ምክር ቤቱ የንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የሚቀርብለትን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል
*********
6ኛው ዙር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 14ኛ መደበኛ ጉባዔ ነገ ይካሄዳል።
ምክር ቤቱ ነገ በሚያካሄደው መደበኛ ጉባዔው፥ የነዳጅ ውጤቶች ግብይት ሥርዓትን ለመደንገግ በተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ላይ የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ የሚያፀድቅ ይሆናል።
በተጨማሪም የንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ በሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ ያፀድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ የምክር ቤቱ መረጃ ያመለክታል።
*********
6ኛው ዙር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 14ኛ መደበኛ ጉባዔ ነገ ይካሄዳል።
ምክር ቤቱ ነገ በሚያካሄደው መደበኛ ጉባዔው፥ የነዳጅ ውጤቶች ግብይት ሥርዓትን ለመደንገግ በተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ላይ የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ የሚያፀድቅ ይሆናል።
በተጨማሪም የንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ በሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ ያፀድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ የምክር ቤቱ መረጃ ያመለክታል።
👍30❤5
የሀገራዊ ፕሮጀክቶች የመስክ ምልከታ እና ግምገማ ቡድኖች መሪዎች ግኝቶቻቸውን አቀረቡ
***********************
የሀገራዊ ፕሮጀክቶች የመስክ ምልከታ እና ግምገማ ቡድኖች መሪዎች ግምገማዎቻቸውን እና ግኝቶቻቸውን አቅርበዋል፡፡
በሚኒስትሮች ምክር ቤት የሀገራዊ ፕሮጀክቶች በክልሎች ደረጃ ያለ አፈፃፀም ግምገማ ተደርጎ እንደነበር ይታወሳል።
ይኽን ተከትሎ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል ኃላፊ እና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት የተመራ ስብሰባ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ዛሬ ተካሂዷል።
በስብሰባው ላይ የመስክ ምልከታ እና ግምገማ ቡድኖች መሪዎች ግምገማዎቻቸውን እና ግኝቶቻቸውን ማቅረባቸው ታውቋል፡፡
ይኽ የሱፐርቪዥን እና የግብረመልስ ሂደት ሰፋ ያለው ሥርዓትን የማጠናከር ተግባር አካል ሲሆን አፈፃፀሞችን በዞን እና ወረዳ ደረጃ በመመልከት ክፍተቶችን መለየትን አላማ ማድረጉንም ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የማኀበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
***********************
የሀገራዊ ፕሮጀክቶች የመስክ ምልከታ እና ግምገማ ቡድኖች መሪዎች ግምገማዎቻቸውን እና ግኝቶቻቸውን አቅርበዋል፡፡
በሚኒስትሮች ምክር ቤት የሀገራዊ ፕሮጀክቶች በክልሎች ደረጃ ያለ አፈፃፀም ግምገማ ተደርጎ እንደነበር ይታወሳል።
ይኽን ተከትሎ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል ኃላፊ እና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት የተመራ ስብሰባ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ዛሬ ተካሂዷል።
በስብሰባው ላይ የመስክ ምልከታ እና ግምገማ ቡድኖች መሪዎች ግምገማዎቻቸውን እና ግኝቶቻቸውን ማቅረባቸው ታውቋል፡፡
ይኽ የሱፐርቪዥን እና የግብረመልስ ሂደት ሰፋ ያለው ሥርዓትን የማጠናከር ተግባር አካል ሲሆን አፈፃፀሞችን በዞን እና ወረዳ ደረጃ በመመልከት ክፍተቶችን መለየትን አላማ ማድረጉንም ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የማኀበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
👍19❤7
የፌዴራል ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች እና ሚኒስትር ዴኤታዎች በብሔራዊ ቤተ - መንግሥት ሙዝየም ያደረጉት ጉብኝት - በምስል
👍13❤1