12 የኢትዮጵያና ኤርትራ ከፍተኛ ባለሥልጣናትና ወታደራዊ አዛዦች በሰሜኑ ጦርነት ወቅት በትግራይ "የጦር ወንጀል" ፈጽመዋል በሚል በጀርመን ክስ እንዲመሰረትባቸው ተጠየቀ
👉🏼ክሱን እንዲመሰረት የጠየቁት የቀድሞ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ሃላፊ እና የትግራይ ተወላጆች የሆኑ ግለሰቦች ናቸዉ
አንድ የቀድሞ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ሃላፊንና አንድ የቀድሞ የረድኤት ሠራተኛን ጨምሮ ስምንት የትግራይ ተወላጆች ፤ 12 የኢትዮጵያና ኤርትራ ከፍተኛ ባለሥልጣናትና ወታደራዊ አዛዦች በሰሜኑ ጦርነት ወቅት በትግራይ "የጦር ወንጀል" እና "በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች" ፈጽመዋል በማለት ለጀርመን ዓቃቤ ሕግ አቤቱታ አቅርበዋል።
የወንጀሎቹ ሰለባና ወንጀሎቹ ሲፈጸም እማኝ የነበሩት አቤቱታ አቅራቢዎቹ፣ የጀርመን ፌደራል ዓቃቤ ሕግ በወንጀሎቹ ላይ የምርመራ መዝገብ እንዲከፍትና በአገሪቱ ፍርድ ቤት ክስ እንዲመሠርት ጠይቀዋል።
ግለሰቦቹ አቤቱታውን ያቀረቡት፣ ሌጋል አክሽን ወርልድዋይድ በተሰኘ የሕግ ተቋምና ሌሎች ድርጅቶችና የሕግ ባለሙያዎች ድጋፍ ነው።
የጀርመን ዓቃቤ ሕግ በውጭ አገራት በተፈጸሙ ዓለማቀፍ አስከፊ ወንጀሎች ዙሪያ ምርመራ የማድረግ ሥልጣን አለው።
ዋዜማ
@Yenetube @Fikerassefa
👉🏼ክሱን እንዲመሰረት የጠየቁት የቀድሞ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ሃላፊ እና የትግራይ ተወላጆች የሆኑ ግለሰቦች ናቸዉ
አንድ የቀድሞ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ሃላፊንና አንድ የቀድሞ የረድኤት ሠራተኛን ጨምሮ ስምንት የትግራይ ተወላጆች ፤ 12 የኢትዮጵያና ኤርትራ ከፍተኛ ባለሥልጣናትና ወታደራዊ አዛዦች በሰሜኑ ጦርነት ወቅት በትግራይ "የጦር ወንጀል" እና "በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች" ፈጽመዋል በማለት ለጀርመን ዓቃቤ ሕግ አቤቱታ አቅርበዋል።
የወንጀሎቹ ሰለባና ወንጀሎቹ ሲፈጸም እማኝ የነበሩት አቤቱታ አቅራቢዎቹ፣ የጀርመን ፌደራል ዓቃቤ ሕግ በወንጀሎቹ ላይ የምርመራ መዝገብ እንዲከፍትና በአገሪቱ ፍርድ ቤት ክስ እንዲመሠርት ጠይቀዋል።
ግለሰቦቹ አቤቱታውን ያቀረቡት፣ ሌጋል አክሽን ወርልድዋይድ በተሰኘ የሕግ ተቋምና ሌሎች ድርጅቶችና የሕግ ባለሙያዎች ድጋፍ ነው።
የጀርመን ዓቃቤ ሕግ በውጭ አገራት በተፈጸሙ ዓለማቀፍ አስከፊ ወንጀሎች ዙሪያ ምርመራ የማድረግ ሥልጣን አለው።
ዋዜማ
@Yenetube @Fikerassefa
👍40❤3😁2
በአፍሪካ እየጨመረ የመጣው የስፑትኒክ ተፅዕኖ እንዳሳሰበው የአውሮፓ የውጭ አገልግሎት ገለጸ
የአውሮፓ ሕብረት የዲፕሎማሲ አገልግሎት ሪፖርት የስፑትኒክ አፍሪካ የፈረንሳይኛ ይዘት ዓለም አቀፍ ተደራሽነት እና ተፅዕኖ አየጨመረ መጥቷል ብሏል።
ሪፖርቱ "የአውሮፓ ሕብረት እ.አ.አ 2022 አርቲ እና ስፑትኒክ ላይ እገዳ ከጣለ በኋላ የሩሲያ መገናኛ ብዙኃን አፍሪካ ውስጥ በከፍተኛ ሁኔታ እየተንቀሳቀሱ እንደሆነ" ጠቁሟል።
🗣"ይህ ዝንባሌ ሩሲያ በግልጽ የሚዲያ ተፅዕኖ አቅጣጫ የመቀየር እና በአንድ ክልል ውስጥ ያሉ ገደቦችን ለማካካስ ሌላ ቦታ ተጽዕኖዋን ማጠናከር እንደምትችል ያሳያል" ሲል ሪፖርቱ ገልጿል።
የሩሲያ መንግሥት በአውሮፓ ሕብረት ውስጥ በሩሲያ ሚዲያ ላይ የተጣለው እገዳ ፖለቲካዊ ሳንሱር እንደሆነና የአውሮፓ ባለስልጣናት "የተቃውሞ ድምጽ የማፈን ፖሊሲያቸውን" እያጠናከሩ መምጣታቸውን ደጋግሞ ይገልጻል።
@Yenetube @Fikerassefa
የአውሮፓ ሕብረት የዲፕሎማሲ አገልግሎት ሪፖርት የስፑትኒክ አፍሪካ የፈረንሳይኛ ይዘት ዓለም አቀፍ ተደራሽነት እና ተፅዕኖ አየጨመረ መጥቷል ብሏል።
ሪፖርቱ "የአውሮፓ ሕብረት እ.አ.አ 2022 አርቲ እና ስፑትኒክ ላይ እገዳ ከጣለ በኋላ የሩሲያ መገናኛ ብዙኃን አፍሪካ ውስጥ በከፍተኛ ሁኔታ እየተንቀሳቀሱ እንደሆነ" ጠቁሟል።
🗣"ይህ ዝንባሌ ሩሲያ በግልጽ የሚዲያ ተፅዕኖ አቅጣጫ የመቀየር እና በአንድ ክልል ውስጥ ያሉ ገደቦችን ለማካካስ ሌላ ቦታ ተጽዕኖዋን ማጠናከር እንደምትችል ያሳያል" ሲል ሪፖርቱ ገልጿል።
የሩሲያ መንግሥት በአውሮፓ ሕብረት ውስጥ በሩሲያ ሚዲያ ላይ የተጣለው እገዳ ፖለቲካዊ ሳንሱር እንደሆነና የአውሮፓ ባለስልጣናት "የተቃውሞ ድምጽ የማፈን ፖሊሲያቸውን" እያጠናከሩ መምጣታቸውን ደጋግሞ ይገልጻል።
@Yenetube @Fikerassefa
👍16❤3🔥2👀1
የሱዳን ጦር ከሁለት ዓመት ጦርነት በኋላ የፕሬዝዳንቱን ቤተ መንግስት መልሶ ያዘ
