YeneTube
Photo
ጄ/ ፃድቃን ምን አሉ❓❓👇
" አራት የፖለቲካ ፓርቲዎችና ሁለት ነባር ወታደራዊ አመራሮች ' ምንቅስቓስ ደለይቲ ለውጢ ' (የለውጥ ፈላጊዎች እንቅስቃሴ) የሚባል ስብስብ ፈጥረናል ! " - ሌ/ጄነራል ፃድቃን ገብረትንሳኤ‼️
➡️ " ' ከኮር በላይ በሚሉ የሰራዊት አመራር ነን ' በሚሉ ጥቂት አመራሮችና የሻዕብያ ሰላይ ሰርገ ገቦች ምክንያት ወደ ትግራይ ለመግባት የማልችል መሆኔ እጅግ እጅግ ይቆጨኛል ! "
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት የነበሩት ሌተናል ጀነራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ አዲስ የለውጥ እንቅስቃሴ እየመሩ ናቸው።
ጄነራሉ የሚመሩት እንቅስቃሴ " ምንቅስቓስ ደለይቲ ለውጢ (የለውጥ ፈላጊዎች እንቅስቃሴ) ይባላል።
ትላንት ትግራይ ብሮድካስቲንግ ስርቪስ ( TBS) ከተባለ ሚዲያ ጋር ቃለምልልስ ያደረጉ ሲሆን ሰፊ ጉዳዮችን አንስተዋል።
ምን አሉ ?
➡️ በአቶ ጌታቸው ረዳ እና በራሳቸው በተመራው ጊዜያዊ አስተዳደር ወቅት ፦
- ሁሉም አስተሳሰቦች ማስተናገድ የሚችል ካውንስል እንዲቋቋም ፣
- ለወደፊቱ በምርጫ የሚቋቋሙ የህዝብ ምክር ምክር ቤቶች እውነተኛ የህዝብ ችግር የሚንፀባረቅባቸው እንዲሆኑ ፣
- ብዙህነት አስተሳሰብ የማራመድ ልምድ እንዲኖራቸው የሚያደርግ ሁኔታ እንዲፈጠር ጥረት ቢያደርጉም እንዳልተሳካ ገልጸዋል።
" ጠቅላይ አስተሳሰብ ካላቸው ቡድኖች ከፍተኛ ተግዳሮት ገጥሞኛል " ያሉት ጄነራሉ " በብዙ ጥረት የተለያዩ ፓርቲዎችና አስተሳሰቦች የተካተቱበት ጊዚያዊ ምክር ቤት ቢቋቋምም እንደታለመለት አልቀጠለም " ብለዋል።
የመንግስትንና የፖርቲ መደበላለቅ እንዲለያይ በጥናት የተደገፈ መፍትሄ ቢቀርብም በክልሉ ለ30 ዓመታት በብቸኝነት ተቆጣጠሮ የቆየው የህወሓት አስተሳሰብና አሰራር ሊያራምዳቸው እንዳልቻለ ተናግረዋል።
በተደረገው ጥናት የ19 ወረዳ አመራሮች በምክር ቤት ሳይሆን በህወሓት የተሾሙ ሆኖው እንደተገኙ ፤ ይህንን ለመቀየር ብዙ ርቀት እንዳይሄዱ ለዓመታት የተተበተበው ኔትወርክ ሊያሰራቸው እንዳልቻለ ተናግረዋል።
➡️ ጄነራል ፃድቃን ሲመሩት የነበረው ጊዚያዊ አስተዳደር ተቆጥረው የተሰጡትን ሃላፊነቶች እንዳይወጣ በተለይ የያኔው ምክትል ፕሬዚዳንት የአሁኑ ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) የሚመራው የፀጥታ ሃይል አኗኗሩ እንዲበላሽ በማድረግ በጊዚያዊ እስተዳደሩ ተቃዉሞ እንዲኖረው በመስራት ለስልጣን መወጣጫ እንደተጠቀመበት ከሰዋል።
➡️ ጄነራሉ " ከኮር በላይ የሰራዊት አመራር ነን " የሚሉ በግላጭ የህወሓት ደጋፊ የሆኑ አካላት ጊዚያዊ አስተዳደሩን አላሰራ አላንቀሳቅስ እንዳሉት ፤ የተከመሩ ችግሮችን ፣ የውጭውን ይቅርና የውስጥ ስራዎችን ለመስራት እንዳልቻሉ ተናግረዋል።
➡️ አሁን ሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ ስለሚመሩት አስተዳደርም ተናግረዋል። ይህ አስተዳደር ለውጥ የማምጣት አቅምና ቅንነት የለውም ብለዋል።
" ያለፉት 30 ዓመታት በትግራይ የነበረው መንግስትና ፓርቲ አንድ ናቸው የሚል የቆየ አስተሳሰብ ነው እያራመደ ያለው ፤ በዚህ መሰል መንገድ ደግሞ በአሁናዊ የትግራይ ሁኔታ ህዝብን የሚጠቅም ለውጥ ማምጣት አይቻልም " ብለዋል።
" አሁን ያለው የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ወደ ስልጣን የመጣበት መንገድ ትክክለኛ አይደለም " ያሉት ጄነራሉ " የህዝብ አጀንዳ ያለው አስተዳደር አይደለም ፣ ለዚህ ነው በደቡባዊና ደቡባዊ ምስራቅ ዞን የሚታየው የህዝብ ንቅናቄ ለማፈን የሚንቀሳቀሰው " ብለዋል።
➡️ ጄነራሉ ቢያንስ 49 (ተፎኳኳሪዎች) በ51 (ህወሓት) የነበረው የጊዚያዊ አስተዳደሩ አወቃቀር አሁን መቶ በመቶ በሚባል መልኩ በህወሓት ቁጥጥር ስር እንዲውል መደረጉን አሳውቀዋል።
" የፌደራል መንግስት ለዚህ መሰል አስተዳደር ትግራይ እንዲመራ ፍቃደኝነት ማሳየቱ በበኩሌ የምቀበለውና የሚገባኝ አይደለም " ብለዋል።
➡️ አዲሱን የለውጥ ስብስብ በተመለከተም ጄነራል ፃድቃን " የትግራይ ህዝብ መሪ ነው ያጣው እንጂ ለለውጥ ዝግጁ ነው ፤ በመሬት ላይ የምናየው ይህንን ነው ይህንን የለውጥ ፍላጎት በሰላማዊ መንገድ በተገቢው መመራት አለበት " ብለዋል።
" ከዚህ በመነሳት አራት የፖለቲካ ፓርቲዎችና ሁለት ነባር ወታደራዊ አመራሮች ' ምንቅስቓስ ደለይቲ ለውጢ ' (የለውጥ ፈላጊዎች እንቅስቃሴ) የሚባል ስብስብ ፈጥረናል " ሲሉ ገልጸዋል።
" ይህ የተፈጠረው ፦
- በዓረና ፣
- በውናት፣
- በባይቶና ፣
- በስምረት ሲሆን ፣ ወታደራዊ አመራሮቹ ደግሞ እኔ (ጀነራል ፃድቃና) እና ጀነራል ተኽላይ አሸብር ነን " ሲሉ ተናግረዋል።
" የእንቅስቃሴው ሰብሳቢ እኔ ነኝ " ያሉት ጄነራሉ " የፈጠርነው እንቅስቃሴ ምንጭ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ሆኖ ጦርነት መልሶ እንዳይጀመር ለመከላከል ፣ የፖለቲካ ለውጥ እንዲደረግ ለመስራት ሲሆን ፣ ዋነኛ ዓላማዎቹ ሦስት ሆነው እነሱ ደግሞ ፦
- መንግስት ስለ ሌለ መንግስት መመስረት ፣
- በትግራይ ጦርነት እንዳይፈጠር ድምፅ መሆን ፣
- ህወሓት ቅቡልነት ስለአጣ ለመተካትና ለቀጣይ ምርጫ ለመዘጋጀት የሚሉ ናቸው " ብለዋል።
" የጀመርነው ለውጥ የእኛ ሳይሆን የተተኪው ሃይል ድርሻ ነው ፣ እኛ እያደርግን ያለነው ለተተኪው መንገዱን የማሳየት ስራ ነው፣ የትግራይ ህዝብ በተለይ ወጣቱ የጀመርነው እንቅስቃሴ ባለቤት መሆኑ ማወቅና መደገፍ አለበት ፣ የፌደራል መንግስትም ይህንን የለውጥ ጥያቄ የመደገፍ ሃላፊነት አለበት " ሲሉ ገልጸዋል።
➡️ ጄነራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ " ህዝቡ ምርጫዬ ሰላም ነው እምቢ ለጦርነት ማለት መቻል አለበት ፣ የአንድ ፓርቲ የእድሜ ልክ አገዛዝ በቃኝ የብዙሃን አመራር ነው የምፈልገው ማለት መቻል አለበት " ብለዋክ።
" ' ከኮር በላይ በሚሉ የሰራዊት አመራር ነን ' በሚሉ ጥቂት አመራሮችና የሻዕብያ ሰላይ ሰርገ ገቦች ምክንያት ወደ ትግራይ ለመግባት የማልችል መሆኔ እጅግ እጅግ ይቆጨኛል " ያሉት ጄነራሉ " ወደ ትግራይ መግባት የሚከለክል ይህንን መሰል አደገኛ ፖለቲካ ቶሎ መቀየር አለበት " ብለዋል።
