#Adawa #አብን
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ለንቅናቄያችን አባላትና ደጋፊዎች፣ ለአማራ እና መላ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንኳን ለ124ኛው የአድዋ የድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ ይላል፤
አፍሪካን እንደ ቅርጫ ሥጋ ለመከፋፈል የአውሮጳ ሃያላን በጀርመን በርሊን ኮንፈረንስ ከተሰባሰቡና ስምምነት ላይ ከደረሱ በኋላ ጣሊያን ኢትዮጵያን ቅኝ ግዛት ለማድረግና ሀብቷን ለመመዝበር፣ በሂደትም ኮሎኒያሊስት ሰፋሪዎችን አየሩ ተስማሚ በሆነው በኢትዮጵያ ደጋማ መሬቶች ለማስፈር ቋመጠች። ኢትዮጵያን አንበርክካ የቅኝ ግዛትን ኅልሟን ለማሳካት የጦር ክተት ዘመቻዋን አወጀች፡፡
ጠንቃቃና ብልህ የነበሩት የወቅቱ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገሥት ግርማዊ ዳግማዊ አፄ ምኒሊክ (እምየ ምኒሊክ) የፋሽስት ጣሊያንን ኅልም ለማምከን መስከረም 17 ቀን 1888 ዓ.ም ሕዝባቸው ለአገሩ ነፃነትና ለማንነቱ እንዲፋለም ብሔራዊ የክተት ዘመቻ ጥሪ አወጁ፡፡
ተጨማሪ⬇️
https://telegra.ph/Adawa-03-01-2
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ለንቅናቄያችን አባላትና ደጋፊዎች፣ ለአማራ እና መላ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንኳን ለ124ኛው የአድዋ የድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ ይላል፤
አፍሪካን እንደ ቅርጫ ሥጋ ለመከፋፈል የአውሮጳ ሃያላን በጀርመን በርሊን ኮንፈረንስ ከተሰባሰቡና ስምምነት ላይ ከደረሱ በኋላ ጣሊያን ኢትዮጵያን ቅኝ ግዛት ለማድረግና ሀብቷን ለመመዝበር፣ በሂደትም ኮሎኒያሊስት ሰፋሪዎችን አየሩ ተስማሚ በሆነው በኢትዮጵያ ደጋማ መሬቶች ለማስፈር ቋመጠች። ኢትዮጵያን አንበርክካ የቅኝ ግዛትን ኅልሟን ለማሳካት የጦር ክተት ዘመቻዋን አወጀች፡፡
ጠንቃቃና ብልህ የነበሩት የወቅቱ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገሥት ግርማዊ ዳግማዊ አፄ ምኒሊክ (እምየ ምኒሊክ) የፋሽስት ጣሊያንን ኅልም ለማምከን መስከረም 17 ቀን 1888 ዓ.ም ሕዝባቸው ለአገሩ ነፃነትና ለማንነቱ እንዲፋለም ብሔራዊ የክተት ዘመቻ ጥሪ አወጁ፡፡
ተጨማሪ⬇️
https://telegra.ph/Adawa-03-01-2