ከ48 ቢሊዮን እስከ አዲሱ የ8 ቢሊዮን ግብ፡ የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ ታሪካዊ ጉዞ
ኢትዮጵያ በ2011 ዓ.ም በይፋ የጀመረችው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር፣ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል እና የተፈጥሮ ሀብትን ለመንከባከብ ከተካሄዱ ታላላቅ ሀገራዊ ንቅናቄዎች አንዱ ነው::
በተለይም በየዓመቱ የሚካሄዱት "የአንድ ጀምበር" የችግኝ ተከላ ዘመቻዎች በግዙፍ የሕዝብ ተሳትፎ እና በአስደማሚ የአፈፃፀም አቅም የኢትዮጵያን ስም በዓለም አቀፍ ደረጃ በግንባር ቀደምትነት ያስጠሩ ታሪካዊ ኩነቶች ናቸው
ኢትዮጵያ በ2011 ዓ.ም በይፋ የጀመረችው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር፣ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል እና የተፈጥሮ ሀብትን ለመንከባከብ ከተካሄዱ ታላላቅ ሀገራዊ ንቅናቄዎች አንዱ ነው::
በተለይም በየዓመቱ የሚካሄዱት "የአንድ ጀምበር" የችግኝ ተከላ ዘመቻዎች በግዙፍ የሕዝብ ተሳትፎ እና በአስደማሚ የአፈፃፀም አቅም የኢትዮጵያን ስም በዓለም አቀፍ ደረጃ በግንባር ቀደምትነት ያስጠሩ ታሪካዊ ኩነቶች ናቸው
❤19🙏4👏3
ኢትዮጵያ እና አሜሪካ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ ዘርፍ በጋራ መሥራት በሚችሉባቸው ሁኔታዎች ላይ ተወያዩ
በአሜሪካ መንግሥት የመካከለኛው ምሥራቅ እና አፍሪካ ምክትል ረዳት ሚኒስትር ማርክ ሚሼል የተመራ ከፍተኛ ልዑክ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የሥራ ጉብኝት አድርጓል::
በጉብኝቱ ወቅት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) ለልዑካን ቡድኑ ባደረጉት ገለጻ፣ በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን የረጅም ዓመታት ታሪካዊ ግንኙነት በማስታወስ፣ ኢንስቲትዩቱ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፍ የሚያከናውናቸውን ዋና ዋና ተግባራት በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል
በአሜሪካ መንግሥት የመካከለኛው ምሥራቅ እና አፍሪካ ምክትል ረዳት ሚኒስትር ማርክ ሚሼል የተመራ ከፍተኛ ልዑክ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የሥራ ጉብኝት አድርጓል::
በጉብኝቱ ወቅት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) ለልዑካን ቡድኑ ባደረጉት ገለጻ፣ በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን የረጅም ዓመታት ታሪካዊ ግንኙነት በማስታወስ፣ ኢንስቲትዩቱ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፍ የሚያከናውናቸውን ዋና ዋና ተግባራት በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል
❤13
በ2018 በጀት ዓመት ከ607 ሚሊዮን ዶላር በላይ ምርት ለውጭ ገበያ ቀረበ
በ2018 የበጀት ዓመት 607 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚያወጣ ምርት ለውጭ ገበያ ማቅረብ መቻሉን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል::
የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ መንግሥት ለማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት እና በ”ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ አማካኝነት በዘርፉ አመርቂ ውጤቶች እየተመዘገቡ ይገኛሉ፡፡ በዚህም ከፍተኛ የሥራ ዕድል የመፍጠር እና የሀገር ውስጥ ምርትን የማሳደግ አቅም እየጎለበተ መምጣቱን አንስተዋል
በ2018 የበጀት ዓመት 607 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚያወጣ ምርት ለውጭ ገበያ ማቅረብ መቻሉን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል::
የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ መንግሥት ለማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት እና በ”ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ አማካኝነት በዘርፉ አመርቂ ውጤቶች እየተመዘገቡ ይገኛሉ፡፡ በዚህም ከፍተኛ የሥራ ዕድል የመፍጠር እና የሀገር ውስጥ ምርትን የማሳደግ አቅም እየጎለበተ መምጣቱን አንስተዋል
