#አቀበት
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በገበየሁ_አየለ
አካሌ ቀድሞ ከነበሩበት ፈረንሳይ ለጋስዮን፣ አሁን ወዳሉበት ቶሎሣ ሰፈር ከተዛወሩ አንድ ዓመት ቢሆናቸውም፣ ከአካባቢውም ሆነ ከቅርብ ጎረቤቶቻቸው
ጋር መላመዱ አልሆነላቸውም፡፡ ዓይናፋርና ሽቁጥቁጥ ናቸው፣ ቶሎ ሰው የማይቀርቡ፡፡ የቀድሞ መኖሪያቸውን
የቀየሩት፣ ቀዳሚና ተከታይ ያልነበራት ልጃቸው ሸዋዬ ስትሞትባቸው ነው። ባላቸው በአፍላ ዕድሜ በድንገተኛ
ህመም ስለሞቱባቸው እናትም አባትም ሆነው ነበር ሸዋዬን ያሳደጓት በኋላም የዳሯት፡፡
ሸዋዬና መምህሩ ባሏ ተካ ትዳራቸውን ለማደላደል ሌተ ቀን ይጥሩ ጀመር፡፡ በተጋቡ በዓመቱ ሴት ልጅ ወለዱ። በሸዋዬ መውለድ እጅግ የተደሰቱት፣ ከባልና ሚስቱ ይልቅ አካሌ ናቸው:: ሕጻኗን ከእቅፋቸው አላወጣት አሉ: በኋላም ውሎና አዳራቸው በአብዛኛው
እዚያው ሆነ፡፡ የዚህ ምክንያቱ፡፡ በፊት በፊት የህጻኗ ፍቅር ቢሆንም፣ በኋላ ግን የሸዋዩ ሕመም ነበር።ከዛሬ ነገ ይሻላታል ቢባል፣ ከሆስፒታል ሆስፒታል ቢያንከራትቷት፣ የሚፈውሳት መድኃኒት ታጣ፡፡ የኋላ ኋላ ሀኪሞቹ በሽታዋ የማይድን መሆኑን ገልጠው"ሸዋዬ ሕጻኗን ጡት እንዳታጠባት" በማለት አስጠነቀቁ።
በዚህ ሁኔታ የሸዋዬ በሽታ ከዕለት ወደ ዕለት እየከፋ ሄደና በዓመት ከመንፈቋ ሞተች፡፡ እሷ ባሞተች በሳልስቱ ባሏ ተካ የሚሄድበትን ሳይናገር ተሰወረ::በሽዋዬ ሞት ቅስማቸው የተሰበረው አካሌ ክፉኛ
ደነገጠ:: በከባዱ ሀዘናቸው ላይ እናትና አባት የሌላትን ሕጻን የማሳደጉ ኃላፊነት ተጨመረ፡፡ዙሪያው ገደል ሆነባቸው:: "ይሁን፣ ተመስገን፣ ሸዋዬ ምትኳን ትታልኝ
ነው የሞተችው:: ህጻኗ በዕድሏ ታድጋለች" እንዳይሉ፣
"ሸዋዬን የገደላት ክፉ ደዌ ወደ ልጅዋም ይተላለፋል" ማለትን ስለሰሙ ተስፋቸው ይበልጥ ጨለመ።
ያኔ ነው የአሁኗ ቡና አጣጭ ጎደኛቸው ወይዘሮ ብርቄ ህፃኗን እናስመርምራት
እንደሚባለው ሊሆንም ላይሆንም ይችላል እኮ ያሏቸው:: እንዳሉት አደረጉ፣
ህጻኗ ከደዌው ነጻ ነች ተባለ፡፡ ይህ ለአካሌ ታላቅ የምስራች ነበር፡፡ "ተመስገን አምላኬ የዓይን ማረፊያ አልነሳኸኝም፣ የሀዘኔን ማስረሻ ሰጥተኸኛል" አሉ፡፡
ህጻኗንም ማስረሻ ብለው ጠሯት፡፡
የአካሌ ጓደኛ ወይዘሮ ብርቄ ትንሽ ዘግየት ብለው ደግሞ ሌላ ምክር አመጡ፡፡ "ሸዋዬ እሞተችበት ሆስፒታል እንሂድና የሞቷን ምክንያት የሚገልጥ ወረቀት ስጡን እንበላቸው:: የሞተችበት በሽታ እርዳታ የሚያስገኝ ሆኗል።ወረቀቱ ከተገኘ ህጻኗን ይዘው ወደ እርዳታ ለጋሾቹ በመቅረብ 'ወላጆቿን አጥታለች::ደካማ አሮጊት ነኝ፣ እልሰው እቀምሰው የሌለኝ ይበሉ፡፡በደንብ ይረዱዎታል :: ማንም አይደለም እንዴ የሚረዳው? ዛሬ በአዲሱ በሽታ ዘመድ የሚሞትበት ድሀ እርዳታ ይገኛል! ነባሮቹ በሽታዎቻችን እንዲህ ከእርዳታ ጋር ቢመጡ ኖሮ ደግ ነበር፣ 'የቸገረው ዱቄት ከንፋስ ይዛመዳል ማለትኮ ውነትነት አለው' አሉ
ዓይኖቻቸውን እያሻሹ::
አካሌ በብርቄ ምክርና አይዞሽ ባይነት እየተበረታቱ በየቢሮው ብዙ ከተንከራተቱ በኋላ ተሳካላቸውና በኤድስ
ህመም ወላጆቿን ያጣች ህጻን አሳዳጊ በመባል ከበጎ አድራጊ ድርጅቶች እርዳታ ያገኙ ጀመር፡፡የማስረሻን አባት፣ የተካን መሰወር አስመልከተው ሰዎች ብዙ መላምት አወሩ፣ "ሚስቱን የገደላት በሽታ
እሱንም የያዘው መሆኑን ስላወቀ እራሱን ገድሏል፣ገዳም ገብቶ ነው፣ እማይታወቅበት ስፍራ ሄዶ ኑሮውን
እዚያው መስርቷል. .አሉ፡፡
እንዲህ ያለ ብዙ ነገር ከተወራበትና ከተረሳ ከ 6 ወር በኋላ ተካ አንድ ቀን ብቅ አለ።
የቅርብ ጎረቤቶቹ በመገረምም፣ በሀዘኔታም፣ "እንኳን ደህና መጣህ" እያሉ ሲቀባበሉት፣ አካሌ ግን "ዓይኑን
አላየውም" አሉ ክፉኛ ተቀይመውት፡፡ ከዚያም ይልቅ ከተረሳና እንደሞተ ከተቆጠረ በኋላ መምጣቱ ለመልካም
አለመሆኑ ተሰማቸው:: "ያሰበው ደባ ቢኖር ነው" ብለው
ክፉኛ ሰጉ፡፡ በመሆኑም አማላጆች ቢለምኗቸው፣ ቢማጠኗቸው "ከኔ ጋር አይኖራትም!" አሉ።
በአማላጅነት አልሆንልህ ያለው ተካ፣ አካሌን የቀበሌ ሹሞች ዘንድ ከሰሳቸው:: ሹሞቹ የሁለቱንም ክርክር ካዳመጡ በኋላ፣ "ጠፍቶ ቢከርምም፣ የቤቱ
ተከራይ እሱ ነው፣ አብሮኝ አይኖርም፣ አጠገቤ አይድረስ ካሉ የቤቱ መሀል በር ታሽጎ ሁለት ላይ ይከፈልና
በተለያየ በርና አቅጣጫ እየተገለገላችሁ ለየብቻ መኖር አለባችሁ" በማለት ወሰኑ፡፡
በዚሁ መሠረት በግድግዳ የተለያዩ ደባሎች ሆነው አንድ ሳምንት ያህል እንደቆዩ፣ ተካ እንደገና አካሌን
ከሰሰና ሹሞቹ ዘንድ አቀረባቸው::
አንድ ቀን አመሻሹ ላይ አካሌ እንደ ሁልጊዜያቸው ቡና አፈሉና ብርቄን ጠሯቸው።ሥጋትና ፍርሃታቸውን ሊያወያዩዋቸው አስበዋል፡፡
"ይሄን ሰውዬ ፈራሁት" አሉ አካሌ የቀዱትን አቦል ቡና ለብርቄ እየሰጧቸው፡፡
የቀይ ዳማ ፊታቸው እንደለበሱት የሀዘን ልብስ ጠቁሯል።
"ተካን ማለትዎ ነው?" አሉ ብርቄ ትንንሽ
ዓይኖቻቸውን አፍጠው።
«አዎን» በረጅሙ ተነፈሱ አካሌ፡፡
ከእንግዲህ የሚያገናኛችሁ በር ታሽጓል» አሉ ሽበታቸውን በእንዝርታቸው ጫፍ እያከኩ።
"ያ ከምን ያግደዋል ብርቄ ? ይህችን ልጅ
ለመውሰድ ሲል እሽጉን በር ሰብሮ በመግባት ቢገድለኝስ? ምኑ ይታመናል? የት ከርሞ እንደመጣ፣ ወዴትስ እንደሚሄድ ማን ያውቃል?"
"ዛሬ ከተካ ጋር አካባቢው ሹሞች ዘንድ
የቀረባችሁት ለምን ነበር?" አሉ ብርቄ
"ከሶኝ ነዋ ልጄን ትስጠኝ ብሎ::"
"ማስረሻን?"
አካሌ በአዎንታ እራሳቸውን ነቀነቁና በማቃሰት ተነፈሱ፡፡
"ማስረሻ ልውሰዳት ማለቱ እንዴት ሊያሳድጋት ነው? ምን ሊያበላት? ለራሱ ይቀምሰው ይልሰው የለው:: አባይ ማደሪያ የለው ግንድ ይዞ ይዞራል' አሉ፡፡"
"ምን አውቄለት፡፡" አሉ አካሌ ማስረሻ ወደተኛችበት ቦታ አልጋ አንጋጠው እየተመለከቱ፡፡
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በገበየሁ_አየለ
አካሌ ቀድሞ ከነበሩበት ፈረንሳይ ለጋስዮን፣ አሁን ወዳሉበት ቶሎሣ ሰፈር ከተዛወሩ አንድ ዓመት ቢሆናቸውም፣ ከአካባቢውም ሆነ ከቅርብ ጎረቤቶቻቸው
ጋር መላመዱ አልሆነላቸውም፡፡ ዓይናፋርና ሽቁጥቁጥ ናቸው፣ ቶሎ ሰው የማይቀርቡ፡፡ የቀድሞ መኖሪያቸውን
የቀየሩት፣ ቀዳሚና ተከታይ ያልነበራት ልጃቸው ሸዋዬ ስትሞትባቸው ነው። ባላቸው በአፍላ ዕድሜ በድንገተኛ
ህመም ስለሞቱባቸው እናትም አባትም ሆነው ነበር ሸዋዬን ያሳደጓት በኋላም የዳሯት፡፡
ሸዋዬና መምህሩ ባሏ ተካ ትዳራቸውን ለማደላደል ሌተ ቀን ይጥሩ ጀመር፡፡ በተጋቡ በዓመቱ ሴት ልጅ ወለዱ። በሸዋዬ መውለድ እጅግ የተደሰቱት፣ ከባልና ሚስቱ ይልቅ አካሌ ናቸው:: ሕጻኗን ከእቅፋቸው አላወጣት አሉ: በኋላም ውሎና አዳራቸው በአብዛኛው
እዚያው ሆነ፡፡ የዚህ ምክንያቱ፡፡ በፊት በፊት የህጻኗ ፍቅር ቢሆንም፣ በኋላ ግን የሸዋዩ ሕመም ነበር።ከዛሬ ነገ ይሻላታል ቢባል፣ ከሆስፒታል ሆስፒታል ቢያንከራትቷት፣ የሚፈውሳት መድኃኒት ታጣ፡፡ የኋላ ኋላ ሀኪሞቹ በሽታዋ የማይድን መሆኑን ገልጠው"ሸዋዬ ሕጻኗን ጡት እንዳታጠባት" በማለት አስጠነቀቁ።
በዚህ ሁኔታ የሸዋዬ በሽታ ከዕለት ወደ ዕለት እየከፋ ሄደና በዓመት ከመንፈቋ ሞተች፡፡ እሷ ባሞተች በሳልስቱ ባሏ ተካ የሚሄድበትን ሳይናገር ተሰወረ::በሽዋዬ ሞት ቅስማቸው የተሰበረው አካሌ ክፉኛ
ደነገጠ:: በከባዱ ሀዘናቸው ላይ እናትና አባት የሌላትን ሕጻን የማሳደጉ ኃላፊነት ተጨመረ፡፡ዙሪያው ገደል ሆነባቸው:: "ይሁን፣ ተመስገን፣ ሸዋዬ ምትኳን ትታልኝ
ነው የሞተችው:: ህጻኗ በዕድሏ ታድጋለች" እንዳይሉ፣
"ሸዋዬን የገደላት ክፉ ደዌ ወደ ልጅዋም ይተላለፋል" ማለትን ስለሰሙ ተስፋቸው ይበልጥ ጨለመ።
ያኔ ነው የአሁኗ ቡና አጣጭ ጎደኛቸው ወይዘሮ ብርቄ ህፃኗን እናስመርምራት
እንደሚባለው ሊሆንም ላይሆንም ይችላል እኮ ያሏቸው:: እንዳሉት አደረጉ፣
ህጻኗ ከደዌው ነጻ ነች ተባለ፡፡ ይህ ለአካሌ ታላቅ የምስራች ነበር፡፡ "ተመስገን አምላኬ የዓይን ማረፊያ አልነሳኸኝም፣ የሀዘኔን ማስረሻ ሰጥተኸኛል" አሉ፡፡
ህጻኗንም ማስረሻ ብለው ጠሯት፡፡
የአካሌ ጓደኛ ወይዘሮ ብርቄ ትንሽ ዘግየት ብለው ደግሞ ሌላ ምክር አመጡ፡፡ "ሸዋዬ እሞተችበት ሆስፒታል እንሂድና የሞቷን ምክንያት የሚገልጥ ወረቀት ስጡን እንበላቸው:: የሞተችበት በሽታ እርዳታ የሚያስገኝ ሆኗል።ወረቀቱ ከተገኘ ህጻኗን ይዘው ወደ እርዳታ ለጋሾቹ በመቅረብ 'ወላጆቿን አጥታለች::ደካማ አሮጊት ነኝ፣ እልሰው እቀምሰው የሌለኝ ይበሉ፡፡በደንብ ይረዱዎታል :: ማንም አይደለም እንዴ የሚረዳው? ዛሬ በአዲሱ በሽታ ዘመድ የሚሞትበት ድሀ እርዳታ ይገኛል! ነባሮቹ በሽታዎቻችን እንዲህ ከእርዳታ ጋር ቢመጡ ኖሮ ደግ ነበር፣ 'የቸገረው ዱቄት ከንፋስ ይዛመዳል ማለትኮ ውነትነት አለው' አሉ
ዓይኖቻቸውን እያሻሹ::
አካሌ በብርቄ ምክርና አይዞሽ ባይነት እየተበረታቱ በየቢሮው ብዙ ከተንከራተቱ በኋላ ተሳካላቸውና በኤድስ
ህመም ወላጆቿን ያጣች ህጻን አሳዳጊ በመባል ከበጎ አድራጊ ድርጅቶች እርዳታ ያገኙ ጀመር፡፡የማስረሻን አባት፣ የተካን መሰወር አስመልከተው ሰዎች ብዙ መላምት አወሩ፣ "ሚስቱን የገደላት በሽታ
እሱንም የያዘው መሆኑን ስላወቀ እራሱን ገድሏል፣ገዳም ገብቶ ነው፣ እማይታወቅበት ስፍራ ሄዶ ኑሮውን
እዚያው መስርቷል. .አሉ፡፡
እንዲህ ያለ ብዙ ነገር ከተወራበትና ከተረሳ ከ 6 ወር በኋላ ተካ አንድ ቀን ብቅ አለ።
የቅርብ ጎረቤቶቹ በመገረምም፣ በሀዘኔታም፣ "እንኳን ደህና መጣህ" እያሉ ሲቀባበሉት፣ አካሌ ግን "ዓይኑን
አላየውም" አሉ ክፉኛ ተቀይመውት፡፡ ከዚያም ይልቅ ከተረሳና እንደሞተ ከተቆጠረ በኋላ መምጣቱ ለመልካም
አለመሆኑ ተሰማቸው:: "ያሰበው ደባ ቢኖር ነው" ብለው
ክፉኛ ሰጉ፡፡ በመሆኑም አማላጆች ቢለምኗቸው፣ ቢማጠኗቸው "ከኔ ጋር አይኖራትም!" አሉ።
በአማላጅነት አልሆንልህ ያለው ተካ፣ አካሌን የቀበሌ ሹሞች ዘንድ ከሰሳቸው:: ሹሞቹ የሁለቱንም ክርክር ካዳመጡ በኋላ፣ "ጠፍቶ ቢከርምም፣ የቤቱ
ተከራይ እሱ ነው፣ አብሮኝ አይኖርም፣ አጠገቤ አይድረስ ካሉ የቤቱ መሀል በር ታሽጎ ሁለት ላይ ይከፈልና
በተለያየ በርና አቅጣጫ እየተገለገላችሁ ለየብቻ መኖር አለባችሁ" በማለት ወሰኑ፡፡
በዚሁ መሠረት በግድግዳ የተለያዩ ደባሎች ሆነው አንድ ሳምንት ያህል እንደቆዩ፣ ተካ እንደገና አካሌን
ከሰሰና ሹሞቹ ዘንድ አቀረባቸው::
አንድ ቀን አመሻሹ ላይ አካሌ እንደ ሁልጊዜያቸው ቡና አፈሉና ብርቄን ጠሯቸው።ሥጋትና ፍርሃታቸውን ሊያወያዩዋቸው አስበዋል፡፡
"ይሄን ሰውዬ ፈራሁት" አሉ አካሌ የቀዱትን አቦል ቡና ለብርቄ እየሰጧቸው፡፡
የቀይ ዳማ ፊታቸው እንደለበሱት የሀዘን ልብስ ጠቁሯል።
"ተካን ማለትዎ ነው?" አሉ ብርቄ ትንንሽ
ዓይኖቻቸውን አፍጠው።
«አዎን» በረጅሙ ተነፈሱ አካሌ፡፡
ከእንግዲህ የሚያገናኛችሁ በር ታሽጓል» አሉ ሽበታቸውን በእንዝርታቸው ጫፍ እያከኩ።
"ያ ከምን ያግደዋል ብርቄ ? ይህችን ልጅ
ለመውሰድ ሲል እሽጉን በር ሰብሮ በመግባት ቢገድለኝስ? ምኑ ይታመናል? የት ከርሞ እንደመጣ፣ ወዴትስ እንደሚሄድ ማን ያውቃል?"
