለሆነች መደሰት ሲገባው ወረደብኝ ወረደብኝ አይገልፀውም በተግፃፅ እና በምፀት ደበደበኝ ብል ይቀለኛል
"አንተ ግን ምንድን ነው ወንድ አደለህ እንዴ ቆፍጠን በል እንጂ ምን ያዝረከርክሀል ኧረ በናትህ ለሴት ልጅ እሄን ያህል መሸነፍ መዋረድ ነው ለኔ ፍቅር ምናምን ትላለህ እንዴ ፍቅር አንተ ካልደረስክበት አይደርስብህም አንተ ፊት ካልሰጠከው ድርሽ አይልም ለሴት ልጅ የሚያለቅስ ጓደኛ ስላለኝ በጣም ነው ያፈርህምኩት ጓደኛቿ ሁሉ እኮ በፍቅሯ እግሯ ስር እንደጣለችህ ነው የሚያወሩት ኧረ እኔ ለሴት መቼም ቢሆን እንዳንተ ከምሆን ብሞት ይሻለኛል!"
አለኝ ይህን ፀባዩን እና አመለካከቱን በሌሎች ጓደኛቻችን ላይም ሲያንፀባርቀው ስላየሁ በውስጤ "ደርሶብህ እየው ያኔ ብናወራ ይሻላል ፍቅርን የሚያውቀው ያጣጣመው አልያም አልያም አናቱ ላይ ወጥቶ ያብከነከነው ብቻ ነው" እያልኩ ካጠገቡ ከመሄድ በቀር መልስ አልሰጠሁትም።
እንደው ሰው አማህ አትበሉኝና ጓደኛዬ ከምጣላበት የምወድለት ባህሪው በልጦብኝ ዘለቅን እንጂ የሚያናድድ ጢባር አለበት።
ደፋር ነኝ አደል ሰው አማህ አትበሉኝና ማለቴ ?
ቆይ እንዲህ በሀሜት አንስቼ እያፈረጥኩት
ሰው አማህ ካላላችሁኝ ምን ልትሉኝ ነው ?
ምን ላርግ ሲሉ ሰምቼ ነው።
ሲሉ ሰምቼ ያልኩትም ሲሉ ሰምተው ሲሉ ሰምቼ ነው።
አንዳንድ ሰዎች አንድን ሰው በሀሜት ስጋውን ቦጫጭቀው ባጥንቱ ሊያስቀሩት መንደርደር እንደጀመሩ መግቢያ አድርገው የሚጠቀሙት
"ሰው አማህ(አማሽ) አትበሉኝና!"
የሚለውን ፈንጅ አምካኝ ንግግር ነው ሰው ላይ የሀሜት ፈንጅ እየወረወሩ እነሱ ላይ የሚወረወረውን የትዝብት ፈንጅ የሚያመክኑት "ሰው አማህ /ሰው አማሽ አትበሉኝና" በሚለው ቅድመ ሀሜት ንግግራቸው ነው።
እናም ሁሌም እንደዚህ የሚሉ ሰዎች ሲያጋጥሟችሁ ሰው እያሙ ሰው አማህ ወይም ሰው አማሽ ካላላቹሀቸው ምን ምን እንደምትሏቸው ማሰብ ጀምሩ።
መልሱን ለናንተ ልተወውና ወደ ጉዳዬ ልመለስ
ሰው አማህ አትበሉኝና ጋደኛዬ ክሩቤል በተለይ በተለይ በፍቅር ዙርያ ያለው አመለካከትና በፍቅር መሀል ጣልቃ ለመግባት ያለው ድፍረት ያናድደኛል።
ፍቅርም አይዘኝም ፍቅር የምታስይዘኝም ሴት የለችም መፈክሩ ነው።
አንድ ቀን የኔዋ ሊሊ •••
"ጋደኛዬ ጓደኛህን ክሩቤልን ወዳዋለች ልጁ ግን እሚገባው ነገር አደለም እባክህን አናግረው እስቲ ሶልዬ!" ስትለኝ በጣም ደነገጥኩ ሄጄ ሳናግረው ምን እንደሚለኝ! እንዴት እንደሚላላጥብኝ! አንተን አረከኝ እንዴ ብሎ እንደሚዘልፈኝም አውቀዋለሁ ቢሆንም የማይቻል ወይም ጭራሽ የማይሞከር ካልሆነ በስተቀር ሊሊዬ ምንም አድርግልኝ ብትለኝ የትም ሂድልኝ ብትለኝ እምቢ ለማለት አቅም የለኝምና ኩሩቤልን አናግሬው ምላሹን እንደምነግራት ቃል ገብቼ ተለያየን።
ሄጄ ሳናግረው እንደፈራሁት ተላላጠብኝ ብዙ ነገር አውርቶ በመጨረሻ ጥየው ስሄድ ጮክ ብሎ "ቢጤሽን ፈልጊ በላት "አለኝ ።
ለሊዬ በቃ ልጁ አይሆናትም ይቅርባት ምላሹ ጥሩ አደለም አልኳት። ልጅታ ከሊሊ መልሱን ስትሰማ "ያፈቀረ ሲቆርጥም የመረረ!" እንዲሉ እርግፍ አድርጋ ተወችው ። ከተወሰነ ግዜ ቡሀላ ልጅቷ ከአንድ ልጅ ጋር ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ አዘውትራ መታየት ጀመረች።
ፍቅር ላይ ንጉስ ነኝ የሚለው ጓደኛዬ።
ፍቅሯ ተገልብጦ መቆሚያ መቀመጫ አሳጥቶታል ታግሎ ታግሎ ሲሸነፍ መሸነፉን ሊተነፍሰው ግድ ሆነበት ሲል የነበረውን ያውቀዋልና እንዴት እንደሚነግረኝ ግራ ገብቶት ሁለት ግዜ በጣም እፈልግሀለሁ እያለ ቀጥሮኝ ሳይነግረኝ ተለያየን ። የመጀመሪያው የትምህርት መንፈቀ አመት ተጠናቆ እረፍት ላይ ነበርን ለሶስተኛ ግዜ ቀጥሮኝ እቤታቸው ሄድኩኝ ክፍሉ ስገባ በሆዱ ተኝቶ ያስቴርን ሙዚቃ እያዳመጠ ነበር
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_ሦስት
፡
፡
#በጥላሁን
...እሄ መፈላሰፍ ነው እንዴ መፈላሰፍ እራሱ ምን ማለት ነው! ወጣም ወረደም ፍቅር የያዘው ሰው ሁለመናው ማፍቀሩን ስለሚናገር ምን ልናገር ብዬ ባልጨነቅስ!
የእረፍት ሰአት ተደወለና ተያይዘን ትንሽ እንደሄድን
"ለምን ነበር እረፍት ሰአት ልታናግሪኝ የፈለከው ሶልዬ?" ስትለኝ ደንግጬ አይን አይኗን ከማየት በስተቀር ሌላው እንኳን ቢቀር ወዬ ሊሊዬ የምትለውን ቃል ለመናገር ብሞክር ኔትወርኩ እንደጠፋ ስልክ ምላሴ ላይ እየተሽከረከረች አልወርድ አለችኝ።
የስልክ ኔትወርክስ ቦታ በመቀያየር ይፈለግ ይሆናል የኔን ኔትወርክ ምኑን ቀያይሬ ላምጣው!
ቸርነቱ ብዙ አንደበቱን ሰጥቶኝ
ፍቅሬን እንዳልገልጠው ፍቅርሽ ዲዳ አረገኝ እባክሽን ማሬ ያንደበቴን ትተሽ
ውስጤን ተረጅልኝ አይኔን ተመልክተሽ!!
ብለው ዘፍነው ይሆን እንዴ ዘፋኛቹ ?
አይመስለኝም •••
መጨነቄን በማስተዋል ስታይ የነበረችው ሊሊ
"ሶልዬ አትጨነቅ በቃ እንደምትወደኝ እንኳን እኔ ጓደኛቼም ያውቃሉ!
ታፈቅረኛለህ አደል?
እሱን ልትነግረኝ ፈልገህ ነው አደል እንዲህ ፈንጅ እንደረገጠ ሰው በቆምክበት ደርቀህ ምላስህም ሰውነትህም አልንቀሳቀስ ያለው ?ስትለኝ ጆሮዬን ማመን ተሳነኝ ።
ንግግሯ ምላሴ የታሰረበትን ገመድ በጣጠሰው መሰለኝ
" ሊሊዬ አዎ አፈቅርሻለሁ ግን እንደማፈቅርሽ በምን አውቅሽ ?
ጓደኛችሽ እንዴት አወቁ ? ስላት ሳቋን ለቀቅችው
"አንተስ እንዳፈቀርከኝ በምን አወክ? ብላ ግራ የገባው ጥያቄ በመጠየቅ ግራ አጋባችኝ ቢሆንም ምላሴ ተፈቷልና ለመመለስ አልቦዘንኩም•••
እኔማ እንዴት አላውቅም ሊሊዬ
ለሰከንድ ስላንቺና አንቺን ከማሰብ ተዘናግቼ አላውቅም ።
የሚዘፈነው የፍቅር ዘፈን በሙሉ ላንቺ የተዘፈነ ይመስለኛል ።
በፍቅሯ የሆንኩትን በሙሉ ለመዘርዘር ሲዳዳኝ •••
አንገቴ ላይ ድንገት ተጠምጥማ " እኔም እወድሀለሁኮ ሶልዬ!" ስትለኝ ከደረቴ በታች የሆነ ብቻ ለመግለፅም የሚከብድ እስከዛሬ ተሰምቶኝ የማያውቅ ስሜት ተሰማኝ።
ምን አልሽኝ ሊሊዬ አልኩ እንድትደግምልኝ ፈልጌ ዝም አለች። ደግሜ ለመስማት ፈልጌ በዝምታ ጠብኳት ። ደገመችው ።ደጋገመችው። አብረን ሆንን።
እኔ ከሊሊ ጋር በፍቅር ብን ማለቴ ጨርሶ ያልተዋጠለትና ያልተመቸው ሰው ቢኖር ጓደኛዬ ነው
እሄ ጓደኛዬ ኪሩቤል ይባላል ከወንድ ጓደኛቼ በጣም የምወደውና እንደወንድሜ የማየው ከልጅነት ጀምሮ ለብዙ አመታት ተለይቼው የማላውቅ ጓደኛዬ ነው
ታድያ እንደጓደኛ የማፈቅራት ልጅ እሺ ስላለችኝ እና አብራኝ ስለሆነች መደሰት ሲገባው ወረደብኝ ወረደብኝ አይገልፀውም በተግፃፅ እና በምፀት ደበደበኝ ብል ይቀለኛል
"አንተ ግን ምንድን ነው ወንድ አደለህ እንዴ ቆፍጠን በል እንጂ ምን ያዝረከርክሀል ኧረ በናትህ ለሴት ልጅ እሄን ያህል መሸነፍ መዋረድ ነው ለኔ ፍቅር ምናምን ትላለህ እንዴ ፍቅር አንተ ካልደረስክበት አይደርስብህም አንተ ፊት ካልሰጠከው ድርሽ አይልም ለሴት ልጅ የሚያለቅስ ጓደኛ ስላለኝ በጣም ነው ያፈርህምኩት ጓደኛቿ ሁሉ እኮ በፍቅሯ እግሯ ስር እንደጣለችህ ነው የሚያወሩት ኧረ እኔ ለሴት መቼም ቢሆን እንዳንተ ከምሆን ብሞት ይሻለኛል!"
አለኝ ይህን ፀባዩን እና አመለካከቱን በሌሎች ጓደኛቻችን ላይም ሲያንፀባርቀው ስላየሁ በውስጤ "ደርሶብህ እየው ያኔ ብናወራ ይሻላል ፍቅርን የሚያውቀው ያጣጣመው አልያም አልያም አናቱ ላይ ወጥቶ ያብከነከነው ብቻ ነው" እያልኩ ካጠገቡ ከመሄድ በቀር መልስ አልሰጠሁትም።
እንደው ሰው አማህ አትበሉኝና ጓደኛዬ ከምጣላበት የምወድለት ባህሪው በልጦብኝ ዘለቅን እንጂ የሚያናድድ ጢባር አለበት።
ደፋር ነኝ አደል ሰው አማህ አትበሉኝና ማለቴ ?
ቆይ እንዲህ በሀሜት አንስቼ እያፈረጥኩት
ሰው አማህ ካላላችሁኝ ምን ልትሉኝ ነው ?
ምን ላርግ ሲሉ ሰምቼ ነው።
ሲሉ ሰምቼ ያልኩትም ሲሉ ሰምተው ሲሉ ሰምቼ ነው።
አንዳንድ ሰዎች አንድን ሰው በሀሜት ስጋውን ቦጫጭቀው ባጥንቱ ሊያስቀሩት መንደርደር እንደጀመሩ መግቢያ አድርገው የሚጠቀሙት
"ሰው አማህ(አማሽ) አትበሉኝና!"
የሚለውን ፈንጅ አምካኝ ንግግር ነው ሰው ላይ የሀሜት ፈንጅ እየወረወሩ እነሱ ላይ የሚወረወረውን የትዝብት ፈንጅ የሚያመክኑት "ሰው አማህ /ሰው አማሽ አትበሉኝና" በሚለው ቅድመ ሀሜት ንግግራቸው ነው።
እናም ሁሌም እንደዚህ የሚሉ ሰዎች ሲያጋጥሟችሁ ሰው እያሙ ሰው አማህ ወይም ሰው አማሽ ካላላቹሀቸው ምን ምን እንደምትሏቸው ማሰብ ጀምሩ።
መልሱን ለናንተ ልተወውና ወደ ጉዳዬ ልመለስ
ሰው አማህ አትበሉኝና ጋደኛዬ ክሩቤል በተለይ በተለይ በፍቅር ዙርያ ያለው አመለካከትና በፍቅር መሀል ጣልቃ ለመግባት ያለው ድፍረት ያናድደኛል።
ፍቅርም አይዘኝም ፍቅር የምታስይዘኝም ሴት የለችም መፈክሩ ነው።
አንድ ቀን የኔዋ ሊሊ •••
"ጋደኛዬ ጓደኛህን ክሩቤልን ወዳዋለች ልጁ ግን እሚገባው ነገር አደለም እባክህን አናግረው እስቲ ሶልዬ!" ስትለኝ በጣም ደነገጥኩ ሄጄ ሳናግረው ምን እንደሚለኝ! እንዴት እንደሚላላጥብኝ! አንተን አረከኝ እንዴ ብሎ እንደሚዘልፈኝም አውቀዋለሁ ቢሆንም የማይቻል ወይም ጭራሽ የማይሞከር ካልሆነ በስተቀር ሊሊዬ ምንም አድርግልኝ ብትለኝ የትም ሂድልኝ ብትለኝ እምቢ ለማለት አቅም የለኝምና ኩሩቤልን አናግሬው ምላሹን እንደምነግራት ቃል ገብቼ ተለያየን።
ሄጄ ሳናግረው እንደፈራሁት ተላላጠብኝ ብዙ ነገር አውርቶ በመጨረሻ ጥየው ስሄድ ጮክ ብሎ "ቢጤሽን ፈልጊ በላት "አለኝ ።
ለሊዬ በቃ ልጁ አይሆናትም ይቅርባት ምላሹ ጥሩ አደለም አልኳት። ልጅታ ከሊሊ መልሱን ስትሰማ "ያፈቀረ ሲቆርጥም የመረረ!" እንዲሉ እርግፍ አድርጋ ተወችው ። ከተወሰነ ግዜ ቡሀላ ልጅቷ ከአንድ ልጅ ጋር ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ አዘውትራ መታየት ጀመረች።
ፍቅር ላይ ንጉስ ነኝ የሚለው ጓደኛዬ።
ፍቅሯ ተገልብጦ መቆሚያ መቀመጫ አሳጥቶታል ታግሎ ታግሎ ሲሸነፍ መሸነፉን ሊተነፍሰው ግድ ሆነበት ሲል የነበረውን ያውቀዋልና እንዴት እንደሚነግረኝ ግራ ገብቶት ሁለት ግዜ በጣም እፈልግሀለሁ እያለ ቀጥሮኝ ሳይነግረኝ ተለያየን ። የመጀመሪያው የትምህርት መንፈቀ አመት ተጠናቆ እረፍት ላይ ነበርን ለሶስተኛ ግዜ ቀጥሮኝ እቤታቸው ሄድኩኝ ክፍሉ ስገባ በሆዱ ተኝቶ ያስቴርን ሙዚቃ እያዳመጠ ነበር
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍2
#ፍቅር_ሲሸሽ
አንድም ፍጡር ላይኖር ከስ'ተት የጸዳ
ሆድሽ እጅግ ጠቦ ልብሽ እጅግ ከብዳ
ጠርጥረሽ ላትበይው
አኝከሽ ላትውጪው
በማላመጥ ብዛት ኮስሶ አኮሰስሽው
ጓዴ የሆነውን ዘርዝሬ ብነግርሽ
በጉዳቱ አዝነሽ
እጅግ ተቆጭተሽ
እምዬ ማሪያምን አብረሽው በቆረብሽ
የጨረቃ ወጋገን ፈክቶ በሰማይ ላይ
አንቀላፍታ ሳለች ምድሪቷ በአንድ ላይ
ፍቅርን ሲለግስሽ ስትሰጪው ፍቅርን
ድንገት አውሬ አይቶ በቁም ሲባንን
ነግረሽው ነበረ ውሻ መሆኑን
ነገር ግን . . . ነገር ግን . . .