የሱዳን ጦር በካርቱም የሚገኘውን ፕሬዚዳንታዊ ቤተ መንግስት ከተቀናቃኙ ፓራሚሊተሪ የፈጣን ደጋፊ ሃይሎች በመንጠቅ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ወታደራዊ መሪዎች ገልፀዋል። በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የተለጠፉት ቪዲዮ እና ፎቶግራፎች የተደሰቱ ወታደሮች የጦር መሳሪያቸውን ከፍ በማድረግ ሲጮሁ እና ተንበርክከው ሲፀልዩ ያሳያሉ። ሰራዊቱ አርኤስኤፍ ተብሎ የሚጠራውን የትጥቅ ተቀናቃኞቹ ከተባረረ ከሁለት አመት በኋላ ዋና ከተማይቱን መልሶ ለመቆጣጠር የተዘጋጀ ይመስላል።
የመከላከያ ቡድኑ እስካሁን አስተያየት አልሰጠም።የጦሩ ቃል አቀባይ ነቢል አብደላህ በመንግስት ቲቪ እንደተናገሩት ወታደሮቹ በማዕከላዊ ካርቱም የሚገኘውን ቤተ መንግስት እና ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችን ተቆጣጥረዋል ብለዋል። አብደላህ አክለውም ሰራዊታችን የጠላት ተዋጊዎችን እና መሳሪያዎችን ሙሉ በሙሉ አውድመዋል ሲሉ ተደምጠዋል። ድሉ እስኪጠናቀቅ ድረስ ትግላችንን እንደምንቀጥል እናረጋግጣለን ብለዋል። ካርቱም የሀገሪቱ የእርስ በርስ ጦርነት ከሁለት አመት በፊት የጀመረባት እና አንዳንድ ታላላቅ ጦርነቶች የተካሄዱባት ከተማ ናት።
ጦርነቱ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቴ አርኤስኤፍ አብዛኛውን ዋና ከተማዋን እና የሱዳንን ምዕራባዊ ክፍል ይዞ ቆይቷል።ካርቱምን ማስመለስ ለሱዳን ጦር ኃይሎች ትልቅ ድል እና በግጭቱ ውስጥ ወሳኝ ምዕራፍ ነው። ሰራዊቱ ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ በማዕከላዊ ሱዳን አንዳንድ ክፍሎችም ድል አስመዝግቧል። ሐሙስ እለት፣ በሪፐብሊካን ቤተ መንግስት አቅራቢያ በሰው አልባ አውሮፕላኖች ጥቃት እና የአየር ድብደባ ከባድ ፍንዳታ እንደነበረም እማኞች ተናግረዋል።ቅዳሜ እለት በቀረፀ የቪዲዮ መልዕክት፣ የአር ኤስ ኤፍ ኮማንደር መሀመድ ሃምዳን ዳጋሎ፣ ሄሜቲ በመባል የሚታወቁት፣ በፕሬዝዳንቱ ቤተ መንግስት እና በአካባቢው በቁጥጥራችን ስር ያሉትን አካባቢዎች ለመከላከል ቃል ገብተው ነበር።
@Yenetube @FikerAssefa
የሱዳን ጦር በካርቱም የሚገኘውን ፕሬዚዳንታዊ ቤተ መንግስት ከተቀናቃኙ ፓራሚሊተሪ የፈጣን ደጋፊ ሃይሎች በመንጠቅ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ወታደራዊ መሪዎች ገልፀዋል። በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የተለጠፉት ቪዲዮ እና ፎቶግራፎች የተደሰቱ ወታደሮች የጦር መሳሪያቸውን ከፍ በማድረግ ሲጮሁ እና ተንበርክከው ሲፀልዩ ያሳያሉ። ሰራዊቱ አርኤስኤፍ ተብሎ የሚጠራውን የትጥቅ ተቀናቃኞቹ ከተባረረ ከሁለት አመት በኋላ ዋና ከተማይቱን መልሶ ለመቆጣጠር የተዘጋጀ ይመስላል።
የመከላከያ ቡድኑ እስካሁን አስተያየት አልሰጠም።የጦሩ ቃል አቀባይ ነቢል አብደላህ በመንግስት ቲቪ እንደተናገሩት ወታደሮቹ በማዕከላዊ ካርቱም የሚገኘውን ቤተ መንግስት እና ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችን ተቆጣጥረዋል ብለዋል። አብደላህ አክለውም ሰራዊታችን የጠላት ተዋጊዎችን እና መሳሪያዎችን ሙሉ በሙሉ አውድመዋል ሲሉ ተደምጠዋል። ድሉ እስኪጠናቀቅ ድረስ ትግላችንን እንደምንቀጥል እናረጋግጣለን ብለዋል። ካርቱም የሀገሪቱ የእርስ በርስ ጦርነት ከሁለት አመት በፊት የጀመረባት እና አንዳንድ ታላላቅ ጦርነቶች የተካሄዱባት ከተማ ናት።
ጦርነቱ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቴ አርኤስኤፍ አብዛኛውን ዋና ከተማዋን እና የሱዳንን ምዕራባዊ ክፍል ይዞ ቆይቷል።ካርቱምን ማስመለስ ለሱዳን ጦር ኃይሎች ትልቅ ድል እና በግጭቱ ውስጥ ወሳኝ ምዕራፍ ነው። ሰራዊቱ ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ በማዕከላዊ ሱዳን አንዳንድ ክፍሎችም ድል አስመዝግቧል። ሐሙስ እለት፣ በሪፐብሊካን ቤተ መንግስት አቅራቢያ በሰው አልባ አውሮፕላኖች ጥቃት እና የአየር ድብደባ ከባድ ፍንዳታ እንደነበረም እማኞች ተናግረዋል።ቅዳሜ እለት በቀረፀ የቪዲዮ መልዕክት፣ የአር ኤስ ኤፍ ኮማንደር መሀመድ ሃምዳን ዳጋሎ፣ ሄሜቲ በመባል የሚታወቁት፣ በፕሬዝዳንቱ ቤተ መንግስት እና በአካባቢው በቁጥጥራችን ስር ያሉትን አካባቢዎች ለመከላከል ቃል ገብተው ነበር።
@Yenetube @FikerAssefa
👍16👎1
OPEN BOOSTGRAM -
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👍1
ኢትዮጵያ የመጀመሪያዎቹን የኢንቨስትመንት ባንኮች እና የሰነድ ሙዓለንዋይ ገበያ አከናዋኝ አገኘች!
