2 ዜና 7 (2 Chronicles)
13፤ ዝናብ እንዳይወርድ ሰማያቱን ብዘጋ፥ ወይም ምድሪቱን ይበላ ዘንድ አንበጣን ባዝዘው፥ ወይም በሕዝብ ላይ ቸነፈር ብሰድድ፥
14፤ በስሜ የተጠሩት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ፥ ፊቴንም ቢፈግሉ፥ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ፥ በሰማይ ሆኜ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ።
15፤ አሁንም በዚህ ስፍራ ለሚጸለይ ጸሎት ዓይኖቼ ይገለጣሉ፥ ጆሮቼም ያደምጣሉ።
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
13፤ ዝናብ እንዳይወርድ ሰማያቱን ብዘጋ፥ ወይም ምድሪቱን ይበላ ዘንድ አንበጣን ባዝዘው፥ ወይም በሕዝብ ላይ ቸነፈር ብሰድድ፥
14፤ በስሜ የተጠሩት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ፥ ፊቴንም ቢፈግሉ፥ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ፥ በሰማይ ሆኜ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ።
15፤ አሁንም በዚህ ስፍራ ለሚጸለይ ጸሎት ዓይኖቼ ይገለጣሉ፥ ጆሮቼም ያደምጣሉ።
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
Forwarded from ፩ ሃይማኖት
ዕጣን
✍ የተሃድሶ መናፍቃን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ከሚተቹበት ምክንያቶች አንዱ በዕጣን መሥዋዕት ላይ ነው እኛ ኦርቶዶክሳውያን ግን ቅዱሳት መጻሕፍትንና የቤተ ክርስቲያን አባቶቻችን ትምህርት መሠረት በማድረግ የዕጣን መሥዋዕትን እናቀርባለን።
✞ ዕጣን ለቤተ መቅድስ አገልግሎት ይውላል ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ዕጣንን የተመላ ሰማያዊ ማዕጠንት በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት እየሰገዱ ለዓለም ድኅነት የሚለምኑበት ነው በቤተክርስቲያንም ካህናት መንፈቀ ሌሊት በነግህ ጊዜ በቅዳሴ ጊዜ በየማዕዘኑ ዕጣን ያጥናሉ ቅዳሴውን ጸሎቱንና ልመናውን ወደ እግዚአብሔር ያሳርጉበታል።
✞ የተሃድሶ መናፍቃኑ በኦሪት የዕጣን መሥዋዕት ይሠዋ የነበረው የደም መሥዋዕቱን ሽታ ለመለወጥ ነው ብለው ያስባሉ ይህ ግን ፍጹም ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጪ የሆነ ስህተት ነው ምክንያቱም ራሱን ችሎ የታዘዘ መሥዋዕት ነውና ለዛም ነው በዘፀ 30፥34-38 ላይ እንምናነበው ለመዓዛው ብቻ የሚፈለግ ቢሆን ኖሮ ለእግዚአብሔር የተዘጋጀውን ዓይነት በቤት ውስጥ መጠቀም ባልተከለከለም ነበር በዛላይ በዘፀ 30፥1 ላይ "የዕጣን መሠዊያ ሥራ" የሚለው ቃል ዕጣን በራሱ መሥዋዕት መሆኑን ያመለክታል።
✍ እግዚአብሔር በእስራኤል ኃጢአት ተቆጥቶ ሊያጠፋቸው በተነሣ ጊዜ ሙሴ አሮንን፦ በዘኁ 16፥45 ላይ "ጥናህን ውሰድ፥ ከመሠዊያውም ላይ እሳት አድርግበት፥ ዕጣንም ጨምርበት፥ ወደ ማኅበሩም ፈጥነህ ውሰደው አስተስርይላቸውም" በማለት ነገረው ይህም ዕጣን የኃጢአት ማስተሥረያ መሆኑን ያሳያል።
☞ ዕጣን ማጠን የተፈቀደው ለካህናት ብቻ ነው ይህንን ሥርዓት በግዴለሽነት ለመጣስ የሞከሩት ዳታንና አቤሮን ተቀስፈዋል/ዘኁ 16፥20-30/ ሌላው ደግሞ ሰማያውያን ካህናት ሱራፌል በራእ 5፥8 ላይ "መጽሐፉንም በወሰደ ጊዜ አራቱ እንስሶችና ሀያ አራቱ ሽማግሌዎች በበጉ ፊት ወደቁ፥ እያንዳንዳቸውም በገናንና የቅዱሳን ጸሎት የሆነ ዕጣን የሞላበትን የወርቅ ዕቃ ያዙ" ይላል።
✍ ነብዩ ሚልክያስ በዘመነ ሐዲስ የዕጣን መሥዋዕት በየቦታው እንደሚሰዋ ሲገልጥ ሚልክ 1፥11 ላይ "ከፀሐይ መውጫ ጀምሮ እስከ መግቢያዋ ድረስ ስሜ በአሕዛብ ዘንድ ታላቅ ይሆናልና፤ በየስፍራውም ለስሜ ዕጣን ያጥናሉ፥ ንጹሕም ቍርባን ያቀርባሉ፤ ስሜ በአሕዛብ ዘንድ ታላቅ ይሆናልና፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር" ብሏል የእግዚአብሔር ስም በአህዛብ ዘንድ ታላቅ የሆነው በዘመነ ሐዲስ ነው ስለዚህ ይህ ትንቢት የተፈጸመው በዘመነ ሐዲስ መሆኑን ያመለክታል።
✍ ሌላው ራእ 8፥3 ላይ "ሌላም መልአክ መጣና የወርቅ ጥና ይዞ በመሰዊያው አጠገብ ቆመ፤ በዙፋኑም ፊት ባለው በወርቅ መሰዊያ ላይ ለቅዱሳን ሁሉ ጸሎት እንዲጨምረው ብዙ ዕጣን ተሰጠው" ይላል መሥዋዕተ ዕጣን የቀረ ቢሆን ኖሮ በሰማያዊ ሥርዓት ያውም በዘመነ ሐዲስ ባልተገለጠ ነበረ ደግምሞ ክርስቶስ ሲወለድም ሰብአ ሰገል ለጌታችን እጅ መንሻ ካመጧቸው ነገሮች አንዱ ዕጣን ነበረ።
✞ ዕጣን የክርስቶስ ምሳሌ ነው ምክንያቱም ዕጣን ተሰውቶ መዓዛው አካባቢውን እንዲለውጠው ሁሉ ጌታም ተሰውቶ ዓለምን ከመርገም ወደ በረከት ለውጧልና፤ ዕጣን ተሰውቶ ኀጢአትን እንደሚያስተሰርየው ሁሉ ጌታችንም ተሰውቶ የዓለምን ኃጢአት አስተሥርዮአልና።
✞ አንድም ዕጣን የቅዱሳን ምሳሌ ነው ዕጣን ተሰውቶ ለሌሎች መዓዛው እንደሚተርፍ ሁሉ ቅዱሳንም ተሰውተው ቃል ኪዳናቸው ለሌሎች ተርፏልና።
✍ ስለዚህ እኛም ኦርቶዶክሳውያን ይህንን መጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነት ምክንያት በማድረግ የዕጣን መስዋእትን ወደ አምላካችን እንሰዋለን የተሃድሶ መናፍቃኑም ወደ እውነተኛዋ መንገድ ወደ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ይመጡ ዘንድ እንጸልያለን።
✞ የዘካርያስን ዕጣን የተቀበለ አምላክ የኛንም ጸሎት ልመናችንን ይቀበለን!!! አሜን!!!
