♥#ቅዱስ_ሚካኤል_ሊቀ✞መላእክት ♥
✝ቅዱስ ሚካኤል በጥንተ ተፈጥሮ #በኢዮር : #ኃይላት
በተባሉት ነገደ መላእክት ተሹሞ ነበር:: ሳጥናኤል በካደ ጊዜ
እግዚአብሔር ባወቀ: አንድም በትሕትናውና ደግነቱ በ99ኙ
ነገደ መላእክት ላይ ሁሉ ተሹሟል::
✞ከፍጥረት ወገን #ከእመቤታችን ቀጥሎ የቅዱስ ሚካኤልን
ያሕል ክብርና ርሕሩሕ የለም:: በምልጃውም: በረዳትነቱም
የታወቀ መልአክ ነው:: መጽሐፍ "መልአከ ምክሩ
ለእግዚአብሔር" ይለዋል:: "ወስሙ መስተሣሕልም"
ይለዋል:: ቂም የሌለው: ለምሕረት የሚፋጠን: ደግ መልአክ
ነውና::
✝በብሉይ ኪዳን በመከራ ለነበሩ ቅዱሳን ሁሉ ሞገስ: ረዳትና
አዳኝ ቢሆናቸው "መጋቤ ብሉይ" ተሰኝቷል:: እሥራኤልን 40
ዘመን በበርሃ መርቷል: መግቧልም:: ቅዱስ መጽሐፍ ስለ
እርሱ ብዙ ይላል:: (ዘፍ. 48:16, ኢያ. 5:13, መሳ. 13:17,
ዳን. 10:21, 12:1, መዝ. 33:7, ራዕይ. 12:7)
✝ደስ የሚለው ደግሞ ርሕሩሑ መልአክ ከእመቤታችን ጋር
#ልዩ_ፍቅር አለው:: ከእናቷ ማሕጸን ጀምሮ እስከ ዛሬ እነሆ
አብሯት አለ:: ደስ ብሎት ይታዘዛታል:: ማማለድ ሲፈልግም
"#እመቤቴ_ሆይ!_ቅደሚ" ይላታል:: ወደ እሳት መጋረጃ አብረው
ገብተው ለዓለም ምሕረትን: በረከትን ያወርዳሉ::
✝ቅዱስ ሚካኤልን በዚሕች ዕለት ስለ እነዚህ ነገሮች
እናከብረዋለን:-
1.በመላእክት ሁሉ ላይ አለቃ ሆኖ መሾሙን
2.ቅዳሴ ቤቱን (ግብፅ ውስጥ)
3.ቅድስት አፎምያን መርዳቱን
4.ቅዱስ ባሕራንን መጎብኘቱን
5.ቅዱስ ላሊበላን ወደ ሰማያት ማሳረጉን
6.ለፍጥረታት ሁሉ ምሕረት የሚጠይቅበት ዕለት ነውና::
♥ሊቀ መላእክት በክንፈ ረድኤቱ ከክፉ ሁሉ ይጠብቀን::♥
✝ቅዱስ ሚካኤል በጥንተ ተፈጥሮ #በኢዮር : #ኃይላት
በተባሉት ነገደ መላእክት ተሹሞ ነበር:: ሳጥናኤል በካደ ጊዜ
እግዚአብሔር ባወቀ: አንድም በትሕትናውና ደግነቱ በ99ኙ
ነገደ መላእክት ላይ ሁሉ ተሹሟል::
✞ከፍጥረት ወገን #ከእመቤታችን ቀጥሎ የቅዱስ ሚካኤልን
ያሕል ክብርና ርሕሩሕ የለም:: በምልጃውም: በረዳትነቱም
የታወቀ መልአክ ነው:: መጽሐፍ "መልአከ ምክሩ
ለእግዚአብሔር" ይለዋል:: "ወስሙ መስተሣሕልም"
ይለዋል:: ቂም የሌለው: ለምሕረት የሚፋጠን: ደግ መልአክ
ነውና::
✝በብሉይ ኪዳን በመከራ ለነበሩ ቅዱሳን ሁሉ ሞገስ: ረዳትና
አዳኝ ቢሆናቸው "መጋቤ ብሉይ" ተሰኝቷል:: እሥራኤልን 40
ዘመን በበርሃ መርቷል: መግቧልም:: ቅዱስ መጽሐፍ ስለ
እርሱ ብዙ ይላል:: (ዘፍ. 48:16, ኢያ. 5:13, መሳ. 13:17,
ዳን. 10:21, 12:1, መዝ. 33:7, ራዕይ. 12:7)
✝ደስ የሚለው ደግሞ ርሕሩሑ መልአክ ከእመቤታችን ጋር
#ልዩ_ፍቅር አለው:: ከእናቷ ማሕጸን ጀምሮ እስከ ዛሬ እነሆ
አብሯት አለ:: ደስ ብሎት ይታዘዛታል:: ማማለድ ሲፈልግም
"#እመቤቴ_ሆይ!_ቅደሚ" ይላታል:: ወደ እሳት መጋረጃ አብረው
ገብተው ለዓለም ምሕረትን: በረከትን ያወርዳሉ::
✝ቅዱስ ሚካኤልን በዚሕች ዕለት ስለ እነዚህ ነገሮች
እናከብረዋለን:-
1.በመላእክት ሁሉ ላይ አለቃ ሆኖ መሾሙን
2.ቅዳሴ ቤቱን (ግብፅ ውስጥ)
3.ቅድስት አፎምያን መርዳቱን
4.ቅዱስ ባሕራንን መጎብኘቱን
5.ቅዱስ ላሊበላን ወደ ሰማያት ማሳረጉን
6.ለፍጥረታት ሁሉ ምሕረት የሚጠይቅበት ዕለት ነውና::
♥ሊቀ መላእክት በክንፈ ረድኤቱ ከክፉ ሁሉ ይጠብቀን::♥
♥ቅዱስ ሕዝቅያስ♥
በነገሠ በ14ኛው ዓመት
የአሕዛብ (የአሦር) ንጉሥ ሰናክሬም በጠላትነት ተነሳበት::
ወደ አካባቢውም መጥቶ: ከቦ አስጨነቀው:: ሰናክሬም
በጦር እጅግ ኃይለኛ ነበር:: በዚያውም ላይ ጦር የሚመዙ
ከ185,000 በላይ ብርቱ ተዋጊዎች ነበሩትና ሕዝቅያስ
እንደማይችለው ተረድቶ መልእክተኛ ላከበት::
"እገብርልሃለሁ:: የፈለግከውንም እሰጥሃለሁ:: ሃገሬን
ግን አታጥፋ:: ኢየሩሳሌምን አታቃጥል:: ሕዝቤንም
አትግደል" በሚል ለመነው:: እጅ መንሻ ግብሩንም
ከከተማዋ የተገኘውን ወርቅና ብር ሁሉ ጭኖ ላከለት::
ሰናክሬም ግን ሰይጣን ያደረበት ነውና የሕዝቅያስን
ልመና ወደ ጐን ብሎ የእሥራኤልን አምላክ : ቅዱስ
ስሙንም ተገዳደረ:: ለሕዝቅያስም "ከእኔ እጅ የሚያድንህ
ማነው? ሕዝቡንም #እግዚአብሔር ያድናል ብለህ
አታታልላቸው" ሲል ላከበት:: ቅዱስ ሕዝቅያስ በዚህ ጊዜ
የፈጣሪው ስም ሲቃለል ሰምቷልና ፈጽሞ አዘነ::
መልእክተኞችን ወደ ነቢዩ #ቅዱስ_ኢሳይያስ ልኮ እርሱ
ወደ ቤተ መቅደስ ገባ:: በእግዚአብሔር ፊት ልብሱን
ቀድዶ ማቅ ለበሰ:: ስለ ኢየሩሳሌምና ሕዝቡም ፈጽሞ
አለቀሰ:: በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር የሰናክሬምን
መገዳደርና የሕዝቅያስን ልመና ሰምቷልና በኢሳይያስ
አንደበት እንዲሕ አለ:- "ስለ ባሪያየ ስለ #ዳዊት
ከተማዋን አድናታለሁ::"
በዚያች ሌሊትም ድንቅ መልአክ #ቅዱስ_ሚካኤል
ከሰማያት በግርማ ወረደ:: ወደ ሰናክሬም የጦር ሠፈር
ደርሶ አንድ ጊዜ የእሳት ሰይፉን መዝዞ ቢያሳያቸው
ከአሕዛብ ሠራዊት 185 ሺ ኃያላን እንደ ቅጠል ረገፉ::
በለኪሶ የነበረው ሰናክሬም በጧት ቢነሳ ሠራዊቱ ሁሉ
ወደ አስከሬን ክምር ተቀይሯል::
+በድንጋጤ ወደ #ነነዌ ሒዶ ወደ ጣዖት ቤቱ ሲገባ የራሱ
ልጆች (አድራማሌክና ሳራሳር) ገደሉት:: ትዕቢተኛው
ሰናክሬም ለአሕዛብ ሁሉ መዘባበቻ ሆነ:: ቅዱስ ሕዝቅያስ
ግን በፈጣሪው ታምኗልና ቅዱስ ሚካኤል ሞገስ ሆኖ
የዓለም ነገሥታት ሁሉ ፈሩት:: (1ነገ. 18:13, 19:1)
በነገሠ በ14ኛው ዓመት
የአሕዛብ (የአሦር) ንጉሥ ሰናክሬም በጠላትነት ተነሳበት::
ወደ አካባቢውም መጥቶ: ከቦ አስጨነቀው:: ሰናክሬም
በጦር እጅግ ኃይለኛ ነበር:: በዚያውም ላይ ጦር የሚመዙ
ከ185,000 በላይ ብርቱ ተዋጊዎች ነበሩትና ሕዝቅያስ
እንደማይችለው ተረድቶ መልእክተኛ ላከበት::
"እገብርልሃለሁ:: የፈለግከውንም እሰጥሃለሁ:: ሃገሬን
ግን አታጥፋ:: ኢየሩሳሌምን አታቃጥል:: ሕዝቤንም
አትግደል" በሚል ለመነው:: እጅ መንሻ ግብሩንም
ከከተማዋ የተገኘውን ወርቅና ብር ሁሉ ጭኖ ላከለት::
ሰናክሬም ግን ሰይጣን ያደረበት ነውና የሕዝቅያስን
ልመና ወደ ጐን ብሎ የእሥራኤልን አምላክ : ቅዱስ
ስሙንም ተገዳደረ:: ለሕዝቅያስም "ከእኔ እጅ የሚያድንህ
ማነው? ሕዝቡንም #እግዚአብሔር ያድናል ብለህ
አታታልላቸው" ሲል ላከበት:: ቅዱስ ሕዝቅያስ በዚህ ጊዜ
የፈጣሪው ስም ሲቃለል ሰምቷልና ፈጽሞ አዘነ::
መልእክተኞችን ወደ ነቢዩ #ቅዱስ_ኢሳይያስ ልኮ እርሱ
ወደ ቤተ መቅደስ ገባ:: በእግዚአብሔር ፊት ልብሱን
ቀድዶ ማቅ ለበሰ:: ስለ ኢየሩሳሌምና ሕዝቡም ፈጽሞ
አለቀሰ:: በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር የሰናክሬምን
መገዳደርና የሕዝቅያስን ልመና ሰምቷልና በኢሳይያስ
አንደበት እንዲሕ አለ:- "ስለ ባሪያየ ስለ #ዳዊት
ከተማዋን አድናታለሁ::"
በዚያች ሌሊትም ድንቅ መልአክ #ቅዱስ_ሚካኤል
ከሰማያት በግርማ ወረደ:: ወደ ሰናክሬም የጦር ሠፈር
ደርሶ አንድ ጊዜ የእሳት ሰይፉን መዝዞ ቢያሳያቸው
ከአሕዛብ ሠራዊት 185 ሺ ኃያላን እንደ ቅጠል ረገፉ::
በለኪሶ የነበረው ሰናክሬም በጧት ቢነሳ ሠራዊቱ ሁሉ
ወደ አስከሬን ክምር ተቀይሯል::
+በድንጋጤ ወደ #ነነዌ ሒዶ ወደ ጣዖት ቤቱ ሲገባ የራሱ
ልጆች (አድራማሌክና ሳራሳር) ገደሉት:: ትዕቢተኛው
ሰናክሬም ለአሕዛብ ሁሉ መዘባበቻ ሆነ:: ቅዱስ ሕዝቅያስ
ግን በፈጣሪው ታምኗልና ቅዱስ ሚካኤል ሞገስ ሆኖ
የዓለም ነገሥታት ሁሉ ፈሩት:: (1ነገ. 18:13, 19:1)
♥ እንኩዋን ለታላቁ #ጻድቅና_ገዳማዊ #አባ_ዓቢየ_እግዚእ ዓመታዊ የተአምር በዓል በሰላም አደረሳችሁ♥
✝ጻድቅና #ገዳማዊ_አባ_ዓቢየ_እግዚእ
ጐንደር ከተማ ነዋሪ ከሆኑ ወይም ከተማዋን የሚያውቁዋት ከሆነ አንድ ጥያቄ ልጠይቅዎ::
¤ከተማዋ ውስጥ ጅብና እባብን የመሠሉ አራዊት ነዋሪውን
ሲገድሉ ወይም ሲያቆስሉ ተመልክተው: ካልሆነም በታሪክ
ሰምተው ያውቃሉ?
