የኡስታዝ አቡ ሀይደር ትምህርቶች ስብስብ
17.2K subscribers
306 photos
106 videos
47 files
801 links
ኡስታዝ አቡ ሀይደር በፌስቡክ ያስተማራቸው የኦዲዮ የጹሁፍ እና የቪዲዮ ትምህርቶች ተሰባስበው የሚገኙበት ቻናል ነው።
Download Telegram
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በረመዷን ወር በሐላባ፣ በሀድያና በከንባታ የሚገኙ ምስኪኖችን ለማስፈጠርና ወሩን ደስተኛ ኾነው እንዲያሳልፉ በኸይር ሥራ መተባበር የምትፈልጉ ሁሉ በነዚህ አካውንት የነየታችሁትን ያህል ማስገባት ትችላላችሁ!

SADIK MOHAMMED AHMED
COMMERCIAL BANK OF ETHIOPIA
1000317507589
0911 10 32 31

SADIK MOHAMMED AHMED
0871170135101
ወጋገን ባንክ
ስልክ 0911103231

SDIK MOHAMMED AHMED
1011300008645
ኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ
0911103231

ከነዚህ ውጭ በሌላ አካውንት እንዳታስገቡ!
የኡስታዝ አቡ ሀይደር ትምህርቶች ስብስብ
Voice message
📚አዲስ ትምሕርት 📚
"ኪታብ ኡሱሉል_ኢማን" ክፍል 19

🎙 አዘጋጅ⇊
በኡስታዝ አቡ ሀይደር

Mp3 ዳውሎድ ለማድረግ


Join ➤➤ t.me/abuhyder
Click and Like ➤➤ https://www.facebook.com/Ustaz.Abuhyder
የኡስታዝ አቡ ሀይደር ትምህርቶች ስብስብ
Voice message
Audio
📚አዲስ ትምሕርት
"ኪታብ ኡሱሉል_ኢማን" ክፍል 20

🎙 አዘጋጅ⇊
በኡስታዝ አቡ ሀይደር

Mp3 ዳውሎድ ለማድረግ


Join ➤➤ t.me/abuhyder
Click and Like ➤➤ https://www.facebook.com/Ustaz.Abuhyder
👍2
እንኳን ለ 1442ኛው የረመዷን ወር ፆም አላህ በሰላምና በጤና አደረሳችሁ!!

ጌታ አላህ ወሩን የተባረከ፣ የዒባዳ ወቅት ያድርግላችሁ። በተለይ በተለይ ዱዓእ ላይ እንበርታ። በኡምማው ላይ ክፋትና ተንኮልን ያሰቡ ጠላቶች: በራሳቸው ላይ እንዲገለበጥ አላህን አጥብቀን እንለምነው።

ረመዷን ሙባረክ
ለረመን ሰይጣናት ከታሰሩ ሰዎች ለምን አልሰለሙም?

በአቡ ሀይደር

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው
ክብርና ምስጋና ለዓለማቱ ጌታ ለአላህ የተገባ ይሁን (አል-ፋቲሓ 2)፡፡ የአላህ ሰላምና ውዳሴ የሰው ዘር ታላቅ መሪ ለሆኑት ለነቢዩ ሙሐመድ (አል-አሕዛብ 56) ለመላው የአላህ መልክተኞች (አል-ሷፍፋት 181) የሐቅንም መንገድ በተከተለ ሁሉ ላይ ይሁን (ጣሀ 47)፡፡

አንዱ ክርስቲያን ነው ይህን ጥያቄ ያቀረበው፡፡ እናንተ ሙስሊሞች እንደምትሉት በረመዷን ወር ሰይጣናት የሚታሰሩ ከሆነ፡ አሁን የሚያሳስተን የለምና፡ ለምን እኛ ክርስቲያኖች ሙስሊም አልሆንም ታዲያ? የሚል፡፡ ለዚህ ጥያቄም መጠነኛ ምላሹ እንዲህ ይቀርባል፡-

ጥቅላዊ ምላሽ፡-

ወገናችን! ሰዎችን ኹሉ ያከፈረው (ከሀዲ ያደረገው) ሸይጧን ነው ማን አለህ ቀድሞውኑ? እንደዛ ተብሎ ቢሆን ኖሮ፡ በታሰረ ጊዜ የከፈሩት በጠቅላላ ለምን ተመልሰው አልሰለሙም? የሚል ጤናማ ጥያቄ ማቅረቡ ተገቢ ይኾን ነበር፡፡ ግን ባልተባለ ነገር ላይ ቆሞ ጥያቄ ማቅረብ ትልቅ የአስተሳሰብ መዛባት ነው፡፡ ሸይጧን ለሰዎች ክህደትና አመጽ ጎትጓች በመሆኑ፡ የጥፋት ሰበብ ተደርጎ ይወሰዳል እንጂ፡ በሰዎች ልብ ላይ ተሹሞ፡ በልባቸውና በእምነት መካከል ጣልቃ በመግባት እንዳያምኑ ይጋርዳል አልተባለም፡፡ ይህን የማድረግ ስልጣንም አልተሰጠውም፡፡ እሱ ወደ ኃጢአት ይጣራል እንጂ፡ ኃጢአቱን የሚፈጽመው ሰውየው እራሱ ነው፡፡ ስለሆነም ስለ ሥራው ይጠየቃል፡፡ አንተም በሸይጧን መታሰር ሰበብ እኔ ለምን አልሰለምኩም ታዲያ? ላልከው፡ እውን ለመስለምና አላህን ብቻ ለማምለክ እራስህን አዘጋጅተህ ነበርን? ከሸይጧን የከፋውን ጠላትህንስ (ነፍሲያህን) መከተል አቁመህ ነበርን? በማለት ልንጠይቅህ እንወዳለን፡፡ እስኪ አንተም ውስጥህን መርምረውና የዚያኔ መልሱን ታገኘዋለህ፡፡