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ለአምስት አዳዲስ ድርጅቶች የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪ ፈቃድ መስጠቱን አስታውቋል።ይህ ውሳኔ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢንቨስትመንት ባንኮችና የሰነድ ሙዓለንዋይ ገበያ አከናዋኝ ፈቃድ የተሰጠበት እንዲሁም አጠቃላይ ፈቃድ የተሰጣቸው የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች ቁጥር ከአራት ወደ ዘጠኝ ከፍ ያደረገበት ነው።
ፈቃድ የተሰጣቸው ድርጅቶች ሲቢኢ ካፒታል አ.ማ - ኢንቨስትመንት ባንክ ፣ ወጋገን ካፒታል ኢንቨስትመንት ባንክ አ.ማ - ኢንቨስትመንት ባንክ ፣ ኢትዮ-ፊደሊቲ ሴኩሪቲስ አ.ማ - የሰነድ ሙዓለንዋይ ገበያ አከናዋኝ (Securities Dealer) ፣ ኤች ኤስ ቲ ኢንቨስትመንት አድቫይዘሪ ሰርቪስስ ኃ.የተ.የግ. ማ - የሰነድ ሙዓለንዋይ ኢንቨስትመንት አማካሪ ፣ ኢኩዥን የሰነድ ሙዓለንዋይ ኢንቨስትመንት አማካሪ ኃ.የተ.የግ. ማ - የሰነድ ሙዓለንዋይ ኢንቨስትመንት አማካሪ መሆናቸው ተጠቁሟል።
ይህ ታሪካዊ ክስተት የኢትዮጵያን የፋይናንስ ገበያ ለማሳደግና ለኢንቨስትመንት እድሎች መስፋፋት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተገልጿል።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ለአምስት አዳዲስ ድርጅቶች የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪ ፈቃድ መስጠቱን አስታውቋል።ይህ ውሳኔ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢንቨስትመንት ባንኮችና የሰነድ ሙዓለንዋይ ገበያ አከናዋኝ ፈቃድ የተሰጠበት እንዲሁም አጠቃላይ ፈቃድ የተሰጣቸው የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች ቁጥር ከአራት ወደ ዘጠኝ ከፍ ያደረገበት ነው።
ፈቃድ የተሰጣቸው ድርጅቶች ሲቢኢ ካፒታል አ.ማ - ኢንቨስትመንት ባንክ ፣ ወጋገን ካፒታል ኢንቨስትመንት ባንክ አ.ማ - ኢንቨስትመንት ባንክ ፣ ኢትዮ-ፊደሊቲ ሴኩሪቲስ አ.ማ - የሰነድ ሙዓለንዋይ ገበያ አከናዋኝ (Securities Dealer) ፣ ኤች ኤስ ቲ ኢንቨስትመንት አድቫይዘሪ ሰርቪስስ ኃ.የተ.የግ. ማ - የሰነድ ሙዓለንዋይ ኢንቨስትመንት አማካሪ ፣ ኢኩዥን የሰነድ ሙዓለንዋይ ኢንቨስትመንት አማካሪ ኃ.የተ.የግ. ማ - የሰነድ ሙዓለንዋይ ኢንቨስትመንት አማካሪ መሆናቸው ተጠቁሟል።
ይህ ታሪካዊ ክስተት የኢትዮጵያን የፋይናንስ ገበያ ለማሳደግና ለኢንቨስትመንት እድሎች መስፋፋት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተገልጿል።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
👍29🔥3😁1
ለኢትዮ ፌሪስ ጣና የሀገር ውስጥ የውኃ ትራንስፖርት የተገዙት ሁለት ዘመናዊ ጀልባዎች እየገቡ ነው
በኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ለኢትዮ ፌሪስ ጣና የሀገር ውስጥ የውሃ ትራንስፖርት እንዲያገለግሉ የተገዙት ሁለት ዘመናዊ ጀልባዎች ከጅቡቲ ወደብ ተጭነው ወደ ሀገር ቤት በማምራት ላይ ናቸው።
ጣና ነሽ ፪ የተሰኘችው ዘመናዊ የህዝብ ትራንስፖርት ጀልባ 38ሜ እርዝመት እንዳላት እና በአንድ ግዜ 188 ሰዎችን የመጫን አቅም እንዳላት መዘገቡ ይታወሳል።
ሌላኛዋ መለስተኛ ፈጣን ቃኝ ጀልባ ዘመናዊ የሰው ማጓጓዣና የመዝናኛ ጀልባ እንደሆነች የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መረጃ ያመለክታል።
@Yenetube @Fikerassefa
በኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ለኢትዮ ፌሪስ ጣና የሀገር ውስጥ የውሃ ትራንስፖርት እንዲያገለግሉ የተገዙት ሁለት ዘመናዊ ጀልባዎች ከጅቡቲ ወደብ ተጭነው ወደ ሀገር ቤት በማምራት ላይ ናቸው።
ጣና ነሽ ፪ የተሰኘችው ዘመናዊ የህዝብ ትራንስፖርት ጀልባ 38ሜ እርዝመት እንዳላት እና በአንድ ግዜ 188 ሰዎችን የመጫን አቅም እንዳላት መዘገቡ ይታወሳል።
ሌላኛዋ መለስተኛ ፈጣን ቃኝ ጀልባ ዘመናዊ የሰው ማጓጓዣና የመዝናኛ ጀልባ እንደሆነች የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መረጃ ያመለክታል።
@Yenetube @Fikerassefa
👍31❤3😁3
በመዲናዋ የደንብ ልብስ መለያን አስመስለው በመልበስ ሕዝቡን ሲያሳስቱ ነበር የተባሉ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣንን መለያ አስመስለው በመልበስ ሕዝቡን ሲያሳስቱ ነበር የተባሉ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የከተማዋ ፖሊስ አስታወቀ፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ ሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ም/ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት÷ተጠርጣሪዎቹ የደንብ ልብሱን አስመስለው በመልበስ የባለስልጣኑ ሰራተኞች አላስፈላጊ ተግባራትን እንደፈጸሙ በማስመሰል የሱቅ ማስታወቂያ ሰርተዋል፡፡
