፩ ሃይማኖት
9K subscribers
246 photos
29 videos
21 files
96 links
ኦርቶዶክሳዊ ምላሾች
የሚቀርቡበት፡፡
👉"፩ ኃይማኖት"👈
@And_Haymanot
ቤተክርስቲያን ባህረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት
የገሀነም ደጆች አያናውጧትም
✞ እ...ና...ታ...ች...ን
#አ__ት__ታ__ደ__ስ__ም፡፡
@And_Haymanot
ኦርቶዶክስ መልስ አላት፡፡
ለአስተያየት
@And_Haymanot_bot

፩ ሃይማኖት ኤፌ 4፥5
Download Telegram
የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ዕርገት አስመልክቶ በጥያቄና መልስ የቀረበ ጽሑፍ ነው። እናንተም ተጋበዙልኝ።

ጥያቄ ፩፦ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ድንግል ማርያም ዕርገት አይናገርም። ታድያ "ዐረገች" ማለታችሁ ስህተት አይኾንም?

መልስ ፩፦ አንድ ነገር መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ስላልተጻፈ ብቻ "ሀሰት" ሊባል አይችልም። ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ የአምስት ሺሕ ዓመታትን ታሪክ የያዘ እንደ መኾኑ ኹሉንም ታሪኮች በአንድነት ጠቅልሎ ይይዛል ማለት ዘበት ነው። የአንድ ንጉሥ ታሪክ እንኳን እጅግ በጣም ብዙ ገጽ መጽሐፍ ሊወጣው እንደሚችል እናውቃለን። ታድያ "በግልጽ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ስላልተጻፈ ሀሰት ነው" ልንል የምንችለው እንዴት ነው?

አንድም በመጽሐፍ ቅዱስ መገደብ አንችልም። ምክንያቱም "መጽሐፍ ቅዱስ እንደ እገሌ ከሰማይ ወረደ" ብለን አናምንም። መጻሕፍቱ በአበው፣ በነቢያትና በሐዋርያት እጅ በተለያየ ጊዜና በተለያየ ቦታ መጻፋቸውን እናውቃለን። ከእነዚህ ውጪም በሐዋርያቱ ስም የተጻፉ የሀሰት መጻሕፍትም ነበሩ። እነዚህን እውነተኛዎቹንና ሀሰተኛዎቹን መጻሕፍት ከዓለም ያሰባሰቡትና የለዩት አባቶች ናቸው። ለመጻሕፍቱም ቅድስና የሰጡት እነርሱ ናቸው።

በመኾኑም መጽሐፍ ቅዱስን ለማመን የአባቶችን አማናዊነት መቀበል ግድ ይለናል። ካልኾነ ግን እነርሱ የራሳቸውን አስተምህሮ ተከትለው እውቅና የሰጧቸው ቅዱሳት መጻሕፍት በጠቅላላ ጥርጣሬ ውስጥ ይገባሉ። ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስን የሚያምን ኹሉ በእመቤታችን ዕርገት ማመን ይጠበቅበታል። ምክንያቱም ለመጻሕፍቱ ቅድስና እውቅና የሰጡ አባቶች በጠቅላላ በእመቤታችን ዕርገት ያምናሉ።

ጥያቄ ፪፦ እውን ድንግል ማርያም ዐርጋ ቢኾን ኑሮ ሐዋርያቱ በግልጽ ያልተናገሩትና በመጽሐፋቸው ላይ ያልጻፉት ለምንድን ነው?
......
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን 'ኢየሱስ ያድናል' ብላ ስትናገር በእውነተኛው (አማናዊው) የጌታ ሥጋና ደም በማመን እንጂ መታሰቢያ ነው በማለት አይደለም። ልዩነቱ ግልጽ ነው!
መልካም ወጣት

ነፍስህን ከቅድስና ህይወት ማሸሽህ ሳይታይህ ስጋህን ከሱስ ለማራቅ የምትታለልበት አዲሱ ጸረ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ፕሮጀክት መሆኑን አውቀህ ንቃ

🙏 ቅዱስ ወጣት ሁን 🙏
@And_Haymanot
በስፋት እንመጣበታለን
፩ ሃይማኖት
Photo
+ ድንገት የተበጠሰ ገመድ +

የደብረ ዳሞ ገዳም በገመድ ብቻ የሚወጣ እጅግ ጥንታዊ ገዳም ነው:: ይህንን አቡነ አረጋዊ በዘንዶ የወጡትን ታላቅ ገዳም ለመውጣት በግንባታው ወቅት በአፄ ገብረ መስቀል የተሠራ ደረጃ ነበረው:: ሆኖም አቡነ አረጋዊ ደረጃውን ዳህምሞ (አፍርሰው) ብለው በማዘዛቸው እስከ አሁን ድረስ በገመድ የሚወጣበት ገዳም ሆኖአል::

የደብረ ዳሞ መውጫ ገመድ እጅግ ወፍራም ሲሆን እስከ አሁን ድረስ በብዙ ሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተንጠላጥለው ወጥተው ወርደውበታል:: ይህ እጅግ ወፍራም ገመድ ለዘመናት ሲያገለግል ተበጥሶ ሰው ጥሎ አያውቅም:: በታሪክ የማይዘነጋና መሃል ላይ የተበጠሰበትና ሰው የጣለበት ቀን አለ:: (የዲያቢሎስ መተናኮል ነው የሚል አለ)

በዚያ ቀን በተበጠሰው ገመድ ላይ የወረደው መንገደኛ ጻድቁ አባ ተክለ ሃይማኖት ነበሩ:: መነኮሳቱን ተሰናብተው በዚያ ገመድ ሲወርዱ ተበጥሶ የማያውቀው ገመድ ድንገት ተበጠሰ:: ከላይ የሚያዩት አባቶች ቁልቁል እያዩ በድንጋጤ ጮኹ:: ሆኖም እግዚአብሔር ለጻድቁ የብርሃን ክንፍ ሠጥቶአቸው ከተበጠሰው ገመድ ተለይተው እንደ መልአክ በርረው ሁለት ሺህ ክንድ ያህል ወርደው መሬት ላይ አረፉ:: ባረፉባት ሥፍራም ቤተ ክርስቲያን ተሠራባት::