@And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
✍ የተሃድሶ መናፍቃን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ከሚተቹበት ምክንያቶች አንዱ በዕጣን መሥዋዕት ላይ ነው እኛ ኦርቶዶክሳውያን ግን ቅዱሳት መጻሕፍትንና የቤተ ክርስቲያን አባቶቻችን ትምህርት መሠረት በማድረግ የዕጣን መሥዋዕትን እናቀርባለን።
✞ ዕጣን ለቤተ መቅድስ አገልግሎት ይውላል ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ዕጣንን የተመላ ሰማያዊ ማዕጠንት በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት እየሰገዱ ለዓለም ድኅነት የሚለምኑበት ነው በቤተክርስቲያንም ካህናት መንፈቀ ሌሊት በነግህ ጊዜ በቅዳሴ ጊዜ በየማዕዘኑ ዕጣን ያጥናሉ ቅዳሴውን ጸሎቱንና ልመናውን ወደ እግዚአብሔር ያሳርጉበታል።
✞ የተሃድሶ መናፍቃኑ በኦሪት የዕጣን መሥዋዕት ይሠዋ የነበረው የደም መሥዋዕቱን ሽታ ለመለወጥ ነው ብለው ያስባሉ ይህ ግን ፍጹም ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጪ የሆነ ስህተት ነው ምክንያቱም ራሱን ችሎ የታዘዘ መሥዋዕት ነውና ለዛም ነው በዘፀ 30፥34-38 ላይ እንምናነበው ለመዓዛው ብቻ የሚፈለግ ቢሆን ኖሮ ለእግዚአብሔር የተዘጋጀውን ዓይነት በቤት ውስጥ መጠቀም ባልተከለከለም ነበር በዛላይ በዘፀ 30፥1 ላይ "የዕጣን መሠዊያ ሥራ" የሚለው ቃል ዕጣን በራሱ መሥዋዕት መሆኑን ያመለክታል።
✍ እግዚአብሔር በእስራኤል ኃጢአት ተቆጥቶ ሊያጠፋቸው በተነሣ ጊዜ ሙሴ አሮንን፦ በዘኁ 16፥45 ላይ "ጥናህን ውሰድ፥ ከመሠዊያውም ላይ እሳት አድርግበት፥ ዕጣንም ጨምርበት፥ ወደ ማኅበሩም ፈጥነህ ውሰደው አስተስርይላቸውም" በማለት ነገረው ይህም ዕጣን የኃጢአት ማስተሥረያ መሆኑን ያሳያል።
☞ ዕጣን ማጠን የተፈቀደው ለካህናት ብቻ ነው ይህንን ሥርዓት በግዴለሽነት ለመጣስ የሞከሩት ዳታንና አቤሮን ተቀስፈዋል/ዘኁ 16፥20-30/ ሌላው ደግሞ ሰማያውያን ካህናት ሱራፌል በራእ 5፥8 ላይ "መጽሐፉንም በወሰደ ጊዜ አራቱ እንስሶችና ሀያ አራቱ ሽማግሌዎች በበጉ ፊት ወደቁ፥ እያንዳንዳቸውም በገናንና የቅዱሳን ጸሎት የሆነ ዕጣን የሞላበትን የወርቅ ዕቃ ያዙ" ይላል።
✍ ነብዩ ሚልክያስ በዘመነ ሐዲስ የዕጣን መሥዋዕት በየቦታው እንደሚሰዋ ሲገልጥ ሚልክ 1፥11 ላይ "ከፀሐይ መውጫ ጀምሮ እስከ መግቢያዋ ድረስ ስሜ በአሕዛብ ዘንድ ታላቅ ይሆናልና፤ በየስፍራውም ለስሜ ዕጣን ያጥናሉ፥ ንጹሕም ቍርባን ያቀርባሉ፤ ስሜ በአሕዛብ ዘንድ ታላቅ ይሆናልና፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር" ብሏል የእግዚአብሔር ስም በአህዛብ ዘንድ ታላቅ የሆነው በዘመነ ሐዲስ ነው ስለዚህ ይህ ትንቢት የተፈጸመው በዘመነ ሐዲስ መሆኑን ያመለክታል።
✍ ሌላው ራእ 8፥3 ላይ "ሌላም መልአክ መጣና የወርቅ ጥና ይዞ በመሰዊያው አጠገብ ቆመ፤ በዙፋኑም ፊት ባለው በወርቅ መሰዊያ ላይ ለቅዱሳን ሁሉ ጸሎት እንዲጨምረው ብዙ ዕጣን ተሰጠው" ይላል መሥዋዕተ ዕጣን የቀረ ቢሆን ኖሮ በሰማያዊ ሥርዓት ያውም በዘመነ ሐዲስ ባልተገለጠ ነበረ ደግምሞ ክርስቶስ ሲወለድም ሰብአ ሰገል ለጌታችን እጅ መንሻ ካመጧቸው ነገሮች አንዱ ዕጣን ነበረ።
✞ ዕጣን የክርስቶስ ምሳሌ ነው ምክንያቱም ዕጣን ተሰውቶ መዓዛው አካባቢውን እንዲለውጠው ሁሉ ጌታም ተሰውቶ ዓለምን ከመርገም ወደ በረከት ለውጧልና፤ ዕጣን ተሰውቶ ኀጢአትን እንደሚያስተሰርየው ሁሉ ጌታችንም ተሰውቶ የዓለምን ኃጢአት አስተሥርዮአልና።
✞ አንድም ዕጣን የቅዱሳን ምሳሌ ነው ዕጣን ተሰውቶ ለሌሎች መዓዛው እንደሚተርፍ ሁሉ ቅዱሳንም ተሰውተው ቃል ኪዳናቸው ለሌሎች ተርፏልና።
✍ ስለዚህ እኛም ኦርቶዶክሳውያን ይህንን መጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነት ምክንያት በማድረግ የዕጣን መስዋእትን ወደ አምላካችን እንሰዋለን የተሃድሶ መናፍቃኑም ወደ እውነተኛዋ መንገድ ወደ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ይመጡ ዘንድ እንጸልያለን።
✞ የዘካርያስን ዕጣን የተቀበለ አምላክ የኛንም ጸሎት ልመናችንን ይቀበለን!!! አሜን!!!
@And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
አንዲት ቫይረስ ዓለምን እንዲህ በአንድ እግሯ ካቆመቻት ሐሳዊ መሲሕ ሲመጣ እንዴት ትኾን፣ የትስ ትገባ፣ ምንስ ይውጣት ይኾን ? ዓለም ይህን ያኽል ደካማ ናት።
አይዟችሁ! እንጸልይ፤ ንስሐም እንግባ !
By Abayneh kassie
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
አይዟችሁ! እንጸልይ፤ ንስሐም እንግባ !
By Abayneh kassie
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
እንዲሳካ ፀልዩ!
.
የኮሮና ቫይረስን በሳይንሳዊ ምርምር በተደገፈ የሀገር በቀል
እውቀት ከዘመናዊ ሳይንስ ጋር በማቀናጀት ቫይረሱን ለማከም
የተሰራው መድሃኒት መሰረታዊ የምርምር ሂደት በማለፍ
ተደጋጋሚ የቤተ ሙከራ ሞዴሊንግ ሂደቶችን በስኬት አልፏል፡፡
@And_Haymanot
ተወዳጆች ስንቱ ሃሰተኛ ነብያት በስንቱ እየተጫወቱ መሆኑን እያየን ነው አይደል? እባካችሁ እባካችሁ ወደ ንስሃ ተመልሰን እነሱም እንዲመለሱ በቻልነው መጠን የንስሃ ትምህርቶችን ሼር እናድርግላቸው ለማለት እንወዳለን
@And_Haymanot
እግዚአብሔር ቸር ያሰማን ሃገራችንንም ለአላም መድሃኒት ያድርግልን
@And_Haymanot_bot
.
የኮሮና ቫይረስን በሳይንሳዊ ምርምር በተደገፈ የሀገር በቀል
እውቀት ከዘመናዊ ሳይንስ ጋር በማቀናጀት ቫይረሱን ለማከም
የተሰራው መድሃኒት መሰረታዊ የምርምር ሂደት በማለፍ
ተደጋጋሚ የቤተ ሙከራ ሞዴሊንግ ሂደቶችን በስኬት አልፏል፡፡
@And_Haymanot
ተወዳጆች ስንቱ ሃሰተኛ ነብያት በስንቱ እየተጫወቱ መሆኑን እያየን ነው አይደል? እባካችሁ እባካችሁ ወደ ንስሃ ተመልሰን እነሱም እንዲመለሱ በቻልነው መጠን የንስሃ ትምህርቶችን ሼር እናድርግላቸው ለማለት እንወዳለን
@And_Haymanot
እግዚአብሔር ቸር ያሰማን ሃገራችንንም ለአላም መድሃኒት ያድርግልን
@And_Haymanot_bot
Forwarded from ፩ ሃይማኖት
የያረድ ዉብ ዜማ
የያረድ ዉብ ዜማ ድንግል እመቤቴ ስጦታየ ነሺ / 2/
በምን አንደበቴ እንደምን ባለ ቃል ማርያም ልበልሺ/ 2
ምድርና ሰማዩ ተአምርሺን ይንገሩ
ፍጥረታት በሙሉ ስለ አንቺ ይመስክሩ
ተነግሮ የማያልቅ ድንቅ ነው ስራሺ
ድንግል ሆይ እናተ አምሳያም የለሺ
ማርያም ድንግል እረዳተ
የምትደርሺልኝ ነይ ስልሽ በጭንቀተ
ታምርሺን በአይነ አይቻለሁ
ጽዮን ሆይ ስልሽ ድንግል ሆይ እጠግባለሁ
አዝ - - -
የእግዚአብሀር ጥበቡ በአንቺ ተገለጠ
የአዳም ዘር በሙሉ ከሞት አመለጠ
ለፍጥረቱ ሁሉ መሰላል የሆንሺ
ነገን ባላውቅ እነም ቢያስፈራኚ
አንቺ ካለሺኝ በፍጹም አልወድቅም
በፊትሺም እንድቆም ለምስጋና
ማርያም ልበልሽ በትህትና
አዝ - - -
ትውልዱ በሙሉ ለምስጋና ይቁም
ባንቺ ስለሆነ የቀረለት መርገም
አዳም ከነልጁ በሰማይ በምድር
ማርያም ማርያም ይበል ተአምርሺን ይናገር
ጨለማው ከፊተ ተገፈፈ
ማርያም በምልጃሽ ልበ አረፈ
ከጎነ ነይ ስልሺ እጽናናለሁ
እሳት ገደሉን ሁሉንም አልፈዋለሁ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
የያረድ ዉብ ዜማ ድንግል እመቤቴ ስጦታየ ነሺ / 2/
በምን አንደበቴ እንደምን ባለ ቃል ማርያም ልበልሺ/ 2
ምድርና ሰማዩ ተአምርሺን ይንገሩ
ፍጥረታት በሙሉ ስለ አንቺ ይመስክሩ
ተነግሮ የማያልቅ ድንቅ ነው ስራሺ
ድንግል ሆይ እናተ አምሳያም የለሺ
ማርያም ድንግል እረዳተ
የምትደርሺልኝ ነይ ስልሽ በጭንቀተ
ታምርሺን በአይነ አይቻለሁ
ጽዮን ሆይ ስልሽ ድንግል ሆይ እጠግባለሁ
አዝ - - -
የእግዚአብሀር ጥበቡ በአንቺ ተገለጠ
የአዳም ዘር በሙሉ ከሞት አመለጠ
ለፍጥረቱ ሁሉ መሰላል የሆንሺ
ነገን ባላውቅ እነም ቢያስፈራኚ
አንቺ ካለሺኝ በፍጹም አልወድቅም
በፊትሺም እንድቆም ለምስጋና
ማርያም ልበልሽ በትህትና
አዝ - - -
ትውልዱ በሙሉ ለምስጋና ይቁም
ባንቺ ስለሆነ የቀረለት መርገም
አዳም ከነልጁ በሰማይ በምድር
ማርያም ማርያም ይበል ተአምርሺን ይናገር
ጨለማው ከፊተ ተገፈፈ
ማርያም በምልጃሽ ልበ አረፈ
ከጎነ ነይ ስልሺ እጽናናለሁ
እሳት ገደሉን ሁሉንም አልፈዋለሁ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
Forwarded from ፩ ሃይማኖት
ሳልፆም ሊፈሰክ ነው
አይ የኔ ነገር !
