+++ "እመቤታችን ከጌታ ዕርገት በኋላ" +++
መድኃኔዓለም ክርስቶስ በቅዱስ መስቀሉ ላይ ባፈሰሰው ክቡር ደሙ የመሠረታትን ቤተ ክርስቲያን ለሐዋርያቱ አደራ ሰጥቷል፡፡ በመጀመሪያው ምዕት ዓመት በነበረው የቤተ ክርስቲያን ሕይወት ውስጥ የጌታ እናቱ እመቤታችን የነበራት ድርሻ ትልቅ ነበር፡፡ ከክርስቶስ ዕርገት በኋላ እመቤታችን በሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ቤት ሳለች፣ የሐዲስ ኪዳኗ ቤተ ክርስቲያን ራስ እና ፈጻሚ የሆነው ክርስቶስ የተገኘባትን እርሷን ለማየት ከሁሉም የዓለም ክፍላት የሚመጡ ሰዎች ብዙ ነበሩ፡፡ ድንግልም ወደ እርሷ የመጡትን ሁሉ እየባረከች፣ ያዘኑትንም እያጽናናች፣ በንስሓ ሕይወት እንዲኖሩ በመምከር ተስፋና ደስታን እየሞላች ትሸኛቸው ነበር፡፡ በርግጥም እግዚአብሔር ሰው ሆኖ በምድር ላይ ለመገለጡ፣ እንደ ሕፃናት ጥቂት በጥቂት ለማደጉና በመጨረሻም ለፈጸመው የቤዛነት ሥራው ሁሉ እናቱና አገልጋዩ ከምትሆን ከእመቤታችን የበለጠ ምስክር ከየት ሊመጣ? እርሷን ለማየት ባይጓጉ ነበር የሚደንቀን፡፡
ከሰባ ሁለቱ አርድዕት አንዱ የሆነው ቅዱስ ሉቃስም ወንጌሉን ሲጽፍ በሕይወቷ ውስጥ የተፈጸሙ እርሷ ብቻ የምታውቃቸውንና ብቻዋን ሆና የሰማቻቸውን እንደ ብሥራት ያሉ ታሪኮችን በመንገር እረድታዋለች፡፡ ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ በቃልም በመጽሐፍም አይሁድን ተከራክሮ ድል ባደረጋቸው ጊዜ፣ ተቆጥተው ድንጋይ ሲያነሡበትና ሲከቡት ከሩቅ በማየቷ የሰማዕትነት ሥራውን በጽናት ይፈጽም ዘንድ በጸሎቷ እንዳበረታችው በጥንታውያን የታሪክ መዛግብት ሰፍሮ እናገኛለን፡፡
እመቤታችንን የማየት ዕድል ካገኙት አንዱ የሆነው ቅዱስ ዲዮናስዮስ ዘአርዮስፋጎስ እርሷን ባየ ጊዜ ሐዋርያቱ ሰው መሆኗን ባይነግሩት ኖሮ አምላክ መስላው እንደ ነበር ጽፏል፡፡ የፊቷን ደም ግባትና ሰላም፣ በእርሷም ላይ ይንጸባረቅ የነበረውን የቅድስና ብርሃን አይቶ በልጇ የማያምን እንደ ሌለም መስክሯል፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ደቀ መዝሙርና የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳስ የነበረው ቅዱስ አግናጥዮስም ለመምህሩ (ቅዱስ ዮሐንስ) በላከለት መልእክት፣ ክርስቲያኖች በሚሳደዱበት በዚያ ዘመን የእግዚአብሔር እናቱ እመቤታችን በስደቱ ደስተኛ እንደ ሆነች፣ በመከራዎችም ውስጥ ሆና እንደማታጉረመርምና እርሷንም ይነቅፉ በነበሩ ሰዎች እንዳልተቆጣች ይናገራል፡፡
