#ባሌን_እጠብቃለሁ
አንድ ሰው ሌላ አገር ሄዶ ገንዘብ ለማግኘትና ለመነገድ ያስባል። ሚስቱን ማማከር ስለነበረበት ከእርሷ ጋር በጠረጴዛ ዙርያ ተቀመጡ።
"ሚስቴ ሆይ አንድ ሐሳብ ላማክርሽ ወደድኩ። ሌላ አገር ሄጄ ወጥቼ ወርጄ ትርፍንም አግኝቼ ይዤ ለመመለስ አስቤያለሁ።" ብሎ ሐሳቡን አቀረበላት። ከተወሰነ ውይይት በኋላም
"አሁን የሚያስፈልግሽ ሁሉ እተውልሻለሁ፤ ስንት ዓመት እንደምቆይ ስለማላውቅ አብዝቼ እሰጥሻለሁ።" አላት ። በመንፈስ የበረታ አልነበረምና እያመነታ እንዲህ ሲል ሃሳቡን ቀጠለ "አንድ በጣም ሊያስቸግርሽ የሚችል ነገር ቢኖር የሥጋዊ ፍላጎት ሐሳብና ፈተና ነው። እሱንም ላንቺ ትቼዋለሁ ። በራስሽ ጥበብና ዘዴ ተወጪው አላት ። "
በዚህ ተስማምተው እንባ ተራጭተው ተሰነባበቱ።
#ባል_ሳይመለስ_ብዙ_ዘመናት_አለፉ ። ሚስት ወደፊት የሚሆነው አይታወቅም ብላ ትንሽ ገቢ የሚያስገኝላት ቀለል ያለ ሥራ መስራት ጀመረች ። ጊዜ እየገፋ ሲሄድ የሥጋ ነገር ስራው መስራት ጀመረ ። ብዙ ጊዜ ብትታገስም እያዳከማት መጣ ። እንዲህ ዓይነት ፈተና እንዴት እንደምታሸንፍ ምክር ስላልተሰጣት፣ በዚያ ላይም ሐሳቡ ለእርስዋ ብቻ መተዉ እንደ ሙሉ ነፃነት ቆጥራው አእምሮዋ እየተዳከመ፣ እየተሸነፈች መጣች ።
ታድያ የምትሰራበት ቦታ ውስጥ አንድ ሰው ዓይኗ ውስጥ ገባ ። እሱ ባለበት ሁሉ ትሄዳለች። እሱ ባለበት ኅብረት
ውስጥ ትገኛለች፤ ባጠቃላይ እሱ በሚገኝበት ቦታ የምታደርጋቸው ትዕይንቶች ሁሉ እሱን ወደ ወጥመዷ ለማስገባት ያተኮሩ ነበሩ ።
እሱ ባያስበውም። አንድ ቀን መንገድ ላይ ጠብቃ "አንድ የማዋይህ ነገር ስላለኝ አንድ ቦታ ለብቻችን ተገናኝተን ብናወራ ምን ይመስልሃል? " አለችው።
እሱም እውንታውን ገልፆላት በቀጠሮ ተለያዩ።
በተባለው ቀን፣ ቦታና ሰዓት ተገናኙ።
ከትንሽ ጨዋታ በኋላ ወደ ዋናው ቁምነገር እንግባ ተባብለው እሷ ጀመረች። ታሪኳ ሁሉ ነግራው ስሜቷን ይረዳላትና የፈለገችውን ይፈጽምላት እንደሆነ ጠየቀችው።
ትንሽ እንደማሰብ ብሎ "ችግር የለውም ግን
" አለና አንድ ታሪክ ያጫውታት ጀመር።
"የግቢ (የ university) ተማሪ እያለሁ ከአቅሜ በላይ፣ ልቋቋመው የማልችል ችግር ደርሶብኝ ነበር። ይህ ችግር ሊፈታው የሚችል እግዚአብሔር ብቻ መሆኑ ተረድቼ እንባዬን ወደ እግዚአብሔር አፈሰስኩ። በጸሎቴ ውስጥም 'እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ ከእኔ ከኃጢአተኛው ልጅህ የምትወጣውን ይህች ጸሎት ሰምተህ ችግሬን ብታስወግድልኝ፣ ከዚህ ግቢ ተመርቄ ስወጣ አንድ ዓመት ሙሉ ምሳዬን አንድ ዳቦና አንድ ብርጭቆ ውሃ እራቴንም እንዲሁ እያደረግሁ የቻልኩትን እየጸለይኩና እየሰገድኩ አሳልፈዋለሁ።'
ስል ስዕለት ገባሁ። አሁን የቀረኝ 60 ቀን ነው። ምናልባት ፈቃደኛ ከሆንሽ 30 ውን ቀን እኔ 30 ውን አንቺ ተከፋፍለን ቶሎ ብንጨርሰውና ከዛ በኋላ ብንወስን ምን ይመስልሻል?"
