YeneTube
119K subscribers
31.3K photos
483 videos
79 files
3.85K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
YeneTube
የፌደራል ቴክኒክ እና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኤጀንሲ የ2011 የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ተቋማት #መቀበያ ነጥብ ይፋ አድርጓል። @yenetube @mycase27
ኤጀንሲው የቴክኒክና ሙያ ተቋማት መቀበያ ነጥብ #ይፋ አደረገ

የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኤጀንሲ በ2011 ወደ ቴክኒክና ሙያ ተቋማት መግቢያ ነጥብን ይፋ #አድርጓል፡፡

ኤጀንሲው ዛሬ እንዳስታወቀው በየዓመቱ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት #መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ተፈታኞች መካከል የሥራ ገበያውን መሰረት በማድረግ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት መቀበያ መስፈርት ተመርኩዞ የመቁረጫ ነጥቡን ይፋ እንዳደረገ አመልክቷል፡፡

በዚህም መሰረት በ2010 የትምህርት ዘመን የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱት መካከል 725 ሺህ 652 የሚሆኑት ወደ ቴክኒክና ሙያ ተቋማት በመደበኛው ዘርፍ እንደሚገቡ ኤጀንሲው አመልክቷል፡፡

ከዚህም ውስጥ 230 ሺህ 828 ሴቶች ናቸው፡፡ በመምህራን ኮሌጅ እንዲሁም በፖሊስና መከላከያ ማሰልጠኛ ተቋማት የሚገቡት ቁጥር በዚህ መግለጫ አለመካተቱም ተመልክቷል፡፡

ምንጭ፡የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኤጀንሲ
@yenetube @mycase27
ሰበር ዜና ‼️

ታከለ ኡማና እስክንድር ነጋ ተገናኙ

❇️ህዝባዊ ስብሰባዎች እንዲፈቀዱ ተስማሙ❇️

በዛሬው ዕለት፣ መጋቢት 30/ ቀን 2011 ዓ.ም፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማና የአዲስ አበባ ባለአደራ ምክር ቤት ሰብሳቢ እስክንድር ነጋ ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል፡፡

በውይይቱ ወቅት፣ እንደመነሻ ሃሳብ ሆኖ፣ በአዲስ አበባ ጉዳይ ልዩነቶች እንዳሉ፣ ልዩነቶች ግን በሰላማዊ መንገድ መፈታት እንዳለባቸው ተስማምተዋል፡፡
በቀጣይነትም፣ ወደዋነው አጀንዳ ለመግባት፣ መጋቢት 1 ቀን 2011 ዓ.ም በባልደራስ አዳራሽ የተሰበሰቡ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ያወጡትን የአቋም መግለጫ በፅሁፍ እንዲቀበሉ በእስክንድር በኩል ጥያቄ የቀረበ ሲሆን፣ አቶ ታከለ ጥያቄውን ለመቀበል ፈቃደኛ #አለመሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ እስክንድርም ለአቶ ታከለ በሰጠው ምላሽ፣ የህዝቡን #ጥያቄ እንዳልተቀበሉ ለህዝብ #ይፋ_እንደሚደረግ ገልፆላቸዋል፡፡

በአዲስ አበባ ጉዳይ ያሉትን ልዩነቶች በሰላማዊ መንገድ መፍታት እንዲያስችል፣ ህዝባዊ ስብሰባዎች ሊፈቀዱ እንደሚገባ በእስክንድር በኩል ሃሳብ ቀርቦ፤ አቶ ታከለ ኡማ ሃሳቡን ሙሉ በሙሉ ተቀብለው ከከተማዋ #የፀጥታ ኃላፊ #ጋር_በስልክ_አገናኝተውታል፡፡ በዚህ መልክ ህዝባዊ ስብሰባዎች ያለምንም ችግር እንዲደረጉ ከከተማዋ ባለስልጣናት ጋር ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡

በዚህም መሰረት፣ ከሚቀጥለው #ቅዳሜና_እሁድ_ጀምሮ፣ በየክፍለ ከተሞች በሚጠሩ ህዝባዊ ስብሳባዎች በኩል የአደረጃጀት ስራ የሚጀምር መሆኑን እንገልፃለን፡፡


የአዲስ አበባ ባለአደራ ምክር ቤት (ባልደራስ)
አዲስ አበባ
መጋቢት 30/2011 ዓ.ም
@YeneTube @FikerAssefa
የ 12 ክፍል የተስተካከለሁ SAT #ይፋ መሆኑን ተማሪዎች እየጠቆሙን ይገኛል እንደ ተለመደው ውጤታችሁን ማየት ትችላላችሁ።
@YeneTube @Fikerassefa