Spiritual Gift መንፈሳዊ ስጦታ
YAHO💚 WOMEN'S GIFT PACKAGE
- ነጠላ
- ዉዳሴ ማርያም
- የሚያበራ ምስል
- ሽቶ
FREE DELIVERY
⨳ዋጋ 3500br
For order @Fikerassefa
YAHO💚 WOMEN'S GIFT PACKAGE
- ነጠላ
- ዉዳሴ ማርያም
- የሚያበራ ምስል
- ሽቶ
FREE DELIVERY
⨳ዋጋ 3500br
For order @Fikerassefa
❤10😁5
ማስታወቂያ
በZoje Digital slightly Used ማሽን interlock, Overlock, Single needles machine ያላቹ በዚህ @Fikerassefa ያናግሩን።
በZoje Digital slightly Used ማሽን interlock, Overlock, Single needles machine ያላቹ በዚህ @Fikerassefa ያናግሩን።
❤6
ኤርትራ 10 ኪ.ሜ ወደ ኢትዮጵያ ገብታለች
በትግራይ ክልል ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ የጀርመን ዜና ወኪል ከስፍራው አንድ ዘገባ አሰራጭቷል፡፡
በመቀሌ ነዋሪ የሆኑ አንዲት ለዜና አውታሩ ሲናገሩ ‹‹አሁን ላይ ሆነን ምንም ማቀድ አንችልም፡፡ አዲስ ጦርነት ነገ ሊጀመር ይችላል፡፡›› ያሉ ሲሆን ነዋሪው በዚህ የተነሳ ከፍተኛ ፍርሀት ውስጥ መውደቁን አስረድተዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹ኑሮ በጣም እየተወደደ ነው፡፡ እኛ ሰላማዊ መፍትሄ መጥቶ ወደስራችን መመለስና ህይወታችንን መልሰን መገንባት ነው የምንፈልገው›› ብለዋል፡፡
እንደዘገባው በህወሀት ውስጥ የተፈጠረውን ክፍፍል ተከትሎ የትግራይ መከላከያ ሀይል(ቲዲኤፍ) ዋና አዛዥ የነበሩት ታደሰ ወረደ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ሆነዋል፡፡፡ እሳቸው በህዝቡ ዘንድ ያለውን ስጋት በማጣጣል ‹‹ጦርነት አይኖርም፡፡
ከትግራይ በኩል ምንም አይነት ቀስቃሽ ሁኔታ የለም›› በማለት እየተናገሩ መሆናቸውንም አስረድቷል፡፡ ዘገባው ሲቀጥል በሌላ በኩል የህወሀት ሊቀመንበር የሆኑት ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ደግሞ በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ለተፈጠረው ችግር ፖለቲካዊ መፍትሄ እንዲፈለግ እያሳሰቡ መሆናቸውን ገልጿል፡፡ የፌዴራል መንግስቱና አጋሮቹ ለጦርነት እያደረጉ ካለው ዝግጅት እንዲቆጠብ አለም አቀፉ ማህበረሰብ ጫና እንዲያደርግበት ጥሪ ማቅረባቸውንም አስረድቷል፡፡
ይሁንና እነዚህ ሁሉ የመቀሌ ነዋሪዎችን ስጋት እንዳልቀረፉ ገልጿል፡፡ አንድ የከተማው ነዋሪ ሲናገሩ ‹‹ህዝቡ አሁን ከባንክ ገንዘብ እያወጣ ነው፡፡ እንደጤፍ የመሳሰሉ እህሎችም ከመጋዘን እያለቁ ነው›› ያሉ ሲሆን ለሁለቱም የህወሀት አንጃዎችም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ በመልእክታቸውም ‹‹ሁለቱም የህወሀት አንጃዎች ወይ ስልጣን ይልቀቁ፣ አልያም ተፅእኗቸውን ተጠቅመው ከማእከላዊው መንግስት ጋር ይህንን ቀውስ ለማስወገድና ጦርነትን ለማስቀረት ይስሩ›› ማለታቸውን ዘገባው ጠቅሷል፡፡
በሌላ በኩል በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል ድጋሚ ጦርነት ይቀሰቀሳል የሚል ስጋት እንዳለ የጠቀሰውዘገባው በዚህ ጉዳይ የጀርመን አለም አቀፍና የደህንነት ጉዳዮች ኢኒስቲትዩት የአፍሪካ ጉዳዮች ኤክስፐርት የሆኑትን ጊርት ኩርዝ ማነጋገሩን አስታውቋል፡፡
ኩርዝ ለዜና አውታሩ በሰጡት ማብራሪያ ሁለቱ አገራት ሙሉ ጦርነት ውስጥ ይገባሉ የሚል እምነት እንደሌላቸው ጠቅሰው ይሁንና በውክልና የሚደረግ ግጭት እንደሚኖር አስረድተዋል፡፡
ዘገባው አያይዞም ኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ ግዛት 10 ኪሎሜትር መግባቷንና ጦር እያሰለጠነች መሆኑን ዘገባው ጠቅሷል።
@Yenetube @Fikerassefa
በትግራይ ክልል ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ የጀርመን ዜና ወኪል ከስፍራው አንድ ዘገባ አሰራጭቷል፡፡
