EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)
133K subscribers
43.2K photos
483 videos
80 files
13.7K links
EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation) @etvafaanoromoo1
@ETVkidschannel
@EBCWORLD1
@etventertainment1
Download Telegram
ኢትዮጵያውያን በአንድነት ወጥተው በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ታሪክ የሚሠሩበት ዕለት - 5 ቀን ቀረው!
8👍5👏4
ከ48 ቢሊዮን እስከ አዲሱ የ8 ቢሊዮን ግብ፡ የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ ታሪካዊ ጉዞ

ኢትዮጵያ በ2011 ዓ.ም በይፋ የጀመረችው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር፣ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል እና የተፈጥሮ ሀብትን ለመንከባከብ ከተካሄዱ ታላላቅ ሀገራዊ ንቅናቄዎች አንዱ ነው::

በተለይም በየዓመቱ የሚካሄዱት "የአንድ ጀምበር" የችግኝ ተከላ ዘመቻዎች በግዙፍ የሕዝብ ተሳትፎ እና በአስደማሚ የአፈፃፀም አቅም የኢትዮጵያን ስም በዓለም አቀፍ ደረጃ በግንባር ቀደምትነት ያስጠሩ ታሪካዊ ኩነቶች ናቸው
19🙏4👏3
5 ቀናት ቀሩት!

በሁሉም የሀገራችን ማዕዘናት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለጸናች ኢትዮጵያ ያላቸውን ጠንካራ አንድነት እና የጋራ ኃላፊነት በሚያንጸባርቀው፣ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ሥር ለታሪካዊው ሀገራዊ ዘመቻ በጋራ በመሰብሰብ በአንድ ቀን 800 ሚሊዮን ችግኞችን ይተክላሉ::

ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም
እርሶም የዚህ ታሪካዊ ንቅናቄ አካል ይሁኑ!
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት
6🙏3
የአንድ ጀምበር ተዓምር፦ 800 ሚሊዮን ችግኝ እና የኢትዮጵያ አረንጓዴ አብዮት

በአንድ ጀምበር፣ በተወሰኑ የብርሃን ሰዓታት ውስጥ፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ እጆች ለአንዲት ሀገር የጋራ ዓላማ ሲሰባሰቡ ማየት እጅግ አስደናቂ ሀገራዊ ተዓምር ነው::

በኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ታሪክ ውስጥ "አንድ ጀምበር" የሚለው ቃል ትርጉሙ እጅግ ጥልቅ፣ መንፈሱም እጅግ ረቂቅ ነው
9👍5🔥2
ኢትዮጵያ እና አሜሪካ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ ዘርፍ በጋራ መሥራት በሚችሉባቸው ሁኔታዎች ላይ ተወያዩ

በአሜሪካ መንግሥት የመካከለኛው ምሥራቅ እና አፍሪካ ምክትል ረዳት ሚኒስትር ማርክ ሚሼል የተመራ ከፍተኛ ልዑክ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የሥራ ጉብኝት አድርጓል::

በጉብኝቱ ወቅት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) ለልዑካን ቡድኑ ባደረጉት ገለጻ፣ በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን የረጅም ዓመታት ታሪካዊ ግንኙነት በማስታወስ፣ ኢንስቲትዩቱ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፍ የሚያከናውናቸውን ዋና ዋና ተግባራት በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል
13
በ2018 በጀት ዓመት ከ607 ሚሊዮን ዶላር በላይ ምርት ለውጭ ገበያ ቀረበ

በ2018 የበጀት ዓመት 607 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚያወጣ ምርት ለውጭ ገበያ ማቅረብ መቻሉን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል::

የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ መንግሥት ለማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት እና በ”ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ አማካኝነት በዘርፉ አመርቂ ውጤቶች እየተመዘገቡ ይገኛሉ፡፡ በዚህም ከፍተኛ የሥራ ዕድል የመፍጠር እና የሀገር ውስጥ ምርትን የማሳደግ አቅም እየጎለበተ መምጣቱን አንስተዋል
10👍3
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአዘርባጃን ብሔራዊ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ጋር ተወያዩ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአዘርባጃን ሪፐብሊክ ብሔራዊ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ሳሂባ ጋፋሮቫ ጋር ፍሬያማ ውይይት ማካሄዳቸውን አስታወቁ::

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጽ ባሰፈሩት መልዕክት፣ ከአፈ ጉባኤዋ ጋር ያደረጉት ውይይት የኢትዮጵያን እና የአዘርባጃንን ስትራቴጂያዊ አጋርነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደነበር ጠቁመዋል
17👍6🙏2
“ለሚቀጥለው ትውልድ የብልጽግና መሠረት ከምንጥልባቸው መንገዶች አንዱ ዛፎችን መትከል ነው”
8
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በ2018 በጀት ዓመት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ገቢ አገኘ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በ2018 የሥራ ዘመን ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ (9.1 ቢሊዮን ዶላር) ገቢ ማግኘቱን ይፋ አደረገ::

የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው የአየር መንገዱን የ2018 በጀት ዓመት አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም አስመልክተው በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት፣ ዘንድሮ የተመዘገበው ገቢ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ20 በመቶ ዕድገት ያሳየ ነው
👍125
የአረንጓዴ ዐሻራ መሪ ቃሎች
***************
አረንጓዴ ዐሻራ ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ የነበሩ መሪ ቃሎች
2011 ዓ.ም በአንድ ሰው 40 ችግኝ
2012 ዓ.ም እየተጠነቀቅን እንተክላለን
2013 ዓ.ም ኢትዮጵያን እናልብሳት
2014 ዓ.ም ዐሻራችን ለትውልዳችን
2015 ዓ.ም ነገን ዛሬ እንትከል
2016 ዓ.ም የምትተክል ሀገር የሚፀና ትውልድ
2017 ዓ.ም በመትከል ማንሰራራት
2018 ዓ.ም ተስፋን እንትከል
Ethiopian Broadcasting Corporation #EBC #Ethiopia #EBCDotStream #GreenLegacy #EconomicGrowth #CarbonMarket #ClimateAction
7👍7
የአረንጓዴ ተዓምር ኢኮኖሚያዊ ዕይታ

በኢትዮጵያ ውስጥ በስፋት እየተተገበረ ያለው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የተፈጥሮን ሚዛን ከመጠበቅ ባለፈ፣ የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ መዋቅር ከሥር መሠረቱ እያደሰ እና እየገነባ ያለ ግዙፍ የፋይናንስ ሞተር ሆኗል::

ይህ ንቅናቄ ዛፍ ከመትከል የዘለለ እጅግ ጥልቅ ትርጉም ያለው ሲሆን፣ "ከጥላ ማግኘት ወደ ኪስ ማዳበር"፣ "ከጓሮ ውበት ወደ ማዕድ መሙላት" እንዲሁም "ከአካባቢ ጥበቃ ወደ አግሮ-ኢንዱስትሪ ትሥሥር" የተደረገ ታላቅ የኢኮኖሚ ሽግግር በውስጡ ያዘለ ነው
10🥰3
የጽናት ዐሻራ፡ ከፈተናዎች ባሻገር የኢትዮጵያውያን ተፈጥሮን የማደስ ቃል ኪዳን

የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ለኢትዮጵያውያን ተፈጥሮን የማደስ እና የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ተግባር ብቻ ሳይሆን፣ ለነገዋ ሀገር ተስፋን የመትከል ታላቅ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው::

ይህ ጉዞ ጊዜያዊ ስሜት ወይም የታሪክ አጋጣሚ ያመጣው ሳይሆን፣ ዘላቂ እና የማይበገር ሕዝባዊ ራዕይ መሆኑን በተግባር አስመስክረናል
👍6👏2🙏21
“ዛሬ የምንተክለው ነገ ልጆቻችን ይጠለሉበታል፤ ነገ ልጆቻችን አይሰደዱም፤ ነገ ልጆቻችን አይለምኑም ብለን ነው።” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
🥰144👍4🤣4🏆2👏1
ኢትዮጵያ እና አሜሪካ በማዕድን ዘርፍ ላይ በጋራ መስራት በሚቻልባቸው እድሎች እና የትብብር መስኮች ዙሪያ ተወያዩ

የማዕድን ሚኒስትሩ ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ በአሜሪካ መንግሥት የመካከለኛው ምሥራቅ እና አፍሪካ ምክትል ረዳት ሚኒስትር ማርክ ሚሼል የተመራ ከፍተኛ ልዑክ ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም አሜሪካ በኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ በጋራ መስራት በሚቻልባቸው እድሎች እና የትብብር መስኮች ዙሪያ በሰፊው መክረዋል::

የኢትዮጵያ መንግሥት ለማዕድን ዘርፍ ከፍተኛ ትኩረት መስጠቱን የገለጹት ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኘ የአሜሪካ ኩባንያዎች በሀገሪቱ በማዕድን ልማት እና ኢንቨስትመንት ተሰማርተው መስራት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል
10👏2🙏2
አረንጓዴ ዐሻራ፡ በኢትዮጵያውያን ዘንድ አዲስ የኅብረት እና የጋራ ዓላማ ባህልን የፈጠረ መርሐ-ግብር

ኢትዮጵያ በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የጀመረችው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ዛሬ ላይ የኢትዮጵያን ገጽታ ከመስዋብ አልፎ የምግብ ዋስትና እና የዲፕሎማሲ አቅም የለወጠ ታላቅ ሀገራዊ እና አህጉራዊ ንቅናቄ ሆኖ ታይቷል::

ባለፉት ሰባት ዓመታት የተመዘገቡት ስኬቶች ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ላይ ያሳየችውን ተግባራዊ ምላሽ እና ያስመዘገበችውን ዘላቂ ፍሬ በጥልቀት የሚያስረዱ ናቸው
👏5👍42
የገበታ ፕሮጀክቶች እና ኮሪደር ልማት የኢትዮጵያን ቱሪዝም እንዴት ቀየሩ?