እመቤታችን በልጇ ሕይወት ውስጥ ወሳኝ ታሪኮች የተፈጸሙባቸውን ስፍራዎች መጎብኘት ትወድ ነበር፡፡ የልደቱን ነገር፣ የእረኞችና የመላክቱን ዝማሬ፣ የጥበበኞቹን ስጦታ አስባ ቤተልሔም ትሄዳለች፡፡ ከሁሉም በላይ ግን መከራ ወደ ተቀበለበት ስፍራ መሄድ ታዘወትራለች፡፡ በዚያም የተቀበላቸውን ሕማማት፣ የደረሰበትን ተዋርዶ እና መከዳቱን እያሰበች ታነባለች፡፡ ‹ይህ ልጄ የተገረፈበት፣ ይህ የእሾህ አክሊል የተቀዳጀበት፣ ይህ ደግሞ መስቀል ተሸክሞ የሄደበት፣ ይህ የተሰቀለበት ነው› ትላለች፡፡ ወደ መቃብሩ ስፍራ ስትመጣ ግን በልዩ ደስታ እየተሞላች ‹‹ይህ በሦስተኛው ቀን ከሞት የተነሣበት ቦታ ነው›› ትል ነበር፡፡
በተሰጣት ቃል ኪዳን እኛ ኃጥአን የሆንን ልጆቿን ታስምረን!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
abelzebahiran@gmail.com
አዲስ አበባ
መድኃኔዓለም ክርስቶስ በቅዱስ መስቀሉ ላይ ባፈሰሰው ክቡር ደሙ የመሠረታትን ቤተ ክርስቲያን ለሐዋርያቱ አደራ ሰጥቷል፡፡ በመጀመሪያው ምዕት ዓመት በነበረው የቤተ ክርስቲያን ሕይወት ውስጥ የጌታ እናቱ እመቤታችን የነበራት ድርሻ ትልቅ ነበር፡፡ ከክርስቶስ ዕርገት በኋላ እመቤታችን በሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ቤት ሳለች፣ የሐዲስ ኪዳኗ ቤተ ክርስቲያን ራስ እና ፈጻሚ የሆነው ክርስቶስ የተገኘባትን እርሷን ለማየት ከሁሉም የዓለም ክፍላት የሚመጡ ሰዎች ብዙ ነበሩ፡፡ ድንግልም ወደ እርሷ የመጡትን ሁሉ እየባረከች፣ ያዘኑትንም እያጽናናች፣ በንስሓ ሕይወት እንዲኖሩ በመምከር ተስፋና ደስታን እየሞላች ትሸኛቸው ነበር፡፡ በርግጥም እግዚአብሔር ሰው ሆኖ በምድር ላይ ለመገለጡ፣ እንደ ሕፃናት ጥቂት በጥቂት ለማደጉና በመጨረሻም ለፈጸመው የቤዛነት ሥራው ሁሉ እናቱና አገልጋዩ ከምትሆን ከእመቤታችን የበለጠ ምስክር ከየት ሊመጣ? እርሷን ለማየት ባይጓጉ ነበር የሚደንቀን፡፡
ከሰባ ሁለቱ አርድዕት አንዱ የሆነው ቅዱስ ሉቃስም ወንጌሉን ሲጽፍ በሕይወቷ ውስጥ የተፈጸሙ እርሷ ብቻ የምታውቃቸውንና ብቻዋን ሆና የሰማቻቸውን እንደ ብሥራት ያሉ ታሪኮችን በመንገር እረድታዋለች፡፡ ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ በቃልም በመጽሐፍም አይሁድን ተከራክሮ ድል ባደረጋቸው ጊዜ፣ ተቆጥተው ድንጋይ ሲያነሡበትና ሲከቡት ከሩቅ በማየቷ የሰማዕትነት ሥራውን በጽናት ይፈጽም ዘንድ በጸሎቷ እንዳበረታችው በጥንታውያን የታሪክ መዛግብት ሰፍሮ እናገኛለን፡፡