በመቀሌ ነዋሪ የሆኑ አንዲት ለዜና አውታሩ ሲናገሩ ‹‹አሁን ላይ ሆነን ምንም ማቀድ አንችልም፡፡ አዲስ ጦርነት ነገ ሊጀመር ይችላል፡፡›› ያሉ ሲሆን ነዋሪው በዚህ የተነሳ ከፍተኛ ፍርሀት ውስጥ መውደቁን አስረድተዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹ኑሮ በጣም እየተወደደ ነው፡፡ እኛ ሰላማዊ መፍትሄ መጥቶ ወደስራችን መመለስና ህይወታችንን መልሰን መገንባት ነው የምንፈልገው›› ብለዋል፡፡
እንደዘገባው በህወሀት ውስጥ የተፈጠረውን ክፍፍል ተከትሎ የትግራይ መከላከያ ሀይል(ቲዲኤፍ) ዋና አዛዥ የነበሩት ታደሰ ወረደ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ሆነዋል፡፡፡ እሳቸው በህዝቡ ዘንድ ያለውን ስጋት በማጣጣል ‹‹ጦርነት አይኖርም፡፡
ከትግራይ በኩል ምንም አይነት ቀስቃሽ ሁኔታ የለም›› በማለት እየተናገሩ መሆናቸውንም አስረድቷል፡፡ ዘገባው ሲቀጥል በሌላ በኩል የህወሀት ሊቀመንበር የሆኑት ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ደግሞ በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ለተፈጠረው ችግር ፖለቲካዊ መፍትሄ እንዲፈለግ እያሳሰቡ መሆናቸውን ገልጿል፡፡ የፌዴራል መንግስቱና አጋሮቹ ለጦርነት እያደረጉ ካለው ዝግጅት እንዲቆጠብ አለም አቀፉ ማህበረሰብ ጫና እንዲያደርግበት ጥሪ ማቅረባቸውንም አስረድቷል፡፡
ይሁንና እነዚህ ሁሉ የመቀሌ ነዋሪዎችን ስጋት እንዳልቀረፉ ገልጿል፡፡ አንድ የከተማው ነዋሪ ሲናገሩ ‹‹ህዝቡ አሁን ከባንክ ገንዘብ እያወጣ ነው፡፡ እንደጤፍ የመሳሰሉ እህሎችም ከመጋዘን እያለቁ ነው›› ያሉ ሲሆን ለሁለቱም የህወሀት አንጃዎችም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ በመልእክታቸውም ‹‹ሁለቱም የህወሀት አንጃዎች ወይ ስልጣን ይልቀቁ፣ አልያም ተፅእኗቸውን ተጠቅመው ከማእከላዊው መንግስት ጋር ይህንን ቀውስ ለማስወገድና ጦርነትን ለማስቀረት ይስሩ›› ማለታቸውን ዘገባው ጠቅሷል፡፡
በሌላ በኩል በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል ድጋሚ ጦርነት ይቀሰቀሳል የሚል ስጋት እንዳለ የጠቀሰውዘገባው በዚህ ጉዳይ የጀርመን አለም አቀፍና የደህንነት ጉዳዮች ኢኒስቲትዩት የአፍሪካ ጉዳዮች ኤክስፐርት የሆኑትን ጊርት ኩርዝ ማነጋገሩን አስታውቋል፡፡
ኩርዝ ለዜና አውታሩ በሰጡት ማብራሪያ ሁለቱ አገራት ሙሉ ጦርነት ውስጥ ይገባሉ የሚል እምነት እንደሌላቸው ጠቅሰው ይሁንና በውክልና የሚደረግ ግጭት እንደሚኖር አስረድተዋል፡፡
ዘገባው አያይዞም ኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ ግዛት 10 ኪሎሜትር መግባቷንና ጦር እያሰለጠነች መሆኑን ዘገባው ጠቅሷል።
@Yenetube @Fikerassefa
❤63👍1👀1
Forwarded from YeneTube
በሩን ይክፈቱ ችግረወን
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
❤8
የሞሳድ ኃላፊ የጋዛ ነዋሪዎችን ወደ ኢትዮጵያ፣ ሊቢያና ኢንዶኔዥያ ለማዘዋወር አሜሪካ ድጋፍ እንድታደርግ መጠየቃቸው ተዘግበ!
የእስራኤል የስለላ ድርጅት (ሞሳድ) ኃላፊ ዴቪድ ባርኔያ የጋዛ ነዋሪዎችን ወደ ኢትዮጵያ፣ ሊቢያ፣ ኢንዶኔዥያ ለማዘዋወር አሜሪካ ድጋፍ እንድታደርግ የሀገሪቱን ልዩ መልዕክተኛ መጠየቃቸው ተዘግበ።የሞሳድ ኃላፊው ይህን ጥያቄ ያቀረቡት በዚህ ሳምንት በዋሽንግተን ባደረጉት ጎብኝት ወቅት መሆኑን አክሲዮስ ዘግቧል።
እስራኤል ፍልስጤማውያንን ከጋዛ ለማዘዋወር የትራምፕን አስተዳደር እርዳታ እየፈለገች መሆኑን ጉዳዩን የሚያውቁ ሁለት ምንጮችን ጠቅሶ የዜና አውታሩ ዘግቧል፣ ሁለቱ ምንጮች እንደገለፁት፤ የሞሳዱ ኃላፊ ባርኔያ፤ ኢትዮጵያ፣ ኢንዶኔዥያ እና ሊቢያ ከጋዛ የፍልስጤማውያን ስደተኞችን ለመቀበል ፈቃደኝነት አሳይተዋል ሲሉ ለአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ ተናግረዋል። እናም ዋሽንግተን እነዚህ ሀገራት ስደተኞችን ለማዛወር እንዲስማሙ “ማበረታቻ” መስጠት አለባት ማለታቸው ተገልጿል።
ይሁን እንጂ ስቲቭ ዊትኮፍ በጉዳዩ ላይ ቁርጠኛ አልነበረም ሲሉ አንደኛው ምንጭ ገልጿል።የአሜሪካ ባለስልጣናትም ከአረብ ከሀገራት ተቃውሞ የሚያከትል በመሆኑ ዋይት ሀውስ ፍልስጤማውያንን ከጋዛ የማስወጣት ፍላጎት እንደሌለው ገልጸዋል ሲል ዘገባው አክሏል።
