ማስታወቂያ
የገንዘብ እጥረት ሲያጋጥምዎ ከእጅ ስልክዎ የጎደልዎትን የሚሞሉበት የችግር ጊዜ ዋስትናዎ የሆነው የሲንቄ ባንክ ወቢ ዲጂታል ብድር አገልግሎትን በመጠቀም አስቸኳይ የገንዘብ ፍላጎትዎን ያሟሉ፡፡
#Siinqee_Bank #Baankii_Siinqee #ሲንቄ_ባንክ #Siinqee_Digital #Siinqee_Ihsan #Financial_Inclusion #EMPOWERED_TOGETHER
የገንዘብ እጥረት ሲያጋጥምዎ ከእጅ ስልክዎ የጎደልዎትን የሚሞሉበት የችግር ጊዜ ዋስትናዎ የሆነው የሲንቄ ባንክ ወቢ ዲጂታል ብድር አገልግሎትን በመጠቀም አስቸኳይ የገንዘብ ፍላጎትዎን ያሟሉ፡፡
#Siinqee_Bank #Baankii_Siinqee #ሲንቄ_ባንክ #Siinqee_Digital #Siinqee_Ihsan #Financial_Inclusion #EMPOWERED_TOGETHER
❤7
"የማይናወጥ ሀገር ግንባታ፦ ትውልድ አልባሽና ዘመን ተሻጋሪ ተቋማት!"
*********************
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) "በመደመር መንግሥት" መጽሐፍ እና መደመር ፍልስፍና ውስጥ የተቋማት ግንባታ የሀገር ግንባታ ዋና ምሰሶ ተደርጎ ተወስዷል። መንግሥትም ይህንን እሳቤ በተግባር በመተርጎም፣ ተቋማትን ገለልተኛ፣ ዘመናዊ እና ውጤታማ የማድረግ ሪፎርም ሥራዎችን አከናውኗል።
እነዚህ ሥራዎች በግለሰቦች ፍላጎት ላይ ሳይሆን ግልጽ በሆኑ ሕጎችና መመሪያዎች ላይ እንዲመሠረቱ በማድረጋቸው፣ አስተማማኝ ተቋማዊ መረጋጋት ተፈጥሯል።
“የሀገር ህልውና እና ቀጣይነት የሚረጋገጠው በግለሰቦች በጎ ፈቃድ ሳይሆን፣ በማይናወጥ የሕግና የተቋማት መሠረት ላይ ሲገነባ ብቻ ነው።” — ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
እንደ ፍትህ ስርዓት፣ የፀጥታና የደኅንነት ተቋማት የሀገረ መንግሥት ምልክቶች በመሆናቸው ከማንኛውም ወገንተኝነት ነፃ ሆነው በብሔራዊ ጥቅምና በሕግ ላይ ብቻ ተመሥርተው እንዲዋቀሩ መደረጉ፣ በሀገራችን የፍትሕ ሥርዓትና በዴሞክራሲ ግንባታ ሂደት ላይ ጽኑ ተቋማዊ እምነት እንዲገነባ አስችሏል።
ሙያዊነት እንዲበረታታና ብቃትና ውጤታማነት የተቋማዊ ማሻሻያዎች አንኳር እንዲሆኑ መደረጋቸው፣ ለፈጣን ሀገራዊ እድገት ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ ጉዟችን ከፍተኛ ኃይል ሆኗል።
“ጠንካራ ተቋማት ማለት ዕውቀት፣ ቴክኖሎጂ እና ሥነ-ምግባር ተደምረው ለሕዝብ ጥቅም የሚውሉባቸው ማዕከላት ማለት ናቸው።” — ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
በመደመር መንግሥት እሳቤ የአገልግሎት ሰጭ ተቋማትን በቴክኖሎጂ የማዘመንና ለሀገራችን ብልጽግና ወሳኝ የሆኑ አዳዲስ የልህቀት ማዕከላትን የመገንባት ሥራዎች፣ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተወዳዳሪነት አሳድገዋል።
እነዚህ የተቋማት ግንባታ ሥራዎች መጨረሻ ግባቸው የሕግ የበላይነት የነገሠባትና ጠንካራ ኢኮኖሚ ያላት የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን ማድረግ ነው።
*********************
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) "በመደመር መንግሥት" መጽሐፍ እና መደመር ፍልስፍና ውስጥ የተቋማት ግንባታ የሀገር ግንባታ ዋና ምሰሶ ተደርጎ ተወስዷል። መንግሥትም ይህንን እሳቤ በተግባር በመተርጎም፣ ተቋማትን ገለልተኛ፣ ዘመናዊ እና ውጤታማ የማድረግ ሪፎርም ሥራዎችን አከናውኗል።
እነዚህ ሥራዎች በግለሰቦች ፍላጎት ላይ ሳይሆን ግልጽ በሆኑ ሕጎችና መመሪያዎች ላይ እንዲመሠረቱ በማድረጋቸው፣ አስተማማኝ ተቋማዊ መረጋጋት ተፈጥሯል።
“የሀገር ህልውና እና ቀጣይነት የሚረጋገጠው በግለሰቦች በጎ ፈቃድ ሳይሆን፣ በማይናወጥ የሕግና የተቋማት መሠረት ላይ ሲገነባ ብቻ ነው።” — ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