ሽሽትን መረጠ ከነፈ ከቤቱ
አንድያ ነውና ለናትና አባቱ
አንቺ ግን . . . አንቺ ግን .
ደብቀሽ ሳትይዥ ይሄ ሚስጥሩን
ሃገር እንዲያውቅ አርገሽ ትንሹ ልቡን
“ ጥንቸሊቱ ” አስባልሽው መጠሪያ ስሙን
ውቢት . . .ውቢት .
ሊሳሳት ይችላል ማንም በቀን ውሎ
ቢሮጥ ምን ነበረ እኔን አስከትሎ
ብለሽ ተቀይመሽ ልብሽን አትዝጊው
ለበጎ ነው ብለሽ ሁሉንም አስቢው
ደ'ሞም ዱብ እዳ ነው አስጨናቂ ብርቱ
አውሬ ሲያጋጥመው ሳያስብ ከፊቱ
ሊሆን ደ'ሞ ይችላል የደፈጣ ስልቱ
ይህን አውሬ ፍጡር ሊያቆስለው በብርቱ
ብለሽ አስቢና አፍቅሪው ካ'ንጀትሽ
ታድያ ምኑ ላይ ነው ሩሩ ሴትነትሽ
ውቢት........
ምን አልባት . . .ምን አልባት . . .
የወሬ ነጋሪ ጭራሽ እንዳይጠፋ
ይሆናል መሮጡ ሳይነግር ከፊትሽ
ሲያወራው ለመኖር ዝነኛውን ፍቅርሽ፡
🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
አንድም ፍጡር ላይኖር ከስ'ተት የጸዳ
ሆድሽ እጅግ ጠቦ ልብሽ እጅግ ከብዳ
ጠርጥረሽ ላትበይው
አኝከሽ ላትውጪው
በማላመጥ ብዛት ኮስሶ አኮሰስሽው
ጓዴ የሆነውን ዘርዝሬ ብነግርሽ
በጉዳቱ አዝነሽ
እጅግ ተቆጭተሽ
እምዬ ማሪያምን አብረሽው በቆረብሽ
የጨረቃ ወጋገን ፈክቶ በሰማይ ላይ
አንቀላፍታ ሳለች ምድሪቷ በአንድ ላይ
ፍቅርን ሲለግስሽ ስትሰጪው ፍቅርን
ድንገት አውሬ አይቶ በቁም ሲባንን
ነግረሽው ነበረ ውሻ መሆኑን
ነገር ግን . . . ነገር ግን . . .
ሽሽትን መረጠ ከነፈ ከቤቱ
አንድያ ነውና ለናትና አባቱ
አንቺ ግን . . . አንቺ ግን .
ደብቀሽ ሳትይዥ ይሄ ሚስጥሩን
ሃገር እንዲያውቅ አርገሽ ትንሹ ልቡን
“ ጥንቸሊቱ ” አስባልሽው መጠሪያ ስሙን
ውቢት . . .ውቢት .
ሊሳሳት ይችላል ማንም በቀን ውሎ
ቢሮጥ ምን ነበረ እኔን አስከትሎ
ብለሽ ተቀይመሽ ልብሽን አትዝጊው
ለበጎ ነው ብለሽ ሁሉንም አስቢው
ደ'ሞም ዱብ እዳ ነው አስጨናቂ ብርቱ
አውሬ ሲያጋጥመው ሳያስብ ከፊቱ
ሊሆን ደ'ሞ ይችላል የደፈጣ ስልቱ
ይህን አውሬ ፍጡር ሊያቆስለው በብርቱ
ብለሽ አስቢና አፍቅሪው ካ'ንጀትሽ
ታድያ ምኑ ላይ ነው ሩሩ ሴትነትሽ
ውቢት........
ምን አልባት . . .ምን አልባት . . .
የወሬ ነጋሪ ጭራሽ እንዳይጠፋ
ይሆናል መሮጡ ሳይነግር ከፊትሽ
ሲያወራው ለመኖር ዝነኛውን ፍቅርሽ፡
🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#በኔ_የደረሰ
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በጥላሁን
...ፍቅር ላይ ንጉስ ነኝ የሚለው ጓደኛዬ።
ፍቅሯ ተገልብጦ መቆሚያ መቀመጫ አሳጥቶታል ታግሎ ታግሎ ሲሸነፍ መሸነፉን ሊተነፍሰው ግድ ሆነበት
ሲል የነበረውን ያውቀዋልና እንዴት እንደሚነግረኝ ግራ ገብቶት ሁለት ግዜ በጣም እፈልግሀለሁ እያለ ቀጥሮኝ ሳይነግረኝ ተለያየን ። የመጀመሪያው የትምህርት መንፈቀ አመት ተጠናቆ እረፍት ላይ ነበርን ለሶስተኛ ግዜ ቀጥሮኝ እቤታቸው ሄድኩኝ ክፍሉ ስገባ በሆዱ ተኝቶ ያስቴርን ሙዚቃ እያዳመጠ ነው •••
ስገባ ቀና አለ ። ሁኔታውን ሳየው እንኳን እሱ እኔም ሲለኝ የነበረውን ነገር ሁሉ ረሳሁት። አንጀቴን በላኝ ትናንት እንደዛ ስትል እንዳልነበር ዛሬ እያልኩ በፍቅር በወደቀው ዛፍ ላይ መጥረቢያ ማብዛቱን በጭራሽ አልፈለኩም።
እንኳን እንደዛ ልለው የሆነውን ከሁኔታው ተረድቼ ሳለሁ ምን ሆነሀል? ብዬ ላስጨንቀው አልፈለኩም።
እራሴ ወደጉዳዩ ቀጥታ ብገባ ሁለቴ ቀጥሮኝ ለመናገር የከበደውን ነገር እንደማቀልለት አሰብኩና •••
ትናንት ያጣጣልካትን ልጁ መልሰህ ስላፈቀርካት አይሰማህ ጋደኛዬ ይህ ፍቅር ጉልበቱን የሚያሳይበት አንዱ ባህሪው ነውና "ትናንት እሷ አፍቅራኝ ቢጤሽን ፈልጊ ያልኳትን ልጅ እንዴት እንዲህ በፍቅሯ ልንበረከክ ቻልኩ " እያልክ ከራስህ ጋር አትጣላ የደካማነት ስሜትም እንዳይሰማህ።
ማፍቀር መታደል እንጂ መሸነፍ ወይም መዋረድ አይደለም።ስለፍቅር ሊያውም ጥቂቱ የሚያውቀው ያፈቀረ ብቻ ነው ። ትናንት ስለማታውቀው ፍቅር ምንም ብትል አይገርምም።
አሁን ማፍቀር ዝቅ ማለት መሸነፍ መዝረክረክ ሳይሆን መታደል መሆኑን የተረዳህ ይመስለኛል? ይህን ተናግሬ ቀና መልሱን ስጠብቅ ጭንቄቱን በማወዛወዝ አዎንታውን ከገለፀልኝ ቡሀላ
"እና ያኔ ባልኩህ ነገር አልተቀየምከኝም ማለት ነው ጓደኛዬ? ከተቀየምከኝ ግን ይቅርታ!" አለኝ። አነጋገሩ እና አስተያየቱ በጣም ያሳዝን ነበር።
በጭራሽ አልተቀየምኩህም ጓደኛዬ በጣም የምወድህ ጓደኛዬ እኮ ነህ ከልጅነታችን ጀምሮ ብዙ ነገር አብረን ያሳለፍን ወንድማማቾች ነን ።
እኔ እናት እና አባቴ እህት እንጂ ወንድም አልሰጡኝም አንተ ነህ ከፈጣሪ የተሰጠከኝ ወንድሜም ጋደኛዬም ።
ጋደኛማቾች ነን ማለት ግን አንድ አይነት አስተሳሰብና አመለካከት አለን ማለት አይደለም የአመለካከት ወይም የሀሳብ ልዩነት ደግሞ አያቀያይምም። በርግጥ ጣልቃ ገብተህ ስትገስፀኝ እናደድብህ ይሆናል ቢሆንም በፍቅር ዙርያ የነበረን የአመለካከት ልዩነት ጓደኝነታችንን የማሻከር አቅም የለውም። ስለው ተነስቶ አቀፈኝ። ተቃቀፍን።
"እሺ ምንድን ነው የማናደርገው ሶልዬ እኔ የማብድ የማብድ እየመሰለኝ ነው ከልጁ ጋር ፍቅር የጀመሩ ይመስልሀል?" ሲለኝ•••
አይመስለኝም ለሁሉም ነገር መጀመሪያ የኔዋ ሊሊን ያለውን ነገር በግልፅ እንድትነግረኝ እጠይቃታለሁ ከዛ የሷን መልስ ከሰማሁ ቡሀላ ያለህበትን ሁኔታ መንገር ይኑርብኝ አይኑርብኝ ወስናለሁ።
ጋደኛዬ አንድ ነገር ግን ልነግርህ እፈልጋለሁ ልጅቷን በጣም እንዳፈቀርካት ተረድቻለሁ ከተሳካ እሰየው ባይሳካም ግን ሂወት እንደምትቀጥልና ያንተ ብትሆን ኖሮ እንደሚሳካ ያልተሳካው ፈጣሪ እሷን ላንተ ስላላላት መሆኑን አምነህ ለመቀበል ተዠጋጅ።
ካልሆነ ግን ከዚህኛው ጉዳት ያኛው ይከብዳል ። የሰው እንደሆነች እና እንደማታገኛት እያወክ ማፍቀርን የመሰለ ከባድ ህመም የለም።
ህመሙ ባይቀርልህም እንዳይጠናብህና እራስህን እንዳትጥል ቅድም እንዳልኩህ ሌላ ሂወት እንዳለና ያንተ የሆነችውን ለማግኘት ያንተ ያልሆነችውን ረስተህ እራስህን ሳትጥል መጠበቅ እንዳለብህ ማመን አለብህ ያለበለዝያ ያንተ ያልሆነችውን በማይሳካው የፍቅር አለም ውስጥ ስታሳድድ ያንተ የሆነውን ሁሉ ታጣለህ።
በቅድሚያ ከራስህ ትጣላለህ ። በመቀጠል በዙርያህ ያሉ ሰዎች ሁሉ ያስጠሉህና ከነሱም ትጣላለህ ።
ከዛ በየመንገዱ ከድንጋዩም ከግድግዳውም ከአየሩም ከንፋሱም መጣላት ብቻህን ማውራት ትጀምራለህ ። በመጨረሻ አብደህ ከፈጠርህ ጋም ትጣላና የሰይጣን ትሆናለህ።
ስለዚህ በማፍቀርህ ልክ ባይሳካ ለመርሳትም ተዘጋጅ።
እሺ ሶልዬ በጣም አመሰግናለሁ ግን ልጁን የምታፈቅረው ይመስልሀል?"
እኔ በምን አውቃለሁ ጓደኛዬ እኔም እንዳንተው አብረው አየኋቸው እንጂ ሌላ ምንም የማውቀው ነገር የለም ።
ስንቱ ተቃቅፎ እየሄደ በሆዱ በሚሰዳደብባት አለም አብረው ስለተቀመጡና አብረው ስለሄዱ ብቻ ይፋቀራሉ ብሎ መደምደም መጃጃል ነው
"እሺ አሁን ሊሊን መቼ ልታናግራት ወሰንክ ሶልዬ!"
"ነገ እንገናኛለን ነገ አናግራታለሁ "
"ኧረ ሶልዬ እስከነገ ለምን አሁን ብትደውልላት አይሻልም ቢያንስ ከልጁ ጋር ያላትን ጉኑኝነት ሰምቼ ቁርጤን እንዳውቅ!" ከስልክ ይልቅ ሳገኛት ባወራት እንደሚሻል ውስጤ ቢያምን በዚህ ስሜት ውስጥ ሆኖ አልደውልም ብለው ምን ያህል እንደሚከፋው በማሰብ ስልኬን አውጥቼ ደወልኩ።
ሊሊዬ ስልኬን አንስታው የራሳችንን ወሬ ከጨረስን ቡሀላ በጎደኛዋና ሰሞኑን አብራት በሚታየው ልጅ መካከል ያለው ግኑኝነት ምን እንደሆነ ስጠይቃት ገብቷት ነው መሰለኝ ረጅም ሳቅ ሳቀች።
ሳቋን ስትጨርስ ለምን እንደሳቀች ስጠይቃት
"ለምን እንደሳኩ እንድነግርህ አንተ በቅድሚያ ለምን እንደጠየከኝ ንገረኝ?" አለችኝ አሁንም ሙሉ በሙሉ ከሳቋ ሳታባራ።
ምን እንደምላት ጨነቀኝ ፍንጭ ካልሰጠኋት ልትነግረኝ እንደማትችል ስረዳ ከጓደኛዬ ክፍል እየወጣው
" ማንነቱን ሳልነግራት አንድ ጓደኛዬ በፍቅሯ እየትንገላታ መሆኑን ልነግራት ገና በቃ አንድ ጋደኛዬ አፍቅሯት•••
ስል በድጋሚ ሳቋ አቃረጠኝ ከሳቋ ከጠል አድርጋ
"ዋው ቀመራችን ሰርቷል ማለት ነዋ "
አለች የምን ቀመር ሊሊዬ?
ቀመሩ ወንዶች ስትባሉ የጣላችሁትን እንኳን ሲያነስባችሁ እንደምትወዱ አውቀን የቀመርነው ነዋ!"
