አላህ #ከዘረኝነት_ይጠብቀን
ዘረኝነት:– የራስን ቋንቋ፣ ባህልና ስርአት ማክበር፣ ቀጣይነት እንዲኖረውና እንዳይጠፋ መንከባከብ፣ ማንነትንም በዘርና በቋንቋ መግለፅ አይደለም!!።
ዘረኝነት:– የራስን ቋንቋ፣ ባህልና ስርአት: ከሌላው ዘርና ቋንቋ፣ ባህልና ስርአት: ከፍ አድርጎ መመልከት፣ የሌላውን ማንቋሸሽና አሳንሶ ማየት፣ ዕውቅና አለመስጠትና ዝቅ አድርጎ መመልከት ነው!!።
ዘረኝነት:– ራስን ከሌላው ለየት አድርጎ መመልከት፣ ለራሱ የሚገባውን ነገረረ ለሌሎቹ የማይገባ ነገር አድርጎ ማሰብ፣ በሌሎች ላይ ግዳጅ የሆነውን ነገር እኔን አይመለከተኝም ብሎ ማሰብ፣ አብሮነትን በመጠየፍ ለብቻ መመገብና ለብቻ መኖር ይገባኛል ማለት፣ በህይወት ተደሳች መሆን እኔ ብቻ ነኝ የሚገባኝ ማለት፣ የራሱን ዕልቅናና ክብር በሌሎች ውርደትና ዝቅተኝነት ላይ መገንባትን፣ የራስን ሀብትና ብልፅግና በሌሎች ድህነት ላይ መገንባትን፣ ሰላምና መረጋጋትን በሌሎች ረብሽና ወከባ ላይ መመስረትን፣ የራስን ህይወት በሌሎች ሞትና መስዋእትነት ላይ ማቆምን ማሰብ ነው!።
وَمِنْ آيَاتِهِ خَلْقُ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَاخْتِلَافُ أَلْسِنَتِكُمْ وَأَلْوَانِكُمْ ۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَاتٍ لِّلْعَالِمِينَ
(ሱረቱ አል-ሩም - 22)
ሰማያትንና ምድርንም መፍጠሩ፣ የቋንቋዎቻችሁና የመልኮቻችሁም መለያየት፣ ከአስደናቂ ምልክቶቹ ነው፡፡ በዚህ ውስጥ ለዐዋቂዎች ተዓምራቶች አልሉበት፡፡
يَا أَيُّهَا النَّاسُ إِنَّا خَلَقْنَاكُم مِّن ذَكَرٍ وَأُنثَىٰ وَجَعَلْنَاكُمْ شُعُوبًا وَقَبَائِلَ لِتَعَارَفُوا ۚ إِنَّ أَكْرَمَكُمْ عِندَ اللَّهِ أَتْقَاكُمْ ۚ إِنَّ اللَّهَ عَلِيمٌ خَبِيرٌ
(ሱረቱ አል-ሁጁራት - 13)
እናንተ ሰዎች ሆይ! እኛ ከወንድና ከሴት ፈጠርናችሁ፡፡ እንድትተዋወቁም ጎሳዎችና ነገዶች አደረግናችሁ፡፡ አላህ ዘንድ በላጫችሁ በጣም አላህን ፈሪያችሁ ነው፡፡ አላህ ግልጽን ዐዋቂ ውስጥንም ዐዋቂ ነው፡፡
"ሁላችሁም ከአደም ናችሁ። አደም ደግሞ ከዐፈር ነው" ነቢዩ ሙሐመድ
"ዐረብ የኾነው ዐረብ ባልኾነው ላይ አላህን በመፍራት ካልሆነ በቀር ብልጫ የለውም" ነቢዩ ሙሐመድ
"እሷ (ዘረኝነት) ጥንብ ናትና ተዏት" ነቢዩ ሙሐመድ
"ክፉ ስራው ወደ ኋላ የጎተተው: ዘሩ ወደፊት አያስቀድመውም" ነቢዩ ሙሐመድ
"ወደ ዘሩ (በዳይም ቢሆን ለማገዝ) የተጣራ፣ ለዘሩ ሲል (በባጢልም ቢሆን) የተጋደለ፣ ለዘሩ ብሎ (ያለ አግባብ) የሞተ ሰው ከኛ አይደለም" ነቢዩ ሙሐመድ
Join us➤ t.me/abuhyder