¤መቸም መልስዎ "በጭራሽ አላውቅም" እንደሚሆን
እገምታለሁ:: "ግን ለምን?" ካሉ ነገሬን እንዲረዱኝ ሌሎች
የሃገራችን ዋና ዋና ከተሞችን ልብ ይበሉልኝ:: እንኩዋን
በሌሊት በቀንም አራዊቱ አይጠፉባቸውም::
¤ታዲያ ጐንደር ከተማ ውስጥ ጅብ የማይገባው: እባብና
ጊንጥ ሰው የማይገድለው በጻድቁ በአባ ዓቢየ እግዚእ ቃል
ኪዳን ምክንያት ነው:: (ሁሉም የሃገራችን ከተሞች የተባረኩ
መሆናቸውን ሳንዘነጋ ማለት ነው:: )
☞ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
አባ ዓቢየ እግዚእ የተወለዱት በ14ኛው መቶ ክ/ዘመን
#ትግራይ ተንቤን ( #መረታ) ውስጥ ነው:: የተባረኩ
ወላጆቻቸው #ያፍቅረነ_እግዚእ እና # ጽርሐ_ቅድሳት
ይባላሉ:: አጥምቀው "#ዓቢየ_እግዚእ " ሲሉ ስም
ያወጡላቸው የወቅቱ ዻዻስ #ሰላማ_መተርጉመ_መጻሕፍት
ናቸው:: ትርጉሙም 'በጌታ ዘንድ ታላቅ ሰው' ማለት ነው::
ዓቢየ እግዚእ በሕጻንነታቸው ሌሊት ሌሊት ባሕር ውስጥ
ሰጥመው ሲጸልዩ አድረው ቀን ቀን እየተማሩ ብሉይ ከሐዲስ
ጠነቀቁ:: ገና በወጣትነታቸው ወደ ታላቁ መነኮስ # አቡነ_መድኃኒነ_እግዚእ (ደብረ_በንኮል) ሔደው መንኩሰዋል:: በገዳሙ በጾም: በጸሎትና በስግደት ተወስነው ከኖሩ በሁዋላ ወደ #ዋልድባ ሔደው የተሰወረች ቤተ ክርስቲያን
አግኝተዋል:: በጊዜው በ40 ቀን አንዲት ቅጠል ብቻ
ለቁመተ ሥጋ ይበሉ ነበር::
ከዚያም ወደ ሃገራቸው ተንቤን ተመልሰው ዛሬም ድረስ
ድንቅ ሆኖ የሚታየውን ገዳም መሥርተው ብዙ መናንያንን
አፍርተዋል:: ዓቢየ እግዚእ ገዳማዊና ጻድቅ ብቻ ሳይሆን
#ሐዋርያዊ አባትም ነበሩ:: ከትግራይ እስከ #ደንቢያ ደግሞ
ሃገረ ስብከታቸው ነው::
አንድ ጊዜ ደቀ መዛሙርትን አስከትለው ለስብከት
ሲንቀሳቀሱ #ተከዜ ወንዝ አካባቢ ደረሱ:: ቀኑ ነሐሴ 10
ነውና ተከዜ እስከ ገደፉ ሞልቶ ለ3 ቀናት ባለመጉደሉ
ከ1,000 በላይ ሰዎች ሲያለቅሱ ደረሱ:: ጻድቁ ባካባቢው
የነበሩት ኢ-አማንያን (አሕዛብ) ቢሆኑም ራርተዋልና
"አምላከ_ሙሴ" ብለው ጸልየው ወደ ጥልቁ ውስጥ ገቡ::
#ቅዱስ_ሚካኤል አብሯቸው ነበርና ተከዜ ግራና ቀኝ
ተከፍሎ መሃሉ የብስ ሆነ:: ይሕን ድንቅ ያዩ ከ940 በላይ
አሕዛብም አምነው በጻድቁ እጅ ተጠምቀዋል:: ይሕም
ዘወትር ነሐሴ 10 ቀን በቤተ ክርስቲያናቸው (ጐንደር)
ይከበራል::
+ከዚያም እያስተማሩ ጐንደር ደረሱ:: ያኔ ጐንደር በቀሃና
አንገረብ ወንዞች የታጠረች አንዲት መንደር ነበረች:: ጻድቁ
ቀን ቀን እየሰበኩ ማታ ዛሬ ቤተ ክርስቲያናቸው የታነጸበት
ሥፍራ ላይ ሲጸልዩ ያድሩ ነበር::
+በዚያ ዘመን ጐንደር ውስጥ ጅብ: እባብና መሠል አራዊት
ገብተው ሕዝቡን ጨረሱት:: ይሕንን የተመለከቱት አባ ዓቢየ
እግዚእ ወደ እግዚአብሔር አለቀሱ:: በፍጹም ልባቸውም ስለ
ሕዝቡ ለመኑ::
የለመኑትን የማይነሳ ጌታ ወደ ጻድቁ ቀርቦ "በስምሕ
የተማጸኑ: በቃል ኪዳንህ ያመኑ: በምድር አራዊት
አይሠለጥኑባቸውም:: በሰማይም እሳትን አያዩም::
ጐንደርንም አራዊት ገብተው ሰውን አይጐዱም::" ብሏቸው
አርጉዋል:: ጻድቁም የወንጌል አገልግሎታቸውን ፈጽመው ወደ
ገዳማቸው #ተንቤን ተመልሰዋል:: ይሔው እኛ ምን
ብንከፋ: ጻድቁንም ብንረሳቸው #እግዚአብሔር ግን ዛሬም
በጻድቁ ምልጃ ከተማዋን ጠብቆ ይኖራል:: ነገን ደግሞ እርሱ
ያውቃል:: ዛሬ ቤተ ክርስቲያኑ የታነጸበት ቦታ ( #ጎንደር ቀበሌ
09 #ኪዳነ_ምሕረት ) ጻድቁ የጸለዩበት ቦታ ነው:: እንኩዋን
በወርሃዊ በዓላቸው (በ19) ይቅርና በዓመታዊ በዓላቸው
(ግንቦት 19, ነሐሴ 10) እንኩዋ ለንግስ የሚመጣው ሰው
ቁጥር ያስተዛዝባል::
አባ ዓቢየ እግዚእ በገዳማቸው ተንቤን ለብዙ ዘመናት
በቅድስና ኑረው: 3 ሙታንን አስነስተው: ብዙ ድውያንን
ፈውሰው: #ብሔረ_ብጹዓንን ጎብኝተው: የድኅነት ቃል
ኪዳንም ተቀብለው: በ140 ዓመታቸው ግንቦት 19 ቀን
አርፈዋል:: የጻድቁ ክብር ለሁሉ ነውና እናስባቸው::
ይህች ዕለት ባሕረ ተከዜን ከፍለው ሕዝቡን ያሻገሩባት:
አሕዛብንም ያጠመቁባት ናትና በገዳማቸው: ጐንደር ውስጥ
በሚገኘው ቤተ ክርስቲያናቸውም ይከበራል::
¤በረከታቸው ይደርብን::
✝ጻድቅና #ገዳማዊ_አባ_ዓቢየ_እግዚእ
ጐንደር ከተማ ነዋሪ ከሆኑ ወይም ከተማዋን የሚያውቁዋት ከሆነ አንድ ጥያቄ ልጠይቅዎ::
¤ከተማዋ ውስጥ ጅብና እባብን የመሠሉ አራዊት ነዋሪውን
ሲገድሉ ወይም ሲያቆስሉ ተመልክተው: ካልሆነም በታሪክ
ሰምተው ያውቃሉ?
¤መቸም መልስዎ "በጭራሽ አላውቅም" እንደሚሆን
እገምታለሁ:: "ግን ለምን?" ካሉ ነገሬን እንዲረዱኝ ሌሎች
የሃገራችን ዋና ዋና ከተሞችን ልብ ይበሉልኝ:: እንኩዋን
በሌሊት በቀንም አራዊቱ አይጠፉባቸውም::
¤ታዲያ ጐንደር ከተማ ውስጥ ጅብ የማይገባው: እባብና
ጊንጥ ሰው የማይገድለው በጻድቁ በአባ ዓቢየ እግዚእ ቃል
ኪዳን ምክንያት ነው:: (ሁሉም የሃገራችን ከተሞች የተባረኩ
መሆናቸውን ሳንዘነጋ ማለት ነው:: )
☞ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
አባ ዓቢየ እግዚእ የተወለዱት በ14ኛው መቶ ክ/ዘመን
#ትግራይ ተንቤን ( #መረታ) ውስጥ ነው:: የተባረኩ
ወላጆቻቸው #ያፍቅረነ_እግዚእ እና # ጽርሐ_ቅድሳት
ይባላሉ:: አጥምቀው "#ዓቢየ_እግዚእ " ሲሉ ስም
ያወጡላቸው የወቅቱ ዻዻስ #ሰላማ_መተርጉመ_መጻሕፍት
ናቸው:: ትርጉሙም 'በጌታ ዘንድ ታላቅ ሰው' ማለት ነው::
ዓቢየ እግዚእ በሕጻንነታቸው ሌሊት ሌሊት ባሕር ውስጥ
ሰጥመው ሲጸልዩ አድረው ቀን ቀን እየተማሩ ብሉይ ከሐዲስ
ጠነቀቁ:: ገና በወጣትነታቸው ወደ ታላቁ መነኮስ # አቡነ_መድኃኒነ_እግዚእ (ደብረ_በንኮል) ሔደው መንኩሰዋል:: በገዳሙ በጾም: በጸሎትና በስግደት ተወስነው ከኖሩ በሁዋላ ወደ #ዋልድባ ሔደው የተሰወረች ቤተ ክርስቲያን
አግኝተዋል:: በጊዜው በ40 ቀን አንዲት ቅጠል ብቻ
ለቁመተ ሥጋ ይበሉ ነበር::
ከዚያም ወደ ሃገራቸው ተንቤን ተመልሰው ዛሬም ድረስ
ድንቅ ሆኖ የሚታየውን ገዳም መሥርተው ብዙ መናንያንን
አፍርተዋል:: ዓቢየ እግዚእ ገዳማዊና ጻድቅ ብቻ ሳይሆን
#ሐዋርያዊ አባትም ነበሩ:: ከትግራይ እስከ #ደንቢያ ደግሞ
ሃገረ ስብከታቸው ነው::
አንድ ጊዜ ደቀ መዛሙርትን አስከትለው ለስብከት
ሲንቀሳቀሱ #ተከዜ ወንዝ አካባቢ ደረሱ:: ቀኑ ነሐሴ 10
ነውና ተከዜ እስከ ገደፉ ሞልቶ ለ3 ቀናት ባለመጉደሉ
ከ1,000 በላይ ሰዎች ሲያለቅሱ ደረሱ:: ጻድቁ ባካባቢው
የነበሩት ኢ-አማንያን (አሕዛብ) ቢሆኑም ራርተዋልና
"አምላከ_ሙሴ" ብለው ጸልየው ወደ ጥልቁ ውስጥ ገቡ::
#ቅዱስ_ሚካኤል አብሯቸው ነበርና ተከዜ ግራና ቀኝ
ተከፍሎ መሃሉ የብስ ሆነ:: ይሕን ድንቅ ያዩ ከ940 በላይ
አሕዛብም አምነው በጻድቁ እጅ ተጠምቀዋል:: ይሕም
ዘወትር ነሐሴ 10 ቀን በቤተ ክርስቲያናቸው (ጐንደር)
ይከበራል::
+ከዚያም እያስተማሩ ጐንደር ደረሱ:: ያኔ ጐንደር በቀሃና
አንገረብ ወንዞች የታጠረች አንዲት መንደር ነበረች:: ጻድቁ
ቀን ቀን እየሰበኩ ማታ ዛሬ ቤተ ክርስቲያናቸው የታነጸበት
ሥፍራ ላይ ሲጸልዩ ያድሩ ነበር::
+በዚያ ዘመን ጐንደር ውስጥ ጅብ: እባብና መሠል አራዊት
ገብተው ሕዝቡን ጨረሱት:: ይሕንን የተመለከቱት አባ ዓቢየ
እግዚእ ወደ እግዚአብሔር አለቀሱ:: በፍጹም ልባቸውም ስለ
ሕዝቡ ለመኑ::
የለመኑትን የማይነሳ ጌታ ወደ ጻድቁ ቀርቦ "በስምሕ
የተማጸኑ: በቃል ኪዳንህ ያመኑ: በምድር አራዊት
አይሠለጥኑባቸውም:: በሰማይም እሳትን አያዩም::
ጐንደርንም አራዊት ገብተው ሰውን አይጐዱም::" ብሏቸው
አርጉዋል:: ጻድቁም የወንጌል አገልግሎታቸውን ፈጽመው ወደ
ገዳማቸው #ተንቤን ተመልሰዋል:: ይሔው እኛ ምን
ብንከፋ: ጻድቁንም ብንረሳቸው #እግዚአብሔር ግን ዛሬም
በጻድቁ ምልጃ ከተማዋን ጠብቆ ይኖራል:: ነገን ደግሞ እርሱ
ያውቃል:: ዛሬ ቤተ ክርስቲያኑ የታነጸበት ቦታ ( #ጎንደር ቀበሌ
09 #ኪዳነ_ምሕረት ) ጻድቁ የጸለዩበት ቦታ ነው:: እንኩዋን
በወርሃዊ በዓላቸው (በ19) ይቅርና በዓመታዊ በዓላቸው
