‹‹መዳንም በሌላ በማንም የለም›› የሐዋ 4፥12
@And_Haymanot
«መዳንም በሌላ በማንም የለም እንድንበት ዘንድ የተሰጠን ከሰማይ በታች ሌላ የለም» የሐዋ 4፥12 ይህ እውነተኛ የእግዚአብሔር ቃል ነው። ከእርሱ በቀር አዳኝ አምላክ የለም። ኢሳ 45፡21 ከኢየሱስ ውጪ አዳኝ የለም ስንል ኢየሱስ እግዚአብሔር ነው ማለታችን ነው ምክንቱም ከእግዚአብሔር ውጪ የሚያድን ስለሌለ ነገር ግን አምላካችን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በእርሱ ለአመኑትን #የጸጋ_የማዳን_ስልጣን_ለቅዱሳን ሰጥቶአቸዋል። መጽ መሳፍ 3፡9 የእስራኤልም ልጆች ወደ እግዚአብሔር ጮኹ እግዚአብሔርም የሚያድናቸውን አዳኝ የካሌብን የታናሽ ወንድሙን የቄኔዝን ልጅ ጎቶንያልን አስነሣላቸው። መጽ መሳፍ 3፥15 የእስራኤልም ልጆች ወደ እግዚአብሔር ጮኹ እግዚአብሔርም ብንያማዊውን የጌራን ልጅ ናዖድን ግራኙን ሰው አዳኝ አስነሣላቸው የእስራኤልም ልጆች በእርሱ እጅ ወደ ሞዓብ ንጉሥ ወደ ዔግሎም ግብር ላኩ።
የያዕቆብ ወንድም የይሁዳ መል ቁጥር 22 እንዲ ይላል "አንዳንዶች ተካራካሪዎችንም ዉቀሱ አንዳንዶችንም ከእሳት ነጥቃችሁ አድኑ" የጌታ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ቃል መፅሀፍ ቅዱስ የተናገረውን መካድ የክርስቲያን ጠባይ አይደለም። ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በሞቱ ፍጥረታቱ ሁሉ በደሙ ከሐጢአታችን አንጽቶናል። ይህን ስራ ማንም ሊያደርገው አይችልም። ነገር ግን ሰዎች ከሐጢአት መንገድ መመለስ አንዱ የማዳን ሥራ ነው። ሐጢአት መስራት በራሱ ሞት ነውና። ከዚህ ከሐጢአት ሞት ሰዎችን በመመለስ በህይወት እንድኖሩ ማድረግ ለቅዱሳን ሰዎች የተሰጠ ስልጣን ነዉ። ስለ ሰው ሐጢአት መጸለይ የማዳን ስራ ነው። ሰዎች ወደ ቅድስና ሕይወት እንዲመለሱ ማድረግን የማዳን ስራ ነው። ነገር ግን የአዳምን በደል በሞቱ ያጠፋው ጌታችን አባታችን ኢየሱስ ከርስቶስ ብቻ በመስቀል ዲያቢሎስን ድል በመድረግ አዳነን። ለአንዴና ለመጨረሻ በእርሱ ተፈጸመ።
@And_Haymanot
ዛሬ ግን እርሱ በየቀኑ አይሞትልንም እኛ ሞቱን ስለበደላችን እንደሆነ እንመሰክራለን። በጌታ የሚያምኑ ቅዱሳን ሰዎች ለሌሎችን ሐጢአት ይጸልያሉ ከሐጢአት ሞት በጸሎት ያድናሉ።ያዕ5፡16ሐዋርያዉ ቅዱስ ጰዉሎስም እንኳን እንዲህ በማለት ተናግሮአል 'ወንድሞቼ ሆይ ስለ እኛ ጸልዩ" ወደ 1ኛ ተሰሎ 5 ፡ 25
