የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ለጸጥታ አመራሮች ሹመት ሰጠ!
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ከነሐሴ 22 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ለተለያዩ ጸጥታ አመራሮች ሹመት ሰጥቷል፡፡
በዚህ መሰረትም ፡-
1. ኮሚሽነር ደስዬ ደጀን ወልዴ - የአብክመ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር
2. ኮሎኔል ግርማ ገሰሰ ገ/መስቀል- የአብክመ ሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ
3. ኮሚሽነር ሀብታሙ ሲሳይ ገዳሙ- የአብክመ ማረሚያ ቤቶች አገ/ኮሚሽን ኮሚሽነር
4. ዶ.ር እሸቱ የሱፍ አየለ - በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ
5. ደጀኔ ልመንህ በዛብህ - በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ
6. በሪሁን መንግሥቱ ከበደ - የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ
7. ዳኛው በለጠ ጎኔ - የአብክመ ሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ
8. ገደቤ ኃይሉ በላይ - የአብክመ ሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ
9. ኮሚሽነር ውበቱ አለነ - የፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የወንጀል ምርመራ ዘርፍ ኃላፊ
10. ኮማንደር አያልነህ ተስፋዬ - የፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሰው ኃይል አስተዳደር ዘርፍ ኃላፊ
11. ም/ኮሚሽነር ሰይድ አህመድ - የፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሎጀስቲክስ ዘርፍ ኃላፊ ሆነው መሾማቸውን አሚኮ ዘግቧል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ከነሐሴ 22 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ለተለያዩ ጸጥታ አመራሮች ሹመት ሰጥቷል፡፡
በዚህ መሰረትም ፡-
1. ኮሚሽነር ደስዬ ደጀን ወልዴ - የአብክመ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር
2. ኮሎኔል ግርማ ገሰሰ ገ/መስቀል- የአብክመ ሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ
3. ኮሚሽነር ሀብታሙ ሲሳይ ገዳሙ- የአብክመ ማረሚያ ቤቶች አገ/ኮሚሽን ኮሚሽነር
4. ዶ.ር እሸቱ የሱፍ አየለ - በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ
5. ደጀኔ ልመንህ በዛብህ - በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ
6. በሪሁን መንግሥቱ ከበደ - የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ
7. ዳኛው በለጠ ጎኔ - የአብክመ ሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ
8. ገደቤ ኃይሉ በላይ - የአብክመ ሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ
9. ኮሚሽነር ውበቱ አለነ - የፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የወንጀል ምርመራ ዘርፍ ኃላፊ
10. ኮማንደር አያልነህ ተስፋዬ - የፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሰው ኃይል አስተዳደር ዘርፍ ኃላፊ
11. ም/ኮሚሽነር ሰይድ አህመድ - የፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የሎጀስቲክስ ዘርፍ ኃላፊ ሆነው መሾማቸውን አሚኮ ዘግቧል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
👎47👍36❤5
የሀዋሳ ከተማ ምክር ቤት በመጪው ሰኞ በሚያካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ በተሰናባቹ አቶ ጸጋዬ ቱኬ ምትክ አዲስ ከንቲባ ሊሾም ነው!
የሀዋሳ ከተማ ምክር ቤት በመጪው ሰኞ ነሐሴ 29፤ 2015 በሚያካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ የከተማዋን ከንቲባ ጨምሮ የካቢኔ አባላትን ሹመት ሊሰጥ ነው። የከተማዋ ምክር ቤት ሹመቶችን የሚሰጠው፤ የሲዳማ ክልል ካደረገው ግምገማ በኋላ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባን ጨምሮ ሌሎች አመራሮችም እንዲነሱ መወሰኑን ተከትሎ ነው።
የሲዳማ ክልል ከአንድ ሳምንት በፊት ካካሄደው የፓርቲ እና የመንግስት አፈጻጸም ግምገማ በኋላ፤ “ብልሹ አሰራር ፈጽመዋል” ያላቸውን 10 ከፍተኛ አመራሮችን ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ውሳኔ ማሳለፉን አስታውቆ ነበር።በዚህ ግምገማ ከስልጣናቸው እንዲነሱ ውሳኔ ከተላለፈባቸው ባለስልጣናት መካከል ሰባቱ በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ተመድበው የሚሰሩ ከፍተኛ አመራሮች መሆናቸውን “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ያገኘችው ዝርዝር ያመለክታል።
ከእነዚህ የከተማይቱ አስተዳደር አመራሮች ውስጥ በስልጣን ከፍተኛውን ቦታ የያዙት፤ ለሶስት ዓመታት ገደማ ሀዋሳን በከንቲባነት የመሩት አቶ ጸጋዬ ቱኬ ናቸው።አቶ ጸጋዬ እና ሌሎች ስድስት የካቢኔያቸው አባላት ከስልጣን ከተነሱ በኋላ ባሉት ሳምንታት፤ የከተማዋን የስራ እንቅስቃሴ ሲመሩ የቆዩት የሀዋሳ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ካሱ አሩሳ ናቸው ተብሏል።
@YeneTube @FikerAssefa
የሀዋሳ ከተማ ምክር ቤት በመጪው ሰኞ ነሐሴ 29፤ 2015 በሚያካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ የከተማዋን ከንቲባ ጨምሮ የካቢኔ አባላትን ሹመት ሊሰጥ ነው። የከተማዋ ምክር ቤት ሹመቶችን የሚሰጠው፤ የሲዳማ ክልል ካደረገው ግምገማ በኋላ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባን ጨምሮ ሌሎች አመራሮችም እንዲነሱ መወሰኑን ተከትሎ ነው።
የሲዳማ ክልል ከአንድ ሳምንት በፊት ካካሄደው የፓርቲ እና የመንግስት አፈጻጸም ግምገማ በኋላ፤ “ብልሹ አሰራር ፈጽመዋል” ያላቸውን 10 ከፍተኛ አመራሮችን ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ውሳኔ ማሳለፉን አስታውቆ ነበር።በዚህ ግምገማ ከስልጣናቸው እንዲነሱ ውሳኔ ከተላለፈባቸው ባለስልጣናት መካከል ሰባቱ በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ተመድበው የሚሰሩ ከፍተኛ አመራሮች መሆናቸውን “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ያገኘችው ዝርዝር ያመለክታል።
ከእነዚህ የከተማይቱ አስተዳደር አመራሮች ውስጥ በስልጣን ከፍተኛውን ቦታ የያዙት፤ ለሶስት ዓመታት ገደማ ሀዋሳን በከንቲባነት የመሩት አቶ ጸጋዬ ቱኬ ናቸው።አቶ ጸጋዬ እና ሌሎች ስድስት የካቢኔያቸው አባላት ከስልጣን ከተነሱ በኋላ ባሉት ሳምንታት፤ የከተማዋን የስራ እንቅስቃሴ ሲመሩ የቆዩት የሀዋሳ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ካሱ አሩሳ ናቸው ተብሏል።
@YeneTube @FikerAssefa
👍32❤10👎2
የአይደር ሪፈራል ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ17 ወራት ዉዝፍ የሰራተኞች ደሞዝ ክፍያ እዳ እንዳለበት ተነገረ!