❤10👍3
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአዘርባጃን ብሔራዊ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ጋር ተወያዩ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአዘርባጃን ሪፐብሊክ ብሔራዊ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ሳሂባ ጋፋሮቫ ጋር ፍሬያማ ውይይት ማካሄዳቸውን አስታወቁ::
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጽ ባሰፈሩት መልዕክት፣ ከአፈ ጉባኤዋ ጋር ያደረጉት ውይይት የኢትዮጵያን እና የአዘርባጃንን ስትራቴጂያዊ አጋርነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደነበር ጠቁመዋል
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአዘርባጃን ሪፐብሊክ ብሔራዊ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ሳሂባ ጋፋሮቫ ጋር ፍሬያማ ውይይት ማካሄዳቸውን አስታወቁ::
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጽ ባሰፈሩት መልዕክት፣ ከአፈ ጉባኤዋ ጋር ያደረጉት ውይይት የኢትዮጵያን እና የአዘርባጃንን ስትራቴጂያዊ አጋርነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደነበር ጠቁመዋል
❤17👍6🙏2
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በ2018 በጀት ዓመት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ገቢ አገኘ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በ2018 የሥራ ዘመን ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ (9.1 ቢሊዮን ዶላር) ገቢ ማግኘቱን ይፋ አደረገ::
የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው የአየር መንገዱን የ2018 በጀት ዓመት አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም አስመልክተው በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት፣ ዘንድሮ የተመዘገበው ገቢ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ20 በመቶ ዕድገት ያሳየ ነው
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በ2018 የሥራ ዘመን ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ (9.1 ቢሊዮን ዶላር) ገቢ ማግኘቱን ይፋ አደረገ::
የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው የአየር መንገዱን የ2018 በጀት ዓመት አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም አስመልክተው በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት፣ ዘንድሮ የተመዘገበው ገቢ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ20 በመቶ ዕድገት ያሳየ ነው
👍12❤5
የአረንጓዴ ዐሻራ መሪ ቃሎች
***************
አረንጓዴ ዐሻራ ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ የነበሩ መሪ ቃሎች
2011 ዓ.ም በአንድ ሰው 40 ችግኝ
2012 ዓ.ም እየተጠነቀቅን እንተክላለን
2013 ዓ.ም ኢትዮጵያን እናልብሳት
2014 ዓ.ም ዐሻራችን ለትውልዳችን
2015 ዓ.ም ነገን ዛሬ እንትከል
2016 ዓ.ም የምትተክል ሀገር የሚፀና ትውልድ
2017 ዓ.ም በመትከል ማንሰራራት
2018 ዓ.ም ተስፋን እንትከል
Ethiopian Broadcasting Corporation #EBC #Ethiopia #EBCDotStream #GreenLegacy #EconomicGrowth #CarbonMarket #ClimateAction
***************
አረንጓዴ ዐሻራ ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ የነበሩ መሪ ቃሎች
2011 ዓ.ም በአንድ ሰው 40 ችግኝ
2012 ዓ.ም እየተጠነቀቅን እንተክላለን
2013 ዓ.ም ኢትዮጵያን እናልብሳት
2014 ዓ.ም ዐሻራችን ለትውልዳችን
2015 ዓ.ም ነገን ዛሬ እንትከል
2016 ዓ.ም የምትተክል ሀገር የሚፀና ትውልድ
2017 ዓ.ም በመትከል ማንሰራራት
2018 ዓ.ም ተስፋን እንትከል
Ethiopian Broadcasting Corporation #EBC #Ethiopia #EBCDotStream #GreenLegacy #EconomicGrowth #CarbonMarket #ClimateAction