ዝርዝር ምላሽ፡-

1ኛ/ ከሁሉ በፊት ሊታወቅ የሚገባው ጉዳይ ቢኖር፡- ለማመንም ሆነ ለመካድ ሰበቡ ሰውየው እራሱ መሆኑን ነው፡፡ በእምነትና በክህደት ጉዳይ ላይ አንዱን በመምረጥ ቁርጥ ውሳኔ ለማድረግ የኛ ፈቃድ ሚናውን ይጫወታል፡፡ ሸይጣን ይህንን ውሳኔአችንን ለማስቀየር ወይንም ለመቀልበስ ምንም ስልጣን አልተሰጠውም፡፡ የሱ ድርሻው መጎትጎትና በኃጢአት ባሕር ላይ ዋኝተን እንድንቀር፡ በተውበት (ንሰሀ) ወደ አላህ መንገድ እንዳንመለስ፡ መጥፎውን ጥሩ በማስመሰል የማታለያ መንገዶችን መጠቀም ነው እንጂ፡ በፍጹም ሰው ከልቡ ወስኖ ለመስራት ያቀደውን ነገር (ጥሩም ሆነ መጥፎ) ለማገድና ለመቀየር የሚያስችል ስልጣን አልተሰጠውም! የለውምም፡፡

ያ ቢሆን ኖሮ፡ ስለኛ ኃጢአት የሚጠየቀው እሱ በኾነ ነበር፡፡ ስለዚህ አንተም ሙስሊም ያልኾንከው በተሰጠህ ነጻ-ፈቃድ የአላህን መንገድ ለመከተል ባለመምረጥህ ሰበብ እንጂ፡ ባንተ ፍላጎትና ፈቃድ ላይ ሸይጧን ተሸሞብህ ከልክሎህ አይደለም፡፡ ያ በመኾኑም የሸይጧን መታሰርም ሆነ መፈታት ባንተ ውሳኔ ላይ ምንም የሚያመጣው ለውጥ የለም፡፡ እሱ ከእውነት መንገድ ሰዎችን ለማገድ ከመጎትጎትና ወደ ጥፋት መንገድ ከመጥራት ውጭ ሌላ አቅም አልተሰጠውምና፡፡ የአላህ ቃል በትንሳኤው ዕለት (የውሙል ቂያም) በሸይጧንና በተከታዮቹ መካከል ስለሚደረገው የቃላት ምልልስ እንዲህ ይነግረናል፡-

" وَقَالَ الشَّيْطَانُ لَمَّا قُضِيَ الْأَمْرُ إِنَّ اللَّهَ وَعَدَكُمْ وَعْدَ الْحَقِّ وَوَعَدْتُكُمْ فَأَخْلَفْتُكُمْ وَمَا كَانَ لِيَ عَلَيْكُمْ مِنْ سُلْطَانٍ إِلَّا أَنْ دَعَوْتُكُمْ فَاسْتَجَبْتُمْ لِي فَلَا تَلُومُونِي وَلُومُوا أَنْفُسَكُمْ مَا أَنَا بِمُصْرِخِكُمْ وَمَا أَنْتُمْ بِمُصْرِخِيَّ إِنِّي كَفَرْتُ بِمَا أَشْرَكْتُمُونِ مِنْ قَبْلُ إِنَّ الظَّالِمِينَ لَهُمْ عَذَابٌ أَلِيمٌ " سورة إبراهيم 22
"ነገሩም በተፈጸመ ጊዜ፣ ሰይጣን ይላቸዋል፦ አላህ እውነተኛውን ቃል ኪዳን ገባላችሁ፤ ቃል ኪዳንም ገባሁላችሁ፤ አፈረስኩባችሁም፣ ለኔም በናንተ ላይ ምንም ሥልጣን አልነበረኝም ግን ጠራኋችሁ፤ ለኔም ታዘዛችሁ ስለዚህ አትውቀሱኝ፤ ነፍሶቻችሁንም ውቀሱ እኔ የምረዳችሁ አይደለሁም፤ እናንተም የምትረዱኝ አይደላችሁም፤ እኔ ከአሁን በፊት ለአላህ ተጋሪ በአደረጋችሁት ነገር ካድኩ፤ በዳዮቹ ለነርሱ በእርግጥ አሳማሚ ቅጣት አልላቸው።" (ሱረቱ ኢብራሂም 14፡22)፡፡

ይህ አንቀጽ የሚያስረዳው፡- አላህ በባሮቹ መካከል ፍትሐዊ ዳኝነትን በመዳኘት፡ የጀነቱም ወደ ጀነት፣ የጀሀነሙም ወደ ጀሀነም እንዲገባ ፍርድንና ውሳኔን ባስተላለፈ ወቅት፡ ሸይጧንም ለከሀዲያን፡- አላህ መቀስቀስና ከሞት መነሳት፡ ከዛም በእኔ ዘንድ ቆማችሁ መዳኘትና፡ ለሥራችሁ ተገቢ የኾነን ክፍያ እከፍላችኋለሁ በማለት፡ በነቢያቱ አንደበትና በመለኮታዊ መጽሐፍቱ አማካኝነት እውነተኛ ቃል ኪዳንን ገብቶላችሁ ነበር፡፡ እኔ ደግሞ፡ ሞቶ መቀስቀስ የሚባል ነገር የለም፡፡ ጀነት እና ጀሀነም የሚባለውን ዓለምም ማንም ሄዶ ያየው የለም፡ ስለዚህ በዚህቹ ምድራዊ ህይወታችሁ እንዳሻችሁ ሁኑ፡ ምንም አትሆኑም አይዟችሁ! በማለት የሀሰት ቃልን ገብቼላችሁ አፈረስኩ፡፡ ቢሆንም እናንተ እኔን መውቀስ አትችሉም!፡፡ ምክንያቱም እኔ ስጠራችሁ እሺ ብላችሁ የታዘዛችሁኝ እናንተው ናችሁ እንጂ፡ እኔ እናንተን ለማስገደድ ስልጣን አልነበረኝምና፡፡ ያ በመሆኑም የገዛ ነፍሳችሁን ውቀሱ እንጂ፡ እኔን አትውቀሱ! አሁን እኔ እናንተን የምረዳችሁ፡ ወይም እናንተ እኔን የምትረዱ አይደላችሁምና፡ በምድራዊ ህይወታችሁ ከአላህ ሌላ በማምለክ ባጋራችሁበት ነገር ሁሉ ክጃለሁ አላውቃችሁም! እንደሚላቸው ነው፡፡

