የዓረና ፓርቲ ሊቀ መንበር ዓምዶም ገብረስላሴን ጨምሮ ዛሬ ብቻ ከ20 በላይ ሰዎች ታሰሩ!
በትግራይ ክልል 'ጥምረት ለስር ነቀል ለውጥ” በሚል የተሰባሰቡ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በዛሬ እለት ከጠሩት ሠላማዊ ሰልፍ ጋር ተያይዞ ከጠዋት ጀምሮ ይህ ዘገባ እስከወጣበት ሰዓት ድረስ ቢያንስ ከ20 የሚበልጡ ሰዎች ታስረዋል ተባለ።
የሠልፉ አስተባባሪ ኮሚቴ አባል እና የውድብ ናፃነት ትግራይ (ውናት) ምክትል ሊቀ መንበር አለምሰገድ አረጋይ ለአዲስ ዘይቤ እንደገለፁት “ሰልፉን የሚያስተባብሩ ከተፎካካሪ ፓርቲዎቹ የተውጣጡ የኮሚቴ አባላቶች በሙሉ ከሁለት አስተባባሪዎች በስተቀር ታስረዋል”።
እንደ መረጃ ምንጮቹ ከሆነ ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ ብቻ ከፖለቲካ ፓርቲዎች አመራርና አባላት ብቻ ዓምዶምን ጨምሮ 13 ሰዎች የታሰሩ ሲሆን፣ ስድስት የቀድሞ የትግራይ ሠራዊት (ቲዲኤፍ) ሰዎች፣ አራት ለሰላማዊ ሰልፍ የወጡ ንፁሃን ሰዎች በአጠቃላይ ከ20 በላይ ሰዎች ለእስር ተዳርገዋል።
ሰላማዊ ሰልፉ የተጠራበት ሮማናት አደባባይ አካባቢ “ከሰልፈኞች ቁጥር ያለተናነሰ የፀጥታ ኃይል” መኖሩ የተገለፀ ሲሆን አሁንም በሰልፈኞች እና በፀጥታ ኃይሎች መካከል ግብግብ ቀጥሏል።
Via Addis Zeybe
@YeneTube @FikerAssefa
በትግራይ ክልል 'ጥምረት ለስር ነቀል ለውጥ” በሚል የተሰባሰቡ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በዛሬ እለት ከጠሩት ሠላማዊ ሰልፍ ጋር ተያይዞ ከጠዋት ጀምሮ ይህ ዘገባ እስከወጣበት ሰዓት ድረስ ቢያንስ ከ20 የሚበልጡ ሰዎች ታስረዋል ተባለ።
የሠልፉ አስተባባሪ ኮሚቴ አባል እና የውድብ ናፃነት ትግራይ (ውናት) ምክትል ሊቀ መንበር አለምሰገድ አረጋይ ለአዲስ ዘይቤ እንደገለፁት “ሰልፉን የሚያስተባብሩ ከተፎካካሪ ፓርቲዎቹ የተውጣጡ የኮሚቴ አባላቶች በሙሉ ከሁለት አስተባባሪዎች በስተቀር ታስረዋል”።
እንደ መረጃ ምንጮቹ ከሆነ ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ ብቻ ከፖለቲካ ፓርቲዎች አመራርና አባላት ብቻ ዓምዶምን ጨምሮ 13 ሰዎች የታሰሩ ሲሆን፣ ስድስት የቀድሞ የትግራይ ሠራዊት (ቲዲኤፍ) ሰዎች፣ አራት ለሰላማዊ ሰልፍ የወጡ ንፁሃን ሰዎች በአጠቃላይ ከ20 በላይ ሰዎች ለእስር ተዳርገዋል።
ሰላማዊ ሰልፉ የተጠራበት ሮማናት አደባባይ አካባቢ “ከሰልፈኞች ቁጥር ያለተናነሰ የፀጥታ ኃይል” መኖሩ የተገለፀ ሲሆን አሁንም በሰልፈኞች እና በፀጥታ ኃይሎች መካከል ግብግብ ቀጥሏል።
Via Addis Zeybe
@YeneTube @FikerAssefa
👍25👎2❤1
ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብቶች ባለሙያ ቡድን ኮሚሽን በኢትዮጵያ የሥራ ጊዜው በአንድ ዓመት እንዲራዘም 63 ድርጅቶች ጠየቁ፡፡
ሁለቱ የሰብዓዊ መብቶች ተከራካሪ ድርጅቶች ሂዩውማን ራይትስ ዎችና አምነስቲ ኢንተርናሽናልን ጨምሮ 63 ድርጅቶች ከቀናት በኋላ የሚጠናቀቀው የኮሚሸኑ የሥራ ጊዜ እስከ መስከረም 2024 እ.አ.አ. ወይም አንድ ዓመት እንዲራዘም ለተባባሩት መንግስታት ድርጅት 54ኛው የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ ባለኩት ደብዳቤ ጠይቀዋል፡፡
እነዚህ የሲቪልና የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች እንደሚሉት በኢትዮጵያ ያለው የከፋ የሰብኣዊ መብቶች አያያዝ፣ የኮሚሽኑን የሥራ ጊዜ እንዲራዘም የሚያስገድድ ነው፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት የኮሚሽኑን ሥራ ደጋግሞ ለማደናቀፍ ቢሞክርም፣ ይህ የባለሙያዎች ቡድን እጅግ ጠቃሚ ስራዎችን መስራቱን ደብዳቤው አመልክቷል፡፡ መንግስት በኮሚሽኑ ላይ እንቅፋት ሆኗል ሲል ከተጠቀሳቸው ጉዳዮች መካከል ‹‹ ባለሙያዎቹ በአዲስ አበባ እንጂ በሌሎች ግጭት ባለባቸው አካባቢዎች እንዳይሄድ፣ ለኮሚሽኑ በጀት እንዳይመደብና ስራው ሙሉ በሙሉ እንዲቀለበስ ደጋግሞ መሞከር ›› የሚሉት ይገኙበታል፡፡
እነዚህ ፈተናዎች ቢኖሩም ‹‹ ኮሚሽኑ በወርሃ መስከረም 2022 እ.አ.አ. ይፋ ባደረገው የመጀመሪያ ዙር ሪፖርት የሰሜን ኢትዮጵያ ሁሉም ተፋላሚ ሀይላት የጦር ወንጀል መፈፀማቸውን ሊያሳምን የሚችል ማስረጃዎችን አጋልጧል ›› ብሏል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ሁለቱ የሰብዓዊ መብቶች ተከራካሪ ድርጅቶች ሂዩውማን ራይትስ ዎችና አምነስቲ ኢንተርናሽናልን ጨምሮ 63 ድርጅቶች ከቀናት በኋላ የሚጠናቀቀው የኮሚሸኑ የሥራ ጊዜ እስከ መስከረም 2024 እ.አ.አ. ወይም አንድ ዓመት እንዲራዘም ለተባባሩት መንግስታት ድርጅት 54ኛው የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ ባለኩት ደብዳቤ ጠይቀዋል፡፡
እነዚህ የሲቪልና የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች እንደሚሉት በኢትዮጵያ ያለው የከፋ የሰብኣዊ መብቶች አያያዝ፣ የኮሚሽኑን የሥራ ጊዜ እንዲራዘም የሚያስገድድ ነው፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት የኮሚሽኑን ሥራ ደጋግሞ ለማደናቀፍ ቢሞክርም፣ ይህ የባለሙያዎች ቡድን እጅግ ጠቃሚ ስራዎችን መስራቱን ደብዳቤው አመልክቷል፡፡ መንግስት በኮሚሽኑ ላይ እንቅፋት ሆኗል ሲል ከተጠቀሳቸው ጉዳዮች መካከል ‹‹ ባለሙያዎቹ በአዲስ አበባ እንጂ በሌሎች ግጭት ባለባቸው አካባቢዎች እንዳይሄድ፣ ለኮሚሽኑ በጀት እንዳይመደብና ስራው ሙሉ በሙሉ እንዲቀለበስ ደጋግሞ መሞከር ›› የሚሉት ይገኙበታል፡፡
እነዚህ ፈተናዎች ቢኖሩም ‹‹ ኮሚሽኑ በወርሃ መስከረም 2022 እ.አ.አ. ይፋ ባደረገው የመጀመሪያ ዙር ሪፖርት የሰሜን ኢትዮጵያ ሁሉም ተፋላሚ ሀይላት የጦር ወንጀል መፈፀማቸውን ሊያሳምን የሚችል ማስረጃዎችን አጋልጧል ›› ብሏል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
👍35❤3
"ግጭቶች ሳይፈጠሩ ቀድመን ወደ ውይይት መምጣት አለብን፣ እሣት ማጥፋት ላይ መጠመድ የለብንም" ሲሉ የመብቶችና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል /ካርድ/ ዋና ዳይሬክተር አቶ በፍቃዱ ሀይሉ ተናገሩ፡፡