ወዳጄ በሕይወትህ ድንገት የተበጠሰ ገመድ የለም? ሳትጠብቀው የተበጠሰ ገመድ ማንም ላይ ሳይበጠስ አንተ ላይ የጨከነ ገመድ የለም? ምን ዓይነት ገመድ አትበለኝ:: የእንጀራ ገመድ የኑሮ ገመድ የትምህርት ገመድ የፈለግኸው ገመድ በለው:: እሱን ተጠምጥመህ ይዘህ ወደ አንዳች ቦታ ለመድረስ የተማመንክበት ተስፋህን ሙሉ በሙሉ የጣልክበት ገመድ የለም? ድንገት ተበጥሶ ዙሪያው ገደል አልሆነብህም? ሰዎች ማንም ላይ ያልተበጠሰ ገመድ አንተ ላይ ሲበጠስ አይተው "ምኑ ዕድለ ቢስ ነው?" ብለው የተደነቁብህ እንደ ቅዱስ ጳውሎስ "ከባሕር አደጋ ተርፎ ዕባብ የነደፈው እንዴት ኃጢአተኛ ቢሆን ነው?" ብለው በትዝብት ዓይን እንዲያዩህ ያደረገ በሕይወትህ ሳታስበው ተበጥሶ ዙሪያው ገደል የሆነ ሥፍራ ላይ የጣለህ የሕይወት ገመድ ይኖር ይሆናል::

በዕድልህ አትማረር በሕይወትህ ድንገት የሚበጠስብህ ገመድ የምትወድቅበት ሳይሆን ክንፍ አውጥተህ የምትበርበት ነው:: ፈጣሪ የተማመንክበትን የምታየውን ገመድ እንዲበጠስብህ ከፈቀደ ያላየኸውን ክንፍ ሊሠጥህ እንጂ ሊጥልህ አይደለም:: የሕይወትህን ገመድ የተበጠሰበትን ቀን "እግዚአብሔር ለመልካም አሰበው" ብለህ እንደ ዮሴፍ ታመሰግንበታለህ::
ገመድህን የሚበጥሰው ከገደል ሊጥልህ ሳይሆን በክንፍ አብቅሎ ሊተክልህ ነው:: የሚተክልህ በበረሃ ሳይሆን በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ ነው:: ተራ ተክል የምትሆን እንዳይመስልህ:: የሃይማኖት ተክል (ተክለ ሃይማኖት) ትሆናለህ:: ተክለ መንፈስ ቅዱስ ተክለ ወልድ ተክለ አብ ትሆናለህ:: አብ የተከለው ደግሞ አይነቀልም!

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ታኅሣሥ 24 2013 ዓ ም
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
👍1
በቅዱሳን ስም መነገድን እንቃወማለን
*** SHARE ***
@And_Haymanot
+ ዘኬዎስ አጭር ባይሆን +

ዘኬዎስ በማጠሩ ምክንያት በኢያሪኮ እያለፈ ያለውን ክርስቶስን ለማየት ተቸገረ:: ሕዝቡ ብዙ ነውና የቆሙት ሁሉ ጌታን ከማየት ከለሉት:: የሾላ ዛፍ ላይ ወጥቶ ጌታን ለማየት ሲሞክር ጌታ አሻቅቦ አየው::

እሱ ዛፍ ላይ ጌታን ሊያይ እንጂ ሊታይ አልወጣም:: ጌታ ሊታዩ ከሚሞክሩ ይልቅ ሊያዩት የሚሹትን ይወዳልና ዘኬዎስን ጠራው::

ከምድር ቆመን ዓይናችንን አንጋጥጠን ማረን የምንለው ጌታ ዘኬዎስን ከምድር ሆኖ ወደ ላይ እያየ ና ልማርህ አለው:: "ዛሬ በቤትህ እውል ዘንድ ይገባኛል" አለው:: ጌታ ወደ ቤቱ ገባ:: ለዘኬዎስ ቤት መዳን ሆነለት::

ዘኬዎስ አጭር ባይሆን ኖሮ ከሰዎች ጋር እየተጋፋ ጌታን ያይ ይሆናል እንጂ በጌታው ዓይን ለመታየት የሚያበቃ ትጋት አያሳይም ነበር:: ምናልባትም ሰዎችን ገለል በሉ እያለ በኩራት ሲጋፋ ከአንዱ ጋር ሲጣላ ሊቆይ ይችል ነበር::

ዘኬዎስ አጭር ባይሆን ከዛፍ ላይ አይወጣም ነበር::
ዘኬዎስ አጭር ባይሆን የሠራዊት አምላክ ወደ ቤቱ አይገባም ነበር:: በኪሩቤል ላይ የሚቀመጠው ንጉሥ በቤቱ ወንበሮች ላይ የተቀመጠው ዘኬዎስ በማጠሩ ምክንያት ነው:: የዘኬዎስ ነፍስ የዳነው በቁመቱ ማጠር ነበር:: እግዚአብሔር የመዳኑን ቀን የቆረጠለት ቁመቱን ሲያሳንሰው ነበር:: በምድር በመጽሐፍ ቅዱስ በሰማይ በሕይወት መዝገብ ስሙ የተጻፈው ዘኬዎስ አጭር በመሆኑ ነው::

ስለ ቁመት የማወራ እንዳይመስልህ:: እግዚአብሔር ለነፍሳችን መዳን የሚያሳጥርብን ብዙ ነገር አለ::
እንደ ዘኬዎስ ቁመትህ አጭር ባይሆን የሚያጥርህ ነገር ግን አይጠፋም::

ይሄ ጎደለኝ የምትለው ከሰዎች አነስኩበት የምትለው ነገር አንዳች ነገር የለም? እሱን ማለቴ ነው::
ይሄ ይጎድለኛል ከሰው አንሳለሁ እያልክ አትማረር::
እጥረትህ መክበሪያህ ነው:: ጉድለትህም መዳኛህ ነው::

እግዚአብሔር ያጎደለብህ የመሰለህ ነገር ወደ ዛፍ እንድትወጣ ምክንያትህ ይሁን:: በጉድለትህ እንደ ዘኬዎስ ከፍ በልበት:: ያኔ ሰዎች አንተን አንጋጠው ከማየት ውጪ አማራጭ አይኖራቸውም::
ፈጣሪ በፍቅሩ ይይህ እንጂ ሰዎች ወዳንተ ያዘነብላሉ:: በቤትህ መዳን ይሆንልሃል:: ከዚያም ስላጠረህ ስለጎደለህ ነገር ፈጣሪህን ስታመሰግነው ትኖራለህ::

እመነኝ አንዳንድ ጉድለቶች እድሎች ናቸው::
ዘኬዎስ አጭር ባይሆን ይሄኔ በሾላው ዛፍ ጥርሱን እየፋቀ ይቀር ነበር::


©ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ

@And_Haymanot
👍2
መስቀል በኢትዮጵያ


✞ ተወዳጆች በቅድሚያ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሰን!!! አደረሳችው ✞


❖ "ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ" ገላ 6፥14 ❖

  @And_Haymanot

ኢትዮጵያ ሃገራችን የክርስቲያን ደሴት ከመባሏም በላይ የእግዚአብሔር ቸርነት ያላት የበረከት የረድኤት ሀገር ናት ይኽም የጌታ ግማደ መስቀል በ14ኛው ክፍለ ዘመን በአጼ ዳዊት ዘመነ መንግሥት ወደ ኢትዮጵያ መጥቷል