እኛም የአላህን ቃል ተከትለን የምንለው፡- ሰዎች ኢስላምን እንዳይቀበሉ ሸይጧን ጉትጎታ ከማቅረብ ውጭ ሌላ ሚና የለውም፡፡ ኃይሉን ተጠቅሞ ማስቆምም አይችልም ነው፡፡ ደግሞም የሸይጧን ተንኮሉ ደካማ ነውና፡ በአላህ ኃይልና እገዛ ኃይሉንና ተንኮሉን መና ማስቀረት ይቻላል፡፡ የአላህ ቃል እንዲህ ይላል፡-

" الَّذِينَ آمَنُوا يُقَاتِلُونَ فِي سَبِيلِ اللَّهِ وَالَّذِينَ كَفَرُوا يُقَاتِلُونَ فِي سَبِيلِ الطَّاغُوتِ فَقَاتِلُوا أَوْلِيَاءَ الشَّيْطَانِ إِنَّ كَيْدَ الشَّيْطَانِ كَانَ ضَعِيفًا " سورة النساء 76
"እነዚያ ያመኑት ሰዎች፣ በአላህ መንገድ ይጋደላሉ፤ እነዛ የካዱትም በጣዖት መንገድ ይጋደላሉ፤ የሰይጣንንም ጭፍሮች ተጋደሉ። የሰይጣን ተንኮል ደካማ ነውና።" (ሱረቱ-ኒሳእ 4፡76)፡፡

2ኛ/ ሰው ነጻ ፈቃድ ያለው ፍጡር ነው፡፡ እንደ ሮቦት በተሞላው ነገር ብቻ የሚንቀሳቀስ ግኡዝ ፍጥረት አይደለም፡፡ ነጻ ፈቃድም ስላለው ከአምላኩ ዘንድ፡- ይህንን አድርግ! ይህንን ደግሞ አትቅረብ! የሚል መለኮታዊ ትእዛዝን በኃላፊነት ተቀብሏል፡፡ በኃላፊቱም ልክ፡ ነገ በጌታው ዘንድ ይጠየቃል፡፡ ግዳጁን በአግባቡ ተወጥቶ እንደኾን የጌታውን እዝነት ጀነትን ይጎናጸፋል፡፡ ግዳጁን ችላ ብሎ የሸይጧንን መስመር ተከትሎ እንደኾን የጌታውን የቁጣው መገለጫ የኾነውን ጀሀነም እሳትን ይገባል፡፡
እንግዲያውስ ሸይጧን በሰው ነጻ ፈቃድ ላይ ጣልቃ በመግባት፡ ሰዎችን ከመልካም ሥራ በማገድ እንቅፋት መሆን ከቻለ፡ የኛ ነጻ ፈቃድ ትርጉሙ ምኑ ላይ ነው? አንድ አባት በጠዋቱ ማልዶ ይነሳና ልጁን፡- ከሰአት ለምሳ ቤት እስክመለስ ድረስ ከገበያ ወጥተህ እነዚህን ነገራት ገዝተህ ጠብቀኝ! በማለት ትእዛዝ ይሰጠውና፡ ልጁን ከበሩ ማገር ጋር እንዳይንቀሳቀስ ጥፍር አድርጎ አስሮት ወደ ስራው ይኼዳል፡፡ ይህ አባት ከሰዓት ላይ ለምሳ ወደቤቱ ሲመለስ፡ ልጁን እዛው የታሰረበት በሩ ላይ ያገኘውና፡ የላክሁህን እቃ ለምን አላመጣህም? በማለት ይቀጣዋል፡፡ አሁን የዚህ አባት እርምጃ ትክክለኛ ነበር! ብሎ የሚያስብ ሰው ይኖራልን? በፍፁም የለም! ከተባለ ደግሞ፡- እንግዲያውስ አባት ለልጁ ከሚያዝነው በላይ፡ ለባሮቹ የሚራራው አምላክስ፡ የሱን ትእዛዛት እንዳናከብር ሰይጣን በኃይሉ እንቅፋት ሲሆንብን፡ እያየና እየሰማ በዝምታ በማለፍ፡ ከዚያም የቂያም ቀን፡ ለምን ትእዛዜን አላከበራችሁም በማለት ይቀጣናል ብሎ ማሰብስ እንዴት ይቻላል?

ለምን ሰው የገዛ ነፍሱን ድክመት በሸይጧን ጉትጎታ ያሳብባል? አላህም እኮ ነጻ ፈቃድ የሰጠን፡ አመስጋኝ ሆነን የእምነትን መንገድ እንድንከተል፡ ወይንም ከሀዲ ሆነን የጥመትን መንገድ በመከተል በፈቃዳችን እንድንወስን ነው፡፡ የአላህ ቃል ሲናገር እንዲህ ይላል፡-

" إِنَّا خَلَقْنَا الْإِنْسَانَ مِنْ نُطْفَةٍ أَمْشَاجٍ نَبْتَلِيهِ فَجَعَلْنَاهُ سَمِيعًا بَصِيرًا (2) إِنَّا هَدَيْنَاهُ السَّبِيلَ إِمَّا شَاكِرًا وَإِمَّا كَفُورًا " سورة الإنسان 3-2
"እኛ ሰዉን፥ (በሕግ ግዳጅ) የምንሞክረዉ ስንሆን፥ ቅልቅሎች ከሆኑ የፍትወት ጠብታ ፈጠርነዉ፤ ሰሚ ተመልካችም አደረግነዉ። እኛ፥ ወይ አመስጋኝ ወይም ከሐዲ ሲሆን መንገዱን መራነዉ፤ (ገለጽንለት)።" (ሱረቱል ኢንሳን 76፡2-3)፡፡

3ኛ/ ሌላው ወገናችን ያልተረዳው ነጥብ፡ ሸይጧናት ይታሰራሉ ሲባል፡ ሁሉንም አለመሆኑን ነው፡፡ በነቢያዊ ትምሕርቱ ላይ እንደተብራራው፡ እነዚህ በረመዷን ወር የሚታሰሩት ሸይጧናት እጅግ አመጸኞቹን አስቸጋሪዎቹን እንደሆነ ነው፡፡ ቀጣዩ ሐዲሥም ይህን እውነት እንዲህ ይገልጸዋል፡-