"ልጁ ዘመዷ ነው አብራ መታየት የጀመረችው ሆን ብለን ተማክረን ነበር ጓደኛህ ወጥመዳችን ውስጥ ዘሎ መግባቱ እንደማይቀር ገምቼ ነበር ስትለኝ ደነገጥኩም ደስ አለኝም።
ስልኩን ዘግቼ የጓደኛዬን ክፍል በር በርግጄ ገባሁ
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#በጥላሁን
...ፍቅር ላይ ንጉስ ነኝ የሚለው ጓደኛዬ።
ፍቅሯ ተገልብጦ መቆሚያ መቀመጫ አሳጥቶታል ታግሎ ታግሎ ሲሸነፍ መሸነፉን ሊተነፍሰው ግድ ሆነበት
ሲል የነበረውን ያውቀዋልና እንዴት እንደሚነግረኝ ግራ ገብቶት ሁለት ግዜ በጣም እፈልግሀለሁ እያለ ቀጥሮኝ ሳይነግረኝ ተለያየን ። የመጀመሪያው የትምህርት መንፈቀ አመት ተጠናቆ እረፍት ላይ ነበርን ለሶስተኛ ግዜ ቀጥሮኝ እቤታቸው ሄድኩኝ ክፍሉ ስገባ በሆዱ ተኝቶ ያስቴርን ሙዚቃ እያዳመጠ ነው •••
ስገባ ቀና አለ ። ሁኔታውን ሳየው እንኳን እሱ እኔም ሲለኝ የነበረውን ነገር ሁሉ ረሳሁት። አንጀቴን በላኝ ትናንት እንደዛ ስትል እንዳልነበር ዛሬ እያልኩ በፍቅር በወደቀው ዛፍ ላይ መጥረቢያ ማብዛቱን በጭራሽ አልፈለኩም።
እንኳን እንደዛ ልለው የሆነውን ከሁኔታው ተረድቼ ሳለሁ ምን ሆነሀል? ብዬ ላስጨንቀው አልፈለኩም።
እራሴ ወደጉዳዩ ቀጥታ ብገባ ሁለቴ ቀጥሮኝ ለመናገር የከበደውን ነገር እንደማቀልለት አሰብኩና •••
ትናንት ያጣጣልካትን ልጁ መልሰህ ስላፈቀርካት አይሰማህ ጋደኛዬ ይህ ፍቅር ጉልበቱን የሚያሳይበት አንዱ ባህሪው ነውና "ትናንት እሷ አፍቅራኝ ቢጤሽን ፈልጊ ያልኳትን ልጅ እንዴት እንዲህ በፍቅሯ ልንበረከክ ቻልኩ " እያልክ ከራስህ ጋር አትጣላ የደካማነት ስሜትም እንዳይሰማህ።
ማፍቀር መታደል እንጂ መሸነፍ ወይም መዋረድ አይደለም።ስለፍቅር ሊያውም ጥቂቱ የሚያውቀው ያፈቀረ ብቻ ነው ። ትናንት ስለማታውቀው ፍቅር ምንም ብትል አይገርምም።
አሁን ማፍቀር ዝቅ ማለት መሸነፍ መዝረክረክ ሳይሆን መታደል መሆኑን የተረዳህ ይመስለኛል? ይህን ተናግሬ ቀና መልሱን ስጠብቅ ጭንቄቱን በማወዛወዝ አዎንታውን ከገለፀልኝ ቡሀላ
"እና ያኔ ባልኩህ ነገር አልተቀየምከኝም ማለት ነው ጓደኛዬ? ከተቀየምከኝ ግን ይቅርታ!" አለኝ። አነጋገሩ እና አስተያየቱ በጣም ያሳዝን ነበር።
በጭራሽ አልተቀየምኩህም ጓደኛዬ በጣም የምወድህ ጓደኛዬ እኮ ነህ ከልጅነታችን ጀምሮ ብዙ ነገር አብረን ያሳለፍን ወንድማማቾች ነን ።
እኔ እናት እና አባቴ እህት እንጂ ወንድም አልሰጡኝም አንተ ነህ ከፈጣሪ የተሰጠከኝ ወንድሜም ጋደኛዬም ።
ጋደኛማቾች ነን ማለት ግን አንድ አይነት አስተሳሰብና አመለካከት አለን ማለት አይደለም የአመለካከት ወይም የሀሳብ ልዩነት ደግሞ አያቀያይምም። በርግጥ ጣልቃ ገብተህ ስትገስፀኝ እናደድብህ ይሆናል ቢሆንም በፍቅር ዙርያ የነበረን የአመለካከት ልዩነት ጓደኝነታችንን የማሻከር አቅም የለውም። ስለው ተነስቶ አቀፈኝ። ተቃቀፍን።
"እሺ ምንድን ነው የማናደርገው ሶልዬ እኔ የማብድ የማብድ እየመሰለኝ ነው ከልጁ ጋር ፍቅር የጀመሩ ይመስልሀል?" ሲለኝ•••
አይመስለኝም ለሁሉም ነገር መጀመሪያ የኔዋ ሊሊን ያለውን ነገር በግልፅ እንድትነግረኝ እጠይቃታለሁ ከዛ የሷን መልስ ከሰማሁ ቡሀላ ያለህበትን ሁኔታ መንገር ይኑርብኝ አይኑርብኝ ወስናለሁ።
ጋደኛዬ አንድ ነገር ግን ልነግርህ እፈልጋለሁ ልጅቷን በጣም እንዳፈቀርካት ተረድቻለሁ ከተሳካ እሰየው ባይሳካም ግን ሂወት እንደምትቀጥልና ያንተ ብትሆን ኖሮ እንደሚሳካ ያልተሳካው ፈጣሪ እሷን ላንተ ስላላላት መሆኑን አምነህ ለመቀበል ተዠጋጅ።
ካልሆነ ግን ከዚህኛው ጉዳት ያኛው ይከብዳል ። የሰው እንደሆነች እና እንደማታገኛት እያወክ ማፍቀርን የመሰለ ከባድ ህመም የለም።
ህመሙ ባይቀርልህም እንዳይጠናብህና እራስህን እንዳትጥል ቅድም እንዳልኩህ ሌላ ሂወት እንዳለና ያንተ የሆነችውን ለማግኘት ያንተ ያልሆነችውን ረስተህ እራስህን ሳትጥል መጠበቅ እንዳለብህ ማመን አለብህ ያለበለዝያ ያንተ ያልሆነችውን በማይሳካው የፍቅር አለም ውስጥ ስታሳድድ ያንተ የሆነውን ሁሉ ታጣለህ።
በቅድሚያ ከራስህ ትጣላለህ ። በመቀጠል በዙርያህ ያሉ ሰዎች ሁሉ ያስጠሉህና ከነሱም ትጣላለህ ።
ከዛ በየመንገዱ ከድንጋዩም ከግድግዳውም ከአየሩም ከንፋሱም መጣላት ብቻህን ማውራት ትጀምራለህ ። በመጨረሻ አብደህ ከፈጠርህ ጋም ትጣላና የሰይጣን ትሆናለህ።
ስለዚህ በማፍቀርህ ልክ ባይሳካ ለመርሳትም ተዘጋጅ።
እሺ ሶልዬ በጣም አመሰግናለሁ ግን ልጁን የምታፈቅረው ይመስልሀል?"
እኔ በምን አውቃለሁ ጓደኛዬ እኔም እንዳንተው አብረው አየኋቸው እንጂ ሌላ ምንም የማውቀው ነገር የለም ።
ስንቱ ተቃቅፎ እየሄደ በሆዱ በሚሰዳደብባት አለም አብረው ስለተቀመጡና አብረው ስለሄዱ ብቻ ይፋቀራሉ ብሎ መደምደም መጃጃል ነው
"እሺ አሁን ሊሊን መቼ ልታናግራት ወሰንክ ሶልዬ!"
"ነገ እንገናኛለን ነገ አናግራታለሁ "
"ኧረ ሶልዬ እስከነገ ለምን አሁን ብትደውልላት አይሻልም ቢያንስ ከልጁ ጋር ያላትን ጉኑኝነት ሰምቼ ቁርጤን እንዳውቅ!" ከስልክ ይልቅ ሳገኛት ባወራት እንደሚሻል ውስጤ ቢያምን በዚህ ስሜት ውስጥ ሆኖ አልደውልም ብለው ምን ያህል እንደሚከፋው በማሰብ ስልኬን አውጥቼ ደወልኩ።
ሊሊዬ ስልኬን አንስታው የራሳችንን ወሬ ከጨረስን ቡሀላ በጎደኛዋና ሰሞኑን አብራት በሚታየው ልጅ መካከል ያለው ግኑኝነት ምን እንደሆነ ስጠይቃት ገብቷት ነው መሰለኝ ረጅም ሳቅ ሳቀች።
ሳቋን ስትጨርስ ለምን እንደሳቀች ስጠይቃት
"ለምን እንደሳኩ እንድነግርህ አንተ በቅድሚያ ለምን እንደጠየከኝ ንገረኝ?" አለችኝ አሁንም ሙሉ በሙሉ ከሳቋ ሳታባራ።
ምን እንደምላት ጨነቀኝ ፍንጭ ካልሰጠኋት ልትነግረኝ እንደማትችል ስረዳ ከጓደኛዬ ክፍል እየወጣው
" ማንነቱን ሳልነግራት አንድ ጓደኛዬ በፍቅሯ እየትንገላታ መሆኑን ልነግራት ገና በቃ አንድ ጋደኛዬ አፍቅሯት•••
ስል በድጋሚ ሳቋ አቃረጠኝ ከሳቋ ከጠል አድርጋ
"ዋው ቀመራችን ሰርቷል ማለት ነዋ "
አለች የምን ቀመር ሊሊዬ?
ቀመሩ ወንዶች ስትባሉ የጣላችሁትን እንኳን ሲያነስባችሁ እንደምትወዱ አውቀን የቀመርነው ነዋ!"
"ልጁ ዘመዷ ነው አብራ መታየት የጀመረችው ሆን ብለን ተማክረን ነበር ጓደኛህ ወጥመዳችን ውስጥ ዘሎ መግባቱ እንደማይቀር ገምቼ ነበር ስትለኝ ደነገጥኩም ደስ አለኝም።
ስልኩን ዘግቼ የጓደኛዬን ክፍል በር በርግጄ ገባሁ
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
❤1👍1
#እንዳለ_ይቀመጥ
ተፋቅረን አየሁ ብልሽ
መጣላት አረግሽው
መሳሳቃችንንም
አላቅሰሽ አረፍሽው
በጥሩ መፍታት ሲቻል
ሁሉን ተቀራርቦ
እኔ አራምባ ስልሽ
አንቺ ካልሽኝ ቆቦ
ህልሜን ከፍቅሬ ጋር
ከምትፈቺው አብረሽ
ከሰለሞን ጥበብ
ካዋቂ ዘንድ ወስደሽ
ሳይቀንስ ሳይጨምር
አስቀምጪው አስቋጥረሽ፡፡
ተፋቅረን አየሁ ብልሽ
መጣላት አረግሽው
መሳሳቃችንንም
አላቅሰሽ አረፍሽው
በጥሩ መፍታት ሲቻል
ሁሉን ተቀራርቦ
እኔ አራምባ ስልሽ
አንቺ ካልሽኝ ቆቦ
ህልሜን ከፍቅሬ ጋር
ከምትፈቺው አብረሽ
ከሰለሞን ጥበብ
ካዋቂ ዘንድ ወስደሽ
ሳይቀንስ ሳይጨምር
አስቀምጪው አስቋጥረሽ፡፡
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#በኔ_የደረሰ
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በጥላሁን
"ዋው ቀመራችን ሰርቷል ማለት ነዋ "
አለች የምን ቀመር ሊሊዬ?ቀመሩ ወንዶች ስትባሉ የጣላችሁትን እንኳን ሲያነስባችሁ እንደምትወዱ አውቀን የቀመርነው ነዋ!"
"ልጁ ዘመዷ ነው አብራ መታየት የጀመረችው ሆን ብለን ተማክረን ነበር ጓደኛህ ወጥመዳችን ውስጥ ዘሎ መግባቱ እንደማይቀር ገምቼ ነበር ስትለኝ ደነገጥኩም ደስ አለኝም።
ስልኩን ዘግቼ የጓደኛዬን ክፍል በር በርግጄ ገባሁ •••
ገብቼ ሊሊዬ ያለችን ስነግረው ያ እንደሀምሌ ወር የፍቅር ደመና የጠቆረው ስሜቱ ፈጎ እንደመስከረም ፀሀይ አብራ።
ወድያው በድጋሚ ሊሊዬ ጋር ደውዬ በነገው ቀጦሮአችን ላይ ኬርያንም ይዛት እንድትመጣ ነገርኳት።
በንጋታው ተገናኝተን ሁሉም ነገር በጣም ደስ በሚል ሁኔታ ተጠናቀቀ። ሁለቱም አብረው ሆኑ።
አራታችንም የይንቨርስቲ መግቢያ ፈተና እስክንፈተን እና እስክንበታተን ድረስ ሁለት አመታትን አስደሳች የፍቅር ግዜ በዛው ትምህርት ቤታችን ውስጥ አሳለፍን ።
የማትሪክ ውጤት እኔ ሊሊዬ እና ስናመጣ ኬርያ አልተሳካላትም
እኔ አዳማ ዩንቨርስቲ ስመደብ ሊሊዬ ድሬ ዳዋ ዩንቨርስቲ ደረሳት ቢሆንም አባቷ ከአጠገቡ ርቃ እንድትሄድ ስላልፈለገ ውጪ ሀገር ልኮ እንደሚያስተምራት ቃል ገብቶ አስቀራት። ጋደኛዬ ጅማ ዩንቨርስቲ ደረሰው ። በተመደበልን ግዜ እኔ ወደ አዳማ እሱ ወደ ጅማ ተጓዝን ።
ፍቅራችን ካለበት ሞቅታ ሳይቀዘቅዝ ጭራሽ መነፋፈቅ እያጋለው ቀጠለ።
ዩንቨርስቲ ገብተን ስድስት ወር ሳንማር አለምን ባስጨነቀው ባዲሱ ወረርሽኝ በኮሮና ምክንያት ሀገሪቱ ውስጥ ያሉት ዩንቨርስቲዎች ተዘግተው ወደየቤታችን እንድንሄድ ተደረገ።
ሊሊዬ ያደገችበት ቤተሰብ እና እኔ ያደኩበት ቤተሰብ ለየቅል ነው ።
በዚህ ምክንያት ፍቅር ሀ ብለን ከጀመርንበት ቀን ጀምሮ የማይዋጥላት ነገር አባቴን አብዝቼ መፍራቴ ነው። ባትረዳኝ አልፈርድባትም። አሁን ከዩንቨርስቲ እቤት ተቀመጡ ተብለን ከመጣን በሳምንቱ ደውላ
"እኔ ዝም ብሎ በስልክ ብቻ አንተን እያገኙ መኖር ከበደኝ ሶልዬ ሳምንት ሆነን እኮ እዚሁ አንድ ከተማ ውስጥ ሆነን ሳምንት ሙሉ አለመገናኘት ምን ማለት እንደሆነ አስበከዋል ቆይ አልናፍቅህም ግን ?
" ኧረ ሊሊዬ በርግጠኝነት የኔን ያህል አትናፍቂም ግን ምን ላድርግ ያባዬን ባህሪ ታውቂው የለ እንኳን ወረርሽኝ ገባ ከቤት አትውጡ ብሎ መንግስት አውጆለት ድሮም ቢሆን መች ያለ ምክንያት መዞር ይፈቀድልኛል?