ግለሰቦቹ በዚህ ሕገ ወጥ ተግባራቸውም በርካታ ሰዎችን ማሳሳታቸውን ነው የገለጹት፡፡
ተጠርጣሪዎቹ አሁን ላይ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው እየተጣራ እንደሚገኝም አመልክተዋል፡፡
@Yenetube @Fikerassefa
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣንን መለያ አስመስለው በመልበስ ሕዝቡን ሲያሳስቱ ነበር የተባሉ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የከተማዋ ፖሊስ አስታወቀ፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ ሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ም/ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት÷ተጠርጣሪዎቹ የደንብ ልብሱን አስመስለው በመልበስ የባለስልጣኑ ሰራተኞች አላስፈላጊ ተግባራትን እንደፈጸሙ በማስመሰል የሱቅ ማስታወቂያ ሰርተዋል፡፡
ግለሰቦቹ በዚህ ሕገ ወጥ ተግባራቸውም በርካታ ሰዎችን ማሳሳታቸውን ነው የገለጹት፡፡
ተጠርጣሪዎቹ አሁን ላይ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው እየተጣራ እንደሚገኝም አመልክተዋል፡፡
@Yenetube @Fikerassefa
👍24😁12❤3
#በሱዳን የፕሬዝዳንቱ ቤተ-መንግሥት ላይ በሰነዘረ የድሮን ጥቃት 3 ጋዜጠኖች ተገደሉ
መጋቢት 12/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል (አር ኤስ ኤፍ) በሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም በሚገኘው የሪፐብሊካን ቤተ-መንግሥት ላይ ባደረሰው የድሮን ጥቃት ሦስት ጋዜጠኖች መገደላቸው ተገልጿል፡፡
በጀነራል አብዱልፈታህ አል-ቡርሃን የሚመራው የሱዳን ጦር ሠራዊት (ኤስ ኤ ኤፍ) ፕሬዝዳንታዊ ቤተ-መንግሥቱን ጀነራል ሃምዳን ዳጋሎ ከሚመሩት በፈጥኖ ደራሽ ኃይል (አር ኤስ ኤፍ) እጅ በማስለቀቅ በዛሬው ዕለት በቁጥጥሩ ሥራ ማስገባቱን አሐዱ መዘገቡ ይታወሳል፡፡
ይህንንም ተከትሎ፤ ከሰዓታት በኋላ የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ በከፈተውና በቤተ-መንግሥቱ ውስጥ በሚገኝ ወታደራዊ እና የሚዲያ ስብስብ አዳራሽ ላይ ባነጣጠረ የሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) ጥቃት 3 ጋዜጠኞች መገደላቸው ተገልጿል፡፡
ጋዜጠኞች በቤተ-መንግሥቱ ተገኝተው ለሱዳን መንግሥት ቴሌቪዥን ጣቢያ ሲዘግቡ በነበሩበት ወቅት በጥቃቱ ሰለባ እንደሆኑም የሱዳን ጦር ምንጮች ለኤፍ ፒ ገልጸዋል፡፡
ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ቤተ-መንግሥቱን ጨምሮ የሱዳን በርካታ አካባቢዎችን ለበርካታ ጊዜያት ተቆጣጥሮ የቆየ ሲሆን፤ የሱዳን ጦር ከሁለት ዓመት ጦርነት በኋላ ፕሬዝዳንታዊ ቤተ-መንግሥቱን መልሶ በመቆጣጠሩ ወሳኝ የተባለን ድል መቀዳጀቱ ተነግሯል።
ነገር ግን አሁን ላይ ፈጥኖ ደራሹ ኃይሉ በቤተ-መንግሥቱ ጥቃት ከማድረሱ በተጨማሪ፤ አሁንም የካርቱም ደቡባዊ ክፍልን እና የካርቱም ተጎራባች በሆነችውን ኦምዱርማን ከተማ መካከል ያሉ ቦታዎችን ተቆጣጥሮ ይገኛል።
@Yenetube @Fikerassefa
መጋቢት 12/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል (አር ኤስ ኤፍ) በሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም በሚገኘው የሪፐብሊካን ቤተ-መንግሥት ላይ ባደረሰው የድሮን ጥቃት ሦስት ጋዜጠኖች መገደላቸው ተገልጿል፡፡
በጀነራል አብዱልፈታህ አል-ቡርሃን የሚመራው የሱዳን ጦር ሠራዊት (ኤስ ኤ ኤፍ) ፕሬዝዳንታዊ ቤተ-መንግሥቱን ጀነራል ሃምዳን ዳጋሎ ከሚመሩት በፈጥኖ ደራሽ ኃይል (አር ኤስ ኤፍ) እጅ በማስለቀቅ በዛሬው ዕለት በቁጥጥሩ ሥራ ማስገባቱን አሐዱ መዘገቡ ይታወሳል፡፡
ይህንንም ተከትሎ፤ ከሰዓታት በኋላ የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ በከፈተውና በቤተ-መንግሥቱ ውስጥ በሚገኝ ወታደራዊ እና የሚዲያ ስብስብ አዳራሽ ላይ ባነጣጠረ የሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) ጥቃት 3 ጋዜጠኞች መገደላቸው ተገልጿል፡፡
ጋዜጠኞች በቤተ-መንግሥቱ ተገኝተው ለሱዳን መንግሥት ቴሌቪዥን ጣቢያ ሲዘግቡ በነበሩበት ወቅት በጥቃቱ ሰለባ እንደሆኑም የሱዳን ጦር ምንጮች ለኤፍ ፒ ገልጸዋል፡፡
ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ቤተ-መንግሥቱን ጨምሮ የሱዳን በርካታ አካባቢዎችን ለበርካታ ጊዜያት ተቆጣጥሮ የቆየ ሲሆን፤ የሱዳን ጦር ከሁለት ዓመት ጦርነት በኋላ ፕሬዝዳንታዊ ቤተ-መንግሥቱን መልሶ በመቆጣጠሩ ወሳኝ የተባለን ድል መቀዳጀቱ ተነግሯል።
ነገር ግን አሁን ላይ ፈጥኖ ደራሹ ኃይሉ በቤተ-መንግሥቱ ጥቃት ከማድረሱ በተጨማሪ፤ አሁንም የካርቱም ደቡባዊ ክፍልን እና የካርቱም ተጎራባች በሆነችውን ኦምዱርማን ከተማ መካከል ያሉ ቦታዎችን ተቆጣጥሮ ይገኛል።
@Yenetube @Fikerassefa
👍32❤4👀2😭1
ፖሊስ ቲክቶከሮቹ በቁቁጥር ስለዋሉበት ጉዳይ ተጨማሪ መረጃ ይፋ አደረገ