ከወራት በፊት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የጋዛ ሰርጥ ግንባት ሲጀመር የጋዛ ነዋሪዎች በሙሉ ላልተወሰነ ጊዜ ወደሌላ ቦታ እንዲዘዋወሩ ሀሳብ ማቅረባቸው ይታወቃል። ሀሳቡን የእራኤሉ መሪ ኔታንያሁ እና ጥምረታቸው ሲደግፉ፣ የአረብ ሀገራት እና አብዛኛው የምዕራቡ ዓለም በብርቱ ተቃውመውታል።
Via Axios/AS
@YeneTube @FikerAssefa
የእስራኤል የስለላ ድርጅት (ሞሳድ) ኃላፊ ዴቪድ ባርኔያ የጋዛ ነዋሪዎችን ወደ ኢትዮጵያ፣ ሊቢያ፣ ኢንዶኔዥያ ለማዘዋወር አሜሪካ ድጋፍ እንድታደርግ የሀገሪቱን ልዩ መልዕክተኛ መጠየቃቸው ተዘግበ።የሞሳድ ኃላፊው ይህን ጥያቄ ያቀረቡት በዚህ ሳምንት በዋሽንግተን ባደረጉት ጎብኝት ወቅት መሆኑን አክሲዮስ ዘግቧል።
እስራኤል ፍልስጤማውያንን ከጋዛ ለማዘዋወር የትራምፕን አስተዳደር እርዳታ እየፈለገች መሆኑን ጉዳዩን የሚያውቁ ሁለት ምንጮችን ጠቅሶ የዜና አውታሩ ዘግቧል፣ ሁለቱ ምንጮች እንደገለፁት፤ የሞሳዱ ኃላፊ ባርኔያ፤ ኢትዮጵያ፣ ኢንዶኔዥያ እና ሊቢያ ከጋዛ የፍልስጤማውያን ስደተኞችን ለመቀበል ፈቃደኝነት አሳይተዋል ሲሉ ለአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ ተናግረዋል። እናም ዋሽንግተን እነዚህ ሀገራት ስደተኞችን ለማዛወር እንዲስማሙ “ማበረታቻ” መስጠት አለባት ማለታቸው ተገልጿል።
ይሁን እንጂ ስቲቭ ዊትኮፍ በጉዳዩ ላይ ቁርጠኛ አልነበረም ሲሉ አንደኛው ምንጭ ገልጿል።የአሜሪካ ባለስልጣናትም ከአረብ ከሀገራት ተቃውሞ የሚያከትል በመሆኑ ዋይት ሀውስ ፍልስጤማውያንን ከጋዛ የማስወጣት ፍላጎት እንደሌለው ገልጸዋል ሲል ዘገባው አክሏል።
ከወራት በፊት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የጋዛ ሰርጥ ግንባት ሲጀመር የጋዛ ነዋሪዎች በሙሉ ላልተወሰነ ጊዜ ወደሌላ ቦታ እንዲዘዋወሩ ሀሳብ ማቅረባቸው ይታወቃል። ሀሳቡን የእራኤሉ መሪ ኔታንያሁ እና ጥምረታቸው ሲደግፉ፣ የአረብ ሀገራት እና አብዛኛው የምዕራቡ ዓለም በብርቱ ተቃውመውታል።
Via Axios/AS
@YeneTube @FikerAssefa
❤33😁23😭6👎4🔥1
በደብቡ ወሎ ዞን ከተለያዮ የኢትዮጱያ አካባቢ ተፈናቅለዉ በመጠለያ ካምፕ ዉስጥ የሚገኙ የሀገር ዉስጥ ተፈናቃዮች ዝናቡ በመጨመሩ መጠለያ ድንዃኖቻቸዉ እየፈረሱና ዝናብ እያስገቡ መሆኑን ተናገሩ።
ለስድስት ወራት አገልግሎት እንዲሰጡ የመጡ የመጠለያ ድንዃኖች ለሶስት አመት ያገለገሉ ሲህን በፀሀይና ዝናብ ብዛት ተቀዳዶ አገልግሎት የማይሰጥበት ደረጃ ላይ ደርሶል ብለዋል።ነፍሰ ጡር እናቶች ህፃናትና አረጋዉያን በከፍተኛ ችግር ዉስጥ እንዳሉም ተነግሯል።
ከ4 ዓመታት በፊት በሞቀ ጎጃቸው ውስጥ ሆነው የክረምቱን መምጣት በጉጉት የሚጠብቁ የሚያርሱ እና የሚያመርቱ ገበሬዎች ነበሩ፡፡ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች በተፈጠሩ የሰላም መደፍረሶች ቤታቸውን ትተው የተፈናቀሉት እነኝህ በደቡብ ወሎ ዞን ባሉ 11 የመጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ የሚገኙ ቁጥራቸው ከ14 ሺ የሚልቅ ተፈናቃዮች ዛሬ ላይ ግን የተጠለሉበት የሸራ ድንኳን እና ላስቲክ ከክረምቱ ዝናብ የሚያስጥል ሆኖ አላገኙትም፡፡ ለበረከት ሲፈልጉት የነበረው ዝናብም ቤታቸውን አፍራሽ ሆኗል ነው የሚሉት፡፡
‹‹ በክረምቱ ብዙ ሰዎች ተቸገሩብን፤ ዝናብ እየጎዳን ነው በጣም ከብዷል፡፡ አሁን ከሞቱት እኛ እንሻላለን የሚል ነው እንጂ ዝናቡ ከባድ ነው፡፡›› ‹‹የዝናቡ ነገር አላህ ይዞት ነው እንጂ ልብስ ደራርበን ነው የምንተኛው በጣም ነው የተቸገርነው››፡፡ ማለታቸውን DW ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
ለስድስት ወራት አገልግሎት እንዲሰጡ የመጡ የመጠለያ ድንዃኖች ለሶስት አመት ያገለገሉ ሲህን በፀሀይና ዝናብ ብዛት ተቀዳዶ አገልግሎት የማይሰጥበት ደረጃ ላይ ደርሶል ብለዋል።ነፍሰ ጡር እናቶች ህፃናትና አረጋዉያን በከፍተኛ ችግር ዉስጥ እንዳሉም ተነግሯል።