"ሶልዬ እኔ ጋር መምጣት በቂ ምክንያት ነው ከዚህ በላይ ምን ምክንያት አለ ደሞ ልዙር ፍቀድልኝ በላቸው መች አልኩህ እንገናኝ ልትለኝ ካልሆነ እንዳትደውልልኝ አኩርፌሀለሁ በቃ በቃ የምሬን ነው! "
ሊሊዬ እንዲህ ነች ተናግራ ነው እምታኮርፈው።
እውነቷን ነው ናዝሬት ትምህርት ላይ በነበርኩበት ባለፉት ወራት ቢያንስ በሳምንት አንድ ግዜ እንገናኝ ነበር ።
የምሯን እንደሆነ እንደተናደደችብኝ አውቃለሁ ግን ምን ላድርግ ።
አባዬ እንደሆነ ድሮም ድሮ ነው እሄ ወረርሽኝ ሀገራችን ገባ ከተባለበት ግዜ ጀምሮ መንግስት ብቻ ሳይሆን አባዬም ቤቱን ወደ ቤተሰብ ለይቶ ማቆያ የቀየረው እስኪመስለን ድረስ እኔም እህቴም እናቴም እንኳን ወደ ውጪ ልንወጣ የውጪ በር ሲንኳኳ እንኳን እንድንከፍት አይፈቀድልንም።
አባዬ ከቁጥጥሩም ባልተናነሰ ለኛ ለልጆቹ ያለው ፍቅር እስከጥግ ነበርና ቁጥጥሩ በፍቅሩ ስለሚጣፋ በጭራሽ ላስቀይመው አልፈልግም በኔ አዝኖ ከማየው ሞቴን እምመርጥ ይመስለኛል ።
መቆጣት ሲኖርብት የሚቆጣ ፍቅር መመገብ ሲኖርበት ፍቅሩን ሳይሰስት ለልጆቹ የሚመግብ አባት ነው አባቴ በቁጣው በቁጥጥሩ ውስጤ ሲነድ በፍቅሩ ዝናብ እያጠበ ያበርደኛል።
የተመጣጠነ ምግብ ብቻ ሳይሆን የተመጣጠነ ባህሪ መግቦ ነው ያሳደገን።
ምንም ብለው ስለማይፈቅድልኝ ሊሊዬን ሳልፈልግ ዝም አልኳት ። ስልክም አልደወልኩም ሶስት ቀን ሳንደዋወል ስንቆይ ጨነቀኝ ቢሆንም ቻልኩት።
አምስት ቀን ሞላን።
በአምስተኛው ቀን ልክ ከቀኑ በስምንት ሰአት አልጋዬ ላይ ጋደም ብዬ በፊት ተገናኝተን ደብረዘይት ሀዋሳ እየሄድን በምንዝናናበት ወቅት የተነሳናቸውን ፎቶዎች በተመስጦ እየተመለከትኩ ከፎቶው ጋር ሳወራ ድንገት የጮኸው ስልኬ አስደንግጦ ከሄድኩበት የትዝታ አለም ጎትቶ አወጣኝ።
ሊሊዬ ነበረች የደወለችው ።
የኔ ፍቅር በኔ እንደማይስችልሽ እኮ አውቃለሁ ግን ደናነሽልኝ ስላት •••
" አንተ ግን አስችሎህ ዘጋከኝ አደል ?" አልች ድምጿ ውስጥ መከፋታ ያስተጋባል ።
ምን ላድርግ ሊሊዬ አባዬን ከማስቀይመው ብዬ እኮ ነው
ልክ ነህ አባትህን ከምታስቀይመው እኔን ብታስቀይመኝ ይሻላል ተረዳሁህ
ይቅርታም አረኩልህ ግን ከነገወድያ ልደቴ ነው ልደቴ እንዴት እንደሚከበርልኝ ታውቃለህ የፈለገውን ያህል ቢከበርልኝ አንተ ከሌለህ ግን ምኑም ደስ እንደማይለኝም ታውቃለህ ታድያ ልደቴንም ልትቀር ነው ?
ስትለኝ መሀል አናቴን በዘነዘና የተረከኩት እስኪመስለኝ በቆሙኩበት ስንጥቅ አልኩ። አዋ ልደቷ እንዴት እንደሚከበርላት በደንብ አውቃለሁ ። ለሷ ልደት የሚወጣው ወጪ ሶስት መለስተኛ የድሀ ሰርግ ይሸፍናል ብል አልተጋነነም ።። ቀን የተጀመረ ሲበላ ሲጠጣ ተመሽቶ ማታ ለዚሁ ልደት በተዘገጀው ሌላ ክፍል ውስጥ በድጄው ልብ የሚሰውሩ ሙዚቃዎች ለጉድ ሲቀውጥ ሲጨፈር ይታደራል ።
ትልቁን የህይወት ፈተና እየተፈተንኩ መሰለኝ። ሊሊዬን ልደትሽ ላይ አልገኝም ብላት በተገኘሁበት ላትደርስ ምላ እንደምትለየኝ አልጠራጠርም።
አባዬ ደግሞ በዚህ ግዜ እንኳን ውሎ እና አዳር ልሂድ ልለው ከቤታችን ፊት ለፊት ካለው ሱቅ የሞባይል ካርድ ገዝቼ ልምጣ ስለው ቁጭ በል እኔ አመጣላሀለሁ ብሎ ያረጀች ቮልስ ዋገን መኪናውን እያስጮኸ ሄዶ ያመጣልኛል እንጂ ገዝተህ ና ብሎ እንደማይፈቅድልኝ አውቃለሁ።
ኮሮና ብሎ የተረገመ በሽታ መጥቶ ገና አንድ ወር ሳይሆነው ሂወቴን ፈተና አደረጋት ።
ሊሊዬ በዚህ ሰአት ልክ አምና እንዳከበርሽው ያ ሁሉ ሰው ተጠርቶ ሊከበር ነው ማለቴ ለሊት ጭፈራ ምናምን እኮ በዚህ ግዜ ስል ገና ካፌ ቀብል አድርጋ•••
"ቲቭው ላይ ሰልችቶን ያጠፋነውን በአስቸኳይ በአስገዳጅ የሚሉት አዋጅ የተከለከሉትን ምናምን አንተም ልደግምልኝ ነው ሶል
ደሞ ብዙ ሰው የሚመጣ አይመስለኝም የማታው የጭፈራ ብሮግራም ግን የማይቀር ነው!"
ቲቪውን ከምታጠፉት በሽታውን ባጠፋችሁት ይሻል ነበር እያልኩ ስልጎሞጎም
"ምን አልከኝ ?"አለችኝ ።
አይ ምንም !
"እሺ ትመጣለህ አትመጣም?
መምጣት መጣለሁ ግን ቀን አልመጣም ተረጅኝ ሊሊዬ እኛ ቤት እራት በግዜ ሁለት ሰአት አከባቢ ሁላችንም አብረን ስለምንበላ የግድ እራት ላይ መገኘት አለብኝ ከዛ ክፍሌ ውስጥ ገብቼ የተኛሁ በማስመሰል የበሩን ቁልፍ ሰርቄም ቢሆን ውጥቼ ለመምጣት እሞክራለሁ። አልኳት ደርሶ ሊሂድ አልሂድ ባላውቅም እንደዛ ከማለት ውጪ አማራጭ አልነበተኝም።
"እሺ ይሁን የኔ ፍቅር ፍቅር እኮ ነህ ዋናው መምጣትህ ነው ግን እሞክራለሁ ሳይሆን እመጣለሁ ነው የሚባለው ኪኪኪኪ ደሞ ልትወጣ ቢያንስ ሀያ ደቂቃ ሲቀርህ ደውልልኝ ዳጊን እልከውና ይዞህ ይመጣል እሺ?"
እሺ አልኳት። ዳጊ ሹፌራቸው ነው። ተስነባበትን።ሁለቱን ቀናት እማዬ•••
"ልጄ ትናንት እና ዛሬ በአካል እዚህ ከኛው ጋር ቁጭ ብለህ በሀሳብ ብን ብለህ ስትጠፋ እያስተዋልኩ ነው ምንድን ነው እሱ ምን ሆነሀል?"
ብላ እስክትጠይቀኝ ድረስ በጭንቀት አሳለፍኳቸው የሊሊ ቤተሰቦች ስራቸው በሙሉ ከውጪ ሀገር ጉዞ ጋር የተያያዘ ነው ወንድማ ዱባይና ሳውዲ እየሄደ እቃ ያመጣል አጎቷ አባቷ ከንግድ ስራቸው ጋር በተያያዘ ውጪ
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በጥላሁን
"ዋው ቀመራችን ሰርቷል ማለት ነዋ "
አለች የምን ቀመር ሊሊዬ?ቀመሩ ወንዶች ስትባሉ የጣላችሁትን እንኳን ሲያነስባችሁ እንደምትወዱ አውቀን የቀመርነው ነዋ!"
"ልጁ ዘመዷ ነው አብራ መታየት የጀመረችው ሆን ብለን ተማክረን ነበር ጓደኛህ ወጥመዳችን ውስጥ ዘሎ መግባቱ እንደማይቀር ገምቼ ነበር ስትለኝ ደነገጥኩም ደስ አለኝም።
ስልኩን ዘግቼ የጓደኛዬን ክፍል በር በርግጄ ገባሁ •••
ገብቼ ሊሊዬ ያለችን ስነግረው ያ እንደሀምሌ ወር የፍቅር ደመና የጠቆረው ስሜቱ ፈጎ እንደመስከረም ፀሀይ አብራ።
ወድያው በድጋሚ ሊሊዬ ጋር ደውዬ በነገው ቀጦሮአችን ላይ ኬርያንም ይዛት እንድትመጣ ነገርኳት።
በንጋታው ተገናኝተን ሁሉም ነገር በጣም ደስ በሚል ሁኔታ ተጠናቀቀ። ሁለቱም አብረው ሆኑ።
አራታችንም የይንቨርስቲ መግቢያ ፈተና እስክንፈተን እና እስክንበታተን ድረስ ሁለት አመታትን አስደሳች የፍቅር ግዜ በዛው ትምህርት ቤታችን ውስጥ አሳለፍን ።
የማትሪክ ውጤት እኔ ሊሊዬ እና ስናመጣ ኬርያ አልተሳካላትም
እኔ አዳማ ዩንቨርስቲ ስመደብ ሊሊዬ ድሬ ዳዋ ዩንቨርስቲ ደረሳት ቢሆንም አባቷ ከአጠገቡ ርቃ እንድትሄድ ስላልፈለገ ውጪ ሀገር ልኮ እንደሚያስተምራት ቃል ገብቶ አስቀራት። ጋደኛዬ ጅማ ዩንቨርስቲ ደረሰው ። በተመደበልን ግዜ እኔ ወደ አዳማ እሱ ወደ ጅማ ተጓዝን ።
ፍቅራችን ካለበት ሞቅታ ሳይቀዘቅዝ ጭራሽ መነፋፈቅ እያጋለው ቀጠለ።
ዩንቨርስቲ ገብተን ስድስት ወር ሳንማር አለምን ባስጨነቀው ባዲሱ ወረርሽኝ በኮሮና ምክንያት ሀገሪቱ ውስጥ ያሉት ዩንቨርስቲዎች ተዘግተው ወደየቤታችን እንድንሄድ ተደረገ።
ሊሊዬ ያደገችበት ቤተሰብ እና እኔ ያደኩበት ቤተሰብ ለየቅል ነው ።
በዚህ ምክንያት ፍቅር ሀ ብለን ከጀመርንበት ቀን ጀምሮ የማይዋጥላት ነገር አባቴን አብዝቼ መፍራቴ ነው። ባትረዳኝ አልፈርድባትም። አሁን ከዩንቨርስቲ እቤት ተቀመጡ ተብለን ከመጣን በሳምንቱ ደውላ
"እኔ ዝም ብሎ በስልክ ብቻ አንተን እያገኙ መኖር ከበደኝ ሶልዬ ሳምንት ሆነን እኮ እዚሁ አንድ ከተማ ውስጥ ሆነን ሳምንት ሙሉ አለመገናኘት ምን ማለት እንደሆነ አስበከዋል ቆይ አልናፍቅህም ግን ?
" ኧረ ሊሊዬ በርግጠኝነት የኔን ያህል አትናፍቂም ግን ምን ላድርግ ያባዬን ባህሪ ታውቂው የለ እንኳን ወረርሽኝ ገባ ከቤት አትውጡ ብሎ መንግስት አውጆለት ድሮም ቢሆን መች ያለ ምክንያት መዞር ይፈቀድልኛል?
"ሶልዬ እኔ ጋር መምጣት በቂ ምክንያት ነው ከዚህ በላይ ምን ምክንያት አለ ደሞ ልዙር ፍቀድልኝ በላቸው መች አልኩህ እንገናኝ ልትለኝ ካልሆነ እንዳትደውልልኝ አኩርፌሀለሁ በቃ በቃ የምሬን ነው! "
ሊሊዬ እንዲህ ነች ተናግራ ነው እምታኮርፈው።
እውነቷን ነው ናዝሬት ትምህርት ላይ በነበርኩበት ባለፉት ወራት ቢያንስ በሳምንት አንድ ግዜ እንገናኝ ነበር ።
የምሯን እንደሆነ እንደተናደደችብኝ አውቃለሁ ግን ምን ላድርግ ።
አባዬ እንደሆነ ድሮም ድሮ ነው እሄ ወረርሽኝ ሀገራችን ገባ ከተባለበት ግዜ ጀምሮ መንግስት ብቻ ሳይሆን አባዬም ቤቱን ወደ ቤተሰብ ለይቶ ማቆያ የቀየረው እስኪመስለን ድረስ እኔም እህቴም እናቴም እንኳን ወደ ውጪ ልንወጣ የውጪ በር ሲንኳኳ እንኳን እንድንከፍት አይፈቀድልንም።
አባዬ ከቁጥጥሩም ባልተናነሰ ለኛ ለልጆቹ ያለው ፍቅር እስከጥግ ነበርና ቁጥጥሩ በፍቅሩ ስለሚጣፋ በጭራሽ ላስቀይመው አልፈልግም በኔ አዝኖ ከማየው ሞቴን እምመርጥ ይመስለኛል ።
መቆጣት ሲኖርብት የሚቆጣ ፍቅር መመገብ ሲኖርበት ፍቅሩን ሳይሰስት ለልጆቹ የሚመግብ አባት ነው አባቴ በቁጣው በቁጥጥሩ ውስጤ ሲነድ በፍቅሩ ዝናብ እያጠበ ያበርደኛል።
የተመጣጠነ ምግብ ብቻ ሳይሆን የተመጣጠነ ባህሪ መግቦ ነው ያሳደገን።
ምንም ብለው ስለማይፈቅድልኝ ሊሊዬን ሳልፈልግ ዝም አልኳት ። ስልክም አልደወልኩም ሶስት ቀን ሳንደዋወል ስንቆይ ጨነቀኝ ቢሆንም ቻልኩት።
አምስት ቀን ሞላን።
በአምስተኛው ቀን ልክ ከቀኑ በስምንት ሰአት አልጋዬ ላይ ጋደም ብዬ በፊት ተገናኝተን ደብረዘይት ሀዋሳ እየሄድን በምንዝናናበት ወቅት የተነሳናቸውን ፎቶዎች በተመስጦ እየተመለከትኩ ከፎቶው ጋር ሳወራ ድንገት የጮኸው ስልኬ አስደንግጦ ከሄድኩበት የትዝታ አለም ጎትቶ አወጣኝ።
ሊሊዬ ነበረች የደወለችው ።
የኔ ፍቅር በኔ እንደማይስችልሽ እኮ አውቃለሁ ግን ደናነሽልኝ ስላት •••
" አንተ ግን አስችሎህ ዘጋከኝ አደል ?" አልች ድምጿ ውስጥ መከፋታ ያስተጋባል ።
ምን ላድርግ ሊሊዬ አባዬን ከማስቀይመው ብዬ እኮ ነው
ልክ ነህ አባትህን ከምታስቀይመው እኔን ብታስቀይመኝ ይሻላል ተረዳሁህ
ይቅርታም አረኩልህ ግን ከነገወድያ ልደቴ ነው ልደቴ እንዴት እንደሚከበርልኝ ታውቃለህ የፈለገውን ያህል ቢከበርልኝ አንተ ከሌለህ ግን ምኑም ደስ እንደማይለኝም ታውቃለህ ታድያ ልደቴንም ልትቀር ነው ?
