ግድያ በመጽሐፍ ቅዱስ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኛ በሆነው፡፡
17፥33 *”ያቺንም አላህ ያወገዛትን ነፍስ ያለ ሕግ አትግደሉ”*፡፡ وَلَا تَقْتُلُوا النَّفْسَ الَّتِي حَرَّمَ اللَّهُ إِلَّا بِالْحَقِّ
መጽሐፍ ቅዱስ የፍቅር እና የሰላም መጽሐፍ ነው ለምትሉ ሁሉ ከፍትሕ ጋር በተያያዘ አራት ጥያቄዎችን እንጠይቃለን፦
ቁጥር አንድ
መጽሐፍ ቅዱስ የሰላምና የፍቅር መጽሐፍ ከሆነ እንዴት ሰውን ግደሉ ይላል?
ሕዝ 9፥6፤ “”ሽማግሌውንና ጐበዙን ቈንጆይቱንም ሕፃናቶቹንና ሴቶቹን”” ፈጽማችሁ “”ግደሉ””፤ ነገር ግን ምልክቱ ወዳለበት ሰው ሁሉ አትቅረቡ፤ በመቅደሴም ጀምሩ አላቸው። በቤቱም አንጻር ባሉ ሽማግሌዎች ጀመሩ።
መሳ 21:10 ማኅበሩም ወደዚያ አሥራ ሁለት ሺህ ኃያላን ሰዎች ሰድደው። ሂዱ በኢያቢስ ገለዓድም ያሉትን ሰዎች “”ከሴቶችና ከሕፃናት”” ጋር በሰይፍ ስለት “ግደሉ””።
1ሳሙ 15:3፤ አሁንም ሄደህ አማሌቅን ምታ፥ ያላቸውንም ሁሉ ፈጽመህ አጥፋ፥ አትማራቸውም፤ “”ወንዱንና ሴቱን ብላቴናውንና ሕፃኑን በሬውንና በጉን ግመሉንና አህያውን ግደል””።
ዘዳ 20:14 ነገር ግን “”ሴቶቹንና ሕፃናትን እንስሶቹንም”” በከተማይቱም ያለውን ምርኮ ሁሉ በዝብዘህ ለአንተ ትወስዳለህ፤ አምላክህም እግዚአብሔር የሚሰጥህን የጠላቶችህን ምርኮ ትበላለህ።
ዘዳ.3:6፤ በሐሴቦንም ንጉሥ በሴዎን እንዳደረግን ፈጽሞ አጠፋናቸው፤ ከተሞቹን ሁሉ “”ከወንዶችና ከሴቶች ከሕፃናቶችም ጋር አጠፋናቸው””።
ኢያ 6:21፤ በከተማይቱም የነበሩትን ሁሉ፥ “”ወንዱንና ሴቱን፥ ሕፃኑንና ሽማግሌውን፥ በሬውንም በጉንም አህያውንም፥ በሰይፍ ስለት ፈጽመው አጠፉ””።
እንደ ምዕራባውያን ሚዛን ሰው የፈለገውን ማምለክ መብቱና ነፃነቱ አይደለምን? ከዚያ አልፎ አረጋውያንን፣ ሴቶችን፣ ሕፃናትንና እንስሳቱን መግደል ለምን አስፈለገ? እስቲ ይነበብ ይህን የፍቅርና የሰላም መጽሐፍ።
ቁጥር ሁለት
መጽሐፍ ቅዱስ የሰላምና የፍቅር መጽሐፍ ከሆነ እንዴት ሰውን እረዱ ይላል?
ዘጸ 32:27 የእናንተም ሰው ሁሉ ወንድሙን ወዳጁንም ጎረቤቱንም “ይረድ” וְהִרְג֧וּ አላቸው።
1ነገ 18:40 ኤልያስም ከበኣል ነቢያት አንድ ሰው እንዳያመልጥ ያዙ አላቸው። ያዙአቸውም፤ ኤልያስም ወደ ቂሶን ወንዝ ወስዶ በዚያ “”አሳረዳቸው”” וַיִּשְׁחָטֵ֖ם።
2ነገ 10:11 ኢዩም ከአክዓብ ቤት የቀረውን ሁሉ፥ ታላላቆቹንም ሁሉ፥ ወዳጆቹንና ካህናቱን ማንም ሳይቀር በኢይዝራኤል “አረዳቸው” וַיִּשְׁחָטֵ֖ם ።
2ነገ 10:14፤ እርሱም። በሕይወታቸው ያዙአቸው አለ። ያዙአቸውም፥ በበግ ጠባቂዎችም ቤት አጠገብ ባለው ጕድጓድ አርባ ሁለቱን ሰዎች “አረዷቸው” וַיִּשְׁחָטֵ֖ם ፤ ማንንም አላስቀረም።
1ሳሙ 17:51፤ ዳዊትም ሮጦ በፍልስጥኤማዊው ላይ ቆመ፤ ሰይፉንም ይዞ ከሰገባው መዘዘው፥ ገደለውም፥ ራሱንም “አረደው” וַיְמֹ֣תְתֵ֔הוּ ።
ይህ ምንድን ነው? ቄራ ወይስ የፍቅርና የሰላም መጽሐፍ?
