YeneTube
119K subscribers
31.3K photos
483 videos
79 files
3.85K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
የተባበሩት_አረብ_ኤምሬትስ #ቢትኮይን ኩባንያ በ #ኢትዮጵያ የማይኒንግ አቅሙን በ52 ሜጋ ዋት ኣሳደገ

የተባበሩተ አረብ ኤምሬትስ የቢትኮይን ማይኒንግ ኩባንያ የሆነው ፎኒክስ ግሩፕ፤ በኢትዮጵያ ባለው የማይኒንግ አቅም ላይ 52 ሜጋ ዋት ጭማሪ ማድረጉን አስታውቋል።

ኩባንያው ትናንት ሚያዚያ 21 ቀን 2017 እንዳስታወቀው፤ አዲስ ተግባራዊ ካደረገው ጭማሪ ጋር በኢትዮጵያ የፎኒክስ የቢትኮይን ማይኒንግ አቅም 132 ሜጋ ዋት ደርሷል። የኩባንያው አጠቃላይ አቅም አሁን ከ500 ሜጋ ዋት በላይ መሻገሩ ተገልጿል።

የፎኒክስ ተባባሪ መስራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሙናፍ አሊ፤ የኩባንያው ስትራቴጂ "የተትረፈረፈ እና ዝቅተኛ ኃይል ወጭ ያላቸውን ዋና ዋና አካባቢዎች ማገኘት ላይ የተመሠረተ ነው" ብለዋል።

"በኢትዮጵያ ያደረግነውን የቅርብ ጊዜ መስፋፋታችን የመሳሰሉ ተነሳሽነቶች ወሳኝ እርምጃዎች ናቸው፣ ዛሬ ከፍተኛ ዋጋ በመፍጠር ብቻ ሳይሆን አቋማችንን በማጠናከር ላይም ይገኛሉ" ሲሉም መናገራቸውን ኮይንቴሌግራፍ ዘግቧል።

ይህ ማስፋፊያ ዜና የተሰማው የ #አቡ_ዳቢው ክሪፕቶማይኒንግ ኩባንያ ፎኒክስ ግሩፕ የ80 ሜጋ ዋት ኃይል ግዥ ስምምነት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር መፈራረሙን ተከትሎ ነው። በወቅቱ ኩባንያው በ2025 ሁለተኛው ሩብ አመት ስራ እንደሚጀምር ገልጿል።

ፎኒክስ ኩባንያ በአቡዳቢ ኢንተርናሽናል ሆልዲንግ ኩባንያ (IHC) የሚደገፍ ሲሆን፣ በመላው #ኤምሬትስ#አሜሪካ እና #ካናዳ ውስጥ የክሪፕቶ ማይኒንግ ስራዎችን ያከናውናል።

@Yenetube @Fikerassefa
👍373👎2😁1