"ዛሬ ከተካ ጋር አካባቢው ሹሞች ዘንድ
የቀረባችሁት ለምን ነበር?" አሉ ብርቄ
"ከሶኝ ነዋ ልጄን ትስጠኝ ብሎ::"
"ማስረሻን?"
አካሌ በአዎንታ እራሳቸውን ነቀነቁና በማቃሰት ተነፈሱ፡፡
"ማስረሻ ልውሰዳት ማለቱ እንዴት ሊያሳድጋት ነው? ምን ሊያበላት? ለራሱ ይቀምሰው ይልሰው የለው:: አባይ ማደሪያ የለው ግንድ ይዞ ይዞራል' አሉ፡፡"
"ምን አውቄለት፡፡" አሉ አካሌ ማስረሻ ወደተኛችበት ቦታ አልጋ አንጋጠው እየተመለከቱ፡፡
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍4
#መልክአ_ሕይወት
ቧልትን ከፈገግታ
ሣቅን ከፌዝ ጋር
ባ'ንድ ላይ ቀይጠን
አቅልመን በጥብጠን
በሐዘን በሃር ላይ፣ብናቆረቁርም
ባሕሩ ሰፊ ነው፣መልኩን አይቀይርም
🔘በእውቀቱ ስዩም🔘
ቧልትን ከፈገግታ
ሣቅን ከፌዝ ጋር
ባ'ንድ ላይ ቀይጠን
አቅልመን በጥብጠን
በሐዘን በሃር ላይ፣ብናቆረቁርም
ባሕሩ ሰፊ ነው፣መልኩን አይቀይርም
🔘በእውቀቱ ስዩም🔘
#ሲታነፅ_ሲወቀር
እኔም አንድ ሰሞን
ልክ እንደ ሰሎሞን
“ሁሉም ከንቱ ከንቱ ነፋስን መከተል”
ሳይጥሉ መታገል፣ ሳይከብሩ መባተል
እያልሁ አጨልሜ
በራሴ ለግሜ
እፈላሰፍ ነበር።
ከዚያ አንቺን አገኘሁ
በጓሮ በር በኩል፣ ሰሎሞኔን ሸኘሁ
መፈጠሬን ወደድሁ
ነፋስ አሳድጄ
እንደ ቆቅ አጠመድሁ
ከፀሐይዋ በቻት፣ ግልገል ፀሐይ ፈጠርሁ
ለኦናው አምፖሌ፣ ብርሃን አበደርሁ
ማቅ የነበረው ጨርቅ፣ ሸማ ሆኖ ቆየኝ
ከንቱ የነበረው፣ አንቱ ሆኖ ታየኝ።
ለካስ
ጠቢብ ቢያስተምረው፣ መከራ ቢመክረው
አካሉና ልቡ ቢታነፅ፣ ቢወቀር
ሰው አቅሙን አያውቅም፣ ካልወደደ በቀር።
🔘በውቀቱ ስዩም🔘
እኔም አንድ ሰሞን
ልክ እንደ ሰሎሞን
“ሁሉም ከንቱ ከንቱ ነፋስን መከተል”
ሳይጥሉ መታገል፣ ሳይከብሩ መባተል
እያልሁ አጨልሜ
በራሴ ለግሜ
እፈላሰፍ ነበር።
ከዚያ አንቺን አገኘሁ
በጓሮ በር በኩል፣ ሰሎሞኔን ሸኘሁ
መፈጠሬን ወደድሁ
ነፋስ አሳድጄ
እንደ ቆቅ አጠመድሁ
ከፀሐይዋ በቻት፣ ግልገል ፀሐይ ፈጠርሁ
ለኦናው አምፖሌ፣ ብርሃን አበደርሁ
ማቅ የነበረው ጨርቅ፣ ሸማ ሆኖ ቆየኝ
ከንቱ የነበረው፣ አንቱ ሆኖ ታየኝ።
ለካስ
ጠቢብ ቢያስተምረው፣ መከራ ቢመክረው
አካሉና ልቡ ቢታነፅ፣ ቢወቀር
ሰው አቅሙን አያውቅም፣ ካልወደደ በቀር።
🔘በውቀቱ ስዩም🔘
#አቀበት
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#በገበየሁ_አየለ
"ምን አሉት ታዲያ ሹሞቹ?"
"ትሰጭዋለሽ ወይ ብለው ጠየቁኝ፡፡
አላደርገውም ብዬ ክፉኛ ስከራከራቸው ጊዜ ፍርድ ቤት ሂድና ክሰሳት፣ ይህን የመሰለውን ጉዳይ መበየን የኛ ስልጣን አይደለም" አለት።
"እሰይ፡ ይሂድና ይክሰስዎት፣ ያኔ ደግሞ አንድዬ ያውቅሉሃል::"
"ኧረ እሱ እስከዚያውም የሚታገስ አይመስል ክፉኛ ነው የፎከረብኝ::"
ብርቄ ፡ "ልጅቱን አላሳይ ስላሉት ነው ልውሰዳት ማለቱ።ምናለበት ብቅ እያለ እንዲያያት ቢፈቅዱለት?"ለማለት አሰቡና ተውት።አካሌ በግልጽ አይናገሩት
እንጂ ተካ ከማስረሻ ጋር እንዳይቀራረብ አጥብቀው የሚከላከሉት ከሷ ይለየኛል ብለው ብቻ ሳይሆን እሱ ከወሰዳት በሷ ምክንያት የማገኘው እርዳታ ይቀርብኛል
በሚል ሥጋት ጭምር መሆኑን ተረድተዋል፡፡
ሁለቱም የየራሳቸውን አሳብ ሲያሰላስሉ ሳለ ብርቄ ጉሮሯቸውን ሞረዱና "የሰፈሩ ሰዎች ናቸው ተካን ክፉ የሚመክሩት፡፡ መከራ ሰውን ዓመለኛ ያደርገዋል እንጂ
ተካ ደግ ሰው ነበር" አሉ።
"መክረውት ይሆናል ብዬ እኔም እጠራጠራለሁ::ቢያደርጉትም አያፈረድባቸውም፡ አብሯቸው የኖረ እሱ፡
እኔን የት ያውቁኛል፡፡" አለ አካሌ ማስረሻን ከአልጋ ላይ አንስተው እያቀፏት::
መከራም ያልፋል::" አሉ የማስረሻን ፀጉር እያሻሹ::
"ሰው ቢመክርና ቢመቀኝ ምን ሊያመጣ የማታ እንጀራ ያልነፈገዎ ፈጣሪ ያውቅሉሀል::" አሉ ብርቄ
ትንሽ አሰብ አደረጉና ደግሞ እኔም አለሁ
በደከሙ ዓይኖቼ እየተጨናበስኩና እየፈተልኩ ልቃቂት ሽጨ አዳሪዋ፣ ፈጣሪ ቢያድለኝና ሁለቱ ልጆቼ በሕይወት
ቢኖሩልኝ ኑሮ ያሳርፉኝ ነበር::"
“ሁለት ብቻ ነበር የወለዱት? "
"አዎን ሁለት ብቻ ነበሩ፡: ደረሱልኝ ሊያሳርፉኝ ነው እያልኩ ዓይን ዓይናቸውን በጉጉት ስመለከት ሳለሁ ድንገት ብድግ ብለው ለናት አገራችን ካልሞትን አሉ፡፡
ተው ልጆቼ እኔን ለማን ጥላችሁ ነው የምትሞቱ፡ከመኖራችሁ እንጂ ከሞታችሁ ምን እጠቀማለሁ የምትገዳደሉትኮ ያንድ እናት ልጆች ናችሁ::' ብላቸው
አልሰማሽ አሉ:: ፀባቸውን ከቤት ጀመሩት:: ከመገዳደል ሌላ የፀብ ማብረጃ መንገድ አልታይ አላቸው:: አንደኛው የመንግሥት ሆነ ሌላው ከመንግሥት ጋር ከሚጣላው
ወገን ነበረ፡፡ እየተዛዛቱና እየተጣደፉ ወደሞታቸው ሮጡ:: እንዳሉትም ተገዳደሉና እኔን የወላድ መካን
አደረጉኝ:: ማን የት እንደወደቀ እንኳን የሚነግረኝ አላገኘሁም::" ብለው እንባቸውን በነጠላቸው ጫፍ እየጠራረጉ "ፎቶግራፋቸውን አቅፌ ቀረሁ” አሉ፡፡ አካሌም እንባ ያጤዙ አይኖቻቸውን ጠራረጉና፣" አይዘኑ፣ እስከዛሬ ያኖረዎ እግዚአብሄር ያውቅልዎታል፡ ሀዘንም ይረሳል፡መከራም ያልፋል::" አሉ የማስረሻን ፀጉር እያሻሹ::
በዚህ ሁኔታ ሲወያዩ ካመሹ በኋላ ብርቄ ወደ ቤታቸው ለመሄድ በላስቲክ ከረጢት የያዙትን ጥጥ እንዝርት ያስተካክሉ ጀመር፡፡
"እንግዲህ ያድምጡኝ ተካ ዛሬ ክፉኛ ነው
የዛተብኝ:: ከተተናኮለኝ መጮሄ አይቀርም::" አሉ ኣካሌ ጓደኛቸውን ለመሸኘት ብድግ እያሉ፡፡ "አይዝዎት፣
እንኳን ከዛቻ ከተወረወረም የሚያድን አምላክ ይጠብቅዎታል" አሉ ብርቄ ዓይኖቻቸውን ወደጣራው
አቅንተው።
አካሌ ብርቄን ከሸኙአቸው በኋላ ማስረሻን በነጠላቸው ጥብቅ አድርገው አዘሏትና የምሽት ተግባራቸውን ለማጠናቀቅ ጉድ ጉድ ይሉ ጀመር፡፡ ተካ
ከመጣ ወዲህ ሲንቀሳቀሱም ሆነ ሲቀመጡ ማስረሻ እንዳትለያቸው ወስነዋል፣ አካሏ ከአካላቸው ትንፋሽዋ
ከትንፋሻቸው እንዳይርቅ::በራቸውን ከወትሮው ይልቅ ጠበቅብቅ አድርገው
ዘጉት:: ተካ ያመጣብኛል ብለው የፈሩት ችግር ከደቂቃ ደቀቃ ከሰዓት ወደ ሰዓት ያሳስባቸው ጀመር፡፡
"የሚያደርገውን ያድርግ እንግዲህ ምነው ኣካለወርቅ የሚሆነው ከመሆኑ በፊት በፍርሃት አልሞትም::" አሉ
ለራሳቸው::
እንዲህ እራሳቸውን ለማጎበዝ ይሞክሩ እንጂ ምሽቱ፡እየገፋ በሄደ ቁጥር ብርታታቸው መናዱ ኣልቀረም።
ማስረሻን አልጋቸው ላይ እስተኙዋትና፣ ቆም ብለው ወደ ተካ ክፍል ያስገባ የነበረውን እሽግ በር በጥርጣሬ
ተመለከቱት፣ የተካ ኣቋራጭ ማጥቂያ በዚያ እንደሚሆን እርግጠኛ ናቸው።
አሮጌ መጥረብያቸውን ከስርቻ ፈልገው ያዙና በእድሜ የላላ የእጅ ጡንቻቸውን ፈርጠም አድርገው ለጥቂት ጊዜ ወደ እሽጉ በር ካፈጠጠ በኋላ። እራስጌያቸው አስቀመጡት::
እንዲህ በማድረግ ላይ ሳሉ ነው ድንገት ተካ ክፍል ውስጥ የእርምጃና የእንቅስቃሴ ድምጽ የሰሙት::ወዲያውኑ የልባቸው አመታት ስለፈጠነባቸው
ደረታቸውን በሁለት እጆቻቸው ያዙና "እንዴ!" አሉ በሹክሽኩታ:: ተካ ከወትሮው ቀደም ብሎ መምጣቱ
ይበልጥ አስደነገጣቸው በፀጥታ አዳመጠ:: እያገሣ ያንጎራጉር ጀመር፡፡ ሞቅ ብሎት ሲመጣ የሚያደርገው
ልምድ ነው:: አካሌ ከአስፈሪ አውሬ ጋር የተፋጠጡ ይመስል እቆሙበት ተተክለው ቀሩ፡፡
"ዝግጅቱን በጊዜ ለመጀመር ነው ቀደም ብሎ የመጣው" አሉ በአሳባቸው:: የተካ እንጉርጉሮ ብዙም አልቆየ ሰው የሌለበት እስኪመስል ድረስ ክፍሉን ፀጥታ ዋጠው
አካሌ ለአስር ደቂቃ ያህል በዝምታ ካዳመጡ በኋላ፡ ቀስ ብለው አልጋቸው ጠርዝ ላይ ቁጭ አሉ።
እንደገና ለአምስት ደቂቃ ያህል አዳመጡ ከማስረሻ የእንቅልፍ ልብ አተነፋፈስና ከራሳቸው ልብ ምት ሌላ የሚሰማ ነገር የለም አይኖቻቸውን እሽጉ በር ላይ እንደተከሉ እራስጊያቸው ያለውን መጥረቢያ በዳበሳ አነሱና ጠበቅ አድርገው ያዙት:: እንደገና ጥቂት
ካዳመጡ በኋላ፣ "መተኛቴን ነው የሚያዳምጠው"አሉና ጉሮሯቸውን በመሞረድ ያለማንቀላፋታቸውን
የሚያመለክት ድምጽ አሰሙ:: ቀጥለው ደግሞ በያዙት መጥረቢያ ዛቢያ ወለላቸውን መታ መታ አደረጉት።.....
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#በገበየሁ_አየለ
"ምን አሉት ታዲያ ሹሞቹ?"