عن أبي هريرة رضي الله عنه قال : قال رسول الله صلى الله عليه وسلم: ( إِذَا كَانَ أَوَّلُ لَيْلَةٍ من شَهْرِ رَمَضَانَ صُفِّدَتِ الشَّيَاطِينُ وَمَرَدَةُ الْجِنِّ ، وَغُلِّقَتْ أَبْوَابُ النَّارِ فلم يُفْتَحْ منها بَابٌ ، وَفُتِّحَتْ أَبْوَابُ الْجَنَّةِ فلم يُغْلَقْ منها بَابٌ ...) الحديث ، رواه الترمذي (682) ، وابن ماجه (1642) ، وحسَّنه الألباني في " صحيح الجامع " (759).
ከአቢ ሁረይራህ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደተላለፈው የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "የረመዷን ወር የመጀመሪያው ለሊት ሲገባ፡ ሸይጧናትና አመጸኛ ጂንኒዎች ይታሰራሉ፡፡ የጀሀነም በሮች አንድም ሳይቀር ይከረቸማሉ፡፡ የጀነት በሮች አንድም ሳይቀር ይከፈታሉ…" (ቲርሚዚይ 682፣ ኢብኑ ማጀህ 1642፣ አልባኒይ ሶሒሑል ጃሚዕ 759)፡፡)

ከዚህ ሐዲሥ በመነሳት፡ በረመዷን የሚታሰሩት፡ ለሰዎች አስቸጋሪና አመጸኛ የሆኑ ሸይጧናት መሆናቸውን መረዳት እንችላለን፡፡ አቅመ ደካማዎቹና ሽሜዎቹ ደግሞ የጉትጎታ ሥራቸውን ይቀጥላሉ ማለት ነው፡፡ ወላሁ አዕለም፡፡

4ኛ/ በተጨማሪም ይህ ወገናችን የሳተው ነገር፡ ሰዎቹን ከአላህ መንገድ ለማደናቀፍ ያላሰለሰ ጥረት የሚያደርገው ከጂንኒ ወገን የኾነው ሸይጧንን ብቻ አድርጎ መሳሉ ነው፡፡ የገዛ ነፍሲያችንም (ስሜት) እጅግ አደገኛ ጠላት ነው፡፡ ሰው የሸይጧንን ጉትጎታ ማሸነፍ የሚችለው፡ በነፍሲያው ላይ ድልን ከተቀዳጀ በኋላ ነው፡፡ ነፍሲያችን ትእዛዝን አትወድም፡፡ ስሜትንና ዝንባሌን እንድንከተል ትመክረናለች፡፡ ከአላህ መንገድና እሱን ከማምለክ ታዘናጋናለች፡፡ ስለዚህ የሸይጧን ጉትጎታ ብቻ ሳይሆን የገዛ ነፍሲያችንም ከኛው ጋር ትግል ውስጥ መሆኗን ማወቅ አለብህ፡፡ አንተንም ለመስለም የሚከለክልህ ይህ የነፍሲያህ እምቢተኝነት መሆኑን አስተውለሀልን?

5ኛ/ በመጨረሻም ለዚህ ወገናችን የምናስተላልፈው መልእክት፡ ሂዳያ (ቅኑን ጎዳና ማግኘት) የአላህ ተውፊቅ (መልካሙን ዕድል እንድታገኝ መግጠም) እንጂ፡ የገዛ ሥራችን ውጤት አይደለም፡፡ እኛ መሆን የምንችለው ነገር ቢኖር ሰበብ መሆን ብቻ ነው፡፡ ውጤቱ ግን ከአላህ ዘንድ ብቻ የሚሰጥ ነው፡፡ ስለዚህ ዕድሜህን ሙሉ ከአላህ መንገድ ወጥተህ፡ የነፍሲያህና የሸይጧን መጫወቻ ለመሆን ፈቅደህ ስታበቃ፡ ሸይጧን ነው ከመንገድ ያስወጣኝ ማለት አያዋጣም፡፡ ቅድሚያ ነፍሲያህንና ሸይጧንን ታግለህ በአላህ መንገድ ለመታገል ከወሰንክ አላህም ቅኑን ጎዳና እንደሚመራህ በመግለጽ ቃልን ገብቷልና፡ አንተም ለማመን እራስህን አዘጋጅ፡ ሸይጧን ስለታሰረ የሚሰልም፡ ስለተፈታ ደግሞ የሚክድ ሰው የለምና፡፡ የአላህ ቃል እንዲህ ይላል፡-

" وَالَّذِينَ جَاهَدُوا فِينَا لَنَهْدِيَنَّهُمْ سُبُلَنَا وَإِنَّ اللَّهَ لَمَعَ الْمُحْسِنِينَ " سورة العنكبوت 69
"እነዚያም በኛ መንገድ የታገሉ መንገዳችንን በእርግጥ እንመራቸዋለን፤ አላህም በእርግጥ ክበጎ ሠሪዎች ጋር ነው።" (ሱረቱል ዐንከቡት 29፡69)፡፡

Click and Like ➤➤
https://www.facebook.com/Ustaz.Abuhyder
የረመዷን ትውስታ የ5 ደቂቃ መልዕክት ስሁርና ኢፍጧር ክፍል 1
በኡስታዝ አቡ ሐይደር

Join ➤➤ t.me/abuhyder
Click and Like ➤➤ https://www.facebook.com/Ustaz.Abuhyder
የኡስታዝ አቡ ሀይደር ትምህርቶች ስብስብ
Voice message
የረመዷን ትውስታ የ5 ደቂቃ መልዕክት እስቲግፋር በረመዷን ክፍል 2
በኡስታዝ አቡ ሐይደር