በመቐለ ከተማ የሚገኘዉ አይደር ሪፈራል ስፔሻላይዝድ ሆፒራል ከፍተኛ የበጀት እጥረት እንዳለበት የሆስፒታሉ ቺፍ ክሊኒካል ዳይሬክተር ዶ/ር አብርሃ ገብረእግዚአብሔር ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። አይደር ሪፈራል ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ጦርነቱ በነበረባቸዉ ጊዚያት ለሰራተኞቹ ያልከፈለዉ ዉዝፍ የ 17ወራት የደሞዝ ክፍያ እዳ እንዳለበትም ዶ/ር አብርሃ ገልጸዋል።
ለ 2016 በጀት አመት ለሆስፒታሉ የመደበዉ የገንዘብ መጠንም እስከ ቀጣዩ አመት የሚያዚያ ወር ብቻ የሚበቃዉ ነዉ ብለዋል። ሆስፒታሉ ባለበት እዳ ላይ በቀጣይ አመት የበጀት እጥረት ስጋት ተደቅኖበታልም ሲሉ ገልጸዋል።
ሆስፒታሉ በጦርነት ወቅት የሰራተኞች ደሞዝ ክፍያ በማቋረጡ ባለሙያዎች ካለ ክፍያ አገልግሎት ሲሰጡ መቆየታቸውን አስታዉሰዋል። ከሰላም ስምምነቱ በኋላም ቢሆን ይህን የሚያካክስ ሁኔታ አልተፈጠልንም ሲሉ ክሊኒካል ዳይሬክተሩ ለጣቢያችን ገልጸዋል። ለአብነትም ሲሉ ለሰራተኞቹ ደሞዝ እና የስራ ማስኬጃ ወጪዎች ከ 2012 በጀት አመት ከተላለፈዉ 50 በመቶ የቀነሰ በጀት ለቀጣዩ አመት ተለቋል ነዉ ያሉት።
የደሞዝ ክፍያዎችን በሚመለከትም በየጊዜው ከሰራተኞቹ የፍርድቤት መጥሪያ ለሆስፒታሉ እንደሚደርሰዉ ዶ/ር አብርሃ ጠቁመዋል። ሆስፒታሉ በዚህ ልክ አጋጥሞታል የተባለዉን የበጀት እጥረት በሚመለከት ለፌደራል መንግስት ጥያቄ አቅርበዉ እንደሆነ ጣቢያችን ጠይቋል።
ክሊኒካል ዳይሬክተሩ በምላሻቸዉ ለጤና ሚኒስቴር እና የትምህርት ሚኒስቴር ጥያቄ ማቅረባቸውን ገልጸዉ ፤ "እናግዛችኋለን ከሚል ምላሽ ዉጪ ተጨባጭ እርዳታ አላገኘንም" ብለዋል። ሆስፒታሉ ከፌዴራል መንግስት ፣ የትምህርት ሚኒስቴር እና ጤና ሚኒስቴር አስተዳደራዊ ፣ የገንዘብ እና የህክምና አገልግሎት መስጫ ግብዓቶች ድጋፍ ይሻል ሲሉ የአይደር ሪፈራል ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቺፍ ክሊኒካል ዳይሬክተር ዶ/ር አብርሃ ገብረእግዚአብሔር ጨምረዉ ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።
Via Bisrat FM
@YeneTube @FikerAssefa
በመቐለ ከተማ የሚገኘዉ አይደር ሪፈራል ስፔሻላይዝድ ሆፒራል ከፍተኛ የበጀት እጥረት እንዳለበት የሆስፒታሉ ቺፍ ክሊኒካል ዳይሬክተር ዶ/ር አብርሃ ገብረእግዚአብሔር ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። አይደር ሪፈራል ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ጦርነቱ በነበረባቸዉ ጊዚያት ለሰራተኞቹ ያልከፈለዉ ዉዝፍ የ 17ወራት የደሞዝ ክፍያ እዳ እንዳለበትም ዶ/ር አብርሃ ገልጸዋል።
ለ 2016 በጀት አመት ለሆስፒታሉ የመደበዉ የገንዘብ መጠንም እስከ ቀጣዩ አመት የሚያዚያ ወር ብቻ የሚበቃዉ ነዉ ብለዋል። ሆስፒታሉ ባለበት እዳ ላይ በቀጣይ አመት የበጀት እጥረት ስጋት ተደቅኖበታልም ሲሉ ገልጸዋል።
ሆስፒታሉ በጦርነት ወቅት የሰራተኞች ደሞዝ ክፍያ በማቋረጡ ባለሙያዎች ካለ ክፍያ አገልግሎት ሲሰጡ መቆየታቸውን አስታዉሰዋል። ከሰላም ስምምነቱ በኋላም ቢሆን ይህን የሚያካክስ ሁኔታ አልተፈጠልንም ሲሉ ክሊኒካል ዳይሬክተሩ ለጣቢያችን ገልጸዋል። ለአብነትም ሲሉ ለሰራተኞቹ ደሞዝ እና የስራ ማስኬጃ ወጪዎች ከ 2012 በጀት አመት ከተላለፈዉ 50 በመቶ የቀነሰ በጀት ለቀጣዩ አመት ተለቋል ነዉ ያሉት።
የደሞዝ ክፍያዎችን በሚመለከትም በየጊዜው ከሰራተኞቹ የፍርድቤት መጥሪያ ለሆስፒታሉ እንደሚደርሰዉ ዶ/ር አብርሃ ጠቁመዋል። ሆስፒታሉ በዚህ ልክ አጋጥሞታል የተባለዉን የበጀት እጥረት በሚመለከት ለፌደራል መንግስት ጥያቄ አቅርበዉ እንደሆነ ጣቢያችን ጠይቋል።
ክሊኒካል ዳይሬክተሩ በምላሻቸዉ ለጤና ሚኒስቴር እና የትምህርት ሚኒስቴር ጥያቄ ማቅረባቸውን ገልጸዉ ፤ "እናግዛችኋለን ከሚል ምላሽ ዉጪ ተጨባጭ እርዳታ አላገኘንም" ብለዋል። ሆስፒታሉ ከፌዴራል መንግስት ፣ የትምህርት ሚኒስቴር እና ጤና ሚኒስቴር አስተዳደራዊ ፣ የገንዘብ እና የህክምና አገልግሎት መስጫ ግብዓቶች ድጋፍ ይሻል ሲሉ የአይደር ሪፈራል ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቺፍ ክሊኒካል ዳይሬክተር ዶ/ር አብርሃ ገብረእግዚአብሔር ጨምረዉ ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።