እርግጥ አልበላሁም ስጋም ሆነ ቅቤ
አልፆም አለኝ እንጂ አመፀኛ ልቤ
ካምናና ካቻምና የዘንድሮ ብሶ
መላ ማንነቴ በሀጢያት ተለውሶ
ስዋሽ ስቀጥፍ
ህግን ስተላለፍ
ስሰድብ ሳደማ
የሰው ስጋ ሳማ
ባይኔ ሳመነዝር
የሰው ሰው ሳማትር
ገላዬን_ሳራቁት
አዳምን/ሔዋንን ሳሳስት
ስረሳ ስቃይህን
መስቀል ህማምህን
ያን ሁሉ ግርፋት
ነብሴ ሳያስጨንቃት
አይ እኔ
በሀሰት ስመሰክር
በሀጢያት ስዳክር
ለማይሞላ ኑሮ
ሳልሻል ዘንድሮ
ፆሙ ተጋመሰ
ጊዜው ተጋመሰ
ጌታ ሆይ
አቤቱ አስበኝ
ለንሰሀ አብቃኝ
እስቲ የቀረውን ለበረከት በለው
አመፀኛ ልቤ ፆምህን ይፁመው
"ከደጀ ሰላሙ ከካህኑ እግር ስር
ንስሀዬን ልውሰድ ስለመስቀል ፍቅር" 🙏
================
ከናንተው የተላከ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
አይ የኔ ነገር !
እርግጥ አልበላሁም ስጋም ሆነ ቅቤ
አልፆም አለኝ እንጂ አመፀኛ ልቤ
ካምናና ካቻምና የዘንድሮ ብሶ
መላ ማንነቴ በሀጢያት ተለውሶ
ስዋሽ ስቀጥፍ
ህግን ስተላለፍ
ስሰድብ ሳደማ
የሰው ስጋ ሳማ
ባይኔ ሳመነዝር
የሰው ሰው ሳማትር
ገላዬን_ሳራቁት
አዳምን/ሔዋንን ሳሳስት
ስረሳ ስቃይህን
መስቀል ህማምህን
ያን ሁሉ ግርፋት
ነብሴ ሳያስጨንቃት
አይ እኔ
በሀሰት ስመሰክር
በሀጢያት ስዳክር
ለማይሞላ ኑሮ
ሳልሻል ዘንድሮ
ፆሙ ተጋመሰ
ጊዜው ተጋመሰ
ጌታ ሆይ
አቤቱ አስበኝ
ለንሰሀ አብቃኝ
እስቲ የቀረውን ለበረከት በለው
አመፀኛ ልቤ ፆምህን ይፁመው
"ከደጀ ሰላሙ ከካህኑ እግር ስር
ንስሀዬን ልውሰድ ስለመስቀል ፍቅር" 🙏
================
ከናንተው የተላከ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
+ አቤቱ ቅጣኝ ነገር ግን እንዳታዋርደኝ! +
እግዚአብሔር ፍቅር ነው ፣ መሐሪ ነው ፣ ይቅር ባይ ነው፡፡ ፍቅር ይቆጣል ወይ? ይቅር ባይስ ይቀጣል ወይ? ብዙዎቻችን ስለ ክርስቶስ ሲነገረን መሐሪነቱና ፍቅሩ ብቻ ቢነገረን አንጠላም፡፡ ጨርሶ የማንፈራው እግዚአብሔር እንፈልጋለን፡፡ እንዲህ አታድርግ! የሚለን ሲመጣ ‘አትፍረድ’ እንላለን ፤ ቆይተን ግን የሰማዩን ዳኝም አትፍረድ ማለት ይቃጣናል፡፡ ቅጣት የሌለበት ክርስትና እንሻለን፡፡
ይህ ዓይነቱን ክርስትና ‘ጣፋጭ ክርስትና’ {የስኳር ክርስትና ይሉታል} ምንም ምሬት የሌለበት ሁሌም ማር ማር የሚል ሕይወት አድርገው ክርስትናን የሚሰብኩም ብዙ ናቸው፡፡ ‘አይዞህ ብትታመም ትፈወሳለህ ፣ ቤትህ ይሞላል ፣ ቀዳዳህ ይደፈናል ፣ ብትበድልም አትቀጣም’ ብቻ የሚሉ ስብከቶች የስኳር ክርስትና ስብከቶች ናቸው፡፡ ይህንን ብቻ የሚያጮሁ ሰዎች ክርስቶስ ‘የምድር ጨው ናችሁ’ ያለውን ትተው የምድር ስኳር ለመሆንና ዓለምን ለማስደሰት የሚፈልጉ ናቸው፡፡
በእርግጥ እግዚአብሔር ይቆጣል ወይ? አዎን ይቆጣል! እንዲህ ይላል መጽሐፉ
‘እግዚአብሔር ቀናተኛና ተበቃይ አምላክ ነው እግዚአብሔር ተበቃይና መዓትን የተሞላ ነው እግዚአብሔር ተቃዋሚዎቹን ይበቀላል፥ ለጠላቶቹም ቍጣውን ይጠብቃል። በቍጣው ፊት የሚቆም ማን ነው? የቍጣውንም ትኵሳት ማን ይታገሣል? መዓቱ እንደ እሳት ይፈስሳል፥ ከእርሱም የተነሣ ዓለቶች ተሰነጠቁ’ ናሆ 1፡1፣6
‘‘ከቍጣው የተነሣ ምድር ትንቀጠቀጣለች አሕዛብም መዓቱን አይችሉም’’ ኤር 10፡10
‘‘እኛ በቍጣህ አልቀናልና፥ በመዓትህም ደንግጠናልና’’ መዝ. 90፡7
እግዚአብሔር በተቆጣ ጊዜ የሚመልሰው የለም፡፡ ቅዱሳን የቁጣውን መጠን ስለሚያውቁ በትሕትና ይለምኑታል፡፡
ይሁንና መጽሐፍ ቅዱስ ስለ እግዚአብሔር ቁጣ ደጋግሞ ቢነግረንም አንድ ሌላ ደስ የሚያሰኝ ነገርም ነግሮናል፡፡ የእግዚአብሔር ቁጣው ለዘላለም አይደለም፡፡ "ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" ይላል እንጂ "ቁጣው ለዘላለም ነውና" አይልም:: የእግዚአብሔር ቁጣ ጊዜያዊ ነው፡፡
‘መሐሪ ነኝና ለዘላለም አልቆጣም’ ኤር 3፡12
‘ቁጣው ለጥቂት ጊዜ ሞገሱ ግን ለሕይወት ዘመን ነው’ መዝ 29፡5
‘ጌታ ለዘላለም አይጥልም ቢያሳዝንም እንደ ምሕረቱ ብዛት ይራራል ፤ የሰው ልጆችን ከልቡ አያስጨንቅም አያሳዝንምም’ ሰ.ኤር 3፡31
የፈጣሪን የነነደ የቁጣ እሳት ማጥፋት የሚቻለን በዕንባ ነው፡፡ በደላችንን አምነን ቅጣት ይገባናል ነገር ግን መሐሪ ነህና ማረን ማለት ይገባል፡፡ ንጉሥ ዳዊት ‘አቤቱ በቁጣህ አትቅሠፈኝ በመዓትህም አትገሥፀኝ’ ብሎ የፈጣሪን ቁጣ አበረደ፡፡ /መዝ 38፡1/ ነቢዩ ኤርያስም ‘አቤቱ ቅጣኝ ነገር ግን እንዳታዋርደኝ በመጠን ይሁን እንጂ በቁጣ አይሁን’ ብሎ ተለማመጠ፡፡ ኤር 10፡24
አንድ ሠዓሊ በጣም ብዙ ደክሞ የተጠበበትን ሥዕሉን የፈለገ ቢበሳጭ ለረዥም ጊዜ ያንን ሥዕል ለመሳል የተጠበበትን ጥበብ አስቦ ሥዕሉን ወደ እሳት አይጨምረውም፡፡ አባ ጊዮርጊስ እንዲህ ሲል ይለምናል ‘ሠዓሊ ሥዕሉን ያጠፋል ወይ? [ጌታ ሆይ እኔን ስትፈጥር የተጠበብክበትን] የቀደመ ጥበብህን አስብ እንጂ! አስበህም ማረኝ! [ያጠፋዖኑ ለሥዕሉ ሠዓሊ ፤ ኪነተከ ዘትካት ኀሊ]
ይቅርታውን በንስሓ ለሚለምኑ ሁሉ ምሕረቱ ቅርብ ነው፡፡ በቀኝና በግራው ወንበዴዎች በተሰቀሉበት በዕለተ አርብ የግራው ወንበዴ ሲሰድበው ጌታ መልስ አልሠጠም፡፡ የቀኙ ወንበዴ ማረኝ ሲለው ግን ከአፉ ተቀብሎ በገነት ትሆናለህ አለው፡፡ ቁጣው የራቀ ምሕረቱ የበዛ እርሱ የራበው ሰው ለምግብ የሚቸኩለውን ያህል ይቅር ለማለት ይቸኩላል፡፡ ‘ምሕረትን ይወድዳልና ቁጣውንም ለዘላለም አይጠብቅም ተመልሶ ይምረናል ፤ ክፋታችንንም ይጠቀጥቃል ፤ ኃጢአታችንንንም በባሕሩ ጥልቅ ይጥለዋል’ ሚክ 7፡18
ልጆች ሳለን ጥፋት ስናጠፋ ከወላጆቻችን እንደበቃለን፡፡በተደበቅንበት ሰዓት ውስጣችን በፍርሃት ይርዳል፡፡ ‘ዛሬ ገደለኝ’ ‘ዛሬ መሞቴ ነው’ ብለን እንጨነቃለን፡፡ የሚደርስብንን ቅጣት እጅግ አጋንነን ከመፍራታችን የተነሣ መሬት ተሰንጥቃ ብትውጠን አንጠላም፡፡ በዚያ ሁሉ ጭንቀት ውስጥ ግን ወላጆቻችንም እስኪያገኙን ይጨንነቃሉ፡፡ እግዚአብሔርም እንዲህ ነው፡፡ አጥፍቶ በገነት ዛፎች መካከል የተሸሸገ አዳምን ወዴት ነህ ብሎ የፈለገ እርሱ እኛንም ይፈልገናል፡፡ አዳም ከገነት ሳይባረር ገነት ውስጥ እንደጠፋ ፈጣሪ ሳያባርረን ራሳችንን በኃጢአት ተሸማቅቀን ያባረርን እኛን ይፈልገናል፡፡ እርሱ ስለመጥፋትህ ይጨነቃል አንተ ‘ዛሬስ አይምረኝም’ ትላለህ፡፡
የሚገርመው በጥፋታችን ከተደበቅንበት ወላጆቻችን ካገኙን በኋላ ሁለተኛው ዙር ጭንቀታችን ‘ምን አጥፍተህ ነው የተደበቅከው’ መባል ነው፡፡ ጥፋታችንን ሲያውጣጡን እንንቀጠቀጣለን፡፡ ያጠፋነውን ስለምናውቀው ስንት እንደሚያስገርፈንም እናውቀዋለን፡፡ ‘ብትናገር ይሻላል? ግዴለህም!’ ብለው አግባብተውም አስፈራርተውም ወላጆቻችን ጥፋታችንን ያውጣጡናል፡፡ እየፈራን ያጠፋነውን ጥፋት ስንናዘዝ ግን ወላጆቻችን በጥፋታችን ቅጥል ብለው ‘አልመታህም ተናገር’ ያሉንን ረስተው የዱላ ዝናም ያዘንቡብናል፡፡ እግዚአብሔር ግን ጥፋትህን ስትነግረው ቁጣው የሚገነፍል አባት አይደለም፡፡
’’ኃጢአታችንን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነፃን የታመነና ጻድቅ ነው’ 1ዮሐ 1፡9