ብሎ ሐሳቡን በጥያቄ አጠቃለለ።
'እንዴት ዓይነት ችግር ቢገጥመው ነው?' ብላ እያሰበች ነበርና አሳዘናት። ነገር ግን ባቀረበላት ሐሳብ ደግሞ ደስ አላት ።
የተባለችው በትክክል ከፈፀመች እሺ የማለቱ ዕድል በጣም ሰፊ ነውና።
በተባለችው መሰረት በአንድ ዳቦና በአንድ ብርጭቆ ውሃ ተጋድሎዋን ቀጠለች።
29 ኛው ቀን ሲትደርስ ሌላ ጭንቀት ውስጥ ገባች። ነገሮች ሁሉ ተቀያይረዋል። ድሮ የነበራት ስሜት አሁን የለም።
የሥጋ ነገር መድኃኒቱ ገብቷታል ። ያስጨነቃትም ይህ ነበር።
ሐሳቧ እንዴት ትቀይር?! እራሷ ጀምራ እራሷ እምቢታዋን እንዴት ትግለፅ? -- ጨነቃት።
በ 30 ኛው ቀን በቀጠሯቸው መሰረት ተገናኙ። ሌላ አማራጭ አልነበራትምና እንደምንም ብላ የሆነውን ሁሉ
ከነገረችው በኋላ "-- #ባሌን_እጠብቃለሁ " ስትል ሥጋ ሲያስቸግር በእንዲህ ዓይነት ተጋድሎ በትዳሯ መጽናት እንደምትፈልግ ነገረችው። መልሱ እንዴት ሊሰቀጥጥ እንደሚችል ቢገባትም ተራራን የሚያክል የስድብ ናዳ ብወርድባትም ለመቀበል ተዘጋጅታለች። እሱም በምስጋና ዓይኖቹን ወደ ሰማይ አንጋጠጠ። በፈገታም ያላት ሁሉ እውነት እንዳልነበረ ነገራት። ለካ እሱስ የፆምን ኃይል ሊያሳያት፣ ሊያስረዳትና በተግባርም ሊያስተምራት ፈልጎ እንጂ እሱም ሐሳቡን ፈልጎት አልነበረም።
"ጾም ትፌውስ ቁስለ ነፍስ፣ ወታጸምም ኩሎ ፍትወታተ ዘሥጋ፣ ወትምሄሮሙ ለወራዙት ፅሞና ፦ ጾም የነፍስን ቁስል ትፈውሳለች፣ የስጋ ፍትወታትም ሁሉ ጸጥ ታደርጋቸዋለች፣ ለወጣቶችም ጽሞናን፣ ትዕግስትን፣ ጸጥታን ታስተምራቸዋለች"
#ወዳጆቼ ከዚ ፅሑፍ ከሥጋዊ ባልና ሚስት ባሻገር ሰፊ ምስጢር እንደምትረዱ ተስፋ አደርጋለሁ ። ምክንያቱ ሚስት ሴት ብቻ አደለችምና ። ምን ለማለት ፈልጎ ነው ? ከሴት ውጪ ሚስት አለችን ?? ! ብላችሁ በአግራሞት ልትጠይቁ ይሆናል ። እኔ ግን አዎ ከሴት ውጪ ማግባት ያለብን ማፍቀር ያለብን ብዙ ሚስቶች አሉ ብዬ እመልሳለሁ ። ለምሳሌ ንፅህና ፣ ጾም ጸሎት ፣ ምጽዋት... ሚስት መሆን ይችላሉ ። እነሱን አግብተን በቅድስናና በንፅህና በመኖር ሰማያዊው ሰርግ ቤት መንግስተ ሰማያት ማግኘት ይቻላል ። ቅዱሳን አባቶቻችን ይህንን በተግባር አሳይተውናልና ።