የያዕቆብ መል 5፤20 ኃጢአተኛን ከተሳሳተበት መንገድ የሚመልሰው ነፍሱን ከሞት እንዲያድን፥ የኃጢአትንም ብዛት እንዲሸፍን ይወቅ። በዚህ የእግዚአብሔር ቃል ላይ የማዳን ስልጣን የተሰጠው ለቅዱሳን ነው። የእነ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ጥላ ብዙ በሽተኖችን አድኗል።ሐዋ5፡15 በሐዋርያው ቅዱስ ጳዉሎስ ልብስ ብዙዎች ድነዋል።ሐዋ19፡11 እራሱ ጌታችን እንዲህ በማለት የተናገረው ቃል አለ በእኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን ያደርጋል ከእኔም የበለጠ ያደርጋል በማለት ታላቅ ሥልጣንን ሰጥቶአቸዋል።ዮሐ14፡12 ጌታችን ኢየሱስ አዳኝነት የባህሪ ገንዘቡ እንደሆነ ሁሉ በርሱ ያመኑ ቅዱሳንም ይህ ጸጋ ይሰጣቸዋል ፡፡ቅዱሳን የጸጋ ማዳን ስልጣን በመጽሐፍ ቅዱስ አላቸው። ቅድሰት ቤተ ክርስቲያናችን የጌታ የባህሪ ብቸኛ አዳኝነት ታምናለች። ለቅዱሳንም የጸጋ ማዳን ስልጣን ትቀበላለች።እንደ ጌታችን ቅዱስ ቃል ትመራበታለችም። ቅዱሳን ይህ ቃል የተሰጣቸው እርሱን ተጠግተው ነው።ቃሉን ሰምተው የተሰጣቸው ልዩ ስጦታ ነው። እንደውም እርሱን ለመቀበል የመጀመሪያው መስፈርት አድርጎታል፡፡ሐዋርያው መዳን በሌላ በማንም የለም ሲል የክርቶስን ማዳን ማንም አይተካዉም፣ የሚተካውማ ቢኖር ወደዚህ ምድር ምን አስመጣው??? በኦሪቱ ብዙ መስዋት ተሰውቷል፡ ብዙ ነብያትም ነበሩ፡ አልቻሉም ምክንያቱም አዳማዊ ሀጢያት በደማቸው ስለ ነበር፡ አካላዊ ቃል፣ በርሱ ፈቃድ በአባቱ ፈቃድ እንዲሁም በባሕሪ ህይወቱ በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ ወደዚህ ምድር መጣ። እኛን ሊያድን። አዳነን ነጻም አወጣን ። ስለዚህ ይህ ድኅነት በማንም አልነበረም ወደፊትም አይኖርም፡፡ ስለዚህም ከአዳም ሀጢያት መዳን የሚቻለው #የባህሪ_አዳኝ_በሆነው_በኢየሱስ እንጂ በሌላ በማንም እንዳልሆነ በዚህ እንረዳለን ፡፡
@And_Haymanot
አሁንም ማዳን የሚችለው እርሱ ኢየሱስ ነው እርሱ ግን በፈለገው አድሮ ያድናል። እግዚአብሔርን አሰራር ማን ይከሳል። አቤሜሌክን አብርሃም ይጸልይልህና እኔ ልማርህ ያለ አምላክ ነው። የዛሬዎችን አይነት ሰዎች እንደሚሉት ቢሆን ኖሮ ለምን መንገድ ያረዝማል? ራሱ ማዳን እየቻለ እርሱ ይጸልይልህ እንዴት ይላል? ለሶስቱ ሰነፎች ኢዮብ ይጸልይላችሁና ላድናችሁ እንዴት ይላል? ራሱ በቀጥታ ማዳን ሲችል። ይህ ሁሉ እግዚአብሔር እንዲከበር ነው። ደግሞም የወዳጆቹን ክብር እግዚአብሔር መግለጥ ደስ ያሰኘዋል። በእውነት እግዚአብሔር ምስጢሩን ከአብርሃም ይሰውራልን እንዳለው ራሱ ጌታ እግዚአብሔር። እግዚአብሄር ቅዱሳንን ስለሚያደርገው አስቀድሞ ይገልጣል አማክሮም ያውቃል፡ እርሱ ምክር የሚፈልግ ሆኖ አይደለም