" እንደ ህዝብ የሚያጠፋን ፖለቲካ ቶሎ እንዲቀየርና ምዕራፉ እንዲዘጋ ተቀናጅተን በጋራ መታገል አለብን " ሲሉ አክለዋል።
" ' የትግራይ የሰላም ሃይል ' በሚል የተጀመረውን የሰራዊት እንቅስቃሴ እደግፈወለሁ " ያሉት ጄነራሉ የትግራይ ኃይል አባላት እንዲቀላቀሉት ፤ ወጣቶች በራያ በዓዲጉዶምና ሌሎች አከባቢዎች የጀመሩትን የእምቢታ እንቅስቃሴ እንቂቀጥሉም ጥሪ ሲያቀርቡ ተደምጠዋል።
ቃለ ምልልሱ የተወሰደው ከTBS ቴሌቪዥን ነው።
" አራት የፖለቲካ ፓርቲዎችና ሁለት ነባር ወታደራዊ አመራሮች ' ምንቅስቓስ ደለይቲ ለውጢ ' (የለውጥ ፈላጊዎች እንቅስቃሴ) የሚባል ስብስብ ፈጥረናል ! " - ሌ/ጄነራል ፃድቃን ገብረትንሳኤ‼️
➡️ " ' ከኮር በላይ በሚሉ የሰራዊት አመራር ነን ' በሚሉ ጥቂት አመራሮችና የሻዕብያ ሰላይ ሰርገ ገቦች ምክንያት ወደ ትግራይ ለመግባት የማልችል መሆኔ እጅግ እጅግ ይቆጨኛል ! "
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት የነበሩት ሌተናል ጀነራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ አዲስ የለውጥ እንቅስቃሴ እየመሩ ናቸው።
ጄነራሉ የሚመሩት እንቅስቃሴ " ምንቅስቓስ ደለይቲ ለውጢ (የለውጥ ፈላጊዎች እንቅስቃሴ) ይባላል።
ትላንት ትግራይ ብሮድካስቲንግ ስርቪስ ( TBS) ከተባለ ሚዲያ ጋር ቃለምልልስ ያደረጉ ሲሆን ሰፊ ጉዳዮችን አንስተዋል።
ምን አሉ ?
➡️ በአቶ ጌታቸው ረዳ እና በራሳቸው በተመራው ጊዜያዊ አስተዳደር ወቅት ፦
- ሁሉም አስተሳሰቦች ማስተናገድ የሚችል ካውንስል እንዲቋቋም ፣
- ለወደፊቱ በምርጫ የሚቋቋሙ የህዝብ ምክር ምክር ቤቶች እውነተኛ የህዝብ ችግር የሚንፀባረቅባቸው እንዲሆኑ ፣
- ብዙህነት አስተሳሰብ የማራመድ ልምድ እንዲኖራቸው የሚያደርግ ሁኔታ እንዲፈጠር ጥረት ቢያደርጉም እንዳልተሳካ ገልጸዋል።
" ጠቅላይ አስተሳሰብ ካላቸው ቡድኖች ከፍተኛ ተግዳሮት ገጥሞኛል " ያሉት ጄነራሉ " በብዙ ጥረት የተለያዩ ፓርቲዎችና አስተሳሰቦች የተካተቱበት ጊዚያዊ ምክር ቤት ቢቋቋምም እንደታለመለት አልቀጠለም " ብለዋል።
የመንግስትንና የፖርቲ መደበላለቅ እንዲለያይ በጥናት የተደገፈ መፍትሄ ቢቀርብም በክልሉ ለ30 ዓመታት በብቸኝነት ተቆጣጠሮ የቆየው የህወሓት አስተሳሰብና አሰራር ሊያራምዳቸው እንዳልቻለ ተናግረዋል።
በተደረገው ጥናት የ19 ወረዳ አመራሮች በምክር ቤት ሳይሆን በህወሓት የተሾሙ ሆኖው እንደተገኙ ፤ ይህንን ለመቀየር ብዙ ርቀት እንዳይሄዱ ለዓመታት የተተበተበው ኔትወርክ ሊያሰራቸው እንዳልቻለ ተናግረዋል።
➡️ ጄነራል ፃድቃን ሲመሩት የነበረው ጊዚያዊ አስተዳደር ተቆጥረው የተሰጡትን ሃላፊነቶች እንዳይወጣ በተለይ የያኔው ምክትል ፕሬዚዳንት የአሁኑ ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) የሚመራው የፀጥታ ሃይል አኗኗሩ እንዲበላሽ በማድረግ በጊዚያዊ እስተዳደሩ ተቃዉሞ እንዲኖረው በመስራት ለስልጣን መወጣጫ እንደተጠቀመበት ከሰዋል።
➡️ ጄነራሉ " ከኮር በላይ የሰራዊት አመራር ነን " የሚሉ በግላጭ የህወሓት ደጋፊ የሆኑ አካላት ጊዚያዊ አስተዳደሩን አላሰራ አላንቀሳቅስ እንዳሉት ፤ የተከመሩ ችግሮችን ፣ የውጭውን ይቅርና የውስጥ ስራዎችን ለመስራት እንዳልቻሉ ተናግረዋል።
➡️ አሁን ሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ ስለሚመሩት አስተዳደርም ተናግረዋል። ይህ አስተዳደር ለውጥ የማምጣት አቅምና ቅንነት የለውም ብለዋል።
" ያለፉት 30 ዓመታት በትግራይ የነበረው መንግስትና ፓርቲ አንድ ናቸው የሚል የቆየ አስተሳሰብ ነው እያራመደ ያለው ፤ በዚህ መሰል መንገድ ደግሞ በአሁናዊ የትግራይ ሁኔታ ህዝብን የሚጠቅም ለውጥ ማምጣት አይቻልም " ብለዋል።
" አሁን ያለው የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ወደ ስልጣን የመጣበት መንገድ ትክክለኛ አይደለም " ያሉት ጄነራሉ " የህዝብ አጀንዳ ያለው አስተዳደር አይደለም ፣ ለዚህ ነው በደቡባዊና ደቡባዊ ምስራቅ ዞን የሚታየው የህዝብ ንቅናቄ ለማፈን የሚንቀሳቀሰው " ብለዋል።
➡️ ጄነራሉ ቢያንስ 49 (ተፎኳኳሪዎች) በ51 (ህወሓት) የነበረው የጊዚያዊ አስተዳደሩ አወቃቀር አሁን መቶ በመቶ በሚባል መልኩ በህወሓት ቁጥጥር ስር እንዲውል መደረጉን አሳውቀዋል።
" የፌደራል መንግስት ለዚህ መሰል አስተዳደር ትግራይ እንዲመራ ፍቃደኝነት ማሳየቱ በበኩሌ የምቀበለውና የሚገባኝ አይደለም " ብለዋል።
➡️ አዲሱን የለውጥ ስብስብ በተመለከተም ጄነራል ፃድቃን " የትግራይ ህዝብ መሪ ነው ያጣው እንጂ ለለውጥ ዝግጁ ነው ፤ በመሬት ላይ የምናየው ይህንን ነው ይህንን የለውጥ ፍላጎት በሰላማዊ መንገድ በተገቢው መመራት አለበት " ብለዋል።
" ከዚህ በመነሳት አራት የፖለቲካ ፓርቲዎችና ሁለት ነባር ወታደራዊ አመራሮች ' ምንቅስቓስ ደለይቲ ለውጢ ' (የለውጥ ፈላጊዎች እንቅስቃሴ) የሚባል ስብስብ ፈጥረናል " ሲሉ ገልጸዋል።
" ይህ የተፈጠረው ፦
- በዓረና ፣
- በውናት፣
- በባይቶና ፣
- በስምረት ሲሆን ፣ ወታደራዊ አመራሮቹ ደግሞ እኔ (ጀነራል ፃድቃና) እና ጀነራል ተኽላይ አሸብር ነን " ሲሉ ተናግረዋል።
" የእንቅስቃሴው ሰብሳቢ እኔ ነኝ " ያሉት ጄነራሉ " የፈጠርነው እንቅስቃሴ ምንጭ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ሆኖ ጦርነት መልሶ እንዳይጀመር ለመከላከል ፣ የፖለቲካ ለውጥ እንዲደረግ ለመስራት ሲሆን ፣ ዋነኛ ዓላማዎቹ ሦስት ሆነው እነሱ ደግሞ ፦
- መንግስት ስለ ሌለ መንግስት መመስረት ፣
- በትግራይ ጦርነት እንዳይፈጠር ድምፅ መሆን ፣
- ህወሓት ቅቡልነት ስለአጣ ለመተካትና ለቀጣይ ምርጫ ለመዘጋጀት የሚሉ ናቸው " ብለዋል።
" የጀመርነው ለውጥ የእኛ ሳይሆን የተተኪው ሃይል ድርሻ ነው ፣ እኛ እያደርግን ያለነው ለተተኪው መንገዱን የማሳየት ስራ ነው፣ የትግራይ ህዝብ በተለይ ወጣቱ የጀመርነው እንቅስቃሴ ባለቤት መሆኑ ማወቅና መደገፍ አለበት ፣ የፌደራል መንግስትም ይህንን የለውጥ ጥያቄ የመደገፍ ሃላፊነት አለበት " ሲሉ ገልጸዋል።