ዘረኝነት:– የራስን ቋንቋ፣ ባህልና ስርአት ማክበር፣ ቀጣይነት እንዲኖረውና እንዳይጠፋ መንከባከብ፣ ማንነትንም በዘርና በቋንቋ መግለፅ አይደለም!!።
ዘረኝነት:– የራስን ቋንቋ፣ ባህልና ስርአት: ከሌላው ዘርና ቋንቋ፣ ባህልና ስርአት: ከፍ አድርጎ መመልከት፣ የሌላውን ማንቋሸሽና አሳንሶ ማየት፣ ዕውቅና አለመስጠትና ዝቅ አድርጎ መመልከት ነው!!።
ዘረኝነት:– ራስን ከሌላው ለየት አድርጎ መመልከት፣ ለራሱ የሚገባውን ነገረረ ለሌሎቹ የማይገባ ነገር አድርጎ ማሰብ፣ በሌሎች ላይ ግዳጅ የሆነውን ነገር እኔን አይመለከተኝም ብሎ ማሰብ፣ አብሮነትን በመጠየፍ ለብቻ መመገብና ለብቻ መኖር ይገባኛል ማለት፣ በህይወት ተደሳች መሆን እኔ ብቻ ነኝ የሚገባኝ ማለት፣ የራሱን ዕልቅናና ክብር በሌሎች ውርደትና ዝቅተኝነት ላይ መገንባትን፣ የራስን ሀብትና ብልፅግና በሌሎች ድህነት ላይ መገንባትን፣ ሰላምና መረጋጋትን በሌሎች ረብሽና ወከባ ላይ መመስረትን፣ የራስን ህይወት በሌሎች ሞትና መስዋእትነት ላይ ማቆምን ማሰብ ነው!።
وَمِنْ آيَاتِهِ خَلْقُ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَاخْتِلَافُ أَلْسِنَتِكُمْ وَأَلْوَانِكُمْ ۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَاتٍ لِّلْعَالِمِينَ
(ሱረቱ አል-ሩም - 22)
ሰማያትንና ምድርንም መፍጠሩ፣ የቋንቋዎቻችሁና የመልኮቻችሁም መለያየት፣ ከአስደናቂ ምልክቶቹ ነው፡፡ በዚህ ውስጥ ለዐዋቂዎች ተዓምራቶች አልሉበት፡፡
يَا أَيُّهَا النَّاسُ إِنَّا خَلَقْنَاكُم مِّن ذَكَرٍ وَأُنثَىٰ وَجَعَلْنَاكُمْ شُعُوبًا وَقَبَائِلَ لِتَعَارَفُوا ۚ إِنَّ أَكْرَمَكُمْ عِندَ اللَّهِ أَتْقَاكُمْ ۚ إِنَّ اللَّهَ عَلِيمٌ خَبِيرٌ
(ሱረቱ አል-ሁጁራት - 13)
እናንተ ሰዎች ሆይ! እኛ ከወንድና ከሴት ፈጠርናችሁ፡፡ እንድትተዋወቁም ጎሳዎችና ነገዶች አደረግናችሁ፡፡ አላህ ዘንድ በላጫችሁ በጣም አላህን ፈሪያችሁ ነው፡፡ አላህ ግልጽን ዐዋቂ ውስጥንም ዐዋቂ ነው፡፡
"ሁላችሁም ከአደም ናችሁ። አደም ደግሞ ከዐፈር ነው" ነቢዩ ሙሐመድ
"ዐረብ የኾነው ዐረብ ባልኾነው ላይ አላህን በመፍራት ካልሆነ በቀር ብልጫ የለውም" ነቢዩ ሙሐመድ
"እሷ (ዘረኝነት) ጥንብ ናትና ተዏት" ነቢዩ ሙሐመድ
"ክፉ ስራው ወደ ኋላ የጎተተው: ዘሩ ወደፊት አያስቀድመውም" ነቢዩ ሙሐመድ
"ወደ ዘሩ (በዳይም ቢሆን ለማገዝ) የተጣራ፣ ለዘሩ ሲል (በባጢልም ቢሆን) የተጋደለ፣ ለዘሩ ብሎ (ያለ አግባብ) የሞተ ሰው ከኛ አይደለም" ነቢዩ ሙሐመድ
Join us➤ t.me/abuhyder
Telegram
የኡስታዝ አቡ ሀይደር ትምህርቶች ስብስብ
ኡስታዝ አቡ ሀይደር በፌስቡክ ያስተማራቸው የኦዲዮ የጹሁፍ እና የቪዲዮ ትምህርቶች ተሰባስበው የሚገኙበት ቻናል ነው።