የነበሩ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ ለምፍታት፣ እየመጡ ያሉ የሚታዩ ግጭቶችን ቀድሞ ለመከላከልና መልስ እንዲያገኙ ለማድረግ እና በሰላማዊ መንገድ የተፈቱ ግጭቶችን ዛላቂ ለማድረግ ሁሉን አካታች የውይይት መድረክ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡በሀገራችን እስካሁን ድረስ እየተደረጉ ያሉት ሙከራዎች እሣት የማጥፋት ሁኔታዎቸ ናቸው ያሉት ዋና ዳይሬከተሩ የውይይት መድረኮች ግጭቶች ሳይፈጠሩ ቀድመው መከናወን አለባቸው ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ በተለያዩ አቅጣጫዎች ግጭቶች ሲመጡ ቀድመው ይታያሉ ስለዚህም እነዚህን ግጭቶች ለመከላከል የሚያስችል የውይይት መድረክ ያስፈልጋል ሲሉ ተደምጠዋል፡፡
በባለፈው ዓመት በተመሳሳይ በትግራይ የነበረው ጦርነት እንዲቆም ጥሪ አቅርበን ከመንግስት ከፍተኛ ውግዘትን ብናስተናግድም ከተወሰኑ ወራት ባኃላ የፕሪቶሪያው ውይይት ተካሂዷል ብለዋል አቶ በፍቃዱ ሀይሉ፡፡በመሆኑም መንግስት አሁንም ሁሉን አቀፍ የሆነና ዘላቂ የሆነ መድረክ አዘጋጅቶ ያሉበትን ችግሮች በውይይት መፍታት ያስፈልገዋል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
የነበሩ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ ለምፍታት፣ እየመጡ ያሉ የሚታዩ ግጭቶችን ቀድሞ ለመከላከልና መልስ እንዲያገኙ ለማድረግ እና በሰላማዊ መንገድ የተፈቱ ግጭቶችን ዛላቂ ለማድረግ ሁሉን አካታች የውይይት መድረክ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡በሀገራችን እስካሁን ድረስ እየተደረጉ ያሉት ሙከራዎች እሣት የማጥፋት ሁኔታዎቸ ናቸው ያሉት ዋና ዳይሬከተሩ የውይይት መድረኮች ግጭቶች ሳይፈጠሩ ቀድመው መከናወን አለባቸው ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ በተለያዩ አቅጣጫዎች ግጭቶች ሲመጡ ቀድመው ይታያሉ ስለዚህም እነዚህን ግጭቶች ለመከላከል የሚያስችል የውይይት መድረክ ያስፈልጋል ሲሉ ተደምጠዋል፡፡
በባለፈው ዓመት በተመሳሳይ በትግራይ የነበረው ጦርነት እንዲቆም ጥሪ አቅርበን ከመንግስት ከፍተኛ ውግዘትን ብናስተናግድም ከተወሰኑ ወራት ባኃላ የፕሪቶሪያው ውይይት ተካሂዷል ብለዋል አቶ በፍቃዱ ሀይሉ፡፡በመሆኑም መንግስት አሁንም ሁሉን አቀፍ የሆነና ዘላቂ የሆነ መድረክ አዘጋጅቶ ያሉበትን ችግሮች በውይይት መፍታት ያስፈልገዋል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
👍23❤1
“ትንሣኤ 70 እንደርታ” የተሰኘ በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀስ ፓርቲ፤ መስራች ጉባኤውን በነገው ዕለት ሊያካሄድ ነው!
በትግራይ ክልል “የተንሰራፋውን ጭቆና እና የአንድ ፓርቲ ስርዓት” ለመታገል መነሳቱን የገለጸው ትንሣኤ 70 እንደርታ ፓርቲ (ትሰእፓ) የተሰኘ ክልላዊ ፓርቲ፤ መስራች ጉባኤውን ነገ አርብ ጷጉሜ 3 በአዲስ አበባ ከተማ ሊያካሄድ ነው። በትግራይ ክልል “ህብረ ብሔራዊ ስርዓት እንዲፈጠር” እንደሚታገል የጠቆመው ፓርቲው፤ ይህ የማይሳካ ከሆነ የእንደርታ ህዝብ “ከሌሎች ህዝቦች ጋር በጋራ ወይም ለብቻው” “የራሱን ክልላዊ መንግስት” እንዲመሰርት እንደሚታገልም አስታውቋል።
ከሰባት ወራት በፊት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጊዜያዊ ምዝገባ ፈቃድ ያገኘው ትሰእፓ፤ ጠቅላላ ጉባኤውን ከዛሬ ሐሙስ ጷጉሜ 2፤ 2015 ጀምሮ እንደሚያካሄድ አስቀድሞ ገልጾ ነበር። ይህንን ተከትሎም የፓርቲው አባላት እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ጠቅላላ ጉባኤው በሚካሄድበት የአዲስ አበባ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ዛሬ ከጠዋት ጀምሮ ተገኝተው ነበር።
ሆኖም መስራች ጉባኤውን ለመታዘብ በቦታው የተገኙት ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተወካዮች፤ ስብሰባው ከመደረጉ አስቀድሞ መሟላት የሚገባቸው ነገሮች አለመሟላታቸውን በማስታወቃቸው ጠቅላላ ጉባኤው ለነገ መተላለፉን የፓርቲው አመራሮች በስፍራው ለተገኘው የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ዘጋቢ ተናግረዋል። አመራሮቹ በምርጫ ቦርድ “ማሟላት ይገባችኋል” የተባሏቸውን ጉዳዮች ግን ከመናገር ተቆጥበዋል።
Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
በትግራይ ክልል “የተንሰራፋውን ጭቆና እና የአንድ ፓርቲ ስርዓት” ለመታገል መነሳቱን የገለጸው ትንሣኤ 70 እንደርታ ፓርቲ (ትሰእፓ) የተሰኘ ክልላዊ ፓርቲ፤ መስራች ጉባኤውን ነገ አርብ ጷጉሜ 3 በአዲስ አበባ ከተማ ሊያካሄድ ነው። በትግራይ ክልል “ህብረ ብሔራዊ ስርዓት እንዲፈጠር” እንደሚታገል የጠቆመው ፓርቲው፤ ይህ የማይሳካ ከሆነ የእንደርታ ህዝብ “ከሌሎች ህዝቦች ጋር በጋራ ወይም ለብቻው” “የራሱን ክልላዊ መንግስት” እንዲመሰርት እንደሚታገልም አስታውቋል።
ከሰባት ወራት በፊት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጊዜያዊ ምዝገባ ፈቃድ ያገኘው ትሰእፓ፤ ጠቅላላ ጉባኤውን ከዛሬ ሐሙስ ጷጉሜ 2፤ 2015 ጀምሮ እንደሚያካሄድ አስቀድሞ ገልጾ ነበር። ይህንን ተከትሎም የፓርቲው አባላት እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ጠቅላላ ጉባኤው በሚካሄድበት የአዲስ አበባ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ዛሬ ከጠዋት ጀምሮ ተገኝተው ነበር።
ሆኖም መስራች ጉባኤውን ለመታዘብ በቦታው የተገኙት ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተወካዮች፤ ስብሰባው ከመደረጉ አስቀድሞ መሟላት የሚገባቸው ነገሮች አለመሟላታቸውን በማስታወቃቸው ጠቅላላ ጉባኤው ለነገ መተላለፉን የፓርቲው አመራሮች በስፍራው ለተገኘው የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ዘጋቢ ተናግረዋል። አመራሮቹ በምርጫ ቦርድ “ማሟላት ይገባችኋል” የተባሏቸውን ጉዳዮች ግን ከመናገር ተቆጥበዋል።
Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
👍21👎4❤3
በጋምቤላ ክልል ጥቃት አራት ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ!