እንደ ፍትህ ስርዓት፣ የፀጥታና የደኅንነት ተቋማት የሀገረ መንግሥት ምልክቶች በመሆናቸው ከማንኛውም ወገንተኝነት ነፃ ሆነው በብሔራዊ ጥቅምና በሕግ ላይ ብቻ ተመሥርተው እንዲዋቀሩ መደረጉ፣ በሀገራችን የፍትሕ ሥርዓትና በዴሞክራሲ ግንባታ ሂደት ላይ ጽኑ ተቋማዊ እምነት እንዲገነባ አስችሏል።
ሙያዊነት እንዲበረታታና ብቃትና ውጤታማነት የተቋማዊ ማሻሻያዎች አንኳር እንዲሆኑ መደረጋቸው፣ ለፈጣን ሀገራዊ እድገት ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ ጉዟችን ከፍተኛ ኃይል ሆኗል።
“ጠንካራ ተቋማት ማለት ዕውቀት፣ ቴክኖሎጂ እና ሥነ-ምግባር ተደምረው ለሕዝብ ጥቅም የሚውሉባቸው ማዕከላት ማለት ናቸው።” — ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
በመደመር መንግሥት እሳቤ የአገልግሎት ሰጭ ተቋማትን በቴክኖሎጂ የማዘመንና ለሀገራችን ብልጽግና ወሳኝ የሆኑ አዳዲስ የልህቀት ማዕከላትን የመገንባት ሥራዎች፣ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተወዳዳሪነት አሳድገዋል።
እነዚህ የተቋማት ግንባታ ሥራዎች መጨረሻ ግባቸው የሕግ የበላይነት የነገሠባትና ጠንካራ ኢኮኖሚ ያላት የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን ማድረግ ነው።
❤15
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌድዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከአሜሪካው ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ
*****************
የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌድዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ዛሬ በጽሕፈት ቤታቸው የአሜሪካውን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክሪስቶፈር ላንዳውን ተቀብለው አነጋግረዋል።
በውይይታቸውም በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን የቆየ ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ መክረዋል፡፡
በተጨማሪም በቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ ሰፊ የሐሳብ ልውውጥ አድርገዋል።
ኢትዮጵያና አሜሪካ ለ120 ዓመታት የዘለቀ ታሪካዊና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸው ሲሆን፤ የዛሬው ውይይትም ይህንን ስትራቴጂካዊ ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ያለመ ነው።
*****************
የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌድዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ዛሬ በጽሕፈት ቤታቸው የአሜሪካውን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክሪስቶፈር ላንዳውን ተቀብለው አነጋግረዋል።
በውይይታቸውም በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን የቆየ ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ መክረዋል፡፡
በተጨማሪም በቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ ሰፊ የሐሳብ ልውውጥ አድርገዋል።
ኢትዮጵያና አሜሪካ ለ120 ዓመታት የዘለቀ ታሪካዊና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸው ሲሆን፤ የዛሬው ውይይትም ይህንን ስትራቴጂካዊ ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ያለመ ነው።
❤23🙏13👍4👌2🕊1
"በስማችሁ ገንዘብ ተጠይቆባችሁ ያውቃል? ወዳጅ ዘመዶቻችሁ ለሳይበር ሌቦች ሰለባ እንዳይሆኑ ይህንን የጥንቃቄ መልዕክት ያጋሩላቸው!"