እመቤታችንን የማየት ዕድል ካገኙት አንዱ የሆነው ቅዱስ ዲዮናስዮስ ዘአርዮስፋጎስ እርሷን ባየ ጊዜ ሐዋርያቱ ሰው መሆኗን ባይነግሩት ኖሮ አምላክ መስላው እንደ ነበር ጽፏል፡፡ የፊቷን ደም ግባትና ሰላም፣ በእርሷም ላይ ይንጸባረቅ የነበረውን የቅድስና ብርሃን አይቶ በልጇ የማያምን እንደ ሌለም መስክሯል፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ደቀ መዝሙርና የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳስ የነበረው ቅዱስ አግናጥዮስም ለመምህሩ (ቅዱስ ዮሐንስ) በላከለት መልእክት፣ ክርስቲያኖች በሚሳደዱበት በዚያ ዘመን የእግዚአብሔር እናቱ እመቤታችን በስደቱ ደስተኛ እንደ ሆነች፣ በመከራዎችም ውስጥ ሆና እንደማታጉረመርምና እርሷንም ይነቅፉ በነበሩ ሰዎች እንዳልተቆጣች ይናገራል፡፡
እመቤታችን በልጇ ሕይወት ውስጥ ወሳኝ ታሪኮች የተፈጸሙባቸውን ስፍራዎች መጎብኘት ትወድ ነበር፡፡ የልደቱን ነገር፣ የእረኞችና የመላክቱን ዝማሬ፣ የጥበበኞቹን ስጦታ አስባ ቤተልሔም ትሄዳለች፡፡ ከሁሉም በላይ ግን መከራ ወደ ተቀበለበት ስፍራ መሄድ ታዘወትራለች፡፡ በዚያም የተቀበላቸውን ሕማማት፣ የደረሰበትን ተዋርዶ እና መከዳቱን እያሰበች ታነባለች፡፡ ‹ይህ ልጄ የተገረፈበት፣ ይህ የእሾህ አክሊል የተቀዳጀበት፣ ይህ ደግሞ መስቀል ተሸክሞ የሄደበት፣ ይህ የተሰቀለበት ነው› ትላለች፡፡ ወደ መቃብሩ ስፍራ ስትመጣ ግን በልዩ ደስታ እየተሞላች ‹‹ይህ በሦስተኛው ቀን ከሞት የተነሣበት ቦታ ነው›› ትል ነበር፡፡
በተሰጣት ቃል ኪዳን እኛ ኃጥአን የሆንን ልጆቿን ታስምረን!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
abelzebahiran@gmail.com
አዲስ አበባ
❤232🙏21❤🔥4👍4🔥3🥰2😁1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
እግዚአብሔር አሕዛብ ያለ ሐዋርያት ስብከት በሥላሴ ማመን እንደማይችሉ፣ ሐዋርያትም ያለ መንፈስ ቅዱስ መውረድ በየአገሩ ቋንቋዎች ሁሉ መስበክ እንደማይችሉ ዐወቀ፡፡ ስለዚህም በሰናዖር ሜዳ የተበተኑትን የዓለምን ቋንቋዎች በሐዋርያት አንደበት ሰብስቦ ያኖር ዘንድ ቅዱስ መንፈሱን ላከ፡፡ የተላከውም መንፈስ ያለ አንድ ቋንቋ የማይናገረውን የሐዋርያቱን አንደበት በቅጽበት አሰለጠነው። በእውነት እንደ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ያለ አስማሪ ማን ነው?!በዚህችም እለት ሐዋርያቱ በዓለም ሁሉ ቋንቋዎች ተሞልተው ከእርሷ የወጡባት የጽዮን አዳራሽ (ጽርሐ ጽዮን) እንደ ምን ያለች ናት?! መንፈስ ቅዱስ ከዚያም በፊት ከዚያም በኋላ ታይታ የማትታወቅ ልዩ ትምህርት ቤት አደረጋት፡፡
