የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC
9.68K subscribers
9.58K photos
133 videos
1 file
1.55K links
ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው።

"ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።
Download Telegram
በቀጣና ሁለት ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን “የተዘጋጀ ትውልድ” በሚል መሪ ቃል በሊደርሺፕ ትራንስፎሜሽን ሚኒስትሪ ከተለያዩ ቤተ ክርስቲያን ለተወጣጡ ወጣት መሪዎች ሴሚናሪ ተካሄደ።

በቀጠና ሁለት ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ቤተ ክርስቲያን “አንድ የተዘጋጀ ትውልድ” በሚል መሪ ቃል በሊደርሺፕ ትራንስፎርሜሽን ሚኒስትሪ ከተለያዩ ቤተ ክርስቲያናት ለተወጣጡ ወጣት መሪዎች ሴሚናሪ ተካሂዷል።

የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት መጋቢ ዳንኤል ሲሆኑ እንዲሁም በእለቱ ወጣትነት እግዚአብሔር ለሀገር እና ለቤተ ክርስቲያን ለለውጥ እና ለተሃድሶ ጠቃሚ እንደሆነ ተናግረው የወጣትነት ጊዜ በምን አይነት መንገድ መያዝ እንዳለበት አስተምረዋል።

መጋቢ ዳንኤል ወጣትነት በሰዎች እድሜ ውስጥ ወርቃማ የእድሜ ክልል እንደመሆኑ ወጣትነትን በሚገባ ለመጠቀም እና የእግዚአብሔርን ቃል ለማወቅ መትጋት ያስፈልጋል ሲሉም ተናግረዋል።

ቄስ ትዕግስቱ መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ 1 ላይ ከሚገኘው ክፍል ላይ በመነሳት ወጣቶች እንዴት ራሳቸውን ከሀጥያት ማራቅ እንዳለባቸው አስተምረዋል።

በከሰዓቱ ፕሮግራምም ላይ ወንድም ለማ ደገፋ ጥሪ ፣ ብቃት ፣ ስብዕና እና ተግባራት በተሰኙ በተለያዩ ርዕሶች ላይ ትምርህትን ሰጥተዋል።

ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቃልኪዳን እንዳለ