❤7👍7
የአረንጓዴ ተዓምር ኢኮኖሚያዊ ዕይታ
በኢትዮጵያ ውስጥ በስፋት እየተተገበረ ያለው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የተፈጥሮን ሚዛን ከመጠበቅ ባለፈ፣ የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ መዋቅር ከሥር መሠረቱ እያደሰ እና እየገነባ ያለ ግዙፍ የፋይናንስ ሞተር ሆኗል::
ይህ ንቅናቄ ዛፍ ከመትከል የዘለለ እጅግ ጥልቅ ትርጉም ያለው ሲሆን፣ "ከጥላ ማግኘት ወደ ኪስ ማዳበር"፣ "ከጓሮ ውበት ወደ ማዕድ መሙላት" እንዲሁም "ከአካባቢ ጥበቃ ወደ አግሮ-ኢንዱስትሪ ትሥሥር" የተደረገ ታላቅ የኢኮኖሚ ሽግግር በውስጡ ያዘለ ነው
በኢትዮጵያ ውስጥ በስፋት እየተተገበረ ያለው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የተፈጥሮን ሚዛን ከመጠበቅ ባለፈ፣ የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ መዋቅር ከሥር መሠረቱ እያደሰ እና እየገነባ ያለ ግዙፍ የፋይናንስ ሞተር ሆኗል::
ይህ ንቅናቄ ዛፍ ከመትከል የዘለለ እጅግ ጥልቅ ትርጉም ያለው ሲሆን፣ "ከጥላ ማግኘት ወደ ኪስ ማዳበር"፣ "ከጓሮ ውበት ወደ ማዕድ መሙላት" እንዲሁም "ከአካባቢ ጥበቃ ወደ አግሮ-ኢንዱስትሪ ትሥሥር" የተደረገ ታላቅ የኢኮኖሚ ሽግግር በውስጡ ያዘለ ነው
❤10🥰3
ኢትዮጵያ እና አሜሪካ በማዕድን ዘርፍ ላይ በጋራ መስራት በሚቻልባቸው እድሎች እና የትብብር መስኮች ዙሪያ ተወያዩ
የማዕድን ሚኒስትሩ ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ በአሜሪካ መንግሥት የመካከለኛው ምሥራቅ እና አፍሪካ ምክትል ረዳት ሚኒስትር ማርክ ሚሼል የተመራ ከፍተኛ ልዑክ ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም አሜሪካ በኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ በጋራ መስራት በሚቻልባቸው እድሎች እና የትብብር መስኮች ዙሪያ በሰፊው መክረዋል::
የኢትዮጵያ መንግሥት ለማዕድን ዘርፍ ከፍተኛ ትኩረት መስጠቱን የገለጹት ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኘ የአሜሪካ ኩባንያዎች በሀገሪቱ በማዕድን ልማት እና ኢንቨስትመንት ተሰማርተው መስራት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል
የማዕድን ሚኒስትሩ ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ በአሜሪካ መንግሥት የመካከለኛው ምሥራቅ እና አፍሪካ ምክትል ረዳት ሚኒስትር ማርክ ሚሼል የተመራ ከፍተኛ ልዑክ ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም አሜሪካ በኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ በጋራ መስራት በሚቻልባቸው እድሎች እና የትብብር መስኮች ዙሪያ በሰፊው መክረዋል::
የኢትዮጵያ መንግሥት ለማዕድን ዘርፍ ከፍተኛ ትኩረት መስጠቱን የገለጹት ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኘ የአሜሪካ ኩባንያዎች በሀገሪቱ በማዕድን ልማት እና ኢንቨስትመንት ተሰማርተው መስራት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል
❤10👏2🙏2
አረንጓዴ ዐሻራ፡ በኢትዮጵያውያን ዘንድ አዲስ የኅብረት እና የጋራ ዓላማ ባህልን የፈጠረ መርሐ-ግብር
ኢትዮጵያ በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የጀመረችው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ዛሬ ላይ የኢትዮጵያን ገጽታ ከመስዋብ አልፎ የምግብ ዋስትና እና የዲፕሎማሲ አቅም የለወጠ ታላቅ ሀገራዊ እና አህጉራዊ ንቅናቄ ሆኖ ታይቷል::
ባለፉት ሰባት ዓመታት የተመዘገቡት ስኬቶች ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ላይ ያሳየችውን ተግባራዊ ምላሽ እና ያስመዘገበችውን ዘላቂ ፍሬ በጥልቀት የሚያስረዱ ናቸው
ኢትዮጵያ በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የጀመረችው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ዛሬ ላይ የኢትዮጵያን ገጽታ ከመስዋብ አልፎ የምግብ ዋስትና እና የዲፕሎማሲ አቅም የለወጠ ታላቅ ሀገራዊ እና አህጉራዊ ንቅናቄ ሆኖ ታይቷል::
ባለፉት ሰባት ዓመታት የተመዘገቡት ስኬቶች ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ላይ ያሳየችውን ተግባራዊ ምላሽ እና ያስመዘገበችውን ዘላቂ ፍሬ በጥልቀት የሚያስረዱ ናቸው
👏5👍4❤2
የገበታ ፕሮጀክቶች እና ኮሪደር ልማት የኢትዮጵያን ቱሪዝም እንዴት ቀየሩ?