በጋምቤላ ክልል ማጃንግ ብሔረሰብ ዞን ጎዳሬ ወረዳ ውስጥ ባለፈው ሳምንት እሁድ ነሐሴ 28 ቀን፣ 2015 ዓ.ም «ያልታወቁ» የተባሉ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት የአራት ሰዎች ሕይወት ማለፉ እና 2 ሰዎች መቁሰላቸውን ዞኑ ዐስታወቀ። የአካባቢው ባለሥልጣናት በስልክ ለዶይቸ ቬለ እንደተናገሩት፦ በወረዳው በተከተሰው የፀጥታ ችግር ምክንያት ተቋማት እስከ ዛሬ ጠዋት ድረስ ተዘግተው ቆይተዋል።
በጋምቤላ ክልል ማጃንጃግ ብሔረሰብ ዞን ጎዳሬ ወረዳ ባለፈው ሳምንት እሁድ ደረሰ በተባለው ጥቃት የደረሰው ጉዳት መጠን ሊጨምር እንደሚችልም ነዋሪዎች ተናግረዋል። እሁድ ዕለት የደረሰው ጥቃት ወደ ዞን ዋና ከተማው መጢ ከተማ በመስፋፋቱ የፈዴራል ፀጥታ ኃይሎች ወደ ስፋራው መሰማራታቸውም ተዘግቧል።በዛሬው ዕለት በወረዳው አንጻራዊ ሰላም መስፈኑ፤ ዛሬ ከሰዓት የመንግስት ተቋማት በከፊል ሥራ መጀመራቸውም ተገልጿል።
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
በጋምቤላ ክልል ማጃንግ ብሔረሰብ ዞን ጎዳሬ ወረዳ ውስጥ ባለፈው ሳምንት እሁድ ነሐሴ 28 ቀን፣ 2015 ዓ.ም «ያልታወቁ» የተባሉ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት የአራት ሰዎች ሕይወት ማለፉ እና 2 ሰዎች መቁሰላቸውን ዞኑ ዐስታወቀ። የአካባቢው ባለሥልጣናት በስልክ ለዶይቸ ቬለ እንደተናገሩት፦ በወረዳው በተከተሰው የፀጥታ ችግር ምክንያት ተቋማት እስከ ዛሬ ጠዋት ድረስ ተዘግተው ቆይተዋል።
በጋምቤላ ክልል ማጃንጃግ ብሔረሰብ ዞን ጎዳሬ ወረዳ ባለፈው ሳምንት እሁድ ደረሰ በተባለው ጥቃት የደረሰው ጉዳት መጠን ሊጨምር እንደሚችልም ነዋሪዎች ተናግረዋል። እሁድ ዕለት የደረሰው ጥቃት ወደ ዞን ዋና ከተማው መጢ ከተማ በመስፋፋቱ የፈዴራል ፀጥታ ኃይሎች ወደ ስፋራው መሰማራታቸውም ተዘግቧል።በዛሬው ዕለት በወረዳው አንጻራዊ ሰላም መስፈኑ፤ ዛሬ ከሰዓት የመንግስት ተቋማት በከፊል ሥራ መጀመራቸውም ተገልጿል።
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
👍30❤1
Facebook, Twitter, Instagram እና በመሳሳሉት የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ድርጅትዎን ፤ አገልግሎትዎን እና ምርትዎን ማስተዋወቅ ፈልገዋል? እንግዲያውስ መፍትሄው እኛ ጋር ነው።
በማንኛውም Social Media Boost ለማድረግ ካሰቡ ይደውሉልን፤ በተመጣጣኝ ዋጋ ታማኝና ቀልጣፋ አገልግሎት እንሰጣለን::
ከዚህም በተጨማሪ የቴሌግራም ፕሪሚየም ጨምሮ ለተለያዩ ኢንተርናሽናል አገልግሎቶች ክፍያዎችን መፈጸም ካስፈለግዎ ከስር በተቀመጡ አድራሻዎች ያናግሩን።
Telegram: @adsommar
📞0929334267
በማንኛውም Social Media Boost ለማድረግ ካሰቡ ይደውሉልን፤ በተመጣጣኝ ዋጋ ታማኝና ቀልጣፋ አገልግሎት እንሰጣለን::
ከዚህም በተጨማሪ የቴሌግራም ፕሪሚየም ጨምሮ ለተለያዩ ኢንተርናሽናል አገልግሎቶች ክፍያዎችን መፈጸም ካስፈለግዎ ከስር በተቀመጡ አድራሻዎች ያናግሩን።
Telegram: @adsommar
📞0929334267
👍10❤1
ፓስፖርት ለማግኘት የሚጠባበቁ ከ 300 ሺህ በላይ ሰዎች መኖራቸውን የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አሳወቀ!
የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አዲስ አመራር ከተሾመለት ወዲህ ላለፈዉ አንድ ወር ያከናወነዉን የማሻሻያ ስራ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት በዛሬዉ እለት ለጋዜጠኞች ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በአሁኑ ሰዓት በአገልግሎቱ ፓስፖርት ለማግኘት ወረፋ በመጠባበቅ ላይ ያሉ ከ 300 ሺህ በላይ ዜጎች መኖራቸዉን ዋና ዳይሬክተሯ ገልጸዋል። የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አዲሷ ዳይሬክተር ፤ ላለፈዉ አንድ ወር በተቋማቸዉ አሉ ያሏቸዉን ችግሮች ለመቅረፍ ምልከታ ማድረጋቸዉን ተናግረዋል።
በዚህም ተቋሙ የአጭር ፣ መካከለኛ እና የረጅም ጊዜ እቅድ ነድፎ እየሰራ ነዉ ብለዋል። በኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት የሚነሳዉን እና ዜጎችን ያማረረዉ የሌብነት እና ብልሹ አሰራር ለመቅረፍ አዲስ የአሰራር መንገድ በመዘርጋት ላይ መሆኑን ገልጸዋል። በርከት ባሉ የተቋሙ ዳይሬክተሮች ፣ ሰራተኞች እና በጊቢዉ ዙሪያ ባሉ ማስረጃ በተገኘባቸዉ ደላሎች ላይ ከአስተዳደራዊ እስከ ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን ተናግረዋል።
በሌላ በኩል የተከሰተዉን ከፍ ያለ የፓስፖርት እጥረት ለመቅረፍ በዉጪ ከሚገኝ አምራች ተቋም ጋር ከስምምነት መድረሳቸዉን ጠቅሰዋል። ለእጥረቱ የዉጪ ምንዛሬ እጥረት እና አለማቀፍ ምክኒያቶች መንስኤ ነበሩ ብለዋል። ችግሩ አሁን በመጠኑ በመቀረፉ 190 ሺህ አዲስ ፓስፖርት ማተም መቻሉን ገልጸዉ ፤ አንገብጋቢ ለሆኑ ጉዳዮች ማለትም በአረቡ አለም ለሚገኙና በተለያዩ የዉጪ ሀገራት ካለ ፓስፖርት ለሚኖሩ ዜጎች ቅድሚያ መሰጠቱን ተናግረዋል።
በተጨማሪም ባለፉት 90 ቀናት ዉስጥ የፓስፖርት ቀጠሮአቸው በተለያዩ ምክኒያቶች ያለፋቸዉ ሰዎች ዘወትር ቅዳሜ አገልግሎት እንደሚሰጥ ጠቅሰዋል። ወደ ኢትዮጵያ ከዉጭ በሚመጡ ሰዎች ላይም ቪዛ ለማግኘት በነበረዉ ሂደት ይፈጸም ነበር ያሉትን ሌብነት ለመቀነስ ዘመናዊ አሰራር ተዘርግቷል ነዉ ያሉት። ወደ ኢትዮጵያ በገቡበት ሰዓትም ወዲያዉኑ ቪዛ የሚያገኙበትን On Arrival Visa ከመስከረም 15 ቀን ጀምሮ መሰጠት ይጀምራል ብለዋል።
የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ፤ የቀጠሮ መያዣ ስርዓቱ የመሳስሎ ተሰርቶ ለደላሎች እና ሌቦች ተጋልጦ የነበረ መሆኑን ፣ አሰራሩ ዘመኑን ያልዋጀ እና ኋላ ቀር የነበረ መሆኑን ፣ እነዚህና ሌሎች ጥቃቅን ችግሮችን በተደራራቢነት የሚያመጡ ክፍተቶች ነበሩበት ብለዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አዲስ አመራር ከተሾመለት ወዲህ ላለፈዉ አንድ ወር ያከናወነዉን የማሻሻያ ስራ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት በዛሬዉ እለት ለጋዜጠኞች ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በአሁኑ ሰዓት በአገልግሎቱ ፓስፖርት ለማግኘት ወረፋ በመጠባበቅ ላይ ያሉ ከ 300 ሺህ በላይ ዜጎች መኖራቸዉን ዋና ዳይሬክተሯ ገልጸዋል። የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አዲሷ ዳይሬክተር ፤ ላለፈዉ አንድ ወር በተቋማቸዉ አሉ ያሏቸዉን ችግሮች ለመቅረፍ ምልከታ ማድረጋቸዉን ተናግረዋል።
በዚህም ተቋሙ የአጭር ፣ መካከለኛ እና የረጅም ጊዜ እቅድ ነድፎ እየሰራ ነዉ ብለዋል። በኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት የሚነሳዉን እና ዜጎችን ያማረረዉ የሌብነት እና ብልሹ አሰራር ለመቅረፍ አዲስ የአሰራር መንገድ በመዘርጋት ላይ መሆኑን ገልጸዋል። በርከት ባሉ የተቋሙ ዳይሬክተሮች ፣ ሰራተኞች እና በጊቢዉ ዙሪያ ባሉ ማስረጃ በተገኘባቸዉ ደላሎች ላይ ከአስተዳደራዊ እስከ ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን ተናግረዋል።
በሌላ በኩል የተከሰተዉን ከፍ ያለ የፓስፖርት እጥረት ለመቅረፍ በዉጪ ከሚገኝ አምራች ተቋም ጋር ከስምምነት መድረሳቸዉን ጠቅሰዋል። ለእጥረቱ የዉጪ ምንዛሬ እጥረት እና አለማቀፍ ምክኒያቶች መንስኤ ነበሩ ብለዋል። ችግሩ አሁን በመጠኑ በመቀረፉ 190 ሺህ አዲስ ፓስፖርት ማተም መቻሉን ገልጸዉ ፤ አንገብጋቢ ለሆኑ ጉዳዮች ማለትም በአረቡ አለም ለሚገኙና በተለያዩ የዉጪ ሀገራት ካለ ፓስፖርት ለሚኖሩ ዜጎች ቅድሚያ መሰጠቱን ተናግረዋል።
በተጨማሪም ባለፉት 90 ቀናት ዉስጥ የፓስፖርት ቀጠሮአቸው በተለያዩ ምክኒያቶች ያለፋቸዉ ሰዎች ዘወትር ቅዳሜ አገልግሎት እንደሚሰጥ ጠቅሰዋል። ወደ ኢትዮጵያ ከዉጭ በሚመጡ ሰዎች ላይም ቪዛ ለማግኘት በነበረዉ ሂደት ይፈጸም ነበር ያሉትን ሌብነት ለመቀነስ ዘመናዊ አሰራር ተዘርግቷል ነዉ ያሉት። ወደ ኢትዮጵያ በገቡበት ሰዓትም ወዲያዉኑ ቪዛ የሚያገኙበትን On Arrival Visa ከመስከረም 15 ቀን ጀምሮ መሰጠት ይጀምራል ብለዋል።
የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ፤ የቀጠሮ መያዣ ስርዓቱ የመሳስሎ ተሰርቶ ለደላሎች እና ሌቦች ተጋልጦ የነበረ መሆኑን ፣ አሰራሩ ዘመኑን ያልዋጀ እና ኋላ ቀር የነበረ መሆኑን ፣ እነዚህና ሌሎች ጥቃቅን ችግሮችን በተደራራቢነት የሚያመጡ ክፍተቶች ነበሩበት ብለዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
👍24❤2🔥1
አጎአን ጨምሮ የአሜሪካ መንግስት በኢትዮጵያ ላይ የጣለውን ማዕቀብ ለአንድ ዓመት አራዘመ!
- እ.ኤ.አ. መስከረም 2021 ከሁለት ዓመታት በፊት በአሜሪካ ኤግዚኪዩቲቭ ኦርደር 14046 መሰረት በብሄራዊ ደህንነት እና የውጭ ፖሊሲ ላይ የተደቀነ ስጋትን ለመቋቋም በሚል ከትግራይ ክልል ጦርነት ጋር ተያይዞ በኢትዮጵያ መንግስት ላይ የጣለውን ማዕቀብ ለአንድ ዓመት አራዝሟል።
- የኢትዮጵያ መንግስት እና ባለስልጣናት ማዕቀቡን በተደጋጋሚ “በውስጥ ጉዳይ ተገብቶ የተጣለ ማዕቀብ” በማለት የሚጠሩት ሲሆን በ2013 ዓ.ም. በድሬዳዋ ከተማ የተደረገውን ጨምሮ የአሜሪካ ማዕቀብ በኢትዮጵያ ላይ ሊያሳድር በሚችለው ጫና ላይ ያተኮሩ ውይይቶች ሲደረጉ ተስተውሏል።
- ማዕቀቦቹ የኢትዮጵያ እንዲሁም የኤርትራ ባለስልጣናት፣ ወታደራዊ ሰራተኞች እና ሌሎች ግለሰቦች የቪዛ እገዳ፣ በትግራይ ክልል እና በኢትዮጵያ ለተስፋፋው ብጥብጥ፣ ግፍ እና ከባድ የሰብአዊ መብት ጥሰት ተጠያቂ የሆኑ አካላት እና ግለሰቦች ላይም ልዩ ማዕቀቦችን ያካተተ ነው።
- በተጨማሪም የመከላከያ አገልግሎቶችም ሆኑ መሳሪያዎች ለኢትዮጵያ እና ኤርትራ የታጠቁ ኃይሎች፣ ለፖሊስ፣ ለስለላ ወይም ለሌሎች የውስጥ ደኅንነት ኃይሎች እንዳይላኩ እንዲሁም ኢትዮጵያ በዓመት እስከ 100 ሚልየን ዶላር ገቢ ታገኝበት የነበረው የአፍሪካ የዕድገትና ዕድል ሕግ (አጎአ) ከቀረጥ ነፃ የአሜሪካን ገበያ ተጠቃሚነትን ማሳጣት ለሚቀጥለው አንድ ዓመት ከሚቀጥሉ ማዕቀቦች ዋነኞቹ ናቸው።
- ማዕቀቦቹ አሁን ለሁለተኛ ጊዜ የተራዘሙ ሲሆን እስከ መስከረም 2024 ይፀናሉ።
✍️Addis Zeybe
@YeneTube @FikerAssefa
- እ.ኤ.አ. መስከረም 2021 ከሁለት ዓመታት በፊት በአሜሪካ ኤግዚኪዩቲቭ ኦርደር 14046 መሰረት በብሄራዊ ደህንነት እና የውጭ ፖሊሲ ላይ የተደቀነ ስጋትን ለመቋቋም በሚል ከትግራይ ክልል ጦርነት ጋር ተያይዞ በኢትዮጵያ መንግስት ላይ የጣለውን ማዕቀብ ለአንድ ዓመት አራዝሟል።
- የኢትዮጵያ መንግስት እና ባለስልጣናት ማዕቀቡን በተደጋጋሚ “በውስጥ ጉዳይ ተገብቶ የተጣለ ማዕቀብ” በማለት የሚጠሩት ሲሆን በ2013 ዓ.ም. በድሬዳዋ ከተማ የተደረገውን ጨምሮ የአሜሪካ ማዕቀብ በኢትዮጵያ ላይ ሊያሳድር በሚችለው ጫና ላይ ያተኮሩ ውይይቶች ሲደረጉ ተስተውሏል።
- ማዕቀቦቹ የኢትዮጵያ እንዲሁም የኤርትራ ባለስልጣናት፣ ወታደራዊ ሰራተኞች እና ሌሎች ግለሰቦች የቪዛ እገዳ፣ በትግራይ ክልል እና በኢትዮጵያ ለተስፋፋው ብጥብጥ፣ ግፍ እና ከባድ የሰብአዊ መብት ጥሰት ተጠያቂ የሆኑ አካላት እና ግለሰቦች ላይም ልዩ ማዕቀቦችን ያካተተ ነው።
- በተጨማሪም የመከላከያ አገልግሎቶችም ሆኑ መሳሪያዎች ለኢትዮጵያ እና ኤርትራ የታጠቁ ኃይሎች፣ ለፖሊስ፣ ለስለላ ወይም ለሌሎች የውስጥ ደኅንነት ኃይሎች እንዳይላኩ እንዲሁም ኢትዮጵያ በዓመት እስከ 100 ሚልየን ዶላር ገቢ ታገኝበት የነበረው የአፍሪካ የዕድገትና ዕድል ሕግ (አጎአ) ከቀረጥ ነፃ የአሜሪካን ገበያ ተጠቃሚነትን ማሳጣት ለሚቀጥለው አንድ ዓመት ከሚቀጥሉ ማዕቀቦች ዋነኞቹ ናቸው።
- ማዕቀቦቹ አሁን ለሁለተኛ ጊዜ የተራዘሙ ሲሆን እስከ መስከረም 2024 ይፀናሉ።
✍️Addis Zeybe
@YeneTube @FikerAssefa
👍50👎14❤2
በፀጥታ ችግር ፈተና ያልወሰዱ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ከመስከረም 8 ቀን ጀምሮ ይፈተናሉ!