Via Bisrat FM
@YeneTube @FikerAssefa
👍35❤6🔥2
የዛሬ ጨዋታዎች:-
ላይፕዢግ፣ሌጂያ ዋርሶ፣ ግሪሚዮንና ዲፌንሳ ጀስቲሳ የተመለከቱ የቤቲንግ መረጃዎች እና ግምቶች በቤትስኬት
ሊንኩን በመጫን በነጻ ያንብቡ👇👇
http://www.betsket.com/ላይፕዢግ፣ሌጂያ-ዋርሶ፣-ግሪሚዮንና-ዲፌ/
ሁል ጊዜ የሚለቀቁ መረጃዎችን በአንድ ላይ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ።👉 @betskett
ላይፕዢግ፣ሌጂያ ዋርሶ፣ ግሪሚዮንና ዲፌንሳ ጀስቲሳ የተመለከቱ የቤቲንግ መረጃዎች እና ግምቶች በቤትስኬት
ሊንኩን በመጫን በነጻ ያንብቡ👇👇
http://www.betsket.com/ላይፕዢግ፣ሌጂያ-ዋርሶ፣-ግሪሚዮንና-ዲፌ/
ሁል ጊዜ የሚለቀቁ መረጃዎችን በአንድ ላይ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ።👉 @betskett
👍7❤1🔥1
"በፀጥታና በሌሎች ችግሮች ፈተና ያልወሰዱ ከ18 ሺህ በላይ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለመፈተን ዝግጅት ተደርጓል"- የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት
በፀጥታና በሌሎች ችግሮች ፈተና ያልወሰዱ ከ18 ሺህ በላይ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለመፈተን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታወቀ።በጎንደር፣ በጋምቤላ፣ በተለያዩ ማረሚያ ቤቶች 17 ሺህ 753 ተማሪዎችና በውጭ ሀገራት 300 ተማሪዎች ይፈተናሉ።
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና ከሐምሌ 19 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በሁለት ዙሮች መሰጠቱ ይታወቃል።ሆኖም በአማራ ክልል እና በጋምቤላ ክልል ተፈጥሮ በነበረው የፀጥታ ችግር ምክንያት ሙሉ ለሙሉና በከፊል ፈተና ያልወሰዱ ተማሪዎች መኖራቸውን የአገልግሎቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ተፈራ ፈይሳ በተለይ ለኢዜአ ገልፀዋል።
በተለይም በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሦስት መፈተኛ ጣቢያዎች ሲፈተኑ ከነበሩ ተማሪዎች መካከል ከ16 ሺህ 580 በላይ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከሁለት እስከ ሦስት የትምህርት ዓይነቶችን ሳይፈተኑ መቅረታቸውን ገልፀዋል።በጋምቤላ ተፈጥሮ በነበረው ችግር ምክንያት ደግሞ ከ100 በላይ የማኅበራዊ ሳይንስና የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተናውን በከፊልና ሙሉ ለሙሉ አልወሰዱም ብለዋል።
በሕግ ጥላ ሥር በማረሚያ ቤቶች የሚገኙ 982 ተማሪዎችና በኢትዮጵያ ሥርዓተ-ትምህርት በውጭ ሀገራት የሚማሩ 300 ተማሪዎችን ጨምሮ በድምሩ ከ18 ሺህ በላይ በከፊልና ሙሉ በሙሉ ፈተና ያልወሰዱ መሆኑን ገልፀዋል።በመሆኑም በፀጥታ ችግር ያቋረጡትን፣ በማረሚያ ቤት የሚገኙና በውጭ ሀገራት የሚማሩ ተማሪዎች ፈተናውን እንዲወስዱ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ለዚህም የፈተና ህትመት፣ የሰው ኃይልና የበጀት ዝግጅት እየደረገ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከየአካባቢው አስተዳደሮች፣ የትምህርት ቢሮዎች፣ ከወላጆችና ከተማሪዎች ጋር ውይይቶች እየተደረጉ ነው ብለዋል።ተማሪዎች ስነ-ልቦናቸው ለፈተና ዝግጁ ሲሆን እንዲሁም አስተማማኝ የፀጥታ ሁኔታ መኖሩን ማረጋገጫ ሲገኝ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲፈተኑ አቅጣጫ መቀመጡንም ጠቁመዋል።
በውጭ ሀገራት በኢትዮጵያ ሥርዓተ-ትምህርት የሚማሩ 300 ተማሪዎችም ከዛሬ ነሐሴ 28 እስከ ጳጉሜ 2 ቀን 2015 ዓ.ም የሚፈተኑ ይሆናል።ለዚህም የፈተና ጣቢያ አስተባባሪዎች ከኢትዮጵያ ፈተናው ወደሚሰጥባቸው ሀገራት መጓዛቸውን ነው ያነሱት።በፀጥታና ሌሎች ችግሮች ፈተና ያልወሰዱ ተማሪዎች በአፋጣኝ የሚፈተኑበትና ውጤታቸው ሐምሌ ላይ ከተፈተኑ ሁሉም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ጋር ውጤታቸውን ይፋ ለማድረግ ታቅዷል ብለዋል።
Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