➡️ ጄነራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ " ህዝቡ ምርጫዬ ሰላም ነው እምቢ ለጦርነት ማለት መቻል አለበት ፣ የአንድ ፓርቲ የእድሜ ልክ አገዛዝ በቃኝ የብዙሃን አመራር ነው የምፈልገው ማለት መቻል አለበት " ብለዋክ።
" ' ከኮር በላይ በሚሉ የሰራዊት አመራር ነን ' በሚሉ ጥቂት አመራሮችና የሻዕብያ ሰላይ ሰርገ ገቦች ምክንያት ወደ ትግራይ ለመግባት የማልችል መሆኔ እጅግ እጅግ ይቆጨኛል " ያሉት ጄነራሉ " ወደ ትግራይ መግባት የሚከለክል ይህንን መሰል አደገኛ ፖለቲካ ቶሎ መቀየር አለበት " ብለዋል።
" እንደ ህዝብ የሚያጠፋን ፖለቲካ ቶሎ እንዲቀየርና ምዕራፉ እንዲዘጋ ተቀናጅተን በጋራ መታገል አለብን " ሲሉ አክለዋል።
" ' የትግራይ የሰላም ሃይል ' በሚል የተጀመረውን የሰራዊት እንቅስቃሴ እደግፈወለሁ " ያሉት ጄነራሉ የትግራይ ኃይል አባላት እንዲቀላቀሉት ፤ ወጣቶች በራያ በዓዲጉዶምና ሌሎች አከባቢዎች የጀመሩትን የእምቢታ እንቅስቃሴ እንቂቀጥሉም ጥሪ ሲያቀርቡ ተደምጠዋል።
ቃለ ምልልሱ የተወሰደው ከTBS ቴሌቪዥን ነው።
❤62
በትግራይ ክልል ቆላ ተንቤን በተከሰተ ድርቅ በሺዎች የሚቆጠሩ ከብቶች ሞቱ!
በማዕከላዊ ትግራይ ቆላ ተንቤን ወረዳ በዚህ ሳምንት በተከሰተው ድርቅ ከፍተኛ ስጋት መፍጠሩ ተገለፀ።በድርቁ በያከር አካባቢ ብቻ ከ18,000 በላይ የቤት እንስሳት ሲሞቱ፤ በመቶዎች የሚቆጠር ሄክታር የእርሻ መሬት ደግሞ ወድሟል።
ይህም አሁን ላይ ከጦርነት ጉዳት ሙሉ ለሙሉ ባላገገመው ክልሉ ውስጥ ረሀብ ሊመለስ ይችላል የሚል ስጋትን ፈጥሯል።
የወረዳው የኢኮኖሚ ዘርፍ ኃላፊ የሆኑት ጎይቶም ገብረሐዋሪያ ለአዲስ ስታንዳርድ እንደተናገሩት ዝናብ ባለመኖሩ እና በመኖ እጥረት ምክንያት 184 ከብቶች፣ 900 አህዮች፣ ከ4,500 በላይ በጎች፣ ከ13,000 በላይ ፍየሎች ሞተዋል። አያይዘውም "እስከዛሬ ድረስ ዝናብ በአካባቢው አልጣለም"ሲሉ ገልጸው "ንቦችም ሙሉ በሙሉ ጠፍተዋል" ሲሉ አክለዋል።
እንደ እሳቸው ገለጻ በህፃናትና በዕድሜ በገፉ ሰዎች ላይ የተመጣጠነ የምግብ እጥረት ምልክቶች፣ እንደ እብጠት ያሉ እና ሌሎችም ከረሃብ ጋር የተያያዙ ምልክቶች እየታዩ ነው።በድርቁ ምክንያት 650 ሄክታር የእርሻ መሬት ሳይዘራ የቀረ ሲሆን 50 ሄክታር ሰሊጥ ደግሞ መብቀል አለመቻሉን ጠቁመዋል።
Via AS
@YeneTube @FikerAssefa
በማዕከላዊ ትግራይ ቆላ ተንቤን ወረዳ በዚህ ሳምንት በተከሰተው ድርቅ ከፍተኛ ስጋት መፍጠሩ ተገለፀ።በድርቁ በያከር አካባቢ ብቻ ከ18,000 በላይ የቤት እንስሳት ሲሞቱ፤ በመቶዎች የሚቆጠር ሄክታር የእርሻ መሬት ደግሞ ወድሟል።
ይህም አሁን ላይ ከጦርነት ጉዳት ሙሉ ለሙሉ ባላገገመው ክልሉ ውስጥ ረሀብ ሊመለስ ይችላል የሚል ስጋትን ፈጥሯል።
የወረዳው የኢኮኖሚ ዘርፍ ኃላፊ የሆኑት ጎይቶም ገብረሐዋሪያ ለአዲስ ስታንዳርድ እንደተናገሩት ዝናብ ባለመኖሩ እና በመኖ እጥረት ምክንያት 184 ከብቶች፣ 900 አህዮች፣ ከ4,500 በላይ በጎች፣ ከ13,000 በላይ ፍየሎች ሞተዋል። አያይዘውም "እስከዛሬ ድረስ ዝናብ በአካባቢው አልጣለም"ሲሉ ገልጸው "ንቦችም ሙሉ በሙሉ ጠፍተዋል" ሲሉ አክለዋል።
እንደ እሳቸው ገለጻ በህፃናትና በዕድሜ በገፉ ሰዎች ላይ የተመጣጠነ የምግብ እጥረት ምልክቶች፣ እንደ እብጠት ያሉ እና ሌሎችም ከረሃብ ጋር የተያያዙ ምልክቶች እየታዩ ነው።በድርቁ ምክንያት 650 ሄክታር የእርሻ መሬት ሳይዘራ የቀረ ሲሆን 50 ሄክታር ሰሊጥ ደግሞ መብቀል አለመቻሉን ጠቁመዋል።
Via AS
@YeneTube @FikerAssefa
😭34❤18
በኮዬ ፈጬ ኮንዶሚንየም ዉስጥ ብሎክ 415 የምትኖር አንዲት ሴት በሰራተኛው ላይ ባደረሰችዉ ጉዳት በህብረተሰቡ ጥቆማ በቁጥጥር ስር ዉላለች።
@Yenetube @Fikerassefa
@Yenetube @Fikerassefa
😭58❤16
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መቀመጫቸውን አሜሪካ በማድረግ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ሥርዓት ታማኝነት ለመናድ እየሰሩ ናቸው ያላቸውን የገንዘብ አስተላላፊዎችን ይፋ አደረገ ⵑⵑ
ባንኩ ዛሬ ለውጭ አገር ለሚገኙ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ በሚል ባወጣው መግለጫ
ህገወጥ የገንዘብ ዝውውርን እና አሸባሪዎችን የገንዘብ ድጋፍን ለመከላከል ተገቢውን ቁጥጥር በማድረግ ድንበር ተሻጋሪ የገንዘብ ዝውውሮች በመደበኛ እና በተስተካከለ የፋይናንስ ስርዓት መከናወን አለባቸው።
ከዚህ መርህ በተቃራኒ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ሥርዓት ታማኝነት ለመናድና የገበያ ዋጋን ለማዛባት በግልጽ በማሰብ በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ በርካታ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች በውጭ አገር ከሚገኙ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ የተሰበሰቡ ገንዘቦችን በመጠቀም በገንዘብ ማሸሽ ተግባር ላይ የተሰማሩና ሕገ-ወጥ ተግባራትን በገንዘብ የሚደግፉ መሆናቸውን ተለይተዋል ።
ባንኩ መቀመጫቸውን አሜሪካ በማድረግ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ሥርዓት ታማኝነት ለመናድ እየሰሩ ናቸው ያላቸውን የገንዘብ አስተላላፊዎችን ዝርዝር በመግለጫው አካቷል በዚህም መሰረት
1. Shgey Money Transfer - Silver Spring, MD, and Falls Church, VA, USA
2. Adulis Money Transfer - Falls Church, VA, and Silver Spring, MD, USA
3. Ramada Pay (Kaah) - Falls Church, VA, USA
4. TAAJ Money Transfer - Minneapolis, MN, USA
በተዘረዘሩት ተቋማት ላይ የሚመለከታቸው አካላት ምርመራ በማካሄድ እንዲተባበሩ ባንኩ ጠይቋል፡፡
[KGEthiopia]
@YeneTube @FikerAssefa