ሸጋው ጫኔ አንለይ፣ መሀመድ ሀምዛ ያሲን፣ አቤኔዘር ተስፋዬ በየነ እና ጌትነት ደምለው ዳምጤ የተባሉ ግለሰቦች በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ልዩ ቦታው ደብረወርቅ ህንፃ አካባቢ የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የቀድሞ የደምብ ልብስ የሚመስል በማሰፋት በጎዳና ንግድ ላይ የሚተዳደሩትን ግለሰቦች ንብረት በመበተንና በመደብደብ የቢሮውን ገፅታ በሚያንቋሽሽ መልኩ የሀሰት ቪዲዮ አዘጋጀተው በቲክቶክ ማሰራጨታቸውን ተከትሎ በቀረበባቸው አቤቱታ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
ግለሰቦቹ በተቋሙ እና በሰራተኞቹ ላይ እንዲሁም በህዝብ ዘንድ አሉታዊ ስሜት እንዲፈጠር አስበው የተቋሙን የቀድሞ የደምብ ልብስ የሚመስል አዘጋጅተው ድርጊቱን መፈፀማቸውን ፖሊስ አስታውቋል፤ የፈፀሙት ድርጊት በህግ የሚያስጠይቅ በመሆኑ በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ፖሊስ ጨምሮ ገልጿል፡፡
ሀሰተኛ መረጃ ማሰራጨት በህግ የሚያስጠይቅ በመሆኑ መሰል ድርጊት የሚፈጽሙ ግለሰቦችም ከህገ ወጥ ድርጊታቸው ሊታቀቡ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስቧል፡፡
ምንጭ:- አአ ፖሊስ
@Yenetube @Fikerassefa
ሸጋው ጫኔ አንለይ፣ መሀመድ ሀምዛ ያሲን፣ አቤኔዘር ተስፋዬ በየነ እና ጌትነት ደምለው ዳምጤ የተባሉ ግለሰቦች በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ልዩ ቦታው ደብረወርቅ ህንፃ አካባቢ የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የቀድሞ የደምብ ልብስ የሚመስል በማሰፋት በጎዳና ንግድ ላይ የሚተዳደሩትን ግለሰቦች ንብረት በመበተንና በመደብደብ የቢሮውን ገፅታ በሚያንቋሽሽ መልኩ የሀሰት ቪዲዮ አዘጋጀተው በቲክቶክ ማሰራጨታቸውን ተከትሎ በቀረበባቸው አቤቱታ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
ግለሰቦቹ በተቋሙ እና በሰራተኞቹ ላይ እንዲሁም በህዝብ ዘንድ አሉታዊ ስሜት እንዲፈጠር አስበው የተቋሙን የቀድሞ የደምብ ልብስ የሚመስል አዘጋጅተው ድርጊቱን መፈፀማቸውን ፖሊስ አስታውቋል፤ የፈፀሙት ድርጊት በህግ የሚያስጠይቅ በመሆኑ በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ፖሊስ ጨምሮ ገልጿል፡፡
ሀሰተኛ መረጃ ማሰራጨት በህግ የሚያስጠይቅ በመሆኑ መሰል ድርጊት የሚፈጽሙ ግለሰቦችም ከህገ ወጥ ድርጊታቸው ሊታቀቡ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስቧል፡፡
ምንጭ:- አአ ፖሊስ
@Yenetube @Fikerassefa
😁29👍18❤6👀2
የገንዘብ ቅጣቱ የመጀመሪያ ደረጃ ጥፋት ፣ሁለተኛ ደረጃ ጥፋት እያለ እስከ አምስተኛ ደረጃ የሚያስቀምጣቸው የቅጣት እርከኖች አሉት።
🗣የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ደምብ 185/2017 የተሰኘ የትራንስፖርት አገልግሎቱን ምሽት 4 ሰዓት ድረስ በመንገድ ዳር የሚገኙ የንግድ ተቋማት ደግሞ ምሽት 3:30 ድረስ እንዲቆዩ የሚያስገድድ ደምብ ከመጋቢት 10 ጀምሮ ተግባራዊ ማድረጉ ይታወቃል።
ደንቡን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ያጸደቀው የካቲት 29/2017 ዓ/ም የነበረ ሲሆን ይህ ደንብ መመሪያዎች ተዘጋጅተውለት ከመጋቢት 10/2017 ዓም ጀምሮ ተግባራዊ መሆን ጀምሯል።
@Yenetube @Fikerassefa
🗣የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ደምብ 185/2017 የተሰኘ የትራንስፖርት አገልግሎቱን ምሽት 4 ሰዓት ድረስ በመንገድ ዳር የሚገኙ የንግድ ተቋማት ደግሞ ምሽት 3:30 ድረስ እንዲቆዩ የሚያስገድድ ደምብ ከመጋቢት 10 ጀምሮ ተግባራዊ ማድረጉ ይታወቃል።
ደንቡን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ያጸደቀው የካቲት 29/2017 ዓ/ም የነበረ ሲሆን ይህ ደንብ መመሪያዎች ተዘጋጅተውለት ከመጋቢት 10/2017 ዓም ጀምሮ ተግባራዊ መሆን ጀምሯል።
@Yenetube @Fikerassefa
👍17👎4❤2😁1
YeneTube
Photo
የነጭ ሳር ብሔራዊ ፓርክ በ2 ክልሎች የ'ይገባኛል' ጥያቄ ምክንያት የህልውና አደጋ እንደተጋረጠበት ተገለጸ
በደቡብ እና ኦሮሚያ ክልሎች አዋሳኝ ላይ የሚገኘው የነጭ ሳር ብሔራዊ ፓርክ በክልሎች የ'ይገባኛል' ጥያቄ ምክንያት የህልውና አደጋ እንደተጋረጠበት ተገልጿል፡፡
ፓርኩ ከአጎራባች አካባቢዎች የመጡ ከአንድ ሺሕ በላይ አባወራዎች ወደ ፓርኩ ከ25 ኪሎ ሜትር በላይ ገብተው በመስፈራቸው ምክንያት፤ 50 በመቶ የፓርኩ ይዞታ ከታቀደለት ዓላማ ውጭ እየሆነ ይገኛል ተብሏል፡፡
ሰፋሪዎቹ በተከለለው በፓርኩ ክፍል መኖሪያ ቤትና ትምህርት ቤቶችን ገንብተዋል፤ በሚያሰማሯቸው የግጦሽ እንስሳት አማካኝነትም ጥብቁን ደን እያወደሙ፣ እንስሳትን እያደኑ፣ እና ሌሎች የፓርኩን ሕልውና የሚፈታተኑ ተግባራት እየፈጸሙ በፓርኩ የተጠለሉ ብርቅዬ እንስሳት ላይ የመጥፋት አደጋ አንዲጋረጥ ማድረጋቸውን የጋሞ ዞን መንግሥት ኮሙኒኬሽን አስታውቋል።