Join ➤➤ t.me/abuhyder
Click and Like ➤➤ https://www.facebook.com/Ustaz.Abuhyder
👍2
Forwarded from .
ኢዜማ እስልምናን የኢትዮጵያ ደህንነት ስጋት አድርጎ የገለጸበት ሚስጥራዊ ሰነድ ይፋ ወጣ
====================================================
«የኢዜማን እውነተኛ ማንነት የማያውቀው ህዝብ እንዳይሸወድ መረጃውን ሼር በማድረግ ህዝቡን እናንቃ! የፓርቲው ማንነት ከቀን ወደ ቀን ይበልጥ ፍንትው እያለ መጥቷል።»
||
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) የተሰኘው የፖለቲካ ፓርቲ በዘንድሮው 6ኛው የሃገራችን ምርጫ ከሚሳተፉ የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል አንዱ ነው። በርካታ እጩዎችን በማስመዝገብ ከአሁኑ ገዢ ፓርቲ (ብልፅግና) በመቀጠል ሁለተኛ ደረጃ ይዟል።

የዚህ ፓርቲ ሊቀመንበር የሆኑት ብርሃኑ ነጋ (ዶ/ር) የርሳቸው ፓርቲ ከተመረጠ ኢስላማዊ ባንክ እንደማይፈቅድ ከአሁን በፊት የተናገሩ ሲሆን፤ ይህን እውነታ ከቀናት በፊት በድጋሜ ማረጋገጣቸው ይታወቃል።
*
ይህ በእንዲህ እንዳለ ሰሞኑን ከዚህ ፓርቲ ያፈተለከ አንድ ሚስጥራዊ መረጃ ይፋ ወጥቷል።
ኢዜማ የሃገሪቷን ወቅታዊ የደህንነት ስጋት የተነተነበት አንድ ባለ 14 ገፅ ሚስጥራዊ ሰነድ አዘጋጅቷል። ዶ/ር ብርሃኑ በዚህ ሰነዳቸው ላይ ከፓርቲያቸው ከኢዜማ እና ከመሰሎቹ በስተቀር ለሀገር ደህንነት ስጋት ብሎ ያልፈረጁት የለም።
ሰነዱ «የሃገሪቷ ወቅታዊ የደህንነት ስጋት ትንተና» ይሰኛል

[ሙሉውን 14ቱንም ገፅ በዚህ ሊንክ ብትገቡ ታገኙታላችሁ።
https://tttttt.me/MuradTadesse/10898]
*
በዚህ ሰነድ ላይ በርካታ አካላት የሃገራችን የደህንነት ስጋት ተብለው የተጠቀሱ ሲሆን፤ እስልምናን በተመለከተ ግን «ወቅታዊ የብሄራዊ ደህንነት ስጋቶች» በተሰኘው የሰነዱ የመጀመሪያ ክፍል ላይ «ጽንፈኝነት» በተሰኘ ዐውድ ስር ገፅ 7 እና 8 ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት በአጽንኦት ተጠቅሷል።
ሰነዱ ካነሳቸው ነጥቦች መካከል፦
①) የእስልምና አክራሪነት በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች እየተስፋፋ መሆኑ፣
②) የእስልምና ኃይማኖት ተከታዮች በብዛት በሚገኙባቸው አካባቢዎች ላይ የእስልምናን አክራሪነት በወጣቱ ላይ የማስረጽ ሥራ እየተሠራ መሆኑ፣
③) በሃገሪቱ የሚነሱ የተለያዩ ቀውሶችን ከማስነሳት አልፎ እስከ ማባባስ ድረስ እየሠሩ መሆኑ፣
④) መስጅዶች የዚህ እንቅስቃሴ ዋነኛ መፍለቂ መሆናቸው፣
⑤) በተለያዩ ባለሃብቶች እንደሚደግፉና የተጠናከረ ህቡዕ አንድነት ያላቸው መሆኑን፣
⑥) ከግብፅ፣ ከሳዑዲ ዓረቢያና ከኳታር ጋር ለዚሁ አላማ ጥብቅ ግንኙነት ያላቸው መሆኑ፣
⑦) የገቢ ምንጫቸው ከውጭ የሚላክ ገንዘብ፣ ከኮንትሮባንድ ሥራ፣ ከመዓድናት ሽያጭና መንግስት በማያውቀው በሌላ መልክ ገቢ የሚያገኙ መሆኑን፣
⑧) አይኤስ፣ አል-ቃዒዳና አል-ሸባብ በኢትዮጵያ እንቅስቃሴ የጀመሩ መሆኑን፣
⑨) ሙስሊም ምሁራንና የማህበረሰብ አንቂዎች ለእምነታቸው የተቆረቆሩ በመምሰል ህዝብ ወደ ጽንፈኝነት እንዲገባ ለመሥራት አቅደው ቆርጠው የተነሱ መሆኑን፣
⑩) ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) በጽንፈኛ ሙስሊሞች የሚሾፈር ስለሆነ እንዲታገድ… ወዘተ የሚሉ እጅግ በጣም አደገኛና መርዘኛ ሃሳቦች ተነስተዋል።

በግሌ ከዚህ ሰነድና ከዚህ በፊትም ኢዜማ ካለው አመለካከት በመነሳት፤
ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ደህንነት ከኢዜማ የበለጠ ስጋት እንደሌለ ተረድቻለሁ።
*
የሚመለከተው አካል የዚህን ፓርቲ መርዘኝነት ተረድቶ ከወዲሁ ከምርጫ ቦርድ ቢያሰናብተው መልካም ነው።
ገና ስልጣን ሳይዙ ይህን ያክል መርዘኛ ከሆኑ፤ አቅሙን ካገኙ ደግሞ ምን ሊሆኑ እንደሚችሉ ለመገመት የግድ ሩቅ አዋቂ መሆን አይጠበቅም።

*
«የፓርቲውን መርዘኝነት ሼር በማድረግ እናሳውቅ! ህዝቡ ሊነቃ ይገባል!»
||
t.me/MuradTadesse
👍2
#ሰላቱ-ተራዊሕ "ቂያሙ–ለይል"
በአቡ ሀይደር
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኛ በሆነው፡፡
ምስጋና የዓለማት ጌታ ለሆነው ለአላህ የተገባ ነው፡፡ የአላህ ውዳሴና ሰላም የሰላም አለቃና መምህር ለሆኑት ለነቢዩ ሙሐመድ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ይሁን፡፡ ድልና የበላይነት ሐቅን ለማንገስና ሀሰትን ለማርከስ በደልን አጥፎቶ ፍትህን ለማስፈን ዕውቀታቸውን፣ ንብረታቸውን፣ ጉልበታቸውን፣ ጊዜያቸውንና ህይወታቸውን መስዋእት በማድረግ ለሚታገሉት ይሁን፡፡

