የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC
9.69K subscribers
9.51K photos
133 videos
1 file
1.55K links
ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው።

"ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።
Download Telegram
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በአለም አቀፉ የሚሽን ማህበር ጉባኤ ላይ የእውቅና ሽልማት አገኘች።

በመካከለኛው አሜሪካ ሁንዱራስ እየተካሄደ በሚገኘውና ሁለተኛ ሳምንቱን በያዘው የአለም አቀፍ ሚሽን ማህበር (IMA) ጉባኤ እየተሳተፈች የምትገኘው የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በመድረኩ በወንጌል ተልዕኮ እያከናወነች ላለው እንቅስቃሴና ከአሞር ቪንቪንቴ ቤተክርስቲያን ጋር ላላት አጋርነት የእውቅና ሽልማት ተበርክቶላታል።

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን በመወከል በስፍራው የሚገኙት የቤተክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ ሽልማቱን ሲቀበሉ "ይህ እውቅና ክርስቶስን ለመስበክ እና መንግስቱን በማህበረሰቦች መካከል ለመገንባት ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያሳይ ግሩም ማስታወሻ ነው።" ሲሉ ገልጸዋል። ፕሬዚዳንቱ አክለውም አለም አቀፉ የሚሽን ማህበር ለወንጌል ስራ እንድንነቃቃ እያደረገ ስላለው አስተዋጽኦ አመሰግናለሁ ብለዋል።

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በተለያየ አለም የሚገኙ አብያተክርስቲያናት በተካተቱበት አለም አቀፍ የሚሽን ማህበር (IMA) መስራች አባል መሆኗ ይታወቃል።
መረጃው የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
3👍1