፩ ሃይማኖት
8.91K subscribers
246 photos
29 videos
21 files
96 links
ኦርቶዶክሳዊ ምላሾች
የሚቀርቡበት፡፡
👉"፩ ኃይማኖት"👈
@And_Haymanot
ቤተክርስቲያን ባህረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት
የገሀነም ደጆች አያናውጧትም
✞ እ...ና...ታ...ች...ን
#አ__ት__ታ__ደ__ስ__ም፡፡
@And_Haymanot
ኦርቶዶክስ መልስ አላት፡፡
ለአስተያየት
@And_Haymanot_bot

፩ ሃይማኖት ኤፌ 4፥5
Download Telegram
አሳዛኝ ዜና!! ሼር!
""ኢትዮጵያ"" የሚለው የመፅሐፍ ቅዱስ ስም ከመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንዲወጣ ተደረገ።

@And_Haymanot

ኢትዮጵያ ሀገራችን ከሠሞኑ ሠፊ ምዕመናን(አማኞች) ያሉባት ሀገር ተብላ በቀዳሚነት ተቀምጣለች፡፡ ከህገ ልቦና ጀምሮ ለአምላኳ ቦታ ያላት ቅድስት ሀገር ናት፡፡ እንደሚታወቀው በመፅሃፍ ቅዱስ ውስጥ ""ኢትዮጵያ"" የሚለው ስም ከ40 በላይ ቦታዎች ላይ ተጠቅሷል። ዛሬ ላይ ግን ይህንን ስም ለማጥፍት ዘምነናል፣ አድገናል የሚሉት አውሮፓዊያን (ሉተራዊያን) ቅድስት ሀገር
ኢትዮጵያ ላይ ዘመቻ ከፍተዋል እነሱም የጀርመን ሉተራን ቤተክርስቲያን ናቸው"" #ኢትዮጲያ"" የሚለውን ስም"" #ኩሽ""
እንጂ ኢትዮጵያ አይባልም ብለው ወስነዋል። ለመሆኑ መፅሐፍ ቅዱስን ማንም እንደፈለገው ተነስቶ የሚያስተካክለው መፅሐፍ ነው? እንደራሳቸው ህገ መንግስት ሲፈልጉ የሚፅፉት ሳይፈልጉ የሚፍቁት የህገ መንግስታቸው መፅሐፍ ነው?
@And_Haymanot
ማንም ቢሆን መፅሐፍ ቅዱስ ላይ መጨመርም ሆነ መቀነስም አይችልም
ይህንን መፅሐፍ ቅዱስ በጥብቅ! ያስጠነቅቀናል እንዲህ ሲል የዮሐንስ ራእይ - ምዕራፍ 22÷18 በዚህ መጽሐፍ የተጻፈውን የትንቢት ቃል ለሚሰማ ሁሉ እኔ እመሰክራለሁ፤ ማንም በዚህ
ላይ አንዳች ቢጨምር እግዚአብሔር በዚህ መጽሐፍ የተጻፉትን መቅሠፍቶች ይጨምርበታል፤ 19 ማንምም በዚህ በትንቢት መጽሐፍ ከተጻፉት ቃሎች አንዳች ቢያጎድል፥ በዚህ መጽሐፍ ከተጻፉት ከሕይወት ዛፍና ከቅድስቲቱ ከተማ እግዚአብሔር ዕድሉን ያጎድልበታል። መፅሀፍ ቅዱስ እንዲህ በጥብቅ እያስጠነቀቀ እና ማነው "ኢትዬጵያ" የሚለውን የመፅፍ ቅዱስ ቃል እንዲፍቁ ስልጣን የሰጣቸው? ለምሳሌ ከተፍቁት ውስጥ መዝሙረ ዳዊት
- ምዕራፍ 68÷31 ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች። የሚለው "ኩሽ" በሚል እንዲቀየር ""ኢትዮጵያ""" የሚለው እንዲፍቅ አድርገውታል።ሌላው ትንቢተ ኤርምያስ
- ምዕራፍ 13÷23 በውኑ ኢትዮጵያዊ መልኩን ወይስ ነብር ዝንጕርጕርነትን
ይለውጥ ዘንድ ይችላልን? የሚለወን ይህንንም ሀይለ ቃል ፍቀው አውጥተውታል "ኢትዮጵያ" የሚለውን የመፅሐፍ ቅዱስ ስም። እና በግልፅ የኢትዮጵያን ስም ከመፅፍ ቅዱስ ውስጥ
እየተለቀመ እንዲጠፍ ሆነ ተብሎ ለማጥፍት የቴሰረ የነጮች የተለመደ የክፍት ውጤት ነው። በርግጥ መፅሀፍ ቅዱስን አሻሻልን እያሉ ሲጨምሩ እና ሲቀንሱ አሁን የመጀመሪያቸው አይደለም ከዚህ ቀደም ብዙ ምእራፎችን ለራሳቸው
እንደሚመቻቸው ሲደልዙ ኖረዋል። በዚህም ብዙ ህገ እግዚአብሔርን ፍቀዋል ከብዙ በጢቂቱ የሰዶምን ሀጢያት እርኩሰት ቤተክርስቲያን በሚሉት ቦታ ላይ ወንድን ከወንድ ሴትን
ከሴት ቆመው ሲያጋቡ አይተናል ሌላም ብዙ... በዚህ መጨመር መቀነስ ጠንቅም ሰዎች ትክክለኝ እና ሙሉ የመፅሐፍ ቅዱስን ትምህርት እና መልእክት እንዳያገኙ ሆነዋል! በዚህም
ሳቢያ ብዙዎች ባልተረዱት (የፈረንጅ እምነት) ውስጥ ገብተው ሲባክኑ አይተናል።
@And_Haymanot
እኛ ግን እድለኞች ነን የኢትዮጵያ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መፅፍ ቅዱስን ሳይጨመረ ሳይቀነስ
እንደተረከብነው ከቅዱሳን ሀዋሪያት ለትውልድ አስተላልፍልናለች። ክብር ምስጋና ለአባቶቻችን እና ለቤተክርስቲያን ሊቃውንት ይሁን ብራና ፍቀው፣ፊደል ቀርፀው ላይ ታች ብለው.... ሳይነካካ ላቆዩልን። የነጮቹ የተንኮል አላማ ግን እንዲህ በቀላሉ የሚተው አይደለም የኛን ብራና መፃህፍት ስርቀው አውሮፓ አግዘው ተርጉመው ከመጠቀም ጅምሮ እስከ ዶክትሬት ድረስ ትምህርት የሚሰጡባቸው መፃህፍት ናቸው።
የኛን ታሪክ እና እሴት ለማጥፍት ግን ሌት ተቀን እየዳከሩ ነው! ሀገሩን እና ሀይማኖቱን የሚወድ ማንም ኢትዮጵያዊ ሊያወግዘው የሚገባ ድርጊት ነው። ያለንን ንፁህ መፅሐፍ ቅዱስም
ሳይጨመር ሳይቀነስ እኛ እንደተረከብነው ለትውልድ የማስተላለፍ ግዴታ የሁላችንም ነው። ሼር በማድረግ ሁሉም አውቆ እንዲጠነቀቅ እንዳርግ!! አሁንም እንደቃሉ


ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች።
@And_Haymanot
@And_Haymanot
የቀላል አማርኛው መዘዝ

@And_Haymanot

ተወዳጆች ትላንት ባቀረብንላችሁ መረጃ ሉተራውያኑ ኢትዮጵያ የሚለውን ስም ከመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ለመፋቅና ኩሽ በሚል እየተኩ እንደሆነ አቅርበንላችኋል [ https://tttttt.me/And_Haymanot/394 ]

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በቀላል አማርኛ እንዲሁም ለመረዳት ቀላል በሚል ህያው ቃሉን እንደሚመቻቸው ሲቀይሩ አይተናል ለዛሬም ጥቂቶቹን ልናቀርብላችሁ ወደድን
@And_Haymanot

በቅድስናው ስፍራ ለእግዚአብሔር ስገዱ >> ይላል ።
ይህ እንግዲህ ስለ ቅድስት ቤ/ክ ተሚናገር ስለሆነ አልተመቻቸውምና በቀላል አማርኛቸው ላይ
👉🏻 << ዝግዚአብሔር ሲገለጥ ስታዩት ስገዱለት >> ብለውታል ።

ሌላው ቀላል አማርኛ ተብሎ በውጣው መጽሐፍ ቅዱስ ላይ የእመቤታችንን ዘላለማዊ ድንግልና አንቀበልም ለሚለው ክሕደታቸው መግቢያ እንዲሆናቸው
<<ሊገልጣት አልወደደም >> የሚለውን
👉🏻👀 ሊያጋልጣት አልወደደም >> ብለውታል ። ማቴ 1÷19 ።
እንዲሁም ስለ እመቤታችን በመዝ 44÷16 ላይ እንዲህ ተብሉ ነው የተጻፈው፦
<< በአባቶችሽ ፋንታ ልጆች ተወለዱልሽ ፤ በምድርም ሁሉ ላይ ገዥዎች አድርገሽ ትሾሚያቸዋለሽ፤ ለልጅ ልጅ ሁሉ ስምሽን ያሳስባሉ>> ይላል ።
መዝሙረኛው አሁንም <<መሰረቶቻ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው ሲል ነው የተቀኝው ።

👉🏻👀የተቀደሱ ተራሮች የተባሉት እነ ኖኅ ፣ አብርሃም ፣ይስሐቅ ፣ ያዕቆብ ••• በካላም ኢያቄምና ሐና ሲሆኑ ሁሉም ቅዱሳን ናቸው።

የእርሷ ቅድስና ግን ከሁሉም በላይ ነውና ቅድስተ ቅዱሳን ትባላለች። እናም
በአባቶችሽ ፍንታ ልጆች ተወለዱልሽ፤ በምድርም ሁሉ ላይ ገዥዎች አድርገሽ ትሾሚያቸዋለሽ>> ሲል የሃይማኖት አባቶቻን እነ አብርሃምን ፣ እነ ዳዊትን ፣ እነ ኢያቄምን መስለው እግዚአብሔርን ደስ የሚያስኙትን ከእርሷ በኋላ የሚመጡትን የሃይማኖት ልጆቻን ካህናት፣ ሊቃውንት ፣ጳጳሳት •••አድርጋ እንደምትሾማቸው ለማስረዳት ነው ቅዱስ ዳዊት ይህን ማለቱ ።
ይህንን የተስጣትን ሥልጣን እነርሱ ይሽሩት ይመስል መናፍቃኑ መሠረቶቻ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው>> የሚለውን ቃል << መስረቶቹ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው >> በማለት ቀይረውታል ።

በአባቶችሽ ፋንታ ልጆች ተወለዱልሽ ፣ በምድርም ሁሉ ላይ ገዥዎች አድርገሽ ትሾሚያቸዋለሽ ለልጅ ልጅ ሁሉ ስምሽን ያሳስባሉ>> የሚለው ደግሞ👉🏻መናፍቃኑ በ1984 ዓ.ም ባሳተሙት ዳዊትና አዲሱ የ1993 መደበኛ ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ ላይ በወንድ አንቀጽ አድርገው << በአባቶችህ ፋንታ ልጆች ተወለዱልህ ፤ በምድርም ሁሉ ላይ ገዥዎች አድርጋህ ትሾማያቸዋለህ ለልጅ ልጅ ሁሉ ስምህን ያሳስባሉ >> በማለት ነው የለወጠት ።

ይህ ግን ብቅዱስ ቃሉ ላይ ማመፅና ማሾፍ እንጂ ክርስቶስን ማክበር አይደለምና በቃሉ ለሚነግዱ ሁሉ ልብ ይስጥልን እኛንም በአንዲት ሀይማኖቷ በተዋህዶ ያጽናን፡፡
በዚህ ርዕስ ወደፊት በሠፊው እንመለስበታለን
@And_Haymanot
፩ ሃይማኖት ተዋህዶ
join
@And_Haymanot
@And_Haymanot