ከ4 ዓመታት በፊት በሞቀ ጎጃቸው ውስጥ ሆነው የክረምቱን መምጣት በጉጉት የሚጠብቁ የሚያርሱ እና የሚያመርቱ ገበሬዎች ነበሩ፡፡ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች በተፈጠሩ የሰላም መደፍረሶች ቤታቸውን ትተው የተፈናቀሉት እነኝህ በደቡብ ወሎ ዞን ባሉ 11 የመጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ የሚገኙ ቁጥራቸው ከ14 ሺ የሚልቅ ተፈናቃዮች ዛሬ ላይ ግን የተጠለሉበት የሸራ ድንኳን እና ላስቲክ ከክረምቱ ዝናብ የሚያስጥል ሆኖ አላገኙትም፡፡ ለበረከት ሲፈልጉት የነበረው ዝናብም ቤታቸውን አፍራሽ ሆኗል ነው የሚሉት፡፡
‹‹ በክረምቱ ብዙ ሰዎች ተቸገሩብን፤ ዝናብ እየጎዳን ነው በጣም ከብዷል፡፡ አሁን ከሞቱት እኛ እንሻላለን የሚል ነው እንጂ ዝናቡ ከባድ ነው፡፡›› ‹‹የዝናቡ ነገር አላህ ይዞት ነው እንጂ ልብስ ደራርበን ነው የምንተኛው በጣም ነው የተቸገርነው››፡፡ ማለታቸውን DW ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
❤20😭3👍1
የማዕድን እሰጥአገባ፣ የኦሮሚያ ማዕድን ባለስልጣን የሆንግኮንጉ ሺንግሹ ማዕድን እንዲያለማ የተሰጠው ፍቃድ እንዲሰረዝ ጠየቀ!
በኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ ላይ ሰፊ አንድምታ ባለው አኳኋን የኦሮሚያ ማዕድን ልማት ባለስልጣን (OMDA) የፌደራል መንግስት በምዕራብ ወለጋ ዞን ማዕድን እንዲያለማ ሶስት ፈቃዶች የተሰጠው ሆንግኮንግ ዢንግሹ ማዕድን ኢንተርናሽናል ኢንቨስትመንት ኩባንያ (Hong Kong Xingxu Mining International Investment Co. Ltd) ፈቃዶቹ እንዲሰረዙ መጠየቁ ተገለጸ።
ባለስልጣኑ ለማዕድን ሚኒስቴር ሐምሌ ቀን 2017 ዓ.ም በጻፈው ደብዳቤ ሆንግ ኮንግ ሺንግሹ ኩባንያ የፌደራል እና የክልሉን መንግስት አዋጆች ባለማክበር፣ ስራውን ባግባቡ ባለማከናወን እና የአካሄድ ጥሰቶችን በመፈጸም “የገባውን ውል አላከበረምል” ሲል በመግለጽ የተሰጠው የማዕድን ፍለጋ ፈቃድ እንዲሰረዝ ጠይቋል።
ባለስለጣኑ በተጨማሪም “በሆንግ ኮንግ ሺንግሹ ማዕድን ያገኘውን የታደሰ የማዕድን ፍለጋ ፈቃድ “እውቅና እንደማይሰጠው” አስታውቋል።አስካሪ ሜታልስ የነጆ ወርቅ ፕሮጀክትን ሙሉ በሙሉ ጠቀለለው በሚል የቀረበውን መረጃ በተመለከተ አዲስ ስታንዳርድ ያነጋገራቸው የሆንግኮንጉ ኩባንያ ሺንግሹ ማዕድን የሀገር ውስጥ ስራ አስኪያጅ ሱራፌል ወንድማገኝ የመገናኛ ብዙሃኑ ዘገባዎች ትክክል አይደሉም ሲሉ አስተባብለዋል።
ሙሉውን ለማንበብ:
https://addisstandard.com/Amharic/?p=8557
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ ላይ ሰፊ አንድምታ ባለው አኳኋን የኦሮሚያ ማዕድን ልማት ባለስልጣን (OMDA) የፌደራል መንግስት በምዕራብ ወለጋ ዞን ማዕድን እንዲያለማ ሶስት ፈቃዶች የተሰጠው ሆንግኮንግ ዢንግሹ ማዕድን ኢንተርናሽናል ኢንቨስትመንት ኩባንያ (Hong Kong Xingxu Mining International Investment Co. Ltd) ፈቃዶቹ እንዲሰረዙ መጠየቁ ተገለጸ።
ባለስልጣኑ ለማዕድን ሚኒስቴር ሐምሌ ቀን 2017 ዓ.ም በጻፈው ደብዳቤ ሆንግ ኮንግ ሺንግሹ ኩባንያ የፌደራል እና የክልሉን መንግስት አዋጆች ባለማክበር፣ ስራውን ባግባቡ ባለማከናወን እና የአካሄድ ጥሰቶችን በመፈጸም “የገባውን ውል አላከበረምል” ሲል በመግለጽ የተሰጠው የማዕድን ፍለጋ ፈቃድ እንዲሰረዝ ጠይቋል።
ባለስለጣኑ በተጨማሪም “በሆንግ ኮንግ ሺንግሹ ማዕድን ያገኘውን የታደሰ የማዕድን ፍለጋ ፈቃድ “እውቅና እንደማይሰጠው” አስታውቋል።አስካሪ ሜታልስ የነጆ ወርቅ ፕሮጀክትን ሙሉ በሙሉ ጠቀለለው በሚል የቀረበውን መረጃ በተመለከተ አዲስ ስታንዳርድ ያነጋገራቸው የሆንግኮንጉ ኩባንያ ሺንግሹ ማዕድን የሀገር ውስጥ ስራ አስኪያጅ ሱራፌል ወንድማገኝ የመገናኛ ብዙሃኑ ዘገባዎች ትክክል አይደሉም ሲሉ አስተባብለዋል።
ሙሉውን ለማንበብ:
https://addisstandard.com/Amharic/?p=8557
@YeneTube @FikerAssefa
❤31
በምስራቅ አፍሪካ የመጀመሪያው የሆነ የፖስ ማሽን መገጣጠሚያ ፋብሪካ በኢትዮጵያ ተመረቀ!