በፀጥታና በሌሎች ችግሮች ፈተና ያልወሰዱ ከ18 ሺህ በላይ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለመፈተን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታወቀ።በጎንደር፣ በጋምቤላ፣ በተለያዩ ማረሚያ ቤቶች 17 ሺህ 753 ተማሪዎችና በውጭ ሀገራት 300 ተማሪዎች ይፈተናሉ።
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና ከሐምሌ 19 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በሁለት ዙሮች መሰጠቱ ይታወቃል።ሆኖም በአማራ ክልል እና በጋምቤላ ክልል ተፈጥሮ በነበረው የፀጥታ ችግር ምክንያት ሙሉ ለሙሉና በከፊል ፈተና ያልወሰዱ ተማሪዎች መኖራቸውን የአገልግሎቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ተፈራ ፈይሳ በተለይ ለኢዜአ ገልፀዋል።
በተለይም በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሦስት መፈተኛ ጣቢያዎች ሲፈተኑ ከነበሩ ተማሪዎች መካከል ከ16 ሺህ 580 በላይ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከሁለት እስከ ሦስት የትምህርት ዓይነቶችን ሳይፈተኑ መቅረታቸውን ገልፀዋል።በጋምቤላ ተፈጥሮ በነበረው ችግር ምክንያት ደግሞ ከ100 በላይ የማኅበራዊ ሳይንስና የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተናውን በከፊልና ሙሉ ለሙሉ አልወሰዱም ብለዋል።
በሕግ ጥላ ሥር በማረሚያ ቤቶች የሚገኙ 982 ተማሪዎችና በኢትዮጵያ ሥርዓተ-ትምህርት በውጭ ሀገራት የሚማሩ 300 ተማሪዎችን ጨምሮ በድምሩ ከ18 ሺህ በላይ በከፊልና ሙሉ በሙሉ ፈተና ያልወሰዱ መሆኑን ገልፀዋል።በመሆኑም በፀጥታ ችግር ያቋረጡትን፣ በማረሚያ ቤት የሚገኙና በውጭ ሀገራት የሚማሩ ተማሪዎች ፈተናውን እንዲወስዱ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ለዚህም የፈተና ህትመት፣ የሰው ኃይልና የበጀት ዝግጅት እየደረገ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከየአካባቢው አስተዳደሮች፣ የትምህርት ቢሮዎች፣ ከወላጆችና ከተማሪዎች ጋር ውይይቶች እየተደረጉ ነው ብለዋል።ተማሪዎች ስነ-ልቦናቸው ለፈተና ዝግጁ ሲሆን እንዲሁም አስተማማኝ የፀጥታ ሁኔታ መኖሩን ማረጋገጫ ሲገኝ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲፈተኑ አቅጣጫ መቀመጡንም ጠቁመዋል።
በውጭ ሀገራት በኢትዮጵያ ሥርዓተ-ትምህርት የሚማሩ 300 ተማሪዎችም ከዛሬ ነሐሴ 28 እስከ ጳጉሜ 2 ቀን 2015 ዓ.ም የሚፈተኑ ይሆናል።ለዚህም የፈተና ጣቢያ አስተባባሪዎች ከኢትዮጵያ ፈተናው ወደሚሰጥባቸው ሀገራት መጓዛቸውን ነው ያነሱት።በፀጥታና ሌሎች ችግሮች ፈተና ያልወሰዱ ተማሪዎች በአፋጣኝ የሚፈተኑበትና ውጤታቸው ሐምሌ ላይ ከተፈተኑ ሁሉም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ጋር ውጤታቸውን ይፋ ለማድረግ ታቅዷል ብለዋል።
Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
👍43❤1
የባሕር ዳር ከተማ ሰላም በመሻሻሉ የተጣለው የሰዓት እላፊ ገደብ መሻሻሉ ተገለጸ፡፡
የባሕር ዳር ከተማ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ኮማንድ ፖስት በከተማው ላይ የነበረውን የመንቀሳቀስ የሰዓት ገደብ ከዛሬ ነሐሴ 28 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ምሽቱ 2:00 ድረስ እንዲሆን ማሻሻሉን አሚኮ ዘግቧል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የባሕር ዳር ከተማ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ኮማንድ ፖስት በከተማው ላይ የነበረውን የመንቀሳቀስ የሰዓት ገደብ ከዛሬ ነሐሴ 28 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ምሽቱ 2:00 ድረስ እንዲሆን ማሻሻሉን አሚኮ ዘግቧል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
👍19👎7❤4
አቶ መኩሪያ መርሻዬ በምክትል ከንቲባ ማእረግ የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሆኑ!
