የጤና ባለሙያዎች ሙሉ ለሙሉ የስራ ማቆም አድማ መጀመራቸውን ተከትሎ በአዲስ አበባና በተለያዩ ከተሞች በሚገኙ ሆስፒታሎች የህክምና አገልግሎት መቋረጡ ተገለጸ!
በመላ ሀገሪቱ የተጀመረው የጤና ባለሙያዎች የስራ ማቆም አድማ ስድስተኛ ቀኑን በያዘበት በዛሬው ዕለት ግንቦት 11 ቀን 2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ የጤና ባለሙያዎች ንቅናቄ ሙሉ በሙሉ የስራ ማቆም ጥሪ ማስተላለፉን ተከትሎ በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች በሚገኙ አንዳንድ ሆስፒታሎች የህክምና አገልግሎቶች መስጠት ማቆማቸው ተገለጸ።
#በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ፍቼ ከተማ በሚገኘው የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሚሰሩ አንድ የጤና ባለሙያ ለአዲስ ስታንዳርድ እንደተናገሩት በሆስፒታሉ የሚገኙ አጠቃላይ ሐኪሞች "ሙሉ በሙሉ የስራ ማቆም አድማውን እየተሳተፉ ነው ሌሎች የሰራተኛ አባላት ግን አሁንም እየሰሩ ናቸው" ብለዋል።
አዲስ ስታንዳርድ በዛሬው ዕለት ማለዳ ላይ በሶስት ዋና ዋና ሆስፒታሎች ማለትም በዳግማዊ #ምኒልክ ሪፈራል ሆስፒታል፣ #በዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል እና #የካቲት 12 ሜዲካል ኮሌጅ ሆስፒታል ባደረገው ጉብኝት የአገልግሎት መስተጓጎል በስፋት ያስተዋለ ሲሆን የተወሰኑ የድንገተኛ ህክምና ክፍሎች ብቻ ስራቸውን ሲቀጥሉ ለመታዘብ ተችሏል።
በተያያዘ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኀበራዊ ፍትሕ (#ኢዜማ) ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ መንግስት “የጤና ባለሙያዎቹን ጥያቄያቸውን ለመፍታት ፍላጎት እንዳለው ለማሳየት ሙከራ እንኳ አላደረገም” ሲል ተችቷል “ማስፈራሪያ አዘል አቅላይ መንገድን መከተሉ ሃላፊነትን በአግባቡ ካለመወጣት የሚመነጭ የመንግስት ስህተት ነው” ብሏል።
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጠቀሙ :-
https://addisstandard.com/Amharic/?p=7822
በመላ ሀገሪቱ የተጀመረው የጤና ባለሙያዎች የስራ ማቆም አድማ ስድስተኛ ቀኑን በያዘበት በዛሬው ዕለት ግንቦት 11 ቀን 2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ የጤና ባለሙያዎች ንቅናቄ ሙሉ በሙሉ የስራ ማቆም ጥሪ ማስተላለፉን ተከትሎ በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች በሚገኙ አንዳንድ ሆስፒታሎች የህክምና አገልግሎቶች መስጠት ማቆማቸው ተገለጸ።
#በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ፍቼ ከተማ በሚገኘው የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሚሰሩ አንድ የጤና ባለሙያ ለአዲስ ስታንዳርድ እንደተናገሩት በሆስፒታሉ የሚገኙ አጠቃላይ ሐኪሞች "ሙሉ በሙሉ የስራ ማቆም አድማውን እየተሳተፉ ነው ሌሎች የሰራተኛ አባላት ግን አሁንም እየሰሩ ናቸው" ብለዋል።
አዲስ ስታንዳርድ በዛሬው ዕለት ማለዳ ላይ በሶስት ዋና ዋና ሆስፒታሎች ማለትም በዳግማዊ #ምኒልክ ሪፈራል ሆስፒታል፣ #በዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል እና #የካቲት 12 ሜዲካል ኮሌጅ ሆስፒታል ባደረገው ጉብኝት የአገልግሎት መስተጓጎል በስፋት ያስተዋለ ሲሆን የተወሰኑ የድንገተኛ ህክምና ክፍሎች ብቻ ስራቸውን ሲቀጥሉ ለመታዘብ ተችሏል።
በተያያዘ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኀበራዊ ፍትሕ (#ኢዜማ) ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ መንግስት “የጤና ባለሙያዎቹን ጥያቄያቸውን ለመፍታት ፍላጎት እንዳለው ለማሳየት ሙከራ እንኳ አላደረገም” ሲል ተችቷል “ማስፈራሪያ አዘል አቅላይ መንገድን መከተሉ ሃላፊነትን በአግባቡ ካለመወጣት የሚመነጭ የመንግስት ስህተት ነው” ብሏል።
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጠቀሙ :-
https://addisstandard.com/Amharic/?p=7822
Addis standard
የጤና ባለሙያዎች ሙሉ ለሙሉ የስራ ማቆም አድማ መጀመራቸውን ተከትሎ በአዲስ አበባና በተለያዩ ከተሞች በሚገኙ ሆስፒታሎች የህክምና አገልግሎት መቋረጡ ተገለጸ - Addis standard
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11/ 2017 ዓ/ም፦ በመላ ሀገሪቱ የተጀመረው የጤና ባለሙያዎች የስራ ማቆም አድማ ስድስተኛ ቀኑን በያዘበት በዛሬው ዕለት ግንቦት 11 ቀን 2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ የጤና ባለሙያዎች ንቅናቄ ሙሉ በሙሉ የስራ ማቆም ጥሪ ማስተላለፉን ተከትሎ በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች በሚገኙ አንዳንድ ሆስፒታሎች የህክምና አገልግሎቶች መስጠት ማቆማቸው ተገለጸ። በአርሲ ዞን አሰላ ከተማ የሚገኘው…
👍108😭21❤8😁5