የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን የደቡብ ምስራቅ አዲስ አበባና አካባቢው ክልል ጠቅላላ ጉባኤ በጾም ጸሎት ተጀመረ።
ነሐሴ አርብ 2/2017 ዓ.ም በ 22 ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን የደቡብ ምስራቅ አዲስ አበባና አካባቢው ክልል ጠቅላላ ጉባኤ በጾም ጸሎት ተጀምሯል።
የቀጠና ሁለት ሙሉ ወንጌል አጥቢያ B ኳየር በዝማሬ በማገልገል ጉባኤው እግዚአብሔርን አምልኮአል።
በመቀጠል በቤተ እምነቱ የቦርድ ስራ አስፈጻሚ ሰብስቢ በመጋቢ ተመስገን አዋኖ ከሐዋሪያት ስራ ምዕራፍ 20 ከቁጥር 1 እስከ 25 ካለው ክፍል "የሐዋርያው ጳውሎስ ሕይወትና አገልግሎት " በሚል ርዕስ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት ለጉባኤው አቅርበዋል።
በጾም ጸሎቱ እግዚአብሔር ያለፈውን በጀት አመት በብዙ ፀጋ ክልሉን ስለረዳ በማመስገን ቀጣይን አመት ለጌታ አደራ በመስጠት ፣ እግዚአብሔር ምድራችን ሰላም እንዲያደርጋት ጸሎት ተካሂዷል።
ጌታ መልካም የጸሎት ጊዜ እንደሰጣቸው አዘጋጆቹ መግለጻቸውንም ቤተ ክርስቲያኒቱ በፌስቡክ ገጿ ላይ አስፍራለች።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
ነሐሴ አርብ 2/2017 ዓ.ም በ 22 ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን የደቡብ ምስራቅ አዲስ አበባና አካባቢው ክልል ጠቅላላ ጉባኤ በጾም ጸሎት ተጀምሯል።
የቀጠና ሁለት ሙሉ ወንጌል አጥቢያ B ኳየር በዝማሬ በማገልገል ጉባኤው እግዚአብሔርን አምልኮአል።
በመቀጠል በቤተ እምነቱ የቦርድ ስራ አስፈጻሚ ሰብስቢ በመጋቢ ተመስገን አዋኖ ከሐዋሪያት ስራ ምዕራፍ 20 ከቁጥር 1 እስከ 25 ካለው ክፍል "የሐዋርያው ጳውሎስ ሕይወትና አገልግሎት " በሚል ርዕስ የእግዚአብሔር ቃል መልዕክት ለጉባኤው አቅርበዋል።
በጾም ጸሎቱ እግዚአብሔር ያለፈውን በጀት አመት በብዙ ፀጋ ክልሉን ስለረዳ በማመስገን ቀጣይን አመት ለጌታ አደራ በመስጠት ፣ እግዚአብሔር ምድራችን ሰላም እንዲያደርጋት ጸሎት ተካሂዷል።
ጌታ መልካም የጸሎት ጊዜ እንደሰጣቸው አዘጋጆቹ መግለጻቸውንም ቤተ ክርስቲያኒቱ በፌስቡክ ገጿ ላይ አስፍራለች።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
❤1
በፓኪስታን በክርስቲያን ልጆች ላይ እየደረሰ የሚገኘው ጥቃት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሻቀበ መምጣቱ ተገለጸ።
በባኪስታን የልጆች መብት ኮሚሽን ያወጣው አዲስ ሪፖርት ክርስቲያኖችን ጨምሮ በተለያዩ አናሳ ማህበረሰቦች ውስጥ የሚገኙ ልጆች ከፍተኛ ለሆነ ጥቃት እየተጋለጡ እንደሆነ ያስነብባል። ሪፖርቱ ከፍተኛውን ጥቃት ያስተናግዳሉ ያላቸው ደግሞ የክርስቲያን ቤተሰቦችን ልጆች ነው። ሪፖርቱ በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በክርስቲያን ልጆች ላይ የደረሱ ጥቃቶችን የሚያነሳ ሲሆን ከእነዛም ውስጥ አስገድዶ እምነት ማስቀየር ፣ ያለአቻ ጋብቻ እና የጉልበት ብዝበዛ ተጠቀሰዋል።
ኮሚሽኑ ከፈረንጆቹ 2023 እስከ 2024 ደረስ የልጆች መታገትን ፣ግድያን እና ያለአቻ ጋብቻን አስመልክቶ 27 አቤቱታዎች ቀርበውለታል። እናም ጥቃት ከደረሱባቸው ልጆች መካከል 547 የሚሆኑት ልጆች የሚገኙባት የፑንጃብ ግዛት በሀገሪቱ ከሚደርሱ ጥቃቶች ውስጥ 40 በመቶ የሚሆነውን ትይዛለች።