"ትሰጭዋለሽ ወይ ብለው ጠየቁኝ፡፡
አላደርገውም ብዬ ክፉኛ ስከራከራቸው ጊዜ ፍርድ ቤት ሂድና ክሰሳት፣ ይህን የመሰለውን ጉዳይ መበየን የኛ ስልጣን አይደለም" አለት።
"እሰይ፡ ይሂድና ይክሰስዎት፣ ያኔ ደግሞ አንድዬ ያውቅሉሃል::"
"ኧረ እሱ እስከዚያውም የሚታገስ አይመስል ክፉኛ ነው የፎከረብኝ::"
ብርቄ ፡ "ልጅቱን አላሳይ ስላሉት ነው ልውሰዳት ማለቱ።ምናለበት ብቅ እያለ እንዲያያት ቢፈቅዱለት?"ለማለት አሰቡና ተውት።አካሌ በግልጽ አይናገሩት
እንጂ ተካ ከማስረሻ ጋር እንዳይቀራረብ አጥብቀው የሚከላከሉት ከሷ ይለየኛል ብለው ብቻ ሳይሆን እሱ ከወሰዳት በሷ ምክንያት የማገኘው እርዳታ ይቀርብኛል
በሚል ሥጋት ጭምር መሆኑን ተረድተዋል፡፡
ሁለቱም የየራሳቸውን አሳብ ሲያሰላስሉ ሳለ ብርቄ ጉሮሯቸውን ሞረዱና "የሰፈሩ ሰዎች ናቸው ተካን ክፉ የሚመክሩት፡፡ መከራ ሰውን ዓመለኛ ያደርገዋል እንጂ
ተካ ደግ ሰው ነበር" አሉ።
"መክረውት ይሆናል ብዬ እኔም እጠራጠራለሁ::ቢያደርጉትም አያፈረድባቸውም፡ አብሯቸው የኖረ እሱ፡
እኔን የት ያውቁኛል፡፡" አለ አካሌ ማስረሻን ከአልጋ ላይ አንስተው እያቀፏት::
መከራም ያልፋል::" አሉ የማስረሻን ፀጉር እያሻሹ::
"ሰው ቢመክርና ቢመቀኝ ምን ሊያመጣ የማታ እንጀራ ያልነፈገዎ ፈጣሪ ያውቅሉሀል::" አሉ ብርቄ
ትንሽ አሰብ አደረጉና ደግሞ እኔም አለሁ
በደከሙ ዓይኖቼ እየተጨናበስኩና እየፈተልኩ ልቃቂት ሽጨ አዳሪዋ፣ ፈጣሪ ቢያድለኝና ሁለቱ ልጆቼ በሕይወት
ቢኖሩልኝ ኑሮ ያሳርፉኝ ነበር::"
“ሁለት ብቻ ነበር የወለዱት? "
"አዎን ሁለት ብቻ ነበሩ፡: ደረሱልኝ ሊያሳርፉኝ ነው እያልኩ ዓይን ዓይናቸውን በጉጉት ስመለከት ሳለሁ ድንገት ብድግ ብለው ለናት አገራችን ካልሞትን አሉ፡፡
ተው ልጆቼ እኔን ለማን ጥላችሁ ነው የምትሞቱ፡ከመኖራችሁ እንጂ ከሞታችሁ ምን እጠቀማለሁ የምትገዳደሉትኮ ያንድ እናት ልጆች ናችሁ::' ብላቸው
አልሰማሽ አሉ:: ፀባቸውን ከቤት ጀመሩት:: ከመገዳደል ሌላ የፀብ ማብረጃ መንገድ አልታይ አላቸው:: አንደኛው የመንግሥት ሆነ ሌላው ከመንግሥት ጋር ከሚጣላው
ወገን ነበረ፡፡ እየተዛዛቱና እየተጣደፉ ወደሞታቸው ሮጡ:: እንዳሉትም ተገዳደሉና እኔን የወላድ መካን
አደረጉኝ:: ማን የት እንደወደቀ እንኳን የሚነግረኝ አላገኘሁም::" ብለው እንባቸውን በነጠላቸው ጫፍ እየጠራረጉ "ፎቶግራፋቸውን አቅፌ ቀረሁ” አሉ፡፡ አካሌም እንባ ያጤዙ አይኖቻቸውን ጠራረጉና፣" አይዘኑ፣ እስከዛሬ ያኖረዎ እግዚአብሄር ያውቅልዎታል፡ ሀዘንም ይረሳል፡መከራም ያልፋል::" አሉ የማስረሻን ፀጉር እያሻሹ::
በዚህ ሁኔታ ሲወያዩ ካመሹ በኋላ ብርቄ ወደ ቤታቸው ለመሄድ በላስቲክ ከረጢት የያዙትን ጥጥ እንዝርት ያስተካክሉ ጀመር፡፡
"እንግዲህ ያድምጡኝ ተካ ዛሬ ክፉኛ ነው
የዛተብኝ:: ከተተናኮለኝ መጮሄ አይቀርም::" አሉ ኣካሌ ጓደኛቸውን ለመሸኘት ብድግ እያሉ፡፡ "አይዝዎት፣
እንኳን ከዛቻ ከተወረወረም የሚያድን አምላክ ይጠብቅዎታል" አሉ ብርቄ ዓይኖቻቸውን ወደጣራው
አቅንተው።
አካሌ ብርቄን ከሸኙአቸው በኋላ ማስረሻን በነጠላቸው ጥብቅ አድርገው አዘሏትና የምሽት ተግባራቸውን ለማጠናቀቅ ጉድ ጉድ ይሉ ጀመር፡፡ ተካ
ከመጣ ወዲህ ሲንቀሳቀሱም ሆነ ሲቀመጡ ማስረሻ እንዳትለያቸው ወስነዋል፣ አካሏ ከአካላቸው ትንፋሽዋ
ከትንፋሻቸው እንዳይርቅ::በራቸውን ከወትሮው ይልቅ ጠበቅብቅ አድርገው
ዘጉት:: ተካ ያመጣብኛል ብለው የፈሩት ችግር ከደቂቃ ደቀቃ ከሰዓት ወደ ሰዓት ያሳስባቸው ጀመር፡፡
"የሚያደርገውን ያድርግ እንግዲህ ምነው ኣካለወርቅ የሚሆነው ከመሆኑ በፊት በፍርሃት አልሞትም::" አሉ
ለራሳቸው::
እንዲህ እራሳቸውን ለማጎበዝ ይሞክሩ እንጂ ምሽቱ፡እየገፋ በሄደ ቁጥር ብርታታቸው መናዱ ኣልቀረም።
ማስረሻን አልጋቸው ላይ እስተኙዋትና፣ ቆም ብለው ወደ ተካ ክፍል ያስገባ የነበረውን እሽግ በር በጥርጣሬ
ተመለከቱት፣ የተካ ኣቋራጭ ማጥቂያ በዚያ እንደሚሆን እርግጠኛ ናቸው።
አሮጌ መጥረብያቸውን ከስርቻ ፈልገው ያዙና በእድሜ የላላ የእጅ ጡንቻቸውን ፈርጠም አድርገው ለጥቂት ጊዜ ወደ እሽጉ በር ካፈጠጠ በኋላ። እራስጌያቸው አስቀመጡት::
እንዲህ በማድረግ ላይ ሳሉ ነው ድንገት ተካ ክፍል ውስጥ የእርምጃና የእንቅስቃሴ ድምጽ የሰሙት::ወዲያውኑ የልባቸው አመታት ስለፈጠነባቸው
ደረታቸውን በሁለት እጆቻቸው ያዙና "እንዴ!" አሉ በሹክሽኩታ:: ተካ ከወትሮው ቀደም ብሎ መምጣቱ
ይበልጥ አስደነገጣቸው በፀጥታ አዳመጠ:: እያገሣ ያንጎራጉር ጀመር፡፡ ሞቅ ብሎት ሲመጣ የሚያደርገው
ልምድ ነው:: አካሌ ከአስፈሪ አውሬ ጋር የተፋጠጡ ይመስል እቆሙበት ተተክለው ቀሩ፡፡
"ዝግጅቱን በጊዜ ለመጀመር ነው ቀደም ብሎ የመጣው" አሉ በአሳባቸው:: የተካ እንጉርጉሮ ብዙም አልቆየ ሰው የሌለበት እስኪመስል ድረስ ክፍሉን ፀጥታ ዋጠው
አካሌ ለአስር ደቂቃ ያህል በዝምታ ካዳመጡ በኋላ፡ ቀስ ብለው አልጋቸው ጠርዝ ላይ ቁጭ አሉ።
እንደገና ለአምስት ደቂቃ ያህል አዳመጡ ከማስረሻ የእንቅልፍ ልብ አተነፋፈስና ከራሳቸው ልብ ምት ሌላ የሚሰማ ነገር የለም አይኖቻቸውን እሽጉ በር ላይ እንደተከሉ እራስጊያቸው ያለውን መጥረቢያ በዳበሳ አነሱና ጠበቅ አድርገው ያዙት:: እንደገና ጥቂት
ካዳመጡ በኋላ፣ "መተኛቴን ነው የሚያዳምጠው"አሉና ጉሮሯቸውን በመሞረድ ያለማንቀላፋታቸውን
የሚያመለክት ድምጽ አሰሙ:: ቀጥለው ደግሞ በያዙት መጥረቢያ ዛቢያ ወለላቸውን መታ መታ አደረጉት።.....
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
🔥1
#ላንዲት_የገጠር_ሴት
ስትፈጭ የኖረች ሴት
መጁ በመጠኗ ፣ ወፍጮውም በልኳ
ጓያ ትፈጫለች
ጓያ ሽሮ ሲኾን ያበቃል ታሪኳ።
አስባው አታውቅም
ወደ ኦናው ምድር ለምን እንደ መጣች
ከ'ለታት አንድ ቀን ከ ናቷ ሆድ ወጣች
ከ'ለታት አንድ ቀን፣ ጡት አጎጠጎጠች
ከ'ለታት ሌላ ቀን ለባሏ ተሰጠች
ተዚያን ቀን ጀምራ
ተዚያን ቀን ጀምሮ
ድንግል ድንጋይ ወቅራ
ትፈጫለች ሽሮ።
አታውቅም፣
ማን እንደሚባሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ
አታውቅም፣
ሹማምንት፣ በ'ሷ ስም፣ምን እንደሚሰሩ
አነሣኹት እንጂ እኔም ለነገሩ
በፖለቲካ ጥበብ ራስን ማራቀቅ
ምን ይጠቅማትና፣ጓያዋን ለማድቀቅ።
ከቶ ማንም የለ፣አበባ የሚሰጣት
ከቶ ማንም የለ፣ከተማ የሚያወጣት
ከቶ ማንም የለ፣በዳንኪራ መላ፣ወጠቧን የሚያቅፋት
ልፋቷም፣ዕረፍቷም፣
ወደዚህ መጅ መሳብ
ወደዚያ መጅ መግፋት።
እንደ ዓባይ ፏፏቴ ሺሕ ዓመትቢንጣለል
ቢጎርፍም ዱቄቱ
እንደ ሲኦል ወለል
ጫፍ የለውም ቋቱ ።
ከዘመናት ባ'ንዱ
መስታወት ፊት ቆማ፣በተወለወለው
ፊቷን ለማየት
ከፀጉሯ ላይ ያለው
ዱቄት ይኹን ሽበት ሲያቅታት መለየት
ያኔ ይገባታል የተሰጣት እጣ
ከማድቀቅ ቀጥሎ መድቀቅ እንደ መጣ።
የመጅ አገፋፏ አምሳለ ሲሲፈስ
ከቋት ስስት እንጂ ሲሳይ አይታፈስ
ትቢያ ሚተነብይ ዱቄት በዙርያዋ
ከባርኔጣ አይሰፋም የኑሮ ጣርያዋ
"ስትፈጭ የኖረች ሴት " ይህ ነው መጠሪያዋ።
#ሲሲፈስ- በግሪክ ተረት ውስጥ የሚገኝ ተኮናኝ ሲኾን ኩነኔው ያለግብ ድንደፈጋይ መግፋት ነው።
🔘በውቀቱ ስዩም🔘
ስትፈጭ የኖረች ሴት
መጁ በመጠኗ ፣ ወፍጮውም በልኳ
ጓያ ትፈጫለች
ጓያ ሽሮ ሲኾን ያበቃል ታሪኳ።
አስባው አታውቅም
ወደ ኦናው ምድር ለምን እንደ መጣች
ከ'ለታት አንድ ቀን ከ ናቷ ሆድ ወጣች
ከ'ለታት አንድ ቀን፣ ጡት አጎጠጎጠች
ከ'ለታት ሌላ ቀን ለባሏ ተሰጠች
ተዚያን ቀን ጀምራ
ተዚያን ቀን ጀምሮ
ድንግል ድንጋይ ወቅራ
ትፈጫለች ሽሮ።
አታውቅም፣
ማን እንደሚባሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ
አታውቅም፣
ሹማምንት፣ በ'ሷ ስም፣ምን እንደሚሰሩ
አነሣኹት እንጂ እኔም ለነገሩ
በፖለቲካ ጥበብ ራስን ማራቀቅ
ምን ይጠቅማትና፣ጓያዋን ለማድቀቅ።
ከቶ ማንም የለ፣አበባ የሚሰጣት
ከቶ ማንም የለ፣ከተማ የሚያወጣት
ከቶ ማንም የለ፣በዳንኪራ መላ፣ወጠቧን የሚያቅፋት
ልፋቷም፣ዕረፍቷም፣
ወደዚህ መጅ መሳብ
ወደዚያ መጅ መግፋት።
እንደ ዓባይ ፏፏቴ ሺሕ ዓመትቢንጣለል
ቢጎርፍም ዱቄቱ
እንደ ሲኦል ወለል
ጫፍ የለውም ቋቱ ።
ከዘመናት ባ'ንዱ
መስታወት ፊት ቆማ፣በተወለወለው
ፊቷን ለማየት
ከፀጉሯ ላይ ያለው
ዱቄት ይኹን ሽበት ሲያቅታት መለየት
ያኔ ይገባታል የተሰጣት እጣ
ከማድቀቅ ቀጥሎ መድቀቅ እንደ መጣ።
የመጅ አገፋፏ አምሳለ ሲሲፈስ
ከቋት ስስት እንጂ ሲሳይ አይታፈስ
ትቢያ ሚተነብይ ዱቄት በዙርያዋ
ከባርኔጣ አይሰፋም የኑሮ ጣርያዋ
"ስትፈጭ የኖረች ሴት " ይህ ነው መጠሪያዋ።
#ሲሲፈስ- በግሪክ ተረት ውስጥ የሚገኝ ተኮናኝ ሲኾን ኩነኔው ያለግብ ድንደፈጋይ መግፋት ነው።
🔘በውቀቱ ስዩም🔘
#ጥጡ_እና_ፈታይዋ
ባበባነት ወቅቱ
ጥጥ ነኝ ብሎ ቀርቧት
ፈታይ ኾና ቀርባው
ከስሩ ፈንቅላው
ከንቡጡ ፈልፍላው
ከማ'ረጉ አውርዳ
መሬት አስተኝታው
በፈገግታ በትር
በሣቅ ማደወርያ
ቀኑን ሙሉ ወቅታው
በድምጧ መንደፊያ
ባይኗ መዳመጫ
ከፍሬው ለይታው
ለካ እሱም ተረትቶ
ሰውነቱን ትቶ
(አምኖ ጥጥነቱን)
መዳፏ ስር ገብቶ
ድድር ገላው ሳስቶ
ጥብቅ ጉልበቱ ላልቶ
ኾኖላት ባዘቶ
በስሜት እንዝርቷ
ታብቶላት ዐሥራው
በራቁት ጭኗ ላይ
አሽከርክራ አሹራው
ሲወፍር አቅጥናው
ሲረግብ አክርራው
ሲያሰኛት ልቃቂት
ሲሻት ቀለም አ'ርጋው
ለካ እሱም ተረቶ
ሰውነቱን ትቶ
ጥጥነቱን አምኖ
እንዳደረገችው እንዳሰኛት ኾኖ
መለወጡን እንኳ ሳያስብ ላ'ንድ አፍታ
ከጥጥነት ልቆ ኾኗት ቀጭን ኩታ
ቀን ቀን ለውበቷ
ማታ ለሙቀቷ
ሲኾን ሰነባብቶ
ዕድፍ እና ትቢያ ከገላዋ አንስቶ
ጸዐዳው አካሉ እያደር ጨቅይቶ
እሷ ሳትለወጥ
እሱ ነትቦ አርጅቶ
ተሽቀንጥሮ ቀረ ኾነና ቡትቶ
በሌላ ጸዐዳ ኩታ ተተክቶ።
🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
ባበባነት ወቅቱ
ጥጥ ነኝ ብሎ ቀርቧት
ፈታይ ኾና ቀርባው
ከስሩ ፈንቅላው
ከንቡጡ ፈልፍላው
ከማ'ረጉ አውርዳ
መሬት አስተኝታው
በፈገግታ በትር
በሣቅ ማደወርያ
ቀኑን ሙሉ ወቅታው
በድምጧ መንደፊያ
ባይኗ መዳመጫ
ከፍሬው ለይታው
ለካ እሱም ተረትቶ
ሰውነቱን ትቶ
(አምኖ ጥጥነቱን)
መዳፏ ስር ገብቶ