ስትለኝ መሀል አናቴን በዘነዘና የተረከኩት እስኪመስለኝ በቆሙኩበት ስንጥቅ አልኩ። አዋ ልደቷ እንዴት እንደሚከበርላት በደንብ አውቃለሁ ። ለሷ ልደት የሚወጣው ወጪ ሶስት መለስተኛ የድሀ ሰርግ ይሸፍናል ብል አልተጋነነም ።። ቀን የተጀመረ ሲበላ ሲጠጣ ተመሽቶ ማታ ለዚሁ ልደት በተዘገጀው ሌላ ክፍል ውስጥ በድጄው ልብ የሚሰውሩ ሙዚቃዎች ለጉድ ሲቀውጥ ሲጨፈር ይታደራል ።
ትልቁን የህይወት ፈተና እየተፈተንኩ መሰለኝ። ሊሊዬን ልደትሽ ላይ አልገኝም ብላት በተገኘሁበት ላትደርስ ምላ እንደምትለየኝ አልጠራጠርም።
አባዬ ደግሞ በዚህ ግዜ እንኳን ውሎ እና አዳር ልሂድ ልለው ከቤታችን ፊት ለፊት ካለው ሱቅ የሞባይል ካርድ ገዝቼ ልምጣ ስለው ቁጭ በል እኔ አመጣላሀለሁ ብሎ ያረጀች ቮልስ ዋገን መኪናውን እያስጮኸ ሄዶ ያመጣልኛል እንጂ ገዝተህ ና ብሎ እንደማይፈቅድልኝ አውቃለሁ።
ኮሮና ብሎ የተረገመ በሽታ መጥቶ ገና አንድ ወር ሳይሆነው ሂወቴን ፈተና አደረጋት ።
ሊሊዬ በዚህ ሰአት ልክ አምና እንዳከበርሽው ያ ሁሉ ሰው ተጠርቶ ሊከበር ነው ማለቴ ለሊት ጭፈራ ምናምን እኮ በዚህ ግዜ ስል ገና ካፌ ቀብል አድርጋ•••
"ቲቭው ላይ ሰልችቶን ያጠፋነውን በአስቸኳይ በአስገዳጅ የሚሉት አዋጅ የተከለከሉትን ምናምን አንተም ልደግምልኝ ነው ሶል
ደሞ ብዙ ሰው የሚመጣ አይመስለኝም የማታው የጭፈራ ብሮግራም ግን የማይቀር ነው!"
ቲቪውን ከምታጠፉት በሽታውን ባጠፋችሁት ይሻል ነበር እያልኩ ስልጎሞጎም
"ምን አልከኝ ?"አለችኝ ።
አይ ምንም !
"እሺ ትመጣለህ አትመጣም?
መምጣት መጣለሁ ግን ቀን አልመጣም ተረጅኝ ሊሊዬ እኛ ቤት እራት በግዜ ሁለት ሰአት አከባቢ ሁላችንም አብረን ስለምንበላ የግድ እራት ላይ መገኘት አለብኝ ከዛ ክፍሌ ውስጥ ገብቼ የተኛሁ በማስመሰል የበሩን ቁልፍ ሰርቄም ቢሆን ውጥቼ ለመምጣት እሞክራለሁ። አልኳት ደርሶ ሊሂድ አልሂድ ባላውቅም እንደዛ ከማለት ውጪ አማራጭ አልነበተኝም።
"እሺ ይሁን የኔ ፍቅር ፍቅር እኮ ነህ ዋናው መምጣትህ ነው ግን እሞክራለሁ ሳይሆን እመጣለሁ ነው የሚባለው ኪኪኪኪ ደሞ ልትወጣ ቢያንስ ሀያ ደቂቃ ሲቀርህ ደውልልኝ ዳጊን እልከውና ይዞህ ይመጣል እሺ?"
እሺ አልኳት። ዳጊ ሹፌራቸው ነው። ተስነባበትን።ሁለቱን ቀናት እማዬ•••
"ልጄ ትናንት እና ዛሬ በአካል እዚህ ከኛው ጋር ቁጭ ብለህ በሀሳብ ብን ብለህ ስትጠፋ እያስተዋልኩ ነው ምንድን ነው እሱ ምን ሆነሀል?"
ብላ እስክትጠይቀኝ ድረስ በጭንቀት አሳለፍኳቸው የሊሊ ቤተሰቦች ስራቸው በሙሉ ከውጪ ሀገር ጉዞ ጋር የተያያዘ ነው ወንድማ ዱባይና ሳውዲ እየሄደ እቃ ያመጣል አጎቷ አባቷ ከንግድ ስራቸው ጋር በተያያዘ ውጪ
👍1
ሀገር መሄድ ክፍለ ሀገር እንደመሄድ ቀላል ነው ለነሱ።
አምና እንዳየሁት ከሆነ በልደቷ ላይ የሚገኙ የማላውቃቸው ጓደኞቿ እና ዘመድ አዝማዶቿ በሙሉ
ተመሳሳይ ስራና ተመሳሳይ ኑሮ ውስጥ ያሉ ናቸው እኔስ በገዛ ቅብጠቴ የደረሰው ይድረስብኝ ብቻ ወደቤተሰቦቼ ሌላ ጣጣ ይዤ እንዳልመጣ እያልኩ ስወዛወዝ ስላስተዋለችኝ ነበር እማዬ እንደዛ ያለችኝ።
ተደነባብሬ አይ በስንት ናፍቆት እና ትጋት ዩንቨርስቲ ገብቼ አንድ አመት እንኳን ሳልማር በዘመኑ አዲስ በሽታ ምክንያት መቋረጡ ገርሞኝ እሄን ሁለት ቀን ዝም ብዬ አስበዋለሁ አልኳት አፌ ላይ የመጣልኝን።
አባዬ ብድግ ብሎ በመጠጋት ፀጉሬን እያሻሸ አይዞህ የኔ ልጅ ሁሉም ነገር በጎ ይሆናል በርግጥ በጎም መጥፎም የምናረገው እኛው ነን እኛ ተጠንቅቀን ፈጣሪም ታክሎበት በጎ እንደሚሆን እና ሁሉም በነበረበት እንደሚቀጥል ግን ይታይኛል ልጄ!አለኝ።
ጭራሽ ጭንቅላቴ ተበጠበጠ ክፍሌ ገብቼ ተጋደምኩ በጭንቀት ደና እንቅልፍ ሳልተኛ ስላደርኩ ነው መሰለኝ እንቅልፍ ይዞኝ ሄደ።
ማታ ላይ እናቴ ክፍሌ መጥታ
"ሰለሞኔ ተነስ እንጂ ምንድን ነው እንደዚህ እንቅልፍ ማብዛት በል ተነስ ባይሆን እራትህን ብላና ተመልሰህ ትተኛለህ!" ብላ ስትቀሰቅሰኝ ተፈናጥሬ በመነሳት ሰአቴን ተመለከትኩ ከምሽቱ አንድ ተኩል ሆኗል
ስልኬን ከፍቼ ስመለከት ጋደኛዬ አራት ግዜ ደውሎ አላነሳ ስለው መልእክት ልካል
"አረ ባክህ ሼም ነው አትመጣም እንዴ እኔና ፍቅር እንኳን ከደረስን ስንት ሰአት አለፈን እኮ !" ይላል መልክቱ።
በረጅሙ ተነፈስኩና የምለብሰውን ናብስና ጫማ አዘገጃጅቼ ወደ ሊሊ ሚስኮል አድርጌ ሳሎን በመሄድ ምንም ሳላወራ በዝምታ ከነማዬ ጋር እራት በልቼ ተመለስኩ እንቅልፉ የተጫጫነኝ ስለመሰላቸው ዝምታዬ አልገረማቸውም ።
ቀን ነበር ተለይቶ የተቀመጠውን የውጪውን በር አንድ ትርፍ ቁልፍ የወሰድኩት። ክፍሌ ገብቼ ልብሴን ቶሎ ቶሎ በመቀየር በመስኮት ዘልዬ በመውጣት ኮቴም የውጪው በር ሲከፈት ድምፅም ሳላሰማ ከፍቼ ስወጣ መኪናው ድሮ መጥቶ ቆሟል ሰላም ብየው ገቢና ገባሁ።
እነ ሊሊ ቤት ደርሼ ገና ሊሊ ወዳለችበት ክፍል ሳልገባ እህቷ ይዛኝ ወደውስጥ ስንገባ ደረጃውን ሽቅብ እየወጣሁ ዘወር ስል ከታች በኩል ድንገት በተከፈተችው በር ታሞ የተኛ ሰው ተመለከትኩ
በድንጋጤ ከደረጃው ላይ ቁልቁል ልፈጠፈጥ ምን ቀረኝ በደንብ አየሁት አጎቷ ነው ጉሉኮስ ተደርጎለታል
እንዴ ምን ሆኖ ነው ያ አጎታችሁ ነው አደል ስላት እህቷን አዎ ባክህ በቅርቡ ነው ከውጪ የመጣው መጥቶ ትንሽ እንደቆየ ታመመ
ታድያ ሀኪም ቤት ምን ለውጥ አለው ባክህ እዛም ቢሄድ ዶክተር ነው እሚያየው !
እዚህ ድረስ እየመጣ የሚያየው የቤተሰብ ዶክተር አለ! እያለችኝ ያጎታቸውን ሳል ሰማሁት ድንብርብሬ እንደወጣ በድን ሆኜ እነ ሊሊ ወዳሉበት ክፍል ስገባ ቤቱ ከጥግ እስከ ጥግ ጢም ብሏል
ፊትህን አዙረህ እሩጥ እሩጥ እለኝ•••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
አምና እንዳየሁት ከሆነ በልደቷ ላይ የሚገኙ የማላውቃቸው ጓደኞቿ እና ዘመድ አዝማዶቿ በሙሉ
ተመሳሳይ ስራና ተመሳሳይ ኑሮ ውስጥ ያሉ ናቸው እኔስ በገዛ ቅብጠቴ የደረሰው ይድረስብኝ ብቻ ወደቤተሰቦቼ ሌላ ጣጣ ይዤ እንዳልመጣ እያልኩ ስወዛወዝ ስላስተዋለችኝ ነበር እማዬ እንደዛ ያለችኝ።
ተደነባብሬ አይ በስንት ናፍቆት እና ትጋት ዩንቨርስቲ ገብቼ አንድ አመት እንኳን ሳልማር በዘመኑ አዲስ በሽታ ምክንያት መቋረጡ ገርሞኝ እሄን ሁለት ቀን ዝም ብዬ አስበዋለሁ አልኳት አፌ ላይ የመጣልኝን።
አባዬ ብድግ ብሎ በመጠጋት ፀጉሬን እያሻሸ አይዞህ የኔ ልጅ ሁሉም ነገር በጎ ይሆናል በርግጥ በጎም መጥፎም የምናረገው እኛው ነን እኛ ተጠንቅቀን ፈጣሪም ታክሎበት በጎ እንደሚሆን እና ሁሉም በነበረበት እንደሚቀጥል ግን ይታይኛል ልጄ!አለኝ።
ጭራሽ ጭንቅላቴ ተበጠበጠ ክፍሌ ገብቼ ተጋደምኩ በጭንቀት ደና እንቅልፍ ሳልተኛ ስላደርኩ ነው መሰለኝ እንቅልፍ ይዞኝ ሄደ።
ማታ ላይ እናቴ ክፍሌ መጥታ
"ሰለሞኔ ተነስ እንጂ ምንድን ነው እንደዚህ እንቅልፍ ማብዛት በል ተነስ ባይሆን እራትህን ብላና ተመልሰህ ትተኛለህ!" ብላ ስትቀሰቅሰኝ ተፈናጥሬ በመነሳት ሰአቴን ተመለከትኩ ከምሽቱ አንድ ተኩል ሆኗል
ስልኬን ከፍቼ ስመለከት ጋደኛዬ አራት ግዜ ደውሎ አላነሳ ስለው መልእክት ልካል
"አረ ባክህ ሼም ነው አትመጣም እንዴ እኔና ፍቅር እንኳን ከደረስን ስንት ሰአት አለፈን እኮ !" ይላል መልክቱ።
በረጅሙ ተነፈስኩና የምለብሰውን ናብስና ጫማ አዘገጃጅቼ ወደ ሊሊ ሚስኮል አድርጌ ሳሎን በመሄድ ምንም ሳላወራ በዝምታ ከነማዬ ጋር እራት በልቼ ተመለስኩ እንቅልፉ የተጫጫነኝ ስለመሰላቸው ዝምታዬ አልገረማቸውም ።
ቀን ነበር ተለይቶ የተቀመጠውን የውጪውን በር አንድ ትርፍ ቁልፍ የወሰድኩት። ክፍሌ ገብቼ ልብሴን ቶሎ ቶሎ በመቀየር በመስኮት ዘልዬ በመውጣት ኮቴም የውጪው በር ሲከፈት ድምፅም ሳላሰማ ከፍቼ ስወጣ መኪናው ድሮ መጥቶ ቆሟል ሰላም ብየው ገቢና ገባሁ።
እነ ሊሊ ቤት ደርሼ ገና ሊሊ ወዳለችበት ክፍል ሳልገባ እህቷ ይዛኝ ወደውስጥ ስንገባ ደረጃውን ሽቅብ እየወጣሁ ዘወር ስል ከታች በኩል ድንገት በተከፈተችው በር ታሞ የተኛ ሰው ተመለከትኩ
በድንጋጤ ከደረጃው ላይ ቁልቁል ልፈጠፈጥ ምን ቀረኝ በደንብ አየሁት አጎቷ ነው ጉሉኮስ ተደርጎለታል
እንዴ ምን ሆኖ ነው ያ አጎታችሁ ነው አደል ስላት እህቷን አዎ ባክህ በቅርቡ ነው ከውጪ የመጣው መጥቶ ትንሽ እንደቆየ ታመመ
ታድያ ሀኪም ቤት ምን ለውጥ አለው ባክህ እዛም ቢሄድ ዶክተር ነው እሚያየው !
እዚህ ድረስ እየመጣ የሚያየው የቤተሰብ ዶክተር አለ! እያለችኝ ያጎታቸውን ሳል ሰማሁት ድንብርብሬ እንደወጣ በድን ሆኜ እነ ሊሊ ወዳሉበት ክፍል ስገባ ቤቱ ከጥግ እስከ ጥግ ጢም ብሏል
ፊትህን አዙረህ እሩጥ እሩጥ እለኝ•••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍3
#ሽፍታው_አዕምሮአችን
በበርሃ ተጓዥ
ሽፍታው አዕምሮአቸን
ስንቅና ትጥቅ ይዞ
ምስኪኑን ገላችን
ደምን ከስጋ ጋ
በልቶ የሚፋፋ
አጥንት ምርኩዝ ሆኖት
የሚጓዝ በተስፋ
ነቀዝ ነው አምሳያው
ጠቅላላው ተፈጥሮ
አመንምኖ የሚያስቀር
አካልን ሽርሽሮ፡፡
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
በበርሃ ተጓዥ
ሽፍታው አዕምሮአቸን
ስንቅና ትጥቅ ይዞ
ምስኪኑን ገላችን
ደምን ከስጋ ጋ
በልቶ የሚፋፋ
አጥንት ምርኩዝ ሆኖት
የሚጓዝ በተስፋ
ነቀዝ ነው አምሳያው
ጠቅላላው ተፈጥሮ
አመንምኖ የሚያስቀር
አካልን ሽርሽሮ፡፡
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
#በኔ_የደረሰ
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በጥላሁን
በድንጋጤ ከደረጃው ላይ ቁልቁል ልፈጠፈጥ ምን ቀረኝ በደንብ አየሁት አጎቷ ነው ጉሉኮስ ተደርጎለታል
እንዴ ምን ሆኖ ነው ያ አጎታችሁ ነው አደል ስላት እህቷን
"አዎ ባክህ በቅርቡ ነው ከውጪ የመጣው መጥቶ ትንሽ እንደቆየ ታመመ!"