#ዛሬ_አንድ_በጣም_የገረመኝ_ነገር_አንድ_ወዳጄ " ሁሉም ነገር ( ሙዝቃ ፣ መጠጥ ፣ ጭፈራ ወዘተ ) ማቆም እችላለሁ ። አንድ የከበደኝ ነገር ግን ማመንዘርን እንዴት ላቁም?" ብሎ ጠየቀኝ ። ጥያቄው ለመለወጥ ካለው ከፍተኛ ፍላጎት የተነሳ በመሆኑ በጣም ደስ ብሎኛል ። እና የጠየከኝ ወዳጄ እድሁም ውድ ይህንን ፅሑፍ የተመለከታችሁ ሁሉ ቢከብድም መልሱ ከላይ ያነበባችሁት ታሪክ ነው የሚሆነው ። እና የፍትወት መድኃኒቱ ጾም ጸሎት ነውና ሁላችንም በጾሙ ልንበረታ ያስፈልጋል ።
ጾሙ የፍቅር የደስታ እንድሁም የቁስለ ሥጋ የቁስለ የፍስ መፈወሻ የጽድቅ መውረሻ እንድንሆንልን የአምላካችን ፈቃድ ይሁንልን ።
" ባሌን እጠብቃለሁ !"
አንድ ሰው ሌላ አገር ሄዶ ገንዘብ ለማግኘትና ለመነገድ ያስባል። ሚስቱን ማማከር ስለነበረበት ከእርሷ ጋር በጠረጴዛ ዙርያ ተቀመጡ።
"ሚስቴ ሆይ አንድ ሐሳብ ላማክርሽ ወደድኩ። ሌላ አገር ሄጄ ወጥቼ ወርጄ ትርፍንም አግኝቼ ይዤ ለመመለስ አስቤያለሁ።" ብሎ ሐሳቡን አቀረበላት። ከተወሰነ ውይይት በኋላም
"አሁን የሚያስፈልግሽ ሁሉ እተውልሻለሁ፤ ስንት ዓመት እንደምቆይ ስለማላውቅ አብዝቼ እሰጥሻለሁ።" አላት ። በመንፈስ የበረታ አልነበረምና እያመነታ እንዲህ ሲል ሃሳቡን ቀጠለ "አንድ በጣም ሊያስቸግርሽ የሚችል ነገር ቢኖር የሥጋዊ ፍላጎት ሐሳብና ፈተና ነው። እሱንም ላንቺ ትቼዋለሁ ። በራስሽ ጥበብና ዘዴ ተወጪው አላት ። "
በዚህ ተስማምተው እንባ ተራጭተው ተሰነባበቱ።