ድድር ገላው ሳስቶ
ጥብቅ ጉልበቱ ላልቶ
ኾኖላት ባዘቶ
በስሜት እንዝርቷ
ታብቶላት ዐሥራው
በራቁት ጭኗ ላይ
አሽከርክራ አሹራው
ሲወፍር አቅጥናው
ሲረግብ አክርራው
ሲያሰኛት ልቃቂት
ሲሻት ቀለም አ'ርጋው
ለካ እሱም ተረቶ
ሰውነቱን ትቶ
ጥጥነቱን አምኖ
እንዳደረገችው እንዳሰኛት ኾኖ
መለወጡን እንኳ ሳያስብ ላ'ንድ አፍታ
ከጥጥነት ልቆ ኾኗት ቀጭን ኩታ
ቀን ቀን ለውበቷ
ማታ ለሙቀቷ
ሲኾን ሰነባብቶ
ዕድፍ እና ትቢያ ከገላዋ አንስቶ
ጸዐዳው አካሉ እያደር ጨቅይቶ
እሷ ሳትለወጥ
እሱ ነትቦ አርጅቶ
ተሽቀንጥሮ ቀረ ኾነና ቡትቶ
በሌላ ጸዐዳ ኩታ ተተክቶ።
🔘በዕውቀቱ ስዩም🔘
#አቀበት
፡
፡
#ክፍል_ሦስት (የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#በገበየሁ_አየለ
..የሚሰማ ነገር የለም፡፡ ዓይኖቻቸውን እሽጉ በር ላይ እንደተከሉ እራስጌያቸው ያለውን መጥረቢያ በዳበሳ አነሱና ጠበቅ አድርገው ያዙት:: እንደገና ጥቂት
ካዳመጡ በኋላ፣ "መተኛቴን ነው የሚያዳምጠው" አሉና ጉሮሯቸውን በመሞረድ ያለማንቀላፋታቸውን
የሚያመለክት ድምጽ አሰሙ።ቀጥለው ደግሞ በያዙት መጥረቢያ ዛቢያ ወለላቸውን መታ መታ አደረጉት።
"አልተኙም እንዴ አካሌ!" አለ ተካ ከሳቅ ጋር በተቀላቀለ አነጋገር፡፡ የመጠጡ ኃይል ምላሱን ትንሽ ያዝ ያድርገው እንጂ. ወፍራም ድምፁ ስልቱን
አልሳተም::
"አይዞት አይፍሩ እኔ ጠብቅዎታለሁ" ብሎ እንደገና ሳቀ::
"ከግንድ ያጣብቅህ" ለማለት አሰቡና ተውት፡፡
"አገር ቤት ነው የከረምኩት" አለ በረጅሙ
ተንፍሶ። የነገሩ አቅጣጫ ድንገት
በመለወጠ ቢገርማቸውም፡ መልስ አልሰጡትም::
"እማዬ እንደምንዎት ደህና ከረሙ ወይ በዓይነ ስጋ ለመገናኘት ያብቃን ብላዎታለች::"
"ደህና ናቸው? " አሉ እካሌ ድምጻቸውን ከፍ እድርገው።
"ደህና ነኝ” ትላለች የገጠር በተለያ የሷ አካባቢ ሰው ደህና አይደለሁም ማለቱን አያውቅበትም። ቃሬዛ ላይ እስኪጫን ድረስ ደህና ነኝ ነው የሚል፡፡ የትውልድ
ቀዬዬ ሰዎች ደህንነትን የሚለኩት ቆመው ከመሄዳቸው አንፃር ነው።
"እህህም" አሉ አካሌ "በ-ጄ ቀጥል » በማለት አኳኋን፡፡የተካ ጉዳይ ከማስረሻ ጉዳይ ወደሌላ በመቀየሩና አነጋገሩም የወዳጅነት በመምሰሉ ፍርሃታቸው ረገብ አለ።
"ታናሽ እህቴ በምጥ ሞተች፡ ሰባተኛ ልጅዋን ስትገላገል፡፡ እኔ እዛው ሆኜ ነው የሞተችው:: አጎቴን ወባ ገላገለው:: እማዬ የአጎቴን ሞት ስታረዳኝ `አረፈ
አለችኝ፡፡ አረፈ ለአካባቢው አገላለጥ ትክክለኛ ቋንቋ ነው:: በችጋርና በበሽታ እየተገረፈ ለሚኖር ሕዝብ፡ ሞት እረፍት ነው: ግልግል:: አይደለም እንዴ አካሌ?"
አለ ድምጹን ከቀድሞው ጎላ አድርጎ።
“እህህም" ብለው ዝም አሉ:: የተካ ንግግር ቀስ በቀስ ወደ አንጀታቸው የሚገባ ቀዝቃዛ ስሜት አሳደረባቸው።
« ሰውን አረገፈው' ትላለች እማዬ ፡ ሞት
በአካባቢው ያለውን ብርታት ስትገልጥ፡፡ እገሌንና እገሌን ተስቦ ወሰዳቸው እገሌ በደም ተቅማጥ አረፈ፣ እገሌን ወራጅ ውሃ ወሰደው፣ ያን የመሰለ ጉብል ፣ 'እናቱ በሀዘን አብዳ መቃብር ቤት ነው እምታድር .. ከብቱ ሣር አጥቶ አለት እየጋጠ በየሜዳው ተፈነቸረ' "ትላለች።
"አቤት አቤት፣ ይሄ ከላይ የመጣ መዓት ነው" አሉ አካሌ ማቃሰት በሚመስል ድምጽ፡፡
"እማዬም እንዲሁ ነው የምትል:: የአገሩ ሰው በየቤተክርስቲያኑና መስጊዱ እየተሰበሰበ "እግዚኦ ከዚህ
መዓት ሰውረን" እያለ አምላኩን በመማጠን ላይ ነው::"ብሎ ካዛጋ በኋላ እንደመሳል አለና፣
"የእማዬ አገር ሰዎች አሟሟትን ያውቁበታል፡አንቀላፉ እንዴ አካሌ?» አለ።
"ኧረ ሰማሀለሁ አሉ ሀዘን በተጫነው ድምጽ፡”
በቁሙ ነው ሞትን የሚጀምረውም የሚጨርሰውም።
"እንዴት? "
'ከችጋር ጋር ስለሚኖር ረሀብ ገደለኝ አይልም፡፡ጠኔ ሲያንገላታው መገጣጠሚያ አንጓዎቹ ሲላሉ፡ በሌላ
በሽታ አመካኝቶ ጣጣቴ እየተተኮሰ፡ ሳንባው ከጀርባው ተጣብቆ መተንፈስ ሲያቅተው ፡ በዋግምት እየተነጠቀ. እንዲያ እንዲያ እያለ ይሞተዋል።
ይሰሙኛል?»
"አዎን እሰማሀለሁ"
"ሽዋዬ እንደሞተች እናቴ ዘንድ ሄድኩ፣ ሞትን እዚያ ሆኜ ልጠብቀው ብዬ:: ለካ ሞት ወደነገሰበት ሥፍራ ኖሯል የሄድኩት:: ፊት ለፊት የተገናኘሁት
እስኪመስለኝ ድረስ በሥራው አየሁት፡፡ በችጋርና በደዌ ፈረስ እየጋለበ ሕዝቡንና ከብቱን ፈጅቶታል፣ አገሩን ወና አድርጎታል፡፡"
"ሞትን ተሸክሜ እንደሄድኩባት ያልጠረጠረችው እናቴ ምን አለች መሰለዎት" ብሎ እንደማሰብ አለና፣
ለወራት ከተኛችበት መደብ ላይ ቀና ብላ፣ የፈዘዙ ዓይኖቿን እያንከራተተች፣ ማመን አቅቷት እንደ እንሰት በደረቁ እጆቿ እራሴንና ፊቴን እየደባበሰች፣ ቀባሪ
ያላሳጣኸኝ ፈጣሪ ተመስገን፡፡ በመሞቻዬ ዋዜማ የልጄን ዓይን አሳየኸኝ' አለች፡፡ ድምጽ አጣች እንጂ እልል ለማለትም ሞክራለች፡፡ በደረቁ ከንፈሮቿ ፊቴን፣ እራሴን የአንገቴ ሥር ሁሉ ሳመችኝ ከመኪና ተራ የገዛሁትን ደረቅ ዳቦ በውኃ እየነከርኩ ሳጎርሳት በስስት ቶሎ ቶሎ
በላችና፣ 'ተመስገን አምላኬ፣ እንደኔ ማንን አድለሃል በቃ አሁን ጠግቤአለሁ የሞት ስንቄን አግኝቻለሁ፣ቀባሪዪም መጥቷል፤
ቶሎ ውሰደኝ አለች::"
"እኔን እኔን እንዴት ተጎድተው ኖሯል? " አሉ አካሌ ከልብ በሆነ ሀዘኔታ፡፡
"ፀሎቷ አልተመለሰላትም፤ እስከዛሬ አለች::"ብሎ ትንሽ ዝም አለና ለጉድ የጎለተኝ' ትላለች እማዬ ስለራሷ በምትናገርበት ጊዜ፡፡ «የመከራ ምስክር አድርጎኛል ጎተራዬ ሙሉ፣ በረቴ በከብት ትንፋሽ የሞቀ፣ ቤቴ የርሃብተኞች መሸሻ እንዳልነበረ ሁሉ የችጋርና የሞት ምሳሌ ሆኛለሁ" ትላለች፡፡ «እየሰሙኝ ነው አካሌ?»
«አዎን፣ ሰማሃለሁ::»
"እንዲህ ሆኖ አገኘሁት፣ የእማዬንና የአካባቢዋን ሁኔታ:: እኔማ በድብቅ የምሞትበትን ሥፍራ መርጨ
ነበር ወደዚያ መሄዴ፡፡ ሀገሩ ግን የሚሸሹት እንጂ የሚሸሽበት አልሆነም፡፡ እኔ ውስጥ ካለው ሞት ይልቅ፣እዚያ ያለው ገዝፎ ታየኝ፡፡ የሞት መላእክት ትዕዛዝ ለመፈጸም በየተራራው አናት ላይ በተጠንቀቅ ቆመው ቁልቁል የሚመለከቱ እስኪመስል ድረስ ነው፣ አካባቢው
የሚያስጨንቀው:: ለዚህ ነው ሸሽቼ እንደሄድኩ የመጣሁት:: ሕይወት ካለ ተስፋም መኖሩ ተሰማኝ፡፡አንድ ቀንም ዕድሜ ነው አልኩ፡፡ ነገ የተሻለ ነገር ይዞ
አይመጣም ያለው ማነው? ብዬ አሰብኩ፡፡ የሞትን ሹክሹክታ ከማዳመጥ ይልቅ፣ ተስፋን ማዛጋት ጥሩ ሆኖ ታየኝ፡፡ ተስፋ ሲሞት ነው እውነተኛው ሞት::
አይደለም እንዴ አካሌ?››
"ነው እንጂ! እኔ እምልህ ተካ'
"እመት"
“እውን መንፈቁን በሙሉ እናትህ ዘንድ ነበርክ?"
"አዎን"
እንዴት ብትጨክን ነው ብቅ ብለህ እንኳን ሳታየን መክረምህ?
"ጨክኜ አይደለም አካሌ፣ እንደሞትኩ ቆጥራችሁ እንድትረሱኝ ፈልጌ ነበር፡፡ በተለይ ሚጣዬ እናቷን እንዳጣች ሁሉ እኔንም እንደሌለሁ ብትቆጥረኝ ይሻላል
ብዬ አሰብኩ፡፡ እናቷን ስታጣ ተሳቀቀች፣ እኔ ስለያት ደግሞ ለምን ትደንግጥ? በተለይ ይበልጥ ከተላመደችኝና
የአባትነቴ ትርጉሙ ከገባት በኋላ ስታጣኝ፣ ሀዘኗ መሪር ይሆናል በማለት ነበር
"ቀድሞ ሟቹን እግዜአብሄር ነው የሚያውቀው:: ደግሞም ቅድም እንዳልከው ደግ ደጉን ማሰብ ይሻላል"
አሉ አካሌ፡፡
"ደግ ደጉን በማሰቤ ነው መንገዴን የቀየርኩ"
"ይሻላል ደጉን ማሰብ፣ ደጉን ማድረግ. .
"ደጉን መኖር" አለ ተካ ፈጠን ብሎ ጥቂት ዝም አለና ደግሞ፣
"ታዲያ እርስዎ ስለኔ ለምን ደግ አያስቡም? " አለ
ዝም አሉት አካሌ፡፡
"አካሌ"
"ወይ"
"ስለኔ ደግ አያስቡም? "
"ስለራሱ ደግ ለማያሰብ ሰው እንደምን ደግ ይታሰብለታል?
እንዲህ ሲወያዩ እኩለ ሌሊት አለፈ:: አካሌ ሀሳባቸውን ወደ ክፍላቸው ሰብሰብ አድርገው ሲመለከቱ፣
ጨብጠውት የነበረ መጥረቢያ ከእጃቸው ተንሸራትቶ መሬት ወድቋል፡፡ ወደ ማስረሻ ተመለከቱ፣ ከእንቅልፉ ከነቃች የቆየች ትመስላለች፡፡ ዓይኖቿን በሰፊው ከፍታ
ታያቸዋለች:: አልጋው ላይ ወጡና ዘና ብለው በመተኛት አቀፏት::
"ስለ ራሴም ሆነ፣ ለእርስዎና ለማስረሻ መልካም ማሰቤን በተግባር አሳይዎታለሁ አካሌ" አለ ተካ ሲያሰላስል ቆይቶ:፡ ኣካሌ ዝም ብለው የማስረሻን ፊት አንሶላውን እስከደረቷ ዝቅ አደረገችው::
"አይግፉኝ አካሌ" አለ ተካ ድምጸን ለዘብ አድርጎ
ውይይታቸውን ማስረሻ እንድትሰማው ስላልፈለጉ ዝም አሉት
አይግፉኝ፣ ዕድል
፡
፡
#ክፍል_ሦስት (የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#በገበየሁ_አየለ
..የሚሰማ ነገር የለም፡፡ ዓይኖቻቸውን እሽጉ በር ላይ እንደተከሉ እራስጌያቸው ያለውን መጥረቢያ በዳበሳ አነሱና ጠበቅ አድርገው ያዙት:: እንደገና ጥቂት
ካዳመጡ በኋላ፣ "መተኛቴን ነው የሚያዳምጠው" አሉና ጉሮሯቸውን በመሞረድ ያለማንቀላፋታቸውን
የሚያመለክት ድምጽ አሰሙ።ቀጥለው ደግሞ በያዙት መጥረቢያ ዛቢያ ወለላቸውን መታ መታ አደረጉት።
"አልተኙም እንዴ አካሌ!" አለ ተካ ከሳቅ ጋር በተቀላቀለ አነጋገር፡፡ የመጠጡ ኃይል ምላሱን ትንሽ ያዝ ያድርገው እንጂ. ወፍራም ድምፁ ስልቱን
አልሳተም::
"አይዞት አይፍሩ እኔ ጠብቅዎታለሁ" ብሎ እንደገና ሳቀ::
"ከግንድ ያጣብቅህ" ለማለት አሰቡና ተውት፡፡
"አገር ቤት ነው የከረምኩት" አለ በረጅሙ
ተንፍሶ። የነገሩ አቅጣጫ ድንገት
በመለወጠ ቢገርማቸውም፡ መልስ አልሰጡትም::
"እማዬ እንደምንዎት ደህና ከረሙ ወይ በዓይነ ስጋ ለመገናኘት ያብቃን ብላዎታለች::"
"ደህና ናቸው? " አሉ እካሌ ድምጻቸውን ከፍ እድርገው።
"ደህና ነኝ” ትላለች የገጠር በተለያ የሷ አካባቢ ሰው ደህና አይደለሁም ማለቱን አያውቅበትም። ቃሬዛ ላይ እስኪጫን ድረስ ደህና ነኝ ነው የሚል፡፡ የትውልድ
ቀዬዬ ሰዎች ደህንነትን የሚለኩት ቆመው ከመሄዳቸው አንፃር ነው።
"እህህም" አሉ አካሌ "በ-ጄ ቀጥል » በማለት አኳኋን፡፡የተካ ጉዳይ ከማስረሻ ጉዳይ ወደሌላ በመቀየሩና አነጋገሩም የወዳጅነት በመምሰሉ ፍርሃታቸው ረገብ አለ።
"ታናሽ እህቴ በምጥ ሞተች፡ ሰባተኛ ልጅዋን ስትገላገል፡፡ እኔ እዛው ሆኜ ነው የሞተችው:: አጎቴን ወባ ገላገለው:: እማዬ የአጎቴን ሞት ስታረዳኝ `አረፈ
አለችኝ፡፡ አረፈ ለአካባቢው አገላለጥ ትክክለኛ ቋንቋ ነው:: በችጋርና በበሽታ እየተገረፈ ለሚኖር ሕዝብ፡ ሞት እረፍት ነው: ግልግል:: አይደለም እንዴ አካሌ?"