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
መጋቢት 18 2012 ዓ ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
እግዚአብሔር ፍቅር ነው ፣ መሐሪ ነው ፣ ይቅር ባይ ነው፡፡ ፍቅር ይቆጣል ወይ? ይቅር ባይስ ይቀጣል ወይ? ብዙዎቻችን ስለ ክርስቶስ ሲነገረን መሐሪነቱና ፍቅሩ ብቻ ቢነገረን አንጠላም፡፡ ጨርሶ የማንፈራው እግዚአብሔር እንፈልጋለን፡፡ እንዲህ አታድርግ! የሚለን ሲመጣ ‘አትፍረድ’ እንላለን ፤ ቆይተን ግን የሰማዩን ዳኝም አትፍረድ ማለት ይቃጣናል፡፡ ቅጣት የሌለበት ክርስትና እንሻለን፡፡
ይህ ዓይነቱን ክርስትና ‘ጣፋጭ ክርስትና’ {የስኳር ክርስትና ይሉታል} ምንም ምሬት የሌለበት ሁሌም ማር ማር የሚል ሕይወት አድርገው ክርስትናን የሚሰብኩም ብዙ ናቸው፡፡ ‘አይዞህ ብትታመም ትፈወሳለህ ፣ ቤትህ ይሞላል ፣ ቀዳዳህ ይደፈናል ፣ ብትበድልም አትቀጣም’ ብቻ የሚሉ ስብከቶች የስኳር ክርስትና ስብከቶች ናቸው፡፡ ይህንን ብቻ የሚያጮሁ ሰዎች ክርስቶስ ‘የምድር ጨው ናችሁ’ ያለውን ትተው የምድር ስኳር ለመሆንና ዓለምን ለማስደሰት የሚፈልጉ ናቸው፡፡
በእርግጥ እግዚአብሔር ይቆጣል ወይ? አዎን ይቆጣል! እንዲህ ይላል መጽሐፉ
‘እግዚአብሔር ቀናተኛና ተበቃይ አምላክ ነው እግዚአብሔር ተበቃይና መዓትን የተሞላ ነው እግዚአብሔር ተቃዋሚዎቹን ይበቀላል፥ ለጠላቶቹም ቍጣውን ይጠብቃል። በቍጣው ፊት የሚቆም ማን ነው? የቍጣውንም ትኵሳት ማን ይታገሣል? መዓቱ እንደ እሳት ይፈስሳል፥ ከእርሱም የተነሣ ዓለቶች ተሰነጠቁ’ ናሆ 1፡1፣6
‘‘ከቍጣው የተነሣ ምድር ትንቀጠቀጣለች አሕዛብም መዓቱን አይችሉም’’ ኤር 10፡10
‘‘እኛ በቍጣህ አልቀናልና፥ በመዓትህም ደንግጠናልና’’ መዝ. 90፡7
እግዚአብሔር በተቆጣ ጊዜ የሚመልሰው የለም፡፡ ቅዱሳን የቁጣውን መጠን ስለሚያውቁ በትሕትና ይለምኑታል፡፡
ይሁንና መጽሐፍ ቅዱስ ስለ እግዚአብሔር ቁጣ ደጋግሞ ቢነግረንም አንድ ሌላ ደስ የሚያሰኝ ነገርም ነግሮናል፡፡ የእግዚአብሔር ቁጣው ለዘላለም አይደለም፡፡ "ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" ይላል እንጂ "ቁጣው ለዘላለም ነውና" አይልም:: የእግዚአብሔር ቁጣ ጊዜያዊ ነው፡፡
‘መሐሪ ነኝና ለዘላለም አልቆጣም’ ኤር 3፡12
‘ቁጣው ለጥቂት ጊዜ ሞገሱ ግን ለሕይወት ዘመን ነው’ መዝ 29፡5
‘ጌታ ለዘላለም አይጥልም ቢያሳዝንም እንደ ምሕረቱ ብዛት ይራራል ፤ የሰው ልጆችን ከልቡ አያስጨንቅም አያሳዝንምም’ ሰ.ኤር 3፡31
የፈጣሪን የነነደ የቁጣ እሳት ማጥፋት የሚቻለን በዕንባ ነው፡፡ በደላችንን አምነን ቅጣት ይገባናል ነገር ግን መሐሪ ነህና ማረን ማለት ይገባል፡፡ ንጉሥ ዳዊት ‘አቤቱ በቁጣህ አትቅሠፈኝ በመዓትህም አትገሥፀኝ’ ብሎ የፈጣሪን ቁጣ አበረደ፡፡ /መዝ 38፡1/ ነቢዩ ኤርያስም ‘አቤቱ ቅጣኝ ነገር ግን እንዳታዋርደኝ በመጠን ይሁን እንጂ በቁጣ አይሁን’ ብሎ ተለማመጠ፡፡ ኤር 10፡24
አንድ ሠዓሊ በጣም ብዙ ደክሞ የተጠበበትን ሥዕሉን የፈለገ ቢበሳጭ ለረዥም ጊዜ ያንን ሥዕል ለመሳል የተጠበበትን ጥበብ አስቦ ሥዕሉን ወደ እሳት አይጨምረውም፡፡ አባ ጊዮርጊስ እንዲህ ሲል ይለምናል ‘ሠዓሊ ሥዕሉን ያጠፋል ወይ? [ጌታ ሆይ እኔን ስትፈጥር የተጠበብክበትን] የቀደመ ጥበብህን አስብ እንጂ! አስበህም ማረኝ! [ያጠፋዖኑ ለሥዕሉ ሠዓሊ ፤ ኪነተከ ዘትካት ኀሊ]
ይቅርታውን በንስሓ ለሚለምኑ ሁሉ ምሕረቱ ቅርብ ነው፡፡ በቀኝና በግራው ወንበዴዎች በተሰቀሉበት በዕለተ አርብ የግራው ወንበዴ ሲሰድበው ጌታ መልስ አልሠጠም፡፡ የቀኙ ወንበዴ ማረኝ ሲለው ግን ከአፉ ተቀብሎ በገነት ትሆናለህ አለው፡፡ ቁጣው የራቀ ምሕረቱ የበዛ እርሱ የራበው ሰው ለምግብ የሚቸኩለውን ያህል ይቅር ለማለት ይቸኩላል፡፡ ‘ምሕረትን ይወድዳልና ቁጣውንም ለዘላለም አይጠብቅም ተመልሶ ይምረናል ፤ ክፋታችንንም ይጠቀጥቃል ፤ ኃጢአታችንንንም በባሕሩ ጥልቅ ይጥለዋል’ ሚክ 7፡18
ልጆች ሳለን ጥፋት ስናጠፋ ከወላጆቻችን እንደበቃለን፡፡በተደበቅንበት ሰዓት ውስጣችን በፍርሃት ይርዳል፡፡ ‘ዛሬ ገደለኝ’ ‘ዛሬ መሞቴ ነው’ ብለን እንጨነቃለን፡፡ የሚደርስብንን ቅጣት እጅግ አጋንነን ከመፍራታችን የተነሣ መሬት ተሰንጥቃ ብትውጠን አንጠላም፡፡ በዚያ ሁሉ ጭንቀት ውስጥ ግን ወላጆቻችንም እስኪያገኙን ይጨንነቃሉ፡፡ እግዚአብሔርም እንዲህ ነው፡፡ አጥፍቶ በገነት ዛፎች መካከል የተሸሸገ አዳምን ወዴት ነህ ብሎ የፈለገ እርሱ እኛንም ይፈልገናል፡፡ አዳም ከገነት ሳይባረር ገነት ውስጥ እንደጠፋ ፈጣሪ ሳያባርረን ራሳችንን በኃጢአት ተሸማቅቀን ያባረርን እኛን ይፈልገናል፡፡ እርሱ ስለመጥፋትህ ይጨነቃል አንተ ‘ዛሬስ አይምረኝም’ ትላለህ፡፡
የሚገርመው በጥፋታችን ከተደበቅንበት ወላጆቻችን ካገኙን በኋላ ሁለተኛው ዙር ጭንቀታችን ‘ምን አጥፍተህ ነው የተደበቅከው’ መባል ነው፡፡ ጥፋታችንን ሲያውጣጡን እንንቀጠቀጣለን፡፡ ያጠፋነውን ስለምናውቀው ስንት እንደሚያስገርፈንም እናውቀዋለን፡፡ ‘ብትናገር ይሻላል? ግዴለህም!’ ብለው አግባብተውም አስፈራርተውም ወላጆቻችን ጥፋታችንን ያውጣጡናል፡፡ እየፈራን ያጠፋነውን ጥፋት ስንናዘዝ ግን ወላጆቻችን በጥፋታችን ቅጥል ብለው ‘አልመታህም ተናገር’ ያሉንን ረስተው የዱላ ዝናም ያዘንቡብናል፡፡ እግዚአብሔር ግን ጥፋትህን ስትነግረው ቁጣው የሚገነፍል አባት አይደለም፡፡
’’ኃጢአታችንን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነፃን የታመነና ጻድቅ ነው’ 1ዮሐ 1፡9
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
መጋቢት 18 2012 ዓ ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
በግብረ ሕማማት ውስጥ የሚገኙ ባዕድ ቃላት
በግብረ ሕማማት ውስጥ ወደ ግእዝም ሆነ በኋላ ወደ አማርኛ ሳይተረጎሙ የተቀመጡ የዕብራይስጥ፣ የቅብጥ እና የግሪክ ቃላት ይገኛሉ፡፡ የእነዚህ ቃላት ትርጉም የሚከተለው ነው፡፡
🔔 ኪርያላይሶን
ቃሉ የግሪክ ሲሆን አጠራሩ «ኪርዬ ኤሌይሶን» ነው፡፡ «ኪርያ» ማለት «እግዝእትነ» ማለት ሲሆን «ኪርዬ» ማለት ደግሞ «እግዚኦ» ማለት ነው፡፡ ሲጠራም «ኪርዬ ኤሌይሶን» መባል
አለበት፡፡ ትርጉሙም «አቤቱ ማረን» ማለት ነው፡፡ «ኪርያላይሶን» የምንለው በተለምዶ ነው፡፡ ይኼውም ኪርዬ ከሚለው «ዬ» ኤላይሶን ከሚለው ደግሞ «ኤ» በመሳሳባቸው በአማርኛ «ያ»ን ፈጥረው ነው፡፡
🔔 ናይናን
የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «መሐረነ፣ ማረን» ማለት ነው፡፡
🔔 እብኖዲ
የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «አምላክ» ማለት ነው፡፡ «እብኖዲ ናይናን» ሲልም «አምላክ ሆይ ማረን» ማለቱ ነው
🔔 ታኦስ
የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «ጌታ፣ አምላክ» ማለት ነው፡፡ «ታኦስ ናይናን» ማለትም «ጌታ ሆይ ማረን» ማለት ነው፡፡
🔔 ማስያስ
የዕብራይስጥ ቃል ሲሆነ ትርጉሙ «መሲሕ» ማለት ነው፡፡ «ማስያስ ናይናን» ሲልም «መሲሕ ሆይ ማረን» ማለት ነው