ባለፉት አምስት ዓመታት የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ ከውሱን የገቢ ምንጭነት ገጽታው በመውጣት፣ ወደ ዋነኛ የሀገር ግንባታ፣ የሰላም ማስፋፊያ እና የኅብረ ብሔራዊ አንድነት መገንቢያ ማኅበራዊ መሣሪያነት የተሸጋገረበት ታሪካዊ ምዕራፍ ተመዝግቧል::
ይህ ስትራቴጂያዊ ሽግግር በዘፈቀደ የመጣ ሳይሆን ሀገራችን በራሷ አቅም እና ዕውቀት ላይ መሠረት አድርጋ በነደፈችው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ፖሊሲ ውስጥ ዘርፉን እንደ አንድ ጠንካራ ብሔራዊ ምሰሶ አድርጎ የመቅረጽ ጥልቅ ራዕይ ውጤት ነው
ባለፉት አምስት ዓመታት የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ ከውሱን የገቢ ምንጭነት ገጽታው በመውጣት፣ ወደ ዋነኛ የሀገር ግንባታ፣ የሰላም ማስፋፊያ እና የኅብረ ብሔራዊ አንድነት መገንቢያ ማኅበራዊ መሣሪያነት የተሸጋገረበት ታሪካዊ ምዕራፍ ተመዝግቧል::
ይህ ስትራቴጂያዊ ሽግግር በዘፈቀደ የመጣ ሳይሆን ሀገራችን በራሷ አቅም እና ዕውቀት ላይ መሠረት አድርጋ በነደፈችው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ፖሊሲ ውስጥ ዘርፉን እንደ አንድ ጠንካራ ብሔራዊ ምሰሶ አድርጎ የመቅረጽ ጥልቅ ራዕይ ውጤት ነው
❤4👍3
በጥቃቅንና በንዑስ ቡድኖች የተነሱ የአጀንዳ ሀሳቦች ለስልታዊ ቡድን መቅረብ ጀመሩ
ዛሬ በነበረው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከ16 የባለ 250 አባላት ስልታዊ ከእያንዳንዳቸው የተመረጡ 25 ወኪሎች ከጥቃቅን ቡድኖች እስከ ንዑስ ቡድኖች በነበረው ሂደት የተነሱ የአጀንዳ ሃሳቦችን በቃለ ጉባኤ አጠናቅረው ለባለ 250 ስልታዊ ቡድን ማቅረብ ጀምረዋል፡፡
የበዚህ መድረክ አጀንዳ ሃሳቦች ቀርበው ያልተካተቱ፣ ያልተብራሩና መጨመር የሚገባቸው ከተመካካሪዎች ተነስተው አጠናቃሪዎቹ ሰብስበዋል፡፡
16ቱ ባለ 250 አባላት ስልታዊ ቡድኖች በቀረቡላቸው የአጀንዳ ሃሳች መግባባት ላይ እስሚደርሱ ውይይቱ በሁሉም ቡድኖች በቀጣይ ቀናትም ተጠናክሮ የሚቀጥለ ይሆናል፡፡
ዛሬ በነበረው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከ16 የባለ 250 አባላት ስልታዊ ከእያንዳንዳቸው የተመረጡ 25 ወኪሎች ከጥቃቅን ቡድኖች እስከ ንዑስ ቡድኖች በነበረው ሂደት የተነሱ የአጀንዳ ሃሳቦችን በቃለ ጉባኤ አጠናቅረው ለባለ 250 ስልታዊ ቡድን ማቅረብ ጀምረዋል፡፡
የበዚህ መድረክ አጀንዳ ሃሳቦች ቀርበው ያልተካተቱ፣ ያልተብራሩና መጨመር የሚገባቸው ከተመካካሪዎች ተነስተው አጠናቃሪዎቹ ሰብስበዋል፡፡
16ቱ ባለ 250 አባላት ስልታዊ ቡድኖች በቀረቡላቸው የአጀንዳ ሃሳች መግባባት ላይ እስሚደርሱ ውይይቱ በሁሉም ቡድኖች በቀጣይ ቀናትም ተጠናክሮ የሚቀጥለ ይሆናል፡፡
👍5❤4