አለ ድምጹን ከቀድሞው ጎላ አድርጎ።
“እህህም" ብለው ዝም አሉ:: የተካ ንግግር ቀስ በቀስ ወደ አንጀታቸው የሚገባ ቀዝቃዛ ስሜት አሳደረባቸው።
« ሰውን አረገፈው' ትላለች እማዬ ፡ ሞት
በአካባቢው ያለውን ብርታት ስትገልጥ፡፡ እገሌንና እገሌን ተስቦ ወሰዳቸው እገሌ በደም ተቅማጥ አረፈ፣ እገሌን ወራጅ ውሃ ወሰደው፣ ያን የመሰለ ጉብል ፣ 'እናቱ በሀዘን አብዳ መቃብር ቤት ነው እምታድር .. ከብቱ ሣር አጥቶ አለት እየጋጠ በየሜዳው ተፈነቸረ' "ትላለች።
"አቤት አቤት፣ ይሄ ከላይ የመጣ መዓት ነው" አሉ አካሌ ማቃሰት በሚመስል ድምጽ፡፡
"እማዬም እንዲሁ ነው የምትል:: የአገሩ ሰው በየቤተክርስቲያኑና መስጊዱ እየተሰበሰበ "እግዚኦ ከዚህ
መዓት ሰውረን" እያለ አምላኩን በመማጠን ላይ ነው::"ብሎ ካዛጋ በኋላ እንደመሳል አለና፣
"የእማዬ አገር ሰዎች አሟሟትን ያውቁበታል፡አንቀላፉ እንዴ አካሌ?» አለ።
"ኧረ ሰማሀለሁ አሉ ሀዘን በተጫነው ድምጽ፡”
በቁሙ ነው ሞትን የሚጀምረውም የሚጨርሰውም።
"እንዴት? "
'ከችጋር ጋር ስለሚኖር ረሀብ ገደለኝ አይልም፡፡ጠኔ ሲያንገላታው መገጣጠሚያ አንጓዎቹ ሲላሉ፡ በሌላ
በሽታ አመካኝቶ ጣጣቴ እየተተኮሰ፡ ሳንባው ከጀርባው ተጣብቆ መተንፈስ ሲያቅተው ፡ በዋግምት እየተነጠቀ. እንዲያ እንዲያ እያለ ይሞተዋል።
ይሰሙኛል?»
"አዎን እሰማሀለሁ"
"ሽዋዬ እንደሞተች እናቴ ዘንድ ሄድኩ፣ ሞትን እዚያ ሆኜ ልጠብቀው ብዬ:: ለካ ሞት ወደነገሰበት ሥፍራ ኖሯል የሄድኩት:: ፊት ለፊት የተገናኘሁት
እስኪመስለኝ ድረስ በሥራው አየሁት፡፡ በችጋርና በደዌ ፈረስ እየጋለበ ሕዝቡንና ከብቱን ፈጅቶታል፣ አገሩን ወና አድርጎታል፡፡"
"ሞትን ተሸክሜ እንደሄድኩባት ያልጠረጠረችው እናቴ ምን አለች መሰለዎት" ብሎ እንደማሰብ አለና፣
ለወራት ከተኛችበት መደብ ላይ ቀና ብላ፣ የፈዘዙ ዓይኖቿን እያንከራተተች፣ ማመን አቅቷት እንደ እንሰት በደረቁ እጆቿ እራሴንና ፊቴን እየደባበሰች፣ ቀባሪ
ያላሳጣኸኝ ፈጣሪ ተመስገን፡፡ በመሞቻዬ ዋዜማ የልጄን ዓይን አሳየኸኝ' አለች፡፡ ድምጽ አጣች እንጂ እልል ለማለትም ሞክራለች፡፡ በደረቁ ከንፈሮቿ ፊቴን፣ እራሴን የአንገቴ ሥር ሁሉ ሳመችኝ ከመኪና ተራ የገዛሁትን ደረቅ ዳቦ በውኃ እየነከርኩ ሳጎርሳት በስስት ቶሎ ቶሎ
በላችና፣ 'ተመስገን አምላኬ፣ እንደኔ ማንን አድለሃል በቃ አሁን ጠግቤአለሁ የሞት ስንቄን አግኝቻለሁ፣ቀባሪዪም መጥቷል፤
ቶሎ ውሰደኝ አለች::"
"እኔን እኔን እንዴት ተጎድተው ኖሯል? " አሉ አካሌ ከልብ በሆነ ሀዘኔታ፡፡
"ፀሎቷ አልተመለሰላትም፤ እስከዛሬ አለች::"ብሎ ትንሽ ዝም አለና ለጉድ የጎለተኝ' ትላለች እማዬ ስለራሷ በምትናገርበት ጊዜ፡፡ «የመከራ ምስክር አድርጎኛል ጎተራዬ ሙሉ፣ በረቴ በከብት ትንፋሽ የሞቀ፣ ቤቴ የርሃብተኞች መሸሻ እንዳልነበረ ሁሉ የችጋርና የሞት ምሳሌ ሆኛለሁ" ትላለች፡፡ «እየሰሙኝ ነው አካሌ?»
«አዎን፣ ሰማሃለሁ::»
"እንዲህ ሆኖ አገኘሁት፣ የእማዬንና የአካባቢዋን ሁኔታ:: እኔማ በድብቅ የምሞትበትን ሥፍራ መርጨ
ነበር ወደዚያ መሄዴ፡፡ ሀገሩ ግን የሚሸሹት እንጂ የሚሸሽበት አልሆነም፡፡ እኔ ውስጥ ካለው ሞት ይልቅ፣እዚያ ያለው ገዝፎ ታየኝ፡፡ የሞት መላእክት ትዕዛዝ ለመፈጸም በየተራራው አናት ላይ በተጠንቀቅ ቆመው ቁልቁል የሚመለከቱ እስኪመስል ድረስ ነው፣ አካባቢው
የሚያስጨንቀው:: ለዚህ ነው ሸሽቼ እንደሄድኩ የመጣሁት:: ሕይወት ካለ ተስፋም መኖሩ ተሰማኝ፡፡አንድ ቀንም ዕድሜ ነው አልኩ፡፡ ነገ የተሻለ ነገር ይዞ
አይመጣም ያለው ማነው? ብዬ አሰብኩ፡፡ የሞትን ሹክሹክታ ከማዳመጥ ይልቅ፣ ተስፋን ማዛጋት ጥሩ ሆኖ ታየኝ፡፡ ተስፋ ሲሞት ነው እውነተኛው ሞት::
አይደለም እንዴ አካሌ?››
"ነው እንጂ! እኔ እምልህ ተካ'
"እመት"
“እውን መንፈቁን በሙሉ እናትህ ዘንድ ነበርክ?"
"አዎን"
እንዴት ብትጨክን ነው ብቅ ብለህ እንኳን ሳታየን መክረምህ?
"ጨክኜ አይደለም አካሌ፣ እንደሞትኩ ቆጥራችሁ እንድትረሱኝ ፈልጌ ነበር፡፡ በተለይ ሚጣዬ እናቷን እንዳጣች ሁሉ እኔንም እንደሌለሁ ብትቆጥረኝ ይሻላል
ብዬ አሰብኩ፡፡ እናቷን ስታጣ ተሳቀቀች፣ እኔ ስለያት ደግሞ ለምን ትደንግጥ? በተለይ ይበልጥ ከተላመደችኝና
የአባትነቴ ትርጉሙ ከገባት በኋላ ስታጣኝ፣ ሀዘኗ መሪር ይሆናል በማለት ነበር
"ቀድሞ ሟቹን እግዜአብሄር ነው የሚያውቀው:: ደግሞም ቅድም እንዳልከው ደግ ደጉን ማሰብ ይሻላል"
አሉ አካሌ፡፡
"ደግ ደጉን በማሰቤ ነው መንገዴን የቀየርኩ"
"ይሻላል ደጉን ማሰብ፣ ደጉን ማድረግ. .
"ደጉን መኖር" አለ ተካ ፈጠን ብሎ ጥቂት ዝም አለና ደግሞ፣
"ታዲያ እርስዎ ስለኔ ለምን ደግ አያስቡም? " አለ
ዝም አሉት አካሌ፡፡
"አካሌ"
"ወይ"
"ስለኔ ደግ አያስቡም? "
"ስለራሱ ደግ ለማያሰብ ሰው እንደምን ደግ ይታሰብለታል?
እንዲህ ሲወያዩ እኩለ ሌሊት አለፈ:: አካሌ ሀሳባቸውን ወደ ክፍላቸው ሰብሰብ አድርገው ሲመለከቱ፣
ጨብጠውት የነበረ መጥረቢያ ከእጃቸው ተንሸራትቶ መሬት ወድቋል፡፡ ወደ ማስረሻ ተመለከቱ፣ ከእንቅልፉ ከነቃች የቆየች ትመስላለች፡፡ ዓይኖቿን በሰፊው ከፍታ
ታያቸዋለች:: አልጋው ላይ ወጡና ዘና ብለው በመተኛት አቀፏት::
"ስለ ራሴም ሆነ፣ ለእርስዎና ለማስረሻ መልካም ማሰቤን በተግባር አሳይዎታለሁ አካሌ" አለ ተካ ሲያሰላስል ቆይቶ:፡ ኣካሌ ዝም ብለው የማስረሻን ፊት አንሶላውን እስከደረቷ ዝቅ አደረገችው::
"አይግፉኝ አካሌ" አለ ተካ ድምጸን ለዘብ አድርጎ
ውይይታቸውን ማስረሻ እንድትሰማው ስላልፈለጉ ዝም አሉት
አይግፉኝ፣ ዕድል
👍3
አቆራኝታናለች ፣ ሞት ሽዋዬን በመንጠቅ የጎዳው ሁለታችንንም ነው:: ሚጣዬን ጥዬቦት ሸክማችንን እየተረዳዳን የመከራን አቀበት አብረን ብንወጣው አይሻልም።
አካሌ የተካን ንግግር በሰሙትና ባሰላሰሉት ቁጥር፣ውስጣቸው የነበረው የጥላቻና የቅሬታ ካብ ቀስ በቀስ
ይናድ ጀመር፡፡ እሳቸውም እንዲህ በግድግዳ ተለያይተው ሳይሆን ፊት ለፊት እየተያዩ ሀዘንና ስብራታቸውን ሊያወያዩት ከጀሉ፡፡ ሀዘንና ብሶት ለወዳጅ ፣ በተለይም ለቅርብ ሰው ሲያዋዩት ይቀንሳል ይባል የለ?
የተካንና የአካሌን ውይይት ታዳምጥ የነበረችው ማስረሻ ቀና ብላ በመቀመጥ ወደ አካሌ አፈጠጠች::አስተያየቷን ስለፈሩ እሳቸውም ቁጭ አሉና እቅፍ
አደረጓት።
"አካሌ" ተጣራ ተካ፡፡
ዝም አሉት፡፡ እንደገና ተጣራ፡፡
"እንቅልፌ መጥቷል ልተኛ :: የቀረውን ነገ
እንጨዋወታለን” አሉ ማስረሻን እያዩ፡፡
"አዎን ብንጨዋወትና ብንመካከር ይሻላል።የእህል ርሀቤንስ እንደምንም አስታግሰዋለሁ፣ የሚጣዪን ርሀብ እንዴት ልቻለው? የመኖር ፍላጐት ካሳደሩብኝ
ነገሮች አንዱ የርሷ ርሀብ ነው::"
"እራበኝ አለ? " አለች ማስረሻ በኮልታፋ
አንደበቷ፣ አንዴ ወይዘሮ አካሌን አንዴ ደግሞ እሽጉን በር እየተመለከተች አነጋገሯ የጥድፊያ ነበር፡፡
"አይደለም፣ ሌላ ነገር ነው፣ ተኚ ተኚ መሽቷል" አሉ አካሌ በጀርባዋ ሊያጋድሟት እየሞከሩ፣በእምቢታ እጃቸውን እየገፋች ወደ እሽጉ በር አፈጠ
ጠች።
"ተኚ መብራቱን ላጠፋው ነው"
"እምቢየው" ብላ ታለቅስ ጀመር፡፡ ባባበሏት ቁጥር የልቅሶ ድምጽዋ እየጎላ ሄደ፡፡ ጭር ባለው ውድቅት እንዲያ መሆኗ አስጨነቃቸው:: አፏን በመዳፋቸው ከድነው ዝም ሊያሰኝዋት ሞከሩ አልሆነላቸውም፡፡እንዲ.ያ በመሆን ላይ እንዳሉ ተካ ድምጹን ከፍ አደረገና፣
"ሚጣዬ ምነው? " አለ፡፡ ማስረሻ ይህን ስትሰማ ለቅሶዋን አቋረጠችና ወደ እሽጉ በር አፈጠጠች::
ል አቆራኝታናለች ፣ ሞት ሽዋዬን በመንጠቅ የጎዳው ሁለታችንንም ነው:: ሚጣዬን ጥዬቦት ሸክማችንን እየተረዳዳን የመከራን አቀበት አብረን ብንወጣው አይሻልም።
አካሌ የተካን ንግግር በሰሙትና ባሰላሰሉት ቁጥር፣ውስጣቸው የነበረው የጥላቻና የቅሬታ ካብ ቀስ በቀስ
ይናድ ጀመር፡፡ እሳቸውም እንዲህ በግድግዳ ተለያይተው ሳይሆን ፊት ለፊት እየተያዩ ሀዘንና ስብራታቸውን ሊያወያዩት ከጀሉ፡፡ ሀዘንና ብሶት ለወዳጅ ፣ በተለይም ለቅርብ ሰው ሲያዋዩት ይቀንሳል ይባል የለ?
የተካንና የአካሌን ውይይት ታዳምጥ የነበረችው ማስረሻ ቀና ብላ በመቀመጥ ወደ አካሌ አፈጠጠች::
"እንጀራ ልስጥሽ? ዳቦ ወተት ላምጣ?» አሉ አካሌ እየተርበተበቱ፡፡ የጠየቋትን ሁለ እንደማትፈልግ ትከሻዋን ሽቅብ ቁልቁል በመነቅነቅ ገለጠችላቸው::
አኳኋኗን ስለፈሩት ወደኋላቸው ደገፍ ብለው በዝምታ ይመለከቷት ጀመር፡፡ ዓይኖቿን አፍጣና አንገቷን አስግጋ
ከተካ ክፍል የሚመጣ ድምጽ ስትጠብቅ ቆየችና ከቀድሞው በከፋ ሁኔታ አለቀሰች::
"ተካ?" አሉ አካሌ ከአልጋው ላይ እየወረዱ።ማስረሻም እያለቀሰች ተከተለቻቸው::
"እመት"
"ምን ይሻላል"
ዝም አላቸው::
"የፊትለፊቱን በር እከፍትልሀለሁ ዙረህ ና" አሉ ጭንቅ እያላቸው:: ማስረሻ ይህን ስትሰማ ዝም አለች፡፡
ትንሽ ጠበቁና "ተካ" አሉ አካሌ
እመት"
"ምነው ዞረህ በፊት ለፊቱ በር ና አልኩህ እኮ!"