🔔 ትስቡጣ
«ዴስፓታ» ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም ደግ ገዥ ማለት ነው
🔔 አምነስቲቲ ሙኪርያቱ አንቲ ፋሲልያሱ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም «ተዘከረነ እግዚኦ በውስተ
መንግሥትከ- አቤቱ በመንግሥትህ አስበኝ» ማለት ነው፡፡
🔔 አምንስቲቲ መዓግያ አንቲ ፋሲልያሱ
የቅብጥ ቃል ሲሆን «ተዘከረነ ኦ ቅዱስ በውስተ መንግሥትከ - ቅዱስ ሆይ በመንግሥትህ አስበን» ማለት ነው አምንስቲቲ ሙዳሱጣ አንቲ ፋሲልያሱ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም «ተዘከረነ እግዚአ ኩሉ በውስተ መንግሥትከ- የሁሉ የበላይ የሆንክ ወይ በመንግሥትህ አስበን» ማለት ነው፡፡
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
በግብረ ሕማማት ውስጥ ወደ ግእዝም ሆነ በኋላ ወደ አማርኛ ሳይተረጎሙ የተቀመጡ የዕብራይስጥ፣ የቅብጥ እና የግሪክ ቃላት ይገኛሉ፡፡ የእነዚህ ቃላት ትርጉም የሚከተለው ነው፡፡
🔔 ኪርያላይሶን
ቃሉ የግሪክ ሲሆን አጠራሩ «ኪርዬ ኤሌይሶን» ነው፡፡ «ኪርያ» ማለት «እግዝእትነ» ማለት ሲሆን «ኪርዬ» ማለት ደግሞ «እግዚኦ» ማለት ነው፡፡ ሲጠራም «ኪርዬ ኤሌይሶን» መባል
አለበት፡፡ ትርጉሙም «አቤቱ ማረን» ማለት ነው፡፡ «ኪርያላይሶን» የምንለው በተለምዶ ነው፡፡ ይኼውም ኪርዬ ከሚለው «ዬ» ኤላይሶን ከሚለው ደግሞ «ኤ» በመሳሳባቸው በአማርኛ «ያ»ን ፈጥረው ነው፡፡
🔔 ናይናን
የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «መሐረነ፣ ማረን» ማለት ነው፡፡
🔔 እብኖዲ
የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «አምላክ» ማለት ነው፡፡ «እብኖዲ ናይናን» ሲልም «አምላክ ሆይ ማረን» ማለቱ ነው
🔔 ታኦስ
የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «ጌታ፣ አምላክ» ማለት ነው፡፡ «ታኦስ ናይናን» ማለትም «ጌታ ሆይ ማረን» ማለት ነው፡፡
🔔 ማስያስ
የዕብራይስጥ ቃል ሲሆነ ትርጉሙ «መሲሕ» ማለት ነው፡፡ «ማስያስ ናይናን» ሲልም «መሲሕ ሆይ ማረን» ማለት ነው
🔔 ትስቡጣ
«ዴስፓታ» ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም ደግ ገዥ ማለት ነው
🔔 አምነስቲቲ ሙኪርያቱ አንቲ ፋሲልያሱ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም «ተዘከረነ እግዚኦ በውስተ
መንግሥትከ- አቤቱ በመንግሥትህ አስበኝ» ማለት ነው፡፡
🔔 አምንስቲቲ መዓግያ አንቲ ፋሲልያሱ
የቅብጥ ቃል ሲሆን «ተዘከረነ ኦ ቅዱስ በውስተ መንግሥትከ - ቅዱስ ሆይ በመንግሥትህ አስበን» ማለት ነው አምንስቲቲ ሙዳሱጣ አንቲ ፋሲልያሱ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም «ተዘከረነ እግዚአ ኩሉ በውስተ መንግሥትከ- የሁሉ የበላይ የሆንክ ወይ በመንግሥትህ አስበን» ማለት ነው፡፡
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
Forwarded from ፩ ሃይማኖት
ጉልባን
ጉልባን ከባቄላ ክክ፣ ከስንዴ ወይንም ከተፈተገ ገብስ ጋር አንድ ላይ ተቀቅሎ የሚዘጋጅና የጸሎተ ሐሙስ ዕለት የሚባላ ንፍሮ ነው፡፡
የጉልባን ትውፊት እስራኤላውያን ከግብፅ ተሰደው በሚወጡበት ጊዜ በችኮላ ስለነበር፤ አቡክተው ጋግረው መብላት ያለመቻላቸውን ሁኔታ ያመለክታል፡፡ ያን ጊዜ ያልቦካውን ሊጥ
እየጋገሩ ቂጣ መብላት፤ ንፍሮም ቀቅለው ስንቅ መያዝ ተግባራቸው ነበርና ይህን ለማሰብ በሰሙነ ሕማማት ቂጣና
ጉልባን በማዘጋጀት በዓሉ ይታሰባል፡፡
በጸሎተ ሐሙስ ይህንን መሠረት በማድረግ የሚዘጋጀው ጉልባን
አንዲህም ቂጣ ጨው በዛ ተደርጎ ይጨመርበታል፡፡ ጨው ውኃ የሚያስጠማ በመሆኑ የጌታን መጠማት ያስታውሳል፡፡ ይህ ትውፊታዊ ሥርዓት ከእስራኤላውያን የመጣ ሲሆን በኢትዮጵያም አብዛኛዎቹ የትውፊት ክንዋኔዎች የብሉይ ኪዳን መነሻ ስላላቸው ሥርዓቱ ዛሬም ይከበራል፡፡
በዲ/ን ቤርዜሊ ተስፋዬ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ጉልባን ከባቄላ ክክ፣ ከስንዴ ወይንም ከተፈተገ ገብስ ጋር አንድ ላይ ተቀቅሎ የሚዘጋጅና የጸሎተ ሐሙስ ዕለት የሚባላ ንፍሮ ነው፡፡
የጉልባን ትውፊት እስራኤላውያን ከግብፅ ተሰደው በሚወጡበት ጊዜ በችኮላ ስለነበር፤ አቡክተው ጋግረው መብላት ያለመቻላቸውን ሁኔታ ያመለክታል፡፡ ያን ጊዜ ያልቦካውን ሊጥ
እየጋገሩ ቂጣ መብላት፤ ንፍሮም ቀቅለው ስንቅ መያዝ ተግባራቸው ነበርና ይህን ለማሰብ በሰሙነ ሕማማት ቂጣና
ጉልባን በማዘጋጀት በዓሉ ይታሰባል፡፡
በጸሎተ ሐሙስ ይህንን መሠረት በማድረግ የሚዘጋጀው ጉልባን
አንዲህም ቂጣ ጨው በዛ ተደርጎ ይጨመርበታል፡፡ ጨው ውኃ የሚያስጠማ በመሆኑ የጌታን መጠማት ያስታውሳል፡፡ ይህ ትውፊታዊ ሥርዓት ከእስራኤላውያን የመጣ ሲሆን በኢትዮጵያም አብዛኛዎቹ የትውፊት ክንዋኔዎች የብሉይ ኪዳን መነሻ ስላላቸው ሥርዓቱ ዛሬም ይከበራል፡፡
በዲ/ን ቤርዜሊ ተስፋዬ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
❖ "ተራሮችን በኃይሉ የሚያስታጥቃቸው ለማገልገል ማበሻ ጨርቅ ታጠቀ፡፡ የባሕርን ውኃ እንደ አቁማዳ የሚሰበስበው በቀላያትም መዝገቦች የሚሾማቸው ርሱ ከወዳጁ ከአልዓዛር ቤት የውኃ ማድጋ አንሥቶ እግሮችን ለማጠብ ያገለግልባት ዘንድ ወደ ኩስኩስት አፈሰሰ፡፡ እጆቻቸውንና እግሮቻቸውን በሚታጠቡበት ገንዘብ የናስ ኩስኩስት ሠርቶ በደብተራ ኦሪት ደጃፍ እንዲያኖራት ሙሴን ያዘዘው ውኃውን በኩስኩስት ሞልቶ የደቀ መዛሙርቱን እግር ሊያጥብ ዠመረ፡፡ የተረከዞቻቸውንም እድፍ በታጠቀው ማበሻ ጨርቅ አሸ፡፡"
{አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ}
{አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ}
❖ "በወገቡ የታጠቀውን ማድረቂያ አይተው መላእክት አደነቁ፤ ስሙ ከፀሓይና ከጨረቃ በፊት የነበረ ርሱ አገልጋይ ኾነ፤ ሕያው ጌታን ሱራፌል ያመሰግኑታል፤ ቦታውን ግን አያውቁም፤ ሱራፌልን የፈጠረ ርሱ በራት ጊዜ ወገቡን ዘርፍ ባለው ዝናር ታጠቀ፤ እንዳያቃጥል በመፍራት የማይታይ እሳት ለሐዋርያት አገልጋይ ኾኖ አብነት ይኾናቸው ዘንድ የትሕትና ሥራን የሚሠራበትን ውሃ በኩስኩስት ቀዳ የደቀ መዛሙርቱን አለቃ ጴጥሮስንም እግሩን ሊያጥበው ጠራው"
{ሃይ. አበው ዘያዕቆብ ዘሥሩግ ክፍል 9}
{ሃይ. አበው ዘያዕቆብ ዘሥሩግ ክፍል 9}
✟ክርስቶስ ተንስዓ ሙታን✟
✟አብይ ሀይል ወበስልጣን✟
✟አሰሮ ለሰይጣን✟
✟አግአዞ ለአዳም✟
✟ሰላም✟
✟እምይዜየሰ✟
✟ኮነ✟
✟ፍስሀ ወሰላም✟
"ሕያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጉታላችሁ ተነስቷል እንጂ በዚህ የለም"ሉቃ፦24፥5
"እንደተናገረ ተነስቷልና በዚህ የለም የተኛበትን ስፍራ ኑና እዩ" ማቴ፦28፥6
እንኳን አደረሰን መልካም በዓል ለሁላችንም!!!