በፀጥታ ችግርና በሌሎች ምክንያቶች ፈተና ያልወሰዱ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞችን ለመፈተን መዘጋጀቱን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል፡፡
የ2015 ዓ.ም የኢትዮጵያ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፊኬት (12ኛ ክፍል) ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ በሁለት ዙር መሰጠቱን አገልግሎቱ አስታውሷል፡፡
ይሁንና በጎንደርና በጋምቤላ በነበረው የፀጥታ ችግር ምክንያት ሙሉ በሙሉ እና በከፊል 14 ሺህ 891 ተማሪዎች እንዲሁም በሕህ ግ ጥላ ስር በማረሚያ ቤቶች የሚገኙ 419 ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናውን ሳይወስዱ መቅረታቸው ተጠቅሷል፡፡
ተፈታኞችን ከመጪው መስከረም 8 እስከ መስከረም 11 ቀን 2016 ዓ.ም ለመፈተን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል፡፡ውጤታቸውም ከመጀመሪያው ዙር ጋር እንደሚገለጽም የአገልግሎቱ መረጃ ያመላክታል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
በፀጥታ ችግርና በሌሎች ምክንያቶች ፈተና ያልወሰዱ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞችን ለመፈተን መዘጋጀቱን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል፡፡
የ2015 ዓ.ም የኢትዮጵያ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፊኬት (12ኛ ክፍል) ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ በሁለት ዙር መሰጠቱን አገልግሎቱ አስታውሷል፡፡
ይሁንና በጎንደርና በጋምቤላ በነበረው የፀጥታ ችግር ምክንያት ሙሉ በሙሉ እና በከፊል 14 ሺህ 891 ተማሪዎች እንዲሁም በሕህ ግ ጥላ ስር በማረሚያ ቤቶች የሚገኙ 419 ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናውን ሳይወስዱ መቅረታቸው ተጠቅሷል፡፡
ተፈታኞችን ከመጪው መስከረም 8 እስከ መስከረም 11 ቀን 2016 ዓ.ም ለመፈተን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል፡፡ውጤታቸውም ከመጀመሪያው ዙር ጋር እንደሚገለጽም የአገልግሎቱ መረጃ ያመላክታል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
👍15❤4
የዛሬ ጨዋታዎች የቤትስኬት ግምት
ማሊ፣ ስፔን፣ ፖርቹጋልን እና ሌቫንቴን የተመለከቱ የቤቲንግ መረጃዎች እና ግምቶች በቤትስኬት
ሊንኩን በመጫን በነጻ ያንብቡ👇👇
http://www.betsket.com/የዛሬ-ጨዋታዎች-የቤትስኬት-ግምት/
ሁል ጊዜ የሚለቀቁ መረጃዎችን በአንድ ላይ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ።👉 @betskett
ማሊ፣ ስፔን፣ ፖርቹጋልን እና ሌቫንቴን የተመለከቱ የቤቲንግ መረጃዎች እና ግምቶች በቤትስኬት
ሊንኩን በመጫን በነጻ ያንብቡ👇👇
http://www.betsket.com/የዛሬ-ጨዋታዎች-የቤትስኬት-ግምት/
ሁል ጊዜ የሚለቀቁ መረጃዎችን በአንድ ላይ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ።👉 @betskett
👍2❤1
የሳኡዲ አረቢያው ፕሮሊግ ለተጨዋቾች ግዥ 1 ቢሊዮን ዶላር ወጭ አደረገ!
የሳኡዲ አረቢያው ፕሮሊግ ለተጨዋቾች ግዥ 1 ቢሊዮን ዶላር ወጭ አደረገ።የዘንድሮው የተጨዋቾች የዝውውር መስኮት ሲዘጋ የሳኡዲ አረቢያው ፕሮሊግ 1 ቢሊዮን ዶላር ወጭ አውጥቷል።
አዲስ የእግር ኳስ መናኸሪያ መሆኗን ያስታወቀችው የነዳጅ ባለጸጋዋ ሳኡዲ አረቢያ ትናንት በባቃው የተጨዋቾች ዝውውር 1 ቢሊዮን ዶላር ማውጣቷን ኤፒ ዘግቧል።በቅርቡ ስሙ የገነነው የሳኡዲ ፕሮሊግ በበርካታ የአውሮፖ ሊግ ታዋቂ ተጨዋቾች መዳረሻ እየሆነ መጥቷል።
ሳኡዲ አረቢያ እግር ኳስን ጨምሮ በጎልፍ፣ በቦክስ፣ ፎርሙላ ዋን ሬሲንግ እና በቴኒስ ላይ ኢንቨስት እያደረገች።ፕሮሊግ በተጠናቀቀው የዝወውር መስኮት ያለወጣው ወጭ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ካወጫው ወጭ ቀጥሎ በሁለተኛ ደረጃ የሚቀመጥ መሆኑን ሮይተርስን ጠቅሶ አል-ዐይን ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
የሳኡዲ አረቢያው ፕሮሊግ ለተጨዋቾች ግዥ 1 ቢሊዮን ዶላር ወጭ አደረገ።የዘንድሮው የተጨዋቾች የዝውውር መስኮት ሲዘጋ የሳኡዲ አረቢያው ፕሮሊግ 1 ቢሊዮን ዶላር ወጭ አውጥቷል።
አዲስ የእግር ኳስ መናኸሪያ መሆኗን ያስታወቀችው የነዳጅ ባለጸጋዋ ሳኡዲ አረቢያ ትናንት በባቃው የተጨዋቾች ዝውውር 1 ቢሊዮን ዶላር ማውጣቷን ኤፒ ዘግቧል።በቅርቡ ስሙ የገነነው የሳኡዲ ፕሮሊግ በበርካታ የአውሮፖ ሊግ ታዋቂ ተጨዋቾች መዳረሻ እየሆነ መጥቷል።
ሳኡዲ አረቢያ እግር ኳስን ጨምሮ በጎልፍ፣ በቦክስ፣ ፎርሙላ ዋን ሬሲንግ እና በቴኒስ ላይ ኢንቨስት እያደረገች።ፕሮሊግ በተጠናቀቀው የዝወውር መስኮት ያለወጣው ወጭ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ካወጫው ወጭ ቀጥሎ በሁለተኛ ደረጃ የሚቀመጥ መሆኑን ሮይተርስን ጠቅሶ አል-ዐይን ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
👍21👎2❤1
ዛሬ ምሽት በተካሄደው በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ውድድር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በግብፅ አቻው 1 ለ 0 ተሸንፏል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የ2023 አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ጨዋታ ከግብጽ አቻው ጋር አካሂዷል፡፡ሁለቱ ቡድኖች ጨዋታቸውን በካይሮ አየር ሃይል ስታዲየም ምሽት 1 ሰዓት ላይ አድርገዋል፡፡
ውጤቱን ተከትሎ የግብጽ ብሄራዊ ቡድን ምድቡን በበላይነት አጠናቋል።በአንጻሩ ዋልያዎቹ የማጣሪያ ውድድራቸውን በአራቱ ተሸንፈው አንድ አቻ በመውጣት እና አንድ ጨዋታ በማሸነፍ በአራት ነጥብ የምድቡን የመጨረሻ ደረጃ ይዘው አጠናቀዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የ2023 አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ጨዋታ ከግብጽ አቻው ጋር አካሂዷል፡፡ሁለቱ ቡድኖች ጨዋታቸውን በካይሮ አየር ሃይል ስታዲየም ምሽት 1 ሰዓት ላይ አድርገዋል፡፡