"
የመሀለን በር ይክፈቱት"
"እንዴት አድርጌ?" አለ በሩ የታሸገባቸውን ሁለት ቀጫጭን ማገሮች እየተመለከቱ::
"እኔ ልክፈተው? " አለ ፈጠን ብሎ
ዝም አሉ።
ወዲያው በሩ ከወደ ተካ ክፍል ስለተገፋ ከሁለቱ የማሽጊያ ማገሮች የላይኛው የተመታበት ምስማር ተነቀለ፣ ቀጥሎ ደግሞ የታችኛው ማገር ምስማር
ተነቀለና በሩ በትንሹ ከፈት አለ፡፡ ተካ ክፍሉ ውስጥ ቆሟል፡፡ ከአካሌ ጋር ፊት ለፊት ተፋጠጡ:: ፈገግ አለና ነጫጭ ጥርሶቹን አሳያቸው:: ትንሽ ከሳና ጎስቆል
ከማለቱ በቀር ብዙ አካላዊ ለውጥ አይታይበትም፡፡ሉጫ ፀጉሩ እንደመጎፈር ብሏል፡፡ የጠይም ፊቱ አጋማሽ
በጺም ተሸፍኗል:: በረጅም ቁመናው ጎንበስ ባለ ጊዜ ነው፣ ማስረሻ እግሩ ሥር መቆሟን አካሌ ልብ ያሉት፡፡
ብድግ አደረገና አቀፋት:: ፊቷን አንገቱ ሥር ሽጉጥ አደረገችው:: የተካ ትልልቅ ዓይኖች እንባ ያዘንቡ ጀመር::
አካሌም ከእንባ እየተናነቁ ወደፊት ራመድ አሉና ወደተካ ክፍል የሚያስገባውን በር በሰፊው ከፈቱት፡፡
ማስረሻን ጥብቅ አድርጎ እንዳቀፋት ታቦት የተሸከመ ይመስል በቀስታ እየተራመደ ወደ አካሌ ክፍል ገባ፡:
ሁለቱም በእንባ ደፍ ውስጥ እየተያዩ ለብዙ ሰኮንዶች ተፋጠጡ፡፡ አንዳቸው እሌላው ውስጥ ያለን የመከራ ታሪክ የሚያነብቡ ይመስሉ ነበር::
"እማዬ" አለች ማስረሻ በመሃለ:: እንባቸውን ጠራረጉና ቀና ብለው አዩዋት:: በአንድ እጅዋ የተካን
አንገት አቅፋ ሌላውን ወደሳቸው ዘርግታለች::ተጠጓት እሳቸውንም አቀፈቻቸው:: ኣካሌ ደሞ አንዱን
እጃቸውን ተካ ትከሻ ላይ አሳረፉና ጉንጨን ሳሙት::እርሱም አጸፋውን መለሰላቸውና።
"ትላንት የነበረን ደስታ ዛሬ እስፍራው አለመኖሩ፡ ሊያገፋፋን አይገባም አካሌ:: የተሻለን ነገር ተስፋ እናድርግ፡ ሀሳብና ምኞታችንን እናጣምር:: እንዲያ
ስናደርግ ነው እፊታችን ያለውን የመከራ አቀበት የመውጫ አቅም የምናገኘው" አለ ከሽኩሽኩታ ትንሽ ጎላ በሚል ድምጽ፡፡ ይሄኔ ማስረሻ የሁለቱንም ትካሻ
መታ መታ አደረገች:: ሁለቱም ካቀረቀሩበት ቀና ብለው ብሩህ የህጻን ፈገግታዋን በሳቃቸው አጀቡት::
💫አለቀ💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
አካሌ የተካን ንግግር በሰሙትና ባሰላሰሉት ቁጥር፣ውስጣቸው የነበረው የጥላቻና የቅሬታ ካብ ቀስ በቀስ
ይናድ ጀመር፡፡ እሳቸውም እንዲህ በግድግዳ ተለያይተው ሳይሆን ፊት ለፊት እየተያዩ ሀዘንና ስብራታቸውን ሊያወያዩት ከጀሉ፡፡ ሀዘንና ብሶት ለወዳጅ ፣ በተለይም ለቅርብ ሰው ሲያዋዩት ይቀንሳል ይባል የለ?
የተካንና የአካሌን ውይይት ታዳምጥ የነበረችው ማስረሻ ቀና ብላ በመቀመጥ ወደ አካሌ አፈጠጠች::አስተያየቷን ስለፈሩ እሳቸውም ቁጭ አሉና እቅፍ
አደረጓት።
"አካሌ" ተጣራ ተካ፡፡
ዝም አሉት፡፡ እንደገና ተጣራ፡፡
"እንቅልፌ መጥቷል ልተኛ :: የቀረውን ነገ
እንጨዋወታለን” አሉ ማስረሻን እያዩ፡፡
"አዎን ብንጨዋወትና ብንመካከር ይሻላል።የእህል ርሀቤንስ እንደምንም አስታግሰዋለሁ፣ የሚጣዪን ርሀብ እንዴት ልቻለው? የመኖር ፍላጐት ካሳደሩብኝ
ነገሮች አንዱ የርሷ ርሀብ ነው::"
"እራበኝ አለ? " አለች ማስረሻ በኮልታፋ
አንደበቷ፣ አንዴ ወይዘሮ አካሌን አንዴ ደግሞ እሽጉን በር እየተመለከተች አነጋገሯ የጥድፊያ ነበር፡፡
"አይደለም፣ ሌላ ነገር ነው፣ ተኚ ተኚ መሽቷል" አሉ አካሌ በጀርባዋ ሊያጋድሟት እየሞከሩ፣በእምቢታ እጃቸውን እየገፋች ወደ እሽጉ በር አፈጠ
ጠች።
"ተኚ መብራቱን ላጠፋው ነው"
"እምቢየው" ብላ ታለቅስ ጀመር፡፡ ባባበሏት ቁጥር የልቅሶ ድምጽዋ እየጎላ ሄደ፡፡ ጭር ባለው ውድቅት እንዲያ መሆኗ አስጨነቃቸው:: አፏን በመዳፋቸው ከድነው ዝም ሊያሰኝዋት ሞከሩ አልሆነላቸውም፡፡እንዲ.ያ በመሆን ላይ እንዳሉ ተካ ድምጹን ከፍ አደረገና፣
"ሚጣዬ ምነው? " አለ፡፡ ማስረሻ ይህን ስትሰማ ለቅሶዋን አቋረጠችና ወደ እሽጉ በር አፈጠጠች::
ል አቆራኝታናለች ፣ ሞት ሽዋዬን በመንጠቅ የጎዳው ሁለታችንንም ነው:: ሚጣዬን ጥዬቦት ሸክማችንን እየተረዳዳን የመከራን አቀበት አብረን ብንወጣው አይሻልም።
አካሌ የተካን ንግግር በሰሙትና ባሰላሰሉት ቁጥር፣ውስጣቸው የነበረው የጥላቻና የቅሬታ ካብ ቀስ በቀስ
ይናድ ጀመር፡፡ እሳቸውም እንዲህ በግድግዳ ተለያይተው ሳይሆን ፊት ለፊት እየተያዩ ሀዘንና ስብራታቸውን ሊያወያዩት ከጀሉ፡፡ ሀዘንና ብሶት ለወዳጅ ፣ በተለይም ለቅርብ ሰው ሲያዋዩት ይቀንሳል ይባል የለ?
የተካንና የአካሌን ውይይት ታዳምጥ የነበረችው ማስረሻ ቀና ብላ በመቀመጥ ወደ አካሌ አፈጠጠች::
"እንጀራ ልስጥሽ? ዳቦ ወተት ላምጣ?» አሉ አካሌ እየተርበተበቱ፡፡ የጠየቋትን ሁለ እንደማትፈልግ ትከሻዋን ሽቅብ ቁልቁል በመነቅነቅ ገለጠችላቸው::
አኳኋኗን ስለፈሩት ወደኋላቸው ደገፍ ብለው በዝምታ ይመለከቷት ጀመር፡፡ ዓይኖቿን አፍጣና አንገቷን አስግጋ
ከተካ ክፍል የሚመጣ ድምጽ ስትጠብቅ ቆየችና ከቀድሞው በከፋ ሁኔታ አለቀሰች::
"ተካ?" አሉ አካሌ ከአልጋው ላይ እየወረዱ።ማስረሻም እያለቀሰች ተከተለቻቸው::
"እመት"
"ምን ይሻላል"
ዝም አላቸው::
"የፊትለፊቱን በር እከፍትልሀለሁ ዙረህ ና" አሉ ጭንቅ እያላቸው:: ማስረሻ ይህን ስትሰማ ዝም አለች፡፡
ትንሽ ጠበቁና "ተካ" አሉ አካሌ
እመት"
"ምነው ዞረህ በፊት ለፊቱ በር ና አልኩህ እኮ!"
"
የመሀለን በር ይክፈቱት"
"እንዴት አድርጌ?" አለ በሩ የታሸገባቸውን ሁለት ቀጫጭን ማገሮች እየተመለከቱ::
"እኔ ልክፈተው? " አለ ፈጠን ብሎ
ዝም አሉ።
ወዲያው በሩ ከወደ ተካ ክፍል ስለተገፋ ከሁለቱ የማሽጊያ ማገሮች የላይኛው የተመታበት ምስማር ተነቀለ፣ ቀጥሎ ደግሞ የታችኛው ማገር ምስማር
ተነቀለና በሩ በትንሹ ከፈት አለ፡፡ ተካ ክፍሉ ውስጥ ቆሟል፡፡ ከአካሌ ጋር ፊት ለፊት ተፋጠጡ:: ፈገግ አለና ነጫጭ ጥርሶቹን አሳያቸው:: ትንሽ ከሳና ጎስቆል
ከማለቱ በቀር ብዙ አካላዊ ለውጥ አይታይበትም፡፡ሉጫ ፀጉሩ እንደመጎፈር ብሏል፡፡ የጠይም ፊቱ አጋማሽ
በጺም ተሸፍኗል:: በረጅም ቁመናው ጎንበስ ባለ ጊዜ ነው፣ ማስረሻ እግሩ ሥር መቆሟን አካሌ ልብ ያሉት፡፡
ብድግ አደረገና አቀፋት:: ፊቷን አንገቱ ሥር ሽጉጥ አደረገችው:: የተካ ትልልቅ ዓይኖች እንባ ያዘንቡ ጀመር::
አካሌም ከእንባ እየተናነቁ ወደፊት ራመድ አሉና ወደተካ ክፍል የሚያስገባውን በር በሰፊው ከፈቱት፡፡
ማስረሻን ጥብቅ አድርጎ እንዳቀፋት ታቦት የተሸከመ ይመስል በቀስታ እየተራመደ ወደ አካሌ ክፍል ገባ፡:
ሁለቱም በእንባ ደፍ ውስጥ እየተያዩ ለብዙ ሰኮንዶች ተፋጠጡ፡፡ አንዳቸው እሌላው ውስጥ ያለን የመከራ ታሪክ የሚያነብቡ ይመስሉ ነበር::
"እማዬ" አለች ማስረሻ በመሃለ:: እንባቸውን ጠራረጉና ቀና ብለው አዩዋት:: በአንድ እጅዋ የተካን
አንገት አቅፋ ሌላውን ወደሳቸው ዘርግታለች::ተጠጓት እሳቸውንም አቀፈቻቸው:: ኣካሌ ደሞ አንዱን
እጃቸውን ተካ ትከሻ ላይ አሳረፉና ጉንጨን ሳሙት::እርሱም አጸፋውን መለሰላቸውና።
"ትላንት የነበረን ደስታ ዛሬ እስፍራው አለመኖሩ፡ ሊያገፋፋን አይገባም አካሌ:: የተሻለን ነገር ተስፋ እናድርግ፡ ሀሳብና ምኞታችንን እናጣምር:: እንዲያ
ስናደርግ ነው እፊታችን ያለውን የመከራ አቀበት የመውጫ አቅም የምናገኘው" አለ ከሽኩሽኩታ ትንሽ ጎላ በሚል ድምጽ፡፡ ይሄኔ ማስረሻ የሁለቱንም ትካሻ
መታ መታ አደረገች:: ሁለቱም ካቀረቀሩበት ቀና ብለው ብሩህ የህጻን ፈገግታዋን በሳቃቸው አጀቡት::
💫አለቀ💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
❤1👍1
#መንገዱን_ጨርቅ_ያድርግልሽ
"የወደደ አበደ ፣ ሲባል የሰማሁት
ባንቺ ነው ዘንድሮ ፣ ደርሶብኝ ያየሁት
የሚለውን ዘፈን
እየሰማሁ ሳለ ፣ ጥዬው ሄድኩኝ ጨርቄን
ይኸው አሳበድሽኝ!
በእርግማን መረኩሽ ፣ እንባሽ ያምጣው ሳቄን
ይኸው አሳበድሸኝ!
አካሄድሽ እንጂ ፣ መች ጎዳኝ መሄድሽ
ልሸኝሽ መርቄ
የወደድሽው ይጥላሽ ፣ ያመንሽው ይካድሽ
ቆመሽ የሰቀልሽው ፣ ቁጭ ብሎ ያውርድሽ
ጨርቃቸውን ጥለው
እብዶች ያለፉበት ፣ ጨርቅ ይሁን መንገድሽ።
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
"የወደደ አበደ ፣ ሲባል የሰማሁት
ባንቺ ነው ዘንድሮ ፣ ደርሶብኝ ያየሁት
የሚለውን ዘፈን
እየሰማሁ ሳለ ፣ ጥዬው ሄድኩኝ ጨርቄን
ይኸው አሳበድሽኝ!
በእርግማን መረኩሽ ፣ እንባሽ ያምጣው ሳቄን
ይኸው አሳበድሸኝ!
አካሄድሽ እንጂ ፣ መች ጎዳኝ መሄድሽ
ልሸኝሽ መርቄ
የወደድሽው ይጥላሽ ፣ ያመንሽው ይካድሽ
ቆመሽ የሰቀልሽው ፣ ቁጭ ብሎ ያውርድሽ
ጨርቃቸውን ጥለው
እብዶች ያለፉበት ፣ ጨርቅ ይሁን መንገድሽ።
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
"ቆንጆ ነኝ" ባይ ማነሽ?
በውበትሽ ማርከሽ
ንጉስን ከዙፋን ፥ ማውረድ ሳትችዪ
ማነሽ "ቆንጆ" ሲሉሽ ፥ አቤት የምትዪ?
ድሮ ድሮ እኮ
የሴት ልጅ ውበቷ ፥ ዙፋንን ያስረሳል
ያንዲት ሴት ቁንጅና ፥ ካንድ ጦር ይብሳል።
ድሮኮ ድሮኮ
መንግስት ህዝብ ላይ ፥ በስልጣን ሲለግም
ከዙፋን ለማውረድ
አንዲት ቆንጆ እንጂ ፥ ትግል አያስፈልግም።
ድሮኮ ድሮኮ
ፈጣሪ የሾመው ፥ ጥበብን አድሎት
ዙፋኑን እንዳይለቅ
"ቆንጆ አታሳየኝ" ነው ፥ ያንድ ጠቢብ ፀሎት።
ንጉስን ለማውረድ ፥ህዝብ ሲያጣ አቅም
እኛው ከኛው ጦር ጋር ፥"ልቀቅ አንለቅም"
እየተባባልን ፥እርስ በርስ ብናልቅም
ቆንጆ ስንል አቤት ፥ ያለንን አናውቅም።
ንጉስን ከዙፋን
በውበትሽ ማርከሸ ፥ ማውረድ የማትችዬ
አንዳችም ደም ሳይፈስ ፥ ህዝብ የምታስጥዬ
ማነሸሸ "ቆንጆ" ሲሉሽ ፣ "አቤት"የምትዪ
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
በውበትሽ ማርከሽ
ንጉስን ከዙፋን ፥ ማውረድ ሳትችዪ
ማነሽ "ቆንጆ" ሲሉሽ ፥ አቤት የምትዪ?
