♥አባ ባይሞን /ዼሜን/ ♥
ይህ ቅዱስ አባት የ4ኛው መቶ ክ/ዘ የቤተ ክርስቲያን ፍሬ
ሲሆን ተሰምተው በማይጠገቡ መንፈሳዊ ቃላቱ (ምክሮቹ)ና
በቅድስና ሕይወቱ ይታወቃል:: ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው
ቢሉ:-
በተጠቀሰው ዘመን በምድረ ግብጽ የምትኖር አንዲት ደግ
ሴት ነበረች:: አምላክ በፈቀደው ጋብቻ ውስጥ ገብታ 7
ወንዶች ልጆችን አፈራች:: እነዚህ 7ቱ የቁጥር ጭማሪ:
የጾታም ቅያሪ የላቸውም:: 7ቱም ወንድማማቾች ገና ሕጻን
እያሉ አባት በመሞቱ እናት ፈተና ውስጥ ገባች::
ነገር ግን ብርቱ ሴት ነበረችና በወዟ ደክማ አሳደገቻቸው::
ሥጋዊ ማሳደጉስ ብዙም አይደንቅም:: ምክንያቱም ሁሉም
እናቶች ይህንን ያደርጉታል ተብሎ ይታመናልና:: የዚህች
እናት የሚገርመው ግን ሁሉንም ንጹሐን: የተባረኩ:
የክርስቶስ ወዳጆች: የቤተ ክርስቲያንም አለኝታዎች እንዲሆኑ
አድርጋ ማሳደጉዋ ነው::
እነዚህ 7 ወንድማማቾች:-
1.አብርሃም
2.ያዕቆብ
3.ዮሴፍ
4.ኢዮብ
5.ዮሐንስ
6.ላስልዮስ እና
7.ባይሞን ( #ዼሜን ) ይባላሉ:: ለእነዚህም ዮሐንስ በኩር
ሲሆን ባይሞን መቁረጫ ነው::
+7ቱም ወጣት በሆኑ ጊዜ ወገባቸውን ታጥቀው እናታቸውን
ያገለግሉ: ለፈጣሪያቸው ይገዙ ያዙ:: ያየ ሁሉ "ከዐይን
ያውጣችሁ" የሚላቸው: ቡሩካንም ሆኑ:: አንድ ቀን ግን
#መንፈስ_ቅዱስ በ7ቱ ልብ ውስጥ አንድ ቅን ሃሳብን
አመጣ:: ሁሉም እንደ አንድ ልብ መካሪ: እንደ አንድ ቃል
ተናጋሪ ስለ ምናኔ አወሱ::
ይህንን ዓለም ከነ ኮተቱ ይተውት ዘንድ መርጠዋልና ወደ
በርሃ ለመሔድ ተስማሙ:: እናታቸው ምን መንፈሳዊ ብትሆን
የትኛዋም እናት ሁሉን ልጆቿን በአንዴ ማጣትን
አትፈልግምና አላማከሯትም:: ይልቁኑ እነርሱ ከሔዱ በሁዋላ
እንዳትቸገር የምትታገዝበትን መንገድ አዘጋጅተውላት
ተሰወሩ::
7 ልጆቿን በአንዴ ያጣችው እናት ብቻ አይደለችም: ሁሉም
አዘነ:: ተፈለጉ: ግን አየሁዋቸው የሚል ሰው አልተገኘም::
7ቱም # ቅዱሳን ከቤታቸው እንደ ወጡ ወደ ገዳም ሔደው
አንዲት በዓት ተቀበሉ:: 7ቱም የሚጸልዩ በጋራ: የሚሠሩ:
የሚመገቡ: የሚውሉ: የሚተኙም በጋራ ነው::
በአገልግሎታቸውም ሆነ በፍቅራቸው አበውን ደስ አሰኙ::
"እምኩሉ የዓቢ ተፋቅሮ - እርስ በርስ መዋደድ ከሁሉ
ይበልጣል" እንዲሉ አበው:: ከዘመናት ተጋድሎ በሁዋላ ግን
ዝናቸው ከገዳሙ አልፎ በከተሞች ተሰማ:: ይህንን
የሰማችው እናታቸው የእርሷ ልጆች መሆናቸውን በማወቁዋ
ፈጥና ወደ ገዳሙ ገሰገሰች::
"ልያችሁ ልጆቼ?" ስትልም ላከችባቸው:: እነሱ ግን
"እናታችን በመንግስተ ሰማያት እንድታይን በዚህ ይቅርብሽ"