ውጤቱን ተከትሎ የግብጽ ብሄራዊ ቡድን ምድቡን በበላይነት አጠናቋል።በአንጻሩ ዋልያዎቹ የማጣሪያ ውድድራቸውን በአራቱ ተሸንፈው አንድ አቻ በመውጣት እና አንድ ጨዋታ በማሸነፍ በአራት ነጥብ የምድቡን የመጨረሻ ደረጃ ይዘው አጠናቀዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
👎50👍23❤2🔥1
የግል ንግድ ባንኮች በገጠማቸው የጥሬ ገንዘብ እጥረት መክፈል ወደማቆም መድረሳቸውን ቢናገሩም ፤ የብሔራዊ ባንክ ም/ል ገዢ ችግሩ የለም ብለዋል
👉🏼 ባለሃብቶች ወደ ኋላቀር የካዝና ቁጠባ ዘዴ መመለሳቸዉን ተናግረዋል
የግል ንግድ ባንኮች የገጠማቸው የጥሬ ገንዘብ እጥረት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ቀጥሎ ለደንበኞቻቸው መክፈል የማይችሉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ዋዜማ ያሰባሰበችው መረጃ ያመለክታል። የጥሬ ገንዘብ ዕጥረቱን ተከትሎ፣ ባለሀብቶችና ነጋዴዎች ጥሬ ገንዘብ ወደ ባንክ ከማስገባት ይልቅ ሌሎች አማራጮችን ለመጠቀም እንደተገደዱ ነግረውናል ስትል ዋዜማ ራዲዮ ዘግባለች። ያነጋገርናቸው ነጋደዎች እና ባለሀብቶች፣ ገንዘባቸውን ቀስ በቀስ ከባንክ እያወጡ በግል ካዝናና ስውር ቦታዎች ማስቀመጥ መምረጣቸውን ይናገራሉ። የባለሀብቶቹ ስጋት በባንክ የተቀመጠ ገንዘባቸውን በፈለጉት ፍጥነት ለማግኘት በመቸገራቸውና የተለያዩ ገደቦች ስለተጣለባቸው ነው።
አንዳንድ ባንኮች ባለፉት ወራት አልፎ አልፎ ለተመረጡ ደንበኞች ሲፈቅዱ የነበረውን ከባንክ ወደ ባንክ የገንዘብ ዝውውር (RTGS) አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ወደማቆም እየመጡ መሆናቸው የባንክ ምንጮቻችን ጠቁመዋል፡፡ ዋዜማ ከነጋገረቻቸው የግል ንግድ ባንክ የሥራ ኃላፊዎች አንዱ “ዛሬ አንድ ሚሊየን ብር አስገብቶ ነገ ሲመጣ የሚፈልገውን ያክል ወጪ እንደማልሰጠው እያወቀ እንዴት ይመጣል?” ሲሉ የነጋዴዎች ጥሬ ገንዘብ መከዘን ገንዘባቸውን በፈለጉበት ጊዜ ማንቀሳቀስ አለመቻል መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ዋዜማ ያጋገረቻቸው የተለያዩ ባንኮች የቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጆች፣ የሚመሩትን ቅርንጫፍ ከ50 ሺህ ብር ባነሰ አዳሪ ገንዘብ ዕለታዊ ሂሳባቸውን የሚዘጉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ጠቁመዋል፡፡ የባንክ ቀርንጫፎች ለደንበኞቻቸው የሚከፍሉት ገንዘብ ሲያጥራቸው ከዋና መስሪያ ቤት (ትሬዠሪ) ገንዘብ እንዲላክላቸው በስፋት ጥያቄ እያቀረቡ ቢሆንም፣ ዋና መስሪያ ቤት ቋት ላይ እጥረቱ ስለበረታ የጠየቁትን ያክል ማግኘት አንዳልቻሉ ተናግረዋል፡፡
በተለይ ለተርታ ለደንበኞቻቸው የሚፈቅዱት ዕለታዊ ወጭ አንዳንዶ ከ10 ሺሕ ብር ያልበለጠ ሲሆን፣ ከፍተኛ የደንበኞች ቅሬታ እያስተገዱ ነው፡፡ በብሔራዊ ባንክ ሕግ መሰረት አንድ የባንክ ደንበኛ በቀን እስከ 50 ሺሕ ብር ጥሬ ገንዘብ የማውጣት መብት አለው፡፡ ከተከሰተ ወራት ያስቆጠረው የጥሬ ገንዘብ እጥረት አሁን ላይ በተለይ የግል ባንኮችን በእጅጉ እየፈተነ መሆኑን ዋዜማ ከተለያዩ የባንክ ምንጮቿ ሰምታለች፡፡
ቀድም ሲል በተለይ አነስተኛ አቅም ካለቸው ባንኮች መካከል የሚመደቡት ላይ በርትቶ የነበረው የጥሬ ገንዘብ እጥረት፣ አሁን ላይ አንጋፋ የግል ንግድ ባንኮች ላይም መበርታቱን ዋዜማ ከራሳቸው ከባንኮቹ ምንጮቿ አረጋግጣለች። ችግሩ ከበረታባቸው የግል ባንኮች መካከል አንዱ በተለይ የነዳጅ ክፍያ በቴሌ ብር አማካኝነት እንዲሰበሰብ መወሰኑን ተከትሎ፣ በየቀኑ ከነዳጅ አዳዮች የሚያገኘውን በሚሊየን የሚቆጠር የጥሬ ገንዘብ ገቢ ማጣቱ ችግር ውስጥ እንዳስገባው የባንኩ ምንጮች ነገረውናል፡፡ የግል ንግድ ባንኮች በገጠማቸው የመከፈል አቅም ውስንነት በርካታ የባንክ ደንበኞቻቸው የሚያንቀሳቅሱትን ገንዘብ ወደ መንግሥታዊው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ማዞራቸውን ከግል ባንኮች ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እስካሁን የጥሬ ገንዘብ እጥረት ውስጥ ካለመግባቱም በላይ ከዚህ ቀደሙ የተሻለ ጥሬ ገንዘብ በስፋት እየሰበሰበ ነው፡፡ ባንኩ ደንበኞች ገንዘባቸውን በሚፈልጉበት ጊዜ ብሔራዊ ባንክ ባስቀመጠው ጣሪያ ልክ፣ ያለገደብ ጥሬ ገንዘብ ማውጣት የሚችሉበት ብቸኛ ባንክ ሆኗል፡፡ ዋዜማ በባንኮች በኩል ያገኘችውን የጥሬ ገንዘብ እጥረት ችግር የባንኮች ተቆጣጣሪ አካል እንዴት እንደሚመለከተው የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥን ፍቃዱ ደግፌን የጠየቀች ሲሆን፣ ባንኮች በሚሉት ደረጃ እጥረት መኖሩን የባንኩ መረጃ እንደማያመላክት ነግረዋታል፡፡
ፍቃዱ ጉዳዩን “እኔ ባለኝ መረጃ ባንኮች ላይ በሚባለው ደረጃ የጥሬ ገንዘብ እጥረት (ሊኪዩዲቲ) የለም” ብለዋል፡፡ ባንኮች ከነዳጅ አዳዮችና ከሌሎች የተለያዩ ደንበኞች በየእለቱ ያገኙት የነበረውን የጥሬ ገንዘብ ገቢ በግዴታ ወደ ቴሌ ብር ስርዓት መቀየሩን ተክትሎ ገጥሞናል ያሉትን ችግር በተመለከተ፣ ምክትል ገዥው ለዋዜማ በሰጧት አስተያየት፣ “እጥረት አለብን ካሉ ተወዳድሮ መሰብሰብ ነው የሚከለክል ሕግ የለም” በማለት ገልጸውታል፡፡
@Yenetube @Fikerassefa
👉🏼 ባለሃብቶች ወደ ኋላቀር የካዝና ቁጠባ ዘዴ መመለሳቸዉን ተናግረዋል
የግል ንግድ ባንኮች የገጠማቸው የጥሬ ገንዘብ እጥረት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ቀጥሎ ለደንበኞቻቸው መክፈል የማይችሉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ዋዜማ ያሰባሰበችው መረጃ ያመለክታል። የጥሬ ገንዘብ ዕጥረቱን ተከትሎ፣ ባለሀብቶችና ነጋዴዎች ጥሬ ገንዘብ ወደ ባንክ ከማስገባት ይልቅ ሌሎች አማራጮችን ለመጠቀም እንደተገደዱ ነግረውናል ስትል ዋዜማ ራዲዮ ዘግባለች። ያነጋገርናቸው ነጋደዎች እና ባለሀብቶች፣ ገንዘባቸውን ቀስ በቀስ ከባንክ እያወጡ በግል ካዝናና ስውር ቦታዎች ማስቀመጥ መምረጣቸውን ይናገራሉ። የባለሀብቶቹ ስጋት በባንክ የተቀመጠ ገንዘባቸውን በፈለጉት ፍጥነት ለማግኘት በመቸገራቸውና የተለያዩ ገደቦች ስለተጣለባቸው ነው።