***********************
በኢትዮጵያ በዋትሳፕ (WhatsApp)፣ በቴሌግራም (Telegram) እና በሌሎች የመልዕክት መላላኪያ ማህበራዊ ገጾች አማካኝነት የሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች እና የማጭበርበር ድርጊቶች በአሳሳቢ ሁኔታ መጨመራቸውን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) አስታወቀ።
ወንጀለኞቹ ወቅታዊ ኩነቶችን፣ ሲምፖዚየሞችን እና ስብሰባዎችን እንደ አጋጣሚ በመጠቀም የተለያዩ የማታለያ ዘዴዎችን እንደሚጠቀሙ አስተዳደሩ ገልጿል።
ከማጭበርበሪያ ስልቶቹ መካከልም "ነጻ የኢንተርኔት ፓኬጅ" እና "ልዩ የሥራ ቅጥር" የሚሉ አሳሳች መልዕክቶችን ማሰራጨት አንዱ መሆኑን ገልጿል።
በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ ተጠቃሚዎች በመልዕክቱ ውስጥ ያሉ ሊንኮችን (Links) እንዲጫኑ በማድረግ አካውንታቸውን መጥለፍ ነው።
በሦስተኛ ደረጃ የተጠለፈውን አካውንት በመጠቀም በተጎጂው ስም ከቅርብ ዘመዶቹ የገንዘብ ድጋፍ መጠየቅ መሆናቸውን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ባወጣው መረጃ አስታውቋል።
እንዲህ አይነት ክስተቶችን ለመከላከል እና ተጎጂ ላለመሆን ማህበረሰቡ ከሳይበር ጥቃት ራሱን መጠበቅ እንዳለበት ያሳሰበው የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በተለይ የሚከተሉትን መውሰድ እነደሚገባ በጥብቅ አሳስቧል፦
1. አጠራጣሪ ሊንኮችን አለመክፈት፡ ከማይታወቁ አድራሻዎች የሚላኩ መልዕክቶችን "Report" እና "Block" ማድረግ።
2. ምስጢራዊ ኮዶችን አለመስጠት፡ በስልክ የሚላክ የማረጋገጫ ኮድን (Verification Code) ለማንም አካል አለመንገር።
3. የሁለትዮሽ ማረጋገጫ (Two-Step Verification)፡ ጠላፊዎች በቀላሉ አካውንትን እንዳይቆጣጠሩ ተጨማሪ የደህንነት ቁልፍ የሚፈጥረውን የቴክኖሎጂ ዘዴ በአስቸኳይ መተግበር።
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ወንጀለኞችን በህግ ተጠያቂ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልጾ፣ ማንኛውም አጠራጣሪ እንቅስቃሴ ሲያጋጥም በነጻ ስልክ መስመር 933 በመደወል ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል።
#EthiopianBroadcastingCorporation #Verification #ኢመደአ
***********************
በኢትዮጵያ በዋትሳፕ (WhatsApp)፣ በቴሌግራም (Telegram) እና በሌሎች የመልዕክት መላላኪያ ማህበራዊ ገጾች አማካኝነት የሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች እና የማጭበርበር ድርጊቶች በአሳሳቢ ሁኔታ መጨመራቸውን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) አስታወቀ።