ባንኩ ዛሬ ለውጭ አገር ለሚገኙ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ በሚል ባወጣው መግለጫ
ህገወጥ የገንዘብ ዝውውርን እና አሸባሪዎችን የገንዘብ ድጋፍን ለመከላከል ተገቢውን ቁጥጥር በማድረግ ድንበር ተሻጋሪ የገንዘብ ዝውውሮች በመደበኛ እና በተስተካከለ የፋይናንስ ስርዓት መከናወን አለባቸው።
ከዚህ መርህ በተቃራኒ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ሥርዓት ታማኝነት ለመናድና የገበያ ዋጋን ለማዛባት በግልጽ በማሰብ በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ በርካታ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች በውጭ አገር ከሚገኙ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ የተሰበሰቡ ገንዘቦችን በመጠቀም በገንዘብ ማሸሽ ተግባር ላይ የተሰማሩና ሕገ-ወጥ ተግባራትን በገንዘብ የሚደግፉ መሆናቸውን ተለይተዋል ።
ባንኩ መቀመጫቸውን አሜሪካ በማድረግ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ሥርዓት ታማኝነት ለመናድ እየሰሩ ናቸው ያላቸውን የገንዘብ አስተላላፊዎችን ዝርዝር በመግለጫው አካቷል በዚህም መሰረት
1. Shgey Money Transfer - Silver Spring, MD, and Falls Church, VA, USA
2. Adulis Money Transfer - Falls Church, VA, and Silver Spring, MD, USA
3. Ramada Pay (Kaah) - Falls Church, VA, USA
4. TAAJ Money Transfer - Minneapolis, MN, USA
በተዘረዘሩት ተቋማት ላይ የሚመለከታቸው አካላት ምርመራ በማካሄድ እንዲተባበሩ ባንኩ ጠይቋል፡፡
[KGEthiopia]
@YeneTube @FikerAssefa
❤34😁15👍6🔥1
በሰው መነገድ ወንጀል ላይ የተሳተፉ 5 ሰዎች ሞት ተፈረደባቸው!
በሰው መነገድ ወንጀል ላይ በተሳተፉ 5 ሰዎች ላይ የሞት ፍርድ እንዲወሰን መደረጉን የፍትህ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ በላይሁን ይርጋ ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ በሰው የመነገድና በህገወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረና የብዙ የሰዎች ህይወት እየቀጠፈ ያለ ወንጀል ነው፡፡
በወንጀሉ ላይ ተሰማርተው የሚገኙ ወንጀለኞች በአዋጅ ቁጥር አንድ ሺህ 178 መሰረት የሞት ቅጣት፣ የዕድሜ ልክ እስራትና እስከ 25 ዓመት እስራት ያስቀጣል ብለዋል፡፡በመሆኑም በ2017 በጀት ዓመት ለመጀመሪያ ጊዜ በሂደቱ የተሳተፉ 5 ሰዎች ላይ የሞት ፍርድ እንዲወስን መደረጉን አስታውቀዋል፡፡
በሰው የመነገድ ወንጀል ለመከከላከልና ለመቆጣጠርም የግንዛቤ ማስጨበጫ እና በክልሎች መካከል ቅንጅትና ትብብር የሚፈጥሩ ስራዎችና መመሪያ የማጽደቅ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡በተጨማሪም በህገወጥ ድርጊቱ በስፋት ተጠቂ ለሆኑት ወጣቶች በሀገር ወስጥ የስራ እድል ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
ሰው የመነገድና በህገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ወንጀልም ድንበር ተሻጋሪ የተደራጀ ወንጀል መሆኑን አንስተው፤ ይህንንም ለመቆጣጠር ከጅቡቲ፣ ኬንያና ማላዊ ጋር ዓለም አቀፍ ትብበር ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡በመሆኑም ባለፈው በጀት ዓመት የተወሰደው የህግ እርምጃ እንደሀገር የተሰጠውን ትኩረት ማሳያ ነው፡፡በቀጣይም የተሻለ ተጠያቂነት ለማረጋገጥ ተጠናክሮ የሚሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
Via Gazette Plus
@YeneTube @FikerAssefa
በሰው መነገድ ወንጀል ላይ በተሳተፉ 5 ሰዎች ላይ የሞት ፍርድ እንዲወሰን መደረጉን የፍትህ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ በላይሁን ይርጋ ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ በሰው የመነገድና በህገወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረና የብዙ የሰዎች ህይወት እየቀጠፈ ያለ ወንጀል ነው፡፡
በወንጀሉ ላይ ተሰማርተው የሚገኙ ወንጀለኞች በአዋጅ ቁጥር አንድ ሺህ 178 መሰረት የሞት ቅጣት፣ የዕድሜ ልክ እስራትና እስከ 25 ዓመት እስራት ያስቀጣል ብለዋል፡፡በመሆኑም በ2017 በጀት ዓመት ለመጀመሪያ ጊዜ በሂደቱ የተሳተፉ 5 ሰዎች ላይ የሞት ፍርድ እንዲወስን መደረጉን አስታውቀዋል፡፡
በሰው የመነገድ ወንጀል ለመከከላከልና ለመቆጣጠርም የግንዛቤ ማስጨበጫ እና በክልሎች መካከል ቅንጅትና ትብብር የሚፈጥሩ ስራዎችና መመሪያ የማጽደቅ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡በተጨማሪም በህገወጥ ድርጊቱ በስፋት ተጠቂ ለሆኑት ወጣቶች በሀገር ወስጥ የስራ እድል ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
ሰው የመነገድና በህገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ወንጀልም ድንበር ተሻጋሪ የተደራጀ ወንጀል መሆኑን አንስተው፤ ይህንንም ለመቆጣጠር ከጅቡቲ፣ ኬንያና ማላዊ ጋር ዓለም አቀፍ ትብበር ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡በመሆኑም ባለፈው በጀት ዓመት የተወሰደው የህግ እርምጃ እንደሀገር የተሰጠውን ትኩረት ማሳያ ነው፡፡በቀጣይም የተሻለ ተጠያቂነት ለማረጋገጥ ተጠናክሮ የሚሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
Via Gazette Plus
@YeneTube @FikerAssefa
❤41👍6⚡1
ኢትዮጵያ በማዕድን ኢንቨስትመንት ማራኪነት በአለም የመጨረሻ ደረጃ ላይ ተቀመጠች!