2ኛ ዙር 8 ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤውን በዛሬው እለት በማካሄድ ላይ ያለው የሐዋሳ ከተማ ምክር ቤት ለከንቲባነት በእጩነት የቀረቡትን አቶ መኩሪያ መርሻዬን ሹመት አፅድቋል።
የሲዳማ ክልል ከተማ ልማትና ካንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ ሆነው በማገልገል ላይ የነበሩት አቶ መኩሪያ መርሻዬ ቃለ መሐላ የፈፀሙ ሲሆን የካቢኔ አባላቶቻቸውን ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።
ላለፉት ሦሥት ዓመታት የሐዋሳ ከተማን ሲያስተዳድሩ የቆዩት እና በቅርቡ በሲዳማ ክልል ምክር ቤት የአፈፃፀም ግምገማ ወቅት ሲተቹ የቆዩት አቶ ፀጋዬ ቱኬ "ከተማ የሚለማው በቅብብሎሽ እንደመሆኑ በቀጣይ ለሚሰየሙ አካላት መልካም የስራ ጊዜ እንዲሆንላቸው ከወዲሁ እመኛለሁ" ሲሉ በፌስቡክ ገፃቸው አስፍረው ነበር።
Via Addis Zeybe
@YeneTube @FikerAssefa
2ኛ ዙር 8 ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤውን በዛሬው እለት በማካሄድ ላይ ያለው የሐዋሳ ከተማ ምክር ቤት ለከንቲባነት በእጩነት የቀረቡትን አቶ መኩሪያ መርሻዬን ሹመት አፅድቋል።
የሲዳማ ክልል ከተማ ልማትና ካንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ ሆነው በማገልገል ላይ የነበሩት አቶ መኩሪያ መርሻዬ ቃለ መሐላ የፈፀሙ ሲሆን የካቢኔ አባላቶቻቸውን ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።
ላለፉት ሦሥት ዓመታት የሐዋሳ ከተማን ሲያስተዳድሩ የቆዩት እና በቅርቡ በሲዳማ ክልል ምክር ቤት የአፈፃፀም ግምገማ ወቅት ሲተቹ የቆዩት አቶ ፀጋዬ ቱኬ "ከተማ የሚለማው በቅብብሎሽ እንደመሆኑ በቀጣይ ለሚሰየሙ አካላት መልካም የስራ ጊዜ እንዲሆንላቸው ከወዲሁ እመኛለሁ" ሲሉ በፌስቡክ ገፃቸው አስፍረው ነበር።
Via Addis Zeybe
@YeneTube @FikerAssefa
👍20❤1
በዩናይትድ ኪንግደም የሰውነት ክብደት ለመቀነስ የሚያስችል ዌጎቪ (Wegovy) የተባለ መድኃኒት ሊሰጥ ነው።
የአገሪቱ ብሔራዊ የጤና ተቋም ይህን መድኃኒት በተወሰነ መጠን ማስገባቱን ተከትሎ ለሕሙማን ሊታዘዝ እንደሚችል ተገልጿል።በመርፌ የሚሰጠው መድኃኒቱ በአገር አቀፍ ተቋሙ በኩል ወይም በግል ሕክምና መስጫዎችም ሊሰጥ ይችላል።በአገሪቱ በአሥር ሺዎች የሚቆጠሩ ሕሙማንን እንደሚረዳ ተገልጿል።
በዓለም የዚህ መድኃኒት እጥረት ስላለ ዋጋው መወደዱ ተዘግቧል።ጥናቶች እንደሚያሳዩት መርፌው ከ10% በላይ ክብደት ለመቀነስ ያስችላል። ይህ የሚሆነውም ሰዎች ምግብ በልተው እንደጠገቡ እንዲሰማቸው አድርጎ ምግብ እንዳይበሉ በማስቻል ነው።በአሜሪካና በሌሎች አገራት ታዋቂ ሰዎች ይህንን መርፌ ይወስዳሉ። ባለሙያዎች እንደሚሉት መድኃኒቱ ጤናማ አመጋገብና የአካል ብቃት እንቅስቃሴን አይተካም።
ሙከራ ሲደረግ መድኃኒቱን የወሰዱ ሰዎች መድኃኒቱን ሲያቆሙ ተመልሰው ክብደት ይጨምራሉ።በዩኬ በምን ያህል ዋጋ እንደሚሸጥ እስካሁን ባይታወቅም በመደበኛነት አራት መርፌ በ73.25 ዩሮ ሲሸጥ ቆይቷል።ተጠቃሚዎች በሳምንት አንዴ መርፌውን ይወስዳሉ።ይህንን መርፌ የሠራው የዴንማርክ ድርጅት ኖቮ ኖርዲስክ ሲሆን፣ ምርቱን በስፋት እስኪያጠናቅቅ ድረስ ዓለም አቀፍ ማከፋፈል ላይ ገደቦች እንደሚኖሩ አሳውቋል።
“ለተወሰነ ጊዜ ምርቱ እንደሚቀንስ እንጠብቃለን። የተወሰነ ምርት ግን በዩኬ ገበያ ይቀርባል” ሲል መግለጫ አውጥቷል።መርፌውን በከፍተኛ ሁኔታ የሚፈልጉ ሕሙማን ቅድሚያ እንዲያገኙ ለማድረግ ከጤና ባለሙያዎች ጋር በቅርበት እንደሚሠራም ገልጿል።ከመጠን ያለፈ ውፍረት ያላቸው ሰዎች ሕክምናውን እንዲያገኙም እንደሚሠራ አክሏል።በዩኬ መድኃኒቱን መውሰድ የሚችሉት ከመጠን ያለፈ ውፍረት ያላቸውና በሰውነት ክብደታቸው ምክንያት ለሕመም የተጋለጡ ሰዎች ናቸው።
ከተመጣጠነ ምግብና ከአካል ብቃት እንቅስቃሴ ጋር ተደምሮ መድኃኒቱ ለሁለት ዓመታት ይሰጣል።አሁን በዩኬ ሆስፒታሎች በኩል መርፌውን ማግኘት የሚችሉት ወደ 35,000 ሰዎች ሲሆኑ በቀጣይ ተጨማሪ ቁጥር ላላቸው ዜጎች እንደሚዳረስ ተገልጿል።የተቋሙ ቃል አቀባይ እንዳሉት የመድኃኒቱን ዓለም አቀፍ እጥረት ከግምት ውስጥ በማስገባት እንደሚሠሩ ገልጸዋል።ወደ 50,000 ሕሙማን መድኃኒቱን ማግኘት እንደሚችሉም ተናግረዋል።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