የዞኑ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ ታከለ ሀሚሶ ፓርኩ በ1966 ዓ.ም. እንደተቋቋመ አስታውሰው፤ እስከ 1983 ዓ.ም ድረስ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን ይተዳደር እንደነበር ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡
"በፓርኩ ውድመት ቅሬታ የተነሳባቸው ሰፋሪዎች፤ ከ1983 ዓ.ም በኋላ ከኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን የፈለሱ ናቸው" ብለዋል፡፡
አክለውም በፓርኩ ውስጥ ያሉ እንደ ዜብራ ያሉ እንስሳትን ለማየት በፓርኩ ውስጥ በትንሹ 30 ደቂቃ መጓዝ እንደሚጠበቅ ጠቁመው፤ "ይህ የሆነውም እንስሳት መኖሪያ ቤታቸውን ተቀምተው በመሸሻቸው ነው" ሲሉ ተናግረዋል።
የመምሪያ ኃላፊው አቶ ታከለ የፓርኩን ነባር ወሰን ለማስጠበቅ፤ ሕገ-ወጥ ሰፋሪዎችን በማስወጣት ሌላ አካባቢ ለማስፈርና እና ፓርኩን በአግባቡ ለማልማት ከኦሮሚያ ክልል ባለድርሻ አካላት ጋር የመግባቢያ ሰነድ ቢፈረምም፤ ወደ ትግበራ አለመግባቱ ለሕገ-ወጥ ሰፋሪዎቹ መስፋፋት ዋነኛ ምክንያት መሆኑን ተናግረዋል።
አሐዱ የጋሞ ዞንን አቤቱታ በመያዝ በኦሮሚያ ክልል የምዕራብ ጉጂ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን መምሪያን ስለ ጉዳዩ አነጋግሯል።
የመምሪያው ኃላፊ ዳዊት ዘለቀ በሰጡት ምላሽም፤ ወደ ፓርኩ የገቡ ሰፋሪዎች መኖራቸውን እንደማያውቁና ፓርኩ በክልሉ ከሚገኙ የቱሪስት መዳረሻዎች መካከል አንዱ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
ነዋሪዎቹ ከአጎራባች ክልሎች በሕገ-ወጥ መንገድ ገብተዋል የሚለው መረጃ ፈፅሞ የተሳሳተ እንደሆነ የገለጹት ኃላፊው፤ "ነዋሪዎቹ የሚገኙትም በነባር ይዞታቸው እና በክልላቸው ነው" ብለዋል፡፡
ነዋሪዎቹን ወደ ሌሎ አካባቢዎች ለማስፈር የተካሄደ ስምምነት ስለመኖሩ እንደማያውቁም ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡
አሐዱ በሁለቱ ክልሎች የ'ይገባኛል' ጥያቄ ምክንያት አደጋ ላይ የወደቀውን የፓርኩን ህልውና ጉዳይ ለማጣራት የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣንን ጠይቋል።
ፓርኩ በሁለቱ ክልሎች የሚገኝ መሆኑንና፣ ሕገ-ወጥ የደን ጭፍጨፋና፣ አደን እየተካሄደበት እንደሚገኝ አምነው "የሚነሳበት የባለቤትነት ጥያቄ በጥናት ያልተረጋገጠ ነው" ሲሉ፤ የባለሥልጣኑ ምክትል ዳይሬክተር ሰለሞን መኮንን ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
ከምዕራብ ጉጂ ዞን ሕገ-ወጥ ሰፋሪዎች መኖራቸውን የገለጹት አቶ ሰለሞን፤ 'ቦታው የሰፋሪዎቱ ነባር ይዞታ ነው' የሚለው ግን የተሳሳተ መረጃ እንዳልሆነ አብራርተዋል።
የባለሥልጣኑ ምክትል ዳይሬክተር አያይዘውም ከዚህ በፊት በሁለቱም ወገን የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመፍታት የጋራ የምክክር መደረክ መዘጋጀቱን አስታውሰው፤ "ለችግሩ ዘላቂ መፍትሔ ለመሰጠት እየተሰራ ይገኛል" ብለዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
በደቡብ እና ኦሮሚያ ክልሎች አዋሳኝ ላይ የሚገኘው የነጭ ሳር ብሔራዊ ፓርክ በክልሎች የ'ይገባኛል' ጥያቄ ምክንያት የህልውና አደጋ እንደተጋረጠበት ተገልጿል፡፡
ፓርኩ ከአጎራባች አካባቢዎች የመጡ ከአንድ ሺሕ በላይ አባወራዎች ወደ ፓርኩ ከ25 ኪሎ ሜትር በላይ ገብተው በመስፈራቸው ምክንያት፤ 50 በመቶ የፓርኩ ይዞታ ከታቀደለት ዓላማ ውጭ እየሆነ ይገኛል ተብሏል፡፡
ሰፋሪዎቹ በተከለለው በፓርኩ ክፍል መኖሪያ ቤትና ትምህርት ቤቶችን ገንብተዋል፤ በሚያሰማሯቸው የግጦሽ እንስሳት አማካኝነትም ጥብቁን ደን እያወደሙ፣ እንስሳትን እያደኑ፣ እና ሌሎች የፓርኩን ሕልውና የሚፈታተኑ ተግባራት እየፈጸሙ በፓርኩ የተጠለሉ ብርቅዬ እንስሳት ላይ የመጥፋት አደጋ አንዲጋረጥ ማድረጋቸውን የጋሞ ዞን መንግሥት ኮሙኒኬሽን አስታውቋል።
የዞኑ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ ታከለ ሀሚሶ ፓርኩ በ1966 ዓ.ም. እንደተቋቋመ አስታውሰው፤ እስከ 1983 ዓ.ም ድረስ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን ይተዳደር እንደነበር ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡
"በፓርኩ ውድመት ቅሬታ የተነሳባቸው ሰፋሪዎች፤ ከ1983 ዓ.ም በኋላ ከኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን የፈለሱ ናቸው" ብለዋል፡፡
አክለውም በፓርኩ ውስጥ ያሉ እንደ ዜብራ ያሉ እንስሳትን ለማየት በፓርኩ ውስጥ በትንሹ 30 ደቂቃ መጓዝ እንደሚጠበቅ ጠቁመው፤ "ይህ የሆነውም እንስሳት መኖሪያ ቤታቸውን ተቀምተው በመሸሻቸው ነው" ሲሉ ተናግረዋል።
የመምሪያ ኃላፊው አቶ ታከለ የፓርኩን ነባር ወሰን ለማስጠበቅ፤ ሕገ-ወጥ ሰፋሪዎችን በማስወጣት ሌላ አካባቢ ለማስፈርና እና ፓርኩን በአግባቡ ለማልማት ከኦሮሚያ ክልል ባለድርሻ አካላት ጋር የመግባቢያ ሰነድ ቢፈረምም፤ ወደ ትግበራ አለመግባቱ ለሕገ-ወጥ ሰፋሪዎቹ መስፋፋት ዋነኛ ምክንያት መሆኑን ተናግረዋል።