ድሮ ድሮ እኮ
የሴት ልጅ ውበቷ ፥ ዙፋንን ያስረሳል
ያንዲት ሴት ቁንጅና ፥ ካንድ ጦር ይብሳል።
ድሮኮ ድሮኮ
መንግስት ህዝብ ላይ ፥ በስልጣን ሲለግም
ከዙፋን ለማውረድ
አንዲት ቆንጆ እንጂ ፥ ትግል አያስፈልግም።
ድሮኮ ድሮኮ
ፈጣሪ የሾመው ፥ ጥበብን አድሎት
ዙፋኑን እንዳይለቅ
"ቆንጆ አታሳየኝ" ነው ፥ ያንድ ጠቢብ ፀሎት።
ንጉስን ለማውረድ ፥ህዝብ ሲያጣ አቅም
እኛው ከኛው ጦር ጋር ፥"ልቀቅ አንለቅም"
እየተባባልን ፥እርስ በርስ ብናልቅም
ቆንጆ ስንል አቤት ፥ ያለንን አናውቅም።
ንጉስን ከዙፋን
በውበትሽ ማርከሸ ፥ ማውረድ የማትችዬ
አንዳችም ደም ሳይፈስ ፥ ህዝብ የምታስጥዬ
ማነሸሸ "ቆንጆ" ሲሉሽ ፣ "አቤት"የምትዪ
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
#ቅበላ
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#ከአዶኒስ
በደብዛዛ ቀይ ብርሃን በተሞላችው ባለ አንድ ክፍል ቤቷ ውስጥ ወደ በሩ ጠጋ ብላ ተቀምጣ ውጭ ውጭውን ታያለች፡፡ ቅዝዝ ያሉ ዐይኖቿን ጨለማው ላይ የሰካች ቢሆንም ምንም ነገር የምታይ አትመስልም።ቀያይ ጭኖቿ ለሚተላለፈዉ መንገደኛ በቅጡ እንዲታዩላት ባለስንጥቅ ቀሚሷን ሆነ ብላ ገለጥለጥ
አድርጋዋለች።አልፎ አልፎ በውል የማይሰሙ ቃላት እያጉተመተመች ከንፈሯን ትመጥጣለች:: ድንገት
ስትታይ ጠና ያለች ሴት ብትመስልም ልብ ብሉይ ላስተዋላት ከሰላሳ አምስት እስከ አርባ ባሉት የዕድሜ አንጓዎች መሃል እንደምትገኝ መገመት አያዳግትም፡፡
ፀዳል ትባላለች።
ከፀዳል በር በስተግራም በስተቀኝም በርካታ ተመሳሳይ በሮች በመደዳው ይታያሉ:: እያንዳንዱ ቤት ምን ያህል ጠባብ እንደሆነ ከበሮቹ መቀራረብ መገመት ይቻላል፡፡ በየቤቱ የተለያዩ ቀለማት ያላቸው አምፖሎች በርተዋል፡፡ ከአንዳንዱ ቤት የሚወጣው ደመና መሰል የጊርጊራ ጢስ መጀመሪያ የቤቱን የመብራት ቀለም እንደያዘ በራፉ ላይ ቡልቅ ይልና ወዲያው ደግሞ ጭለማው ውስጥ ክስም ይላል።
አለፍ አለፍ ብለው ጥቂት የተዘጉ በሮች ይታያሉ፡፡እነኚህ ታዲያ ከውጪ የተቆለፉ ሳይሆኑ ምሽቱ የቀናቸው ባለቤቶቻቸው ለጊዜው ከውስጥ የቀረቀሯቸው
ናቸው:: ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ይከፈቱና የተቀሩትን በሮች ይመስላሉ፡: ባለቤቶቻቸውም ልክ ምንም ያልተፈጠረ ዓይነት ምሽቱ ላይ እንደገና ያፈጡበታል፡፡
እዚህ ቦታ እያንዳንዱ ምሽት ለእያንዳንዷ ሴት አዲስ ነው። ትናንት እንዲህ ነበረና ዛሬ እንዲህ ይሆናል ብሎ መገመት አይቻልም:: ዛሬ ሶስት አራት ደንበኞች
ያስተናገደች ሴት ነገ አንድም ላይቀናት ይችላል።ገበያ የሸሻቸው ዕለት ሴቶቹ የማይጠረጥሩት ነገር የለም።ቢሆንም ባይሆንም በሚል የተለያዩ ሙከራዎችን
ያደርጋሉ:: አለባበስ ይቀይራሉ - ልዩ ልዩ ነገሮች በውሃ እየበጠበጠ ደጃፋቸውን ይረጫሉ የጊርጊራቸውን ጭሳጭስ እየቀያየሩ ይሞክራሉ የተረጩትን ሽቶ
በገደቢስነት ይጠረጥሩና ሌላ ሽቶ ይረጫሉ - የፀጉር አሰራራቸውን ይቀይራሉ - ብቻ የዕለቱ “ቋጠሮ” ይፈታ
ዘንድ የመሰላቸውን ሁሉ ያደርጋሉ፡፡
ዛሬ ከሁለት ወር በኋላ የሚፈታው አቢይ ፆም የሚያዝበት የቅበላ ምሽት ነው:: እናም ፀዳል ወዲህም ወዲያም ብላ ቢያንስ ግማሽ ኪሎ ሥጋ - ይህም አልሆን ካለ የሁለት የሶስት ብር ቅንጥብጣቢ መግዛት መቻል አለበት።
ባጣ ባጣ አንድ ደንበኛ አላጣም በሚል
ተስፋ ወዲያውም በግራና ቀኝ ያሉ ባላንጣዎቿ “አጣች ብለው ደስ እንዳይላቸው” በማለት - ሽንኩርቷን
ስትከታትፍና ስታቁላላ ነው ያመሸችው::
__የፓርላማው ሰዓት የአራት ሰዓቱን ደወል አሰማ::ፀዳል እንደመገረምም እንደመቁ ነጥነጥም አለች::
በባለላስቲክ ጨርቅ ወደላይ ሰብሰባ አስይዛው የነበረውን ፀጉራን የመመንጨቅ ዓይነት ፈታችና ወደ ታች
እየነሰነሰች ማስተካከል ጀመረች።
በስተቀኝ ካለችው የሥራ ባላንጣዋ ቤት እየመጣ ፀዳልን ሲረብሻት የቆየው ቅቤ የጠገበ የረጋ ወጥ ሽታ ጭራሹን እየገነነ መጣ፡፡ ፀዳል መጥፎ ጠረን እንደሽተታት
ሁሉ በአውራ ጣቷና በሌባ ጣቷ አፍንጫዋን ጨመቅ ጨመቅ አደረገችና ከአንገቷ ብቻ ወደ ውስጥ ዘወር ብላ
ግድግዳው ጥግ ካለችው የኬሮሲን ምድጃዋ ላይ አንድ አገር ሽንኩርት ከትፋ የጣደችበትን አነስተኛ የብረት ድስት
አየችው፡፡ ለአፍታ ያህል ወደ ውስጧ ፈገግ ብላ በራሷ ስትመፀት ቆየችና ድንገት በመርፌ ጠቅ ያደረጓት ይመስል
ነጠቅ ብላ በመነሳት ወደ ምድጃው አመራች:: ድስቱን አውርዳ ኬሮሲኑን አጠፋችና እጆቿን ደረቷ ላይ አጣምራ
ከወዲያ ወዲህ መንቆራጠጥ ጀመረች፡፡
“እንግዲህ ወይ እዛች ሜንጦ ጋ ደርስህ ትመጣ እንደሆን እንጂ አለች ለጣራ ግድግዳው የምታወራ ዓይነት።“አንዳንድ ቀን እኮ አያምጣው ነው::” ስትል አጉተመተመችና እንደገና ቦታዋን ይዛ ተቀመጠች።
በመንገዱ የሚያልፈውና የሚያገድመው ሰው ቁጥር እየሳሳ መጥቷል።ብዙም ሳይቆይ መሉ በመሉ ጥምብዝ ማለታቸው በግልፅ የሚታይባቸው አንድ አዛውንተ መላ ቅጡ በጠፋ አረማመድ እየተውተረተሩ በማለፍ ላይ ሳሉ ከፀዳል በራፍ ሲደርሱ ቆም አሉና
ነፋስ እንዳየለበት ለጋ ተክል እየተወዛወዘ ትክ ብለው ያዩዋት ጀመር፡፡ ፀዳል ስንጥቁን ቀሚሷን ከወትሮው በተለየ ግልጥልጥ አድርጋ ጭኖቿን እያሳየቻቸውና ይበልጥ ይስቧቸው ይሆናል ብላ የገመተቻቸውን
ተጨማሪ “እንቁልልጮች እያፈራረቀችባቸው ወጥመዷን ማጠባበቅ ጀመረች:: እጆቻቸውን ሱሪ
ኪሳቸው ውስጥ እንደከተቱ አዛውቱ- ለአፍታ ያህል ዐይኖቻቸውን በፀዳል የተጋለጠ ጭኖች ላይ ሲያንከባልሉ
ከቆዩ በኋላ ግንባራቸውን ቋጠር ፈታ ከንፈራቸውን ሸፈፍ ሸፈፍ አደረጉና ትከሻቸውን ሰብቀው እየተወላከፉ
መንገዳቸውን ቀጠሉ:: ዐዳል ሁለመናዋን መልሳ በመጠኑ ሽከፍከፍ አደረገችና በመገረም ዓይነት እንደገና ከንፈሯን መጠጠች።
“አንተን አይደለም እንዴ ምለው? - እዛች መናጢ ጋ ደርሰህ ና ማለት አማርኛ አይደለም?” አለች ዐይኖቿን ከመንገዱ ላይ ሳትነቅል ወዲያው ከአልጋዋ ስር በደረቱ እየተሳበ አንድ እድሜው ከአስራ አምስት የማይበልጥ ልጅ ብቅ አሐ።
ምን ልበላት” ሲል ጠየቃት ከጀርባዋ ቆሞ ራሱን እያከከና እንደመንጠራራት እያለ።
ስትላት ካለሽ አስር ብር ካልሆነልሽ ደግሞ አምስትም ቢሆን ላኪልኝ ነገ ጠዋት ለቡና ስመጣ ይዤልሽ እመጣለሁ አደራ አደራ ጦም መያዣ አጥቼ ነውና የዛሬን ብቻ ቅበሪኝ ብላሻለች በላት አለችው፣ ዘወር ብላ እንኳን ሳታየው ዐይኖቿን መንገዱ ላይ እንዳቀዘዘች፡፡ “ደግሞ እንደ ዔሊ ስትጎተት ዓመት
ቆይተህ ና አሉ!
ማሙሽት ሙት አምስት ደቂቃ አሳልፍና እንተያያለን
ማሙሸት ልጇ ነው :: ገና ወጣት ሳለች በትዳር ከተቆራኘችውና ብዙም አብሯት ለመኖር ካልታደለው የሕግ ባለቤቷ ያፈራችው:: ማሙሸት ሁለተኛ ዓመቱን
እንኳን በቅጡ ሳያገባድድና አዲሱ ትዳርም ገና ሞቅ ሞቅ ሳይል ነበር የማመሸት አባት ወደ አፈርነቱ
የተመለሰው:: ሕይወተ ገና በጠዋቱ፡ በረቂቅ ጥፊዋ ያስደነገጠቻት ፀዳል ባለቤቷ ትቶላት ባለፈው አነስተኛ
ጥሪት ጥቂት ጊዜ ስትንገታገት ቆየች:: ቀሪ ሀብቴ የምትለውና መማያዋም መገዘቻዋም የሆነው ማሙሸትም
ትምህርት ጀምሮ አንድ ሁለት ክፍል ቆጠረ:: የአባቱ በሕይወት ያለመኖር ልጇ ላይ ሊፈጥርበት የሚችለውን
ክፍተት ለማጥበብ ፀዳል የአቅሟን ሁሉ ጣረች።በሕይወት እስካለች ድረስም ማሙሸት ቢያንስ መሰረታዊ
የሚባሉት ነገሮች ሲያጥሩት ላለማየት ለራሷ ቃል ገባች፡፡
ይሁን እንጂ ነገሮች እንደግምቷ አልሄዱም። ዕለት ተዕለት ማጣፊያው እያጠራት መጣ፡፡ ይሄኔ ነበር
እንደመጨረሻ አማራጭ ሴትኛ ለማደር የቆረጠችው።ታዲያ ይህም ቢሆን እንደአጀማመሩ አልቀጠለም።
ከዓመት ዓመት ዝቅ እያለ የሚሄድ የሕይወት ቁልቁለት ሆነ። ፀዳ ፀዳ ባሉ ሆቴሎችና መዝናኛዎች የተጀመረው
የእንጀራ ገመዷ እየሰለሰለ በመምጣት እዚህ አሁን ካለበት ደረጃ ደረሰ። ያም ሆኖ የልጇ የማሙሸት ትምህርት
አንድም ጊዜ ተስተጓጉሉበት አያውቅም። ማሙሸት የሚያስፈልጉትን ነገሮች ያሟላች ከመሰላት ደግሞ ሌላ
የሚያሳስባት ነገር የለም። በተለይ አሁን አሁን ለዐዳል ሕይወት” ማለት ማሙሸት” ማለት ሆኗል።
በዚህ እንጀራ ከተሰማሩ የፀዳል ጎረቤቶች የተወሰነቱ እንደሷው ሁሉ ባለልጆች ናቸው:: ታዲያ በሥራው ፀባይ ምክንያት ልጆቻቸውን እንደሚፈልጉት
አድርገው ማሳደግ አይቻላቸውም:: ደንበኞቻቸውን የሚያስተናግዱት በአብዛኛው ከአመሻሹ እስከ እኩለ
ሌሊት ባለው ጊዜ ውስጥ በመሆኑ ይሄንን ጊዜ ልጆቹ ከየቤታቸው ውጪ ለማሳለፍ ይገደዳሉ። አንዱ ሎተሪ
ሲያዞር ያመሻል - ሌላው
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#ከአዶኒስ
በደብዛዛ ቀይ ብርሃን በተሞላችው ባለ አንድ ክፍል ቤቷ ውስጥ ወደ በሩ ጠጋ ብላ ተቀምጣ ውጭ ውጭውን ታያለች፡፡ ቅዝዝ ያሉ ዐይኖቿን ጨለማው ላይ የሰካች ቢሆንም ምንም ነገር የምታይ አትመስልም።ቀያይ ጭኖቿ ለሚተላለፈዉ መንገደኛ በቅጡ እንዲታዩላት ባለስንጥቅ ቀሚሷን ሆነ ብላ ገለጥለጥ
አድርጋዋለች።አልፎ አልፎ በውል የማይሰሙ ቃላት እያጉተመተመች ከንፈሯን ትመጥጣለች:: ድንገት
ስትታይ ጠና ያለች ሴት ብትመስልም ልብ ብሉይ ላስተዋላት ከሰላሳ አምስት እስከ አርባ ባሉት የዕድሜ አንጓዎች መሃል እንደምትገኝ መገመት አያዳግትም፡፡
ፀዳል ትባላለች።
ከፀዳል በር በስተግራም በስተቀኝም በርካታ ተመሳሳይ በሮች በመደዳው ይታያሉ:: እያንዳንዱ ቤት ምን ያህል ጠባብ እንደሆነ ከበሮቹ መቀራረብ መገመት ይቻላል፡፡ በየቤቱ የተለያዩ ቀለማት ያላቸው አምፖሎች በርተዋል፡፡ ከአንዳንዱ ቤት የሚወጣው ደመና መሰል የጊርጊራ ጢስ መጀመሪያ የቤቱን የመብራት ቀለም እንደያዘ በራፉ ላይ ቡልቅ ይልና ወዲያው ደግሞ ጭለማው ውስጥ ክስም ይላል።
አለፍ አለፍ ብለው ጥቂት የተዘጉ በሮች ይታያሉ፡፡እነኚህ ታዲያ ከውጪ የተቆለፉ ሳይሆኑ ምሽቱ የቀናቸው ባለቤቶቻቸው ለጊዜው ከውስጥ የቀረቀሯቸው
ናቸው:: ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ይከፈቱና የተቀሩትን በሮች ይመስላሉ፡: ባለቤቶቻቸውም ልክ ምንም ያልተፈጠረ ዓይነት ምሽቱ ላይ እንደገና ያፈጡበታል፡፡
እዚህ ቦታ እያንዳንዱ ምሽት ለእያንዳንዷ ሴት አዲስ ነው። ትናንት እንዲህ ነበረና ዛሬ እንዲህ ይሆናል ብሎ መገመት አይቻልም:: ዛሬ ሶስት አራት ደንበኞች
ያስተናገደች ሴት ነገ አንድም ላይቀናት ይችላል።ገበያ የሸሻቸው ዕለት ሴቶቹ የማይጠረጥሩት ነገር የለም።ቢሆንም ባይሆንም በሚል የተለያዩ ሙከራዎችን
ያደርጋሉ:: አለባበስ ይቀይራሉ - ልዩ ልዩ ነገሮች በውሃ እየበጠበጠ ደጃፋቸውን ይረጫሉ የጊርጊራቸውን ጭሳጭስ እየቀያየሩ ይሞክራሉ የተረጩትን ሽቶ
በገደቢስነት ይጠረጥሩና ሌላ ሽቶ ይረጫሉ - የፀጉር አሰራራቸውን ይቀይራሉ - ብቻ የዕለቱ “ቋጠሮ” ይፈታ
ዘንድ የመሰላቸውን ሁሉ ያደርጋሉ፡፡
ዛሬ ከሁለት ወር በኋላ የሚፈታው አቢይ ፆም የሚያዝበት የቅበላ ምሽት ነው:: እናም ፀዳል ወዲህም ወዲያም ብላ ቢያንስ ግማሽ ኪሎ ሥጋ - ይህም አልሆን ካለ የሁለት የሶስት ብር ቅንጥብጣቢ መግዛት መቻል አለበት።
ባጣ ባጣ አንድ ደንበኛ አላጣም በሚል
ተስፋ ወዲያውም በግራና ቀኝ ያሉ ባላንጣዎቿ “አጣች ብለው ደስ እንዳይላቸው” በማለት - ሽንኩርቷን
ስትከታትፍና ስታቁላላ ነው ያመሸችው::
__የፓርላማው ሰዓት የአራት ሰዓቱን ደወል አሰማ::ፀዳል እንደመገረምም እንደመቁ ነጥነጥም አለች::
በባለላስቲክ ጨርቅ ወደላይ ሰብሰባ አስይዛው የነበረውን ፀጉራን የመመንጨቅ ዓይነት ፈታችና ወደ ታች
እየነሰነሰች ማስተካከል ጀመረች።
በስተቀኝ ካለችው የሥራ ባላንጣዋ ቤት እየመጣ ፀዳልን ሲረብሻት የቆየው ቅቤ የጠገበ የረጋ ወጥ ሽታ ጭራሹን እየገነነ መጣ፡፡ ፀዳል መጥፎ ጠረን እንደሽተታት
ሁሉ በአውራ ጣቷና በሌባ ጣቷ አፍንጫዋን ጨመቅ ጨመቅ አደረገችና ከአንገቷ ብቻ ወደ ውስጥ ዘወር ብላ
ግድግዳው ጥግ ካለችው የኬሮሲን ምድጃዋ ላይ አንድ አገር ሽንኩርት ከትፋ የጣደችበትን አነስተኛ የብረት ድስት
አየችው፡፡ ለአፍታ ያህል ወደ ውስጧ ፈገግ ብላ በራሷ ስትመፀት ቆየችና ድንገት በመርፌ ጠቅ ያደረጓት ይመስል
ነጠቅ ብላ በመነሳት ወደ ምድጃው አመራች:: ድስቱን አውርዳ ኬሮሲኑን አጠፋችና እጆቿን ደረቷ ላይ አጣምራ
ከወዲያ ወዲህ መንቆራጠጥ ጀመረች፡፡
“እንግዲህ ወይ እዛች ሜንጦ ጋ ደርስህ ትመጣ እንደሆን እንጂ አለች ለጣራ ግድግዳው የምታወራ ዓይነት።“አንዳንድ ቀን እኮ አያምጣው ነው::” ስትል አጉተመተመችና እንደገና ቦታዋን ይዛ ተቀመጠች።
በመንገዱ የሚያልፈውና የሚያገድመው ሰው ቁጥር እየሳሳ መጥቷል።ብዙም ሳይቆይ መሉ በመሉ ጥምብዝ ማለታቸው በግልፅ የሚታይባቸው አንድ አዛውንተ መላ ቅጡ በጠፋ አረማመድ እየተውተረተሩ በማለፍ ላይ ሳሉ ከፀዳል በራፍ ሲደርሱ ቆም አሉና
ነፋስ እንዳየለበት ለጋ ተክል እየተወዛወዘ ትክ ብለው ያዩዋት ጀመር፡፡ ፀዳል ስንጥቁን ቀሚሷን ከወትሮው በተለየ ግልጥልጥ አድርጋ ጭኖቿን እያሳየቻቸውና ይበልጥ ይስቧቸው ይሆናል ብላ የገመተቻቸውን
ተጨማሪ “እንቁልልጮች እያፈራረቀችባቸው ወጥመዷን ማጠባበቅ ጀመረች:: እጆቻቸውን ሱሪ
ኪሳቸው ውስጥ እንደከተቱ አዛውቱ- ለአፍታ ያህል ዐይኖቻቸውን በፀዳል የተጋለጠ ጭኖች ላይ ሲያንከባልሉ
ከቆዩ በኋላ ግንባራቸውን ቋጠር ፈታ ከንፈራቸውን ሸፈፍ ሸፈፍ አደረጉና ትከሻቸውን ሰብቀው እየተወላከፉ
መንገዳቸውን ቀጠሉ:: ዐዳል ሁለመናዋን መልሳ በመጠኑ ሽከፍከፍ አደረገችና በመገረም ዓይነት እንደገና ከንፈሯን መጠጠች።
“አንተን አይደለም እንዴ ምለው? - እዛች መናጢ ጋ ደርሰህ ና ማለት አማርኛ አይደለም?” አለች ዐይኖቿን ከመንገዱ ላይ ሳትነቅል ወዲያው ከአልጋዋ ስር በደረቱ እየተሳበ አንድ እድሜው ከአስራ አምስት የማይበልጥ ልጅ ብቅ አሐ።
ምን ልበላት” ሲል ጠየቃት ከጀርባዋ ቆሞ ራሱን እያከከና እንደመንጠራራት እያለ።
ስትላት ካለሽ አስር ብር ካልሆነልሽ ደግሞ አምስትም ቢሆን ላኪልኝ ነገ ጠዋት ለቡና ስመጣ ይዤልሽ እመጣለሁ አደራ አደራ ጦም መያዣ አጥቼ ነውና የዛሬን ብቻ ቅበሪኝ ብላሻለች በላት አለችው፣ ዘወር ብላ እንኳን ሳታየው ዐይኖቿን መንገዱ ላይ እንዳቀዘዘች፡፡ “ደግሞ እንደ ዔሊ ስትጎተት ዓመት
ቆይተህ ና አሉ!
ማሙሽት ሙት አምስት ደቂቃ አሳልፍና እንተያያለን
ማሙሸት ልጇ ነው :: ገና ወጣት ሳለች በትዳር ከተቆራኘችውና ብዙም አብሯት ለመኖር ካልታደለው የሕግ ባለቤቷ ያፈራችው:: ማሙሸት ሁለተኛ ዓመቱን
እንኳን በቅጡ ሳያገባድድና አዲሱ ትዳርም ገና ሞቅ ሞቅ ሳይል ነበር የማመሸት አባት ወደ አፈርነቱ
የተመለሰው:: ሕይወተ ገና በጠዋቱ፡ በረቂቅ ጥፊዋ ያስደነገጠቻት ፀዳል ባለቤቷ ትቶላት ባለፈው አነስተኛ
ጥሪት ጥቂት ጊዜ ስትንገታገት ቆየች:: ቀሪ ሀብቴ የምትለውና መማያዋም መገዘቻዋም የሆነው ማሙሸትም
ትምህርት ጀምሮ አንድ ሁለት ክፍል ቆጠረ:: የአባቱ በሕይወት ያለመኖር ልጇ ላይ ሊፈጥርበት የሚችለውን
ክፍተት ለማጥበብ ፀዳል የአቅሟን ሁሉ ጣረች።በሕይወት እስካለች ድረስም ማሙሸት ቢያንስ መሰረታዊ
የሚባሉት ነገሮች ሲያጥሩት ላለማየት ለራሷ ቃል ገባች፡፡
ይሁን እንጂ ነገሮች እንደግምቷ አልሄዱም። ዕለት ተዕለት ማጣፊያው እያጠራት መጣ፡፡ ይሄኔ ነበር
እንደመጨረሻ አማራጭ ሴትኛ ለማደር የቆረጠችው።ታዲያ ይህም ቢሆን እንደአጀማመሩ አልቀጠለም።
ከዓመት ዓመት ዝቅ እያለ የሚሄድ የሕይወት ቁልቁለት ሆነ። ፀዳ ፀዳ ባሉ ሆቴሎችና መዝናኛዎች የተጀመረው
የእንጀራ ገመዷ እየሰለሰለ በመምጣት እዚህ አሁን ካለበት ደረጃ ደረሰ። ያም ሆኖ የልጇ የማሙሸት ትምህርት
አንድም ጊዜ ተስተጓጉሉበት አያውቅም። ማሙሸት የሚያስፈልጉትን ነገሮች ያሟላች ከመሰላት ደግሞ ሌላ
የሚያሳስባት ነገር የለም። በተለይ አሁን አሁን ለዐዳል ሕይወት” ማለት ማሙሸት” ማለት ሆኗል።
በዚህ እንጀራ ከተሰማሩ የፀዳል ጎረቤቶች የተወሰነቱ እንደሷው ሁሉ ባለልጆች ናቸው:: ታዲያ በሥራው ፀባይ ምክንያት ልጆቻቸውን እንደሚፈልጉት
አድርገው ማሳደግ አይቻላቸውም:: ደንበኞቻቸውን የሚያስተናግዱት በአብዛኛው ከአመሻሹ እስከ እኩለ
ሌሊት ባለው ጊዜ ውስጥ በመሆኑ ይሄንን ጊዜ ልጆቹ ከየቤታቸው ውጪ ለማሳለፍ ይገደዳሉ። አንዱ ሎተሪ
ሲያዞር ያመሻል - ሌላው
👍1
ሲጋራ ያዞራል ሌላኛው ቅቅል እንቁላል - ሌላኛዋ ቆሎ- ያኛው መፋቂያ - ያቺኛዋ በቆልት - ወ.ዘ.ተ:: የተሰማሩበት ሲመለሱ ደግሞ
እዚያው መንደራቸው ውስጥ ውር ውር ሲሉ፣ ሲላፉ፣ አላፊ አግዳሚውን ሲያስቸግሩ፣ ሰካራም ሲዘርፉና
የመሳሰሉትን ሲያደርጉ የመግቢያ ሰዓታቸዉን ይጠባበቃሉ:: የትምህርት ነገር በአብዛኛው የሚታሰብ አይደለም። አንዳንዶቹ፣ ለወጉ ቢጀምሩት እንኳ እምብዛም ሊገፉበት አይቻላቸውም።
ፀዳል ወደዚህ ቦታ ስትመጣ ማሙሽተ ስምንተኛ ዓመቱን እያጋመስ ነበር፡፡ ታዲያ እንደደረሰች አካባቢውን በሚገባ ካጤነች በኋላ በመጀመሪያ የወሰነችው ልጇ
የተቀሩትን የመንደሩ ልጆች ዕጣ የሚጋራበት ሁኔታ እንዳይፈጠር የአቅሟን ሁሉ ለማድረግ ነበር፡፡ እናም
ማሙሸት ቀን ቀን ትምህርት ቤት ይውላል - ከዚያ መልስ ከሷው ጋር እቤት ውስጥ ያመሻሻል እንግዳ በምታስተናግድባቸው ሰዓታት አልጋዋ ሥር ለጥ ብሎ ይቆያል:: ከመንደሩ ልጆች ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት እንዲፈጥር ዕድል አትሰጠውም።
ማሙሽት አልጋ ሥር የሚገባወ እንግዳ
እስኪመጣ ጠብቆ አይደለም:: እንግዳው በየትኛው ሰዓትና ደቂቃ እንደሚመጣ አይታወቅም:: እናም ገና መሸትሸት
ማለት ሲጀምር ማመሽት ከእናቱ አልጋ ሥር ይገባና ለዚሁ ብላ በደረተችለት ጨርቃጨርቅ ላይ ለጥ ይላል፡፡
ፀዳል የቤቷን ሥራ ስትሰራም ሆነ በራፏ ላይ ተቀምጣ ደንበኛ ስትጠብቅ አልጋዋ ሥር ካለው ልጇ ጋር የቆጥ
የባጡን ስታወራ ታመሻለች:: ታዲያ ሚስጥሩን ለማያውቅ ብቻዋን የምትለፈልፍ ወፈፌ ነው የምትመስለው።
ፀዳል ሥራዋን የጀመረች ሰሞን ነባሮቹን ሴቶች ክፉኛ እረፍት የነሳቸው አንድ ጥያቄ ነበር - ከደንበኞቿ
ጋር በምትሆንባቸው ሰዓታት ልጇ የት እንደሚቆይ፡፡የኋላ የኋላ ግን በዚህም በዚያም ብለው አልጋዋ ሥር
የማምሽቱን ሚስጥር ደረሱበት።
እንደው በፈጠረሽ ልጅሽ አይደል እንዴ?
እንዴት ያን ሁሉ ጉድሽን እንዲሰማ ታደርጊዋለሽ?”...
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
እዚያው መንደራቸው ውስጥ ውር ውር ሲሉ፣ ሲላፉ፣ አላፊ አግዳሚውን ሲያስቸግሩ፣ ሰካራም ሲዘርፉና
የመሳሰሉትን ሲያደርጉ የመግቢያ ሰዓታቸዉን ይጠባበቃሉ:: የትምህርት ነገር በአብዛኛው የሚታሰብ አይደለም። አንዳንዶቹ፣ ለወጉ ቢጀምሩት እንኳ እምብዛም ሊገፉበት አይቻላቸውም።
ፀዳል ወደዚህ ቦታ ስትመጣ ማሙሽተ ስምንተኛ ዓመቱን እያጋመስ ነበር፡፡ ታዲያ እንደደረሰች አካባቢውን በሚገባ ካጤነች በኋላ በመጀመሪያ የወሰነችው ልጇ
የተቀሩትን የመንደሩ ልጆች ዕጣ የሚጋራበት ሁኔታ እንዳይፈጠር የአቅሟን ሁሉ ለማድረግ ነበር፡፡ እናም
ማሙሸት ቀን ቀን ትምህርት ቤት ይውላል - ከዚያ መልስ ከሷው ጋር እቤት ውስጥ ያመሻሻል እንግዳ በምታስተናግድባቸው ሰዓታት አልጋዋ ሥር ለጥ ብሎ ይቆያል:: ከመንደሩ ልጆች ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት እንዲፈጥር ዕድል አትሰጠውም።
ማሙሽት አልጋ ሥር የሚገባወ እንግዳ
እስኪመጣ ጠብቆ አይደለም:: እንግዳው በየትኛው ሰዓትና ደቂቃ እንደሚመጣ አይታወቅም:: እናም ገና መሸትሸት
ማለት ሲጀምር ማመሽት ከእናቱ አልጋ ሥር ይገባና ለዚሁ ብላ በደረተችለት ጨርቃጨርቅ ላይ ለጥ ይላል፡፡
ፀዳል የቤቷን ሥራ ስትሰራም ሆነ በራፏ ላይ ተቀምጣ ደንበኛ ስትጠብቅ አልጋዋ ሥር ካለው ልጇ ጋር የቆጥ
የባጡን ስታወራ ታመሻለች:: ታዲያ ሚስጥሩን ለማያውቅ ብቻዋን የምትለፈልፍ ወፈፌ ነው የምትመስለው።
ፀዳል ሥራዋን የጀመረች ሰሞን ነባሮቹን ሴቶች ክፉኛ እረፍት የነሳቸው አንድ ጥያቄ ነበር - ከደንበኞቿ
ጋር በምትሆንባቸው ሰዓታት ልጇ የት እንደሚቆይ፡፡የኋላ የኋላ ግን በዚህም በዚያም ብለው አልጋዋ ሥር
የማምሽቱን ሚስጥር ደረሱበት።
እንደው በፈጠረሽ ልጅሽ አይደል እንዴ?
እንዴት ያን ሁሉ ጉድሽን እንዲሰማ ታደርጊዋለሽ?”...
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍1