“መጽሐፍ ቅዱሳዊ አመራር” “Biblical Leadership” በሚል ስያሜ 3ኛ ዙር የሥልጠና መርሐ ግብር ተጀመረ
በኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር እና በእንግሊዝ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር ትብብር ተግባራዊ እየተደረገ ባለው ፕሮጀክት የተዘጋጀው ሦስተኛው ዙር የሥልጠና መርሐ ግብር ተጀመረ።
በስልጠናው ላይ ቁጥራቸው ከ50 በላይ የሆኑ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፥ ከሕግ ባለሙያዎች፥ ከከፍተኛ ትምህር ተቋማት፥ ከህክምና ሙያ ዘርፍ፥ ከምህንድስና ሙያ ዘርፍ እና ከተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት የተውጣጡ መሪዎችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛል።
እኤአ 2023 ዓ.ም ጀምሮ በልዩ ሁኔታ ተዋቅሮ እየተሰጠ ያለው ይህ ስልጠና “Catalyzing Leaders” በሚል ርዕስ የሚካሄድ ሲሆን ዓላማውም በተለያየ ደረጃ እና ሙያ ላይ የሚገኙ መሪዎች መጽሐፍ ቅዱሳዊ እሴቶችን በመጠቀም ለተሻለና ውጤታማ መሪ እንዲሆኑ መደገፍ ለዚህም መጽሐፍ ቅዱሳዊ እሴቶችን በግብአትነት እንዲጠቀሙ ማበረታታት መሆኑ ተግልጾዋል።
በስልጠናው ላይ ዓለም አቀፍ እውቅና ያለቸው መምህራንና የምርምር ባለሙያዎች በአሰልጣኝነት እየተሳተፉ ይገኛል።
መረጃው የኢትዮጵያ መጽሃፍ ቅዱስ ማህበር ነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፤ ቤተልሔም ደረጄ
በኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር እና በእንግሊዝ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር ትብብር ተግባራዊ እየተደረገ ባለው ፕሮጀክት የተዘጋጀው ሦስተኛው ዙር የሥልጠና መርሐ ግብር ተጀመረ።
በስልጠናው ላይ ቁጥራቸው ከ50 በላይ የሆኑ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፥ ከሕግ ባለሙያዎች፥ ከከፍተኛ ትምህር ተቋማት፥ ከህክምና ሙያ ዘርፍ፥ ከምህንድስና ሙያ ዘርፍ እና ከተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት የተውጣጡ መሪዎችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛል።
እኤአ 2023 ዓ.ም ጀምሮ በልዩ ሁኔታ ተዋቅሮ እየተሰጠ ያለው ይህ ስልጠና “Catalyzing Leaders” በሚል ርዕስ የሚካሄድ ሲሆን ዓላማውም በተለያየ ደረጃ እና ሙያ ላይ የሚገኙ መሪዎች መጽሐፍ ቅዱሳዊ እሴቶችን በመጠቀም ለተሻለና ውጤታማ መሪ እንዲሆኑ መደገፍ ለዚህም መጽሐፍ ቅዱሳዊ እሴቶችን በግብአትነት እንዲጠቀሙ ማበረታታት መሆኑ ተግልጾዋል።
በስልጠናው ላይ ዓለም አቀፍ እውቅና ያለቸው መምህራንና የምርምር ባለሙያዎች በአሰልጣኝነት እየተሳተፉ ይገኛል።
መረጃው የኢትዮጵያ መጽሃፍ ቅዱስ ማህበር ነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፤ ቤተልሔም ደረጄ
❤12🙏3🔥2
የኢትዯጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ከኦርጋኒክ ቸርች ፕላንቲንግ ሚኒስትሪ (Organic Church Planting Ministry) ጋር በመተባበር ለ53 አገልጋይ ሴቶች የአሰልጣኞች ስልጠና ሰጠ።
" መንፈሳዊ ጉዞን መገምገምና ወደ ክርስቶስ ማደግ፣ደቀመዛሙርትንም ማፍራት በሚል ርዕስ" ሐምሌ 17 2017 ዓ.ም. በጉዲና ቱምሳ ማሰልጠኛ ተቋም ስልጠናው የተሰጠ ሲሆን መንፈሳዊ ህይወትን ለመመዘን መሰረታዊ የሆኑ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መርሆዎችን መረዳት፣ ክርስቶስን ማእከል ያደረገ ህይወት የመኖር አስፈላጊነት እንዲሁም የታላቁ ተልዕኮን ሀላፊነት መወጣትና ደቀመዛሙርትን ማፍራት የአገልግሎት መርህ በስልጠናው የተዳሰሱ ሀሳቦች ነበሩ።
ስልጠናውን የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል የሴቶች አገልግሎት ኮሚቴ ያስተባበረ ሲሆን የኮሚቴው ሰብሳቢ ቄስ ፀጋነሽ አየለና ምክትል ሰብሳቢ መምህር ቀለሟ ተፈራ ስልጠናውን ሰጥተዋል። ዶ/ር ገዙ ሞሲሳ የኦርጋኒክ ቸርች ፕላንቲንግ ሚኒስትሪ ዳይሬክተር የእግዚአብሔርን ቃል በማካፈል የሚኒስትሪውን አላማ ያስረዱ ሲሆን መጋቢ ሮማን ሳሙኤል በዝማሬ አገልግለዋል።
የስልጠናው ተሳታፊ አገልጋይ ሴቶች ከቤተሰብ ጀምሮ ባሉበት ቤተእምነትና ማህበረሰብ ክርስቶስን በሚያሳይ የተለወጠ ማንነት እንዲኖሩ እንዲሁም ወንጌልን በመስበክና ደቀመዛሙርትን በማፍራት ጥሪያቸውን እንዲፈጽሙ ከሌሎች አገልጋይ ሴቶች ልምድን እንዲቀስሙ ያደረገ ስልጠና መሆኑን ተናግረዋል።
አክለውም ይህንን በመተግበር ለሌሎች መልካም ምሳሌ በመሆን እንደሚተጉ ተናግረው፤ ይህን መሰል የልምድ ልውውጥና የስልጠና መርሃ ግብር በካውንስሉ የሴቶች አገልግሎት ኮሚቴ በመዘጋጀቱ አመስግነዋል።
መረጃውን ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል መንፈሳዊ ዘርፍ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
" መንፈሳዊ ጉዞን መገምገምና ወደ ክርስቶስ ማደግ፣ደቀመዛሙርትንም ማፍራት በሚል ርዕስ" ሐምሌ 17 2017 ዓ.ም. በጉዲና ቱምሳ ማሰልጠኛ ተቋም ስልጠናው የተሰጠ ሲሆን መንፈሳዊ ህይወትን ለመመዘን መሰረታዊ የሆኑ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መርሆዎችን መረዳት፣ ክርስቶስን ማእከል ያደረገ ህይወት የመኖር አስፈላጊነት እንዲሁም የታላቁ ተልዕኮን ሀላፊነት መወጣትና ደቀመዛሙርትን ማፍራት የአገልግሎት መርህ በስልጠናው የተዳሰሱ ሀሳቦች ነበሩ።
ስልጠናውን የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል የሴቶች አገልግሎት ኮሚቴ ያስተባበረ ሲሆን የኮሚቴው ሰብሳቢ ቄስ ፀጋነሽ አየለና ምክትል ሰብሳቢ መምህር ቀለሟ ተፈራ ስልጠናውን ሰጥተዋል። ዶ/ር ገዙ ሞሲሳ የኦርጋኒክ ቸርች ፕላንቲንግ ሚኒስትሪ ዳይሬክተር የእግዚአብሔርን ቃል በማካፈል የሚኒስትሪውን አላማ ያስረዱ ሲሆን መጋቢ ሮማን ሳሙኤል በዝማሬ አገልግለዋል።
የስልጠናው ተሳታፊ አገልጋይ ሴቶች ከቤተሰብ ጀምሮ ባሉበት ቤተእምነትና ማህበረሰብ ክርስቶስን በሚያሳይ የተለወጠ ማንነት እንዲኖሩ እንዲሁም ወንጌልን በመስበክና ደቀመዛሙርትን በማፍራት ጥሪያቸውን እንዲፈጽሙ ከሌሎች አገልጋይ ሴቶች ልምድን እንዲቀስሙ ያደረገ ስልጠና መሆኑን ተናግረዋል።
አክለውም ይህንን በመተግበር ለሌሎች መልካም ምሳሌ በመሆን እንደሚተጉ ተናግረው፤ ይህን መሰል የልምድ ልውውጥና የስልጠና መርሃ ግብር በካውንስሉ የሴቶች አገልግሎት ኮሚቴ በመዘጋጀቱ አመስግነዋል።
መረጃውን ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል መንፈሳዊ ዘርፍ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከኖርዌይ ቤተ ክርስቲያን የእርዳታ ድርጅት ጋር በመተባበር በበጀት ዓመቱ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን በዋናነትም ያለድሜ ጋብቻ እና የሴት ልጅ ግርዛትን ከመከላከል አንፃር የተሰሩ ሥራዎችን የሚገመግም የምክክር መድረክ በጽሕፈት ቤቱ አካሄደ፡፡
ሐምሌ 17 ቀን 2017 ዓ/ም የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የሴቶች ወጣቶች እና ሕፃናት መመሪያ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ጥሩወርቅ የዕቅድ አፈፃጸም የምክክር መድረክ ዓላማ አስመልክተው ማብራርያ ሰጥተዋል፡፡
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በገባው ስምምነት መሰረት እንዲሁም ካለበት ሃገራዊ እና ሃይማኖታዊ ኃላፊነት አንፃር ከሰላም ግንባታ ሥራው ጎን ለጎን የሴት ልጅ ግርዛት እና ያለዕድሜ ጋብቻ ከመከላከል አንፃር የተሰሩትን ዋና ዋና ሥራዎችን፣ የተገኙ ውጤቶችን እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን ለመድረኩ ተሳታፊዎች አካፍለዋል፡፡
በመቀጠልም የአባል የሃይማኖት ተቋማት ርዕሰ ጉዳዩ የሚመለከታቸው የሥራ ክፍል ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች እንዲሁም የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የሴቶች፣ ወጣቶች እና ሕፃናት መመሪያ ኃላፊ በበጀት ዓመቱ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ከመከላከል አንፃር የሰሯቸውን ሥራዎች በዝርዝር በማቅረብ አንዳቸው ከአንዳቸው ልምድ እና የእርስ በእርስ ትምህርት መውሰድ የሚያስችላቸውን እድል መፍጠር መቻሉ ተገልጿል፡፡
በመጨረሻም በቀረቡት የሥራ አፈፃጸም ሪፖርቶች ላይ ሰፊ ምክክር ከተደረገ እና አስተያየት ከተሰጠ በኋላ በቀጣይ ከዚህ የተሻለ የተቀናጀ ሥራ በመሥራት የተሻለ ወጤት ማስመዝገብ እንደሚያስፈልግ በመግባባት የዕለቱ መድረክ የዕቅድ አፈፃጸም የምክክር መድረክ በታቀደው ዕቅድ መሰረት በስኬት መፈጸሙ ተገልጿል፡፡
መረጃው የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ነው፡፡
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
ሐምሌ 17 ቀን 2017 ዓ/ም የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የሴቶች ወጣቶች እና ሕፃናት መመሪያ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ጥሩወርቅ የዕቅድ አፈፃጸም የምክክር መድረክ ዓላማ አስመልክተው ማብራርያ ሰጥተዋል፡፡
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በገባው ስምምነት መሰረት እንዲሁም ካለበት ሃገራዊ እና ሃይማኖታዊ ኃላፊነት አንፃር ከሰላም ግንባታ ሥራው ጎን ለጎን የሴት ልጅ ግርዛት እና ያለዕድሜ ጋብቻ ከመከላከል አንፃር የተሰሩትን ዋና ዋና ሥራዎችን፣ የተገኙ ውጤቶችን እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን ለመድረኩ ተሳታፊዎች አካፍለዋል፡፡
በመቀጠልም የአባል የሃይማኖት ተቋማት ርዕሰ ጉዳዩ የሚመለከታቸው የሥራ ክፍል ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች እንዲሁም የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የሴቶች፣ ወጣቶች እና ሕፃናት መመሪያ ኃላፊ በበጀት ዓመቱ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ከመከላከል አንፃር የሰሯቸውን ሥራዎች በዝርዝር በማቅረብ አንዳቸው ከአንዳቸው ልምድ እና የእርስ በእርስ ትምህርት መውሰድ የሚያስችላቸውን እድል መፍጠር መቻሉ ተገልጿል፡፡
በመጨረሻም በቀረቡት የሥራ አፈፃጸም ሪፖርቶች ላይ ሰፊ ምክክር ከተደረገ እና አስተያየት ከተሰጠ በኋላ በቀጣይ ከዚህ የተሻለ የተቀናጀ ሥራ በመሥራት የተሻለ ወጤት ማስመዝገብ እንደሚያስፈልግ በመግባባት የዕለቱ መድረክ የዕቅድ አፈፃጸም የምክክር መድረክ በታቀደው ዕቅድ መሰረት በስኬት መፈጸሙ ተገልጿል፡፡
መረጃው የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ነው፡፡
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
❤1