ሐዋርያቱም በመንፈስ ቅዱስ ተሟሙቀው በሰበኩት በመጀመሪያ ዕለት ስበከት ብዙዎችን አሳምነው አጠመቁ። በዚህ የመከር በዓል አይሁድ ከአዲሱ እህል ለእግዚአብሔር ቁርባን ሲያቀርቡ፣ ሐዋርያቱ ግን የክርስቶስ አካል ለሆነችው ለሐዲሲቷ ቤተ ክርስቲያን ከእህል ቁርባን ይልቅ የሚወደዱ ምእመናንን ስጦታ አድርገው አቀረቡ። በአይሁድ የመከር በዓል ቀን በሐዋርያቱ በተሰጠ ትምህርት የእግዚአብሔር እርሻ የሆኑ ምዕመናን በዝተው አብበው ተገኙ። እውነትም የመከር በዓል!!!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
abelzebahiran@gmail.com
ሐዋርያቱም በመንፈስ ቅዱስ ተሟሙቀው በሰበኩት በመጀመሪያ ዕለት ስበከት ብዙዎችን አሳምነው አጠመቁ። በዚህ የመከር በዓል አይሁድ ከአዲሱ እህል ለእግዚአብሔር ቁርባን ሲያቀርቡ፣ ሐዋርያቱ ግን የክርስቶስ አካል ለሆነችው ለሐዲሲቷ ቤተ ክርስቲያን ከእህል ቁርባን ይልቅ የሚወደዱ ምእመናንን ስጦታ አድርገው አቀረቡ። በአይሁድ የመከር በዓል ቀን በሐዋርያቱ በተሰጠ ትምህርት የእግዚአብሔር እርሻ የሆኑ ምዕመናን በዝተው አብበው ተገኙ። እውነትም የመከር በዓል!!!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
abelzebahiran@gmail.com
❤169🙏10👍9👏1
አዳም "አትብላ" ለሚለው የመጀመሪያ ድምጽ ቢታዘዝ ኖሮ፣ "አፈር ነህና፥ ወደ አፈርም ትመለሳለህ" የሚለውን ሁለተኛውን ድምጽ ባልሰማ ነበር።
"ነገ እንሞታለንና እንብላ እንጠጣ" የሚለውን የዐሣማ ፍልስፍና (pig philosophy) እንተው።
"ነገ እንሞታለንና እንጹም!"
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
abelzebahiran@gmail.com
"ነገ እንሞታለንና እንብላ እንጠጣ" የሚለውን የዐሣማ ፍልስፍና (pig philosophy) እንተው።
"ነገ እንሞታለንና እንጹም!"
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
abelzebahiran@gmail.com
❤333🙏40🥰16😢4👏3
በመንገድ እየሄድህ ሳለ በድልድይ ስር ስታልፍ ድንገት ከላይ የሚንጠባጠብ የቆሸሸ ውኃ ቢነካህ ሁኔታው ሊያናድድህ ይችላል። ነገር ግን ያ ቦታ እንደሚያፈስ እያወቅህ ተመላልሰህበት ከበሰበስህ ግን ጥፋቱ የአንተ እንጂ የማንም አይደለም። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደሚለው አንዳንዴ ልክ እንደዚያ ጠብታ ሰይጣን ወደ ኅሊናህ ሊያስገባ የሚሞክረው ነፍስህን የሚያቆሽሽ ክፉ ሐሳብ ይኖራል። አንዴ የነካህ ክፉ ሐሳብ ግን ተመላልሶ እንዲያቆሽሽህ ከፈቀድህ ተወቃሹ አንተ እንጂ ሰይጣን አይሆንም።
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
❤290🙏25👍16🔥3
“በዚህም ነገር ከአለቃችሁ ከሚካኤል በቀር ማንም የሚያጸናኝ የለም።”
ዳን 10:21
እንኳን አደረሰን!
ዳን 10:21
እንኳን አደረሰን!