የአገሪቱ ብሔራዊ የጤና ተቋም ይህን መድኃኒት በተወሰነ መጠን ማስገባቱን ተከትሎ ለሕሙማን ሊታዘዝ እንደሚችል ተገልጿል።በመርፌ የሚሰጠው መድኃኒቱ በአገር አቀፍ ተቋሙ በኩል ወይም በግል ሕክምና መስጫዎችም ሊሰጥ ይችላል።በአገሪቱ በአሥር ሺዎች የሚቆጠሩ ሕሙማንን እንደሚረዳ ተገልጿል።
በዓለም የዚህ መድኃኒት እጥረት ስላለ ዋጋው መወደዱ ተዘግቧል።ጥናቶች እንደሚያሳዩት መርፌው ከ10% በላይ ክብደት ለመቀነስ ያስችላል። ይህ የሚሆነውም ሰዎች ምግብ በልተው እንደጠገቡ እንዲሰማቸው አድርጎ ምግብ እንዳይበሉ በማስቻል ነው።በአሜሪካና በሌሎች አገራት ታዋቂ ሰዎች ይህንን መርፌ ይወስዳሉ። ባለሙያዎች እንደሚሉት መድኃኒቱ ጤናማ አመጋገብና የአካል ብቃት እንቅስቃሴን አይተካም።
ሙከራ ሲደረግ መድኃኒቱን የወሰዱ ሰዎች መድኃኒቱን ሲያቆሙ ተመልሰው ክብደት ይጨምራሉ።በዩኬ በምን ያህል ዋጋ እንደሚሸጥ እስካሁን ባይታወቅም በመደበኛነት አራት መርፌ በ73.25 ዩሮ ሲሸጥ ቆይቷል።ተጠቃሚዎች በሳምንት አንዴ መርፌውን ይወስዳሉ።ይህንን መርፌ የሠራው የዴንማርክ ድርጅት ኖቮ ኖርዲስክ ሲሆን፣ ምርቱን በስፋት እስኪያጠናቅቅ ድረስ ዓለም አቀፍ ማከፋፈል ላይ ገደቦች እንደሚኖሩ አሳውቋል።
“ለተወሰነ ጊዜ ምርቱ እንደሚቀንስ እንጠብቃለን። የተወሰነ ምርት ግን በዩኬ ገበያ ይቀርባል” ሲል መግለጫ አውጥቷል።መርፌውን በከፍተኛ ሁኔታ የሚፈልጉ ሕሙማን ቅድሚያ እንዲያገኙ ለማድረግ ከጤና ባለሙያዎች ጋር በቅርበት እንደሚሠራም ገልጿል።ከመጠን ያለፈ ውፍረት ያላቸው ሰዎች ሕክምናውን እንዲያገኙም እንደሚሠራ አክሏል።በዩኬ መድኃኒቱን መውሰድ የሚችሉት ከመጠን ያለፈ ውፍረት ያላቸውና በሰውነት ክብደታቸው ምክንያት ለሕመም የተጋለጡ ሰዎች ናቸው።
ከተመጣጠነ ምግብና ከአካል ብቃት እንቅስቃሴ ጋር ተደምሮ መድኃኒቱ ለሁለት ዓመታት ይሰጣል።አሁን በዩኬ ሆስፒታሎች በኩል መርፌውን ማግኘት የሚችሉት ወደ 35,000 ሰዎች ሲሆኑ በቀጣይ ተጨማሪ ቁጥር ላላቸው ዜጎች እንደሚዳረስ ተገልጿል።የተቋሙ ቃል አቀባይ እንዳሉት የመድኃኒቱን ዓለም አቀፍ እጥረት ከግምት ውስጥ በማስገባት እንደሚሠሩ ገልጸዋል።ወደ 50,000 ሕሙማን መድኃኒቱን ማግኘት እንደሚችሉም ተናግረዋል።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
👍21👎2🔥2
በእስራኤል መዲና ቴልአቪቭ ኤርትራውያን ጥገኝነት ጠያቂዎች በጎራ ተከፋፍለው ያስነሱት ሁከት “ቀይ መስመሩን” ያለፈ እንደሆነ የአገሪቱ ጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ተናገሩ።
በርካቶች ተጎድተውበታል እንዲሁም ከፍተኛ የንብረት መውደም ተከስቶበታል በተባለውም የቅዳሜ ነሐሴ 27/ 2015 ዓ.ም ግርግር ተሳትፈዋል የተባሉ ኤርትራውያን ጥገኝነት ጠያቂዎችን በአስቸኳይ ከአገር ማባረርን ጨምሮ ጠንከር ያለ እርምጃም ይወሰድባቸዋል ተብሏል።በኤርትራ መንግሥት ደጋፊዎች እና ተቃዋሚዎች መካከል በተነሳው ግርግር እና ከፖሊስ ጋርም በተፈጠረው ግጭት ከ170 ሰዎች በላይ ቆስለዋል።
ኤርትራውያን ጥገኝነት ጠያቂዎች ዱላ፣ ድንጋይ እና ሌሎችም መሣሪያዎችን በመጠቀም እርስ በርስ የተወራወሩ ሲሆን ይህንንም ሁከት ኔታንያሁ “ቀይ መስመሩን ያለፈ” እና “ደም መቃባት የታየበት” ሲሉ ነው የገለጹት።ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ሕገ ወጥ ሰርጎ ገቦች” ሲሉ የገለጿቸውን አፍሪካውያን ስደተኞችን ከአገር የማስወጣት አዲስ ዕቅድም እንዲዘጋጅ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።
በሌሎች አገሮች የታየው በኤርትራ መንግሥት ተቃዋሚዎች እና ደጋፊዎች መካከል የሚፈጠሩ ግጭቶች ከሰሞኑ በእስራኤል፣ ቴልአቪቭ ተከስቷል።ለዚህም መነሻ የሆነው ተቃዋሚዎች በኤርትራ ኤምባሲ አዘጋጅነት የሚካሄደው ፌስቲቫል እንዲሰረዝ የእስራኤል ባለሥልጣናትን መጠየቃቸውን ተከትሎ ነው።
