ስንክሳር
7.32K subscribers
825 photos
4 videos
37 files
237 links
በስንክሳር channal ስንክሳሩ ተገልጦ ቅዱሳን ይዘከራሉ፣ ወቅቱን የጠበቁ መረጃዎችን ያገኛሉ፡፡ ይከታተሉን!
Download Telegram
#ታላቁ_ቅዱስ_መቃርስ
ታላቁ ቅዱስ መቃርስ ( #መቃሬ ) "ጽድቅ እንደ መቃርስ"
የተባለለት: የመነኮሳት ሁሉ አለቃ: ከ80 ዓመታት በላይ በበርሃ
የኖረ: በግብፅ ትልቁን ገዳም (አስቄጥስን) የመሠረተ:
ከ50,000 በላይ መነኮሳትን ይመራና ይመግብ የነበረ ፍፁም
ጻድቅ ነው::
በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን አርዮሳውያን ደጉን ታላቅ አባት
በሰንሰለት አስረው ከግብፅ ወደ እስያ በርሃ ከጉዋደኛው
#ቅዱስ_መቃርዮስ እስክንድርያዊ ጋር አሰድደውታል:: በዚያ
ለ2 ዓመታት ስቃይን ከተቀበሉ በሁዋላ በአረማውያን ፊት ድንቅ
ተአምር አድርገው አረማውያንን ከነንጉሳቸው አጥምቀዋል::
በተሰደዱባት ሃገርም #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ (ስም
አጠራሩ ይክበርና) #እመቤታችንን : #ቅዱሳን_ሐዋርያትን :
#አዕላፍ_መላእክትን : በተለይ ደግሞ ቅዱሳኑን #ዳዊትን:
#ዮሐንስ መጥምቁንና ወንጌላዊውን: #ማርቆስን:_
ዼጥሮስን:_ዻውሎስን አስከትሎ ወርዶ ተገልጦላቸዋል::
በቅዱስ አንደበቱም የምሕረት ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል::
ታላቁ ቅዱስ መቃርስና መቃርዮስ ከ2 ዓመታት ስደትና መከራ
በሁዋላ ስደት በወጡባት በዚችው ዕለት መልዐኩ ኪሩብ በክንፉ
ተሽክሞ ወደ ግብፅ መልሷቸዋል:: በወቅቱም ጻድቁን ለመቀበል
ከ50,000 በላይ የሚሆኑ ልጆቻቸው መነኮሳት በዝማሬ
ወጥተዋል::
ይህች ዕለት ለአባታችን መቃሬ በዓለ ፍልሠቱ ናት::