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
✟አብይ ሀይል ወበስልጣን✟
✟አሰሮ ለሰይጣን✟
✟አግአዞ ለአዳም✟
✟ሰላም✟
✟እምይዜየሰ✟
✟ኮነ✟
✟ፍስሀ ወሰላም✟
"ሕያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጉታላችሁ ተነስቷል እንጂ በዚህ የለም"ሉቃ፦24፥5
"እንደተናገረ ተነስቷልና በዚህ የለም የተኛበትን ስፍራ ኑና እዩ" ማቴ፦28፥6
እንኳን አደረሰን መልካም በዓል ለሁላችንም!!!
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
Forwarded from ፩ ሃይማኖት
ለምን አንጾምም?
ተወዳጆች ሆይ የተሃድሶ መናፍቃን በዓለ ሃምሳን ለምን አትፆሙም ሲሉ ይደመጣሉ ከዛም አልፎ በዓቢይ ጾም የጾማችሁትን ለማካካስ ነው በማለት ይተቻሉ ቅድስት ቤተክርስቲያናችንስ ምን ትላለች?
ጥያቄ:- በበዓለ ሃምሳ ለምን አንጾምም?
በፍትሐ ነገሥት ላይ እንዲህ የሚል ትዕዛዝ አለ፦ "ዳግመኛ በየሳምንቱ ዓርብ እና ረቡዕን መጾም ነው፡፡ በዓለ ሃምሳ፣ የልደት እና የጥምቀት በዓል የተባበሩባቸው ጊዜ ካልሆነ በቀር" /ዐንቀጽ 15:566/።
"የዓርብን እና የረቡዕን ጾም ግን ከልደት፣ ከጥምቀት እና ከበዓለ ሃምሳ በቀር ዘወትር ይጹሙ" /ዐንቀጽ
15:603/። የዐቢይ ጾምን ፍቺ ተከትሎ ለ50 ቀናት የማንጾምበት ምክንያት
ብዙ ጥልቅ ምሥጢር ያለው ሥርዓተ ሃይማኖት ነው። በምሳሌ ለማስረዳትም ፦ ከትንሣኤ በፊት ያለውን አንድ ሳምንት ሰሙነ ሕማማት ብለን የምናስበው ዘመነ ኦሪት እንደሆነ በማሰብ ነው።
በዚኸ ሳምንት ከሌሎች ድርጊቶች በተጨማሪ መስቀል አንሳለምም። ይኸ የሆነበት ምክንያት በዘመነ ኦሪት መስቀል በክርስቶስ መለኮታዊ ደም ተባርኮ አልተሰጠም'ና ነው። ልክ
እንደዚሁ ከትንሣኤ ዕለት ጀምሮ አስከ በዓለ ጰራቂሊጦስ (አስከ የሐዋርያት ጾም መግቢያ ድረስ) ያሉት 50 ቀናት እንደ አንድ ቀን ነው የሚታዩት። ይህም ማለት ሰው ከትንሣኤ በኃላ ፍጹም
ያለ ድካም እንደሚኖር ለማስተማር ጾም እና የንስሐ ቀኖና አይሰጡም።
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ተወዳጆች ሆይ የተሃድሶ መናፍቃን በዓለ ሃምሳን ለምን አትፆሙም ሲሉ ይደመጣሉ ከዛም አልፎ በዓቢይ ጾም የጾማችሁትን ለማካካስ ነው በማለት ይተቻሉ ቅድስት ቤተክርስቲያናችንስ ምን ትላለች?
ጥያቄ:- በበዓለ ሃምሳ ለምን አንጾምም?
በፍትሐ ነገሥት ላይ እንዲህ የሚል ትዕዛዝ አለ፦ "ዳግመኛ በየሳምንቱ ዓርብ እና ረቡዕን መጾም ነው፡፡ በዓለ ሃምሳ፣ የልደት እና የጥምቀት በዓል የተባበሩባቸው ጊዜ ካልሆነ በቀር" /ዐንቀጽ 15:566/።
"የዓርብን እና የረቡዕን ጾም ግን ከልደት፣ ከጥምቀት እና ከበዓለ ሃምሳ በቀር ዘወትር ይጹሙ" /ዐንቀጽ
15:603/። የዐቢይ ጾምን ፍቺ ተከትሎ ለ50 ቀናት የማንጾምበት ምክንያት
ብዙ ጥልቅ ምሥጢር ያለው ሥርዓተ ሃይማኖት ነው። በምሳሌ ለማስረዳትም ፦ ከትንሣኤ በፊት ያለውን አንድ ሳምንት ሰሙነ ሕማማት ብለን የምናስበው ዘመነ ኦሪት እንደሆነ በማሰብ ነው።
በዚኸ ሳምንት ከሌሎች ድርጊቶች በተጨማሪ መስቀል አንሳለምም። ይኸ የሆነበት ምክንያት በዘመነ ኦሪት መስቀል በክርስቶስ መለኮታዊ ደም ተባርኮ አልተሰጠም'ና ነው። ልክ
እንደዚሁ ከትንሣኤ ዕለት ጀምሮ አስከ በዓለ ጰራቂሊጦስ (አስከ የሐዋርያት ጾም መግቢያ ድረስ) ያሉት 50 ቀናት እንደ አንድ ቀን ነው የሚታዩት። ይህም ማለት ሰው ከትንሣኤ በኃላ ፍጹም
ያለ ድካም እንደሚኖር ለማስተማር ጾም እና የንስሐ ቀኖና አይሰጡም።
@And_Haymanot
@And_Haymanot
❝የኪዳነምህረት ተዓምር!❞
ይህ ተዓምር የሆነው በጎፋ መንበረ ጸሐይ ቅድስት ኪዳነምህረት ቤተክርስትያን ነው። ደብሯም ይህቺ በፎቶው ላይ የምታይዋት እጅግ ውቧ ቤተክርስትያን ናት። የሆነውም እንዲህ ነው፦ ይህች የተዋበችው የኪዳነምህረት ቤተክርስትያን የጣሪያ ቆርቆሮዋ ቀለም በጸሐይ ምክንያት ይለቅና ለማየት የሚያምር አልሆነም።
ይሄኔ የደብሯ አገልጋዮች ቀለም ለማስቀባት ወስነው ቀለም እስከ ጉልላቱ ጫፍ ወጥቶ የሚቀባ ባለሞያ ይፈልጋሉ። አንድ ምስኪን ሰው የቀለም ባለሞያ "ደሞ ለጌታዬ እናት
ለኪዳነምህረት......" አለና መቀባት ይጀምራል። እየቀባ ከላይ ከጉልላቱም ይደርሳል። በድንገት ከመሬት እስከ 20 ሜትር (በግምት) ከሚርቀው ጣርያ አንሸራቶት እየተንከባለለ ይወድቃል። ይሄኔ እዚያው ቤተክርስትያን የነበሩ አገልጋዮች እና ጥቂት ምዕመናን ተደናግጠው እየጮሁ ከወደቀበት መጥተው ይመለከቱታል። የለም አይንቀሳቀስ አይናገር አይጋገር። ትንፋሹ
ግን ነበር። ተሸክመውት ወደ ሆስፒታል ይዘውት ይሄዳሉ። ሆስፒታል እንደደረሰ ሃኪሞች ይመረምሩታል። ከሰውየው የተጎዳ ምንም የሰውነት ክፍል ግን አልነበረም። በድንጋጤ ራሱን ስቶ
ብቻ ስለነበር ትንሽ እረፍት አድርጎ ተሸክመውት ከሄዱ አገልጋዮች እና ጥቂት ምዕመናን ጋር በእግሩ እየተራመደ
ተመለሰ። ይህን ያዩ ሁሉ እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ለኪዳነምህረት ምስጋና እያደረሱ ተመለሱ።
©ንሽኩር ረቢና!