አንዳንድ ባንኮች ባለፉት ወራት አልፎ አልፎ ለተመረጡ ደንበኞች ሲፈቅዱ የነበረውን ከባንክ ወደ ባንክ የገንዘብ ዝውውር (RTGS) አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ወደማቆም እየመጡ መሆናቸው የባንክ ምንጮቻችን ጠቁመዋል፡፡ ዋዜማ ከነጋገረቻቸው የግል ንግድ ባንክ የሥራ ኃላፊዎች አንዱ “ዛሬ አንድ ሚሊየን ብር አስገብቶ ነገ ሲመጣ የሚፈልገውን ያክል ወጪ እንደማልሰጠው እያወቀ እንዴት ይመጣል?” ሲሉ የነጋዴዎች ጥሬ ገንዘብ መከዘን ገንዘባቸውን በፈለጉበት ጊዜ ማንቀሳቀስ አለመቻል መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ዋዜማ ያጋገረቻቸው የተለያዩ ባንኮች የቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጆች፣ የሚመሩትን ቅርንጫፍ ከ50 ሺህ ብር ባነሰ አዳሪ ገንዘብ ዕለታዊ ሂሳባቸውን የሚዘጉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ጠቁመዋል፡፡ የባንክ ቀርንጫፎች ለደንበኞቻቸው የሚከፍሉት ገንዘብ ሲያጥራቸው ከዋና መስሪያ ቤት (ትሬዠሪ) ገንዘብ እንዲላክላቸው በስፋት ጥያቄ እያቀረቡ ቢሆንም፣ ዋና መስሪያ ቤት ቋት ላይ እጥረቱ ስለበረታ የጠየቁትን ያክል ማግኘት አንዳልቻሉ ተናግረዋል፡፡
በተለይ ለተርታ ለደንበኞቻቸው የሚፈቅዱት ዕለታዊ ወጭ አንዳንዶ ከ10 ሺሕ ብር ያልበለጠ ሲሆን፣ ከፍተኛ የደንበኞች ቅሬታ እያስተገዱ ነው፡፡ በብሔራዊ ባንክ ሕግ መሰረት አንድ የባንክ ደንበኛ በቀን እስከ 50 ሺሕ ብር ጥሬ ገንዘብ የማውጣት መብት አለው፡፡ ከተከሰተ ወራት ያስቆጠረው የጥሬ ገንዘብ እጥረት አሁን ላይ በተለይ የግል ባንኮችን በእጅጉ እየፈተነ መሆኑን ዋዜማ ከተለያዩ የባንክ ምንጮቿ ሰምታለች፡፡
ቀድም ሲል በተለይ አነስተኛ አቅም ካለቸው ባንኮች መካከል የሚመደቡት ላይ በርትቶ የነበረው የጥሬ ገንዘብ እጥረት፣ አሁን ላይ አንጋፋ የግል ንግድ ባንኮች ላይም መበርታቱን ዋዜማ ከራሳቸው ከባንኮቹ ምንጮቿ አረጋግጣለች። ችግሩ ከበረታባቸው የግል ባንኮች መካከል አንዱ በተለይ የነዳጅ ክፍያ በቴሌ ብር አማካኝነት እንዲሰበሰብ መወሰኑን ተከትሎ፣ በየቀኑ ከነዳጅ አዳዮች የሚያገኘውን በሚሊየን የሚቆጠር የጥሬ ገንዘብ ገቢ ማጣቱ ችግር ውስጥ እንዳስገባው የባንኩ ምንጮች ነገረውናል፡፡ የግል ንግድ ባንኮች በገጠማቸው የመከፈል አቅም ውስንነት በርካታ የባንክ ደንበኞቻቸው የሚያንቀሳቅሱትን ገንዘብ ወደ መንግሥታዊው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ማዞራቸውን ከግል ባንኮች ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እስካሁን የጥሬ ገንዘብ እጥረት ውስጥ ካለመግባቱም በላይ ከዚህ ቀደሙ የተሻለ ጥሬ ገንዘብ በስፋት እየሰበሰበ ነው፡፡ ባንኩ ደንበኞች ገንዘባቸውን በሚፈልጉበት ጊዜ ብሔራዊ ባንክ ባስቀመጠው ጣሪያ ልክ፣ ያለገደብ ጥሬ ገንዘብ ማውጣት የሚችሉበት ብቸኛ ባንክ ሆኗል፡፡ ዋዜማ በባንኮች በኩል ያገኘችውን የጥሬ ገንዘብ እጥረት ችግር የባንኮች ተቆጣጣሪ አካል እንዴት እንደሚመለከተው የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥን ፍቃዱ ደግፌን የጠየቀች ሲሆን፣ ባንኮች በሚሉት ደረጃ እጥረት መኖሩን የባንኩ መረጃ እንደማያመላክት ነግረዋታል፡፡
ፍቃዱ ጉዳዩን “እኔ ባለኝ መረጃ ባንኮች ላይ በሚባለው ደረጃ የጥሬ ገንዘብ እጥረት (ሊኪዩዲቲ) የለም” ብለዋል፡፡ ባንኮች ከነዳጅ አዳዮችና ከሌሎች የተለያዩ ደንበኞች በየእለቱ ያገኙት የነበረውን የጥሬ ገንዘብ ገቢ በግዴታ ወደ ቴሌ ብር ስርዓት መቀየሩን ተክትሎ ገጥሞናል ያሉትን ችግር በተመለከተ፣ ምክትል ገዥው ለዋዜማ በሰጧት አስተያየት፣ “እጥረት አለብን ካሉ ተወዳድሮ መሰብሰብ ነው የሚከለክል ሕግ የለም” በማለት ገልጸውታል፡፡
@Yenetube @Fikerassefa
👍55❤5
አማራ ባንክ ከፋይናንሻል ቴክኖሎጂ አቅራቢዎች እና ኦኘሬተሮች ጋር ያለዉን ግንኙነት በማጠናከር የተለያዩ ዲጅታል ባንኪንግ ኘሮግራሞችን ለደንበኞቹ ለማቅረብ እቅድ ይዤ እየሰራሁ ነው አለ።
ባንኩ በዲጅታል የፋይናንስ እድገት ላይ አተኩሮ እየሰራ መሆኑን የተናገሩት የባንኩ ምክትል ቺፍ አቶ በፍቃዱ ሸሪፍ አዳዲስ ከቴክኖሎጂን ከሚያቀርቡ ተቋማት ጋር በጋራ ለመስራት በእቅድ ላይ ነን ብለዋል።ባንኩ ባሳለፍነው በጀት ዓመት ከቴክኖሎጂ አቅራቢዎች(ፊንቴኮች)ጋር በመስራት የተለያዩ የዲጂታል ባንኪንግ ስርአትን ለደንበኞቼ አቅርቤአለሁ ብሏል።
በዚህም መሰረት ባንኩ ለ 50 ሺህ ደንበኞች በአጭር ጊዜ የክፍያ ካርዶችን ማቅረቡን የተናገረ ሲሆን ለማንኛውም የቢል ክፍያ የቴክኖሎጂ ትስስር በመፍጠር ክፍያዎችን በሞባይል ባንኪንግ እንዲከፍሉ ማስቻሉን ተናግሯል።
የትምህርት ቤት ክፍያ አባስኩል ፔይ የተሰኘ አገልግሎት፣ የሆቴል መያዝ፣ የሜትር ታክሲ ክፍያን ደንበኞች በሞባይል ባንኪንግ መፈፀም እንዲችሉ ማድረግ፣ የኦንላይን ግብይት፣ የኪው አር (QR) የተሰኘ የመክፈያ አማራጭ ለንግድ ተቋማት እንዲሁም ሌሎች አገልግሎቶችን ለደንበኞቹ ማቅረቡን ከባንኩ ሰምተናል።
ባንኩ በ2016 እሰራባቸዋለው ብሎ ካቀዳቸው መካከል የወኪል(ኤጀንሲ) ባንኪንግ መጀመር የሚለው ይገኝበታል።አማራ ባንክ ኦላይን ባንክ ተጠቃሚዎቼ 200 ሺህ ተጠግተዋል ያለ ሲሆን 1.3 ሚሊዮን ደንበኞች ማፍራት እንደቻለም ጠቅሷል፡፡
[Sheger FM]
@YeneTube @FikerAssefa
ባንኩ በዲጅታል የፋይናንስ እድገት ላይ አተኩሮ እየሰራ መሆኑን የተናገሩት የባንኩ ምክትል ቺፍ አቶ በፍቃዱ ሸሪፍ አዳዲስ ከቴክኖሎጂን ከሚያቀርቡ ተቋማት ጋር በጋራ ለመስራት በእቅድ ላይ ነን ብለዋል።ባንኩ ባሳለፍነው በጀት ዓመት ከቴክኖሎጂ አቅራቢዎች(ፊንቴኮች)ጋር በመስራት የተለያዩ የዲጂታል ባንኪንግ ስርአትን ለደንበኞቼ አቅርቤአለሁ ብሏል።
በዚህም መሰረት ባንኩ ለ 50 ሺህ ደንበኞች በአጭር ጊዜ የክፍያ ካርዶችን ማቅረቡን የተናገረ ሲሆን ለማንኛውም የቢል ክፍያ የቴክኖሎጂ ትስስር በመፍጠር ክፍያዎችን በሞባይል ባንኪንግ እንዲከፍሉ ማስቻሉን ተናግሯል።
የትምህርት ቤት ክፍያ አባስኩል ፔይ የተሰኘ አገልግሎት፣ የሆቴል መያዝ፣ የሜትር ታክሲ ክፍያን ደንበኞች በሞባይል ባንኪንግ መፈፀም እንዲችሉ ማድረግ፣ የኦንላይን ግብይት፣ የኪው አር (QR) የተሰኘ የመክፈያ አማራጭ ለንግድ ተቋማት እንዲሁም ሌሎች አገልግሎቶችን ለደንበኞቹ ማቅረቡን ከባንኩ ሰምተናል።
ባንኩ በ2016 እሰራባቸዋለው ብሎ ካቀዳቸው መካከል የወኪል(ኤጀንሲ) ባንኪንግ መጀመር የሚለው ይገኝበታል።አማራ ባንክ ኦላይን ባንክ ተጠቃሚዎቼ 200 ሺህ ተጠግተዋል ያለ ሲሆን 1.3 ሚሊዮን ደንበኞች ማፍራት እንደቻለም ጠቅሷል፡፡
[Sheger FM]
@YeneTube @FikerAssefa
👍32❤3
በሞሮኮ በርዕደ መሬት ሳቢያ ቢያንስ 632 ሰዎች ሞቱ!