#ባል_ሳይመለስ_ብዙ_ዘመናት_አለፉ ። ሚስት ወደፊት የሚሆነው አይታወቅም ብላ ትንሽ ገቢ የሚያስገኝላት ቀለል ያለ ሥራ መስራት ጀመረች ። ጊዜ እየገፋ ሲሄድ የሥጋ ነገር ስራው መስራት ጀመረ ። ብዙ ጊዜ ብትታገስም እያዳከማት መጣ ። እንዲህ ዓይነት ፈተና እንዴት እንደምታሸንፍ ምክር ስላልተሰጣት፣ በዚያ ላይም ሐሳቡ ለእርስዋ ብቻ መተዉ እንደ ሙሉ ነፃነት ቆጥራው አእምሮዋ እየተዳከመ፣ እየተሸነፈች መጣች ።
ታድያ የምትሰራበት ቦታ ውስጥ አንድ ሰው ዓይኗ ውስጥ ገባ ። እሱ ባለበት ሁሉ ትሄዳለች። እሱ ባለበት ኅብረት
ውስጥ ትገኛለች፤ ባጠቃላይ እሱ በሚገኝበት ቦታ የምታደርጋቸው ትዕይንቶች ሁሉ እሱን ወደ ወጥመዷ ለማስገባት ያተኮሩ ነበሩ ።
እሱ ባያስበውም። አንድ ቀን መንገድ ላይ ጠብቃ "አንድ የማዋይህ ነገር ስላለኝ አንድ ቦታ ለብቻችን ተገናኝተን ብናወራ ምን ይመስልሃል? " አለችው።
እሱም እውንታውን ገልፆላት በቀጠሮ ተለያዩ።
በተባለው ቀን፣ ቦታና ሰዓት ተገናኙ።
ከትንሽ ጨዋታ በኋላ ወደ ዋናው ቁምነገር እንግባ ተባብለው እሷ ጀመረች። ታሪኳ ሁሉ ነግራው ስሜቷን ይረዳላትና የፈለገችውን ይፈጽምላት እንደሆነ ጠየቀችው።
ትንሽ እንደማሰብ ብሎ "ችግር የለውም ግን
" አለና አንድ ታሪክ ያጫውታት ጀመር።
"የግቢ (የ university) ተማሪ እያለሁ ከአቅሜ በላይ፣ ልቋቋመው የማልችል ችግር ደርሶብኝ ነበር። ይህ ችግር ሊፈታው የሚችል እግዚአብሔር ብቻ መሆኑ ተረድቼ እንባዬን ወደ እግዚአብሔር አፈሰስኩ። በጸሎቴ ውስጥም 'እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ ከእኔ ከኃጢአተኛው ልጅህ የምትወጣውን ይህች ጸሎት ሰምተህ ችግሬን ብታስወግድልኝ፣ ከዚህ ግቢ ተመርቄ ስወጣ አንድ ዓመት ሙሉ ምሳዬን አንድ ዳቦና አንድ ብርጭቆ ውሃ እራቴንም እንዲሁ እያደረግሁ የቻልኩትን እየጸለይኩና እየሰገድኩ አሳልፈዋለሁ።'
ስል ስዕለት ገባሁ። አሁን የቀረኝ 60 ቀን ነው። ምናልባት ፈቃደኛ ከሆንሽ 30 ውን ቀን እኔ 30 ውን አንቺ ተከፋፍለን ቶሎ ብንጨርሰውና ከዛ በኋላ ብንወስን ምን ይመስልሻል?"