(ግንቦት 19, ነሐሴ 10) እንኩዋ ለንግስ የሚመጣው ሰው
ቁጥር ያስተዛዝባል::
አባ ዓቢየ እግዚእ በገዳማቸው ተንቤን ለብዙ ዘመናት
በቅድስና ኑረው: 3 ሙታንን አስነስተው: ብዙ ድውያንን
ፈውሰው: #ብሔረ_ብጹዓንን ጎብኝተው: የድኅነት ቃል
ኪዳንም ተቀብለው: በ140 ዓመታቸው ግንቦት 19 ቀን
አርፈዋል:: የጻድቁ ክብር ለሁሉ ነውና እናስባቸው::
ይህች ዕለት ባሕረ ተከዜን ከፍለው ሕዝቡን ያሻገሩባት:
አሕዛብንም ያጠመቁባት ናትና በገዳማቸው: ጐንደር ውስጥ
በሚገኘው ቤተ ክርስቲያናቸውም ይከበራል::
¤በረከታቸው ይደርብን::
♥ እንኩዋን ለታላላቁ ቅዱሳን #አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት:
#ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ እና #ቅዱስ_ቶማስ_ዘመርዓስ
ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ♥
ቅዱስ #ተክለ_ሃይማኖት ሐዋርያዊ "*+ #ልደት
መልካም ዛፍ
መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ: #
ጸጋ_ዘአብ ካህኑና #እግዚእ_ኃረያ ናቸው:: እርሱ በክህነቱ:
እርሷ በደግነቷ: በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ
ፍሬን ሰጥቷቸዋል:: +በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ
ቢደርስባቸው #ቅዱስ_ሚካኤል: ጸጋ ዘአብን ከሞት: እግዚእ
ኃረያን ከትድምርተ አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል::
በሁዋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል:: +አቡነ ተክለ
ሃይማኖት የጸነሱት መጋቢት 24, በ1206 (1196) ሲሆን
የተወለዱት ታሕሳስ 24, በ1207 (1197) ዓ/ም ነው::
በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል:: ቤታቸውም
በበረከት ሞልቷል:: #ዕድገት =>የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው
"#ፍሥሃ_ጽዮን" ይሰኛል:: ይሕንን ስም ይዘው: አባታቸው ጸጋ
ዘአብን ተከትለው አድገዋል:: በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን
(ብሉያት: ሐዲሳትን) ተምረዋል:: በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ
አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል:: ዲቁና ከወቅቱ ዻዻስ #አባ_
ጌርሎስ ተቀብለዋል:: #መጠራት =>አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮን
ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ
ተሰማ:: የክብር ባለቤት #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ አእላፍ
መላእክት እያመሰገኑ በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ::
+የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ: "ከዛሬ ጀምሮ
ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን:: አራዊትን
ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ:: ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ
በግርማ ዐረገ:: ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በሁዋላ
ሰዓትን አላጠፉም:: ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ
ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ:: #አገልግሎት
=>ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል
አገልግሎትን ጀመሩ:: በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ (#
ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው
አጠመቁ:: ያንጊዜ #ኢትዮዽያ 2 መልክ ነበራት:: 1.ዮዲት
(ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ
አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል: ወይም በባዕድ
አምልኮ ተጠምዷል:: 2.ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት
ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር:: +ግማሹ ሃገር በጨለመበት
ወቅት የደረሱት #ሐዲስ_ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት
ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ::
ሕዝቡን: መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን
(ጠንቁዋዮችን) አጥፍተዋል:: #ገዳማዊ ሕይወት =>ቅዱስ
ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው
ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል:: እርሳቸው ከሁሉ
የተሻሉ ሳሉም በ3 ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል::
+እነዚህም በአቡነ #በጸሎተ_ሚካኤል ገዳም ለ12 ዓመታት:
በአቡነ #ኢየሱስ_ሞዐ_ዘሐይቅ ገዳም ለ7 ዓመታት: በደብረ
ዳሞ ከአቡነ #ዮሐኒ ጋር ለ7 ዓመታት: በአጠቃላይ ለ26
ዓመታት አገልግለዋል:: +በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ
በሁዋላም ወደ ምድረ ሽዋ #ዞረሬ ተመልሰው በአንዲት በዓት
ውስጥ ለ22 ዓመታት ቆመው ጸልየዋል:: በተሰበረ እግራቸውም
6 ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል:: #
ስድስት ክንፍ =>ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ
ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት
መካናት ተባርከዋል:: ጻድቁ ምድረ #እሥራኤል የገቡት
በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ
ነበር:: +የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት #አባ_ሚካኤል ጋርም
ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል:: ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ
በሁዋላ ነው:: ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ
ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ
እንባቸው ይፈስ ነበር:: +ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው
ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም:: በገሃድ:-
¤በቤተ መቅደስ ብስራቱን ¤በቤተ ልሔም ልደቱን ¤በቤተ ዮሴፍ
ግዝረቱን ¤በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን ¤በቤተ አልዓዛር
ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር:: +የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል
ወደሆነው #ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ
ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን
ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ:: በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ
#እመቤታችን_ድንግል_ማርያም ፈጥና ደርሳ ተክልየን
ወደሰማይ አሳረገቻቸው:: +በዚያም:- ¤የብርሃን ዐይን
ተቀብለው ¤6 ክንፍ አብቅለው ¤የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው
¤ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው ¤ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም
ተደምረው ¤ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው
¤"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ
ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል:: #ተአምራት
=>የተክልየ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው::
*ሙት አንስተዋል *ድውያንን ፈውሰዋል *አጋንንትን አሳደዋል
*እሳትን ጨብጠዋል *በክንፍ በረዋል *ደመናን ዙፋን
አድርገዋል:: +ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን
መሥርተዋል:: በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት
አብረው ኑረዋል:: በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና:: #ዕረፍት
=>ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን
ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው: አእላፍ ፍሬን አፍርተው:
በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው ነሐሴ 24,
በ1306 (1296) ዓ/ም ዐርፈዋል:: ጌታ: ድንግል ማርያምና
ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል:: 10 ትውልድ
የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል::
#ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ እና #ቅዱስ_ቶማስ_ዘመርዓስ
ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ♥
ቅዱስ #ተክለ_ሃይማኖት ሐዋርያዊ "*+ #ልደት
መልካም ዛፍ
መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ: #
ጸጋ_ዘአብ ካህኑና #እግዚእ_ኃረያ ናቸው:: እርሱ በክህነቱ:
እርሷ በደግነቷ: በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ
ፍሬን ሰጥቷቸዋል:: +በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ
ቢደርስባቸው #ቅዱስ_ሚካኤል: ጸጋ ዘአብን ከሞት: እግዚእ
ኃረያን ከትድምርተ አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል::
በሁዋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል:: +አቡነ ተክለ
ሃይማኖት የጸነሱት መጋቢት 24, በ1206 (1196) ሲሆን
የተወለዱት ታሕሳስ 24, በ1207 (1197) ዓ/ም ነው::
በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል:: ቤታቸውም
በበረከት ሞልቷል:: #ዕድገት =>የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው
"#ፍሥሃ_ጽዮን" ይሰኛል:: ይሕንን ስም ይዘው: አባታቸው ጸጋ
ዘአብን ተከትለው አድገዋል:: በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን
(ብሉያት: ሐዲሳትን) ተምረዋል:: በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ
አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል:: ዲቁና ከወቅቱ ዻዻስ #አባ_
ጌርሎስ ተቀብለዋል:: #መጠራት =>አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮን
ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ
ተሰማ:: የክብር ባለቤት #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ አእላፍ
መላእክት እያመሰገኑ በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ::
+የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ: "ከዛሬ ጀምሮ
ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን:: አራዊትን
ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ:: ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ
በግርማ ዐረገ:: ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በሁዋላ
ሰዓትን አላጠፉም:: ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ
ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ:: #አገልግሎት
=>ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል
አገልግሎትን ጀመሩ:: በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ (#
ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው
አጠመቁ:: ያንጊዜ #ኢትዮዽያ 2 መልክ ነበራት:: 1.ዮዲት
(ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ
አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል: ወይም በባዕድ
አምልኮ ተጠምዷል:: 2.ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት
ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር:: +ግማሹ ሃገር በጨለመበት
ወቅት የደረሱት #ሐዲስ_ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት
ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ::
ሕዝቡን: መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን
(ጠንቁዋዮችን) አጥፍተዋል:: #ገዳማዊ ሕይወት =>ቅዱስ
ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው
ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል:: እርሳቸው ከሁሉ
የተሻሉ ሳሉም በ3 ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል::
+እነዚህም በአቡነ #በጸሎተ_ሚካኤል ገዳም ለ12 ዓመታት:
በአቡነ #ኢየሱስ_ሞዐ_ዘሐይቅ ገዳም ለ7 ዓመታት: በደብረ
ዳሞ ከአቡነ #ዮሐኒ ጋር ለ7 ዓመታት: በአጠቃላይ ለ26
ዓመታት አገልግለዋል:: +በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ
በሁዋላም ወደ ምድረ ሽዋ #ዞረሬ ተመልሰው በአንዲት በዓት
ውስጥ ለ22 ዓመታት ቆመው ጸልየዋል:: በተሰበረ እግራቸውም
6 ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል:: #