❤341🙏24🥰10
“ለዘላለም የሚኖር ስሙም ቅዱስ የሆነ፥ ከፍ ያለው ልዑል እንዲህ ይላል፦ የተዋረዱትን ሰዎች መንፈስ ሕያው አደርግ ዘንድ፥ የተቀጠቀጠውንም ልብ ሕያው አደርግ ዘንድ፥ የተቀጠቀጠና የተዋረደ መንፈስ ካለው ጋር በከፍታና በተቀደሰ ስፍራ እቀመጣለሁ”
ኢሳይያስ 57:15
ኢሳይያስ 57:15
❤215🙏12👏7
ፀሐይ ናላ በምታዞርበት እና ሁሉም ለማረፍ ወደ አልጋው በሚሽቀዳደምበት በቀትር ሰዓት አብርሃም ግን በድንኳኑ ደጃፍ ላይ ተቀምጦ እንግዳ በተስፋ ይጠባበቅ ነበር።(ዘፍ 18) በዚህ የቃጠሎ ጊዜ (ስድስት ሰዓት) መንገድ ላይ የሚገኝ ሰው ወይ ምንም ማረፊያ የሌለው ምስኪን ነው፣ አለዚያ ደግሞ እንደዚያች ሳምራዊት ሴት ከሰው የተገለለ ብቸኛ ነው።(ዮሐ 4፥6) አብርሃም ድንኳኑን ያሰናዳው ያማረ ለለበሱ፣ ብድር ለሚመልሱ፣ በመልክም በገንዘብም ዓይን ውስጥ ለሚገቡ ሰዎች ሳይሆን፣ ሰው ለሸሻቸው መጠጊያ ለሌላቸው እና በፀሐይ ንዳድ እየተንገበገቡ ማረፊያ ፈልገው ለሚዞሩ አስታዋሽ አልባ ምስኪኖች ነበር።
አብርሃም በደጁ የሚያልፉ ምስኪን እንግዶቹን “ና እስኪ” ብሎ በማቃለል ቃል አይጠራቸውም። እየሮጠ ወደ እነርሱ ሄዶ “ጌቶች (እመቤት) እባካችሁ ወደ ቤቴ ግቡልኝ” ብሎ በትሕትና ይለምናቸዋል እንጂ።
ይህንን ግን በምን አወቅን? በሦስት ሰዎች ተመስለው ወደ ቤቱ ቅድስት ሥላሴ በመጡ ጊዜ አብርሃም እነርሱን ያስተናገደበትን መንገድ አይተን ተረዳን። አብርሃም በዚህች ቀን ተዘጋጅቶ ይጠብቅ የነበረው ሰውን እንጂ እግዚአብሔርን አልነበረም። እግዚአብሔር ግን አብርሃም ለምስኪናኑ ያሳይ የነበረው ቸርነቱን አይቶ በቤቱ ሊስተናገድ ወደደ።
አብርሃም ለድሆች ሲል በከፈተው በር በኩል በመካንነት ምክንያት የተዘጋውን የሣራን ማኅፀን የሚከፍት የሠራዊት ጌታ ገባለት።
የአንተን የብዙ ዓመታት ጥያቄ ለመመለስ እግዚአብሔር ወደ ሕይወትህ የሚገባው፣ ለሌሎች ሰዎች ብለህ በከፈትኸው የመልካምነት እና የቅንነት በር በኩል ነው።
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
ሐምሌ ቅድስት ሥላሴ -2017 ዓ.ም.
https://tttttt.me/Dnabel
እንኳን አደረሳችሁ!
አብርሃም በደጁ የሚያልፉ ምስኪን እንግዶቹን “ና እስኪ” ብሎ በማቃለል ቃል አይጠራቸውም። እየሮጠ ወደ እነርሱ ሄዶ “ጌቶች (እመቤት) እባካችሁ ወደ ቤቴ ግቡልኝ” ብሎ በትሕትና ይለምናቸዋል እንጂ።
ይህንን ግን በምን አወቅን? በሦስት ሰዎች ተመስለው ወደ ቤቱ ቅድስት ሥላሴ በመጡ ጊዜ አብርሃም እነርሱን ያስተናገደበትን መንገድ አይተን ተረዳን። አብርሃም በዚህች ቀን ተዘጋጅቶ ይጠብቅ የነበረው ሰውን እንጂ እግዚአብሔርን አልነበረም። እግዚአብሔር ግን አብርሃም ለምስኪናኑ ያሳይ የነበረው ቸርነቱን አይቶ በቤቱ ሊስተናገድ ወደደ።
አብርሃም ለድሆች ሲል በከፈተው በር በኩል በመካንነት ምክንያት የተዘጋውን የሣራን ማኅፀን የሚከፍት የሠራዊት ጌታ ገባለት።
የአንተን የብዙ ዓመታት ጥያቄ ለመመለስ እግዚአብሔር ወደ ሕይወትህ የሚገባው፣ ለሌሎች ሰዎች ብለህ በከፈትኸው የመልካምነት እና የቅንነት በር በኩል ነው።
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
ሐምሌ ቅድስት ሥላሴ -2017 ዓ.ም.
https://tttttt.me/Dnabel
እንኳን አደረሳችሁ!
