#Ethiopia #Sport በዓምላክ ተሰማ የአፍሪካ ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታን እንዲመራ ተመረጠ
በአፍሪካ ዋንጫ ወሳኝ ጨዋታዎችን እየዳኘ
የሚገኘው ኢትዮጵያዊው በዓምላክ ተሰማ
የፍፃሜው ጨዋታ እንዲመራ በካፍ የዳኞች
ኮሚቴ ተመርጧል።
በግብፅ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው
ውድድር ሁለት የምድብ፣ አንድ የሩብ ፍፃሜ እና
ትላንት ወደ ፍፃሜ ለማለፍ ወሳኝ የነበረው
የሴኔጋል እና ቱኒዚያን የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታን
የመራ ሲሆን የፊታችን ዓርብ በካይሮ ስታዲየም
በአልጄርያ እና ሴኔጋል መካከል የሚደረገውን
የፍፃሜ ጨዋታም የሚመራ ይሆናል። ይህም
በ1980 የአፍሪካ ዋንጫ #ናይጄርያ ከ #አልጄርያ ያደረጉትን ጨዋታ ከመሩት ተስፋዬ ገብረየሱስ (አሁን የኤርትራ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ናቸው) በኋላ የፍፃሜ ጨዋታን የሚመራ ኢትዮጵያዊ ያደርገዋል።
Via :- Soccer Ethiopia
@YeneTube @FikerAssefa
በአፍሪካ ዋንጫ ወሳኝ ጨዋታዎችን እየዳኘ
የሚገኘው ኢትዮጵያዊው በዓምላክ ተሰማ
የፍፃሜው ጨዋታ እንዲመራ በካፍ የዳኞች
ኮሚቴ ተመርጧል።
በግብፅ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው
ውድድር ሁለት የምድብ፣ አንድ የሩብ ፍፃሜ እና
ትላንት ወደ ፍፃሜ ለማለፍ ወሳኝ የነበረው
የሴኔጋል እና ቱኒዚያን የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታን
የመራ ሲሆን የፊታችን ዓርብ በካይሮ ስታዲየም
በአልጄርያ እና ሴኔጋል መካከል የሚደረገውን
የፍፃሜ ጨዋታም የሚመራ ይሆናል። ይህም
በ1980 የአፍሪካ ዋንጫ #ናይጄርያ ከ #አልጄርያ ያደረጉትን ጨዋታ ከመሩት ተስፋዬ ገብረየሱስ (አሁን የኤርትራ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ናቸው) በኋላ የፍፃሜ ጨዋታን የሚመራ ኢትዮጵያዊ ያደርገዋል።
Via :- Soccer Ethiopia
@YeneTube @FikerAssefa