ወንጀለኞቹ ወቅታዊ ኩነቶችን፣ ሲምፖዚየሞችን እና ስብሰባዎችን እንደ አጋጣሚ በመጠቀም የተለያዩ የማታለያ ዘዴዎችን እንደሚጠቀሙ አስተዳደሩ ገልጿል።
ከማጭበርበሪያ ስልቶቹ መካከልም "ነጻ የኢንተርኔት ፓኬጅ" እና "ልዩ የሥራ ቅጥር" የሚሉ አሳሳች መልዕክቶችን ማሰራጨት አንዱ መሆኑን ገልጿል።
በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ ተጠቃሚዎች በመልዕክቱ ውስጥ ያሉ ሊንኮችን (Links) እንዲጫኑ በማድረግ አካውንታቸውን መጥለፍ ነው።
በሦስተኛ ደረጃ የተጠለፈውን አካውንት በመጠቀም በተጎጂው ስም ከቅርብ ዘመዶቹ የገንዘብ ድጋፍ መጠየቅ መሆናቸውን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ባወጣው መረጃ አስታውቋል።
እንዲህ አይነት ክስተቶችን ለመከላከል እና ተጎጂ ላለመሆን ማህበረሰቡ ከሳይበር ጥቃት ራሱን መጠበቅ እንዳለበት ያሳሰበው የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በተለይ የሚከተሉትን መውሰድ እነደሚገባ በጥብቅ አሳስቧል፦
1. አጠራጣሪ ሊንኮችን አለመክፈት፡ ከማይታወቁ አድራሻዎች የሚላኩ መልዕክቶችን "Report" እና "Block" ማድረግ።
2. ምስጢራዊ ኮዶችን አለመስጠት፡ በስልክ የሚላክ የማረጋገጫ ኮድን (Verification Code) ለማንም አካል አለመንገር።
3. የሁለትዮሽ ማረጋገጫ (Two-Step Verification)፡ ጠላፊዎች በቀላሉ አካውንትን እንዳይቆጣጠሩ ተጨማሪ የደህንነት ቁልፍ የሚፈጥረውን የቴክኖሎጂ ዘዴ በአስቸኳይ መተግበር።
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ወንጀለኞችን በህግ ተጠያቂ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልጾ፣ ማንኛውም አጠራጣሪ እንቅስቃሴ ሲያጋጥም በነጻ ስልክ መስመር 933 በመደወል ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል።
#EthiopianBroadcastingCorporation #Verification #ኢመደአ
❤18🙏1
ስሟን መኖር የጀመረችው አዲስ አበባ - አዲስ ምዕራፍ
**********************************
አዲስ አበባ እንደ ከተማ ከተመሰረተች ከ139 ዓመታት በላይ ዕድሜ ያስቆጠረች ሲሆን፤ ዛሬ ላይ ስሟን በሚመጥን የለውጥ ጎዳና ላይ ትገኛለች።
የፌዴራል መንግሥትና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ በወሰዱት ቁርጠኛ አቋም፣ በኮሪደር ልማት የመዲናዋን ገጽታ ከመሰረቱ እየቀየሩት ይገኛሉ።
የኮሪደር ልማቱ ቀደም ሲል ተሽከርካሪዎች ብቻ ይሳለጡባቸው የነበሩ መንገዶችን ወደ ሰው ተኮር መሰረተ ልማት ቀይሯቸዋል።
አሁን ላይ፦
• ሰፋፊና ምቹ የእግረኛ መንገዶች
• የሳይክል መንገዶች
• ዘመናዊ የመንገድ ዳር መብራቶችና የሕዝብ መናፈሻ ፓርኮች ተገንብተው አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል።