❤209🙏50🔥7🥰6
+++ የሚያክም መጽሐፍ +++
የአሁን ዘመን ፈተና ትኩረትን መረጃ ላይ ማድረግ ነው። ሰው የሚያነበው መረጃ ለመሰብሰብ ለማከማቸት ሆኗል። ይህ ደግሞ ያደግንበት እና የተማርንበት ተጽዕኖ ሊሆን ይችላል። ነገሩ ሲደጋገም ደግሞ ዕውቀት ይህ ብቻ ይመስለናል። ንባባችን ሁሉ መረጃን ለመቃረም እንደ ሆነ ማሰብ እንጀምራለን። እንዲህ ከሆነ ደግሞ እጅግ እንጎዳለን።
መጻሕፍት በጥሩ ጥናት በደንብ የተጣራ መረጃ እና ወደ ሕይወታችን ልንመልሳቸው የሚገቡ ተግባራዊነት ያላቸው እዝናት ሊይዝ ይገባዋል። ብዙ ጊዜ የሚዘጋጁ መጻሕፍት ግን ወደ አንዱ ሲያጋድሉ እንታዘባለን። የመምህር አቤል መጽሐፍ እንደ ዕድል ሆኖ ሁለቱን አስተባብሮ በመያዝ የነፍሳችንን ጥያቄ ይመልስልናል። መጽሐፉ ንባብም ሕይወትም አለው። ሕይወቱ ደግሞ የቅዱስ ጳውሎስ ነው።
አሁን ላይ ከአባቶች የራቅነው በዘመን ብቻ አይመስለኝም። በአስተሳሰብም ጭምር ነው። ይህን የምንረዳው የቀደሙትን አባቶች መጽሐፍ ስናነብ ነው። ሐሳባቸው፣ ሥነ ጽሑፋቸው፣ ንግግራቸው፣ አገላለጻቸው፣ አንባቢው ላይ የሚፈጥሩት ስሜት ለየት ያለ ነው። አንባቢው ከእነርሱ ጋር ያለውን የቦታ እና የጊዜ ርቀት የሚያስረሳ ነው። ለምሳሌ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ ጳውሎስ መልዕክታት ሲጽፍ፣ ይህንን ስሜት ያጋባብናል። መረጃ ከመሰብሰብ ይልቅ፣ በመንፈስ ይወስደናል፣ ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር በሕይወቱ ሳለ የተገናኘን ያህል ይሰማናል። ይህንን የመሰለ ተዋሕዶ ለማግኘት አንድ ሰው በመጽሐፍ ቅዱስ እና በቀደሙት አባቶች ድርሰት ውስጥ ራሱን ቀንና ማታ ማጥመቅ አለበት።
በተለይ ደግሞ ወደ ቅዱስ ጳውሎስ ስንመጣ የበለጠ ተመስጦ ያስፈልጋል፣ ብዙዎችም ሞክረውት አልተሳካም። ጳውልስን ለመረዳት እንደነ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ዓይነት የመንፈስ ልዕልና ይፈልጋል። መምህር አቤል ከአባቶቹ እግር ተጠግቶ ይህን መልካሙን ዜና፣ ምርጡን ዘር አቅርቦልናል። መምህር አቤል ከቅዱስ ዮሐንስ አፈውርቅ፣ ከቅዱስ ኤፍሬም፣ ከቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ጋር ባደረገው ተመስጦ ለቅዱስ ጳውሎስ ራሱን ሲያዘጋጅ ቆይቶ ኖሯል። አሁን ይህን የመጽሐፍ ማር ጋግሮ እነሆ ብሉ ይለናል።