አሏት:: ምክንያቱም 7ቱም የሴትን ፊት ላያዩ ቃል ገብተው
ነበርና:: ይህ ለአንድ እናት ከባድ ቢሆንም እርሷ ግን
ተረዳቻቸው:: ፈጥናም ወደ ቤቷ ተመለሰች::
ከኮከብ ኮከብ ይበልጣልና (1ቆረ. 15:41) ከ7ቱ ቅዱሳን
ደግሞ ትንሹ #አባ_ባይሞን የተለየ አባት ሆነ:: ከንጽሕናው:
ቅድስናና ትጋቱ ባሻገር ከአንደበቱ የሚወጡ ቃላት ሕይወትነት
ያላቸው ሆኑ:: በዘመኑም ከሕጻን እስከ አዋቂ ድረስ ብዙዎች
ከመንፈሳዊ ቃላቱ ተጠቅመዋል::
+እነዚህ ምክሮቹ ዛሬ ድረስ ለምዕመናንም ሆነ ለመነኮሳት
ጣፋጮች ናቸው:: እልፍ አእላፍ ከሆኑ ምክሮቹ እስኪ አንድ
አምስቱን እንጥቀስ:-
1."ባልንጀራህ በወደቀ ጊዜ በፍጹም ተስፋ አትቁረጥበት::
ይልቅስ አንቃው: አበረታታው: ሸክሙንም አቅልለት እንጂ"
2."ለጥሩ ባልጀራህ የምታደርገውን ደግነት ለክፉው በእጥፍ
አድርግለት::
መድኃኒትን የሚሻ የታመመ ነውና:: አልያ ግን ለበጐው
ያደረከው ከንቱ ነው"
3."ባልጀራህ በበደለ ጊዜ አትናቀው:: ያንተ ተራ በደረሰ ጊዜ
ጌታህ ይንቅሃልና"
4."የማንንም ኃጢአት አትግለጥ (አታውራ):: ካላረፍክ ጌታ
ያንተኑ ይገልጥብሃልና"
5."አንደበትህ የተናገረውን ሁሉ ለመሥራት ታገል:: አልያ
ውሸታም ትሆናለህ"
7ቱ ቅዱሳን ወንድማማቾች ለብዙ ዓመታት በፍቅርና
በተጋድሎ ኑረው በዚህች ቀን ዐርፈዋል::
ይህ ቅዱስ አባት የ4ኛው መቶ ክ/ዘ የቤተ ክርስቲያን ፍሬ
ሲሆን ተሰምተው በማይጠገቡ መንፈሳዊ ቃላቱ (ምክሮቹ)ና
በቅድስና ሕይወቱ ይታወቃል:: ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው
ቢሉ:-
በተጠቀሰው ዘመን በምድረ ግብጽ የምትኖር አንዲት ደግ
ሴት ነበረች:: አምላክ በፈቀደው ጋብቻ ውስጥ ገብታ 7
ወንዶች ልጆችን አፈራች:: እነዚህ 7ቱ የቁጥር ጭማሪ:
የጾታም ቅያሪ የላቸውም:: 7ቱም ወንድማማቾች ገና ሕጻን
እያሉ አባት በመሞቱ እናት ፈተና ውስጥ ገባች::
ነገር ግን ብርቱ ሴት ነበረችና በወዟ ደክማ አሳደገቻቸው::
ሥጋዊ ማሳደጉስ ብዙም አይደንቅም:: ምክንያቱም ሁሉም
እናቶች ይህንን ያደርጉታል ተብሎ ይታመናልና:: የዚህች
እናት የሚገርመው ግን ሁሉንም ንጹሐን: የተባረኩ:
የክርስቶስ ወዳጆች: የቤተ ክርስቲያንም አለኝታዎች እንዲሆኑ
አድርጋ ማሳደጉዋ ነው::
እነዚህ 7 ወንድማማቾች:-
1.አብርሃም
2.ያዕቆብ
3.ዮሴፍ
4.ኢዮብ
5.ዮሐንስ
6.ላስልዮስ እና
7.ባይሞን ( #ዼሜን ) ይባላሉ:: ለእነዚህም ዮሐንስ በኩር
ሲሆን ባይሞን መቁረጫ ነው::
+7ቱም ወጣት በሆኑ ጊዜ ወገባቸውን ታጥቀው እናታቸውን
ያገለግሉ: ለፈጣሪያቸው ይገዙ ያዙ:: ያየ ሁሉ "ከዐይን