በካናዳው "Fraser Institute" የተዘጋጀው የ2024 ዓመታዊ የማዕድን ኩባንያዎች ጥናት፣ ኢትዮጵያ በማዕድን ኢንቨስትመንት ማራኪነት ደረጃ ከአለም መጨረሻ ላይ መቀመጧን አመላክቷል። ጥናቱ 82 ሀገራትን ገምግሞ ለኢንቨስትመንት ማራኪ የሚያደርጉ የፖሊሲ መረጋጋት እና ግልጽነት ላይ ችግሮች እንዳሉ በመጠቆም ኢትዮጵያን ከሁሉም በታች አስቀምጧታል።
የኢንቨስትመንት ማራኪነት ደረጃው የሀገሪቱን የጂኦሎጂካል አቅም ከመንግስት የፖሊሲ ማዕቀፎች ጋር በማጣመር የሚሰላ ነው።ምንም እንኳን ኢትዮጵያ በሀብት የበለፀገች ብትሆንም፣ ደካማ የፖሊሲ አሰራር ኢንቨስተሮችን እያራቀ መሆኑን ጥናቱ ያሳያል።
ጥናቱ እንደ የግብር አወሳሰን፣ የህግ ስርዓት እና የፖለቲካ መረጋጋት ያሉ የፖሊሲ ጉዳዮችን የሚገመግም ሲሆን፣ ኢትዮጵያ በዚህ ምድብ ውስጥ ካሉ 10 ዝቅተኛ ደረጃ ከተሰጣቸው ሀገራት ውስጥ አንዷ ነች።
የጥናቱ ተሳታፊዎች እንደገለጹት፣ የማዕድን ሀብት መሠረታዊ ቢሆንም፣ 40% ያህሉ የኢንቨስትመንት ውሳኔዎች የሚወሰኑት በፖሊሲ አሰራር ላይ ነው። ይህም ግልፅ ደንቦች፣ የፖለቲካ መረጋጋት እና ፍትሃዊ የህግ ማዕቀፎች የማዕድን ኢንቨስትመንትን ለመሳብ ምን ያህል ወሳኝ እንደሆኑ ያመለክታል።ሪፖርቱ ኢትዮጵያ የፖሊሲ ክፍተቶቿን ካልሞላች፣ ኢንቨስትመንቶች ግልጽ እና ባለሀብት ወዳድ ወደሆኑ ሀገራት ሊዞሩ እንደሚችሉ አስጠንቅቋል።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
በካናዳው "Fraser Institute" የተዘጋጀው የ2024 ዓመታዊ የማዕድን ኩባንያዎች ጥናት፣ ኢትዮጵያ በማዕድን ኢንቨስትመንት ማራኪነት ደረጃ ከአለም መጨረሻ ላይ መቀመጧን አመላክቷል። ጥናቱ 82 ሀገራትን ገምግሞ ለኢንቨስትመንት ማራኪ የሚያደርጉ የፖሊሲ መረጋጋት እና ግልጽነት ላይ ችግሮች እንዳሉ በመጠቆም ኢትዮጵያን ከሁሉም በታች አስቀምጧታል።
የኢንቨስትመንት ማራኪነት ደረጃው የሀገሪቱን የጂኦሎጂካል አቅም ከመንግስት የፖሊሲ ማዕቀፎች ጋር በማጣመር የሚሰላ ነው።ምንም እንኳን ኢትዮጵያ በሀብት የበለፀገች ብትሆንም፣ ደካማ የፖሊሲ አሰራር ኢንቨስተሮችን እያራቀ መሆኑን ጥናቱ ያሳያል።
ጥናቱ እንደ የግብር አወሳሰን፣ የህግ ስርዓት እና የፖለቲካ መረጋጋት ያሉ የፖሊሲ ጉዳዮችን የሚገመግም ሲሆን፣ ኢትዮጵያ በዚህ ምድብ ውስጥ ካሉ 10 ዝቅተኛ ደረጃ ከተሰጣቸው ሀገራት ውስጥ አንዷ ነች።
የጥናቱ ተሳታፊዎች እንደገለጹት፣ የማዕድን ሀብት መሠረታዊ ቢሆንም፣ 40% ያህሉ የኢንቨስትመንት ውሳኔዎች የሚወሰኑት በፖሊሲ አሰራር ላይ ነው። ይህም ግልፅ ደንቦች፣ የፖለቲካ መረጋጋት እና ፍትሃዊ የህግ ማዕቀፎች የማዕድን ኢንቨስትመንትን ለመሳብ ምን ያህል ወሳኝ እንደሆኑ ያመለክታል።ሪፖርቱ ኢትዮጵያ የፖሊሲ ክፍተቶቿን ካልሞላች፣ ኢንቨስትመንቶች ግልጽ እና ባለሀብት ወዳድ ወደሆኑ ሀገራት ሊዞሩ እንደሚችሉ አስጠንቅቋል።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
😁52❤33👍4👀4👎3😭1
Forwarded from YeneTube
7 ሳይቶችን በጥራት በታማኝነት አስረክበናል::
ለንግድ ሱቅ ፈላጊዎች በሙሉ
📍 ፒያሳ ከሚኒልክ አደባባይ ወደ ሀገር ፍቅር ቲያትር የሚወስደው መንገድ ላይ የንግድ ሱቆችን መሸጥ ጀምረናል።
👉 2 ቤዝመንት ያለው
👉ከ 900,000 ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ
👉በ1 ዓመት ተኩል የምትረከቡት
👉ምድር ቤት
20 ካሬ= 7ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 2.8ሚሊዮን ብር
👉1ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 5.5 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 2 ሚሊዮን ብር
👉2ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 4.8 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 1.5 ሚሊዮን ብር
👉3ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 4.2 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 1.2 ሚሊዮን ብር
👉4ኛ እና 5ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 3.9 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 900 ሺ ብር
👉ቀሪው በግንባታ ሂደት የሚከፈል።
ለበለጠ መረጃ
09-76-19-58-35
Telegram username
@Ruthtemersales
Whats app
Message Temer properties on WhatsApp. https://wa.me/251976195835
ለንግድ ሱቅ ፈላጊዎች በሙሉ
📍 ፒያሳ ከሚኒልክ አደባባይ ወደ ሀገር ፍቅር ቲያትር የሚወስደው መንገድ ላይ የንግድ ሱቆችን መሸጥ ጀምረናል።
👉 2 ቤዝመንት ያለው
👉ከ 900,000 ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ
👉በ1 ዓመት ተኩል የምትረከቡት
👉ምድር ቤት
20 ካሬ= 7ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 2.8ሚሊዮን ብር
👉1ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 5.5 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 2 ሚሊዮን ብር
👉2ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 4.8 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 1.5 ሚሊዮን ብር
👉3ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 4.2 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 1.2 ሚሊዮን ብር
👉4ኛ እና 5ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 3.9 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 900 ሺ ብር
👉ቀሪው በግንባታ ሂደት የሚከፈል።
ለበለጠ መረጃ
09-76-19-58-35
Telegram username
@Ruthtemersales
Whats app
Message Temer properties on WhatsApp. https://wa.me/251976195835
❤6
Forwarded from YeneTube
በሩን ይክፈቱ ችግረወን
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
ጀልባ ተገልብጦ 68 ኢትዮጵያዊያን በየመን አቅራቢያ ህይወታቸው አለፈ!