ሳንቲምፔይ ፋይናንሻል ሶሉሽን በኢትዮጵያ እና በምስራቅ አፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን የፖስ ማሽን መገጣጠሚያ ፋብሪካውን እና ዘመናዊ የክፍያ ስዊች ሲስተምን በይፋ ማስጀመሩን አስታውቋል።ይህ ፋብሪካ የሀገሪቱን ጥሬ ገንዘብ አልባ የግብይት ስርዓት ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ትልቅ አስተዋፅዖ እንደሚያበረክት ይጠበቃል።
በቀን 3,000 ዘመናዊ የፖስ ማሽኖችን የማምረት አቅም ያለው ይህ ፋብሪካ፣ በኢትዮጵያ ልጆች ተገጣጥመው በአገር ውስጥ በተገነቡ ሶፍትዌሮች የታገዙ ማሽኖችን ለባንኮች እና ለተለያዩ የንግድ ተቋማት ማቅረብ ጀምሯል ተብሏል።
ይህ የሀገር ውስጥ ምርት ከዚህ ቀደም ፖስ ማሽኖችን ከአውሮፓና ከቻይና በመግዛት ለሃርድዌር እና ለሶፍትዌር ይወጣ የነበረውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እንደሚያድን የኩባንያው መግለጫ ያመለክታል።
ከፋብሪካው ጎን ለጎን የጥገና ማዕከልም የተቋቋመ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም ለጥገና ወደ ውጭ አገር ይላኩ የነበሩ የፖስ ማሽኖች በአገር ውስጥ እንዲጠገኑ ያስችላል መባሉን ሳንቲም ፔይ አስታዉቋል።
ይህም አገልግሎት የማይሰጡ ማሽኖችን ወደ ስራ በመመለስ ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚያደርግ ይጠበቃል።በተጨማሪም ሳንቲምፔይ ከዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ ከሚገኘው ሳኑ ፔይ ጋር በመተባበር ዘመናዊ የክፍያ ስዊች ስርዓትን ተግባራዊ በማድረግ ለባንኮች እና ለፋይናንሻል ተቋማት ዘመናዊ የክፍያ አገልግሎቶችን ማቅረብ እንደሚጀመር ከመግለጫዉ ለመረዳት ተችሏል።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
ሳንቲምፔይ ፋይናንሻል ሶሉሽን በኢትዮጵያ እና በምስራቅ አፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን የፖስ ማሽን መገጣጠሚያ ፋብሪካውን እና ዘመናዊ የክፍያ ስዊች ሲስተምን በይፋ ማስጀመሩን አስታውቋል።ይህ ፋብሪካ የሀገሪቱን ጥሬ ገንዘብ አልባ የግብይት ስርዓት ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ትልቅ አስተዋፅዖ እንደሚያበረክት ይጠበቃል።
በቀን 3,000 ዘመናዊ የፖስ ማሽኖችን የማምረት አቅም ያለው ይህ ፋብሪካ፣ በኢትዮጵያ ልጆች ተገጣጥመው በአገር ውስጥ በተገነቡ ሶፍትዌሮች የታገዙ ማሽኖችን ለባንኮች እና ለተለያዩ የንግድ ተቋማት ማቅረብ ጀምሯል ተብሏል።
ይህ የሀገር ውስጥ ምርት ከዚህ ቀደም ፖስ ማሽኖችን ከአውሮፓና ከቻይና በመግዛት ለሃርድዌር እና ለሶፍትዌር ይወጣ የነበረውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እንደሚያድን የኩባንያው መግለጫ ያመለክታል።
ከፋብሪካው ጎን ለጎን የጥገና ማዕከልም የተቋቋመ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም ለጥገና ወደ ውጭ አገር ይላኩ የነበሩ የፖስ ማሽኖች በአገር ውስጥ እንዲጠገኑ ያስችላል መባሉን ሳንቲም ፔይ አስታዉቋል።
ይህም አገልግሎት የማይሰጡ ማሽኖችን ወደ ስራ በመመለስ ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚያደርግ ይጠበቃል።በተጨማሪም ሳንቲምፔይ ከዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ ከሚገኘው ሳኑ ፔይ ጋር በመተባበር ዘመናዊ የክፍያ ስዊች ስርዓትን ተግባራዊ በማድረግ ለባንኮች እና ለፋይናንሻል ተቋማት ዘመናዊ የክፍያ አገልግሎቶችን ማቅረብ እንደሚጀመር ከመግለጫዉ ለመረዳት ተችሏል።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
❤28😁9👍4😭1
ሕወሓት ፌደራል መንግሥቱን ከሰሰ!