አሐዱ የጋሞ ዞንን አቤቱታ በመያዝ በኦሮሚያ ክልል የምዕራብ ጉጂ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን መምሪያን ስለ ጉዳዩ አነጋግሯል።
የመምሪያው ኃላፊ ዳዊት ዘለቀ በሰጡት ምላሽም፤ ወደ ፓርኩ የገቡ ሰፋሪዎች መኖራቸውን እንደማያውቁና ፓርኩ በክልሉ ከሚገኙ የቱሪስት መዳረሻዎች መካከል አንዱ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
ነዋሪዎቹ ከአጎራባች ክልሎች በሕገ-ወጥ መንገድ ገብተዋል የሚለው መረጃ ፈፅሞ የተሳሳተ እንደሆነ የገለጹት ኃላፊው፤ "ነዋሪዎቹ የሚገኙትም በነባር ይዞታቸው እና በክልላቸው ነው" ብለዋል፡፡
ነዋሪዎቹን ወደ ሌሎ አካባቢዎች ለማስፈር የተካሄደ ስምምነት ስለመኖሩ እንደማያውቁም ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡
አሐዱ በሁለቱ ክልሎች የ'ይገባኛል' ጥያቄ ምክንያት አደጋ ላይ የወደቀውን የፓርኩን ህልውና ጉዳይ ለማጣራት የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣንን ጠይቋል።
ፓርኩ በሁለቱ ክልሎች የሚገኝ መሆኑንና፣ ሕገ-ወጥ የደን ጭፍጨፋና፣ አደን እየተካሄደበት እንደሚገኝ አምነው "የሚነሳበት የባለቤትነት ጥያቄ በጥናት ያልተረጋገጠ ነው" ሲሉ፤ የባለሥልጣኑ ምክትል ዳይሬክተር ሰለሞን መኮንን ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
ከምዕራብ ጉጂ ዞን ሕገ-ወጥ ሰፋሪዎች መኖራቸውን የገለጹት አቶ ሰለሞን፤ 'ቦታው የሰፋሪዎቱ ነባር ይዞታ ነው' የሚለው ግን የተሳሳተ መረጃ እንዳልሆነ አብራርተዋል።
የባለሥልጣኑ ምክትል ዳይሬክተር አያይዘውም ከዚህ በፊት በሁለቱም ወገን የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመፍታት የጋራ የምክክር መደረክ መዘጋጀቱን አስታውሰው፤ "ለችግሩ ዘላቂ መፍትሔ ለመሰጠት እየተሰራ ይገኛል" ብለዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
👍33👎9❤5
አል ዐይን አማርኛ ሥራ ሊያቆም መሆኑን ተገለፀ
ባለቤትነቱ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች መንግስት የሆነው አል ዐይን አማርኛ የበይነ መረብ የዜና ማሠራጫ፤ ሥራ ሊያቆም መሆኑን ዋዜማ ዘግቧል፡፡
የዜና ማሠራጫው በአማርኛ ቋንቋ ዜናዎችንና ዘገባዎችን የሚያዘጋጁ የኢትዮጵያ ዘጋቢዎቹን የቅጥር ውል ማቋረጡን ዘገባው አረጋግጧል፡፡
ዘጋቢዎቹ ሥራቸውን እየሠሩ ባሉበት ወቅት ምንም ዓይነት ቅድመ ማስጠንቂያ ሳይደርሳቸው፣ በድንገት የሥራ ውላቸው መቋረጡን የሚያመላክት መልዕክት በኢሜይል እንደደረሳቸው ተዘግቧል፡፡
ተቋሙ የሠራተኞቹን ውል ያቋረጠው፤ የአማርኛ ዜና አገልግሎቱን አቁሞ የኢትዮጵያ ቢሮውን ዘግቶ ለመውጣት በማሰቡ መሆኑን የዜና ምንጩ ተረድቻለው በሏል፡፡
Via ዋዜማ
ባለቤትነቱ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች መንግስት የሆነው አል ዐይን አማርኛ የበይነ መረብ የዜና ማሠራጫ፤ ሥራ ሊያቆም መሆኑን ዋዜማ ዘግቧል፡፡
የዜና ማሠራጫው በአማርኛ ቋንቋ ዜናዎችንና ዘገባዎችን የሚያዘጋጁ የኢትዮጵያ ዘጋቢዎቹን የቅጥር ውል ማቋረጡን ዘገባው አረጋግጧል፡፡
ዘጋቢዎቹ ሥራቸውን እየሠሩ ባሉበት ወቅት ምንም ዓይነት ቅድመ ማስጠንቂያ ሳይደርሳቸው፣ በድንገት የሥራ ውላቸው መቋረጡን የሚያመላክት መልዕክት በኢሜይል እንደደረሳቸው ተዘግቧል፡፡
ተቋሙ የሠራተኞቹን ውል ያቋረጠው፤ የአማርኛ ዜና አገልግሎቱን አቁሞ የኢትዮጵያ ቢሮውን ዘግቶ ለመውጣት በማሰቡ መሆኑን የዜና ምንጩ ተረድቻለው በሏል፡፡
Via ዋዜማ
👍28😭20👎6❤4👀3😁1
ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር ከ1 ሰዓት በኋላ የምታደርገውን ጨዋታ ለማየት ይህን አፕ ዳውን ሎድ አድርጉ። Cricfy TV በነፃ ነው። ለሌላ ጊዜም ይጠቅማችኋል።
Application ለማውርድ በዚህ ገፅ ላይ ካደረግን Copyright ሊዘጋብን ሰለሚችል አዲስ ቻናል ከፍተናል ለቀናል አፕልኬሽኑን
https://tttttt.me/+LMTodBBw8oI4MjY0
Application ለማውርድ በዚህ ገፅ ላይ ካደረግን Copyright ሊዘጋብን ሰለሚችል አዲስ ቻናል ከፍተናል ለቀናል አፕልኬሽኑን
https://tttttt.me/+LMTodBBw8oI4MjY0
👍11😁9🔥7❤1
45' | ኢትዮጵያ 🇪🇹 0-2 🇪🇬 ግብፅ
31' ሞ ሳላህ
40' ዚዞ
ጎሉን ለማየት
https://tttttt.me/+LMTodBBw8oI4MjY0
#2026_የዓለም_ዋንጫ_ማጣርያ
31' ሞ ሳላህ
40' ዚዞ
ጎሉን ለማየት
https://tttttt.me/+LMTodBBw8oI4MjY0
#2026_የዓለም_ዋንጫ_ማጣርያ
😁15👍9🔥9👎5👀3❤2
Forwarded from In Africa Together
🚨 Big Announcement! 🚨
🎓 In Africa Together – Global University Seminars! 🌍✨
📢 Join us this Sunday at our new headquarters for exclusive seminars with top universities from the USA 🇺🇸, Canada 🇨🇦, Germany 🇩🇪, Netherlands 🇳🇱, Sweden 🇸🇪, Finland 🇫🇮, and more!