ቁጥር ሶስት
መጽሐፍ ቅዱስ የሰላምና የፍቅር መጽሐፍ ከሆነ እንዴት ሰውን በእሳት አቃጥሉ ይላል?
ዘሌ 20:14 ማናቸውም ሰው እናቲቱንና ልጂቱን ቢያገባ ርኵሰት ነው፤ በመካከላችሁ ኃጢአት እንዳይሆን እርሱና እነርሱ “”በእሳት ይቃጠሉ””።
ዘሌ 21:9 የካህንም ልጅ ራስዋን በግልሙትና ብታረክስ አባትዋን ታረክሰዋለች፤ “”በእሳት ትቃጠል””።
ኢያ 7:15 እርም የሆነውም ነገር የተገኘበት ሰው የእግዚአብሔርን ቃል ኪዳን አፍርሶአልና፥ በእስራኤልም ዘንድ በደል አድርጎአልና እርሱና ያለው ሁሉ “”በእሳት ይቃጠላሉ””።
ዘዳ 7:5 ነገር ግን እንዲህ አድርጉባቸው፤ መሠዊያቸውን አፍርሱ፥ ሐውልቶቻቸውንም ሰባብሩ፥ የማምለኪያ ዐፀዶቻቸውንም ቍረጡ፥ የተቀረጸውን ምስላቸውንም “”በእሳት አቃጥሉ””።
ዘዳ 7:25 የተቀረጸውንም የአምላኮቻቸውን ምስል “”በእሳት ታቃጥላለህ””፤ የተሠራባቸውን ብርና ወርቅ አትመኝ፤ በአምላክህም በእግዚአብሔር ዘንድ ርኩስ ነውና እንዳትጠመድበት ከእርሱ ምንም አትውሰድ።
ዘዳ 12:3 መሠዊያቸውንም አፍርሱ፥ ሐውልቶቻቸውንም ሰባብሩ፥ የማምለኪያ ዐፀዶቻቸውንም “”በእሳት አቃጥሉ””፥ የአማልክቶቻቸውንም የተቀረጹ ምስሎች አንከታክቱ፤ ከዚያም ስፍራ ስማቸውን አጥፉ።
ኢያ 8:8 በያዛችኋትም ጊዜ ከተማይቱን “”በእሳት አቃጥሉአት””፤ እንደ እግዚአብሔር ቃል አድርጉ፤ እነሆ፥ አዝዣችኋለሁ።
ሰው የሚያመልክበትን የማምለኪያ አፀድ እና የሚኖርበትን ከተማ ማቃጠል ፍቅር ነውን?
ቁጥር አራት
መጽሐፍ ቅዱስ የሰላምና የፍቅር መጽሐፍ ከሆነ እንዴት ሰው ባልሠራው በደል አባቶቻቸው በሠሩት በደል ይገደሉ ይላል?
ይህም ትልቅ በደል ነው፦
በደል አንድ
አካን ሰርቆ ባጠፋው ወንዶችና ሴቶች ልጆቹንም፥ በሬዎቹንም፥ አህያዎቹንም፥ በጎቹንም ለምን መቃጠልና መወገር አስፈለገ?
ኢያሱ 7፥24-25 ኢያሱና እስራኤል ሁሉ የዛራን ልጅ አካንን፥ ብሩንም፥ ካባውንም፥ ወርቁንም፥ #ወንዶችና ሴቶች ልጆቹንም፥ በሬዎቹንም፥ አህያዎቹንም፥ በጎቹንም#፥ ድንኳኑንም፥ ያለውንም ሁሉ ወስደው ወደ አኮር ሸለቆ አመጡአቸው። ኢያሱም። ለምን አስጨነቅኸን? እግዚአብሔር ዛሬ ያስጨንቅሃል አለው እስራኤልም ሁሉ በድንጋይ ወገሩት# በእሳትም አቃጠሉአቸው#፥ #በድንጋይም ወገሩአቸው#።
በደል ሁለት
በሙሴ ዘመን አማሌቃውያን ከእስራኤል በመዋጋት ተዋጉ፦
ዘጸአት 17፥8 አማሌቅም መጥቶ ከእስራኤል ጋር በራፊድም ተዋጋ።
በሙሴ ዘመን አማሌቃውያን ከእስራኤል በመዋጋት በበደሉት ከ 400 ዓመት በኃላ የልጅ ልጆቻቸውን በሬውንና በጉን ግመሉንና አህያውን በማስገደል ተበቀለ፤ ይህ ምን የሚሉት በደል ነው?