ሕወሓት፣ የትግራይ ሕዝብ ፍትሃዊ ጥያቄ በጦርነት ዛቻ ሊታፈን አይችልም ሲል ማምሻውን ባወጣው መግለጫ አቋሙን ገልጧል።
ከመሃል አገር ከሄደ የኃይማኖት ልዑካን ቡድን ጋር ሰሞኑን መወያየቱን የገለጠው ሕወሓት፣ የልዑካኑ አባላት በትግራይ ያለው "የሰላም ፍላጎት" እና "ዝግጁነት" ቀደም ሲል ከሠሙት የተለየ መኾኑን ተናግረዋል ብሏል።
ሕወሓት፣ በትግራይ በኩል ለግጭት የሚጋብዝ እንቅስቃሴ በሌለበት ኹኔታ ፌደራል መንግሥቱ የማስፈራራት ዘመቻ እያካሄደ፣ የታጠቁ ሃይሎችን እያደራጀና እያስታጠቀ ይገኛል በማለትም መክሰሱን ዋዜማ ዘግባለች፡፡
መንግሥት በግጭት ማቆም ስምምነቱ መሠረት ግዴታውን እስካልተወጣ ድረስ፣ የትግራይ ሕዝብ ከመሪ ድርጅቱ ጋር ለኅልውናውና ሉዓላዊነቱ ሠላማዊ የፖለቲካ ትግሉን ይቀጥላል ሲል ሕወሓት አቋሙን ገልጧል።
@YeneTube @FikerAssefa
ሕወሓት፣ የትግራይ ሕዝብ ፍትሃዊ ጥያቄ በጦርነት ዛቻ ሊታፈን አይችልም ሲል ማምሻውን ባወጣው መግለጫ አቋሙን ገልጧል።
ከመሃል አገር ከሄደ የኃይማኖት ልዑካን ቡድን ጋር ሰሞኑን መወያየቱን የገለጠው ሕወሓት፣ የልዑካኑ አባላት በትግራይ ያለው "የሰላም ፍላጎት" እና "ዝግጁነት" ቀደም ሲል ከሠሙት የተለየ መኾኑን ተናግረዋል ብሏል።
ሕወሓት፣ በትግራይ በኩል ለግጭት የሚጋብዝ እንቅስቃሴ በሌለበት ኹኔታ ፌደራል መንግሥቱ የማስፈራራት ዘመቻ እያካሄደ፣ የታጠቁ ሃይሎችን እያደራጀና እያስታጠቀ ይገኛል በማለትም መክሰሱን ዋዜማ ዘግባለች፡፡
መንግሥት በግጭት ማቆም ስምምነቱ መሠረት ግዴታውን እስካልተወጣ ድረስ፣ የትግራይ ሕዝብ ከመሪ ድርጅቱ ጋር ለኅልውናውና ሉዓላዊነቱ ሠላማዊ የፖለቲካ ትግሉን ይቀጥላል ሲል ሕወሓት አቋሙን ገልጧል።
@YeneTube @FikerAssefa
❤58😁19👎8👍7
የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር 135.3 ሚሊዮን ደረሰ!
የተባበሩት መንግሥታት የስነ-ሕዝብ ፈንድ (ዩ ኤን ኤፍ ፒ ኤ) በ2025 የዓለም ሕዝብ ቁጥር ሪፖርት ባወጣው መረጃ መሠረት፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር ወደ 135.3 ሚሊዮን ደርሷል። ይህ አኃዝ የመጣው ኢትዮጵያ በ1985 ዓ.ም. ከጸደቀ ከሶስት አስርት ዓመታት በኋላ አዲስ ብሔራዊ የሕዝብ ቁጥር ፖሊሲ ለማውጣት በዝግጅት ላይ ባለችበት ወሳኝ ወቅት ነው።
የፖሊሲው ማሻሻያ እና የተመዘገቡ ስኬቶች
የፕላንና ልማት ሚኒስቴር የአዲሱ ፖሊሲ ማሻሻያ ሂደት መሪ ሲሆን፣ ፖሊሲው የኢትዮጵያን አሁን ያለውን የሥነ ሕዝብና ማኅበራዊ-ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች እንደሚያንፀባርቅ ገልጿል። ይህም የሀገሪቱን የልማት ቁርጠኝነት እና ዓለም አቀፍ የዘላቂ ልማት ግቦችን (SDGs) ለማጣጣም ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።
የሚኒስቴሩ የሕዝብና ልማት ጉዳዮች ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሀብታሙ ጌታቸው፣ የመጀመሪያው ፖሊሲ ከፀደቀበት ጊዜ ጀምሮ ከፍተኛ መሻሻሎች መኖራቸውን ጠቁመዋል።
“የሀገሪቱ የድህነት ምጣኔ ከ45.5% ወደ 19% ቀንሷል” ያሉት አቶ ሀብታሙ፣ የጨቅላ ሕፃናት ሞት መቀነስ፣ የወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም መጨመር እና የትምህርት እድገት መታየቱን አብራርተዋል።
ትንበያዎች እንደሚያመለክቱት፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር በ2035 ከ170 ሚሊዮን በላይ ሊሆን እንደሚችል እና በ2050 ወደ 225 ሚሊዮን ሊጠጋ ይችላል። ይህ እያደገ የመጣው ሕዝብ ዕድሎችንም ሆነ ተግዳሮቶችን የሚያመጣ ሲሆን፣ ዘላቂ የኢኮኖሚ እድገትን፣ ትምህርትን፣ ጤናን፣ ሥራ ስምሪትን እና የአካባቢ ጥበቃን የሚደግፉ ፖሊሲዎችን ይጠይቃል።
ዝርዝር ዘገባዉ :
here
@YeneTube @FikerAssefa
የተባበሩት መንግሥታት የስነ-ሕዝብ ፈንድ (ዩ ኤን ኤፍ ፒ ኤ) በ2025 የዓለም ሕዝብ ቁጥር ሪፖርት ባወጣው መረጃ መሠረት፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር ወደ 135.3 ሚሊዮን ደርሷል። ይህ አኃዝ የመጣው ኢትዮጵያ በ1985 ዓ.ም. ከጸደቀ ከሶስት አስርት ዓመታት በኋላ አዲስ ብሔራዊ የሕዝብ ቁጥር ፖሊሲ ለማውጣት በዝግጅት ላይ ባለችበት ወሳኝ ወቅት ነው።