በመዲናዋ የሚኖሩት አና ዋልድማን የተባሉ የውጭ ሀገር ዜጋ ለሲጂቲኤን (CGTN) በሰጡት ቃል፥ ልማቱ የነዋሪዎችን የኑሮ ደረጃ እንዴት እንደቀየረ አስተውያለሁ ብለዋል። "መሰረተ ልማቱ በመሟላቱ በየቀኑ በሳይክል ወደ ሥራዬ እጓዛለሁ" የሚሉት አና፣ ከልጆቻቸው ጋር በምሽት በነጻነት በእግር መንቀሳቀስና በመዝናኛ ስፍራዎች ጊዜ ማሳለፍ መቻላቸው ትልቅ ደስታ እንደፈጠረላቸው ይናገራሉ።
ሌላኛው በመዲናዋ የተከናወነው አስደናቂ ሥራ የወንዝ ዳርቻ ልማት ነው። የተበከሉ ወንዞች ተጸድተው፣ ዛሬ ለዓይን የሚማርኩና ንጹህ አየር የሚገኝባቸው የቱሪስት መዳረሻዎች ሆነዋል።
የቱሪስት አስጎብኚ ድርጅት ባለቤቱ አቶ ተስፋየሱስ ያቆብ እንደሚሉት፤ ይህ ልማት "የት እንደነበሩ የማይታወቁና የተደበቁ" የከተማዋን ውበቶች ገልጦ አውጥቷል። የወንዝ ዳርቻ ልማቱ አዲስ አበባን በከተማ ቱሪዝም መዳረሻነት በዓለም አቀፍ ደረጃ እንድትታወቅ እያደረጋትም ነው ብለዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት አሥተዳደር ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ከድር አደም እንደሚሉት፣ ይህ ሥራ የከተማዋን መጨናነቅ ከመቀነስ ባለፈ ጤናማ አኗኗርን የሚያበረታታና ለቀጣዩ ትውልድ የሚሸጋገር ታላቅ ዐሻራ ነው።
በመሀመድ ፊጣሞ
#EthiopianBroadcastingCorporation #addisababa #Ethiopia #corridordevelopment
**********************************
አዲስ አበባ እንደ ከተማ ከተመሰረተች ከ139 ዓመታት በላይ ዕድሜ ያስቆጠረች ሲሆን፤ ዛሬ ላይ ስሟን በሚመጥን የለውጥ ጎዳና ላይ ትገኛለች።
የፌዴራል መንግሥትና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ በወሰዱት ቁርጠኛ አቋም፣ በኮሪደር ልማት የመዲናዋን ገጽታ ከመሰረቱ እየቀየሩት ይገኛሉ።
የኮሪደር ልማቱ ቀደም ሲል ተሽከርካሪዎች ብቻ ይሳለጡባቸው የነበሩ መንገዶችን ወደ ሰው ተኮር መሰረተ ልማት ቀይሯቸዋል።
አሁን ላይ፦
• ሰፋፊና ምቹ የእግረኛ መንገዶች
• የሳይክል መንገዶች
• ዘመናዊ የመንገድ ዳር መብራቶችና የሕዝብ መናፈሻ ፓርኮች ተገንብተው አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል።
በመዲናዋ የሚኖሩት አና ዋልድማን የተባሉ የውጭ ሀገር ዜጋ ለሲጂቲኤን (CGTN) በሰጡት ቃል፥ ልማቱ የነዋሪዎችን የኑሮ ደረጃ እንዴት እንደቀየረ አስተውያለሁ ብለዋል። "መሰረተ ልማቱ በመሟላቱ በየቀኑ በሳይክል ወደ ሥራዬ እጓዛለሁ" የሚሉት አና፣ ከልጆቻቸው ጋር በምሽት በነጻነት በእግር መንቀሳቀስና በመዝናኛ ስፍራዎች ጊዜ ማሳለፍ መቻላቸው ትልቅ ደስታ እንደፈጠረላቸው ይናገራሉ።
ሌላኛው በመዲናዋ የተከናወነው አስደናቂ ሥራ የወንዝ ዳርቻ ልማት ነው። የተበከሉ ወንዞች ተጸድተው፣ ዛሬ ለዓይን የሚማርኩና ንጹህ አየር የሚገኝባቸው የቱሪስት መዳረሻዎች ሆነዋል።