154 ሰዎችን ጭና ቀይ ባህርን እያቋረቀጠች የነበረች ጀልባ ተገልብጣ 68ቱ ሲሞቱ የተቀሩትም እስካሁን አልተገኙም። እንደ ዶቸ ቨለ ዘገባ በጀልባዋ ላይ የነበሩት ሁሉም ኢትዮጲያዊያን ዜጎች የነበሩ ሲሆን ፍለጋው አሁንም እንደቀጠለ ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
154 ሰዎችን ጭና ቀይ ባህርን እያቋረቀጠች የነበረች ጀልባ ተገልብጣ 68ቱ ሲሞቱ የተቀሩትም እስካሁን አልተገኙም። እንደ ዶቸ ቨለ ዘገባ በጀልባዋ ላይ የነበሩት ሁሉም ኢትዮጲያዊያን ዜጎች የነበሩ ሲሆን ፍለጋው አሁንም እንደቀጠለ ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
😭90❤11
በሀገራዊ የምክክር ሂደት ውስጥ የተሳታፊዎች ደህንነት ስጋት ላይ ነው ተባለ!
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ባወጣው ዓመታዊ ሪፖርት፣ በሀገራዊ የምክክር ሂደት ውስጥ የተለያዩ ችግሮች መከሰታቸውን ገልጿል። ከእነዚህም መካከል፣ የውይይት ተሳታፊዎች ደህንነትን የሚመለከቱ፣ የአካታችነት ችግሮች እና የግልጽነት ጥያቄዎች በዋናነት ተጠቅሰዋል።
በሪፖርቱ መሠረት፣ በብዙ ክልሎች የተካሄዱ ውይይቶች ላይ ተሳታፊዎች ሀሳባቸውን በነጻነት ሲገልጹ ቢቆዩም፣ ፈቃድ ሳይጠይቁ ምስል እና ቪዲዮ የሚቀርጹ ሚዲያ ነን ባዮች መኖራቸው የብዙዎችን ስጋት ፈጥሯል።
በተለይም በአማራ ክልል አንዳንድ ተሳታፊዎች፣ የታጣቂ ኃይሎች በምክክሩ መሳተፋቸውን በመገናኛ ብዙኃን ካዩ ሊያጠቋቸው እንደሚችሉ በመፍራት ፊታቸውን በመሸፈን እና ሀሳባቸውን ከመግለጽ መቆጠባቸውን አብራርተዋል።
ኢሰመኮ በሪፖርቱ እንደጠቆመዉ አንዳንድ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች የኮሚሽኑን ገለልተኝነት በመጠራጠር ከሂደቱ ራሳቸውን አግልለዋል። በተጨማሪም፣ በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች ውስጥ በታጣቂዎች ቁጥጥር ስር ከሚገኙ አካባቢዎች ተሳታፊዎችን ማካተት ባለመቻሉ፣ የምክክር ሂደቱ ሁሉን አቀፍ እንዳይሆን አድርጎታል ብሏል።
ከዚህ በተጨማሪም በአማራ ክልል ተጽዕኖ ፈጣሪዎች በዋናው ምክክር ላይ እንደሚሳተፉ ሲነገር፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ግን የማይሳተፉበት ምክንያት አለመገለጹ የሂደቱን ግልጽነት ጥያቄ ውስጥ የሚጥል እንደሆነ ተገልጿል።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ባወጣው ዓመታዊ ሪፖርት፣ በሀገራዊ የምክክር ሂደት ውስጥ የተለያዩ ችግሮች መከሰታቸውን ገልጿል። ከእነዚህም መካከል፣ የውይይት ተሳታፊዎች ደህንነትን የሚመለከቱ፣ የአካታችነት ችግሮች እና የግልጽነት ጥያቄዎች በዋናነት ተጠቅሰዋል።
በሪፖርቱ መሠረት፣ በብዙ ክልሎች የተካሄዱ ውይይቶች ላይ ተሳታፊዎች ሀሳባቸውን በነጻነት ሲገልጹ ቢቆዩም፣ ፈቃድ ሳይጠይቁ ምስል እና ቪዲዮ የሚቀርጹ ሚዲያ ነን ባዮች መኖራቸው የብዙዎችን ስጋት ፈጥሯል።
በተለይም በአማራ ክልል አንዳንድ ተሳታፊዎች፣ የታጣቂ ኃይሎች በምክክሩ መሳተፋቸውን በመገናኛ ብዙኃን ካዩ ሊያጠቋቸው እንደሚችሉ በመፍራት ፊታቸውን በመሸፈን እና ሀሳባቸውን ከመግለጽ መቆጠባቸውን አብራርተዋል።
ኢሰመኮ በሪፖርቱ እንደጠቆመዉ አንዳንድ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች የኮሚሽኑን ገለልተኝነት በመጠራጠር ከሂደቱ ራሳቸውን አግልለዋል። በተጨማሪም፣ በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች ውስጥ በታጣቂዎች ቁጥጥር ስር ከሚገኙ አካባቢዎች ተሳታፊዎችን ማካተት ባለመቻሉ፣ የምክክር ሂደቱ ሁሉን አቀፍ እንዳይሆን አድርጎታል ብሏል።
ከዚህ በተጨማሪም በአማራ ክልል ተጽዕኖ ፈጣሪዎች በዋናው ምክክር ላይ እንደሚሳተፉ ሲነገር፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ግን የማይሳተፉበት ምክንያት አለመገለጹ የሂደቱን ግልጽነት ጥያቄ ውስጥ የሚጥል እንደሆነ ተገልጿል።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
❤23👎2👍1😁1
የአፍሪካ ህብረት ከ50 በላይ አል-ሸባብ ታጣቂዎች በደቡባዊ ሶማሊያ መገደላቸውን አረጋገጠ!