ፌስቲቫሉ በተዘጋጀበት ስፍራ ዙሪያ የነበረውን የፖሊስ አጥር ሰባብረው በመግባት ከፍተኛ የሆነ ንብረት መውደሙ ተገልጿል።በቴልአቪቭ የተከሰተውን አመጽ ለመቆጣጠር የእስራኤል ፖሊሶች ጥይት፣ አስለቃሽ ጭስ እና የፕላስቲክ ጥይቶችን የተኮሱ ሲሆን በፈረስ ላይ የተቀመጡ ፖሊሶችም ኤርትራውያኑን በመግፋት ለመበተን ሲሞክሩም ታይተዋል።
ፖሊስ በኤርትራውያን ላይ ጥይት መተኮሱን ተከትሎ ሕጋዊ አሰራር የተከተለ ስለመሆኑ ምርመራ ተከፍቷል ተብሏል።በርካታ አባላቱ እንደቆሰሉበት ያስታወቀው የእስራኤል ፖሊስ በበኩሉ ሕይወታቸው አደጋ ላይ እንደወደቀ ተሰምቷቸዋል ብሏል።ቅዳሜ የእስራኤል ጎዳናዎች የውጊያ ግንባር የመሰሉ ሲሆን በርካቶች እንጨት፣ ዱላ፣ ፌሮ ይዘው እርስ በርስ ሲደባደቡ ታይተዋል።እርስ በርስ ከነበረው ድብድብም በተጨማሪ የሱቆች መስታዎችን እንዲሁም መኪናዎችን መሰባበራቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።
@YeneTube@FikerAssefa
በርካቶች ተጎድተውበታል እንዲሁም ከፍተኛ የንብረት መውደም ተከስቶበታል በተባለውም የቅዳሜ ነሐሴ 27/ 2015 ዓ.ም ግርግር ተሳትፈዋል የተባሉ ኤርትራውያን ጥገኝነት ጠያቂዎችን በአስቸኳይ ከአገር ማባረርን ጨምሮ ጠንከር ያለ እርምጃም ይወሰድባቸዋል ተብሏል።በኤርትራ መንግሥት ደጋፊዎች እና ተቃዋሚዎች መካከል በተነሳው ግርግር እና ከፖሊስ ጋርም በተፈጠረው ግጭት ከ170 ሰዎች በላይ ቆስለዋል።
ኤርትራውያን ጥገኝነት ጠያቂዎች ዱላ፣ ድንጋይ እና ሌሎችም መሣሪያዎችን በመጠቀም እርስ በርስ የተወራወሩ ሲሆን ይህንንም ሁከት ኔታንያሁ “ቀይ መስመሩን ያለፈ” እና “ደም መቃባት የታየበት” ሲሉ ነው የገለጹት።ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ሕገ ወጥ ሰርጎ ገቦች” ሲሉ የገለጿቸውን አፍሪካውያን ስደተኞችን ከአገር የማስወጣት አዲስ ዕቅድም እንዲዘጋጅ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።
በሌሎች አገሮች የታየው በኤርትራ መንግሥት ተቃዋሚዎች እና ደጋፊዎች መካከል የሚፈጠሩ ግጭቶች ከሰሞኑ በእስራኤል፣ ቴልአቪቭ ተከስቷል።ለዚህም መነሻ የሆነው ተቃዋሚዎች በኤርትራ ኤምባሲ አዘጋጅነት የሚካሄደው ፌስቲቫል እንዲሰረዝ የእስራኤል ባለሥልጣናትን መጠየቃቸውን ተከትሎ ነው።
ፌስቲቫሉ በተዘጋጀበት ስፍራ ዙሪያ የነበረውን የፖሊስ አጥር ሰባብረው በመግባት ከፍተኛ የሆነ ንብረት መውደሙ ተገልጿል።በቴልአቪቭ የተከሰተውን አመጽ ለመቆጣጠር የእስራኤል ፖሊሶች ጥይት፣ አስለቃሽ ጭስ እና የፕላስቲክ ጥይቶችን የተኮሱ ሲሆን በፈረስ ላይ የተቀመጡ ፖሊሶችም ኤርትራውያኑን በመግፋት ለመበተን ሲሞክሩም ታይተዋል።
ፖሊስ በኤርትራውያን ላይ ጥይት መተኮሱን ተከትሎ ሕጋዊ አሰራር የተከተለ ስለመሆኑ ምርመራ ተከፍቷል ተብሏል።በርካታ አባላቱ እንደቆሰሉበት ያስታወቀው የእስራኤል ፖሊስ በበኩሉ ሕይወታቸው አደጋ ላይ እንደወደቀ ተሰምቷቸዋል ብሏል።ቅዳሜ የእስራኤል ጎዳናዎች የውጊያ ግንባር የመሰሉ ሲሆን በርካቶች እንጨት፣ ዱላ፣ ፌሮ ይዘው እርስ በርስ ሲደባደቡ ታይተዋል።እርስ በርስ ከነበረው ድብድብም በተጨማሪ የሱቆች መስታዎችን እንዲሁም መኪናዎችን መሰባበራቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።
@YeneTube@FikerAssefa
👍41❤2
የመንገድ ትራፊክ አደጋ ትምህርት በአዲሱ የስርዓተ ትምህርት ላይ እንደተካተተ ተገለጸ፡፡
በኢትዮጵያ የመንገድ ትራፊክ አደጋን ለመቀነስ በእግረኞች ላይ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ በተለያዩ በሀይማኖት ተቋማት፣ በትምህርት ቤቶች እንዲሁም ለማህበረሰቡ የሚሆኑ መድረኮችን በማዘጋጅት እየተሰራ እንደሆነ የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ አገልገሎት ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ፈቲያ ደድገባ ተናግረዋል፡፡ከዚኅም በተጨማሪ በሀገር ደረጃ ዜጎች የመንገድ ደህንነት ጉዳዮችን እንዲያውቁ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር አብሮ በመስራት የትራፊክ ትምህርትን በተለያዩ የትምህርት አይነቶች ውስጥ እንዱተካተተ ተናግረዋል፡፡
Via Ahadu