ታድያ ሀኪም ቤት አልወሰዳችሁትም ?
"ምን ለውጥ አለው ባክህ እዛም ቢሄድ ዶክተር ነው እሚያየው !
እዚህ ድረስ እየመጣ የሚያየው የቤተሰብ ዶክተር አለ!"
እያለችኝ ያጎታቸውን ሳል ሰማሁት ድንብርብሬ እንደወጣ በድን ሆኜ እነ ሊሊ ወዳሉበት ክፍል ስገባ ቤቱ ከጥግ እስከ ጥግ ጢም ብሏል።
ፊትህን አዙረህ እሩጥ እሩጥ እለኝ•••
ገና ብቅ ስል ያየችኝ ሊሊ እየተርገበገበች መጥታ ተጠመጠመችብኝ ብዙ ሰው አይመጣም ብላኝ አልነበር እንዴ እያልኩ በሀሳብ ቢዥታ ውስጥ ሆኜ እኔም አቀፍኳት የሷስ ይሁን ከታዳሚው ተገንጥለው አብረዋት የነበሩ አራት ጓደኛቿ በየተራ "ሰላም ነህ?" ቅብርጥሶ እያሉ በጉንጮቻቸው ጉንጬን ደበደቡት "አትሳሳሙ" የሚለው ማስታወቂያ ትዝ አለኝ ወደ ቤት ከመጣሁና ባባዬ ቁጥጥር ስር ከዋልኩ ወድሂ የመጀሚሪያውን የአትሳሳሙ ህግ ለመጀመሪያ ግዜ ጣስኩ።
በተለይ መጨረሻ ላይ የሳመችኝ የምግብ ብዛት እና አይነቱ እየዘጋት እህል በልታ የማታውቅ የምትመስለው ቅጭጭ ያለች ቀጫጫ ልጅ የፀጉር አሰራራ ነው መሰለኝ እሱን እንድትመስለኝ ያደረገኝ ብቻ የጉንጫ አጥንት ጉንጬን ሲወጋው እራሱ ኮረና ዛሬ አታመልጠኝም አገኘሁህ ያለኝ ነው የመሰለኝ።
ኪሴ ውስጥ ያለችውን በትንሽ ብልቃጥ የያዝኳትን ሳኒታይዘር አውጥቼ እጄን ሳይሆን ፊቴን ልታጠብበት ፈለኩ። ለካ ለእጅ እንጂ ለፊት አይሆንም። ቢሆን ኖሮስ ቤት በኩል ልታጠብ
እንኳን ለመታጠቢያ ለመተንፈሻም ግዜ ሳይሰጡኝ
ሊሊ እና ጓደኞቿ መሀላቸው አስገብተው እያዋከቡ እቤት ውስጥ ወዳሉት ታዳሚዎች መሀል ወሰዱኝ።
እነዛ እቤታቸው ግርግዳ ላይ አንዲት በረሮ ቢያዩ እርርርይ እያሉ ቤቱን ጥለው የሚጠፉ የሀብታም ልጆች ኮሮናን አይፈሩትም ብቻ ሳይሆን ትዝም አይላቸውም ማለት ነው ብዬ እራሴን ጠየኩ ሌላ ማንን እጠይቃለሁ ብጠይቅስ ማን ይመልስልኛል?።
ሁሉንም ሳያቸው ሀገራችንን ጨምሮ በአለም ዙርያ ስለዚህ በሽታ በሚድያ የሚለፈፈውን የሚስበው የኛ ቴሌቭዥን እና ዲሽ ብቻ ነው እንዴ አልኩ።የሚያዳምጠውም የሚያየውም አባዬ ብቻ መስሎ ተሰማኝ።
ጭራሽ ሊሊዬን ሞቀኝ ወደ በሩ አከባቢ ብንሆንስ ብዬ ስጠይቃት የሰመችው ያቺ ኮሮና ስጋ ለብሶ መስላ የታየችኝ ቀጭኗ ልጅ ያጋመሰችውን ቢራ ወደ አፌ እያስጠጋች •••
"እንካ ጎንጨት በልበትና ሞቅ ይበልህ ሞቅ ሲልህ የቤቱ ሙቀት አይታወቅህም ክክክክክክ" አለች። ተከትለዋት ሁሉም ሳቁ ። እኔ እንኳን የምስቅበት የማገጥበትም ጥርስ አልነበረኝም።
አመሰግናለሁ ግን አልጠጣም ብዬ ቢራዋን ከነጇ ከአፌ አከበቢ ገፋ አደረኩት።
ጓደኛዬንና ፍቅረኛውን ከሩቅ አየኋቸው እራሳቸውን አያውቁም በራሳቸው አለም ርቀው ሄደዋል ሊሊዮዬን ጠጋ አልኩና በድጋሚ •••
ስገባ አጎትሽን አየሁት ልበል? አሞታል እንዴ ሊሊዬ? ለምን አልነገርሽኝም እንዳስተዋወቅሽኝ ረስተሽው ነው። መጥቼ እጠይቀው ነበርኮ ።
ዘንድሮ በሽትኛ መጠየቅ ቀርቷል እኮ አልሰማህም እንዴ ኧረ በክህ በልደቷ ቀን ጓደኛዬን ስለበሽታ ስለጥየቃ ምናምን ማውራቱን ተውና ዘና በል " አለችኝ። አሁንም ያችው ልጅ። ወይ ጣጣ ልጅቷ ሊሊ በፊርማዋ አረጋግጣ ውክልና የሰጠቻት ነው እምትመስለው ገና ሊሊን ማናገር ስጀምር ወሬዬን ሳልጨርስ እሷ መልስ እየሰጠች አላስወራ አለችኝ።
ከዛ ቡሀላ አንዳች የሚገላግል ነገር ከዛች ልጅ ካልገላገለኝ በቀር ላለማውራት ወሰንኩ።
ሊሊዬ ከዛም ከዛም እየጠሯት ውክብክብ ስላለች ፍቴን ማየትና መረዳት እንኳን አልቻለችም ነበር።ሁለተኛውን ህግ ጥሻለሁ ርቀቴን ሳልጠብቅ በብዙ የሊሊ ልደት ተጋባዦች መሀል ሆኜ ድንገት ወጥመድ ውስጥ ገብታ መውጫ እንዳጣች ጦጣ ግራ ተጋብቼ ግራ እና ቀኝ ስቁለጨለጭ ቆየሁና በሚጠጡ ፣በሚደንሱ፣ በሚሳሳሙ፣ በሚተሸሹ ሰዎች መሀል ሆኖ በተጨነቀ ፊት መቆየት ከባድ ሆነብኝ።
ይለይለት ብዬ ይሁን ይለይልኝ ብቻ ከቢራውም ከውስኪውም ከወይኑም ቀላቅዬ ስጠጣ ፍርሀት እና ደስታ የተቀላቀለበት ስካር ሰከርኩ።
መጠጡ በላይ በላይ ሲመጣ ፍርሀቱ ጠፍቶ ጊዛዊው ጀግንነት መጣ ድፍረቴ ጨቅ አለ።
ባንድ ግዜ እንደማያ ተለዋውጬላችሁ ቁጭ አልኩ።ኧረ የምናባቱ ኮሮና ሺ አመት አይኖር ሙዚቃውን ከፍ አድርገው ዲጄው ምንድን ነው ለቅሶ ቤት አስመሰለው እኮ ሊሊዬ ዲጄውን ከሰልስት ላይ ነው እንዴ አስነስታችሁ ያመጣችሁት ኬኬኬኬኬኬኬኬ"
እሷም ተከትላኝ
" ኪኪኪኪኪኪኪኪ እሄንን ሶል ነው ስፈልገው የነበረው!" ሊሊም ጓደኞቻም ሳቁ።
ቤቱ አልበቃ አለኝ ከላይ የለበስኩትን ጃኬት አውልቄ ጣልኩት።
ተቀላቀልኩ ፣ ጨፈርኩ ፣ዘለልኩ፣ እየተቀባበልኩ ጠጣሁ፣ ከሊሊዬ ጋር በየደቂቃው መሳሳም፣ መደነስ እስኪደክመን ከጓደኛቿም ጋር ተራ በተራ ጨፈርን አበድን ፣ ከነፍን በረርን ፣
እነሱ የረሱትን ሁሉ ረሳሁ። እነሱ የናቁትን ሁሉ ናቅሁ! እነሱ የሆንኩትን ሁሉ ሆንኩ።
ከለሊቱ ዘጠኝ ሰአት ሲሆን አባዬ ትዝ ብሎኝ ወደቤቴ ካልሸኘሽኝ ብዬ ቤቱን ባንድ እግሩ አቆምኩት በወሰደኝ መኪና ተመልሼ ልክ ግቢያችን በር ላይ ስደርስ ስካሬ ብን ብሎ ጠፋ።
ሹክክ ብዬ እንደወጣሁት ሹክክ ብዬ በመግባት ተጠቀለልኩ።
አይነጋ የለ ነጋ ። ጥዋት 2:30 አከባቢ እማዬ የክፍሌን በር አንኳክታ ሰለሞኔ ተነስ ቁርስ ቀርቧል እየጠበቅንህ ነው ስትለኝ ።መብረቅ ክፍሌ ላይ የወረደባት ይመስል ክው አልኩላችሁ።
ለካ እሄም አለ አሁን እኔ ለሊት እዛ ሁሉ ጉድ ውስጥ አሸሸ ገዳሜ ስል አድሬ እንዴት ነው ከሽማግሌው አባቴና ከአረጊቷ እናቴ ጋር መአድ ባንድ ላይ ቀርቤ እምበላው ?
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በጥላሁን
በድንጋጤ ከደረጃው ላይ ቁልቁል ልፈጠፈጥ ምን ቀረኝ በደንብ አየሁት አጎቷ ነው ጉሉኮስ ተደርጎለታል
እንዴ ምን ሆኖ ነው ያ አጎታችሁ ነው አደል ስላት እህቷን
"አዎ ባክህ በቅርቡ ነው ከውጪ የመጣው መጥቶ ትንሽ እንደቆየ ታመመ!"
ታድያ ሀኪም ቤት አልወሰዳችሁትም ?
"ምን ለውጥ አለው ባክህ እዛም ቢሄድ ዶክተር ነው እሚያየው !
እዚህ ድረስ እየመጣ የሚያየው የቤተሰብ ዶክተር አለ!"