ባለፉት አምስት ዓመታት የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ ከውሱን የገቢ ምንጭነት ገጽታው በመውጣት፣ ወደ ዋነኛ የሀገር ግንባታ፣ የሰላም ማስፋፊያ እና የኅብረ ብሔራዊ አንድነት መገንቢያ ማኅበራዊ መሣሪያነት የተሸጋገረበት ታሪካዊ ምዕራፍ ተመዝግቧል::

ይህ ስትራቴጂያዊ ሽግግር በዘፈቀደ የመጣ ሳይሆን ሀገራችን በራሷ አቅም እና ዕውቀት ላይ መሠረት አድርጋ በነደፈችው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ፖሊሲ ውስጥ ዘርፉን እንደ አንድ ጠንካራ ብሔራዊ ምሰሶ አድርጎ የመቅረጽ ጥልቅ ራዕይ ውጤት ነው
4👍3
በጥቃቅንና በንዑስ ቡድኖች የተነሱ የአጀንዳ ሀሳቦች ለስልታዊ ቡድን መቅረብ ጀመሩ

ዛሬ በነበረው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከ16 የባለ 250 አባላት ስልታዊ ከእያንዳንዳቸው የተመረጡ 25 ወኪሎች ከጥቃቅን ቡድኖች እስከ ንዑስ ቡድኖች በነበረው ሂደት የተነሱ የአጀንዳ ሃሳቦችን በቃለ ጉባኤ አጠናቅረው ለባለ 250 ስልታዊ ቡድን ማቅረብ ጀምረዋል፡፡
የበዚህ መድረክ አጀንዳ ሃሳቦች ቀርበው ያልተካተቱ፣ ያልተብራሩና መጨመር የሚገባቸው ከተመካካሪዎች ተነስተው አጠናቃሪዎቹ ሰብስበዋል፡፡

16ቱ ባለ 250 አባላት ስልታዊ ቡድኖች በቀረቡላቸው የአጀንዳ ሃሳች መግባባት ላይ እስሚደርሱ ውይይቱ በሁሉም ቡድኖች በቀጣይ ቀናትም ተጠናክሮ የሚቀጥለ ይሆናል፡፡
👍54
ኢትዮጵያን ለመንካት ማንም እንዳያስብ፤ እንዳይሞክርም!

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ዛሬ ላይ የገነባው እጅግ አስፈሪ ግርማ ሞገስ፣ የሰው ሀገር ለመውረር፣ ድንበር ለመጋፋት ወይም በሌሎች ሉዓላዊ ሀገራት ላይ ጣልቃ ለመግባት የታለመ አይደለም::

ይልቁንም፣ ይህ አስገራሚ ወታደራዊ እና ተቋማዊ ቁመና ኢትዮጵያ በአስተማማኝ የልማት፣ የብልጽግና እና የሰላም ጎዳና ላይ ያለ ስጋት እንድትጓዝ የሚያስችል፣ የማይደፈር የውስጥ አቅም ግንባታ ታሪካዊ ፍሬ ነው
7👍4🔥2
የብሔራዊ ደኅንነት ዩኒቨርሲቲ ለሀገር ደኅንነት እና ጥቅም መከበር ቁልፍ የአቅም ግንባታ ማዕከል ነው - የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት የብሔራዊ ደኀንነት ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ደኅንነት እና ጥቅም ለማስጠበቅ በሚደረገው ጥረት ውስጥ ቁልፍ የአቅም ግንባታ ማዕከል በመሆን እያገለገለ እንደሚገኝ ገለጹ::

ቋሚ ኮሚቴው በዩኒቨርሲቲው ተገኝቶ የሥራ እንቅስቃሴዎችን ጎብኝቷል
👍3🔥1
ዓባይን ለመጠበቅ የተሻለው መንገድ፦ ከፖለቲካ ሴራ ወደ አረንጓዴ ትብብር

ከዓመታት በፊት የዓባይ ወንዝ ተፋሰስ በከፍተኛ የሥነ ምኅዳር መዛባት እና የሕልውና አደጋ ውስጥ ወድቆ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው::

የደን መመናመን፣ ከፍተኛ የአፈር መሸርሸር እና የአካባቢ መራቆት የወንዙን ዘላቂ ደኅንነት አደጋ ላይ ጥለውት ነበር
13👍8👏2