ብሎ ሐሳቡን በጥያቄ አጠቃለለ።
'እንዴት ዓይነት ችግር ቢገጥመው ነው?' ብላ እያሰበች ነበርና አሳዘናት። ነገር ግን ባቀረበላት ሐሳብ ደግሞ ደስ አላት ።
የተባለችው በትክክል ከፈፀመች እሺ የማለቱ ዕድል በጣም ሰፊ ነውና።
በተባለችው መሰረት በአንድ ዳቦና በአንድ ብርጭቆ ውሃ ተጋድሎዋን ቀጠለች።
29 ኛው ቀን ሲትደርስ ሌላ ጭንቀት ውስጥ ገባች። ነገሮች ሁሉ ተቀያይረዋል። ድሮ የነበራት ስሜት አሁን የለም።
የሥጋ ነገር መድኃኒቱ ገብቷታል ። ያስጨነቃትም ይህ ነበር።
ሐሳቧ እንዴት ትቀይር?! እራሷ ጀምራ እራሷ እምቢታዋን እንዴት ትግለፅ? -- ጨነቃት።
በ 30 ኛው ቀን በቀጠሯቸው መሰረት ተገናኙ። ሌላ አማራጭ አልነበራትምና እንደምንም ብላ የሆነውን ሁሉ
ከነገረችው በኋላ "-- #ባሌን_እጠብቃለሁ " ስትል ሥጋ ሲያስቸግር በእንዲህ ዓይነት ተጋድሎ በትዳሯ መጽናት እንደምትፈልግ ነገረችው። መልሱ እንዴት ሊሰቀጥጥ እንደሚችል ቢገባትም ተራራን የሚያክል የስድብ ናዳ ብወርድባትም ለመቀበል ተዘጋጅታለች። እሱም በምስጋና ዓይኖቹን ወደ ሰማይ አንጋጠጠ። በፈገታም ያላት ሁሉ እውነት እንዳልነበረ ነገራት። ለካ እሱስ የፆምን ኃይል ሊያሳያት፣ ሊያስረዳትና በተግባርም ሊያስተምራት ፈልጎ እንጂ እሱም ሐሳቡን ፈልጎት አልነበረም።
"ጾም ትፌውስ ቁስለ ነፍስ፣ ወታጸምም ኩሎ ፍትወታተ ዘሥጋ፣ ወትምሄሮሙ ለወራዙት ፅሞና ፦ ጾም የነፍስን ቁስል ትፈውሳለች፣ የስጋ ፍትወታትም ሁሉ ጸጥ ታደርጋቸዋለች፣ ለወጣቶችም ጽሞናን፣ ትዕግስትን፣ ጸጥታን ታስተምራቸዋለች"
#ወዳጆቼ ከዚ ፅሑፍ ከሥጋዊ ባልና ሚስት ባሻገር ሰፊ ምስጢር እንደምትረዱ ተስፋ አደርጋለሁ ። ምክንያቱ ሚስት ሴት ብቻ አደለችምና ። ምን ለማለት ፈልጎ ነው ? ከሴት ውጪ ሚስት አለችን ?? ! ብላችሁ በአግራሞት ልትጠይቁ ይሆናል ። እኔ ግን አዎ ከሴት ውጪ ማግባት ያለብን ማፍቀር ያለብን ብዙ ሚስቶች አሉ ብዬ እመልሳለሁ ። ለምሳሌ ንፅህና ፣ ጾም ጸሎት ፣ ምጽዋት... ሚስት መሆን ይችላሉ ። እነሱን አግብተን በቅድስናና በንፅህና በመኖር ሰማያዊው ሰርግ ቤት መንግስተ ሰማያት ማግኘት ይቻላል ። ቅዱሳን አባቶቻችን ይህንን በተግባር አሳይተውናልና ።
#ዛሬ_አንድ_በጣም_የገረመኝ_ነገር_አንድ_ወዳጄ " ሁሉም ነገር ( ሙዝቃ ፣ መጠጥ ፣ ጭፈራ ወዘተ ) ማቆም እችላለሁ ። አንድ የከበደኝ ነገር ግን ማመንዘርን እንዴት ላቁም?" ብሎ ጠየቀኝ ። ጥያቄው ለመለወጥ ካለው ከፍተኛ ፍላጎት የተነሳ በመሆኑ በጣም ደስ ብሎኛል ። እና የጠየከኝ ወዳጄ እድሁም ውድ ይህንን ፅሑፍ የተመለከታችሁ ሁሉ ቢከብድም መልሱ ከላይ ያነበባችሁት ታሪክ ነው የሚሆነው ። እና የፍትወት መድኃኒቱ ጾም ጸሎት ነውና ሁላችንም በጾሙ ልንበረታ ያስፈልጋል ።
ጾሙ የፍቅር የደስታ እንድሁም የቁስለ ሥጋ የቁስለ የፍስ መፈወሻ የጽድቅ መውረሻ እንድንሆንልን የአምላካችን ፈቃድ ይሁንልን ።
" ባሌን እጠብቃለሁ !"