የፖሊሲው ማሻሻያ እና የተመዘገቡ ስኬቶች
የፕላንና ልማት ሚኒስቴር የአዲሱ ፖሊሲ ማሻሻያ ሂደት መሪ ሲሆን፣ ፖሊሲው የኢትዮጵያን አሁን ያለውን የሥነ ሕዝብና ማኅበራዊ-ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች እንደሚያንፀባርቅ ገልጿል። ይህም የሀገሪቱን የልማት ቁርጠኝነት እና ዓለም አቀፍ የዘላቂ ልማት ግቦችን (SDGs) ለማጣጣም ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።
የሚኒስቴሩ የሕዝብና ልማት ጉዳዮች ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሀብታሙ ጌታቸው፣ የመጀመሪያው ፖሊሲ ከፀደቀበት ጊዜ ጀምሮ ከፍተኛ መሻሻሎች መኖራቸውን ጠቁመዋል።
“የሀገሪቱ የድህነት ምጣኔ ከ45.5% ወደ 19% ቀንሷል” ያሉት አቶ ሀብታሙ፣ የጨቅላ ሕፃናት ሞት መቀነስ፣ የወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም መጨመር እና የትምህርት እድገት መታየቱን አብራርተዋል።
ትንበያዎች እንደሚያመለክቱት፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር በ2035 ከ170 ሚሊዮን በላይ ሊሆን እንደሚችል እና በ2050 ወደ 225 ሚሊዮን ሊጠጋ ይችላል። ይህ እያደገ የመጣው ሕዝብ ዕድሎችንም ሆነ ተግዳሮቶችን የሚያመጣ ሲሆን፣ ዘላቂ የኢኮኖሚ እድገትን፣ ትምህርትን፣ ጤናን፣ ሥራ ስምሪትን እና የአካባቢ ጥበቃን የሚደግፉ ፖሊሲዎችን ይጠይቃል።
ዝርዝር ዘገባዉ :
here
@YeneTube @FikerAssefa
❤42👀10😁3🔥2😭1
Forwarded from YeneTube
በሩን ይክፈቱ ችግረወን
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
❤5👎1😁1
ትራምፕ ለሶስተኛ ጊዜ አሜሪካ ለታላቁ የ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የገንዘብ ድጋፍ አድርጋለች ሲሉ የተሳሳተ ንግግር አደረጉ!
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባሳለፍነው ሳምንት አርብ ዕለት የሪፐብሊካን ሴናተሮችን በዋይት ሀውስ ተቀብለው ባስተናገዱበት ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በአሜሪካ የገንዘብ ድጋፍ እንደተደረገለት ሲናገሩ ተደምጠዋል።
“ኢትዮጵያ ግድቡን የገነባችው በአብዛኛው በአሜሪካ ገንዘብ ነው” ሲሉ በአንድ ወር ውስጥ ለሶስተኛ ጊዜ ተናግረዋል።
እውነታው ግን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የተገነባው ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ ህዝብ በህዝባዊ መዋጮ እና በአገር ውስጥ ሀብት መሆኑ ነው። በተጨማሪም ግድቡ ለግብፅ የውሃ ደህንነት ምንም አይነት ስጋት አይፈጥርም።
@YeneTube @FikerAssefa
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባሳለፍነው ሳምንት አርብ ዕለት የሪፐብሊካን ሴናተሮችን በዋይት ሀውስ ተቀብለው ባስተናገዱበት ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በአሜሪካ የገንዘብ ድጋፍ እንደተደረገለት ሲናገሩ ተደምጠዋል።
“ኢትዮጵያ ግድቡን የገነባችው በአብዛኛው በአሜሪካ ገንዘብ ነው” ሲሉ በአንድ ወር ውስጥ ለሶስተኛ ጊዜ ተናግረዋል።
እውነታው ግን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የተገነባው ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ ህዝብ በህዝባዊ መዋጮ እና በአገር ውስጥ ሀብት መሆኑ ነው። በተጨማሪም ግድቡ ለግብፅ የውሃ ደህንነት ምንም አይነት ስጋት አይፈጥርም።
@YeneTube @FikerAssefa
😁34❤13👎9👀1
YeneTube
Photo
"ኢፈርት በክልሉ የተፈጠረው የፖለቲካ ልዩነት ሰለባ ሁኗል፣ለህዝቡ ጥቅም ሲባል ጊዜያዊ አስተዳደር ጣልቃ ለመግባት ይገደዳል" - ሌ/ጀ ታደሰ ወረደ