📅 Date: Sunday, March 23, 2025
📍 Location: CMC, in front of Civil Service
⏰ Time: 09:00 AM - 03:00 PM
🎟 Entry: FREE!
What’s in it for you?
✅ Meet University Representatives – Live sessions from top universities 🌍
✅ Scholarship & Financial Aid Info – Learn how to fund your studies 💰
✅ On-the-Spot Registration & Contracts – Secure your future today! ✍️
✅ Visa & Admission Guidance – Step-by-step expert advice 🛂
🎓Bachelor’s, Masters & PhD
📌 Seats are limited! Register now: [https://forms.gle/qhDWVQLPD6KwHUnp7]
🔄 Share with friends who dream of studying abroad! See you there! 🎉
🎓 In Africa Together – Global University Seminars! 🌍✨
📢 Join us this Sunday at our new headquarters for exclusive seminars with top universities from the USA 🇺🇸, Canada 🇨🇦, Germany 🇩🇪, Netherlands 🇳🇱, Sweden 🇸🇪, Finland 🇫🇮, and more!
📅 Date: Sunday, March 23, 2025
📍 Location: CMC, in front of Civil Service
⏰ Time: 09:00 AM - 03:00 PM
🎟 Entry: FREE!
What’s in it for you?
✅ Meet University Representatives – Live sessions from top universities 🌍
✅ Scholarship & Financial Aid Info – Learn how to fund your studies 💰
✅ On-the-Spot Registration & Contracts – Secure your future today! ✍️
✅ Visa & Admission Guidance – Step-by-step expert advice 🛂
🎓Bachelor’s, Masters & PhD
📌 Seats are limited! Register now: [https://forms.gle/qhDWVQLPD6KwHUnp7]
🔄 Share with friends who dream of studying abroad! See you there! 🎉
👍5
Luxembourg work visa
ሉዘምበርግ የሥራ ቪዛ
መሥፈርቶች
የታደሰ ፖስፖርት
ፎቶ በሶፍት ኮፒ
እድሜ ከ19—65
የትምህርት ደረጃ: ሃይስኩል እና ከዛ በላይ
የስራዎቹ አይነት
የፋብሪካ ሥራዎች
የግብርና ሥራዎች
የጽዳት ሥራዎች
የኮንስትራክሽን ሥራዎች
የሆቴል ሥራዎች
የመጋዘን ሥራዎች
የዴሊቨሪ ሥራዎች
የላውንደሪ ስራ
መምህር
ነርስ
መካኒካል/ሲቪል ኢንጅነሪንግ
ካሸር
መካኒክ
የፎርክ ሊፍት ኦፕሬተር
ደሞዝ እና ጥቅማጥቅም
በሰአት ከ15 - 30 ዶላር
አኮሞዴሽን ያለው
የጤና ኢንሹራንስ ያለው
ፕሮሰስ ግዜ
ከ 2 ወር - 2 ወር ከ15 ቀን ይፈጃል
የመሳካት እድሉ ከ 98% በላይ
ቅድሚያ ክፍያ 25% ቀሪ ክፍያ ቪዛ ሲያልቅ
አጠቃላይ ክፍያ 900,000 ብር ትኬት አይጨምርም
ዋሥትና
የድርጅት ውልና የባንክ ቼክ እንሰጣለን
ለበለጠ መረጃ
የቴሌግራም inbox ላይ : @Sabinavisa2
☎️👇
🤳ስልክ ቁጥር : +251927555551 / 2 / 3 / 4 / 8
Website
https://sabina.et/
ወደ ቢሮአችን ይምጡ !
👉 አድራሻ:- ሃያ ሁለት ጎላጎል ህንፃ ፊት ለፊት ታውን እስኩዌር ሞል 6ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 602
👉እንዲሁም በሃዋሳ ቱሩፋት ወርቁ ቡቼ ታወር ፊት ለፊት አዲስ የገበያ ማዕከል 2ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 201
ከታላቅ አክብሮት ጋር !!!
https://tttttt.me/sabinaadvisor
ሉዘምበርግ የሥራ ቪዛ
መሥፈርቶች
የታደሰ ፖስፖርት
ፎቶ በሶፍት ኮፒ
እድሜ ከ19—65
የትምህርት ደረጃ: ሃይስኩል እና ከዛ በላይ
የስራዎቹ አይነት
የፋብሪካ ሥራዎች
የግብርና ሥራዎች
የጽዳት ሥራዎች
የኮንስትራክሽን ሥራዎች
የሆቴል ሥራዎች
የመጋዘን ሥራዎች
የዴሊቨሪ ሥራዎች
የላውንደሪ ስራ
መምህር
ነርስ
መካኒካል/ሲቪል ኢንጅነሪንግ
ካሸር
መካኒክ
የፎርክ ሊፍት ኦፕሬተር
ደሞዝ እና ጥቅማጥቅም
በሰአት ከ15 - 30 ዶላር
አኮሞዴሽን ያለው
የጤና ኢንሹራንስ ያለው
ፕሮሰስ ግዜ
ከ 2 ወር - 2 ወር ከ15 ቀን ይፈጃል
የመሳካት እድሉ ከ 98% በላይ
ቅድሚያ ክፍያ 25% ቀሪ ክፍያ ቪዛ ሲያልቅ
አጠቃላይ ክፍያ 900,000 ብር ትኬት አይጨምርም
ዋሥትና
የድርጅት ውልና የባንክ ቼክ እንሰጣለን
ለበለጠ መረጃ
የቴሌግራም inbox ላይ : @Sabinavisa2
☎️👇
🤳ስልክ ቁጥር : +251927555551 / 2 / 3 / 4 / 8
Website
https://sabina.et/
ወደ ቢሮአችን ይምጡ !
👉 አድራሻ:- ሃያ ሁለት ጎላጎል ህንፃ ፊት ለፊት ታውን እስኩዌር ሞል 6ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 602
👉እንዲሁም በሃዋሳ ቱሩፋት ወርቁ ቡቼ ታወር ፊት ለፊት አዲስ የገበያ ማዕከል 2ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 201
ከታላቅ አክብሮት ጋር !!!
https://tttttt.me/sabinaadvisor
👍6