የአፍሪካ ህብረት የሶማሊያ የድጋፍ እና ማረጋጋት ተልዕኮ(አውሶም) በሶማሊያ የመንግስት ኃይሎች የሚደገፉት ወታደሮቹ ባሳለፍነው አርብ በደቡባዊ ሶማሊያ በባሪሬ ከተማ በተካሄደ ከባድ ውጊያ ከ50 በላይ የአል-ሸባብ አባላትን መግደላቸውን አስረጋገጠ።
አውሶም ከሶማሊያ መዲና ሞቃዲሾ በሰጠው መግለጫ፤ “በባሪሬ በተልዕኮው ወታደሮች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል” የሚሉ የሚዲያ ዘገባዎችን አስተባብሏል።
"አውሶም ኃይሎቹ ከሶማሊያ ብሔራዊ ጦር ኃይሎች (SNAF) ጋር በመተባበር የባሪሬ ከተማን መልሶ ለመቆጣጠር ሐምሌ 25 ቀን ጥቃት መጀመሩን ግልጽ ማድረግ ይፈልጋል" ሲል የአፍሪካ ህብረት የሶማሊያ የድጋፍ እና ማረጋጋት ተልዕኮ(አውሶም) ገልጿል።
አውሶም ይህን ያለው፤ አል-ሸባብ በባሪሬ በተካሄደው ከባድ ውጊያ፤ "የአፍሪካ ህብረት የወታደሮች ማጓጓዣ ተሽከርካሪዎችን መውደማቸውን እና የአውሶም ወታደሮች ማፈግፈጋቸውን" መግለጹን አስመልክቶ በገዳዩ ላይ ምላሽ ሲሰጥ ነው።
“የጋራ ወታደራዊ ዘመቻው ለአሸባሪው ቡድን ከፍተኛ ኪሳራ አስከትሏል፣ ከ50 በላይ የአልሸባብ ታጣቂዎች ሲገደሉ ሌሎች በርካቶች ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል” ሲል የአፍሪካ ህብረት የሶማሊያ የድጋፍ እና ማረጋጋት ተልዕኮ (አውሶም) ማስታወቁን ዥንዋ ዘግቧል።ከሞቃዲሾ በስተደቡብ ምዕራብ 60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው ባሪሬ ከተማ፤ በሸበሌ ወንዝ ዳርቻ ከሚገኙ ስትራቴጂካዊ አካባቢዎች አንዷ ነች።
Via AS
@YeneTube @FikerAssefa
የአፍሪካ ህብረት የሶማሊያ የድጋፍ እና ማረጋጋት ተልዕኮ(አውሶም) በሶማሊያ የመንግስት ኃይሎች የሚደገፉት ወታደሮቹ ባሳለፍነው አርብ በደቡባዊ ሶማሊያ በባሪሬ ከተማ በተካሄደ ከባድ ውጊያ ከ50 በላይ የአል-ሸባብ አባላትን መግደላቸውን አስረጋገጠ።
አውሶም ከሶማሊያ መዲና ሞቃዲሾ በሰጠው መግለጫ፤ “በባሪሬ በተልዕኮው ወታደሮች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል” የሚሉ የሚዲያ ዘገባዎችን አስተባብሏል።
"አውሶም ኃይሎቹ ከሶማሊያ ብሔራዊ ጦር ኃይሎች (SNAF) ጋር በመተባበር የባሪሬ ከተማን መልሶ ለመቆጣጠር ሐምሌ 25 ቀን ጥቃት መጀመሩን ግልጽ ማድረግ ይፈልጋል" ሲል የአፍሪካ ህብረት የሶማሊያ የድጋፍ እና ማረጋጋት ተልዕኮ(አውሶም) ገልጿል።
አውሶም ይህን ያለው፤ አል-ሸባብ በባሪሬ በተካሄደው ከባድ ውጊያ፤ "የአፍሪካ ህብረት የወታደሮች ማጓጓዣ ተሽከርካሪዎችን መውደማቸውን እና የአውሶም ወታደሮች ማፈግፈጋቸውን" መግለጹን አስመልክቶ በገዳዩ ላይ ምላሽ ሲሰጥ ነው።
“የጋራ ወታደራዊ ዘመቻው ለአሸባሪው ቡድን ከፍተኛ ኪሳራ አስከትሏል፣ ከ50 በላይ የአልሸባብ ታጣቂዎች ሲገደሉ ሌሎች በርካቶች ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል” ሲል የአፍሪካ ህብረት የሶማሊያ የድጋፍ እና ማረጋጋት ተልዕኮ (አውሶም) ማስታወቁን ዥንዋ ዘግቧል።ከሞቃዲሾ በስተደቡብ ምዕራብ 60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው ባሪሬ ከተማ፤ በሸበሌ ወንዝ ዳርቻ ከሚገኙ ስትራቴጂካዊ አካባቢዎች አንዷ ነች።
Via AS
@YeneTube @FikerAssefa
❤15
ከፍተኛ የግብር ጫና ዜጎችን ከመደበኛ ሥራ እያራቃቸው ነው ሲል አይኤምኤፍ አስጠነቀቀ!
በኢትዮጵያ ያለው የግብር ስርዓት፣ በተለይም በዝቅተኛ ገቢ ላይ ባሉ ግብር ከፋዮች ላይ የሚጣለው ከፍተኛ የግብር ተመን፣ ዜጎች ወደ መደበኛ የስራ ዘርፍ እንዳይገቡ ተስፋ እያስቆረጣቸው መሆኑን የአይኤምኤፍ ሪፖርት አመለከተ።
የአለም የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ ) ባወጣው የቅርብ ጊዜ የግብር ግምገማ ላይ እንዳመለከተው፣ የኢትዮጵያ የግብር ስርዓት አወቃቀር በዝቅተኛ የገቢ ደረጃ ላይ ባሉ ዜጎች ላይ ከፍተኛ የግብር ተመን የሚጥል ሲሆን፣ ይህም ድርጅቶችና ሰራተኞች መደበኛ ባልሆነው የንግድ መስክ ውስጥ እንዲቆዩ ሊያደርግ ይችላል። ይህ ደግሞ ለልማት የሚውለውን የግብር ገቢ እንዲቀንስ ያደርጋል።
ሪፖርቱ አክሎም፣ ምንም እንኳ ኢትዮጵያ ጠንካራ የኢኮኖሚ እድገት እያሳየች ብትሆንም፣ የግብር አሰባሰቧ ከሰሃራ በታች ካሉ አገሮች ጋር ሲነጻጸር ዝቅተኛ መሆኑን ጠቅሷል። ከገቢና ትርፍ የሚገኘው የግብር ገቢም ቢሆን ደካማ መሆኑ ተጠቁሟል።
ካፒታል የተመለከተዉ የአይኤምኤፍ ዘገባ እንደሚያሳየው፣ ኢትዮጵያ በብቃት የግብር ስርዓቷን ብታስተካክል ከጠቅላላ ሀገራዊ ምርቷ (GDP) እስከ 17% የሚደርስ ገቢ ማግኘት ትችል ነበር፤ አሁን የምታገኘው ግን 8% ብቻ ነው። ይህ ደግሞ በገንዘብ አሰባሰብ እና አጠቃቀም ላይ ትልቅ ክፍተት መኖሩን ያሳያል።
ሪፖርቱ ይህንን ችግር ለመቅረፍ የግብር አሰባሰብ መሰረትን በማስፋፋት፣ ከአላስፈላጊ የግብር ነጻነቶች በመውጣትና የግብር አክባሪነትን በማሻሻል ዘላቂ የኢኮኖሚ እድገትን ማስቀጠል እንደሚቻል አሳስቧል።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ ያለው የግብር ስርዓት፣ በተለይም በዝቅተኛ ገቢ ላይ ባሉ ግብር ከፋዮች ላይ የሚጣለው ከፍተኛ የግብር ተመን፣ ዜጎች ወደ መደበኛ የስራ ዘርፍ እንዳይገቡ ተስፋ እያስቆረጣቸው መሆኑን የአይኤምኤፍ ሪፖርት አመለከተ።
የአለም የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ ) ባወጣው የቅርብ ጊዜ የግብር ግምገማ ላይ እንዳመለከተው፣ የኢትዮጵያ የግብር ስርዓት አወቃቀር በዝቅተኛ የገቢ ደረጃ ላይ ባሉ ዜጎች ላይ ከፍተኛ የግብር ተመን የሚጥል ሲሆን፣ ይህም ድርጅቶችና ሰራተኞች መደበኛ ባልሆነው የንግድ መስክ ውስጥ እንዲቆዩ ሊያደርግ ይችላል። ይህ ደግሞ ለልማት የሚውለውን የግብር ገቢ እንዲቀንስ ያደርጋል።
ሪፖርቱ አክሎም፣ ምንም እንኳ ኢትዮጵያ ጠንካራ የኢኮኖሚ እድገት እያሳየች ብትሆንም፣ የግብር አሰባሰቧ ከሰሃራ በታች ካሉ አገሮች ጋር ሲነጻጸር ዝቅተኛ መሆኑን ጠቅሷል። ከገቢና ትርፍ የሚገኘው የግብር ገቢም ቢሆን ደካማ መሆኑ ተጠቁሟል።
ካፒታል የተመለከተዉ የአይኤምኤፍ ዘገባ እንደሚያሳየው፣ ኢትዮጵያ በብቃት የግብር ስርዓቷን ብታስተካክል ከጠቅላላ ሀገራዊ ምርቷ (GDP) እስከ 17% የሚደርስ ገቢ ማግኘት ትችል ነበር፤ አሁን የምታገኘው ግን 8% ብቻ ነው። ይህ ደግሞ በገንዘብ አሰባሰብ እና አጠቃቀም ላይ ትልቅ ክፍተት መኖሩን ያሳያል።
ሪፖርቱ ይህንን ችግር ለመቅረፍ የግብር አሰባሰብ መሰረትን በማስፋፋት፣ ከአላስፈላጊ የግብር ነጻነቶች በመውጣትና የግብር አክባሪነትን በማሻሻል ዘላቂ የኢኮኖሚ እድገትን ማስቀጠል እንደሚቻል አሳስቧል።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
❤30👍26
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በየመን ጀልባ መስጠም አደጋ ሕይወታቸውን ላጡ ኢትዮጵያውያን የተሰማውን ሃዘን ገለጸ!