እያለችኝ ያጎታቸውን ሳል ሰማሁት ድንብርብሬ እንደወጣ በድን ሆኜ እነ ሊሊ ወዳሉበት ክፍል ስገባ ቤቱ ከጥግ እስከ ጥግ ጢም ብሏል።
ፊትህን አዙረህ እሩጥ እሩጥ እለኝ•••
ገና ብቅ ስል ያየችኝ ሊሊ እየተርገበገበች መጥታ ተጠመጠመችብኝ ብዙ ሰው አይመጣም ብላኝ አልነበር እንዴ እያልኩ በሀሳብ ቢዥታ ውስጥ ሆኜ እኔም አቀፍኳት የሷስ ይሁን ከታዳሚው ተገንጥለው አብረዋት የነበሩ አራት ጓደኛቿ በየተራ "ሰላም ነህ?" ቅብርጥሶ እያሉ በጉንጮቻቸው ጉንጬን ደበደቡት "አትሳሳሙ" የሚለው ማስታወቂያ ትዝ አለኝ ወደ ቤት ከመጣሁና ባባዬ ቁጥጥር ስር ከዋልኩ ወድሂ የመጀሚሪያውን የአትሳሳሙ ህግ ለመጀመሪያ ግዜ ጣስኩ።
በተለይ መጨረሻ ላይ የሳመችኝ የምግብ ብዛት እና አይነቱ እየዘጋት እህል በልታ የማታውቅ የምትመስለው ቅጭጭ ያለች ቀጫጫ ልጅ የፀጉር አሰራራ ነው መሰለኝ እሱን እንድትመስለኝ ያደረገኝ ብቻ የጉንጫ አጥንት ጉንጬን ሲወጋው እራሱ ኮረና ዛሬ አታመልጠኝም አገኘሁህ ያለኝ ነው የመሰለኝ።
ኪሴ ውስጥ ያለችውን በትንሽ ብልቃጥ የያዝኳትን ሳኒታይዘር አውጥቼ እጄን ሳይሆን ፊቴን ልታጠብበት ፈለኩ። ለካ ለእጅ እንጂ ለፊት አይሆንም። ቢሆን ኖሮስ ቤት በኩል ልታጠብ
እንኳን ለመታጠቢያ ለመተንፈሻም ግዜ ሳይሰጡኝ
ሊሊ እና ጓደኞቿ መሀላቸው አስገብተው እያዋከቡ እቤት ውስጥ ወዳሉት ታዳሚዎች መሀል ወሰዱኝ።
እነዛ እቤታቸው ግርግዳ ላይ አንዲት በረሮ ቢያዩ እርርርይ እያሉ ቤቱን ጥለው የሚጠፉ የሀብታም ልጆች ኮሮናን አይፈሩትም ብቻ ሳይሆን ትዝም አይላቸውም ማለት ነው ብዬ እራሴን ጠየኩ ሌላ ማንን እጠይቃለሁ ብጠይቅስ ማን ይመልስልኛል?።
ሁሉንም ሳያቸው ሀገራችንን ጨምሮ በአለም ዙርያ ስለዚህ በሽታ በሚድያ የሚለፈፈውን የሚስበው የኛ ቴሌቭዥን እና ዲሽ ብቻ ነው እንዴ አልኩ።የሚያዳምጠውም የሚያየውም አባዬ ብቻ መስሎ ተሰማኝ።
ጭራሽ ሊሊዬን ሞቀኝ ወደ በሩ አከባቢ ብንሆንስ ብዬ ስጠይቃት የሰመችው ያቺ ኮሮና ስጋ ለብሶ መስላ የታየችኝ ቀጭኗ ልጅ ያጋመሰችውን ቢራ ወደ አፌ እያስጠጋች •••
"እንካ ጎንጨት በልበትና ሞቅ ይበልህ ሞቅ ሲልህ የቤቱ ሙቀት አይታወቅህም ክክክክክክ" አለች። ተከትለዋት ሁሉም ሳቁ ። እኔ እንኳን የምስቅበት የማገጥበትም ጥርስ አልነበረኝም።
አመሰግናለሁ ግን አልጠጣም ብዬ ቢራዋን ከነጇ ከአፌ አከበቢ ገፋ አደረኩት።
ጓደኛዬንና ፍቅረኛውን ከሩቅ አየኋቸው እራሳቸውን አያውቁም በራሳቸው አለም ርቀው ሄደዋል ሊሊዮዬን ጠጋ አልኩና በድጋሚ •••
ስገባ አጎትሽን አየሁት ልበል? አሞታል እንዴ ሊሊዬ? ለምን አልነገርሽኝም እንዳስተዋወቅሽኝ ረስተሽው ነው። መጥቼ እጠይቀው ነበርኮ ።
ዘንድሮ በሽትኛ መጠየቅ ቀርቷል እኮ አልሰማህም እንዴ ኧረ በክህ በልደቷ ቀን ጓደኛዬን ስለበሽታ ስለጥየቃ ምናምን ማውራቱን ተውና ዘና በል " አለችኝ። አሁንም ያችው ልጅ። ወይ ጣጣ ልጅቷ ሊሊ በፊርማዋ አረጋግጣ ውክልና የሰጠቻት ነው እምትመስለው ገና ሊሊን ማናገር ስጀምር ወሬዬን ሳልጨርስ እሷ መልስ እየሰጠች አላስወራ አለችኝ።
ከዛ ቡሀላ አንዳች የሚገላግል ነገር ከዛች ልጅ ካልገላገለኝ በቀር ላለማውራት ወሰንኩ።
ሊሊዬ ከዛም ከዛም እየጠሯት ውክብክብ ስላለች ፍቴን ማየትና መረዳት እንኳን አልቻለችም ነበር።ሁለተኛውን ህግ ጥሻለሁ ርቀቴን ሳልጠብቅ በብዙ የሊሊ ልደት ተጋባዦች መሀል ሆኜ ድንገት ወጥመድ ውስጥ ገብታ መውጫ እንዳጣች ጦጣ ግራ ተጋብቼ ግራ እና ቀኝ ስቁለጨለጭ ቆየሁና በሚጠጡ ፣በሚደንሱ፣ በሚሳሳሙ፣ በሚተሸሹ ሰዎች መሀል ሆኖ በተጨነቀ ፊት መቆየት ከባድ ሆነብኝ።
ይለይለት ብዬ ይሁን ይለይልኝ ብቻ ከቢራውም ከውስኪውም ከወይኑም ቀላቅዬ ስጠጣ ፍርሀት እና ደስታ የተቀላቀለበት ስካር ሰከርኩ።
መጠጡ በላይ በላይ ሲመጣ ፍርሀቱ ጠፍቶ ጊዛዊው ጀግንነት መጣ ድፍረቴ ጨቅ አለ።
ባንድ ግዜ እንደማያ ተለዋውጬላችሁ ቁጭ አልኩ።ኧረ የምናባቱ ኮሮና ሺ አመት አይኖር ሙዚቃውን ከፍ አድርገው ዲጄው ምንድን ነው ለቅሶ ቤት አስመሰለው እኮ ሊሊዬ ዲጄውን ከሰልስት ላይ ነው እንዴ አስነስታችሁ ያመጣችሁት ኬኬኬኬኬኬኬኬ"
እሷም ተከትላኝ
" ኪኪኪኪኪኪኪኪ እሄንን ሶል ነው ስፈልገው የነበረው!" ሊሊም ጓደኞቻም ሳቁ።
ቤቱ አልበቃ አለኝ ከላይ የለበስኩትን ጃኬት አውልቄ ጣልኩት።
ተቀላቀልኩ ፣ ጨፈርኩ ፣ዘለልኩ፣ እየተቀባበልኩ ጠጣሁ፣ ከሊሊዬ ጋር በየደቂቃው መሳሳም፣ መደነስ እስኪደክመን ከጓደኛቿም ጋር ተራ በተራ ጨፈርን አበድን ፣ ከነፍን በረርን ፣
እነሱ የረሱትን ሁሉ ረሳሁ። እነሱ የናቁትን ሁሉ ናቅሁ! እነሱ የሆንኩትን ሁሉ ሆንኩ።
ከለሊቱ ዘጠኝ ሰአት ሲሆን አባዬ ትዝ ብሎኝ ወደቤቴ ካልሸኘሽኝ ብዬ ቤቱን ባንድ እግሩ አቆምኩት በወሰደኝ መኪና ተመልሼ ልክ ግቢያችን በር ላይ ስደርስ ስካሬ ብን ብሎ ጠፋ።
ሹክክ ብዬ እንደወጣሁት ሹክክ ብዬ በመግባት ተጠቀለልኩ።
አይነጋ የለ ነጋ ። ጥዋት 2:30 አከባቢ እማዬ የክፍሌን በር አንኳክታ ሰለሞኔ ተነስ ቁርስ ቀርቧል እየጠበቅንህ ነው ስትለኝ ።መብረቅ ክፍሌ ላይ የወረደባት ይመስል ክው አልኩላችሁ።
ለካ እሄም አለ አሁን እኔ ለሊት እዛ ሁሉ ጉድ ውስጥ አሸሸ ገዳሜ ስል አድሬ እንዴት ነው ከሽማግሌው አባቴና ከአረጊቷ እናቴ ጋር መአድ ባንድ ላይ ቀርቤ እምበላው ?
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
❤1👏1
#ግዞት
እፍኝ ተበድሮ ነፍሱን ሊያድናት
ባርያ ሆኖ ሞተ ያባቴ አባት
እዳው ተጭኖት
ባርነት ሲመረው ሲያቅት ለግዞት
የጭሰኛ ክብር ሰጡት ለኔ አባት
አርሶ፣ ዘርቶ፣ አጭዶ ጭሰኛው አባቴ
ምርቱን ሲገብረው ለመሬት ከበርቴ
መሬት ለአራሹ ” መፈክር አንስቼ
ታግዬ አሸነፍኩ ከጫካ ገብቼ
ወገኖቼ ሁሉ ቀድመው የተገፉት
በኔ በልጃቸው አሁን ገና አረፉት
ብዬ በተስፋ ስንቅ ቃላት ስደረድር
አንደበት ሳደድር
ከኔም ለካ አልጠፋም የጭቆናው ቀንበር
ካ'ብታም ግዞት ስር ነኝ ተብዬ “ወዝ አደር”
መደብ ከታች እላይ ጎባጣው ሳይቀና
ነጻነት ከቃላት መቼስ አልፎ ያቅና፡፡
🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
እፍኝ ተበድሮ ነፍሱን ሊያድናት
ባርያ ሆኖ ሞተ ያባቴ አባት
እዳው ተጭኖት
ባርነት ሲመረው ሲያቅት ለግዞት
የጭሰኛ ክብር ሰጡት ለኔ አባት
አርሶ፣ ዘርቶ፣ አጭዶ ጭሰኛው አባቴ
ምርቱን ሲገብረው ለመሬት ከበርቴ
መሬት ለአራሹ ” መፈክር አንስቼ
ታግዬ አሸነፍኩ ከጫካ ገብቼ
ወገኖቼ ሁሉ ቀድመው የተገፉት
በኔ በልጃቸው አሁን ገና አረፉት
ብዬ በተስፋ ስንቅ ቃላት ስደረድር
አንደበት ሳደድር
ከኔም ለካ አልጠፋም የጭቆናው ቀንበር
ካ'ብታም ግዞት ስር ነኝ ተብዬ “ወዝ አደር”
መደብ ከታች እላይ ጎባጣው ሳይቀና
ነጻነት ከቃላት መቼስ አልፎ ያቅና፡፡
🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#በኔ_የደረሰ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት (የመጨረሻው ክፍል)
፡
፡
#በጥላሁን
ከለሊቱ ዘጠኝ ሰአት ሲሆን አባዬ ትዝ ብሎኝ ወደቤቴ ካልሸኘሽኝ ብዬ ቤቱን ባንድ እግሩ አቆምኩት በወሰደኝ መኪና ተመልሼ ልክ ግቢያችን በር ላይ ስደርስ ስካሬ ብን ብሎ ጠፋ።
ሹክክ ብዬ እንደወጣሁት ሹክክ ብዬ በመግባት ተጠቀለልኩ።
አይነጋ የለ ነጋ ። ጥዋት 2:30 አከባቢ እማዬ የክፍሌን በር አንኳክታ ሰለሞኔ ተነስ ቁርስ ቀርቧል እየጠበቅንህ ነው ስትለኝ ።መብረቅ ክፍሌ ላይ የወረደባት ይመስል ክው አልኩላችሁ።
ለካ እሄም አለ አሁን እኔ ለሊት እዛ ሁሉ ጉድ ውስጥ አሸሸ ገዳሜ ስል አድሬ እንዴት ነው ከሽማግሌው አባቴና ከአረጊቷ እናቴ ጋር መአድ ባንድ ላይ ቀርቤ እምበላው ••••
እምለው እማረገው ሁሉ ጨነቀኝ ቀና ብዬ እዛው አልጋዬ ላይ ቁጭ አልኩና ሁለቱን እጄቼን ወደ ፊት ዘርግቼ እያየኋቸው •••
ማታ እንዳልተለከፍኩ በምን እርግጠኛ ነኝ እራሴን ጠየኩት?
በምንም ደሞ ጉሮሮህ አከባቢ ህመም እየተሰማህ ነው ይዞህ ይሆን እንዴ ? አለኝ ውስጤ
ጉሮሮዬ እንኳን ማታ ብዙ አይነት መጠጥ እየቀላቀልኩ ስለጠጣሁ ሊሆን ይችላል ያመመኝ ።
ላይሆንም ይችላል በሽታውም አንዱ ምልክቱ እንደዛ ነው?
እስቲ አስበው በዚህ እጅህ ስንቱን ነገር ነክተሀል፣ ከስንቱ ጋር ተጎራርሰህ በልተሀል ፣ከስንቱ ጋር እየተቀባበልክ ጠጥተሀል ፣ ስንቱ የተቀባበለውን ቢራ መክፈቻ ተጠቅመሀል
ውስጤ ሌላ ሰው ተቀምጦ የሚያስፈራራኝ መሰለኝ በሁለት ሀሳብ ተከፍዬ ከራሴ ጋር ስከራከር እራሴን አመመኝ።
አንድ ሰው የማንፈልገውን ወይም የሚረብሸንን ወሬ ቢያወራብን ዝም እንዲል አልያም ወሬ እንዲቀይር እንነግረዋለን ካልሆነ ካጠገቡ ተነስተን እንሄዳለን ከሚድያ ላይ የሚወራውን መስማት ካልፈለግን ተነስተን እንጠረቅመዋለን።
ከደጅ የሚመጣን ጩኸት መስማት ካልፈለግን ጆሮአችንን እንይዛለን
ከውስጣችን የሚመጣውን ጩከት መስማት ባንፈልግ ምናችንን እንይዘዋለን ወዴትስ እንሸሻለን?
እማዬ ድጋሚ የክፍሌን በር አንኳኩታ "ኧረ አባትህ እየጠበቀህ ነው ሰለሞኔ ቁርስ ቀርቧል እኮ!" አለችኝ።
ወጥቼ ሻወር ቤት ገባሁና ከሰዉነቴ ክፍሎች ሁሉ እጄን ደጋግሜ ታጠብኩት።
"ውስጥህንስ በምን ታጥበዋለህ ይዞህ ከሆነ በትንፋሽም እኮ ይተላለፋል አለኝ ከበሽታው በላይ ውጋት የሆነብኝ የውጤ ሀሳብ ነው።
እናባዬ ወዳሉበት ሳሎን ገባሁ ። ግን ሳልጠገቸው ፈንጠር ብዬ ብቻዬን ተቀመጥኩ።
"ዛሬ ምን ሆኗል ልጄ ና እንጂ ቁርስ እንብላ አንተን አይደለም እንዴ የምንጠብቀው" አለ አባዬ።
አይ አይሆንም አባ ካሁን ቡሀላ እሄ ክፉ በሽታ ከሀገራችን ተጠራርጎ እስኪወጣ ምግብም ቢሆን አብረን ለመብላት ስንል መቀራረብ የለብንም ። ለብቻዬ ብታቀርብልኝ ይሻላል አይሻልም አባ? ስል•••
እማ ጣልቃ ገብታ " አበስኩ ገበርኩ የደጁን ይሁን ስል ልጆቼንም ከጉያዬ ሊያርቅብኝ ነው እሄ በሽታ ከመች ወዲህ ነው ልጄ መአድ ተነጣጥለን በልተን የምናውቀው መአድ በአንድ ላይ ቀርቦ መብላት ፍቅርን ያደረጃል ልጄ።
ደሞ በኛ መሀል ኬት ይመጣል ከቤት ወጥተን አናውቅ የምንፈልገውን እቃ እንኳን የባታችሁ ወንድም ነው ገዝቶ የሚያመጣልን እቃ ገዝቶ መጥቶ እንኳን በር ላይ አስቀምጠህ ሂድ እንጂ ግባ ብሎት አያውቅ አባታችሁ።
ዛሬ ድንገት ተነስተህ ለብቻዬ አቅርቡልኝ ማለቱን ምን አመጣው ጥሩ ህልም አላየህም ልጄ እስቲ ንገረኝ?" ብላ ዝም ብዬ ሳያት እኔን ትታ ወደአባዬ ፍቷን መለሰችና
"፣እሄው ልጆቼን የፀሀይ ብርሀን እስኪናፍቃቸው ድረስ አላላውስ ብለህ ተጭነህ ስታስጨንቃቸው በጭንቀት ብዛት የልጄን አይምሮ እንዲቃወስ አድርገከው አረፍክ " ብላ ስታፈጥበት
ደና ነኝ እማዬ ምንም የሆንኩት ነገር የለም አባንም እንደዛ ማለት የለብሽም አባ ልክ ነው ። በቃ ተራራቁ ተብሏል እንራራቅ ነው ያልኩት ቀለል አርጋችሁ እዩትና እሺ በሉኝ እናንተ አንድ ላይ ብሉ ለኔ ለብቻዬ ስጪኝ። ስል እህቴ ከነበረችበት ተነስታ •••
"ባክህ የሌለ ነገር እያወራህ አታጨናንቃቸው ተነስና እንብላ!" እያለች እጄን ይዛ ልትጎትተኝ ነው መሰለኝ ወደኔ ስትጠጋ
ከተቀመጥኩበት ተፈናጥሬ በመነሳት እንዳትጠጊኝ እህቴ ነግሬሻለሁ እንዳትጠጊኝ በቃ ስል አባም ግራ ተጋብቶ ተነስቶ ሲቆም
ተጠግቶ ሳይዘኝ ቤቱን ጥየላቸው ብን ብዬ ልጠፋ አሰብኩና እናቴ ልጄ አበደ ብላ እራሷን ከማጥፋት እንደማትመለስ ሳስበው ፈራሁ።
አንተም እንዳትጠጋኝ አባ በቃ ተረዱኝ አትጠጉኝ አልኩ አትጠጉኝ እያልኩ ወደ ክፍሌ በመግባት ከውስጥ ዘጋሁት።
በስንት ውዝግብ አሳምኛቸው ምግብ መስኮት ላይ እየተደረገልኝ በልቼ አጥቤ እየመለስኩ ስምንት ቀን ሆነኝ ። በዘጠነኛው ቀን ጥዋት ጋደኛዬ ደውሎ
የነ ሊሊ ቤተሰቦች በሽተኛ እቤት ውስጥ መኖሩ ተጠቁሞባቸው ቤተሰቡን በሙሉ አፋፍሰው ካስገባቸው ቡሀላ በምርመራ ሌሎቹ የቤተሰብ አባላት ላይም ስለተገኘ ያን ቀን የሊሊ ልደት ላይ የተገኙት በሙሉ እየታደኑ ወደማቆያ እየተወሰዱ ነው አሉ እኛ ጋም መምጣታቸው አይቀርም አልቆልናል ሶል!"