ብዙ ጊዜ ወደ መስጂድ በመሄድ ከዒሻ ሱንነቱል-ባዕዲያ ቡኋላ የሚሰገደውን ሶላት (ቂያሙ-ለይል) ከኢማሙ ጋር አንጨርሰውም፤ መሐል ላይ እናቋርጣለን፡፡ ወይም ተራዊሕ ጨርሰን ዊትሩን ለቤት ብለን እንወጣለን፡፡፡ ይህ ተግባር የተከለከለ ባይሆንም አግባብነት የለውም፡፡ ለሊቱን ሙሉ በሶላት እንደቆመ እንዲታሰብለት የሚፈልግ አንድ ሙስሊም ከኢማሙ ጋር ሁሉንም አብሮ መጨረስ አለበት፡፡ በመሐል ያለ-ምንም አስገዳጅ ምክንያት ኳቋረጠ ቃል የተገባለትን አጅር ያጣል፡፡ ሐዲሡ የሚለው እንዲህ ነው፡-
አቢ ዘር (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደነገረን የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "ከኢማሙ ጋር እስኪያጠናቅቅ አብሮት የቆመ(የሰገደ) ለሊቱን ሙሉ እንደሰገደ ይጻፍለታል" (ነሳኢይ 1605፣ ቲርሚዚይ 806፣ ኢብኑ ማጀህ 1327)፡፡

በዚህ ምክንያት ሁሉንም ከኢማሙ ጋር ማጠናቀቅ ይገባናል፡፡ አንዳንድ ሰዎች ደግሞ፡- በተጨማሪ ለሊት ላይ ተነስቼ ከሰሑር በፊት መስገድ ስለምፈልግ ነው ዊትሩን የተውኩት ይላሉ፡፡
አላህ ወፍቆት ለይል ላይ በድጋሚ ተነስቶ መስገድ የሚፈልግ ሰውም ተራዊሕን እስከ ዊትሩ ከኢማሙ ጋር አብሮ መስገዱ አይከለክለውም፡፡ ‹‹ከዊትር በኋላ ሶላት የለም!›› ወይም ‹‹የመጨረሻ ሶላታችሁን ዊትር አድሩጉ›› የሚለው ሐዲሥ ክልከላን ሳይሆን አለመስገዱ የተወደደ መሆኑን ለማመላከት የመጣ እንደሆነ የኢስላም ሊቃውንት ያስረዳሉ፡፡ በተጨማሪም የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) አንዳንድ ጊዜ ከዊትር በኋላ ረከዐተይን (ሁለት ረከዓህ) ይሰግዱ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ይህም የሚጠቁመው ከዊትር በኋላ ሶላት መስገድ እንደሚቻል ነው፡፡ ስለዚህ ለይልን በድጋሚ ተነስተህ የምትሰግድ ከሆነ ባለ ጥንድ ረከዓህ (ሁለት ሁለት) እያደረግህ ስገድ፡፡ በድጋሚ ግን ዊትር እንዳትሰግድ፡፡ በአንድ ለሊት ሁለት ዊትር የለምና፡፡

ሌላው በተራዊሕ ወቅት በጁዝእ የሚሰገድባቸው መስጂድ ውስጥ ከሆንክ ቁርኣን ወይም ሞባይልህ ውስጥ የጫንከውን ከፍተህ ኢማሙን ከምትከታተል ሞባይልህን አጥፍተህ ቀልብህን ሰብስበህ የኢማምህን ቂርኣት በማዳመጥ መከታተሉ ላንተ በላጭ ነው፡፡ ምክንያቱም፡-
1ኛ) ቀኝ እጅን በግራ ላይ ደርቦ በደረት ላይ አሳርፎ የማስቀመጡ ሱንና አያመልጥህምና፡፡ ቁርኣኑን ወይም ሞባይሉን ከፍተህ የምትከታተል ከሆነ ግን የግድ ቀኝ እጅህ ካረፈበት ቦታ ይነሳል፡፡
2ኛ) አላስፈላጊ እንቅስቃሴዎችን ትቆጥባለህ፡፡ ኢማሙ ጨርሶ ወደ ሩኩዕ ሲወርድ አንተ ግን፡ ሞባይልህን ወደ ኪስ ለመክተት፡ ቁርኣን ከሆነ ደግሞ መሬት ለማስቀመጥ ቦታ ፍለጋ ውስጥ ትገባለህ፡፡ ቁርአንን ደግሞ ከስሩ ምንም ነገር ሳይኖር መሬት ማስቀመጥ አይቻልም፡፡
3ኛ) በሞባይል ቁርኣን እየተከታተልክ ምንም ስልክህ ሳይለንት ቢሆንም ሰው ከደወለልህ ቁርኣኑን ሸፍኖ የደዋዩን ቁጥር ማሳየቱ አይቀርም፡፡ ስልኩን በመዝጋት ስራ ተጠምደህ አንተም አዛ ልትሆን ነው፡፡ ልብህም ከሶላቱ ወጥቶ (ኤጭ ምን አይነቱ ነው!) የሚል ስራ ውስጥ ሊገባ ነው፡፡ ታዲያ የቱ ይሻልሀል?
ሶስቱ ታላላቅ የኢስላም ሊቃውንቶች (ኢብኑ ዑሠይሚን፣ ኢብኑ ባዝ፣ አልባኒ ራሕመቱላሂ ዐለይሂም) በዚህ ጉዳይ ላይ ክልክል ነው ብለው ባያወግዙም በላጩ ግን መተዉ ነው በማለት መክረዋል፡፡
4ኛ) እኔ ከሞባይል ወይንም ዋና ቁርኣን ከፍቼ ካልተከታተልኩ እንቅልፍ ይመጣብኛል፡፡ ነሻጣዬም ይጠፋል፡፡ ድካም ድካም ይሰማኛል፡፡ ቀልቤ ከሶላት ይወጣል፡፡ ስከታተል ግን የበለጠ እጠነክራለሁ ምትሉ ካላችሁ ደግሞ፡- ታላቁ ዓሊም ሸይኽ ኢብኑ ጅብሪን (ረሒመሁላህ) ችግር የለውም መጠቀም ይችላሉ በማለት ፈትዋ ሰጥተዋል፡፡ ራሳችንን የምናውቀው እኛው ነን፡፡ በዚህ ጊዜ ግን ሰው እየደወለ አዛ እንዳያደርገን የሞባይሉን ኔትወርክ ኦፍላይን እናድርገው፡፡ ወይም call setting ውስጥ በመግባት ወደሌላ ቁጥር divert እናድርገው፡፡ ወይም ሲስተሙን ቢዚ አድርጉት፡፡
ደግሞም ‹‹ኢንና አዕጠይና ፣ ለወገብ ጤና›› እያልን በጁዝእ ከሚሰገድባቸው መስጂዶች አንራቅ፡፡ ዛሬ በዚህ ዱንያ ላይ እግሮችህ ለአላህ መቆምን ካበዙ በምትኩ ነጌ በአኼራ በቃጠሎው ቀን መቆሙ ይቀንስላቸዋልና፡፡ አላህ ይወፍቀን፡፡