15/08/2012 ዓ.ም (ሐሙስ)
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
ይህ ተዓምር የሆነው በጎፋ መንበረ ጸሐይ ቅድስት ኪዳነምህረት ቤተክርስትያን ነው። ደብሯም ይህቺ በፎቶው ላይ የምታይዋት እጅግ ውቧ ቤተክርስትያን ናት። የሆነውም እንዲህ ነው፦ ይህች የተዋበችው የኪዳነምህረት ቤተክርስትያን የጣሪያ ቆርቆሮዋ ቀለም በጸሐይ ምክንያት ይለቅና ለማየት የሚያምር አልሆነም።
ይሄኔ የደብሯ አገልጋዮች ቀለም ለማስቀባት ወስነው ቀለም እስከ ጉልላቱ ጫፍ ወጥቶ የሚቀባ ባለሞያ ይፈልጋሉ። አንድ ምስኪን ሰው የቀለም ባለሞያ "ደሞ ለጌታዬ እናት
ለኪዳነምህረት......" አለና መቀባት ይጀምራል። እየቀባ ከላይ ከጉልላቱም ይደርሳል። በድንገት ከመሬት እስከ 20 ሜትር (በግምት) ከሚርቀው ጣርያ አንሸራቶት እየተንከባለለ ይወድቃል። ይሄኔ እዚያው ቤተክርስትያን የነበሩ አገልጋዮች እና ጥቂት ምዕመናን ተደናግጠው እየጮሁ ከወደቀበት መጥተው ይመለከቱታል። የለም አይንቀሳቀስ አይናገር አይጋገር። ትንፋሹ
ግን ነበር። ተሸክመውት ወደ ሆስፒታል ይዘውት ይሄዳሉ። ሆስፒታል እንደደረሰ ሃኪሞች ይመረምሩታል። ከሰውየው የተጎዳ ምንም የሰውነት ክፍል ግን አልነበረም። በድንጋጤ ራሱን ስቶ
ብቻ ስለነበር ትንሽ እረፍት አድርጎ ተሸክመውት ከሄዱ አገልጋዮች እና ጥቂት ምዕመናን ጋር በእግሩ እየተራመደ
ተመለሰ። ይህን ያዩ ሁሉ እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ለኪዳነምህረት ምስጋና እያደረሱ ተመለሱ።
©ንሽኩር ረቢና!
15/08/2012 ዓ.ም (ሐሙስ)
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
Forwarded from ፩ ሃይማኖት
የያረድ ዉብ ዜማ
የያረድ ዉብ ዜማ ድንግል እመቤቴ ስጦታየ ነሺ / 2/
በምን አንደበቴ እንደምን ባለ ቃል ማርያም ልበልሺ/ 2
ምድርና ሰማዩ ተአምርሺን ይንገሩ
ፍጥረታት በሙሉ ስለ አንቺ ይመስክሩ
ተነግሮ የማያልቅ ድንቅ ነው ስራሺ
ድንግል ሆይ እናተ አምሳያም የለሺ
ማርያም ድንግል እረዳተ
የምትደርሺልኝ ነይ ስልሽ በጭንቀተ
ታምርሺን በአይነ አይቻለሁ
ጽዮን ሆይ ስልሽ ድንግል ሆይ እጠግባለሁ
አዝ - - -
የእግዚአብሀር ጥበቡ በአንቺ ተገለጠ
የአዳም ዘር በሙሉ ከሞት አመለጠ
ለፍጥረቱ ሁሉ መሰላል የሆንሺ
ነገን ባላውቅ እነም ቢያስፈራኚ
አንቺ ካለሺኝ በፍጹም አልወድቅም
በፊትሺም እንድቆም ለምስጋና
ማርያም ልበልሽ በትህትና
አዝ - - -
ትውልዱ በሙሉ ለምስጋና ይቁም
ባንቺ ስለሆነ የቀረለት መርገም
አዳም ከነልጁ በሰማይ በምድር
ማርያም ማርያም ይበል ተአምርሺን ይናገር
ጨለማው ከፊተ ተገፈፈ
ማርያም በምልጃሽ ልበ አረፈ
ከጎነ ነይ ስልሺ እጽናናለሁ
እሳት ገደሉን ሁሉንም አልፈዋለሁ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
የያረድ ዉብ ዜማ ድንግል እመቤቴ ስጦታየ ነሺ / 2/
በምን አንደበቴ እንደምን ባለ ቃል ማርያም ልበልሺ/ 2
ምድርና ሰማዩ ተአምርሺን ይንገሩ
ፍጥረታት በሙሉ ስለ አንቺ ይመስክሩ
ተነግሮ የማያልቅ ድንቅ ነው ስራሺ
ድንግል ሆይ እናተ አምሳያም የለሺ
ማርያም ድንግል እረዳተ
የምትደርሺልኝ ነይ ስልሽ በጭንቀተ
ታምርሺን በአይነ አይቻለሁ
ጽዮን ሆይ ስልሽ ድንግል ሆይ እጠግባለሁ
አዝ - - -
የእግዚአብሀር ጥበቡ በአንቺ ተገለጠ
የአዳም ዘር በሙሉ ከሞት አመለጠ
ለፍጥረቱ ሁሉ መሰላል የሆንሺ
ነገን ባላውቅ እነም ቢያስፈራኚ
አንቺ ካለሺኝ በፍጹም አልወድቅም
በፊትሺም እንድቆም ለምስጋና
ማርያም ልበልሽ በትህትና
አዝ - - -
ትውልዱ በሙሉ ለምስጋና ይቁም
ባንቺ ስለሆነ የቀረለት መርገም
አዳም ከነልጁ በሰማይ በምድር
ማርያም ማርያም ይበል ተአምርሺን ይናገር
ጨለማው ከፊተ ተገፈፈ
ማርያም በምልጃሽ ልበ አረፈ
ከጎነ ነይ ስልሺ እጽናናለሁ
እሳት ገደሉን ሁሉንም አልፈዋለሁ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
Forwarded from ፩ ሃይማኖት
ኃጥእ ነኝ ማለት ብቻ እውነተኛ ትህትና እንዳይደለ በእውነት እናገራለሁ፣ እውነተኛ ትህትናስ ትሩፋት መስራት ነው፡፡
🍃ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ🍃
@And_Haymanot
@AHati_Haymanot
መልካም ዕለተ ሰንበት ይሁንላችሁ
🍃ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ🍃
@And_Haymanot
@AHati_Haymanot
መልካም ዕለተ ሰንበት ይሁንላችሁ
አንድ ተማሪ በፈተና አዳራሽ ገብቶ ሁለት ጥያቄዎችን እንዲሠራ ተሰጠው። ጥያቄዎቹ እነዚህ ናቸው።
1. ስለ እግዚአብሔር ጻፍ
2. ስለ ሰይጣን ጻፍ የሚሉ ነበሩ።
ጥያቄዎቹን ካነበበ በኋላ ስለእግዚአብሔር ጻፍ የሚለውን ይጽፍ ጀመረ። ነገር ግን የተሰጠው ጊዜ አንድ ሰዓት ብቻ ስለነበር ሙሉውን ሰዓት ስለ እግዚአብሔር ሲጽፍ ቆይቶ ሰዐቱን ጨረሰ።
የፈተናውን ወረቀት የሚሰበስበት ጊዜ ደርሶ ደውል ተደወለ ብልሁም ተማሪ ሁለተኛውን ጥያቄ አለመሥራቱን ተረድቶ "ለሰይጣን ጊዜ የለኝም" ብሎ በአንድ መስመር መልስ ሰጠ።
ሰው ሆይ ለሰይጣን ጊዜ አይኑርህ።
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
1. ስለ እግዚአብሔር ጻፍ
2. ስለ ሰይጣን ጻፍ የሚሉ ነበሩ።
ጥያቄዎቹን ካነበበ በኋላ ስለእግዚአብሔር ጻፍ የሚለውን ይጽፍ ጀመረ። ነገር ግን የተሰጠው ጊዜ አንድ ሰዓት ብቻ ስለነበር ሙሉውን ሰዓት ስለ እግዚአብሔር ሲጽፍ ቆይቶ ሰዐቱን ጨረሰ።
የፈተናውን ወረቀት የሚሰበስበት ጊዜ ደርሶ ደውል ተደወለ ብልሁም ተማሪ ሁለተኛውን ጥያቄ አለመሥራቱን ተረድቶ "ለሰይጣን ጊዜ የለኝም" ብሎ በአንድ መስመር መልስ ሰጠ።
ሰው ሆይ ለሰይጣን ጊዜ አይኑርህ።
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
Forwarded from ፩ ሃይማኖት
✞ ግንቦት ፩ እመ አምላክ ድንግል ማርያም ከኢያቄምና ከሐና ስትወለድ የሆነውን ነገር ሐዋርያው ያዕቆብ የጻፈው ጥንታዊ መጽሐፍ ሲገልጽ፡፦
@And_Haymanot
"And Joachim(ኢያቄም) said: Now I know that the Lord has been gracious unto me, and has remitted all my sins . And he went down from the temple of the Lord justified,
and departed to his own house. And her months were fulfilled, and in the ninth month Anna(ሐና) brought forth. And she said to the midwife: What have I brought forth? And she said: A girl. And said Anna: My soul has been magnified this day. And she laid her down. And the days having been fulfilled, Anna was