እግዚአብሔር የቅርብ አምላክ መሆኑን መግለጥ ስለፈለገ እንጂ። እግዚአብሄር የቅርብ አብሮን ያለ ነው። ለበረከቱና ለስጦታው ወሰን የሌለው ነው። ለቅዱሳን የሰጣቸው ክብር ከዚህ አንጻር የምናየው ነው። እርሱ ፈቃዱ ስለሆነ የቅዱሳንን ስም እንጠራልን፡ እርሱ በእነርሱ አድሮ ስለሚያድን አድኑን ብለን አንማጸናቸዋልን። የእግዚአብሔርን ሐሳብ ያልተረዱ ደግሞ እግዚአብሔርን ለማስተካከል መንገዱን ጠመዝማዛ አደረግኸው አስተካክል ብለው ከጌታ ጋር ይሟገታሉ። ጌታ ግን አሰራሩ ድንቅ ነው። አዳኛችን ኢየሱስ ለማዳን የበረታ ጌታ ሁላችንንም በቸርነቱ ያድነን አሜን ! የቅዱሳኑ ምልጃ እና በረከት ይደርብን !! አሜን !
ይቆየን
______፩ ሃይማኖት_____
@And_Haymanot
ቤተክርስቲያን ባህረ ጥበባት አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት የሲኦል ደጆች አይችሏትም ቤተክርስቲያን
@And_Haymanot
#______አትታደስም______!
የሐዋርያት ጉባኤ ስለሆነች ስለአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሰላም እንማልዳለን! (መጽሐፈ ሚስጢር)
@And_Haymanot
ኦርቶዶክስ መልስ አላት
@And_Haymanot
============================
፩ ጌታ
፩ ሃይማኖት
፩ ጥምቀት ኤፌ4:5
@And_Haymanot
«መዳንም በሌላ በማንም የለም እንድንበት ዘንድ የተሰጠን ከሰማይ በታች ሌላ የለም» የሐዋ 4፥12 ይህ እውነተኛ የእግዚአብሔር ቃል ነው። ከእርሱ በቀር አዳኝ አምላክ የለም። ኢሳ 45፡21 ከኢየሱስ ውጪ አዳኝ የለም ስንል ኢየሱስ እግዚአብሔር ነው ማለታችን ነው ምክንቱም ከእግዚአብሔር ውጪ የሚያድን ስለሌለ ነገር ግን አምላካችን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በእርሱ ለአመኑትን #የጸጋ_የማዳን_ስልጣን_ለቅዱሳን ሰጥቶአቸዋል። መጽ መሳፍ 3፡9 የእስራኤልም ልጆች ወደ እግዚአብሔር ጮኹ እግዚአብሔርም የሚያድናቸውን አዳኝ የካሌብን የታናሽ ወንድሙን የቄኔዝን ልጅ ጎቶንያልን አስነሣላቸው። መጽ መሳፍ 3፥15 የእስራኤልም ልጆች ወደ እግዚአብሔር ጮኹ እግዚአብሔርም ብንያማዊውን የጌራን ልጅ ናዖድን ግራኙን ሰው አዳኝ አስነሣላቸው የእስራኤልም ልጆች በእርሱ እጅ ወደ ሞዓብ ንጉሥ ወደ ዔግሎም ግብር ላኩ።
የያዕቆብ ወንድም የይሁዳ መል ቁጥር 22 እንዲ ይላል "አንዳንዶች ተካራካሪዎችንም ዉቀሱ አንዳንዶችንም ከእሳት ነጥቃችሁ አድኑ" የጌታ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ቃል መፅሀፍ ቅዱስ የተናገረውን መካድ የክርስቲያን ጠባይ አይደለም። ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በሞቱ ፍጥረታቱ ሁሉ በደሙ ከሐጢአታችን አንጽቶናል። ይህን ስራ ማንም ሊያደርገው አይችልም። ነገር ግን ሰዎች ከሐጢአት መንገድ መመለስ አንዱ የማዳን ሥራ ነው። ሐጢአት መስራት በራሱ ሞት ነውና። ከዚህ ከሐጢአት ሞት ሰዎችን በመመለስ በህይወት እንድኖሩ ማድረግ ለቅዱሳን ሰዎች የተሰጠ ስልጣን ነዉ። ስለ ሰው ሐጢአት መጸለይ የማዳን ስራ ነው። ሰዎች ወደ ቅድስና ሕይወት እንዲመለሱ ማድረግን የማዳን ስራ ነው። ነገር ግን የአዳምን በደል በሞቱ ያጠፋው ጌታችን አባታችን ኢየሱስ ከርስቶስ ብቻ በመስቀል ዲያቢሎስን ድል በመድረግ አዳነን። ለአንዴና ለመጨረሻ በእርሱ ተፈጸመ።
@And_Haymanot
ዛሬ ግን እርሱ በየቀኑ አይሞትልንም እኛ ሞቱን ስለበደላችን እንደሆነ እንመሰክራለን። በጌታ የሚያምኑ ቅዱሳን ሰዎች ለሌሎችን ሐጢአት ይጸልያሉ ከሐጢአት ሞት በጸሎት ያድናሉ።ያዕ5፡16ሐዋርያዉ ቅዱስ ጰዉሎስም እንኳን እንዲህ በማለት ተናግሮአል 'ወንድሞቼ ሆይ ስለ እኛ ጸልዩ" ወደ 1ኛ ተሰሎ 5 ፡ 25
የያዕቆብ መል 5፤20 ኃጢአተኛን ከተሳሳተበት መንገድ የሚመልሰው ነፍሱን ከሞት እንዲያድን፥ የኃጢአትንም ብዛት እንዲሸፍን ይወቅ። በዚህ የእግዚአብሔር ቃል ላይ የማዳን ስልጣን የተሰጠው ለቅዱሳን ነው። የእነ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ጥላ ብዙ በሽተኖችን አድኗል።ሐዋ5፡15 በሐዋርያው ቅዱስ ጳዉሎስ ልብስ ብዙዎች ድነዋል።ሐዋ19፡11 እራሱ ጌታችን እንዲህ በማለት የተናገረው ቃል አለ በእኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን ያደርጋል ከእኔም የበለጠ ያደርጋል በማለት ታላቅ ሥልጣንን ሰጥቶአቸዋል።ዮሐ14፡12 ጌታችን ኢየሱስ አዳኝነት የባህሪ ገንዘቡ እንደሆነ ሁሉ በርሱ ያመኑ ቅዱሳንም ይህ ጸጋ ይሰጣቸዋል ፡፡ቅዱሳን የጸጋ ማዳን ስልጣን በመጽሐፍ ቅዱስ አላቸው። ቅድሰት ቤተ ክርስቲያናችን የጌታ የባህሪ ብቸኛ አዳኝነት ታምናለች። ለቅዱሳንም የጸጋ ማዳን ስልጣን ትቀበላለች።እንደ ጌታችን ቅዱስ ቃል ትመራበታለችም። ቅዱሳን ይህ ቃል የተሰጣቸው እርሱን ተጠግተው ነው።