☞ አመጣጡም የኢትዮጵያ ነገሥታት የግብጽ ካሊፋዎች ሀገረ ገዥዎች በኃይል ይጋፏቸው ስለነበር የግብጽ ሀገር ገዥዎች ደግሞ የግብጽን ክርስቲያኖች (ኮፕታውያን) ያሰቃዩአቸው ነበር ስለዚህ ይህ አለመግባባት እንዲወገድና የግብጽ ክርስቲያኖች ዕረፍት እንዲያገኙ በማሠብ የኢየሩሳሌሙ ፓትርያርክ አቡነ ዮሐንስ ከግብጽ የአህናስ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቄርሎስንና አባ ማዕምር የሚባሉ ሉዑካን ወደ ኢትዮጵያ መጡ በዚያን ጊዜ አጼ ሠይፈ አርዕደ አርፈው የልጃቸው ልጅ አጼ ዳዊት ነግሠው ነበር እነዚህ ልዑካን በኢትዮጵያውያንና በግብጻውያን ነገስታት መካከል ያለውን ቅራኔ አስወግደው ሲመለሱ አጼ ዳዊት በነበራቸው ቀና መንፈስ አቡነ ዮሐንስ የኢየሩሳሌሙ ፓትርያርክ እሌኒ ንግስት አስቆፍራ ከአስወጣችው ከጌታ ግማደ መስቀል ክፋይ ለበረከት እንዲልኩላቸው ወርቅ፣ አልማዝ፣ ገጸ በረከት አስጭነው ወደ ኢየሩሳሌም መልዕክተኞችን ላኩ መልእክተኞቹም ኢየሩሳሌም ደርሰው ገጸ በረከቱን ለፓትርያርኩ ከሰጡ በኃላ ፓትርያርኩ፦

፩፦ የጌታን ግማደ መስቀል፣ የቀኝ በኩሉን ክፋይ
፪፦ ጌታ ላይ አይሁድ የጫኑበትን (ያረጉለት) አክሊለ ሶኩን
፫፦ ቅዱስ ሉቃስ የሳላት ምስለ ፍቁር ወልዳ የእመቤታችን ስዕል ላኩላቸው።

መልዕክተኞቹም ተቀብለው ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ አጼ ዳዊት መልእክተኞቹን ለመቀበል ሲሄዱ የተቀመጡባት ባዝራ ፈረስ ጥላቸው መሞታቸውን ታሪካቸው ይናገራል መስቀሉ ወደ ሀገራችን የገባው #መስከረም 10 ቀን ነው መስቀሉ የተቀመጠው መስከረም 21 ቀን በወሎ ክፍለ ሃገር በግሸን ማርያም ነው

በዚህ ሁኔታ የገባው የጌታ መስቀል ዛሬም ድረስ ተአምራዊ ነው ይህም ሀገራችን ኢትዮጵያን ለመስቀል ያላትን ታላቅ አክብሮትና ፍቅር የገለጸችበት አብይ ምስክር ነው ሕዝቡም ለመስቀል ያለውን ፍቅርና አክብሮት ለመግለጽ ይነቀሰዋል፣ በልብሱ ላይ ይጠልፈዋል ይህ ደግሞ የሚያሳየው መስቀል በኢትዮጵያውያን ዘንድ ምን ያህል ክብር እንዳለው ነው።


☞ ከተለያዩ ማዕድናት የሚሰራው መስቀል ትርጉም፦

መስቀል ከተለያዩ ማዕድናት ሊሰራ ይችላል መስቀሉ የሚሰራባቸው ማዕድናት የራሳቸው ባህርያት እንዳላቸው ሁሉ ምሳሌውን ለመግለጽ ብቁ ናቸው ብለው አባቶች ያስቀመጡትን ማየት ይገባል።

ከብረት ቢሰራ ክርስቶስ የተቸነከረበትን ችንካር ለማመልከት ነው
ከወርቅ ቢሰራ ወርቅ ንጹህ እንደሆነ ክርስቶስን ንጹሀ ባህርይ እድፈት የሌለብህ ጽኑ አንተ ነህ ብሎ ለመመስከር ነው
ከእንጨት ቢሰራ ክርስቶስ የተሰቀለው በዕጽ በእንጨት ላይ መሆኑን ለማመልከት ነው
ከብር ቢሰራ ተስፋን፣ ዕድልን ያመለክታል ይኸውም ክርስቶስ ለሰው ልጆች ሁሉ የሆነ ቤዛን በደሙ ከፍሏልና በእርሱ ተስፋ እንድናደርግ ያመለክተናል


መስቀል ለእኛ ክርስቲያኖች ኃይላችን፣ ጽንዐችን፣ ቤዛችን፣ መድኃኒታችን ነው "የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና" /1ኛ ቆሮ 1፥18/ ለቅዱስ መስቀል ክብርና ስግደት ይገባል ምክንያቱም በመዝ 131፥7 ላይ "እግሮቹ በሚቆሙበት ሥፍራ እንሰግዳለን" ተብሎ ተጽፏልና።

❖ ሞኝነት ነው ለሚጠፉት መሰናከያቸው
❖ በዓለም ጥበብ ለሚኖሩ እውነት ተስኗቸው
❖ ለጠቢብ ሰው በመንፈስ የሚኖር
❖ የመዳን ቀን እውነተኛ አርማ ነው
❖ ከገሃነም እሳት የሚያድን ነው

ያለ መስቀል ክርስትና ያለ ተጋድሎ ቅድስና የለም!!!

✞ አምላከ ቅዱሳን የመስቀሉን ፍቅር በልባችን ጽላት ላይ ይጻፍልን!!! አሜን ✞✞✞

ኦርቶዶክሳዊ_ምላሾች_እና_መረጃ_ብቻ_የሚቀርቡበት  
           👇👇👇
   አንድ ሃይማኖት
        `ተዋህዶ´´´
   @And_Haymanot
           JOIN
   @And_Haymanot
   @And_Haymanot
     ~Share~
   @And_Haymanot
   @And_Haymanot
      ~JoIN~
   @And_Haymanot
   @And_Haymanot
         ፩  ሃይማኖት
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መልስ አላት
      @And_Haymanot
  የአበው ሃይማኖት አትታደስም፡፡
ጽዮን በመፅሐፍ ቅዱስ ማን ናት??