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በየመን በደረሰው የጀልባ መስጠም አደጋ በኢትዮጵያውያን ዜጎች ላይ በደረሰው የሞት አደጋ የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን ገልጿል፡፡ሚኒስቴሩ የደረሰውን አደጋ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን እያጣራ መሆኑን ለፋና ዲጂታል አስታውቋል፡፡
በደረሰው የጀልባ መስጠም አደጋ ለሕልፈት ለተዳረጉ ኢትዮጵያውያን ዜጎች ቤተሰቦችም መጽናናትን ተመኝቷል፡፡መንግሥት ዜጎች በተለያዩ ሀገራት በሕጋዊ መንገድ ተንቀሳቅሰው መሥራት እንዲችሉ ለማድረግ የተለያዩ ጥረቶችን በማከናወን በርካታ ዜጎችን የዕድሉ ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑ ተመላክቷል፡፡ሚኒስቴሩ ዜጎች በሕጋዊ መንገድ ብቻ የውጭ ሀገራት የሥራ ሥምሪት ተጠቃሚ እንዲሆኑ እና ከሕገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ራሳቸውን እንዲጠብቁም አሳስቧል፡፡
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በየመን በደረሰው የጀልባ መስጠም አደጋ በኢትዮጵያውያን ዜጎች ላይ በደረሰው የሞት አደጋ የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን ገልጿል፡፡ሚኒስቴሩ የደረሰውን አደጋ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን እያጣራ መሆኑን ለፋና ዲጂታል አስታውቋል፡፡
በደረሰው የጀልባ መስጠም አደጋ ለሕልፈት ለተዳረጉ ኢትዮጵያውያን ዜጎች ቤተሰቦችም መጽናናትን ተመኝቷል፡፡መንግሥት ዜጎች በተለያዩ ሀገራት በሕጋዊ መንገድ ተንቀሳቅሰው መሥራት እንዲችሉ ለማድረግ የተለያዩ ጥረቶችን በማከናወን በርካታ ዜጎችን የዕድሉ ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑ ተመላክቷል፡፡ሚኒስቴሩ ዜጎች በሕጋዊ መንገድ ብቻ የውጭ ሀገራት የሥራ ሥምሪት ተጠቃሚ እንዲሆኑ እና ከሕገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ራሳቸውን እንዲጠብቁም አሳስቧል፡፡
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
😁17❤12👎10👍2😭2
የቀድሞው የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በተመድ የአፍሪካ ሕብረት ቋሚ መልዕክተኛ ሆነው ተሾሙ!
የቀድሞው የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና በዓለም የንግድ ድርጅት (ጄኔቫ) የአፍሪካ ሕብረት ቋሚ መልዕክተኛ ሆነው ተሹመዋል።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ ዶ/ር ግርማ አመንቴን ለዚህ ትልቅ ኃላፊነት ለመሾም ያሳለፉትን ውሳኔ በአድናቆት እንደምትመለከተው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል።
ውሳኔው ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረኮች አፍሪካን በመወከል ለምትጫወተው ሚና ሕብረቱ ያለውን ትልቅ ግምት የሚያመላክት ነው ሲል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለኢቢሲ ገልጿል።
ዶ/ር ግርማ አመንቴ የካበተ የአመራር ልምዳቸውን በመጠቀም የተጣለባቸውን ትልቅ ኃላፊነት በላቀ ብቃት እንደሚወጡት ያለውን ሙሉ እምነትም ሚኒስቴሩ ጨምሮ ገልጿል።
Via EBC
@YeneTube @FikerAssefa
የቀድሞው የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና በዓለም የንግድ ድርጅት (ጄኔቫ) የአፍሪካ ሕብረት ቋሚ መልዕክተኛ ሆነው ተሹመዋል።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ ዶ/ር ግርማ አመንቴን ለዚህ ትልቅ ኃላፊነት ለመሾም ያሳለፉትን ውሳኔ በአድናቆት እንደምትመለከተው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል።
ውሳኔው ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረኮች አፍሪካን በመወከል ለምትጫወተው ሚና ሕብረቱ ያለውን ትልቅ ግምት የሚያመላክት ነው ሲል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለኢቢሲ ገልጿል።
ዶ/ር ግርማ አመንቴ የካበተ የአመራር ልምዳቸውን በመጠቀም የተጣለባቸውን ትልቅ ኃላፊነት በላቀ ብቃት እንደሚወጡት ያለውን ሙሉ እምነትም ሚኒስቴሩ ጨምሮ ገልጿል።
Via EBC
@YeneTube @FikerAssefa
❤34😁12
Forwarded from YeneTube
በሩን ይክፈቱ ችግረወን
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
በ 25% ዲስካውንት ለገበያ አቅርበናል!
📌 ፒያሳ ሊሴ ገ/ማርያም ትምህርት ቤት
👉30% እና ከዛ በላይ ለሚከፍል ከከፈሉት ላይ 25% ደረስ የሚደርስ ቅናሽ አዘጋጅተናል
✅ መገልገያዎች
👉 ሦስት ሊፍት
👉 ባለ 3 ፎቅ የመኪና ማቆሚያ ቦታ
👉 ቴራስ
👉 ያልተገደበ የውሃ አቅርቦት
👉 የመጠባበቂያ ጀነሬተር
📌 የካሬ አማራጮች
👉ባለ 1መኝታ - 63 ካሬ
👉ባለ 2 መኝታ - 86 እስከ 103 ካሬ
👉ባለ 3 መኝታ - 132 እስከ 146 ካሬ
👉1 መኝታ 63ካሬ=
10% ቅድመ ክፍያ 693,000 ብር
ሙሉ ክፍያ 6,930,000 ብር
👉2መኝታ 86 ካሬ
10%ቅድመ ክፍያ 946,000 ብር
ሙሉ ክፍያ 9,460,000 ብር
👉3መኝታ 114 ካሬ
10%ቅድመ ክፍያ 1,219,800 ብር
ሙሉ ክፍያ 12,198,000 ብር
ለበለጠ መረጃ
☎️ +251976195835
Telegram username
@Ruthtemersales
What's app
https://wa.me/251976195835
TEMER PROPERTIES
Create | Construct | Deliver
#TemerProperties #Temerrealestate
📌 ፒያሳ ሊሴ ገ/ማርያም ትምህርት ቤት
👉30% እና ከዛ በላይ ለሚከፍል ከከፈሉት ላይ 25% ደረስ የሚደርስ ቅናሽ አዘጋጅተናል
✅ መገልገያዎች
👉 ሦስት ሊፍት
👉 ባለ 3 ፎቅ የመኪና ማቆሚያ ቦታ
👉 ቴራስ
👉 ያልተገደበ የውሃ አቅርቦት
👉 የመጠባበቂያ ጀነሬተር
📌 የካሬ አማራጮች
👉ባለ 1መኝታ - 63 ካሬ
👉ባለ 2 መኝታ - 86 እስከ 103 ካሬ
👉ባለ 3 መኝታ - 132 እስከ 146 ካሬ
👉1 መኝታ 63ካሬ=
10% ቅድመ ክፍያ 693,000 ብር
ሙሉ ክፍያ 6,930,000 ብር
👉2መኝታ 86 ካሬ
10%ቅድመ ክፍያ 946,000 ብር
ሙሉ ክፍያ 9,460,000 ብር
👉3መኝታ 114 ካሬ
10%ቅድመ ክፍያ 1,219,800 ብር
ሙሉ ክፍያ 12,198,000 ብር
ለበለጠ መረጃ
☎️ +251976195835
Telegram username
@Ruthtemersales
What's app
https://wa.me/251976195835
TEMER PROPERTIES
Create | Construct | Deliver
#TemerProperties #Temerrealestate
❤9