♥ #ቅዱስ_ሩፋኤል_ሊቀ _መላዕክት ♥
#ሢመት
ቅዱስ ሩፋኤል በቤተ ክርስቲያን አስተምሕሮ ከ7ቱ ሊቃነ
መላእክት በደረጃው 3ኛ ነው:: በመጀመሪያዋ ዕለተ ፍጥረት
እግዚአብሔር መቶ ነገደ መላእክትን ፈጥሮ በ10 ከተማ
ሲያኖራቸው የቅዱስ ሩፋኤል ዕድል ፈንታው ራማ ሆነች::
በዚያም "መናብርት" ተብለው ለሚጠሩ 10ሩ ነገድ አለቃ
(መሪ) ሆኖ በፈጣሪው ተሹሟል::
በሁዋላም "#መጋብያን " በሚባሉ በ23ቱ ነገድ ላይ
ሹሞታል:: ይህች ዕለትም በዓለ ሲመቱ ናት::
#ቅዱስ_ሩፋኤልና_ሐዋርያት
አንድ ቀን #ጌታችን_ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ
ሐዋርያቱ ቅዱስ ሩፋኤልን እንዲያስተዋውቃቸው ለመኑት::
ጌታም 3ቱን ሊቃናት ( #ሚካኤል: #ገብርኤል እና #ሩፋኤል
) ይመጡ ዘንድ አዘዛቸው::
ቀጥሎም ቅዱስ ሩፋኤልን "ክብርህን ንገራቸው" አለው::
እርሱም ለጌታ ሰግዶ ለሐዋርያት ብዙ ምሥጢር ነገራቸው::
በተለይ ስሙን ለሚጠሩ: መታሰቢያውን ለሚያከብሩ
የሚደረገውን ጸጋ አብራርቶላቸው ዐረገ::
#ረዳትነት
በመጽሐፈ #ጦቢት ላይ ተጽፎ እንደምናገኘው ቅዱሱ
መልአክ ሰው (አዛርያን) መስሎ: ጦብያን ለትዳር አብቅቶ:
ሣራን አስማንድዮስ ከሚባል ሰይጣን አድኖ: የጦቢትን ዐይን
አብርቷል:: በገድላተ ቅዱሳን እንደምናየውም ለብዙ ቅዱሳን
ረዳታቸው ሆኖ ገድላቸውን አስፈጽሟል::
#ቅዳሴ ቤት
ታሪክ እንደሚለው ይህች ቀን ለቅዱስ ሩፋኤል ቅዳሴ
ቤቱም ናት:: በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን በቅዱስ #ቴዎፍሎስ
ዘእስክንድርያ አማካኝነት ቤቱ ታንጿል:: የሚገርመው ደግሞ
የታነጸው በአሣ አንበሪ ጀርባ: ደሴት ላይ ነው:: በመልአኩ
አጋዥነትም ለ300 ዓመታት አገልግሏል::
#ቅዱስ_ሩፋኤል
¤መስተፍስሒ (ልቡናን ደስ የሚያሰኝ)
¤አቃቤ ሥራይ (ባለ መድኃኒት ፈዋሽ)
¤መዝገበ ጸሎት (የጸሎት መዝገብ መክፈቻ የተሰጠው)
¤ሊቀ መናብርት (በዙፋን ላይ በክብር የሚቀመጡ መላእክት
መሪ)
¤ፈታሔ ማሕጸን (የሰውንም ሆነ የእንስሳትን ማሕጸን
የሚፈታ)
¤መወልድ (አዋላጅ: ምጥን የሚያቀል) ይባላል::
"ለሰብእ ወለእንስሳ ፈታሔ ማሕጸኖሙ አንተ" እንዲል::
#ሢመት
ቅዱስ ሩፋኤል በቤተ ክርስቲያን አስተምሕሮ ከ7ቱ ሊቃነ
መላእክት በደረጃው 3ኛ ነው:: በመጀመሪያዋ ዕለተ ፍጥረት
እግዚአብሔር መቶ ነገደ መላእክትን ፈጥሮ በ10 ከተማ
ሲያኖራቸው የቅዱስ ሩፋኤል ዕድል ፈንታው ራማ ሆነች::
በዚያም "መናብርት" ተብለው ለሚጠሩ 10ሩ ነገድ አለቃ
(መሪ) ሆኖ በፈጣሪው ተሹሟል::
በሁዋላም "#መጋብያን " በሚባሉ በ23ቱ ነገድ ላይ
ሹሞታል:: ይህች ዕለትም በዓለ ሲመቱ ናት::
#ቅዱስ_ሩፋኤልና_ሐዋርያት
አንድ ቀን #ጌታችን_ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ
ሐዋርያቱ ቅዱስ ሩፋኤልን እንዲያስተዋውቃቸው ለመኑት::
ጌታም 3ቱን ሊቃናት ( #ሚካኤል: #ገብርኤል እና #ሩፋኤል
) ይመጡ ዘንድ አዘዛቸው::
ቀጥሎም ቅዱስ ሩፋኤልን "ክብርህን ንገራቸው" አለው::
እርሱም ለጌታ ሰግዶ ለሐዋርያት ብዙ ምሥጢር ነገራቸው::
በተለይ ስሙን ለሚጠሩ: መታሰቢያውን ለሚያከብሩ
የሚደረገውን ጸጋ አብራርቶላቸው ዐረገ::
#ረዳትነት
በመጽሐፈ #ጦቢት ላይ ተጽፎ እንደምናገኘው ቅዱሱ
መልአክ ሰው (አዛርያን) መስሎ: ጦብያን ለትዳር አብቅቶ:
ሣራን አስማንድዮስ ከሚባል ሰይጣን አድኖ: የጦቢትን ዐይን
አብርቷል:: በገድላተ ቅዱሳን እንደምናየውም ለብዙ ቅዱሳን
ረዳታቸው ሆኖ ገድላቸውን አስፈጽሟል::
#ቅዳሴ ቤት
ታሪክ እንደሚለው ይህች ቀን ለቅዱስ ሩፋኤል ቅዳሴ
ቤቱም ናት:: በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን በቅዱስ #ቴዎፍሎስ
ዘእስክንድርያ አማካኝነት ቤቱ ታንጿል:: የሚገርመው ደግሞ
የታነጸው በአሣ አንበሪ ጀርባ: ደሴት ላይ ነው:: በመልአኩ
አጋዥነትም ለ300 ዓመታት አገልግሏል::
#ቅዱስ_ሩፋኤል
¤መስተፍስሒ (ልቡናን ደስ የሚያሰኝ)
¤አቃቤ ሥራይ (ባለ መድኃኒት ፈዋሽ)
¤መዝገበ ጸሎት (የጸሎት መዝገብ መክፈቻ የተሰጠው)
¤ሊቀ መናብርት (በዙፋን ላይ በክብር የሚቀመጡ መላእክት
መሪ)
¤ፈታሔ ማሕጸን (የሰውንም ሆነ የእንስሳትን ማሕጸን
የሚፈታ)
¤መወልድ (አዋላጅ: ምጥን የሚያቀል) ይባላል::
"ለሰብእ ወለእንስሳ ፈታሔ ማሕጸኖሙ አንተ" እንዲል::