የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከኖርዌይ ቤተ ክርስቲያን የእርዳታ ድርጅት ጋር በመተባበር በበጀት ዓመቱ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን በዋናነትም ያለድሜ ጋብቻ እና የሴት ልጅ ግርዛትን ከመከላከል አንፃር የተሰሩ ሥራዎችን የሚገመግም የምክክር መድረክ በጽሕፈት ቤቱ አካሄደ፡፡
ሐምሌ 17 ቀን 2017 ዓ/ም የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የሴቶች ወጣቶች እና ሕፃናት መመሪያ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ጥሩወርቅ የዕቅድ አፈፃጸም የምክክር መድረክ ዓላማ አስመልክተው ማብራርያ ሰጥተዋል፡፡
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በገባው ስምምነት መሰረት እንዲሁም ካለበት ሃገራዊ እና ሃይማኖታዊ ኃላፊነት አንፃር ከሰላም ግንባታ ሥራው ጎን ለጎን የሴት ልጅ ግርዛት እና ያለዕድሜ ጋብቻ ከመከላከል አንፃር የተሰሩትን ዋና ዋና ሥራዎችን፣ የተገኙ ውጤቶችን እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን ለመድረኩ ተሳታፊዎች አካፍለዋል፡፡
በመቀጠልም የአባል የሃይማኖት ተቋማት ርዕሰ ጉዳዩ የሚመለከታቸው የሥራ ክፍል ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች እንዲሁም የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የሴቶች፣ ወጣቶች እና ሕፃናት መመሪያ ኃላፊ በበጀት ዓመቱ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ከመከላከል አንፃር የሰሯቸውን ሥራዎች በዝርዝር በማቅረብ አንዳቸው ከአንዳቸው ልምድ እና የእርስ በእርስ ትምህርት መውሰድ የሚያስችላቸውን እድል መፍጠር መቻሉ ተገልጿል፡፡
በመጨረሻም በቀረቡት የሥራ አፈፃጸም ሪፖርቶች ላይ ሰፊ ምክክር ከተደረገ እና አስተያየት ከተሰጠ በኋላ በቀጣይ ከዚህ የተሻለ የተቀናጀ ሥራ በመሥራት የተሻለ ወጤት ማስመዝገብ እንደሚያስፈልግ በመግባባት የዕለቱ መድረክ የዕቅድ አፈፃጸም የምክክር መድረክ በታቀደው ዕቅድ መሰረት በስኬት መፈጸሙ ተገልጿል፡፡
መረጃው የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ነው፡፡
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
ሐምሌ 17 ቀን 2017 ዓ/ም የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የሴቶች ወጣቶች እና ሕፃናት መመሪያ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ጥሩወርቅ የዕቅድ አፈፃጸም የምክክር መድረክ ዓላማ አስመልክተው ማብራርያ ሰጥተዋል፡፡
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በገባው ስምምነት መሰረት እንዲሁም ካለበት ሃገራዊ እና ሃይማኖታዊ ኃላፊነት አንፃር ከሰላም ግንባታ ሥራው ጎን ለጎን የሴት ልጅ ግርዛት እና ያለዕድሜ ጋብቻ ከመከላከል አንፃር የተሰሩትን ዋና ዋና ሥራዎችን፣ የተገኙ ውጤቶችን እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን ለመድረኩ ተሳታፊዎች አካፍለዋል፡፡
በመቀጠልም የአባል የሃይማኖት ተቋማት ርዕሰ ጉዳዩ የሚመለከታቸው የሥራ ክፍል ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች እንዲሁም የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የሴቶች፣ ወጣቶች እና ሕፃናት መመሪያ ኃላፊ በበጀት ዓመቱ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ከመከላከል አንፃር የሰሯቸውን ሥራዎች በዝርዝር በማቅረብ አንዳቸው ከአንዳቸው ልምድ እና የእርስ በእርስ ትምህርት መውሰድ የሚያስችላቸውን እድል መፍጠር መቻሉ ተገልጿል፡፡
በመጨረሻም በቀረቡት የሥራ አፈፃጸም ሪፖርቶች ላይ ሰፊ ምክክር ከተደረገ እና አስተያየት ከተሰጠ በኋላ በቀጣይ ከዚህ የተሻለ የተቀናጀ ሥራ በመሥራት የተሻለ ወጤት ማስመዝገብ እንደሚያስፈልግ በመግባባት የዕለቱ መድረክ የዕቅድ አፈፃጸም የምክክር መድረክ በታቀደው ዕቅድ መሰረት በስኬት መፈጸሙ ተገልጿል፡፡
መረጃው የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ነው፡፡
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
❤1