@And_Haymanot

የተሐድሶ መናፍቃን ከሚያነሱት መከራከሪያ አንዱ በትንቢተ ኢሳያስ 60 ፤14 የተፃፈው ቃል ነው “”””የአስጨናቂዎችሽም ልጆች አንገታቸውን ደፍተው ወደ አንቺ ይመጣሉ፥ የናቁሽም ሁሉ ወደ እግርሽ ጫማ ይሰግዳሉ የእግዚአብሔርም
ከተማ፥ የእስራኤል ቅዱስ የሆንሽ ጽዮን ይሉሻል።””””ይሄ ቃል
የተነገረው ለድንግል ማርያም አይደለም።እንደዛ ከሆነ አሉ፤እንደዛማ ከሆነ እናንተ ኦርቶዶክሶች ድንግል ማርያምን እየተሳደባችሁ አይደላችሁም ፤ምክንያቱም ፤ሌላ ስለ ጽዮንእንዲህ ተብሎ ተጽፏል እኮ በማለት እንዚህን ጥቅሶች ይጠቅሱልናል……

፩ኛ) ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፍ 3 ከቁጥር 16 .ደግሞም እግዚአብሔር እንዲህ አለ፦ የጽዮን ቈነጃጅት
ኰርተዋልና፥ አንገታቸውንም እያሰገጉ በዓይናቸውም እያጣቀሱ፥ ፈንጠርም እያሉ፥ በእግራቸውም እያቃጨሉ ይሄዳሉና 17.ስለዚህ ጌታ የጽዮንን ቈነጃጅት አናት በቡሀነት ይመታል፥
እግዚአብሔርም ኀፍረተ
ሥጋቸውን ይገልጣል።

፪ኛ)ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፍ 52፤2
ኢየሩሳሌም ሆይ፥ ትቢያሽን አራግፊ ተነሺ፥ ተቀመጪ ምርኮኛይቱ
የጽዮን ልጅ ሆይ፥ የአንገትሽን እስራት ፍቺ።እነዚህንና የመሳሰሉትን በመጥቀስ
እናንተ ኦርቶዶክሶች ….ጽዮን የሚለውን ስያሜ ፤ዝም ብላችሁ ለማርያም ከሰጣችሁ፤እነዚህን ጥቅሶችስ አላነባባችሁም ማለት ነው ይሉናል።

፨በመጀመሪያ “””ጽዮን/ZION ”””” የሚለው ቃል የዕብራይስጥ
ሲሆን ትርጉዋሜውም፤”””አንባ፤መሸሸጊያ፤መጠጊያ””””፤ማለት ነው፡፡
መጽሐፈ ዜና መዋዕል ቀዳማዊ 11፤5፦ ዳዊት ግን አምባይቱን ጽዮንን ያዘ እርሷም የዳዊት ከተማ ናት።መረጃ---፩
ትንቢተ ኢሳይያስ 14፡32 ለሕዝቡም መልእክተኞች ምን ብሎ መመለስ ይገባል? እግዚአብሔር ጽዮንን እንደ መሠረተ፥ የሕዝቡም ችግረኞች
በእርስዋ ውስጥ እንደሚጠጉ ነው።
መረጃ --፪ ~ሲቀጥል በመጽሀፍ ቅዱስ ጽዮን የሚለው ቃል ለ አራት፡(4)ነገሮች ነው የተነገረው……..

👉1ኛ ለዳዊት ከተማ እና በውስጧ ያሉትን ተራራዎቹዋንም ጭምር
👉2ኛ ለሰማያዊቷ ኢየሩሳሌም.
👉3ኛለህዝበ/ቤተ እስራኤል.
👉4ኛ ለእናታችን ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ነው……

~~~ማስረጃ፦፦፦
1ኛ ለዳዊት ከተማ ና ተራራዎቹዋ ከ 76 ጊዜ በላይ..ጽዮን በሚለው ስያሜ በመጽሀፍ ቅዱስ ተጠርተዋል.
፩ኛ. መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ 5:2፦ ሰሎሞንም የእግዚአብሔርን ቃል ኪዳን ታቦት ከዳዊት ከተማ ከጽዮን ያወጡ ዘንድ የእስራኤልን ሽማግሌዎችና የነገድ
አለቆችን ሁሉ፥ የእስራኤልን ልጆች የአባቶቻቸውን ቤቶች መሳፍንት፥ ንጉሡ ሰሎሞን ወዳለበት ወደ ኢየሩሳሌም
ሰበሰባቸው።…
፪ኛ .መጽሐፈ ዜና መዋዕል ቀዳማዊ 11፤5 ዳዊት ግን አምባይቱን ጽዮንን ያዘ እርሷም የዳዊት ከተማ ናት
፫ኛ .መጽሐፈ ነገሥት ካልዕ 19፤31 ከኢየሩሳሌም ቅሬታ ከጽዮንም ተራራ ያመለጡት ይወጣሉና የሠራዊት ጌታ የእግዚአብሔር ቅንዓት ይህን ያደርጋል።……..እና ለመሳሰሉት….ተጨማሪውን አንብቡ

~~~ማስረጃ ፦፦፦2ተኛው ለሰማያዊቷ ኢሩሳሌም (ለ 7ተኛዋ ሰማይ) 14 ጊዜ ጽዮን በሚለው ስያሜ በመጽሀፍ ቅዱስ ተጠርታለች፡፡
፩ኛ .ወደ ዕብራውያን 12፤22 ነገር ግን ወደ ጽዮን ተራራና ወደ ሕያው እግዚአብሔር ከተማ ደርሳችኋል፥ ወደ ሰማያዊቱም ኢየሩሳሌም፥ በደስታም ወደ ተሰበሰቡት ወደ አእላፋት
መላእክት፥
፪ኛ.የዮሐንስ ራእይ 14፤1 አየሁም፥ እነሆም፥ በጉ በጽዮን ተራራ
ቆሞ ነበር፥ ከእርሱም ጋር
ስሙና የአባቱ ስም በግምባራቸው የተጻፈላቸው መቶ አርባ አራት ሺህ ነበሩ። መዝሙረዳዊት 50፤2 ከክብሩ ውበት ከጽዮን እግዚአብሔር
ግልጥ ሆኖ ይመጣል።………እና
ለመሳሰሉት….ተጨማሪውን አንብቡ

~~~ማስረጃ 3ተኛው ለህዝበ/ለቤተ እስራኤል(ለእስራኤል ልጆች)፤ጽዮናውያን/ ZIONIST ተብለው ይጠራሉ፤ ከ 46 ጊዜ በላይ በመጽሀፍ ቅዱስ ጽዮን በሚለው ስያሜ
ተጠርተዋል.
፩ኛ. ትንቢተ ኢሳይያስ 52፤2 ኢየሩሳሌም ሆይ፥ ትቢያሽን አራግፊ፡ተነሺ፥ ተቀመጪ ምርኮኛይቱ የጽዮን ልጅ ሆይ፥ የአንገትሽን እስራት ፍቺ።፤8 እነሆ፥ ጕበኞችሽ ጮኸዋል እግዚአብሔር
ወደ ጽዮን በተመለሰ ጊዜ ዓይን በዓይን ይተያያሉና ድምፃቸውን ያነሣሉ፥ በአንድነትም ይዘምራሉ።
፪ኛ.ትንቢተ ኢሳይያስ 3፤16 -17 ደግሞም እግዚአብሔር እንዲህ አለ፦ የጽዮን ቈነጃጅት ኰርተዋልና፥ አንገታቸውንም እያሰገጉ በዓይናቸውም እያጣቀሱ፥ ፈንጠርም እያሉ፥
በእግራቸውም እያቃጨሉ ይሄዳሉና
ስለዚህ ጌታ የጽዮንን ቈነጃጅት አናት በቡሀነት ይመታል፥ እግዚአብሔርም ኀፍረተ ሥጋቸውን ይገልጣል።
፫ኛ.ትንቢተ ኢሳይያስ 4፤3-4 ጌታም የጽዮንን ቈነጃጅት እድፍ ባጠበ ጊዜ፥ የኢየሩሳሌምንም ደም በፍርድ መንፈስና በሚያቃጥል መንፈስ ከመካከልዋ ባነጻ
ጊዜ፥ በጽዮን የቀረ በኢየሩሳሌምም የተረፈ፥ በኢየሩሳሌም ለሕይወት የተጻፈ ሁሉ፥ ቅዱስ ይባላል።
፬ኛ. ትንቢተ ሚክያስ 4፤10-13
የጽዮን ልጅ ሆይ፥ እንደምትወልድ ሴት አምጠሽ ውለጂ አሁን ከከተማ ትወጫለሽና፥ በሜዳም ትቀመጫለሽ፥ ወደ ባቢሎንም ትደርሻለሽ በዚያም
ያድንሻል፥ በዚያም እግዚአብሔር ከጠላቶችሽ እጅ ይቤዥሻል።
11፥ አሁንም። ርኩስ ትሁን፥ ዓይናችንም በጽዮን ላይ ይይ የሚሉ
ብዙ አሕዛብ በአንቺ ላይ ተሰብስበዋል።
13፤ የጽዮን ልጅ ሆይ፥ ቀንድሽን ብረት፥ ጥፍርሽንም ናስ
አደርጋለሁና ተነሺ ሂጂ ብዙ
አሕዛብንም ታደቅቂአለሽ ትርፋቸውንም ለእግዚአብሔር፥ ሀብታቸውንም ለምድር ሁሉ ጌታ ትቀድሻለሽ።………………እና ለመሳሰሉት….ተጨማሪውን አንብቡ……..

~~~ማስረጃ ……4ተኛው ጽዮን የሚለው ስያሜ በመጽሃፍ ቅዱስ የተሰጠው ስሟ ከማር ከወተት ይልቅ ጥዑም የሆነ ፤ክብሯ፤ከፈጣሪ በታች ነገር ግን ከፍጡራን ሁሉ በላይ የሆነ፤
እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ፤ጽዮን በሚለው ስያሜ ተጠርታለች ፤ መረጃ ከማቅረቤ በፊት ለምን ቅድስት ድንግል ማርያም ጽዮን በሚለው ስያሜ ነብያቱ ትንቢት ተናገሩላት ካልን ፤ካላይ
ለመግለረጽ እንደሞከርኩት “””ጽዮን”””” የሚለው ቃል ፤ቃሉ፤የዕብራይስጥ ሲሆን
ትርጉዋሜውም፤”””አንባ፤መሸሸጊያ””””፤ማለት ነው፡፡ ስለሆነም እናታችን ለህዝብ ልጆች ሁሉ በዘመኑ ፍፃሜ(በሀዲስ
ኪዳን) ከልጅዋ ምህረትን ፈልገው ሲመጡ አንባ፡ ጥላ፤ መሸሸጊያ ፤መጠጊያ፤እንደምትሆን፤አ ስቀድመው ነቢያት መንፈስ ቅዱስ ስለገለጸላቸው፤እናታችንን፤ ጽዮን በሚለው ስያሜ ጠርተዋታል፡፡

~~ማስረጃ~~፩ኛ.መዝሙረ ዳዊት 53፡6 መድኃኒትን ከጽዮን ለእስራኤል ማን በሰጠ! እግዚአብሔር የሕዝቡን ምርኮ በመለሰ ጊዜ፥ ያዕቆብ ደስ ይለዋል እስራኤልም ሐሤት
ያደርጋል። ይሄ ትንቢት ሲሆን ተርጉሞ የነገረን ግን ቅዱስ ጳውሎስ ነው
እንዲህ በማለት ሮሜ 11፡26 መድኃኒት ከጽዮን ይወጣል ከያዕቆብም ኃጢአተኛነትን ያስወግዳል።ስለዚህ መዳኒት የተባለው ንጉስ ክርስቶስ
ሲሆን ጽዮን ተብላ የተጠራችሁ ደግሞ እናታችን ቅድስት ድንግል
ማርያም ናት፡፡
፪ኛ.መዝሙረ ዳዊት 87፡2 ሰው እናታችን ጽዮን ይላል፥ በውስጥዋም ሰው ተወለደ እርሱ ራሱም ልዑል መሠረታት።ይሄ ትንቢት ደግሞ ቀራንዮ ላይ ተፈጽሟል ፡፡
የዮሐንስ ወንጌል 19፤27 ከዚህ በኋላ ደቀ መዝሙሩን። እናትህ እነኋት አለው። ከዚህም ሰዓት ጀምሮ ደቀ መዝሙሩ ወደ ቤቱ ወሰዳት።ቅዱስ ዮሐንስ አለምን ወክሎ አስቀድሞ ነብዩ ዳዊት፤
በትንቢቱ ሰው ሁሉ እናታችን ጽዮን ይላል ብሎ የተናገረው ትንቢት እንዲፈጸም ድንግል ማርያምን የአለም ተወካይ(የሰው ልጆች ተወካይ) ሆኖ ለአለሙ እናት እንድትሆን እናት አድርጎ ተቀበለ ።
ይቀጥላል...
🤗1
ጽዮን በመፅሐፍ ቅዱስ ማን ናት??

...የቀጠለ
ልክ አንደ ሙሴ በሲና ተራራ አስርቱን ህግጋትን ከአምላክ ለአለም
መተዳዳሪያ እንዲሆን የአለም ተወካይ(የሰው ልጆች ተወካይ) ሆኖ እንደተቀበለው ፡፡
~~በዚህ ከተስማማን በትንቢተ ኢሳያስ
60 ፤14 የተፃፈው ቃል “””””የአስጨናቂዎችሽም ልጆች
አንገታቸውን ደፍተው ወደ አንቺ
ይመጣሉ፥ የናቁሽም ሁሉ ወደ እግርሽ ጫማ ይሰግዳሉ የእግዚአብሔርም ከተማ፥ የእስራኤል ቅዱስ የሆንሽ ጽዮን ይሉሻል።” የተባለው ከላይ ከተጠቀሱት አራት በጽዮን ስያሜ ከተጠሩት
በማያሻማ መልኩ ፤በትክክል ትንቢቱ የተነገረው፤ለቅድስት፤ድን ግል፥ማርያም፤እንደሆነ፤ማንም፤ህሊና፤
ለው፤ሰው፤መፍረድ ፤ይችላል፡፡ምክንያቱም፤ወደ እግርሽ፤ጫማ፤ተብሏልና፡፡

~~~ነገር ግን በዘመናችን የተነሱት መናፍቃን፤ለድንግል ማርያም፤ምንም ክብር ፤አይገባትም፤ብለው ስለሚያሰስተምሩ፤ይሄን ፤ትንቢት ከላይ
አንደጠቀስኩት ለዳዊት ከተማ ና ተራሮች ሰጥተው፤ይተረጉማሉ፤እዚህ ጋር ግን ሶስት ጥያቄ
አለኝ ~~~
1ኛ ከተማና ተራራ እግር ና ጫማ አላቸው???ካለቸው ይሄ
በአለማችን አዲስ ግኝት ነው ማለት ነው፡፡
2ኛ የዳዊት ከተማ ና ተራራዎቹዋ ሊሰገድላቸው ነው ማለት
ነው?????
3ኛ በእውነቱ የህወይት ምግብና መጠጥ የሆነውን ፤የጽድቅ
ፀሀይ የተባለውን ፤ኢየሱስ፤ክርስቶስን ከማህጸኗ እንካችሁ ብላ የሰጠችን እናት
ግዑዛን ከሆኑት ከዳዊት ከተማና ተራራዎች አንሳ ነው የክብር ስግደት የማይገባት?????? መልሱን ህሊና ላለው ሰው ብቻ ትቻለው…

~~~በመጨረሻም እግዚአብሔር አምላክ በዚህች ቅድስት
ንጽህት በሆነች ሐይማኖት እስከመጨረሻው፤ያጽናን፡፡የእመቤታችን የቅድሰት ድንግል ማርያም፤ረድኤትና
በረከት፤አማላጅነት፤አይለየን፡፡አሜን~~~ ኦርቶዶክስ መልስ አላት፡፡
               Join
     @And_Haymanot
              Join
     @And_Haymanot
              Join
     @And_Haymanot
    
    የአበው ሃይማኖት አትታደስም፡፡
፩ ሃይማኖት
Voice message
ሰላም ተወዳጆች ዛሬ ይዘንላችሁ የቀረብነው በተለያዩ አካላት ለሚጠይቁት መልሥ ነው
የኃልዮ ሀጢአት ምንድነው?
ካህኑ የኃጢአት ማሠርያ እግዚአብሔር ይፍታህ ካለ ለምን የንስሃ አባት አሥፈለገ?
👉እመቤታችን የአለም ቤዛ አትባልም ለሚሉ የተሠጠ መልሥ
   @And_Haymanot
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ለዮናታን እና ለመሰሎቹ ከተሰጡ ድንቅ ምላሾች እነሆ

እንዲህ በጥበብ የተሞላ ምላሽ አላት ተዋህዶ

በስሙ ትርጉም እንኳን ወጥመድ ውስጥ ገባ😊
ልቦናን ይስጥልን 🙏🙏🙏

ሼር አርጉልን የመናፍቃንን ምላሽ በስፋት እንዳሰሳለን ተወዳጆች
@And_Haymanot
👍1
Forwarded from ፩ ሃይማኖት
💗 "ቅድስት ድንግል ማርያምን መውደድ ከሚገባኝ መጠን በላይ አልፌ ወድጄያት ይሆን? ብለህ ሥጋት አይግባህ።
ኢየሱስ ክርስቶስ ከወደዳት በላይ ልትወዳት አትችልምና" 💗
ቅዱስ ማክሲሚሊያን ኮልብ
@And_Haymanot
እመቤታችን ሌሎች ልጆች አሏት?

@And_Haymanot

ይህን ትምህርት የምታነቡ ሁሉ በማስተዋል እና በጽሞና ትረዱ ዘንድ አሳስባችኋለሁ፡፡ ለዘመናት የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ዘለዓለማዊ ድንግልና ለመቃወም ዲያቢሎስ ያዘመታቸው መናፍቃን ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች ሁሉ የማያዳግም መልስ በዝርዝር እና በአንድምታ ቀርቧል ፡፡ ከጌታ ውጭ ከቅዱስ ዮሴፍ ልጅወልዳለች ብለው ለተሰናከሉ ሁሉ በዚሁ አጋጣሚ ስለ ዮሴፍ ማንነት ጭምር ትምህርቱ በጥቂቱ ይዳስሳል መልካም ንባብ ፡-

👉 ‹‹‹ አረጋዊው ዮሴፍ ማነው ?

መናፍቃን ድንግል ማርያም ከጌታ ውጭ ከዮሴፍ እንደወለደች ሲናገሩ እንሰማለን ማስረጃ ባይኖረውም ፡፡ ነገር ግን የዮሴፍን ማንነት በጥቂቱም ቢሆን መረዳት ለስህተታቸው ማሰታገሻ መድኃኒት ነውና እነሆ ፡- አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍ ሀገሩ ናዝሬት ሲሆን ሐናፂም ነጋዴም ነበር ፡፡ ዘሩ ከዳዊት ወገን ነው ፡፡ ሦሰት ሴቶች እና አምሥት ወንዶች ልጆች ነበሩት ፡፡ ልጆቹ ገሚሶቹ ከ12ቱ ሐዋርያት ገሚሶቹ ደግሞ ከ72ቱ አርድዕት ውስጥ የነበሩ ሲሆን ከሚስቱ ጋር 52 ዓመት ፤ ሚስቱ ከሞተች በኋላ
ደግሞ 40 ዓመት ኖሯል ፡፡ በድምሩ 92 ዓመት ከኖረ በኋላ ለእመቤታች ጠባቂ ሆኖ ተመረጠ ፡፡ ከእመቤታችን እና ከጌታ ጋር ደግሞ በስደት ፣ በመከራ 22 ዓመታትን አሳልፏል ፡፡ ሊጠብቃትም ሲመረጥ ከ1,985 ሽማግሌዎች
ውስጥ ዕጣ ደርሶት ነው ፡፡ በፈቃደ እግዚአብሔርም የከተሰበሰቡት ሁሉ የርሱ በትር ለሦስት ጊዜ ያህ በተደጋጋሚ አብባና ለምልማ ተገኘች ፡፡ አረጋዊ ዮሴፍ በ114 ዓመቱ ሐምሌ 26 ቀን አርፏል ፡፡ ከማረፉ በፊት ግን ጌታችንን ‹‹ ሥጋዬን በዚህ ምድር አታስቀረው ›› ብሎ ለምኖት ነበርና ዛሬም ድረስ ዮሴፍ መቀበሩን እንጂ ቅዱስ ሥጋው የት እንዳለ የሚያውቅ የለም ጌታ ስለ ጸሎቱ (ስለልመናው) ሰውሮታልና ፡፡ ‹‹‹ አረጋዊው ዮሴፍ ለምን ተመረጠ ? *ይህ ጻድቅና ንጹሕ አረጋዊ ዮሴፍ ድንግል ማርያምን ሊጠብቅ ስለተመረጠበት ምክንያን አስረጋጭ

ማስረጃዎች እነሆ ፡፡

1ኛ) አገልጋይዋ ተላላኪዋ ሆኖ
ሊጠብቃት ፡፡

2ኛ) መከራዋን እንዲጋራ ፡፡ አንድም ዮሴፍ ዘመዷ ነው መከራን ለብቻ አይዘልቁምና በልጇ አማካኝነት የሚደርስባትን ስደት እና መከራ አብሯት እንዲካለፈል ነው ፡፡ ዝምድናቸው ሲዘረዘር የሚከተለውን ሃቅ ያስረዳናል ፡- + ግንዱ ‹‹ አልዓዛር ›› በሁለት
ወገን የሚከተሉትን ወልዷል ፡-
* ማታን = * ቅስራ*
* ያዕቆብ = * ኢያቄም *
* ዮሴፍ = * ድንግል ማርያም
(የነዚህ የዘር ሐረጋት ግንዱ ከላይ እንዳየነው * አልዓዛር * ነው ስለዚህ የዘር ሃረጋቸው አንድ ነውና ሊጠብቃት እንጂ ሊያገባት አይችልም)

3ኛ) ከመደብደብ ሊያድናት ፡፡ በኦሪ.ዘኁ 5፥19 በተጠቀሰው መሠረት አንዲት ሴት ከባልዋ ውጭ ጸንሳ ብትገኝ ማየ ዘለፋ ያጠጥዋት ነበር ፡፡ እንዲሁም አንዲት ሴት ባል ሳታገባ ብትጸንስ በሙሴ ሕግ መሠረት ደብድበው ይገድሉአት ነበር
፡፡ ስለዚህ እመቤታችን ለዮሴፍ ሳትታጭ ቀርታ ቢሆን ለድብደባ ባበቁአት ነበር ፡፡

4ኛ) ትንቢቱ እንዲፈጸም ነው ፡፡ ጌታ ከዳዊት ቤት እና ወገን እንዲወለድ ኢሳ 11፥1 ፣ 10 ላይ ትንቢት ነበር ፡፡ ዮሴፍም የዳዊት ዘር ነውና ክርስቶስ በዮሴፍ የዳዊት ልጅ ተብሎ እንዲቆጠር ነው ፡፡ ምነው በእናቱ የዳዊት ልጅ አይባልምን? ቢባል አይሁድ ሴትን ከትውልድ ቁጥር አግብተው አይቆጥሩምና ነው ፡፡

5ኛ) ኃይለ አርያማዊት (ከሰማይ ወረደች እንጂ ምድራዊት አይደለችም) የሚሉ ወገኖች ነበሩና ምድራዊት መሆኑኗን ለማጠየቅ ነው ፡፡ ሆኖም
ከምድር መገኘቷን ለመግለጽ እንጂ ድንግል ማርያም በክብሯ ሰማያዊት ናት ፡፡ የባሕርያችን መመኪያ መባሏም ከሰው ዘር መገኘቷን ልብ እንዲሉ ነው ፡፡ ስለዚህ ድንግል ማርያም ለዮሴፍ መታጨቷ ስለዚህ እና ይህን ለመሰለ ምክንያት ነው እንጂ ለሚስትነት አልነበረም ፡፡ አንድም ዮሴፍ እመቤታችን ሊጠብቃት በተመረጠ ጊዜ ጀርባው ጎብጦ ፣ ጉልበቱ ዝሎ ፣ ዓይኑ ሞጭሙጮ ነበር 92 ዓመት አልፎት
ነበር አረጋዊ(ሽማግሌ) መባሉም ለዚህ ነው ፡፡ በሆኑም አረጋዊ ዮሴፍ ስለነዚህ ምክንያት ድንግል ማርያም ሊጠብቃት ተመረጠ እንጂ ሊያገባት አይደለም፡፡ ሊያገባት የተመረጠ ቢሆን ኖሮ ድንግል ማርያም መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ሊያበሥራት ሲመጣ ‹‹ ወንድ ስለማላውቅ እንዴት ይሆናል ›› ባላለችውም ነበር ፡፡ ሊያበሥራት የተላከው ለዮሴፍ ከታጨች በኋላ ነውና ፡፡ በዚህም ንግግሯ ለዮሴፍ የታጨችው ሊጠብቃት እንጂ ሊያገባት እንዳልሆነ አረጋግጣለች፡፡ ዛሬ የተነሱ መናፍቀን ምሥጢር ይጎድላቸዋልና ዮሴፍን እንደወጣት ሰው ቆጥረው ድንግል ማርያምን ሊያገባ እንደታጨ በደካማ ጎናቸው ያስባሉ እውነቱ ግን ይሄ ነው ፡፡
ይቆየን ....
ወስብሀት ለእግዚአብሔር

፩ ሃይማኖት ተዋህዶ

✞_✞_✞
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
1👍1
ገድለ ተክለሃይማኖት እና ተዓምረ ማርያም ላይ ያሉ ጥያቄዎች በአባቶች በስፋት ሲመለስ የኖረ ነው እኛም መልሰን እንዳስሰዋለን ዝግጁ ናችሁ???? ጥያቄ ላለባቸው ሼር በማድረግ እና ወደቻናላችን እንድትጋብዙልን አንላለን
@And_Haymanot
​​እመቤታችን ሌሎች ልጆች አሏት?

