+♥#አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ ( # GIYORGIS_OF_SEG
LA ) ♥+
ታላቁ ኢትዮዽያዊ ሊቅና ጻድቅ የተወለደው ወሎ #ጋስጫ
ውስጥ በ1358 ዓ/ም ነው:: ከልጅነቱ ትምሕርት አልገባሕ
ቢለውም በልቡናው ግን ቅን እና ታዛዥ ነበር:: መምሕሩ
"ትምሕርት አይገባውምና ውሰዱት" ቢላቸው
"የእግዚአብሔር ነውና ያገልግላችሁ" ብለው መለሱት::
መገፋቱን የተመለከተ #አባ_ጊዮርጊስ #እመቤታታችንን
ከልቡ ይወዳት ነበረና ይማጸናት ገባ::
ቀን ቀን ገዳሙን ሲረዳ: እሕል ሲፈጭና ሲከካ: ላቡንም
ሲያፈስ ውሎ ሌሊት ደግሞ ሲጸልይ ያነጋ ነበር:: ድንግል
እመቤታችን ጸሎቱን ሰምታለችና #ቅዱስ_ዑራኤልን አስከትላ
መጣችለት:: በንጹሐት እጆቿ ባርካው ምሥጢርንም
ነገረችው:: "ወነገረቶ ሐምስተ ቃላተ" እንዲል:: ጽዋዐ ልቡናን
አጠጥታው ተሠወረችው::
+ከዚህች ሰዓት ጀምሮ አባ ጊዮርጊስ ፍጹም ተለወጠ::
በጽድቁ ላይ የሊቅነትን ካባ ደረበ:: ቅዱሳት መጻሕፍትን
ይተነትናቸው: መናፍቃንንም ምላሽ ያሳጣቸው ገባ::
የተረጐማቸውና ያተታቸውን ሳይጨምር 41 ድርሰቶችን
ደረሰ:: (መጽሐፈ ሰዓታት: መጽሐፈ ምሥጢር: አርጋኖን:
ኆኅተ ብርሃን: ውዳሴ መስቀል: ወዘተ . . . የእርሱ ድርሰቶች
ነበሩ)
✝ስለ ሃይማኖትም ጠበቃ ነበር:: ስለ ቅድስናውና ውለታው
የኢ/ኦ/ተ/ቤ እንዲህ ትጠራዋለች:-
1. #ሊቀ_ሊቃውንት
2.#በላዔ_መጻሕፍት
3.#ዓምደ_ሃይማኖት
4.#ዳግማዊ_ቄርሎስ
5.#ጠቢብ_ወማዕምር
+ጻድቁ ሊቅ በተወለደ በ60 ዓመቱ በ1418 ዓ/ም በዚህች
ቀን ዐርፏል:: አባ ጊዮርጊስ የተወለደውም ያረፈውም ሐምሌ
7 ቀን ነው::
♥የሥላሴ ቸርነት: የአብርሃም ደግነት: የአበው አባ
ጊዮርጊስና አባ ሲኖዳ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን::♥
LA ) ♥+
ታላቁ ኢትዮዽያዊ ሊቅና ጻድቅ የተወለደው ወሎ #ጋስጫ
ውስጥ በ1358 ዓ/ም ነው:: ከልጅነቱ ትምሕርት አልገባሕ
ቢለውም በልቡናው ግን ቅን እና ታዛዥ ነበር:: መምሕሩ
"ትምሕርት አይገባውምና ውሰዱት" ቢላቸው
"የእግዚአብሔር ነውና ያገልግላችሁ" ብለው መለሱት::
መገፋቱን የተመለከተ #አባ_ጊዮርጊስ #እመቤታታችንን
ከልቡ ይወዳት ነበረና ይማጸናት ገባ::