የተደረገው ጥናትም የሃይማኖት አካታችነት የማይስተዋልበትን የፓኪስታንን አንድ ወጥ ሀገራዊ የትምህርት ካሪኩለም ነቅፏል። በሀገሪቱ የሚገኙ ክርስቲያኖች የማይከተሉትን ሃይማኖት በትምህርት ቤት እንዲያጠኑ እና እንዲማሩ መገደዳቸው የሃይማኖት ነጻነት ከመግታት ባለፈ የትምህርት ውጤት እንደሚጎዳ እና በማህበረሰብ ውስጥ መገለልን እንደሚያስከትል ተጠቅሷል።
የሃይማኖት መሪዎች እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች የፓኪስታን መንግስት አነስተኛ ቁጥር ላላቸው ማህበርሰቦች ሕጋዊ ጥበቃ እንዲያደርግ ፣ የትምህርት ፖሊሲዎችን እንዲያሻሽል እና ተቋማዊ ዝንፈቶችን እንዲያስተካከል ጥሪ እያቀረቡ ይገኛሉ።
መረጃውን ከክርስቲያን ፖስት አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
በባኪስታን የልጆች መብት ኮሚሽን ያወጣው አዲስ ሪፖርት ክርስቲያኖችን ጨምሮ በተለያዩ አናሳ ማህበረሰቦች ውስጥ የሚገኙ ልጆች ከፍተኛ ለሆነ ጥቃት እየተጋለጡ እንደሆነ ያስነብባል። ሪፖርቱ ከፍተኛውን ጥቃት ያስተናግዳሉ ያላቸው ደግሞ የክርስቲያን ቤተሰቦችን ልጆች ነው። ሪፖርቱ በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በክርስቲያን ልጆች ላይ የደረሱ ጥቃቶችን የሚያነሳ ሲሆን ከእነዛም ውስጥ አስገድዶ እምነት ማስቀየር ፣ ያለአቻ ጋብቻ እና የጉልበት ብዝበዛ ተጠቀሰዋል።
ኮሚሽኑ ከፈረንጆቹ 2023 እስከ 2024 ደረስ የልጆች መታገትን ፣ግድያን እና ያለአቻ ጋብቻን አስመልክቶ 27 አቤቱታዎች ቀርበውለታል። እናም ጥቃት ከደረሱባቸው ልጆች መካከል 547 የሚሆኑት ልጆች የሚገኙባት የፑንጃብ ግዛት በሀገሪቱ ከሚደርሱ ጥቃቶች ውስጥ 40 በመቶ የሚሆነውን ትይዛለች።
የተደረገው ጥናትም የሃይማኖት አካታችነት የማይስተዋልበትን የፓኪስታንን አንድ ወጥ ሀገራዊ የትምህርት ካሪኩለም ነቅፏል። በሀገሪቱ የሚገኙ ክርስቲያኖች የማይከተሉትን ሃይማኖት በትምህርት ቤት እንዲያጠኑ እና እንዲማሩ መገደዳቸው የሃይማኖት ነጻነት ከመግታት ባለፈ የትምህርት ውጤት እንደሚጎዳ እና በማህበረሰብ ውስጥ መገለልን እንደሚያስከትል ተጠቅሷል።
የሃይማኖት መሪዎች እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች የፓኪስታን መንግስት አነስተኛ ቁጥር ላላቸው ማህበርሰቦች ሕጋዊ ጥበቃ እንዲያደርግ ፣ የትምህርት ፖሊሲዎችን እንዲያሻሽል እና ተቋማዊ ዝንፈቶችን እንዲያስተካከል ጥሪ እያቀረቡ ይገኛሉ።
መረጃውን ከክርስቲያን ፖስት አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
❤1🙏1
በባንግላዲሽ የሚገኘው አለመረጋጋት ክርስቲያን ጠል ለሆኑ ጥቃቶች በር እንደከፈተ ተገለጸ።
እንደ ኦፕን ዶርስ ዘገባ በባለፈው የፈረንጆቹ አመት ጠቅላይ ሚኒስተር ሼክ ሃሲና ከስልጣን መውረዳቸውን ተከትሎ በፓኪስታን የሚገኙ ክርስቲያኖች እየደረሰባቸው የሚገኘው ጥቃት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል። በሀገሪቱ ውስጥ ጠንካራ ማዕከላዊ አስተዳደር አለመኖሩ እንደ ሃፍዛት እና ሂዝብ ኡት ታህሪር ያሉ ብድኖች በክርስቲያኖች ላይ ከፍተኛ ጥቃት እንዲያደርሱ እድል ሰጥቷል።
የሃሲና መንግስት ከስልጣን ከወረደበት ጊዜ አንስቶ ወደ 100 የሚጠጉ ክርስቲያን ቤተሰቦች ኢየሱስ ክርስቶስን እንዲክዱ ተጽዕኖ እንደተደረገባቸው የተገለጸ ሲሆን ቢያንስ 36 ክርስትያኖች በራሳቸው አልያም በንብረታቸው ላይ ጥቃት እንደደረሰባቸው ተገልጿል።