ለእህቶች፡-
‹‹የአላህን ሴት ባሪያዎች ከአላህ ቤት (መስጂድ) መሄድን አትከልክሏቸው›› የሚለውን ስለ-መብታችሁ የተነገረውን ሐዲሥ ምርኩዝ አድርጋችሁ ከእህቶቻችሁ ጋር በኅብረት ለመስገድ ወደ አላህ ቤት ካቀናችሁ ቀጥሎ ያሉትን ነገራት አደራ ተጠንቀቁ፡-
1) ሒጃባችሁን ጠብቁ፡- ከቤት ስትወጡ ብቻ ሳይሆን መስጂድ ገብታችሁ እስክትሰግዱ ሰግዳችሁም ወደ ቤት እስክትመለሱ ድረስ ሒጃባችሁ ጥብቅ ይሁን፡፡ ወንዶችን የሚፈትን አይነት አለባበስ ለብሳችሁ አትውጡ፡፡ አላህን ፍሩ፡፡ ደግሞም ሽቶ ተቀብታችሁ አትውጡ፡፡ ለማነው የምትዋቡት? ውበታችሁና መዓዛችሁ ለባለቤታችሁ እና ለግላችሁ እንጂ ውጪ ላለ ሰው መሆን ስለሌለበት ከቤት ስትወጡ ተጠንቀቁ፡፡
2) ሰልፍ ማስተካከል፡- አንደኛው ችግራችሁ ነው ይባላል፡፡ (ባለቤቴ እንደነገረቺኝ)፡፡ ሶላት ላይ ተራርቃችሁ ሳይሆን ተጠጋግታችሁ እግር ለእግር ተነካክታችሁ ስገዱ፡፡ በመሐል ሸይጣን እንዳይገባባችሁ ክፍተት አትፍጠሩ፡፡ ምነው በረመዷን ታስሮ አይደል? ካላችሁም አዎ! አመጸኞቹ ታስረዋል፡፡ ሽሜዎቹ እና ደካሞቹ ግን ዕድላቸውን ይሞክራሉና ክፍተት አትፍጠሩላቸው፡፡ መስጂዱ ስላልሞላ በሚል ተበታትናችሁም አትስገዱ፡፡
3) ህጻናትን በተቻለ መጠን መስጂድ አታምጧቸው፡፡ እናንተም እህቶቻችሁም በነሱ ሰበብ አዛ እንዳትሆኑ፡፡ ማምጣቱ ግድ ከሆነና ሰውን አዛ የሚያደርጉ ከሆነም ተገንጥላችሁ ስገዱ፡፡
4) የመጣችሁበት ዓላማ ዒባዳ እስከሆነ ድረስ ሙሉ ተራዊሕን ከኢማሙ ጋር ስገዱ፡፡ አንዳንዴ ከሁለቱ ኢማሞች በድምጹ ማማር የምንወደው ኢማም ከግማሽ በኋላ ከሆነ እሱ እስኪመጣ ድረስ በማለት ገለል ብለን ቁርኣን መቅራት ወይም እንተኛና እሱ ሲጀምር ቀስቅሱኝ እንላለን፡፡ ይህ ስህተት ነው፡፡ የለሊቱን ቂያም ሙሉ አጅር ከፈለግን ሁሉንም እንስገድ፡፡ ወላሁ አዕለም፡፡
አላህ ሆይ! በረመዳን ውስጥ ካለው ኸይር ነገር የምንጠቀም አድርገን! አሚን!
Join ➤➤ t.me/abuhyder
Click and Like ➤➤ https://www.facebook.com/Ustaz.Abuhyder
👍3
የኡስታዝ አቡ ሀይደር ትምህርቶች ስብስብ
Voice message
የረመዷን ትውስታ የ5 ደቂቃ መልዕክት "ሁሉም የሰውነት ክፍል መፆም አለበት" ክፍል 3 በኡስታዝ አቡ ሐይደር