ሲለኝ እኔ እዛው በተኛሁበት አለቀልኝ ። የተኛሁበት በላብ ሲዘፈቅ ትዝ ይለኛል ካልጋዬ ላይ መነሳት አቃተኝ ካንድ ቀን ቡሀላ ብንን ስል መስኮት ላይ ያስቀመጡትን ምግብ ወስጄ አለመብላቴ ያስጨነቃቸው ቤተሰቦቼ እህቴን በመስኮት አዘልለው በማስገባትና ከውስጥ እንድትከፍት በማረግ አልጋዬ ላይ ዙሪያዬን ከበውኝ እስክነቃ በጭንቀት ሲጠባበቁ ተመለከትኩ ። በሂወቴ እንደዛች ቅፅበት መሪር ሀዘን እና የነብሰ ገዳይነት ስሜት ተሰምቶኝ አያውቅም ። እርርይ አልኩ።
በንጋታው ሁላችንንም ወደ ማቆያ ወሰዱን ከቀናት ቡሀላ የምርመራ ውጤቱ ሁላችንም እንዳለብን አመለከተ።
ውጤቱን ስሰማ በተለይ ቤተሰቦቼን በመሉ ማስያዜን ስሰማ ድጋሚ እራሴን ሳትኩ ከሳምንታት ቡሀላ ወደራሴ ስመለስ እና ስነቃ እቤታችን ውስጥ ነኝ።
ሶስታችን አገገምን አባዬ ግን ከመሀላችን
ጎድሏል ።
በነበረበት ስኳር እና ሌላ ተጓዳኝ ህመም ምክንያት በሽታውን መቋቋም አቅቶት በሀገራችን በዚህ በሽታ ከሞቱት ሰዎች መሀል አንዱ ሆነ ።
ይህ ሁሉ በኔ ነው በኔ የደረሰ በማንም አይድረስ!!
💫ተፈፀመ💫
እስቲ ሁላችሁም ይቺን ፅሁፍ በዚች ደቂቃ እያነበባችሁ ያላችሁ #ኮረና የመጣ ጊዜ #ጥንቃቂያችሁ እንዴት ነበር❓❓#አሁንስ❓❓ መልሱን ለራሳችሁ
ግን አሁንም በሽታው ምንም የተቀየረ ነገር የለም መድሃኒት አልተገኘለትም አሁንም የኛ ብቻ ሳይሆን የአለም ስጋት ነው። በየቤታችን እስኪገባ አንጠብቅ እናም ይሄ ታሪክ አንድ ሰው ያስተምራልና #Share እያደረጋቹ።
🛑አሁንም ግን🛑
#እርቀታችንን_እንጠብቅ
#ማክስ_በአግባቡ_እናድርግ
#እጃችንን_በአግባቡ_እንታጠብ
#ከቻልን_ቤት_እንቆይ #ውዶቼ
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_ሰባት (የመጨረሻው ክፍል)
፡
፡
#በጥላሁን
ከለሊቱ ዘጠኝ ሰአት ሲሆን አባዬ ትዝ ብሎኝ ወደቤቴ ካልሸኘሽኝ ብዬ ቤቱን ባንድ እግሩ አቆምኩት በወሰደኝ መኪና ተመልሼ ልክ ግቢያችን በር ላይ ስደርስ ስካሬ ብን ብሎ ጠፋ።
ሹክክ ብዬ እንደወጣሁት ሹክክ ብዬ በመግባት ተጠቀለልኩ።
አይነጋ የለ ነጋ ። ጥዋት 2:30 አከባቢ እማዬ የክፍሌን በር አንኳክታ ሰለሞኔ ተነስ ቁርስ ቀርቧል እየጠበቅንህ ነው ስትለኝ ።መብረቅ ክፍሌ ላይ የወረደባት ይመስል ክው አልኩላችሁ።
ለካ እሄም አለ አሁን እኔ ለሊት እዛ ሁሉ ጉድ ውስጥ አሸሸ ገዳሜ ስል አድሬ እንዴት ነው ከሽማግሌው አባቴና ከአረጊቷ እናቴ ጋር መአድ ባንድ ላይ ቀርቤ እምበላው ••••
እምለው እማረገው ሁሉ ጨነቀኝ ቀና ብዬ እዛው አልጋዬ ላይ ቁጭ አልኩና ሁለቱን እጄቼን ወደ ፊት ዘርግቼ እያየኋቸው •••
ማታ እንዳልተለከፍኩ በምን እርግጠኛ ነኝ እራሴን ጠየኩት?
በምንም ደሞ ጉሮሮህ አከባቢ ህመም እየተሰማህ ነው ይዞህ ይሆን እንዴ ? አለኝ ውስጤ
ጉሮሮዬ እንኳን ማታ ብዙ አይነት መጠጥ እየቀላቀልኩ ስለጠጣሁ ሊሆን ይችላል ያመመኝ ።
ላይሆንም ይችላል በሽታውም አንዱ ምልክቱ እንደዛ ነው?
እስቲ አስበው በዚህ እጅህ ስንቱን ነገር ነክተሀል፣ ከስንቱ ጋር ተጎራርሰህ በልተሀል ፣ከስንቱ ጋር እየተቀባበልክ ጠጥተሀል ፣ ስንቱ የተቀባበለውን ቢራ መክፈቻ ተጠቅመሀል
ውስጤ ሌላ ሰው ተቀምጦ የሚያስፈራራኝ መሰለኝ በሁለት ሀሳብ ተከፍዬ ከራሴ ጋር ስከራከር እራሴን አመመኝ።
አንድ ሰው የማንፈልገውን ወይም የሚረብሸንን ወሬ ቢያወራብን ዝም እንዲል አልያም ወሬ እንዲቀይር እንነግረዋለን ካልሆነ ካጠገቡ ተነስተን እንሄዳለን ከሚድያ ላይ የሚወራውን መስማት ካልፈለግን ተነስተን እንጠረቅመዋለን።
ከደጅ የሚመጣን ጩኸት መስማት ካልፈለግን ጆሮአችንን እንይዛለን
ከውስጣችን የሚመጣውን ጩከት መስማት ባንፈልግ ምናችንን እንይዘዋለን ወዴትስ እንሸሻለን?
እማዬ ድጋሚ የክፍሌን በር አንኳኩታ "ኧረ አባትህ እየጠበቀህ ነው ሰለሞኔ ቁርስ ቀርቧል እኮ!" አለችኝ።
ወጥቼ ሻወር ቤት ገባሁና ከሰዉነቴ ክፍሎች ሁሉ እጄን ደጋግሜ ታጠብኩት።
"ውስጥህንስ በምን ታጥበዋለህ ይዞህ ከሆነ በትንፋሽም እኮ ይተላለፋል አለኝ ከበሽታው በላይ ውጋት የሆነብኝ የውጤ ሀሳብ ነው።
እናባዬ ወዳሉበት ሳሎን ገባሁ ። ግን ሳልጠገቸው ፈንጠር ብዬ ብቻዬን ተቀመጥኩ።
"ዛሬ ምን ሆኗል ልጄ ና እንጂ ቁርስ እንብላ አንተን አይደለም እንዴ የምንጠብቀው" አለ አባዬ።
አይ አይሆንም አባ ካሁን ቡሀላ እሄ ክፉ በሽታ ከሀገራችን ተጠራርጎ እስኪወጣ ምግብም ቢሆን አብረን ለመብላት ስንል መቀራረብ የለብንም ። ለብቻዬ ብታቀርብልኝ ይሻላል አይሻልም አባ? ስል•••
እማ ጣልቃ ገብታ " አበስኩ ገበርኩ የደጁን ይሁን ስል ልጆቼንም ከጉያዬ ሊያርቅብኝ ነው እሄ በሽታ ከመች ወዲህ ነው ልጄ መአድ ተነጣጥለን በልተን የምናውቀው መአድ በአንድ ላይ ቀርቦ መብላት ፍቅርን ያደረጃል ልጄ።
ደሞ በኛ መሀል ኬት ይመጣል ከቤት ወጥተን አናውቅ የምንፈልገውን እቃ እንኳን የባታችሁ ወንድም ነው ገዝቶ የሚያመጣልን እቃ ገዝቶ መጥቶ እንኳን በር ላይ አስቀምጠህ ሂድ እንጂ ግባ ብሎት አያውቅ አባታችሁ።
ዛሬ ድንገት ተነስተህ ለብቻዬ አቅርቡልኝ ማለቱን ምን አመጣው ጥሩ ህልም አላየህም ልጄ እስቲ ንገረኝ?" ብላ ዝም ብዬ ሳያት እኔን ትታ ወደአባዬ ፍቷን መለሰችና
"፣እሄው ልጆቼን የፀሀይ ብርሀን እስኪናፍቃቸው ድረስ አላላውስ ብለህ ተጭነህ ስታስጨንቃቸው በጭንቀት ብዛት የልጄን አይምሮ እንዲቃወስ አድርገከው አረፍክ " ብላ ስታፈጥበት
ደና ነኝ እማዬ ምንም የሆንኩት ነገር የለም አባንም እንደዛ ማለት የለብሽም አባ ልክ ነው ። በቃ ተራራቁ ተብሏል እንራራቅ ነው ያልኩት ቀለል አርጋችሁ እዩትና እሺ በሉኝ እናንተ አንድ ላይ ብሉ ለኔ ለብቻዬ ስጪኝ። ስል እህቴ ከነበረችበት ተነስታ •••
"ባክህ የሌለ ነገር እያወራህ አታጨናንቃቸው ተነስና እንብላ!" እያለች እጄን ይዛ ልትጎትተኝ ነው መሰለኝ ወደኔ ስትጠጋ
ከተቀመጥኩበት ተፈናጥሬ በመነሳት እንዳትጠጊኝ እህቴ ነግሬሻለሁ እንዳትጠጊኝ በቃ ስል አባም ግራ ተጋብቶ ተነስቶ ሲቆም
ተጠግቶ ሳይዘኝ ቤቱን ጥየላቸው ብን ብዬ ልጠፋ አሰብኩና እናቴ ልጄ አበደ ብላ እራሷን ከማጥፋት እንደማትመለስ ሳስበው ፈራሁ።
አንተም እንዳትጠጋኝ አባ በቃ ተረዱኝ አትጠጉኝ አልኩ አትጠጉኝ እያልኩ ወደ ክፍሌ በመግባት ከውስጥ ዘጋሁት።
በስንት ውዝግብ አሳምኛቸው ምግብ መስኮት ላይ እየተደረገልኝ በልቼ አጥቤ እየመለስኩ ስምንት ቀን ሆነኝ ። በዘጠነኛው ቀን ጥዋት ጋደኛዬ ደውሎ
የነ ሊሊ ቤተሰቦች በሽተኛ እቤት ውስጥ መኖሩ ተጠቁሞባቸው ቤተሰቡን በሙሉ አፋፍሰው ካስገባቸው ቡሀላ በምርመራ ሌሎቹ የቤተሰብ አባላት ላይም ስለተገኘ ያን ቀን የሊሊ ልደት ላይ የተገኙት በሙሉ እየታደኑ ወደማቆያ እየተወሰዱ ነው አሉ እኛ ጋም መምጣታቸው አይቀርም አልቆልናል ሶል!"
ሲለኝ እኔ እዛው በተኛሁበት አለቀልኝ ። የተኛሁበት በላብ ሲዘፈቅ ትዝ ይለኛል ካልጋዬ ላይ መነሳት አቃተኝ ካንድ ቀን ቡሀላ ብንን ስል መስኮት ላይ ያስቀመጡትን ምግብ ወስጄ አለመብላቴ ያስጨነቃቸው ቤተሰቦቼ እህቴን በመስኮት አዘልለው በማስገባትና ከውስጥ እንድትከፍት በማረግ አልጋዬ ላይ ዙሪያዬን ከበውኝ እስክነቃ በጭንቀት ሲጠባበቁ ተመለከትኩ ። በሂወቴ እንደዛች ቅፅበት መሪር ሀዘን እና የነብሰ ገዳይነት ስሜት ተሰምቶኝ አያውቅም ። እርርይ አልኩ።
በንጋታው ሁላችንንም ወደ ማቆያ ወሰዱን ከቀናት ቡሀላ የምርመራ ውጤቱ ሁላችንም እንዳለብን አመለከተ።
ውጤቱን ስሰማ በተለይ ቤተሰቦቼን በመሉ ማስያዜን ስሰማ ድጋሚ እራሴን ሳትኩ ከሳምንታት ቡሀላ ወደራሴ ስመለስ እና ስነቃ እቤታችን ውስጥ ነኝ።
ሶስታችን አገገምን አባዬ ግን ከመሀላችን
ጎድሏል ።
በነበረበት ስኳር እና ሌላ ተጓዳኝ ህመም ምክንያት በሽታውን መቋቋም አቅቶት በሀገራችን በዚህ በሽታ ከሞቱት ሰዎች መሀል አንዱ ሆነ ።
ይህ ሁሉ በኔ ነው በኔ የደረሰ በማንም አይድረስ!!
💫ተፈፀመ💫
እስቲ ሁላችሁም ይቺን ፅሁፍ በዚች ደቂቃ እያነበባችሁ ያላችሁ #ኮረና የመጣ ጊዜ #ጥንቃቂያችሁ እንዴት ነበር❓❓#አሁንስ❓❓ መልሱን ለራሳችሁ
ግን አሁንም በሽታው ምንም የተቀየረ ነገር የለም መድሃኒት አልተገኘለትም አሁንም የኛ ብቻ ሳይሆን የአለም ስጋት ነው። በየቤታችን እስኪገባ አንጠብቅ እናም ይሄ ታሪክ አንድ ሰው ያስተምራልና #Share እያደረጋቹ።
🛑አሁንም ግን🛑
#እርቀታችንን_እንጠብቅ
#ማክስ_በአግባቡ_እናድርግ
#እጃችንን_በአግባቡ_እንታጠብ
#ከቻልን_ቤት_እንቆይ #ውዶቼ
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
#አልወጣም_ተራራ
አልወጣም ተራራ
ደመናን ልዳብስ
ቀስተ ደመናውን፣ ሽቅብ ልቀለብስ
አልዋስም እኔ
ካ'ቡነ ተክሌ ክንፍ
ከያዕቆብ መሰላል
እኔ መውጣት ሳስብ
ሰማዩ ዝቅ ይላል፡፡
🔘በዕውቀቱ ሰዪም🔘
አልወጣም ተራራ
ደመናን ልዳብስ
ቀስተ ደመናውን፣ ሽቅብ ልቀለብስ
አልዋስም እኔ
ካ'ቡነ ተክሌ ክንፍ
ከያዕቆብ መሰላል
እኔ መውጣት ሳስብ
ሰማዩ ዝቅ ይላል፡፡
🔘በዕውቀቱ ሰዪም🔘
#ፍግ_ላይ_የበቀለች_አበባ
አበባዪቱም አለች፣
ፍግ ላይ የበቀለች
«ምንድን ነው ጥበቡ?»
ሄክታር ማጣፈጠ
አደይን ማስዋቡ፣
እኔም መለስኩላት፣
"ይብላኝ ለንብ እንጂ ዝንብማ ይተጋል
ከቆሻሻ ዓለም ውስጥ ጣ'ምን ይፈልጋል፡፡››
🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
አበባዪቱም አለች፣
ፍግ ላይ የበቀለች
«ምንድን ነው ጥበቡ?»
ሄክታር ማጣፈጠ
አደይን ማስዋቡ፣
እኔም መለስኩላት፣
"ይብላኝ ለንብ እንጂ ዝንብማ ይተጋል
ከቆሻሻ ዓለም ውስጥ ጣ'ምን ይፈልጋል፡፡››
🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