purified, and gave the breast to the child, and called her name Mary." The Protoevangelium of James, 5
👉 @Konobyos
👉 @And_Haymanot
@And_Haymanot
"And Joachim(ኢያቄም) said: Now I know that the Lord has been gracious unto me, and has remitted all my sins . And he went down from the temple of the Lord justified,
and departed to his own house. And her months were fulfilled, and in the ninth month Anna(ሐና) brought forth. And she said to the midwife: What have I brought forth? And she said: A girl. And said Anna: My soul has been magnified this day. And she laid her down. And the days having been fulfilled, Anna was
purified, and gave the breast to the child, and called her name Mary." The Protoevangelium of James, 5
👉 @Konobyos
👉 @And_Haymanot
[ከእንጦጦ ሰማይ ስር]
(በመ/ሐ ዶ/ር ሮዳስ ታደሰ)
👉 ጸጥ ባለው ምሽት ነፋስ በበዛበት፤
ሰዎችም ቤታቸው ለዕረፍት በተኙበት፤
ድንቁን የአምላክ ሥራን በምሽት ለማየት፤
በእንጦጦ ተራራ ተገኘሁ በድንገት።
👉 ከዋክብት በሰማይ ያብረቀርቃሉ፤
ፕላኔት በጠፈር ደምቀው ይታያሉ፤
በአንድነት በመሆን የፈጣሪን ጥበብ ይመሰክራሉ።
👉 ቀደምት ኢትዮጵያውያን በዕውቀት የላቁ፤
በጠፈር ምርምር እየተራቀቁ፤
የሰማዩን ምስጢር ጠንቅቀው አወቁ፤
ያወቁትን ምስጢር ምንም ሳይደብቁ፤
በጽሑፍ አኑረው በጥበብ መጠቁ።
👉 ንግሥት ካሲዮፕያ ብትወድ ፈለክን፤
መሠየም ጀመረች ሕብረ ከዋክብትን።
👉 ሴፌውስ በአድናቆት እርሱም አስተውሎ፤
ከአንድሮሜዳ ጋር ፈጠነና ቶሎ፤
ያየውን አኖረ ለትውልዱ ብሎ።
👉 ቀደምቶች ያኖሩት የሰማይ ምስጢር፤
አስተዋይ እስኪኖር የሚመረምር፤
በክብር ይቀመጣል ዕውቀት እስኪከብር፤
በዕውቀት መራቀቅ ጊዜው እስኪጀምር።
👉 ቴሌስኮፑን ቶሎ በፍጥነት አቆምኩት፤
መመልከት ጀመርኩ ሰማዩን በትኩረት፤
የግዮኗ ኮከብ ሳይረስን አየኋት፤
የዐባይን ወንዝ መሙላት ቀደምት ያወቁባት።
👉 ኢዮብ የጠቀሰው የኦርዮን ኮከብ፤
ቀበቶውን አርጎ ውበትን በማበብ፤
ደምቆ እየታየ ተከቧል በክበብ።
👉 አይቼው ዞር ስል በሰሜኑ በኩል፤
ዝሁራ ቬነስ የጠፈር ዕንክብል፤
ደምቃ ትታይ ነበር በከዋክብት መሃል።
👉 ማዛሮትና ድብ እነኢዮብ ያይዋቸው፤
እነ ሔኖክ ቀድሞው የመረመሯቸው፤
የኢትዮጵያ ሊቆች የመዘገቧቸው፤
ይታያሉ በእውነት በደንብ ላጤናቸው።
👉 ደስ በሚል ምሽት የጨረቃም ድምቀት ተጨምሮበታል፤
ውስጧንም መመልከት በእጅጉ ያጓጓል።
👉 የጨረቃ ስሟ አንዴ አሶንያ ሌላ ጊዜ ቀመር፤
ብናሴና ኤራዕ ቢሉ ስሟን በማሽከርከር።
👉 ወርህም ዕብላም ቢሉ ደግሞም ሶልያና፤
ይህን ሁሉ ስሟን ጻፉት በብራና።
👉 አቅርቦ ቢያሳየኝ ቴሌስኮፑ ድንገት፤
እቺን ድንቅ ፍጥረት ለካስ ውብ ደማቅ ናት።
👉 ፈጣሪ ይመስገን እነዚህን ሁሉ በአንድነት ያስገኘ፤
ጥበብን የሚገልጽ በእውነት ለተመኘ።
👉 ከዚያ ከተመስጦው ደስ ከሚል ምሽት፤
የጠፈር ዕንቁዎች ደምቀው ካበሩበት፤
ዕውቀት ከሚያበዛው ደስ ከሚል ሌሊት፤
ጊዜው መሽቷልና ተነሣሁ በድንገት።
👉 ከተማ ደረስኩኝ የወሬ ማዕበል ወደ ሚጎርፍበት፤
ጫጫታና ሁከት ወደሰፈነበት፤
ጽሙና ዕርጋታ ከቶ የሌለበት፤
ተፈጥሮንም ማድነቅ የማይታሰብበት።
👉ቢሆንም!! አምላክ የእጅህ ሥራ በእጅጉ ይደንቃል፤
የዓለም ጫጫታን ከኅሊና ያጠፋል፤
አስተዋይ ልቡናን በደስታ ያራቅቃል፤
መንፈስን ልቡናን በፍቅር ያሞቃል፤
ሕሊናን መስጦ ወደ ላይ ያወጣል።
በመ/ሐ/ዶ/ር ሮዳስ ታደሰ
(ግንቦት 4/ 2012 ዓ.ም. ከሌሊቱ 12:12 ተጻፈ)
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
(በመ/ሐ ዶ/ር ሮዳስ ታደሰ)
👉 ጸጥ ባለው ምሽት ነፋስ በበዛበት፤
ሰዎችም ቤታቸው ለዕረፍት በተኙበት፤
ድንቁን የአምላክ ሥራን በምሽት ለማየት፤
በእንጦጦ ተራራ ተገኘሁ በድንገት።
👉 ከዋክብት በሰማይ ያብረቀርቃሉ፤
ፕላኔት በጠፈር ደምቀው ይታያሉ፤
በአንድነት በመሆን የፈጣሪን ጥበብ ይመሰክራሉ።
👉 ቀደምት ኢትዮጵያውያን በዕውቀት የላቁ፤
በጠፈር ምርምር እየተራቀቁ፤
የሰማዩን ምስጢር ጠንቅቀው አወቁ፤
ያወቁትን ምስጢር ምንም ሳይደብቁ፤
በጽሑፍ አኑረው በጥበብ መጠቁ።
👉 ንግሥት ካሲዮፕያ ብትወድ ፈለክን፤
መሠየም ጀመረች ሕብረ ከዋክብትን።
👉 ሴፌውስ በአድናቆት እርሱም አስተውሎ፤
ከአንድሮሜዳ ጋር ፈጠነና ቶሎ፤
ያየውን አኖረ ለትውልዱ ብሎ።
👉 ቀደምቶች ያኖሩት የሰማይ ምስጢር፤
አስተዋይ እስኪኖር የሚመረምር፤
በክብር ይቀመጣል ዕውቀት እስኪከብር፤
በዕውቀት መራቀቅ ጊዜው እስኪጀምር።
👉 ቴሌስኮፑን ቶሎ በፍጥነት አቆምኩት፤
መመልከት ጀመርኩ ሰማዩን በትኩረት፤
የግዮኗ ኮከብ ሳይረስን አየኋት፤
የዐባይን ወንዝ መሙላት ቀደምት ያወቁባት።
👉 ኢዮብ የጠቀሰው የኦርዮን ኮከብ፤
ቀበቶውን አርጎ ውበትን በማበብ፤
ደምቆ እየታየ ተከቧል በክበብ።
👉 አይቼው ዞር ስል በሰሜኑ በኩል፤
ዝሁራ ቬነስ የጠፈር ዕንክብል፤
ደምቃ ትታይ ነበር በከዋክብት መሃል።
👉 ማዛሮትና ድብ እነኢዮብ ያይዋቸው፤
እነ ሔኖክ ቀድሞው የመረመሯቸው፤
የኢትዮጵያ ሊቆች የመዘገቧቸው፤
ይታያሉ በእውነት በደንብ ላጤናቸው።
👉 ደስ በሚል ምሽት የጨረቃም ድምቀት ተጨምሮበታል፤
ውስጧንም መመልከት በእጅጉ ያጓጓል።
👉 የጨረቃ ስሟ አንዴ አሶንያ ሌላ ጊዜ ቀመር፤
ብናሴና ኤራዕ ቢሉ ስሟን በማሽከርከር።
👉 ወርህም ዕብላም ቢሉ ደግሞም ሶልያና፤
ይህን ሁሉ ስሟን ጻፉት በብራና።
👉 አቅርቦ ቢያሳየኝ ቴሌስኮፑ ድንገት፤
እቺን ድንቅ ፍጥረት ለካስ ውብ ደማቅ ናት።
👉 ፈጣሪ ይመስገን እነዚህን ሁሉ በአንድነት ያስገኘ፤
ጥበብን የሚገልጽ በእውነት ለተመኘ።
👉 ከዚያ ከተመስጦው ደስ ከሚል ምሽት፤
የጠፈር ዕንቁዎች ደምቀው ካበሩበት፤
ዕውቀት ከሚያበዛው ደስ ከሚል ሌሊት፤
ጊዜው መሽቷልና ተነሣሁ በድንገት።
👉 ከተማ ደረስኩኝ የወሬ ማዕበል ወደ ሚጎርፍበት፤
ጫጫታና ሁከት ወደሰፈነበት፤
ጽሙና ዕርጋታ ከቶ የሌለበት፤
ተፈጥሮንም ማድነቅ የማይታሰብበት።
👉ቢሆንም!! አምላክ የእጅህ ሥራ በእጅጉ ይደንቃል፤
የዓለም ጫጫታን ከኅሊና ያጠፋል፤
አስተዋይ ልቡናን በደስታ ያራቅቃል፤
መንፈስን ልቡናን በፍቅር ያሞቃል፤
ሕሊናን መስጦ ወደ ላይ ያወጣል።
በመ/ሐ/ዶ/ር ሮዳስ ታደሰ
(ግንቦት 4/ 2012 ዓ.ም. ከሌሊቱ 12:12 ተጻፈ)
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot