በዎላይታ ዞን ከባድ ዝናብ ባስከተለው የመሬት መንሽራተት አደጋ የ7 ወገኖች ሕይወት አለፈ!
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዎላይታ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ በላሾ እና 01 ቀበሌዎች የጣለው ከባድ ዝናብ ባስከተለው የመሬት መንሽራተት አደጋ የሰባት ሰዎች ህይወት አለፈ፡፡የዞኑ ኮሙኒኬሽን መረጃ እንዳስታወቀው በወረዳው በሁለቱም ቀበሌ በጣለው ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ 2 ወንድ 5 ሴት በድምሩ የ7 ሰዎች ህይወት አልፏል።
ከሟቾች በተጨማሪ አንድ ወንድና አንድ ሴት ላይ ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰ ሲሆን በንብረት ላይም ጉዳት መደረሱ ተገልጿል።ከዚህ ቀደም በዞኑ ካዎ ኮይሻ ወረዳ ጤፓ ቀበሌ በከፍተኛ ዝናብ ምክንያት በተከሰተ የመሬት ናዳ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ይታወቃል።
በተመሳሳይ መልኩ በክልሉ ሀምሌ 15፣ 2016 #ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ ከ250 በላይ ሰዎች ህይወት መለፉም አይዘነጋም።
@YeneTube @FikerAssefa
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዎላይታ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ በላሾ እና 01 ቀበሌዎች የጣለው ከባድ ዝናብ ባስከተለው የመሬት መንሽራተት አደጋ የሰባት ሰዎች ህይወት አለፈ፡፡የዞኑ ኮሙኒኬሽን መረጃ እንዳስታወቀው በወረዳው በሁለቱም ቀበሌ በጣለው ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ 2 ወንድ 5 ሴት በድምሩ የ7 ሰዎች ህይወት አልፏል።
ከሟቾች በተጨማሪ አንድ ወንድና አንድ ሴት ላይ ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰ ሲሆን በንብረት ላይም ጉዳት መደረሱ ተገልጿል።ከዚህ ቀደም በዞኑ ካዎ ኮይሻ ወረዳ ጤፓ ቀበሌ በከፍተኛ ዝናብ ምክንያት በተከሰተ የመሬት ናዳ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ይታወቃል።
በተመሳሳይ መልኩ በክልሉ ሀምሌ 15፣ 2016 #ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ ከ250 በላይ ሰዎች ህይወት መለፉም አይዘነጋም።
@YeneTube @FikerAssefa
😭22👍11❤3👀1