ስድስት ክንፍ =>ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ
ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት
መካናት ተባርከዋል:: ጻድቁ ምድረ #እሥራኤል የገቡት
በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ
ነበር:: +የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት #አባ_ሚካኤል ጋርም
ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል:: ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ
በሁዋላ ነው:: ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ
ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ
እንባቸው ይፈስ ነበር:: +ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው
ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም:: በገሃድ:-
¤በቤተ መቅደስ ብስራቱን ¤በቤተ ልሔም ልደቱን ¤በቤተ ዮሴፍ
ግዝረቱን ¤በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን ¤በቤተ አልዓዛር
ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር:: +የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል
ወደሆነው #ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ
ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን
ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ:: በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ
#እመቤታችን_ድንግል_ማርያም ፈጥና ደርሳ ተክልየን
ወደሰማይ አሳረገቻቸው:: +በዚያም:- ¤የብርሃን ዐይን
ተቀብለው ¤6 ክንፍ አብቅለው ¤የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው
¤ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው ¤ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም
ተደምረው ¤ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው
¤"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ
ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል:: #ተአምራት
=>የተክልየ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው::
*ሙት አንስተዋል *ድውያንን ፈውሰዋል *አጋንንትን አሳደዋል
*እሳትን ጨብጠዋል *በክንፍ በረዋል *ደመናን ዙፋን
አድርገዋል:: +ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን
መሥርተዋል:: በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት
አብረው ኑረዋል:: በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና:: #ዕረፍት
=>ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን
ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው: አእላፍ ፍሬን አፍርተው:
በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው ነሐሴ 24,
በ1306 (1296) ዓ/ም ዐርፈዋል:: ጌታ: ድንግል ማርያምና
ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል:: 10 ትውልድ
የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል::
💚💛ቅዱስ አቦሊ ሰማዕት💛❤️
ቅዱስ አቦሊ የሰማዕታቱ #ቅዱስ_ዮስጦስና
#ቅድስት_ታውክልያ ልጅ ሲሆን በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን
ያበራ የቤተ ክርስቲያን ዕንቁ ሰማዕት ነው:: የሚገርመኝ
ሦስቱ የግማሹ ዓለም አስተዳዳሪዎች ነበሩ:: ዮስጦስ
ንጉሥ: ታውክልያ ንግሥት: አቦሊ ደግሞ ልዑል ነው::
ነገር ግን ይህንን ክብራቸውን # በክርስቶስ ፍቅር ጐን: ሚዛን
ላይ ቢያኖሩት በጣም ቀሎ ታያቸው:: 3ቱም ከዙፋናቸው
ወርደው: ወገባቸውንም ታጥቀው: ባሮቻቸው በነበሩ ሰዎች
ስለ ክርስቶስ ብዙ ተንገላቱ:: መራራ ሞትንም ታገሱ::
በተለይ ቅዱስ አቦሊ ከአንጾኪያ ወደ ግብጽ (ብስጣ) ይዘው
አምጥተው ክርስትናውን እንዲተው ያላደረጉት የለም::
በቁሙ ቆዳውን ገፈው: በቆዳው አቅማዳ ሰፍተው: ያንንም
አሸክመው: የተገፈፈ አካሉን ጨውና ኮምጣጤ እየቀቡ
አዙረውታል::
እርሱ ግን ጌታ በላከለት ድንቅ መልአክ #ቅዱስ_ሚካኤል
ረዳትነት ሁሉን ችሎታል:: በዘመኑ ብዙ ተአምራትን የሠራ
ሲሆን አንድ ጊዜ ቤት ተንዶ 16 ሰዎች ቢያልቁ የተገፈፈ
ቆዳውን እየጣለባቸው ተነስተዋል:: በተአምራቱና
በተጋድሎውም ብዙ ሺህ አሕዛብን ለክርስትና: ብሎም
ለሰማዕትነት አብቅቷል::
እርሱም ከብዙ የመከራ ጊዜያት በሁዋላ በዚህች ቀን አንገቱን
ተከልሏል:: ጌታችን "ዜናሕን የጻፈውን: ያነበበውንና
የሰማውን ይቅር እለዋለሁ" ብሎ ቃል ኪዳንን ሰጥቶታል::
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
ፈጣሪ ከጻድቃንና ሰማዕታት በረከትን አይለይብን::
ወርሐ ነሐሴንም ለበረከት ይቀድስልን::
Dn yordanos abebe
ቅዱስ አቦሊ የሰማዕታቱ #ቅዱስ_ዮስጦስና
#ቅድስት_ታውክልያ ልጅ ሲሆን በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን
ያበራ የቤተ ክርስቲያን ዕንቁ ሰማዕት ነው:: የሚገርመኝ
ሦስቱ የግማሹ ዓለም አስተዳዳሪዎች ነበሩ:: ዮስጦስ
ንጉሥ: ታውክልያ ንግሥት: አቦሊ ደግሞ ልዑል ነው::
ነገር ግን ይህንን ክብራቸውን # በክርስቶስ ፍቅር ጐን: ሚዛን
ላይ ቢያኖሩት በጣም ቀሎ ታያቸው:: 3ቱም ከዙፋናቸው
ወርደው: ወገባቸውንም ታጥቀው: ባሮቻቸው በነበሩ ሰዎች
ስለ ክርስቶስ ብዙ ተንገላቱ:: መራራ ሞትንም ታገሱ::
በተለይ ቅዱስ አቦሊ ከአንጾኪያ ወደ ግብጽ (ብስጣ) ይዘው
አምጥተው ክርስትናውን እንዲተው ያላደረጉት የለም::
በቁሙ ቆዳውን ገፈው: በቆዳው አቅማዳ ሰፍተው: ያንንም
አሸክመው: የተገፈፈ አካሉን ጨውና ኮምጣጤ እየቀቡ
አዙረውታል::
እርሱ ግን ጌታ በላከለት ድንቅ መልአክ #ቅዱስ_ሚካኤል
ረዳትነት ሁሉን ችሎታል:: በዘመኑ ብዙ ተአምራትን የሠራ
ሲሆን አንድ ጊዜ ቤት ተንዶ 16 ሰዎች ቢያልቁ የተገፈፈ
ቆዳውን እየጣለባቸው ተነስተዋል:: በተአምራቱና
በተጋድሎውም ብዙ ሺህ አሕዛብን ለክርስትና: ብሎም
ለሰማዕትነት አብቅቷል::
እርሱም ከብዙ የመከራ ጊዜያት በሁዋላ በዚህች ቀን አንገቱን
ተከልሏል:: ጌታችን "ዜናሕን የጻፈውን: ያነበበውንና
የሰማውን ይቅር እለዋለሁ" ብሎ ቃል ኪዳንን ሰጥቶታል::
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
ፈጣሪ ከጻድቃንና ሰማዕታት በረከትን አይለይብን::
ወርሐ ነሐሴንም ለበረከት ይቀድስልን::
Dn yordanos abebe
🌼#ቅዱስ_ሚካኤል_ሊቀ_መላእክት🌼
#ቅዱሳት_መጻሕፍት እንደሚነግሩን የመላእክት ሁሉ
አለቃቸው በፈጣሪው ኃይል ብዙ ድንቆችን ሠርቷል::
ከመጀመሪያው ሰው #አዳም ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ: አምነው
ለሚጠሩት ረዳት ነው:: ዘወትርም ያድናቸው ዘንድ በሚፈሩት
ሰዎች ዙሪያ ይሠፍራል:: (መዝ. 33:7)
¤እግራችን እንዳይሰናከል ዘወትር ይጠብቀናል:: (መዝ.