ቀን ቀን ገዳሙን ሲረዳ: እሕል ሲፈጭና ሲከካ: ላቡንም
ሲያፈስ ውሎ ሌሊት ደግሞ ሲጸልይ ያነጋ ነበር:: ድንግል
እመቤታችን ጸሎቱን ሰምታለችና #ቅዱስ_ዑራኤልን አስከትላ
መጣችለት:: በንጹሐት እጆቿ ባርካው ምሥጢርንም
ነገረችው:: "ወነገረቶ ሐምስተ ቃላተ" እንዲል:: ጽዋዐ ልቡናን
አጠጥታው ተሠወረችው::
+ከዚህች ሰዓት ጀምሮ አባ ጊዮርጊስ ፍጹም ተለወጠ::
በጽድቁ ላይ የሊቅነትን ካባ ደረበ:: ቅዱሳት መጻሕፍትን
ይተነትናቸው: መናፍቃንንም ምላሽ ያሳጣቸው ገባ::
የተረጐማቸውና ያተታቸውን ሳይጨምር 41 ድርሰቶችን
ደረሰ:: (መጽሐፈ ሰዓታት: መጽሐፈ ምሥጢር: አርጋኖን:
ኆኅተ ብርሃን: ውዳሴ መስቀል: ወዘተ . . . የእርሱ ድርሰቶች
ነበሩ)
✝ስለ ሃይማኖትም ጠበቃ ነበር:: ስለ ቅድስናውና ውለታው
የኢ/ኦ/ተ/ቤ እንዲህ ትጠራዋለች:-
1. #ሊቀ_ሊቃውንት
2.#በላዔ_መጻሕፍት
3.#ዓምደ_ሃይማኖት
4.#ዳግማዊ_ቄርሎስ
5.#ጠቢብ_ወማዕምር
+ጻድቁ ሊቅ በተወለደ በ60 ዓመቱ በ1418 ዓ/ም በዚህች
ቀን ዐርፏል:: አባ ጊዮርጊስ የተወለደውም ያረፈውም ሐምሌ
7 ቀን ነው::
♥የሥላሴ ቸርነት: የአብርሃም ደግነት: የአበው አባ
ጊዮርጊስና አባ ሲኖዳ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን::♥
❤ ❤ እንኳን ለቅዱስ ሊቀ ሊቃውንት ማኅሌታይ አምሳለ ሱራፌል ያሬድ ካህን ለተሰወረበት ልዩ ክብረ በዓል አደረሳችሁ። ❤ ❤
#መዘምር_ዘበድርሣን
#ጥዑመ_ልሳን
#ካህነ_ስብሐት
#ማኅሌታይ
#ሊቀ_ሊቃውንት
#አምሳለ_ሱራፌል የኢትዮጵያ ዕንቊ የቤተ ክርቲያን እንዚራ ምድራዊው መልአክ ቅዱስ ያሬድ ሊቅ ማኅሌታይ በረከቱ በእጅጉ በዝታ ትደርብን።
❤❤ያሬድ ማኅሌታይ ለእግዚአብሔር ካህኑ
ስብሐተ ትንሣኤ ዘይዜኑ
ኦሪት ቶታኑ ወወንጌል አሣዕኑ
ትርድአነ ነዓ በህየ መካኑ
ከመ ጸበል ግሁሣን ፀርነ ይኩኑ። ❤❤
#መዘምር_ዘበድርሣን
#ጥዑመ_ልሳን
#ካህነ_ስብሐት
#ማኅሌታይ
#ሊቀ_ሊቃውንት
#አምሳለ_ሱራፌል የኢትዮጵያ ዕንቊ የቤተ ክርቲያን እንዚራ ምድራዊው መልአክ ቅዱስ ያሬድ ሊቅ ማኅሌታይ በረከቱ በእጅጉ በዝታ ትደርብን።
❤❤ያሬድ ማኅሌታይ ለእግዚአብሔር ካህኑ
ስብሐተ ትንሣኤ ዘይዜኑ
ኦሪት ቶታኑ ወወንጌል አሣዕኑ
ትርድአነ ነዓ በህየ መካኑ
ከመ ጸበል ግሁሣን ፀርነ ይኩኑ። ❤❤