ይህ መጽሐፍ ዝም ብሎ የሚነበብ መጽሐፍ አይደለም። ራሱን ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር ማዛመድ ለሚፈልግ ሁሉ የተሰጠ መስኮት ነው። በዚህ መስኮት ቅዱስ ጳውሎስን ከልጅነት ጅምሮ አብረነው እናድጋለን። በመካከልም ቆም እያልን ልክ እንደ 3D ፊልም፣ ታሪኩን ቃኘት ቃኘት እናደርጋለን። ስለዚህ ለተመስጦ የሚመች ቦታ እና ጊዜ መድቦ የሚነበብ መሆን አለበት። ቤተክርስቲያን ሁሌም ከቅዱሳን ጋር ኅብረት እንዳለን ታስተምረናለች። ይህን እውነታ በደንብ የተረዳሁት በዚህ መጽሐፍ ነው። መጽሐፉ ነጥቆ ከ2ሺ ዓመት በፊት ይወስድና ከጳውሎስ ጋር ያገናኘናል። ቅዱስ ጳውሎስ በተከላቸው አብያተ ክርስቲያናት አብረነው እንድንጓዝ ያደርገናል። በዚህ ጉዞውም ውስጥ የጳውሎስ መልዕክታት ፍንትው ብለው ይገለጻሉ። ጳውሎስን በጥቅሶቹ ብቻ ሳይሆን ከነአንድምታው ያጠጣናል። አሁን እኛ ጥቅስ በመማዘዝ ሐዋርያውን ካልተረዱት ወገኖች ጋር ክርክር በመግጠማችን የቅዱስ ጳውሎስን አሳዛኝ ሕይወት እንዳንመረምር የዓይን ሞራ የመሰለ ግርዶሽ ተጥሎብናል። ይህ መጽሐፍ የዓይን ሐኪም ሆኖ እንዳናስተውል የተጋረደብንን ሞራ ይገፍልናል። መጽሐፉ ጳውሎስን ማሳየት ብቻ ሳይሆን፣ በጉዞው ውስጥ አብረን ከድካሙ፣ ከደስታው፣ ከኀዘኑ ጋር እንድንካፈል ዕድል ይሰጠናል። ልቡን ለከፈተ ሰው ደግሞ የጳውሎስን ልብ ከልቡ ከፍቅሩን ከፍቅሩ እንዲዋሐድ ያደርገዋል።
ጥሪው እኔም ደርሶኛል።
እናንተም:- ኑ የጳውሎስ የፍቅሩ ማኅበርተኛ እንሁን።
መልካም ንባብ!
ዲ/ን ዶ/ር ቶማስ ሺመልስ
የአሁን ዘመን ፈተና ትኩረትን መረጃ ላይ ማድረግ ነው። ሰው የሚያነበው መረጃ ለመሰብሰብ ለማከማቸት ሆኗል። ይህ ደግሞ ያደግንበት እና የተማርንበት ተጽዕኖ ሊሆን ይችላል። ነገሩ ሲደጋገም ደግሞ ዕውቀት ይህ ብቻ ይመስለናል። ንባባችን ሁሉ መረጃን ለመቃረም እንደ ሆነ ማሰብ እንጀምራለን። እንዲህ ከሆነ ደግሞ እጅግ እንጎዳለን።
መጻሕፍት በጥሩ ጥናት በደንብ የተጣራ መረጃ እና ወደ ሕይወታችን ልንመልሳቸው የሚገቡ ተግባራዊነት ያላቸው እዝናት ሊይዝ ይገባዋል። ብዙ ጊዜ የሚዘጋጁ መጻሕፍት ግን ወደ አንዱ ሲያጋድሉ እንታዘባለን። የመምህር አቤል መጽሐፍ እንደ ዕድል ሆኖ ሁለቱን አስተባብሮ በመያዝ የነፍሳችንን ጥያቄ ይመልስልናል። መጽሐፉ ንባብም ሕይወትም አለው። ሕይወቱ ደግሞ የቅዱስ ጳውሎስ ነው።
አሁን ላይ ከአባቶች የራቅነው በዘመን ብቻ አይመስለኝም። በአስተሳሰብም ጭምር ነው። ይህን የምንረዳው የቀደሙትን አባቶች መጽሐፍ ስናነብ ነው። ሐሳባቸው፣ ሥነ ጽሑፋቸው፣ ንግግራቸው፣ አገላለጻቸው፣ አንባቢው ላይ የሚፈጥሩት ስሜት ለየት ያለ ነው። አንባቢው ከእነርሱ ጋር ያለውን የቦታ እና የጊዜ ርቀት የሚያስረሳ ነው። ለምሳሌ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ ጳውሎስ መልዕክታት ሲጽፍ፣ ይህንን ስሜት ያጋባብናል። መረጃ ከመሰብሰብ ይልቅ፣ በመንፈስ ይወስደናል፣ ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር በሕይወቱ ሳለ የተገናኘን ያህል ይሰማናል። ይህንን የመሰለ ተዋሕዶ ለማግኘት አንድ ሰው በመጽሐፍ ቅዱስ እና በቀደሙት አባቶች ድርሰት ውስጥ ራሱን ቀንና ማታ ማጥመቅ አለበት።
በተለይ ደግሞ ወደ ቅዱስ ጳውሎስ ስንመጣ የበለጠ ተመስጦ ያስፈልጋል፣ ብዙዎችም ሞክረውት አልተሳካም። ጳውልስን ለመረዳት እንደነ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ዓይነት የመንፈስ ልዕልና ይፈልጋል። መምህር አቤል ከአባቶቹ እግር ተጠግቶ ይህን መልካሙን ዜና፣ ምርጡን ዘር አቅርቦልናል። መምህር አቤል ከቅዱስ ዮሐንስ አፈውርቅ፣ ከቅዱስ ኤፍሬም፣ ከቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ጋር ባደረገው ተመስጦ ለቅዱስ ጳውሎስ ራሱን ሲያዘጋጅ ቆይቶ ኖሯል። አሁን ይህን የመጽሐፍ ማር ጋግሮ እነሆ ብሉ ይለናል።
ይህ መጽሐፍ ዝም ብሎ የሚነበብ መጽሐፍ አይደለም። ራሱን ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር ማዛመድ ለሚፈልግ ሁሉ የተሰጠ መስኮት ነው። በዚህ መስኮት ቅዱስ ጳውሎስን ከልጅነት ጅምሮ አብረነው እናድጋለን። በመካከልም ቆም እያልን ልክ እንደ 3D ፊልም፣ ታሪኩን ቃኘት ቃኘት እናደርጋለን። ስለዚህ ለተመስጦ የሚመች ቦታ እና ጊዜ መድቦ የሚነበብ መሆን አለበት። ቤተክርስቲያን ሁሌም ከቅዱሳን ጋር ኅብረት እንዳለን ታስተምረናለች። ይህን እውነታ በደንብ የተረዳሁት በዚህ መጽሐፍ ነው። መጽሐፉ ነጥቆ ከ2ሺ ዓመት በፊት ይወስድና ከጳውሎስ ጋር ያገናኘናል። ቅዱስ ጳውሎስ በተከላቸው አብያተ ክርስቲያናት አብረነው እንድንጓዝ ያደርገናል። በዚህ ጉዞውም ውስጥ የጳውሎስ መልዕክታት ፍንትው ብለው ይገለጻሉ። ጳውሎስን በጥቅሶቹ ብቻ ሳይሆን ከነአንድምታው ያጠጣናል። አሁን እኛ ጥቅስ በመማዘዝ ሐዋርያውን ካልተረዱት ወገኖች ጋር ክርክር በመግጠማችን የቅዱስ ጳውሎስን አሳዛኝ ሕይወት እንዳንመረምር የዓይን ሞራ የመሰለ ግርዶሽ ተጥሎብናል። ይህ መጽሐፍ የዓይን ሐኪም ሆኖ እንዳናስተውል የተጋረደብንን ሞራ ይገፍልናል። መጽሐፉ ጳውሎስን ማሳየት ብቻ ሳይሆን፣ በጉዞው ውስጥ አብረን ከድካሙ፣ ከደስታው፣ ከኀዘኑ ጋር እንድንካፈል ዕድል ይሰጠናል። ልቡን ለከፈተ ሰው ደግሞ የጳውሎስን ልብ ከልቡ ከፍቅሩን ከፍቅሩ እንዲዋሐድ ያደርገዋል።
ጥሪው እኔም ደርሶኛል።
እናንተም:- ኑ የጳውሎስ የፍቅሩ ማኅበርተኛ እንሁን።
መልካም ንባብ!
ዲ/ን ዶ/ር ቶማስ ሺመልስ
❤99👏3👍1