90:11)
¤የቅዱስ ሚካኤል ስሙ ድንቅ ነው:: (መሳ. 13:18)
¤ከእርሱ በቀርስ የሚያጸና ማን አለና! (ዳን. 10:21)
¤ለሕዝቡም የሚቆም ታዳጊ መልአክ ነው:: (ዳን. 12:1)
¤በፊቱ ሲቆምም ስለ ክብሩ ጫማ አውልቆ: ባጭር ታጥቆ
ነው:: (ኢያ. 5:13)
ይህ ድንቅ መልአክ ከሺህ ዓመታት በፊት በሮም ከተማ
ይህንን ድንቅ ተአምር በዚህች ዕለት መሥራቱን ቤተ ክርስቲያን
ትመሰክራለች:: በድሮው የሮም ግዛት ' #ሩፍምያ ' የምትባል
ከተማ ነበረች:: ይህች ከተማ ክርስቲያኖችም: ኢአማንያንም
ተቀላቅለው የሚኖሩባት ናት::
+በከተማዋ የክርስቲያኖች ቁጥር ትንሽ ቢሆንም በእምነት
ግን ጠንካሮች ነበሩ:: በተለይ ደግሞ የቤተ ክርስቲያኗ መጋቢ ባለ ፍጹም እምነት ሰው ነበር:: በቦታው የቅዱስ ሚካኤል ቤተ
ክርስቲያን በመኖሩም ብዙ ተአምራት ይደረጉ ነበር:: ተበለጥን
የሚል ስሜት የተሰማቸው አሕዛብ (ዮናናውያን) ግን ይሕንን ቤተ ክርስቲያን ለማጥፋት ተማማሉ::
+በቀጥታ ሔደው ቢያፈርሱት ወይም ቢያቃጥሉት በሕግ
እንደሚጠየቁ ያውቃሉና በሥጋዊ ጭንቅላታቸው ዘዴ ያሉትን
መከሩና ወሰኑ:: በከተማዋ ዳር የሚያልፍ አንድ ትልቅ ወንዝ
አለ:: በሞላ ጊዜ ያገኘውን ሁሉ ጠርጐ የሚወስድም ነበር::
+ታዲያ ክፋተኞቹ ሌሊት ሌሊት እየተነሱ የሚሔድበትን
መንገድ ዘግተው: ወደ ቤተ ክርስቲያኑ አቅጣጫ መንገድ ከፈቱለት:: ከቀናት በሁዋላ ከባድ ዝናብ በዚህች ቀን ጣለ:: ወንዙ ትልቅ ነውና ያገኘውን ሁሉ እያገላበጠ ደረሰ::
በወቅቱ በቅዱሱ መልአክ መቅደስ ውስጥ ከመጋቢው በቀር
ሰው አልነበረምና አስፈሪ ድምጽ ሰምቶ ቢወጣ ወንዙ እየደነፋ
ወደ ቤተ ክርስቲያኑ እየመጣ ነው:: አሰበው: ከደቂቃዎች
በሁዋላ ቤተ ክርስቲያኑ እንዳልነበረ ሊሆን ነው::
+እርሱ አንድ ተስፋ ነበረውና ወደ ውስጥ ገብቶ ቅዱስ
ሚካኤልን ተማጸነ:: ከዚያ ላለመውጣትም ወሰነ:: ትንሽ ቆይቶ በታላቅ ኃይል ወንዙ ደረሰ:: በዚህ ጊዜ ግን ቅዱስ ሚካኤል
በግርማ ከሰማይ ወርዶ በወንዙ ፊት ቆመ::
መጋቢውንም "ጽና: አትፍራ" ብሎት በያዘው የብርሃን በትረ-
መስቀል መሬትን አንድ ጊዜ መታት:: በዚያች ቅጽበትም ትልቅ
ሸለቆ ተፈጠረ:: ወንዙም በሸለቆው ውስጥ አልፎ ሔደ::
የሚገርመው ሸለቆው የተፈጠረው በቤተ ክርስቲያኑ በታች
ነው:: ቅዱስ ሚካኤል ግን መጋቢውን ባርኮት በክብር ዐረገ::
በማግስቱ ክርስቲያኖቹ ይህንን አይተው ደስ አላቸው::
መልአኩንም አከበሩት:: አሕዛብ ግን አፈሩ::
Dn yordanos abebe
👉senkesar join us
#ቅዱሳት_መጻሕፍት እንደሚነግሩን የመላእክት ሁሉ
አለቃቸው በፈጣሪው ኃይል ብዙ ድንቆችን ሠርቷል::
ከመጀመሪያው ሰው #አዳም ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ: አምነው
ለሚጠሩት ረዳት ነው:: ዘወትርም ያድናቸው ዘንድ በሚፈሩት
ሰዎች ዙሪያ ይሠፍራል:: (መዝ. 33:7)
¤እግራችን እንዳይሰናከል ዘወትር ይጠብቀናል:: (መዝ.
90:11)
¤የቅዱስ ሚካኤል ስሙ ድንቅ ነው:: (መሳ. 13:18)
¤ከእርሱ በቀርስ የሚያጸና ማን አለና! (ዳን. 10:21)
¤ለሕዝቡም የሚቆም ታዳጊ መልአክ ነው:: (ዳን. 12:1)
¤በፊቱ ሲቆምም ስለ ክብሩ ጫማ አውልቆ: ባጭር ታጥቆ
ነው:: (ኢያ. 5:13)
ይህ ድንቅ መልአክ ከሺህ ዓመታት በፊት በሮም ከተማ
ይህንን ድንቅ ተአምር በዚህች ዕለት መሥራቱን ቤተ ክርስቲያን
ትመሰክራለች:: በድሮው የሮም ግዛት ' #ሩፍምያ ' የምትባል
ከተማ ነበረች:: ይህች ከተማ ክርስቲያኖችም: ኢአማንያንም
ተቀላቅለው የሚኖሩባት ናት::
+በከተማዋ የክርስቲያኖች ቁጥር ትንሽ ቢሆንም በእምነት
ግን ጠንካሮች ነበሩ:: በተለይ ደግሞ የቤተ ክርስቲያኗ መጋቢ ባለ ፍጹም እምነት ሰው ነበር:: በቦታው የቅዱስ ሚካኤል ቤተ
ክርስቲያን በመኖሩም ብዙ ተአምራት ይደረጉ ነበር:: ተበለጥን
የሚል ስሜት የተሰማቸው አሕዛብ (ዮናናውያን) ግን ይሕንን ቤተ ክርስቲያን ለማጥፋት ተማማሉ::
+በቀጥታ ሔደው ቢያፈርሱት ወይም ቢያቃጥሉት በሕግ
እንደሚጠየቁ ያውቃሉና በሥጋዊ ጭንቅላታቸው ዘዴ ያሉትን
መከሩና ወሰኑ:: በከተማዋ ዳር የሚያልፍ አንድ ትልቅ ወንዝ
አለ:: በሞላ ጊዜ ያገኘውን ሁሉ ጠርጐ የሚወስድም ነበር::
+ታዲያ ክፋተኞቹ ሌሊት ሌሊት እየተነሱ የሚሔድበትን
መንገድ ዘግተው: ወደ ቤተ ክርስቲያኑ አቅጣጫ መንገድ ከፈቱለት:: ከቀናት በሁዋላ ከባድ ዝናብ በዚህች ቀን ጣለ:: ወንዙ ትልቅ ነውና ያገኘውን ሁሉ እያገላበጠ ደረሰ::
በወቅቱ በቅዱሱ መልአክ መቅደስ ውስጥ ከመጋቢው በቀር
ሰው አልነበረምና አስፈሪ ድምጽ ሰምቶ ቢወጣ ወንዙ እየደነፋ
ወደ ቤተ ክርስቲያኑ እየመጣ ነው:: አሰበው: ከደቂቃዎች
በሁዋላ ቤተ ክርስቲያኑ እንዳልነበረ ሊሆን ነው::
+እርሱ አንድ ተስፋ ነበረውና ወደ ውስጥ ገብቶ ቅዱስ
ሚካኤልን ተማጸነ:: ከዚያ ላለመውጣትም ወሰነ:: ትንሽ ቆይቶ በታላቅ ኃይል ወንዙ ደረሰ:: በዚህ ጊዜ ግን ቅዱስ ሚካኤል
በግርማ ከሰማይ ወርዶ በወንዙ ፊት ቆመ::
መጋቢውንም "ጽና: አትፍራ" ብሎት በያዘው የብርሃን በትረ-
መስቀል መሬትን አንድ ጊዜ መታት:: በዚያች ቅጽበትም ትልቅ
ሸለቆ ተፈጠረ:: ወንዙም በሸለቆው ውስጥ አልፎ ሔደ::
የሚገርመው ሸለቆው የተፈጠረው በቤተ ክርስቲያኑ በታች
ነው:: ቅዱስ ሚካኤል ግን መጋቢውን ባርኮት በክብር ዐረገ::
በማግስቱ ክርስቲያኖቹ ይህንን አይተው ደስ አላቸው::
መልአኩንም አከበሩት:: አሕዛብ ግን አፈሩ::
Dn yordanos abebe
👉senkesar join us
Forwarded from ዐውደ ምሕረት
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
"የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል #ያድናቸውማል።" መዝ 33:7
👉 ይህን ኃይለ ቃል የተናገረው ልበ አምላክ ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ነው። በግልጽ እንደነገረን የእግዚአብሔር የሆኑት ቅዱሳን መልአክት የሚያድኑ አዳኞች ናቸው። እነርሱን ከሚፈሯቸውና ከሚያምኗቸው ሰዎች አይለዩም። ከሚደርስባቸው መከራ እና ችግር ፈተና ሁሉ ያድኗቸዋል ይታደጓቸዋል። ቅዱሳን መልአክት የሰው ልጆችን የሚያድኑ አዳኞች መሆናቸውን ቅዱስ ያዕቆብ ዮሴፍንና ልጆቹን በባረከ ጊዜም እንዲህ ሲል መስክሯል። "ከታናሽነቴ ጀምሮ እኔን የመገበኝ እግዚአብሔር ከክፉ ነገር ሁሉ #ያዳነኝ_መልአክ እነዚህን ብላቴኖች ይባርክ።" ዘፍ 48:15