Join ➤➤ t.me/abuhyder
Click and Like ➤➤ https://www.facebook.com/Ustaz.Abuhyder
#ዐሽሩል_አዋኺር
በ አቡ ሀይደር
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው
የረመዷን ሀያ ለሊቶች አለፉ፡፡ አላህ ወፍቆት ኸይር የሸመተበትም ሆነ ነፍሲያው አሸንፎት ወደ ኋላ ያስቀረው ይኖራል፡፡ አሁን የቀረውን ጌዜ ግን መጠቀም የሁሉም ድርሻ ነው፡፡ አላህ ዕድሜ ሰጥቶን የምንጠቀም ያድርገን፡፡ ነቢያችን (ዐለይሂ-ሶላቱ ወስ-ሰላም) በረመዷን የመጨረሻው አስርት ቀናት ውስጥ በዒባዳ በሌላው ጊዜ ከሚበረቱት የበለጠ ይበረቱ ነበር (ሙስሊም የዘገበው)፡፡
በዚህ ለሊት ውስጥ የምትጠበቅ አንድ ለሊት አለች፡፡ እሷም ‹‹ለይለቱል-ቀድር›› ትባላለች፡፡ ይህችን ለሊት አላህ ወፍቆት ምሽቷን በዒባዳና በመልካም ተግባር ያሳለፈ የአላህ ባሪያ፡ አላህ ስራውን ከተቀበለው የሚያገኘው ትርፍ እጥፍ ድርብ ነው፡፡ እሱም፡- በሌላ ጊዜ ለአንድ ሺህ ወራት (83 ዓመት ከ4 ወር) ያህል በዒባዳ በማሳለፍ ከሚያገኘው አጅር በላይ ይሆንለታል ነው፡፡ አንዷ ለሊት 83 ዓመታትን በልጣ ተገኘች፡፡ አላሁ አክበር! አላህ ይወፍቀን፡፡
ከዛሬ ማቅሰኞ ምሽት ጀምሮ የረመዷን 21ኛ ለሊት ይጀመራል፡፡ በተከታታይ የሚመጡትን ምሽቶች በዒባዳ ለማሳለፍ እኛም ከልብ ነይተን፡ በአላህ በመታገዝ ቆርጠን እንነሳ፡፡ የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የረመዷን የመጨረሻው አስርት ቀናት ሲገባ ወገባቸውን ጠበቅ በማድረግ (በመዘጋጀት) ለሊቱን በዒባዳ ህያው ያደርጉት ነበር፣ ቤተሰቦቻቸውንም ይቀሰቅሱ ነበር (ቡኻሪና ሙስሊም)፡፡
ለይለቱል-ቀድርን ለማግኘት ከልቡ አምኖና አላህ ዘንድም የሚያገኘውን ምንዳ በማሰብ በሶላት (በዒባዳ) ላይ ያሳለፋት ሰው ያለፈው ኃጢአቱ እንደሚማርለት በሐዲሥ ተገልጾአል (ቡኻሪና ሙስሊም)፡፡
አላህ ወፍቆት ለይለቱል-ቀድርን ለማግኘት አስርቱን ቀናት በዒባዳ የሚያሳልፍ የአላህ ባሪያ ለይለቱል ቀድር በዛሬው ምሽት እንደተገኘች ሊያውቅበት የሚችልባቸው መንገዶች አሉ፡፡ ከነዚህም ውስጥ፡-
ሀ. ጸሀይ ጨረር አልባ መሆኗ፡- ኡበይ ኢብኑ ከዕብ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደነገረን ለይለቱል-ቀድር በለሊቱ ክፍል ከታየች፡ በንጋቱ ጸሀይ በምትወጣ ግዜ እንደተለመደው ጨረር አይኖራትም፡፡ ያለ ጨረር ነጣ ብላ ብቅ ትላለች፡፡ (ሙስሊም 762)፡፡
ለ. ለሊቱ ብርዳማም ሞቃትም አይሆንም፡- ሁሉም ባለበት ሃገር ላይ ባለው የአየር ንብረት ሁኔታ የሚወሰን ነው፡፡ ለይለቱል-ቀድር በምትታይበት ለሊት፡ የለሊቱ ሁኔታ ከዛ በፊት ከነበሩትና ከዛ በኋላ ከሚመጡት ቀናቶች አንጻር ሞቃታማም ሳትሆን ቀዝቃዛም ሳትሆን፡ ሰላማዊ ሆና የምታነጋ ለሊት ነች በማለት ዐብዱላህ ኢብኑ-ዐባስ (ረዲየላሁ ዐንሁማ) ከነቢያችን (ዐለይሂ-ሶላቱ ወስ-ሰላም) የሰማውን ሐዲሥ አስተላልፎልናል (ሶሒሕ ኢብኑ ኹዘይማህ 2192)፡፡
በነጋታው ይህን ምልክት አየሁ ብሎ ግን ከዒባዳ መሸሽ ትልቅ ስህተት ነው፡፡ ይልቁኑ በቀጣዮቹ ተከታታይ ቀናት ያሳለፍነውን ቀን ለይለቱል-ቀድር ታይቶበት ከሆነ አላህ እንዲቀበለን ዱዓ በማድረግ የበለጠ ልንበረታ ይገባል፡፡ በዚህ ለሊት የሚሰሩ መልካም ተግባራትን በተመለከት ለቀባሪው ማርዳት ነውና ብዙም የምለው ነገር የለኝም፡፡ በዚክር፣ በዱዓእ፣ በኢስቲግፋር፣ በቁርኣን ንባብ፣ በለይል ሶላት፣ በነቢያችን ላይ ሶላዋት በማውረድ… እንበራታ፡፡ አላህ ይወፍቀን

Join ➤➤ t.me/abuhyder
Click and Like ➤➤ https://www.facebook.com/Ustaz.Abuhyder
ዘካተል ፊጥር ምንድን ነው ?ለማነው ሚገባው ? በኡስታዝ አቡ ሐይደር
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
መፅሀፍ ቅዱስን አፍዘሃልን?
በእጅህ ስንት ሰዎች ሰለሙ ?

ሌሎችም ጥያቄዎች

ምላሽ በኡስታዝ አቡ ሐይደር
👇👇👇👇👇
https://youtu.be/VgwAzttm4ts
https://youtu.be/VgwAzttm4ts
ከ ኡስታዝ አሕመዲን ጀበል ፔጅ የተወሰደ!!

የጎዳና ላይ ኢፍጣር ዝግጅቱ ነገ ግንቦት 03/2013 በዚያው አደባባይ ከቀኑ በ10 ጀምሮ በመንግስት ሙሉ ወጪ በጸጥታ ኃይሉ ጥበቃና አጀብ ይደረጋል።አንድ ሆነን በጋራ ከቆምን ሌሎች ጥያቄዎቻችንንም እንዲሁ እናስመልሳለን።

Sagantaan Ifxaara kaleesaa dhorkamee bakkuma sila karoorfameetti bor caamsaa 03/2013 baasii guutu mootumaadhaan Qaama nageenyyatiin kabajaan eegamaa sa'a 10 irraa kaasee ni godhama. Tokko taanee yoo waliin dhaabbannee gaaffilee keenya kaanis akkasuma ni debisiifna.
እንኳን ለ1442ኛው የዒዱል ፊጥር በዓል አላህ በሰላም አደረሳችሁ!

ዒዱኩም ሙባረክ!

ተቀበለላሁ ሚንና ወሚንኩም!