1ኛ ሳሙኤል 15፥2-3 የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ “”እስራኤል ከግብጽ በወጣ ጊዜ”” አማሌቅ በመንገድ እየተቃወመ ያደረገበትን #እበቀላለሁ#። አሁንም ሄደህ አማሌቅን ምታ፥ ያላቸውንም ሁሉ ፈጽመህ አጥፋ፥ አትማራቸውም #ወንዱንና ሴቱን ብላቴናውንና ሕፃኑን በሬውንና በጉን ግመሉንና አህያውን ግደል#።
አባቶች ስለ ልጆች አይገደሉ፥ ልጆችም ስለ አባቶች አይገደሉ ነገር ግን ሁሉ እያንዳንዱ በኃጢአቱ ይገደል የሚለው ትዕዛዛት የት ገባና ነው ምንም የማያቁትን ህፃናት ከ 400 ዓመት በኃላ የተፈጁት?
ዘዳግም 24፥16 አባቶች ስለ ልጆች አይገደሉ፥ ልጆችም ስለ አባቶች አይገደሉ ነገር ግን ሁሉ እያንዳንዱ በኃጢአቱ ይገደል።
2ኛ ነገሥት 14፥6 በሙሴ ሕግ መጽሐፍም እንደ ተጻፈ፥ እግዚአብሔርም፦ ሁሉ በኃጢአቱ ይሙት እንጂ አባቶች በልጆች አይሙቱ፥ ልጆችም በአባቶች አይሙቱ ብሎ እንዳዘዘ የነፍሰ ገዳዮቹን ልጆች “አልገደለም””።
ይህንን የሰው ደም ያለበት መጽሐፍ ነው እንግዲህ የፍቅር እና የሰላም መጽሐፍ እየተባለ የሚሰበክለት? ፍርዱ ለኅሊና።
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኛ በሆነው፡፡
17፥33 *”ያቺንም አላህ ያወገዛትን ነፍስ ያለ ሕግ አትግደሉ”*፡፡ وَلَا تَقْتُلُوا النَّفْسَ الَّتِي حَرَّمَ اللَّهُ إِلَّا بِالْحَقِّ
መጽሐፍ ቅዱስ የፍቅር እና የሰላም መጽሐፍ ነው ለምትሉ ሁሉ ከፍትሕ ጋር በተያያዘ አራት ጥያቄዎችን እንጠይቃለን፦
ቁጥር አንድ
መጽሐፍ ቅዱስ የሰላምና የፍቅር መጽሐፍ ከሆነ እንዴት ሰውን ግደሉ ይላል?
ሕዝ 9፥6፤ “”ሽማግሌውንና ጐበዙን ቈንጆይቱንም ሕፃናቶቹንና ሴቶቹን”” ፈጽማችሁ “”ግደሉ””፤ ነገር ግን ምልክቱ ወዳለበት ሰው ሁሉ አትቅረቡ፤ በመቅደሴም ጀምሩ አላቸው። በቤቱም አንጻር ባሉ ሽማግሌዎች ጀመሩ።
መሳ 21:10 ማኅበሩም ወደዚያ አሥራ ሁለት ሺህ ኃያላን ሰዎች ሰድደው። ሂዱ በኢያቢስ ገለዓድም ያሉትን ሰዎች “”ከሴቶችና ከሕፃናት”” ጋር በሰይፍ ስለት “ግደሉ””።
1ሳሙ 15:3፤ አሁንም ሄደህ አማሌቅን ምታ፥ ያላቸውንም ሁሉ ፈጽመህ አጥፋ፥ አትማራቸውም፤ “”ወንዱንና ሴቱን ብላቴናውንና ሕፃኑን በሬውንና በጉን ግመሉንና አህያውን ግደል””።
ዘዳ 20:14 ነገር ግን “”ሴቶቹንና ሕፃናትን እንስሶቹንም”” በከተማይቱም ያለውን ምርኮ ሁሉ በዝብዘህ ለአንተ ትወስዳለህ፤ አምላክህም እግዚአብሔር የሚሰጥህን የጠላቶችህን ምርኮ ትበላለህ።
ዘዳ.3:6፤ በሐሴቦንም ንጉሥ በሴዎን እንዳደረግን ፈጽሞ አጠፋናቸው፤ ከተሞቹን ሁሉ “”ከወንዶችና ከሴቶች ከሕፃናቶችም ጋር አጠፋናቸው””።
ኢያ 6:21፤ በከተማይቱም የነበሩትን ሁሉ፥ “”ወንዱንና ሴቱን፥ ሕፃኑንና ሽማግሌውን፥ በሬውንም በጉንም አህያውንም፥ በሰይፍ ስለት ፈጽመው አጠፉ””።
እንደ ምዕራባውያን ሚዛን ሰው የፈለገውን ማምለክ መብቱና ነፃነቱ አይደለምን? ከዚያ አልፎ አረጋውያንን፣ ሴቶችን፣ ሕፃናትንና እንስሳቱን መግደል ለምን አስፈለገ? እስቲ ይነበብ ይህን የፍቅርና የሰላም መጽሐፍ።
ቁጥር ሁለት
መጽሐፍ ቅዱስ የሰላምና የፍቅር መጽሐፍ ከሆነ እንዴት ሰውን እረዱ ይላል?