👉 እሱም ብቻ አይደለም የሰው ልጅ አምላክ በፈጸመለት የማዳን ተግባር ውስጥ የቅዱሳን መላእክት ሱታፌ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው መሆኑን ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ "ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገልገል የሚላኩ የሚያግዙ መናፍስት አይደሉምን?" ብሎ የሰው ልጅ እንዲድን የቅዱሳን መላእክት አገልግሎት እና እገዛ የግድ እንደሚያስፈልገው ተናግሯል። ዕብ 1:14 እንዲሁም የሰው ልጅ የመዳኑ ነገር ለቅዱሳን መልአክት ታላቅ ደስታ መሆኑን ጌታ በወንጌል እንዲህ በማለት ተናግሯል። "እላችኋለሁ እንዲሁ ንስሐ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይሆናል።" ሉቃ 15: 7
👉 ቅዱሳን መልአክት በተጨነቅን እና በተቸገርን ጊዜ በጸሎት ስንጠራቸው መጥተው ያበረቱናል ያረጋጉናል። ጌታችን በመዋለ ሥጋዌው ለእኛ አርአያ አብነት ይሆነን ዘንድ በምሴተ ሐሙስ መከራን ከመቀበሉ በፊት ሲጸልይ "ከሰማይም መጥቶ የሚያበረታው መልአክ ታየው።" ይላል። ሉቃ 22:43 የመልአክት ፈጣሪያቸው እርሱ ሆኖ ሳለ የሚያበረታው መልአክ ታየው መባሉ ስለምንድን ነው ቢሉ እናንተም በጨነቃችሁ በጠበባችሁ መከራ ውስጥ በገባችሁ ጊዜ ብትጸልዩ ቅዱሳን መልአክት እናንተን ለማበርታት ይላካሉ ሲለን ነው።
👉 ቅዱሳን መልአክት ስለ ሰው ልጆች ዘውትር በአምላክ ፊት ያማልዳሉ። እግዚአብሔርም ምልጃቸውን ቸል አይልም። ዘካ 1:12–13 "የእግዚአብሔርም መልአክ መልሶ። አቤቱ፥ የሠራዊት ጌታ ሆይ፥ እነዚህ ሰባ ዓመት የተቈጣሃቸውን ኢየሩሳሌምንና የይሁዳን ከተሞች የማትምራቸው እስከ መቼ ነው? አለ። እግዚአብሔርም መልሶ ከእኔ ጋር ይነጋገር ለነበረው መልአክ በመልካምና በሚያጽናና ቃል ተናገረው።" እንዲል። መልአኩ እግዚአብሔርን አሳዝነው 70 ዓመት ለተቆጡት እስራኤል ዘሥጋ ከለመነ፤ በቅዱሳን መልአክት ለታመንን እስራኤል ዘነፍስ ለሆንን ለኛ እንዴት አይማልዱልንም? እነርሱም ዘውትር በእግዚአብሔር ፊት ይቆማሉ፣ የእግዚአብሔርንም ፊት ያያሉ። ማቴ 18:10 ኢዮ 1:7 ሉቃ 1:9 "የእግዚአብሔር ዐይኖች ወደ ጻድቃን ጆሮቹም ወደ ጩኸታቸው ናቸውና።" እንዲል የቅዱሳን መልአክትንም ምልጃቸውን ይቀበላል። መዝ 33(34):15
በተጨማሪም #ቅዱሳን_መልአክት
👉 አጽናኞቻችን ናቸው። ዳን 10:20
👉 ይረዱናል። ዳን 10:13
👉 ይጠብቁናል። መዝ 90:1
👉 እንሰግድላቸው ዘንድ ይገባል። ኢያ 5:14 ዘፍ 19:1 ራዕ 19:10 ራዕ 22:8
ሰኔ 12 በዚህች ቀን መልአኩ #ቅዱስ_ሚካኤል የተሾመበት፣ ቅድስት አፎምያን ከሰይጣን ያዳነበት፣ የባሕራንን የሞት ደብዳቤ ወደ ህይወት የቀየረበት ዕለት ነው።
ከመልአኩ ከቅዱስ ሚካኤል ረድኤት በረከት ያሳትፈን።
ይቆየን።
አዘጋጅ #አቤኔዘር
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
..............+++++++++++............
እንድትከታተሉት የምንጋብዝዎ መንፈሳዊ ቻናል
ስንክሳር… @senkesar
"የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል #ያድናቸውማል።" መዝ 33:7
👉 ይህን ኃይለ ቃል የተናገረው ልበ አምላክ ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ነው። በግልጽ እንደነገረን የእግዚአብሔር የሆኑት ቅዱሳን መልአክት የሚያድኑ አዳኞች ናቸው። እነርሱን ከሚፈሯቸውና ከሚያምኗቸው ሰዎች አይለዩም። ከሚደርስባቸው መከራ እና ችግር ፈተና ሁሉ ያድኗቸዋል ይታደጓቸዋል። ቅዱሳን መልአክት የሰው ልጆችን የሚያድኑ አዳኞች መሆናቸውን ቅዱስ ያዕቆብ ዮሴፍንና ልጆቹን በባረከ ጊዜም እንዲህ ሲል መስክሯል። "ከታናሽነቴ ጀምሮ እኔን የመገበኝ እግዚአብሔር ከክፉ ነገር ሁሉ #ያዳነኝ_መልአክ እነዚህን ብላቴኖች ይባርክ።" ዘፍ 48:15
👉 እሱም ብቻ አይደለም የሰው ልጅ አምላክ በፈጸመለት የማዳን ተግባር ውስጥ የቅዱሳን መላእክት ሱታፌ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው መሆኑን ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ "ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገልገል የሚላኩ የሚያግዙ መናፍስት አይደሉምን?" ብሎ የሰው ልጅ እንዲድን የቅዱሳን መላእክት አገልግሎት እና እገዛ የግድ እንደሚያስፈልገው ተናግሯል። ዕብ 1:14 እንዲሁም የሰው ልጅ የመዳኑ ነገር ለቅዱሳን መልአክት ታላቅ ደስታ መሆኑን ጌታ በወንጌል እንዲህ በማለት ተናግሯል። "እላችኋለሁ እንዲሁ ንስሐ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይሆናል።" ሉቃ 15: 7
👉 ቅዱሳን መልአክት በተጨነቅን እና በተቸገርን ጊዜ በጸሎት ስንጠራቸው መጥተው ያበረቱናል ያረጋጉናል። ጌታችን በመዋለ ሥጋዌው ለእኛ አርአያ አብነት ይሆነን ዘንድ በምሴተ ሐሙስ መከራን ከመቀበሉ በፊት ሲጸልይ "ከሰማይም መጥቶ የሚያበረታው መልአክ ታየው።" ይላል። ሉቃ 22:43 የመልአክት ፈጣሪያቸው እርሱ ሆኖ ሳለ የሚያበረታው መልአክ ታየው መባሉ ስለምንድን ነው ቢሉ እናንተም በጨነቃችሁ በጠበባችሁ መከራ ውስጥ በገባችሁ ጊዜ ብትጸልዩ ቅዱሳን መልአክት እናንተን ለማበርታት ይላካሉ ሲለን ነው።
👉 ቅዱሳን መልአክት ስለ ሰው ልጆች ዘውትር በአምላክ ፊት ያማልዳሉ። እግዚአብሔርም ምልጃቸውን ቸል አይልም። ዘካ 1:12–13 "የእግዚአብሔርም መልአክ መልሶ። አቤቱ፥ የሠራዊት ጌታ ሆይ፥ እነዚህ ሰባ ዓመት የተቈጣሃቸውን ኢየሩሳሌምንና የይሁዳን ከተሞች የማትምራቸው እስከ መቼ ነው? አለ። እግዚአብሔርም መልሶ ከእኔ ጋር ይነጋገር ለነበረው መልአክ በመልካምና በሚያጽናና ቃል ተናገረው።" እንዲል። መልአኩ እግዚአብሔርን አሳዝነው 70 ዓመት ለተቆጡት እስራኤል ዘሥጋ ከለመነ፤ በቅዱሳን መልአክት ለታመንን እስራኤል ዘነፍስ ለሆንን ለኛ እንዴት አይማልዱልንም? እነርሱም ዘውትር በእግዚአብሔር ፊት ይቆማሉ፣ የእግዚአብሔርንም ፊት ያያሉ። ማቴ 18:10 ኢዮ 1:7 ሉቃ 1:9 "የእግዚአብሔር ዐይኖች ወደ ጻድቃን ጆሮቹም ወደ ጩኸታቸው ናቸውና።" እንዲል የቅዱሳን መልአክትንም ምልጃቸውን ይቀበላል። መዝ 33(34):15
በተጨማሪም #ቅዱሳን_መልአክት
👉 አጽናኞቻችን ናቸው። ዳን 10:20
👉 ይረዱናል። ዳን 10:13
👉 ይጠብቁናል። መዝ 90:1
👉 እንሰግድላቸው ዘንድ ይገባል። ኢያ 5:14 ዘፍ 19:1 ራዕ 19:10 ራዕ 22:8
ሰኔ 12 በዚህች ቀን መልአኩ #ቅዱስ_ሚካኤል የተሾመበት፣ ቅድስት አፎምያን ከሰይጣን ያዳነበት፣ የባሕራንን የሞት ደብዳቤ ወደ ህይወት የቀየረበት ዕለት ነው።
ከመልአኩ ከቅዱስ ሚካኤል ረድኤት በረከት ያሳትፈን።
ይቆየን።
አዘጋጅ #አቤኔዘር
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
..............+++++++++++............