የቱሪስት አስጎብኚ ድርጅት ባለቤቱ አቶ ተስፋየሱስ ያቆብ እንደሚሉት፤ ይህ ልማት "የት እንደነበሩ የማይታወቁና የተደበቁ" የከተማዋን ውበቶች ገልጦ አውጥቷል። የወንዝ ዳርቻ ልማቱ አዲስ አበባን በከተማ ቱሪዝም መዳረሻነት በዓለም አቀፍ ደረጃ እንድትታወቅ እያደረጋትም ነው ብለዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት አሥተዳደር ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ከድር አደም እንደሚሉት፣ ይህ ሥራ የከተማዋን መጨናነቅ ከመቀነስ ባለፈ ጤናማ አኗኗርን የሚያበረታታና ለቀጣዩ ትውልድ የሚሸጋገር ታላቅ ዐሻራ ነው።
በመሀመድ ፊጣሞ
#EthiopianBroadcastingCorporation #addisababa #Ethiopia #corridordevelopment
❤7🔥1
የቀድሞው የአርሰናል ኮከብ ኢቢሲን ጎበኘ
**************
የቀድሞው የአርሰናል የቀኝ ተከላካይ ባካሪ ሳኛ ዛሬ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽንን (ኢቢሲ) ጎብኝቷል።
ከሰሞኑ በአዲስ አበባ ቆይታ እያደረገ የሚገኘው ፈረንሳዊው ኮከብ በኢቢሲ ዋናው መስሪያ ቤት በመገኘት ዘመናዊውን የኢቢሲ የቴሌቪዥንን እና የሬዲዮ ስቱዲዮዎች ጎብኝቷል።
ኢቢሲ ባሉት ዘመናዊ ስቱዲዮዎች መገረሙን የተናገረው የቀድሞው የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ተከላካይ ተቋሙ ያለበት ቦታ ፍጹም ደስ የሚል መሆኑንም ገልጿል።
ባካሪ ሳኛ በኢትዮጵያ ያለውን ቆይታ እና የእግር ኳስ ህይወቱን በተመለከተ ከኢቢሲ ጋር ያደረገውን ቆይታ በቀጣይ ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል።
በአንተነህ ሲሳይ
#EthiopianBroadcastingCorporation #Bacary_Sagna #africa #Arsenal
**************
የቀድሞው የአርሰናል የቀኝ ተከላካይ ባካሪ ሳኛ ዛሬ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽንን (ኢቢሲ) ጎብኝቷል።
ከሰሞኑ በአዲስ አበባ ቆይታ እያደረገ የሚገኘው ፈረንሳዊው ኮከብ በኢቢሲ ዋናው መስሪያ ቤት በመገኘት ዘመናዊውን የኢቢሲ የቴሌቪዥንን እና የሬዲዮ ስቱዲዮዎች ጎብኝቷል።
ኢቢሲ ባሉት ዘመናዊ ስቱዲዮዎች መገረሙን የተናገረው የቀድሞው የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ተከላካይ ተቋሙ ያለበት ቦታ ፍጹም ደስ የሚል መሆኑንም ገልጿል።
ባካሪ ሳኛ በኢትዮጵያ ያለውን ቆይታ እና የእግር ኳስ ህይወቱን በተመለከተ ከኢቢሲ ጋር ያደረገውን ቆይታ በቀጣይ ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል።
በአንተነህ ሲሳይ
#EthiopianBroadcastingCorporation #Bacary_Sagna #africa #Arsenal
❤46🙏2👏1