ዘጸ 32:27 የእናንተም ሰው ሁሉ ወንድሙን ወዳጁንም ጎረቤቱንም “ይረድ” וְהִרְג֧וּ አላቸው።
1ነገ 18:40 ኤልያስም ከበኣል ነቢያት አንድ ሰው እንዳያመልጥ ያዙ አላቸው። ያዙአቸውም፤ ኤልያስም ወደ ቂሶን ወንዝ ወስዶ በዚያ “”አሳረዳቸው”” וַיִּשְׁחָטֵ֖ם።
2ነገ 10:11 ኢዩም ከአክዓብ ቤት የቀረውን ሁሉ፥ ታላላቆቹንም ሁሉ፥ ወዳጆቹንና ካህናቱን ማንም ሳይቀር በኢይዝራኤል “አረዳቸው” וַיִּשְׁחָטֵ֖ם ።
2ነገ 10:14፤ እርሱም። በሕይወታቸው ያዙአቸው አለ። ያዙአቸውም፥ በበግ ጠባቂዎችም ቤት አጠገብ ባለው ጕድጓድ አርባ ሁለቱን ሰዎች “አረዷቸው” וַיִּשְׁחָטֵ֖ם ፤ ማንንም አላስቀረም።
1ሳሙ 17:51፤ ዳዊትም ሮጦ በፍልስጥኤማዊው ላይ ቆመ፤ ሰይፉንም ይዞ ከሰገባው መዘዘው፥ ገደለውም፥ ራሱንም “አረደው” וַיְמֹ֣תְתֵ֔הוּ ።
ይህ ምንድን ነው? ቄራ ወይስ የፍቅርና የሰላም መጽሐፍ?
ቁጥር ሶስት
መጽሐፍ ቅዱስ የሰላምና የፍቅር መጽሐፍ ከሆነ እንዴት ሰውን በእሳት አቃጥሉ ይላል?
ዘሌ 20:14 ማናቸውም ሰው እናቲቱንና ልጂቱን ቢያገባ ርኵሰት ነው፤ በመካከላችሁ ኃጢአት እንዳይሆን እርሱና እነርሱ “”በእሳት ይቃጠሉ””።
ዘሌ 21:9 የካህንም ልጅ ራስዋን በግልሙትና ብታረክስ አባትዋን ታረክሰዋለች፤ “”በእሳት ትቃጠል””።
ኢያ 7:15 እርም የሆነውም ነገር የተገኘበት ሰው የእግዚአብሔርን ቃል ኪዳን አፍርሶአልና፥ በእስራኤልም ዘንድ በደል አድርጎአልና እርሱና ያለው ሁሉ “”በእሳት ይቃጠላሉ””።
ዘዳ 7:5 ነገር ግን እንዲህ አድርጉባቸው፤ መሠዊያቸውን አፍርሱ፥ ሐውልቶቻቸውንም ሰባብሩ፥ የማምለኪያ ዐፀዶቻቸውንም ቍረጡ፥ የተቀረጸውን ምስላቸውንም “”በእሳት አቃጥሉ””።
ዘዳ 7:25 የተቀረጸውንም የአምላኮቻቸውን ምስል “”በእሳት ታቃጥላለህ””፤ የተሠራባቸውን ብርና ወርቅ አትመኝ፤ በአምላክህም በእግዚአብሔር ዘንድ ርኩስ ነውና እንዳትጠመድበት ከእርሱ ምንም አትውሰድ።
ዘዳ 12:3 መሠዊያቸውንም አፍርሱ፥ ሐውልቶቻቸውንም ሰባብሩ፥ የማምለኪያ ዐፀዶቻቸውንም “”በእሳት አቃጥሉ””፥ የአማልክቶቻቸውንም የተቀረጹ ምስሎች አንከታክቱ፤ ከዚያም ስፍራ ስማቸውን አጥፉ።
ኢያ 8:8 በያዛችኋትም ጊዜ ከተማይቱን “”በእሳት አቃጥሉአት””፤ እንደ እግዚአብሔር ቃል አድርጉ፤ እነሆ፥ አዝዣችኋለሁ።
ሰው የሚያመልክበትን የማምለኪያ አፀድ እና የሚኖርበትን ከተማ ማቃጠል ፍቅር ነውን?