የትግራይ መልሶ ማቋቋም ኢንዶውመንት ፈንድ (ኢፈርት) እና ያቀፋቸው ድርጅቶች በትግራይ ክልል የተፈጠረው ልዩነት ሰለባዎች ሁነዋል ሲሉ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ ገለጹ።በዚህም ምክንያት የሶስተኛ ወገን ጣልቃ እንዲገባ የሚያደርግ እና እየሰፋ የሄደ ከፍተኛ አደጋ ተጋርጦባቸዋል ብለዋል።
ፕሬዝዳንቱ ይህንን የተናገሩት ለሁለት ቀናት ሐምሌ 12 እና 13 ቀን 2017 ዓ.ም በመቀለ ከተማ በተካሄደው ትግራይ መልሶ ማቋቋም ኢንዶውመንት ፈንድ (ኢፈርት) አስቸኳይ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ተቋሙ ስላጋጠመው አደጋ እና ከተሳታፊዎቹ ለቀረበላቸው ጥያቄ ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ነው።
በኢፈርት የተፈጠረውን ችግር ተከትሎ ጉዳዩ በህግ እንዲታይ መቅረቡን ጠቁመው ይህም በባሰ ደረጃ ጉዳዮቹን ሊያወሳሰበው ይችላል ብለዋል፤ ተቋሙ ላጋጠመው ችግር ሁሉም መወገኖች በከፍተኛ የህዝብ ሀላፊነት በምክክር እና በትዕግስት እንዲፈቱት አሳስበዋል።
ይህ የማይሆን ከሆነ ግን ለህዝብ ጥቅም ሲባል የጊዜያዊ አስተዳደሩ ባለበት ሃላፊነት እጁን በማስገባት ሊፈታው እንደሚገደድ አሳታውቀዋል፤ “ለህዝቡ ጥቅም ሲባል የጊዜያዊ አስተዳደሩ ጣልቃ ለመግባት ይገደዳል” ብለዋል።
በኢፈርት መተዳደሪያ ደንብ መሰረት አንድ ሶስተኛ የምክር ቤቱ አባላት ፒቲሽን በማሰባሰብ ጉባኤ መጥራት እንደሚችሉ መደንገጉን ተከትሎ የተጠራ ጉባኤ መሆኑን ከክልሉ መገናኛ ብዙሃን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
ህጋዊ የትዕምርት ባላደራ ቦርድ መሆኑን በመግለጽ ላይ የሚገኘው በአቶ ቴዎድሮስ ሀጎስ የሚመራው አካል በበኩሉ የትግራይ ፍትህ ቢሮ ያሳለፈውን ውሳኔ በመጥቀስ በሁለቱ ቀናት የተካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ ህግን የጣሰ እና በኢፈርት ስር የሚገኙ ድርጅቶችን በቀጣይ ቀውስ ውስጥ የሚከት አካሄድ ነው ማለታቸውን ዘገባዎቹ ጠቁመዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የትግራይ መልሶ ማቋቋም ኢንዶውመንት ፈንድ (ኢፈርት) እና ያቀፋቸው ድርጅቶች በትግራይ ክልል የተፈጠረው ልዩነት ሰለባዎች ሁነዋል ሲሉ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ ገለጹ።በዚህም ምክንያት የሶስተኛ ወገን ጣልቃ እንዲገባ የሚያደርግ እና እየሰፋ የሄደ ከፍተኛ አደጋ ተጋርጦባቸዋል ብለዋል።
ፕሬዝዳንቱ ይህንን የተናገሩት ለሁለት ቀናት ሐምሌ 12 እና 13 ቀን 2017 ዓ.ም በመቀለ ከተማ በተካሄደው ትግራይ መልሶ ማቋቋም ኢንዶውመንት ፈንድ (ኢፈርት) አስቸኳይ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ተቋሙ ስላጋጠመው አደጋ እና ከተሳታፊዎቹ ለቀረበላቸው ጥያቄ ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ነው።
በኢፈርት የተፈጠረውን ችግር ተከትሎ ጉዳዩ በህግ እንዲታይ መቅረቡን ጠቁመው ይህም በባሰ ደረጃ ጉዳዮቹን ሊያወሳሰበው ይችላል ብለዋል፤ ተቋሙ ላጋጠመው ችግር ሁሉም መወገኖች በከፍተኛ የህዝብ ሀላፊነት በምክክር እና በትዕግስት እንዲፈቱት አሳስበዋል።
ይህ የማይሆን ከሆነ ግን ለህዝብ ጥቅም ሲባል የጊዜያዊ አስተዳደሩ ባለበት ሃላፊነት እጁን በማስገባት ሊፈታው እንደሚገደድ አሳታውቀዋል፤ “ለህዝቡ ጥቅም ሲባል የጊዜያዊ አስተዳደሩ ጣልቃ ለመግባት ይገደዳል” ብለዋል።
በኢፈርት መተዳደሪያ ደንብ መሰረት አንድ ሶስተኛ የምክር ቤቱ አባላት ፒቲሽን በማሰባሰብ ጉባኤ መጥራት እንደሚችሉ መደንገጉን ተከትሎ የተጠራ ጉባኤ መሆኑን ከክልሉ መገናኛ ብዙሃን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
ህጋዊ የትዕምርት ባላደራ ቦርድ መሆኑን በመግለጽ ላይ የሚገኘው በአቶ ቴዎድሮስ ሀጎስ የሚመራው አካል በበኩሉ የትግራይ ፍትህ ቢሮ ያሳለፈውን ውሳኔ በመጥቀስ በሁለቱ ቀናት የተካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ ህግን የጣሰ እና በኢፈርት ስር የሚገኙ ድርጅቶችን በቀጣይ ቀውስ ውስጥ የሚከት አካሄድ ነው ማለታቸውን ዘገባዎቹ ጠቁመዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
❤32