📕 ክፍል ሁለት

📜 @And_Haymanot

እመቤታችን ሌሎች ልጆች አሏት(ወልዳለች) በማለት ኑፋቄያቸውን ለሚዘሩ የተሃድሶዎ መናፍቃን በተከታታይ በዚህ ርእሥ የቤተክርስቲያናችንን ምላሽ ማቅረባችንን ቀጥለናል

@Konobyos

‹‹‹ የእጮኛ ትርጉም ›››

እጮኛ የሚለው ቃል ጠባቂ ማለት ነው፡፡ ሌላ ከሰው ልብ የፈለቀ ትርጉም ሊሰጠው አይችልም፡፡ 👉ለምሳሌ ‹‹እናንተን ለዘለዓለም ለእኔ እንድትሆኑ አጭቻችኋለሁ ›› ሆሴ 2፥21 ማለት ለጋብቻ ነውን? ያሳዝናል አጣመው ለተረጎሙት፡፡ 👉አሁንም ሐዋርያው ከጌታችን ጋር ስላዋሐዳቸው ‹‹ ለእርሱ አጭቻችኋለሁ›› 2ኛ ቆሮ 11፥3 ማለቱን እናስተውል፡፡
👉እንደገናም ምእመናንን የከበረች ማደርያው ስላደረጋቸው ‹‹ለሰማያዊው ክብር አጭቻችኋለሁ ›› ኤፌ 5፥26 ታዲያ እንዲህ ሲል ላጋባችሁ ነው ማለት ይሆን(ሎቱ ስብሐት) ፡፡
እመቤታችን ንግሥተ ሰማይ ወምድር ነችና በ15 ዓመቷ መለኮት ተዋሐዳት ፡፡ ሲዋሐዳትም ለዮሴፍ ታጨች ሉቃ1፥26፡፡ እንግዲህ እጮኛ ማለት ትርጉሙን ያላወቁ ይወቁ እንላለን ፡፡ ነገር ግን ሰው በራሱ ፍቃድ አይተርጉም !!! ሌላው እጅግ የሚደንቀው ነገር ደግሞ ድንግል ማርያም ክርስቶስን ከመውለዷ በፊት እንጂ ከወለደች በኋላ ዮሴፍ ‹‹ እጮኛ›› ተብሎ በአንድም ስፍራ አለመጠቀሱ ነው
👉ማስረጃ ‹‹ ሕጻንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብጽ ሽሽ ›› ማቴ 2፥3 እንዲሁም በግብጽ 3 ዓመት ከ3ወር በስደት ከቆዩ በኋላ ይህንኑ ቃል ለዮሴፍ በህልም ተነግሮት ‹‹ ሕጻኑን የሚፈልጉት ሞተዋልና ሕጻንና እናቱን ይዘህ ወደ ናዝሬት ተመለስ ›› አለው እንጂ እጮኛህን (ሚስትህን) ይዘህ
ተመለስ አላለውም ማቴ 2፥20፡፡

‹‹‹ የበኩር ትርጉም ›››

የበኩር ልጇን ወለደች የሚለው ቃል ብዙዎችን አሳስቷል ፡፡ ይህም ሊሆን የቻለው በተለምዶ የበኩር ልጅ የሚባሉ የግድ ተከታይ ያላቸው መሆን አለባቸው የሚል አስተሳሰብ በመናፍቃን ክፉ ልቦና ስለሰረጸነው፡፡ ነገር ግን በተለምዶ የሚባል ነገር መጽሐፍ ቅዱስ ጋር አይሰራምና እንዲህ ይታረማል
👉፡- ‹‹ እግዚአብሔር ሙሴን ከእስራኤል ልጆች ዘንድ ከሰውም ከእንስሳትም ማኅጸንን የሚከፍት በኩር ሁሉ ለእኔ ቀድስልኝ አለው ›› ዘጸ 13፥1-2 ይህ ቃል እንደሚገልጸው በኩር የሚባሉት ለመጀመርያ ጊዜ ከእናታቸው ማኅጸን የሚወጡ መሆናቸውን እንጂ ግዴታ ተከታይ ሊኖራቸው እንደማይገባ ያረጋግጣል ፡፡ አንድም ብቻ ቢሆን የእናቱም ማኅጸን ለመጀመርያ ጊዜ ከፍቶ ከወጣ ተከታይም ባይኖረው በኩር ነው ፡፡ ይሄ የበኩር ትርጉም ካልገባን ወደ ሌላ ፤ ይልቁን ወደ ማንወጣው አዘቅት መዘፈቃችን አይቀሬ ነው ፡፡
👉ለምሳሌ ቆላስየስ 1፥7 ላይ ስለ ክርስቶስ ሲናገር ‹‹ ከፍጥረት ሁሉ በፊት በኩር ነው ›› ይላል እዚህ ጋር በኩር የሚለው ቃል ተወዳዳሪ ላላቸው ነገሮች የሚጠቀስ ሆኖ ከቀረበ ጌታን ፍጡር አድርጎ ከፍጡራን ጋር አነጻጽሮ እርሱ ከፍጥረታት በፊት ቀደም ብሎ የተፈጠረ ፍጡር ነው እንደማለት ይሆናልና(ሎቱ ስብሐት)፡፡
እንደገናም በኩር የሚለውን ቃል በሥጋዊ ደማዊ ሃሳብ ከተረጎምነው ዕብ 1፥6 ላይ 👉‹‹በኩርን ወደ ዓለም ሲያገባ ›› የሚል ቃል አለ እዚህ ላይ የክርስቶስ በኩር ተብሎ መጠራት አብ ቀዳሚ ተከታይ የሌለውን የባሕርይ ልጁን ወደ መሬት ሂድ ፣ ውረድ ተወለድ ፣ ሙት ተሰቀል ብሎ እንደላከው ለመግለጽ ነው ፡፡ ታድያ አብ በኩርን ወደ ዓለም ሲልክ በኩር የሚለው ቃል ተጠቅሷልና አብም ከክርስቶስ ሌላ ልጅ አለው ማለት ነውን? እናንት ግብዞች መናፍቃን የመጽሐፍን ቃል በግርድፍ መረዳት ምን ያህል እንደሚያስት ይረዱ ድንግል ማርያምን የነኩ እየመሰላቸው ባለቤቱን መንቀፋቸው ያሳፍራል !!!
እርሷስ ክብር ይግባትና በተቃዋሚዎች አፍ አትረክስም እርሱ ባለቤቱ አንዴ አክብሯታልና ፡፡ ‹‹ የበኩር ልጇን ወለደች›› መባሉ መጀመርያና መጨረሻ የሌለውን አምላከ አዶናይ ፣ ልዑለ ባሕርይን ወለደች ማለቱ ነው፡፡

ይቀጥላል
📝 ኦርቶዶክስ መልስ አላት፡፡
Join
@Konobyos
Join
@And_Haymanot
Join
@And_Haymanot

ለሌሎች ሼር በማድረግ ኑፋቄያቸውን አብረን እንዋጋ

የአበው ሃይማኖት አትታደስም፡፡ ♥️
👍2