ቁጥር አራት
መጽሐፍ ቅዱስ የሰላምና የፍቅር መጽሐፍ ከሆነ እንዴት ሰው ባልሠራው በደል አባቶቻቸው በሠሩት በደል ይገደሉ ይላል?
ይህም ትልቅ በደል ነው፦
በደል አንድ
አካን ሰርቆ ባጠፋው ወንዶችና ሴቶች ልጆቹንም፥ በሬዎቹንም፥ አህያዎቹንም፥ በጎቹንም ለምን መቃጠልና መወገር አስፈለገ?
ኢያሱ 7፥24-25 ኢያሱና እስራኤል ሁሉ የዛራን ልጅ አካንን፥ ብሩንም፥ ካባውንም፥ ወርቁንም፥ #ወንዶችና ሴቶች ልጆቹንም፥ በሬዎቹንም፥ አህያዎቹንም፥ በጎቹንም#፥ ድንኳኑንም፥ ያለውንም ሁሉ ወስደው ወደ አኮር ሸለቆ አመጡአቸው። ኢያሱም። ለምን አስጨነቅኸን? እግዚአብሔር ዛሬ ያስጨንቅሃል አለው እስራኤልም ሁሉ በድንጋይ ወገሩት# በእሳትም አቃጠሉአቸው#፥ #በድንጋይም ወገሩአቸው#።
በደል ሁለት
በሙሴ ዘመን አማሌቃውያን ከእስራኤል በመዋጋት ተዋጉ፦
ዘጸአት 17፥8 አማሌቅም መጥቶ ከእስራኤል ጋር በራፊድም ተዋጋ።
በሙሴ ዘመን አማሌቃውያን ከእስራኤል በመዋጋት በበደሉት ከ 400 ዓመት በኃላ የልጅ ልጆቻቸውን በሬውንና በጉን ግመሉንና አህያውን በማስገደል ተበቀለ፤ ይህ ምን የሚሉት በደል ነው?
1ኛ ሳሙኤል 15፥2-3 የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ “”እስራኤል ከግብጽ በወጣ ጊዜ”” አማሌቅ በመንገድ እየተቃወመ ያደረገበትን #እበቀላለሁ#። አሁንም ሄደህ አማሌቅን ምታ፥ ያላቸውንም ሁሉ ፈጽመህ አጥፋ፥ አትማራቸውም #ወንዱንና ሴቱን ብላቴናውንና ሕፃኑን በሬውንና በጉን ግመሉንና አህያውን ግደል#።
አባቶች ስለ ልጆች አይገደሉ፥ ልጆችም ስለ አባቶች አይገደሉ ነገር ግን ሁሉ እያንዳንዱ በኃጢአቱ ይገደል የሚለው ትዕዛዛት የት ገባና ነው ምንም የማያቁትን ህፃናት ከ 400 ዓመት በኃላ የተፈጁት?
ዘዳግም 24፥16 አባቶች ስለ ልጆች አይገደሉ፥ ልጆችም ስለ አባቶች አይገደሉ ነገር ግን ሁሉ እያንዳንዱ በኃጢአቱ ይገደል።
2ኛ ነገሥት 14፥6 በሙሴ ሕግ መጽሐፍም እንደ ተጻፈ፥ እግዚአብሔርም፦ ሁሉ በኃጢአቱ ይሙት እንጂ አባቶች በልጆች አይሙቱ፥ ልጆችም በአባቶች አይሙቱ ብሎ እንዳዘዘ የነፍሰ ገዳዮቹን ልጆች “አልገደለም””።
ይህንን የሰው ደም ያለበት መጽሐፍ ነው እንግዲህ የፍቅር እና የሰላም መጽሐፍ እየተባለ የሚሰበክለት? ፍርዱ ለኅሊና።