ቃሉን ሰምተው የተሰጣቸው ልዩ ስጦታ ነው። እንደውም እርሱን ለመቀበል የመጀመሪያው መስፈርት አድርጎታል፡፡ሐዋርያው መዳን በሌላ በማንም የለም ሲል የክርቶስን ማዳን ማንም አይተካዉም፣ የሚተካውማ ቢኖር ወደዚህ ምድር ምን አስመጣው??? በኦሪቱ ብዙ መስዋት ተሰውቷል፡ ብዙ ነብያትም ነበሩ፡ አልቻሉም ምክንያቱም አዳማዊ ሀጢያት በደማቸው ስለ ነበር፡ አካላዊ ቃል፣ በርሱ ፈቃድ በአባቱ ፈቃድ እንዲሁም በባሕሪ ህይወቱ በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ ወደዚህ ምድር መጣ። እኛን ሊያድን። አዳነን ነጻም አወጣን ። ስለዚህ ይህ ድኅነት በማንም አልነበረም ወደፊትም አይኖርም፡፡ ስለዚህም ከአዳም ሀጢያት መዳን የሚቻለው #የባህሪ_አዳኝ_በሆነው_በኢየሱስ እንጂ በሌላ በማንም እንዳልሆነ በዚህ እንረዳለን ፡፡
@And_Haymanot
አሁንም ማዳን የሚችለው እርሱ ኢየሱስ ነው እርሱ ግን በፈለገው አድሮ ያድናል። እግዚአብሔርን አሰራር ማን ይከሳል። አቤሜሌክን አብርሃም ይጸልይልህና እኔ ልማርህ ያለ አምላክ ነው። የዛሬዎችን አይነት ሰዎች እንደሚሉት ቢሆን ኖሮ ለምን መንገድ ያረዝማል? ራሱ ማዳን እየቻለ እርሱ ይጸልይልህ እንዴት ይላል? ለሶስቱ ሰነፎች ኢዮብ ይጸልይላችሁና ላድናችሁ እንዴት ይላል? ራሱ በቀጥታ ማዳን ሲችል። ይህ ሁሉ እግዚአብሔር እንዲከበር ነው። ደግሞም የወዳጆቹን ክብር እግዚአብሔር መግለጥ ደስ ያሰኘዋል። በእውነት እግዚአብሔር ምስጢሩን ከአብርሃም ይሰውራልን እንዳለው ራሱ ጌታ እግዚአብሔር። እግዚአብሄር ቅዱሳንን ስለሚያደርገው አስቀድሞ ይገልጣል አማክሮም ያውቃል፡ እርሱ ምክር የሚፈልግ ሆኖ አይደለም እግዚአብሔር የቅርብ አምላክ መሆኑን መግለጥ ስለፈለገ እንጂ። እግዚአብሄር የቅርብ አብሮን ያለ ነው። ለበረከቱና ለስጦታው ወሰን የሌለው ነው። ለቅዱሳን የሰጣቸው ክብር ከዚህ አንጻር የምናየው ነው። እርሱ ፈቃዱ ስለሆነ የቅዱሳንን ስም እንጠራልን፡ እርሱ በእነርሱ አድሮ ስለሚያድን አድኑን ብለን አንማጸናቸዋልን። የእግዚአብሔርን ሐሳብ ያልተረዱ ደግሞ እግዚአብሔርን ለማስተካከል መንገዱን ጠመዝማዛ አደረግኸው አስተካክል ብለው ከጌታ ጋር ይሟገታሉ። ጌታ ግን አሰራሩ ድንቅ ነው። አዳኛችን ኢየሱስ ለማዳን የበረታ ጌታ ሁላችንንም በቸርነቱ ያድነን አሜን ! የቅዱሳኑ ምልጃ እና በረከት ይደርብን !! አሜን !
ይቆየን
______፩ ሃይማኖት_____
@And_Haymanot
ቤተክርስቲያን ባህረ ጥበባት አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት የሲኦል ደጆች አይችሏትም ቤተክርስቲያን
@And_Haymanot
#______አትታደስም______!
የሐዋርያት ጉባኤ ስለሆነች ስለአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሰላም እንማልዳለን! (መጽሐፈ ሚስጢር)
@And_Haymanot
ኦርቶዶክስ መልስ አላት
@And_Haymanot
============================
፩ ጌታ
፩ ሃይማኖት
፩ ጥምቀት ኤፌ4:5
🙏1