በባለፈው አንድ አመትም ቤተክርስቲያኖች የተበዘበዙ ሲሆን አማኞችም ከሚደርስባቸው እንግልት እና ጥቃት የተነሳ አንዳንዶች ለመደበቅ እንደተገደዱ ክርስቲያን ቱዴይ አስነብቧል።
ክርስቲያኖች ብዙዉን ጊዜ የቀደመውን የሀገሪቱን መንግስት ደጋፊ ናቸው በመባል የሚከሰሱ ሲሆን ይህም የሀገሪቱ ፖለቲካዊ ምህዳር ባልተረጋጋበት ጊዜ ክርስቲያኖች የሌሎችን በደል ተሸካሚ እንዲሆኑ ዳርጓቸዋል። ከዚህም ባለፈ ስለ ክርስቲያኖች ትክክለኛ ያልሆኑ መረጃዎች እና አስተምህሮዎች እየደረሰ ያለውን አደጋ እንዲጨምር አድርገውታል። በዚህም ውስጥ የሀገሪቱ የሕግ አካላት ተጠቂዎችን ለመጠበቅ እና ጥቃት አድራሾችን ተጠያቂ ለማድረግ አለመቻላቸው እያስወቀሳቸው ይገኛል።
ብሔራዊ ምርጫ ለማድረግ ጥቂት ወራት በቀራት በባንግላዲሽ ጽንፈኛ ቡድኖች ወደ ስልጣን ከመጡ በሀገሪቱ የሚገኙ ክርስቲያኖች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊደርስ እንደሚችል መላምቶች ተቀምጠዋል። እየወጡ ያሉ ሪፖርቶችም በባንግላዲሽ የሀይማኖት ነጻነት እንዲከበር እና ተጋላጭ የሆኑ ማህበረሰቦች ጥበቃ እንዲያገኙ ዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ ትኩረት መስጠት እንዳለበት በማሳሰብ ላይ ናቸው።
መረጃውን ከክርስቲያን ቱዴይ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
እንደ ኦፕን ዶርስ ዘገባ በባለፈው የፈረንጆቹ አመት ጠቅላይ ሚኒስተር ሼክ ሃሲና ከስልጣን መውረዳቸውን ተከትሎ በፓኪስታን የሚገኙ ክርስቲያኖች እየደረሰባቸው የሚገኘው ጥቃት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል። በሀገሪቱ ውስጥ ጠንካራ ማዕከላዊ አስተዳደር አለመኖሩ እንደ ሃፍዛት እና ሂዝብ ኡት ታህሪር ያሉ ብድኖች በክርስቲያኖች ላይ ከፍተኛ ጥቃት እንዲያደርሱ እድል ሰጥቷል።
የሃሲና መንግስት ከስልጣን ከወረደበት ጊዜ አንስቶ ወደ 100 የሚጠጉ ክርስቲያን ቤተሰቦች ኢየሱስ ክርስቶስን እንዲክዱ ተጽዕኖ እንደተደረገባቸው የተገለጸ ሲሆን ቢያንስ 36 ክርስትያኖች በራሳቸው አልያም በንብረታቸው ላይ ጥቃት እንደደረሰባቸው ተገልጿል።
በባለፈው አንድ አመትም ቤተክርስቲያኖች የተበዘበዙ ሲሆን አማኞችም ከሚደርስባቸው እንግልት እና ጥቃት የተነሳ አንዳንዶች ለመደበቅ እንደተገደዱ ክርስቲያን ቱዴይ አስነብቧል።
ክርስቲያኖች ብዙዉን ጊዜ የቀደመውን የሀገሪቱን መንግስት ደጋፊ ናቸው በመባል የሚከሰሱ ሲሆን ይህም የሀገሪቱ ፖለቲካዊ ምህዳር ባልተረጋጋበት ጊዜ ክርስቲያኖች የሌሎችን በደል ተሸካሚ እንዲሆኑ ዳርጓቸዋል። ከዚህም ባለፈ ስለ ክርስቲያኖች ትክክለኛ ያልሆኑ መረጃዎች እና አስተምህሮዎች እየደረሰ ያለውን አደጋ እንዲጨምር አድርገውታል። በዚህም ውስጥ የሀገሪቱ የሕግ አካላት ተጠቂዎችን ለመጠበቅ እና ጥቃት አድራሾችን ተጠያቂ ለማድረግ አለመቻላቸው እያስወቀሳቸው ይገኛል።
ብሔራዊ ምርጫ ለማድረግ ጥቂት ወራት በቀራት በባንግላዲሽ ጽንፈኛ ቡድኖች ወደ ስልጣን ከመጡ በሀገሪቱ የሚገኙ ክርስቲያኖች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊደርስ እንደሚችል መላምቶች ተቀምጠዋል። እየወጡ ያሉ ሪፖርቶችም በባንግላዲሽ የሀይማኖት ነጻነት እንዲከበር እና ተጋላጭ የሆኑ ማህበረሰቦች ጥበቃ እንዲያገኙ ዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ ትኩረት መስጠት እንዳለበት በማሳሰብ ላይ ናቸው።
መረጃውን ከክርስቲያን ቱዴይ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