#እግዚአብሔር_መፅናናትን_እንዲያበዛላችሁ_ፀሎታችን_ነዉ።
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል በመካኒሳ መካነ ኢየሱስ ሴሚናሪ እና በአከባቢዉ ማህበረሰብ ላይ በደረሰዉ የጎርፍ አደጋ በህይወት እና በንብረት ላይ ስለደረሰው ጉዳት እጅግ ማዘናችንን እንገልጻለን።
በትላንትናው እለት በጣለው ከፍተኛ በረዶ የቀላቀለ ዝናብ ህይወታቸውን ላጡ እና ንብረቶቻቸው ለወደመባቸው አካላት ካውንስሉ መጽናናትን ይመኛል።
ስለሆነም ሁላችሁም የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል አባላት ቤተእምነቶች፤ ሚኒስትሪዎች እና አገልጋዮች በሙሉ ከሴሚናሪው እና ጉዳት ከደረሰባቸው አካላት ጉን በጸሎታችሁ እና ልዩ ልዩ ድጋፍ በማድረግ አብራችሁ እንድትቆሙ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
ለኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ እና ለተጎጂ ቤተሰቦች እግዚአብሔር መፅናናትን እንዲያበዛላችሁ ፀሎታችን ነዉ።
1 ተሰ. 4፥13-18
ቄስ ደረጀ ጀምበሩ
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካዉንስል ጠቅላይ ፀሐፊ
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል በመካኒሳ መካነ ኢየሱስ ሴሚናሪ እና በአከባቢዉ ማህበረሰብ ላይ በደረሰዉ የጎርፍ አደጋ በህይወት እና በንብረት ላይ ስለደረሰው ጉዳት እጅግ ማዘናችንን እንገልጻለን።
በትላንትናው እለት በጣለው ከፍተኛ በረዶ የቀላቀለ ዝናብ ህይወታቸውን ላጡ እና ንብረቶቻቸው ለወደመባቸው አካላት ካውንስሉ መጽናናትን ይመኛል።
ስለሆነም ሁላችሁም የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል አባላት ቤተእምነቶች፤ ሚኒስትሪዎች እና አገልጋዮች በሙሉ ከሴሚናሪው እና ጉዳት ከደረሰባቸው አካላት ጉን በጸሎታችሁ እና ልዩ ልዩ ድጋፍ በማድረግ አብራችሁ እንድትቆሙ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
ለኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ እና ለተጎጂ ቤተሰቦች እግዚአብሔር መፅናናትን እንዲያበዛላችሁ ፀሎታችን ነዉ።
1 ተሰ. 4፥13-18
ቄስ ደረጀ ጀምበሩ
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካዉንስል ጠቅላይ ፀሐፊ