በሞሮኮ በመሬት መንቀጥቀጥ ሳቢያ ቢያንስ 632 ሰዎች ሞቱ።የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳለው በ6.8 የተለካው የመሬት መንቀጥቀጥ ከፍተኛ ጉዳት አስከትሏል።
በዋነኛነት የመሬት መንቀጥቀጡ የተሰማው በአትላስ ተራራ አካባቢ ነው።ይህም ከማራኬሽ በደቡብ ምዕራብ 71 ኪሎ ሜትር ርቆ ይገኛል። ጥልቀቱም 18.5 ኪሎ ሜትር ነው።
በማራኬሽና በሌሎችም ደቡባዊ አካባቢዎች ሰዎች መሞታቸው ተገልጿል።አል-ሀውዝ፣ ማራኬሽ፣ ኦራዛቴ፣ አዚል፣ ክሪቾዋ እና ታራውዳንት በተባሉት አካባቢዎች ነው ሰዎች የሞቱት።በመሬት መንቀጥቀጡ ሕንጻዎችና ጎዳናዎች ሲጎዱ የሚያሳዩ ቪድዮዎች ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ወጥተዋል።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
በሞሮኮ በመሬት መንቀጥቀጥ ሳቢያ ቢያንስ 632 ሰዎች ሞቱ።የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳለው በ6.8 የተለካው የመሬት መንቀጥቀጥ ከፍተኛ ጉዳት አስከትሏል።
በዋነኛነት የመሬት መንቀጥቀጡ የተሰማው በአትላስ ተራራ አካባቢ ነው።ይህም ከማራኬሽ በደቡብ ምዕራብ 71 ኪሎ ሜትር ርቆ ይገኛል። ጥልቀቱም 18.5 ኪሎ ሜትር ነው።
በማራኬሽና በሌሎችም ደቡባዊ አካባቢዎች ሰዎች መሞታቸው ተገልጿል።አል-ሀውዝ፣ ማራኬሽ፣ ኦራዛቴ፣ አዚል፣ ክሪቾዋ እና ታራውዳንት በተባሉት አካባቢዎች ነው ሰዎች የሞቱት።በመሬት መንቀጥቀጡ ሕንጻዎችና ጎዳናዎች ሲጎዱ የሚያሳዩ ቪድዮዎች ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ወጥተዋል።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
👍19❤2
በጋምቤላ ክልል 13 አመራሮች ከኃላፊነታቸው ተነሱ!
ባለፈው ተከስቶ የነበረውን የፀጥታ ችግር ምክንያት በማድረግ በተካሄደ ግምገማ 13 አመራሮች ከኃላፊነታቸው መነሳታቸውን የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኡሞድ ኡጁሉ አስታወቁ፡፡እንዲሁም 55 አመራሮች አዲስና የሽግሽግ ሹመት መሰጠቱን ነው አቶ ኡሞድ ያስታወቁት፡፡
ሙሉ በሙሉ ከኃላፊነታቸው የተነሱት አመራሮች በብልሹ አሰራር፣ በአፈፃፀማቸውና በፀጥታ ችግር ክፍተት የታየባቸው ናቸው ማለታቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡አዲስና በሽግሽግ ወደ ሹመት የመጡ አመራሮች የክልሉን ህዝብ የሰላምና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ይፈታሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል፡፡
በክልል ማዕከል የተጀመረው አመራሩን የማጥራት ተግባር በቀጣይ በዞንና በወረዳ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡ህዝቡ ለክልሉ ሰላምና ልማት ከዚህ በፊት ሲያደርግ እንደነበረው ሁሉ አሁንም ከመንግሥት ጎን በመሆን የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
ባለፈው ተከስቶ የነበረውን የፀጥታ ችግር ምክንያት በማድረግ በተካሄደ ግምገማ 13 አመራሮች ከኃላፊነታቸው መነሳታቸውን የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኡሞድ ኡጁሉ አስታወቁ፡፡እንዲሁም 55 አመራሮች አዲስና የሽግሽግ ሹመት መሰጠቱን ነው አቶ ኡሞድ ያስታወቁት፡፡
ሙሉ በሙሉ ከኃላፊነታቸው የተነሱት አመራሮች በብልሹ አሰራር፣ በአፈፃፀማቸውና በፀጥታ ችግር ክፍተት የታየባቸው ናቸው ማለታቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡አዲስና በሽግሽግ ወደ ሹመት የመጡ አመራሮች የክልሉን ህዝብ የሰላምና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ይፈታሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል፡፡
በክልል ማዕከል የተጀመረው አመራሩን የማጥራት ተግባር በቀጣይ በዞንና በወረዳ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡ህዝቡ ለክልሉ ሰላምና ልማት ከዚህ በፊት ሲያደርግ እንደነበረው ሁሉ አሁንም ከመንግሥት ጎን በመሆን የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
👍16❤3
በሞሮኮ የመሬት መንቀጥቀጥ ሟቾች ቁጥር ከ1000 አልፈ!
ያልተለመደና እጅግ ክፉኛ የተባለው የሞሮኮ ርዕደ መሬት አርብ ምሽት ተከስቶ ከ1 ሽህ በላይ ሰዎችን ህይወት መቅጠፉ ተነግሯል።አደጋው በታሪካዊቷ ማራካሽ ከተማ ጥንታዊ ህንጻዎችን ዶግ አመድ ማድረጉ ታውቋል።
እስካሁን ድረስ የርዕደ መሬቱ ሙሉ የሟቾች ቁጥር ያልታወቀ ሲሆን፤ በአደጋው ክፉኛ በተጎዱ አካባቢዎች የነፍስ አድን ሰራተኞች መድረስ አለመቻላቸውን አሶሼትድ ፕረስ ዘግቧል። 6.8 ሬክተር ስኬል የተመዘገበው የመሬት መንቀጥቀጥ በሞሮኮ ከ120 ዓመታት በኋላ በእጅጉ የከፋ ነው ተብሏል።
@YeneTube@FikerAssefa
ያልተለመደና እጅግ ክፉኛ የተባለው የሞሮኮ ርዕደ መሬት አርብ ምሽት ተከስቶ ከ1 ሽህ በላይ ሰዎችን ህይወት መቅጠፉ ተነግሯል።አደጋው በታሪካዊቷ ማራካሽ ከተማ ጥንታዊ ህንጻዎችን ዶግ አመድ ማድረጉ ታውቋል።
እስካሁን ድረስ የርዕደ መሬቱ ሙሉ የሟቾች ቁጥር ያልታወቀ ሲሆን፤ በአደጋው ክፉኛ በተጎዱ አካባቢዎች የነፍስ አድን ሰራተኞች መድረስ አለመቻላቸውን አሶሼትድ ፕረስ ዘግቧል። 6.8 ሬክተር ስኬል የተመዘገበው የመሬት መንቀጥቀጥ በሞሮኮ ከ120 ዓመታት በኋላ በእጅጉ የከፋ ነው ተብሏል።
@YeneTube@FikerAssefa
👍14❤3