ያውጣችሁ" የሚላቸው: ቡሩካንም ሆኑ:: አንድ ቀን ግን
#መንፈስ_ቅዱስ በ7ቱ ልብ ውስጥ አንድ ቅን ሃሳብን
አመጣ:: ሁሉም እንደ አንድ ልብ መካሪ: እንደ አንድ ቃል
ተናጋሪ ስለ ምናኔ አወሱ::
ይህንን ዓለም ከነ ኮተቱ ይተውት ዘንድ መርጠዋልና ወደ
በርሃ ለመሔድ ተስማሙ:: እናታቸው ምን መንፈሳዊ ብትሆን
የትኛዋም እናት ሁሉን ልጆቿን በአንዴ ማጣትን
አትፈልግምና አላማከሯትም:: ይልቁኑ እነርሱ ከሔዱ በሁዋላ
እንዳትቸገር የምትታገዝበትን መንገድ አዘጋጅተውላት
ተሰወሩ::
7 ልጆቿን በአንዴ ያጣችው እናት ብቻ አይደለችም: ሁሉም
አዘነ:: ተፈለጉ: ግን አየሁዋቸው የሚል ሰው አልተገኘም::
7ቱም # ቅዱሳን ከቤታቸው እንደ ወጡ ወደ ገዳም ሔደው
አንዲት በዓት ተቀበሉ:: 7ቱም የሚጸልዩ በጋራ: የሚሠሩ:
የሚመገቡ: የሚውሉ: የሚተኙም በጋራ ነው::
በአገልግሎታቸውም ሆነ በፍቅራቸው አበውን ደስ አሰኙ::
"እምኩሉ የዓቢ ተፋቅሮ - እርስ በርስ መዋደድ ከሁሉ
ይበልጣል" እንዲሉ አበው:: ከዘመናት ተጋድሎ በሁዋላ ግን
ዝናቸው ከገዳሙ አልፎ በከተሞች ተሰማ:: ይህንን
የሰማችው እናታቸው የእርሷ ልጆች መሆናቸውን በማወቁዋ
ፈጥና ወደ ገዳሙ ገሰገሰች::
"ልያችሁ ልጆቼ?" ስትልም ላከችባቸው:: እነሱ ግን
"እናታችን በመንግስተ ሰማያት እንድታይን በዚህ ይቅርብሽ"
አሏት:: ምክንያቱም 7ቱም የሴትን ፊት ላያዩ ቃል ገብተው
ነበርና:: ይህ ለአንድ እናት ከባድ ቢሆንም እርሷ ግን
ተረዳቻቸው:: ፈጥናም ወደ ቤቷ ተመለሰች::
ከኮከብ ኮከብ ይበልጣልና (1ቆረ. 15:41) ከ7ቱ ቅዱሳን
ደግሞ ትንሹ #አባ_ባይሞን የተለየ አባት ሆነ:: ከንጽሕናው:
ቅድስናና ትጋቱ ባሻገር ከአንደበቱ የሚወጡ ቃላት ሕይወትነት
ያላቸው ሆኑ:: በዘመኑም ከሕጻን እስከ አዋቂ ድረስ ብዙዎች
ከመንፈሳዊ ቃላቱ ተጠቅመዋል::
+እነዚህ ምክሮቹ ዛሬ ድረስ ለምዕመናንም ሆነ ለመነኮሳት
ጣፋጮች ናቸው:: እልፍ አእላፍ ከሆኑ ምክሮቹ እስኪ አንድ
አምስቱን እንጥቀስ:-
1."ባልንጀራህ በወደቀ ጊዜ በፍጹም ተስፋ አትቁረጥበት::
ይልቅስ አንቃው: አበረታታው: ሸክሙንም አቅልለት እንጂ"
2."ለጥሩ ባልጀራህ የምታደርገውን ደግነት ለክፉው በእጥፍ
አድርግለት::
መድኃኒትን የሚሻ የታመመ ነውና:: አልያ ግን ለበጐው
ያደረከው ከንቱ ነው"
3."ባልጀራህ በበደለ ጊዜ አትናቀው:: ያንተ ተራ በደረሰ ጊዜ
ጌታህ ይንቅሃልና"
4."የማንንም ኃጢአት አትግለጥ (አታውራ):: ካላረፍክ ጌታ
ያንተኑ ይገልጥብሃልና"
5."አንደበትህ የተናገረውን ሁሉ ለመሥራት ታገል:: አልያ
ውሸታም ትሆናለህ"
7ቱ ቅዱሳን ወንድማማቾች ለብዙ ዓመታት በፍቅርና
በተጋድሎ ኑረው በዚህች ቀን ዐርፈዋል::