እንድትከታተሉት የምንጋብዝዎ መንፈሳዊ ቻናል
ስንክሳር… @senkesar
💚💛ተአምረ ቅዱስ ሚካኤል💛❤️
ቅዱስ መጽሐፍ እንደ ነገረን በዚህች ዕለት የመላእክት ሁሉ አለቃቸው: የቅዱሳንም ረዳታቸው የሆነው ደጉ መልአክ #ቅዱስ_ሚካኤል ንጉሡን ሕዝቅያስን ግሩም.በሆነ ተአምር ከከተማው #ኢየሩሳሌም ጋር ታድጐታል:: ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
ከመድኃኒታችን #ክርስቶስ ልደት 700 ዓመታት በፊት #ሕዝቅያስ የሚባል ንጉሥ በይሁዳ ላይ ነግሦ ነበር:: ደጋጉ #ዳዊትና #ሰሎሞን ካረፉ በሁዋላ የሕዝቅያስን ያክል ቅን እና የእግዚአብሔር ሰው በእሥራኤል ላይ አልነገሰም:: ንጉሡ ጣዖት አምልኮን ነቃቅሎ አጥፍቶ ሕዝቡ እግዚአብሔርን ብቻ እንዲያመልክ አድርጐም ነበር::
ነገር ግን ቅዱስ ሕዝቅያስ በነገሠ በ14ኛው ዓመት የአሕዛብ (የአሦር) ንጉሥ ሰናክሬም በጠላትነት ተነሳበት:: ወደ አካባቢውም መጥቶ: ከቦ አስጨነቀው:: ሰናክሬም በጦር እጅግ ኃይለኛ ነበር:: በዚያውም ላይ ጦር የሚመዙ ከ185,000 በላይ ብርቱ ተዋጊዎች ነበሩትና ሕዝቅያስ እንደማይችለው ተረድቶ መልእክተኛ ላከበት::
"እገብርልሃለሁ:: የፈለግከውንም እሰጥሃለሁ:: ሃገሬን ግን አታጥፋ:: ኢየሩሳሌምን አታቃጥል:: ሕዝቤንም
አትግደል" በሚል ለመነው:: እጅ መንሻ ግብሩንም ከከተማዋ የተገኘውን ወርቅና ብር ሁሉ ጭኖ ላከለት::
ሰናክሬም ግን ሰይጣን ያደረበት ነውና የሕዝቅያስን ልመና ወደ ጐን ብሎ የእሥራኤልን አምላክ : ቅዱስ ስሙንም ተገዳደረ:: ለሕዝቅያስም "ከእኔ እጅ የሚያድንህ ማነው? ሕዝቡንም #እግዚአብሔር ያድናል ብለህ አታታልላቸው" ሲል ላከበት:: ቅዱስ ሕዝቅያስ በዚህ ጊዜ የፈጣሪው ስም ሲቃለል ሰምቷልና ፈጽሞ አዘነ::
መልእክተኞችን ወደ ነቢዩ #ቅዱስ_ኢሳይያስ ልኮ እርሱ ወደ ቤተ መቅደስ ገባ:: በእግዚአብሔር ፊት ልብሱን ቀድዶ ማቅ ለበሰ:: ስለ ኢየሩሳሌምና ሕዝቡም ፈጽሞ አለቀሰ:: በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር የሰናክሬምን
መገዳደርና የሕዝቅያስን ልመና ሰምቷልና በኢሳይያስ አንደበት እንዲሕ አለ:- "ስለ ባሪያየ ስለ #ዳዊት ከተማዋን አድናታለሁ::"
በዚያች ሌሊትም ድንቅ መልአክ #ቅዱስ_ሚካኤል ከሰማያት በግርማ ወረደ:: ወደ ሰናክሬም የጦር ሠፈር ደርሶ አንድ ጊዜ የእሳት ሰይፉን መዝዞ ቢያሳያቸው ከአሕዛብ ሠራዊት 185 ሺ ኃያላን እንደ ቅጠል ረገፉ:: በለኪሶ የነበረው ሰናክሬም በጧት ቢነሳ ሠራዊቱ ሁሉ ወደ አስከሬን ክምር ተቀይሯል::
በድንጋጤ ወደ #ነነዌ ሒዶ ወደ ጣዖት ቤቱ ሲገባ የራሱ ልጆች (አድራማሌክና ሳራሳር) ገደሉት:: ትዕቢተኛው ሰናክሬም ለአሕዛብ ሁሉ መዘባበቻ ሆነ:: ቅዱስ ሕዝቅያስ ግን በፈጣሪው ታምኗልና ቅዱስ ሚካኤል ሞገስ ሆኖ የዓለም ነገሥታት ሁሉ ፈሩት:: (1ነገ. 18:13, 19:1)
From:- d/n yordanos abebe
@senkesar @senkesar
ቅዱስ መጽሐፍ እንደ ነገረን በዚህች ዕለት የመላእክት ሁሉ አለቃቸው: የቅዱሳንም ረዳታቸው የሆነው ደጉ መልአክ #ቅዱስ_ሚካኤል ንጉሡን ሕዝቅያስን ግሩም.በሆነ ተአምር ከከተማው #ኢየሩሳሌም ጋር ታድጐታል:: ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
ከመድኃኒታችን #ክርስቶስ ልደት 700 ዓመታት በፊት #ሕዝቅያስ የሚባል ንጉሥ በይሁዳ ላይ ነግሦ ነበር:: ደጋጉ #ዳዊትና #ሰሎሞን ካረፉ በሁዋላ የሕዝቅያስን ያክል ቅን እና የእግዚአብሔር ሰው በእሥራኤል ላይ አልነገሰም:: ንጉሡ ጣዖት አምልኮን ነቃቅሎ አጥፍቶ ሕዝቡ እግዚአብሔርን ብቻ እንዲያመልክ አድርጐም ነበር::
ነገር ግን ቅዱስ ሕዝቅያስ በነገሠ በ14ኛው ዓመት የአሕዛብ (የአሦር) ንጉሥ ሰናክሬም በጠላትነት ተነሳበት:: ወደ አካባቢውም መጥቶ: ከቦ አስጨነቀው:: ሰናክሬም በጦር እጅግ ኃይለኛ ነበር:: በዚያውም ላይ ጦር የሚመዙ ከ185,000 በላይ ብርቱ ተዋጊዎች ነበሩትና ሕዝቅያስ እንደማይችለው ተረድቶ መልእክተኛ ላከበት::
"እገብርልሃለሁ:: የፈለግከውንም እሰጥሃለሁ:: ሃገሬን ግን አታጥፋ:: ኢየሩሳሌምን አታቃጥል:: ሕዝቤንም
አትግደል" በሚል ለመነው:: እጅ መንሻ ግብሩንም ከከተማዋ የተገኘውን ወርቅና ብር ሁሉ ጭኖ ላከለት::
ሰናክሬም ግን ሰይጣን ያደረበት ነውና የሕዝቅያስን ልመና ወደ ጐን ብሎ የእሥራኤልን አምላክ : ቅዱስ ስሙንም ተገዳደረ:: ለሕዝቅያስም "ከእኔ እጅ የሚያድንህ ማነው? ሕዝቡንም #እግዚአብሔር ያድናል ብለህ አታታልላቸው" ሲል ላከበት:: ቅዱስ ሕዝቅያስ በዚህ ጊዜ የፈጣሪው ስም ሲቃለል ሰምቷልና ፈጽሞ አዘነ::
መልእክተኞችን ወደ ነቢዩ #ቅዱስ_ኢሳይያስ ልኮ እርሱ ወደ ቤተ መቅደስ ገባ:: በእግዚአብሔር ፊት ልብሱን ቀድዶ ማቅ ለበሰ:: ስለ ኢየሩሳሌምና ሕዝቡም ፈጽሞ አለቀሰ:: በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር የሰናክሬምን
መገዳደርና የሕዝቅያስን ልመና ሰምቷልና በኢሳይያስ አንደበት እንዲሕ አለ:- "ስለ ባሪያየ ስለ #ዳዊት ከተማዋን አድናታለሁ::"
በዚያች ሌሊትም ድንቅ መልአክ #ቅዱስ_ሚካኤል ከሰማያት በግርማ ወረደ:: ወደ ሰናክሬም የጦር ሠፈር ደርሶ አንድ ጊዜ የእሳት ሰይፉን መዝዞ ቢያሳያቸው ከአሕዛብ ሠራዊት 185 ሺ ኃያላን እንደ ቅጠል ረገፉ:: በለኪሶ የነበረው ሰናክሬም በጧት ቢነሳ ሠራዊቱ ሁሉ ወደ አስከሬን ክምር ተቀይሯል::
በድንጋጤ ወደ #ነነዌ ሒዶ ወደ ጣዖት ቤቱ ሲገባ የራሱ ልጆች (አድራማሌክና ሳራሳር) ገደሉት:: ትዕቢተኛው ሰናክሬም ለአሕዛብ ሁሉ መዘባበቻ ሆነ:: ቅዱስ ሕዝቅያስ ግን በፈጣሪው ታምኗልና ቅዱስ ሚካኤል ሞገስ ሆኖ የዓለም ነገሥታት ሁሉ ፈሩት:: (1ነገ. 18:13, 19:1)
From:- d/n yordanos abebe
@senkesar @senkesar