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ የመንገድ ትራፊክ አደጋን ለመቀነስ በእግረኞች ላይ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ በተለያዩ በሀይማኖት ተቋማት፣ በትምህርት ቤቶች እንዲሁም ለማህበረሰቡ የሚሆኑ መድረኮችን በማዘጋጅት እየተሰራ እንደሆነ የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ አገልገሎት ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ፈቲያ ደድገባ ተናግረዋል፡፡ከዚኅም በተጨማሪ በሀገር ደረጃ ዜጎች የመንገድ ደህንነት ጉዳዮችን እንዲያውቁ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር አብሮ በመስራት የትራፊክ ትምህርትን በተለያዩ የትምህርት አይነቶች ውስጥ እንዱተካተተ ተናግረዋል፡፡
Via Ahadu
@YeneTube @FikerAssefa
👍18❤3
‹‹ በቅፅል ስሙ ልጅ ያሬድ በሚል የሚታወቀው ያሬድ ዘላለም ላይ የማድረገውን ምርመራ አጠናክሬ እቀጥላለሁ ›› - ፌደራል ፖሊስ
የፌደራል ፖሊስ የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ ጄይላን አብዲ ‹‹ በመታወቂያ ስሙ ያሬድ ዘላለም በቅፅል ስሙ ደግሞ ልጅ ያሬድ በሚል የሚታወቀው ግለሰብ ላይ የማድረገውን ምርመራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ›› ለአሻም ነግረዋታል፡፡ከሰሞኑ ‹‹ ልጅ ያሬድ ›› በሚል ቅፅል ስም የሚጠራዉ የቀድሞ ኮሜዲያን ያሬድ ዘላለም በተረጋገጥ የፌስቡክ ገፁ ‹‹ የአንድ ትልቅ የእምነት ተቋምን ክብር በሚያጎድፍ መልኩ ባስተላለፈዉ ጸያፍና ማንንም ብሄር በማይወክል መልዕክት ምክንያት የፌደራል ፖሊስ ነሐሴ 26 ቀን 2015 ዓ.ም በቁጥጥር ስር እንዳዋለው ›› የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊው ተናግረዋል፡፡
‹‹ ግለሰቡ ተሰውሯራል፣ጠፍቷል እያሉ ያልተጣራና ትክክለኛ ያልሆነ መረጃ የሚነዙና ኅብረተሰቡ ላይ ዉዥንብር የሚነዙ ›› ያሏቸው ‹‹ አካላት ከድርጊታቸዉ እንዲቆጠቡም ›› አሳስበዋል፡፡
ጄይላን ሲቀጥሉ ‹‹ ይህን ከኢትጵያዊነት ያፈነገጠ ተግባር የፈጸመዉ ልጅ ያሬድ( ያሬድ ዘላለም) የተባለ ግለሰብ ከ3ቀናት በፊት የፌደራል ፖሊስ በቁጥጥሩ ስር አውሎት እንደሚገኝ ›› ጠቅሰው ‹‹ ህብረተሰቡ ግንዛቤ እንዲኖረው እንወዳለን ›› ሲሉ አክለዋል፡፡
‹‹ ግለሰቡ በማህበራዊ ሚዲያ ወጥቶ የአንድ ብሄር ተወካይ በሚመስል መልኩ ያስተላለፈው ግብረገብነት የጎደለው፣ የተወደደና የተከበረ የእምነት ተቋም ላይ ያስተላለፈው ጸያፍ ቃላቶች ታላቁን የኦሮሞ ህዝብም ሆነ የአማራን ህዝብ የሚወክል አይደልም ›› ሲሉም ነቅፈዋል፡፡
‹‹ ማንም ደግሞ ለዚህ ግለሰብ የሠጠዉ የእምነትም ሆነ የብሔር ውክልና የለም ›› በማለት ፌደራል ፖሊስ የጀመረውን ምርመራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቁዋል፡፡
‹‹ ሌሎችም ከእንዲህ ዓይነት ከኢትጵያዊነት ከወረደና የእምነት ተቋማትን በመሳደብ ህዝብን ለቁጣ የምታነሳሱና፣ አንድን ብሄረሰብ ከሌላዉ ለማጋጨት በተለያየ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች የምትቀሳቀሱ ከድርጊታቸዉ እንዲታቀቡ ›› አሳስበዋል፡፡
በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ‹‹ ልጅ ያሬድ የተባለውን ግለሰብ እና ተባባሪዎቹ ላይ ክስ እንዲመሠረት የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮን ›› ጠይቃለች፡፡
‹‹ በግለሰቡ እና ተባባሪዎቹ ድፍረት የተሞላበት ድርጊት በርካታ ኦርቶዶክሳዊያንም ኢትዮጵያውያንም ላይ ከፍተኛ ቁጣን በመቀስቀሱን እና ከፍትህ አደባባይ ፍርድን ስለሚጠብቁ ፖሊስን ለማገዝ ይሔን አቤቱታ አቅርቤያለሁ ›› ብላለች።
ቤተ ክርስቲያኗ አክላም ‹‹ የተከሳሹ ድርጊት በዋናነት የቤተ ክርስቲያኗን መልካም ስም የሚያጎድፍ ድርጊት፤ ለቤተ ክርስቲያን ያለውን ጥላቻ በመግለጽ ሰዎችን ለአመጽ እና ብጥብጥ የሚያነሳሳ፤ የቤተክርስቲያንን የአምልኮ ቦታ ያራከሰ ፤ የምዕመናኑን ስሜት የሚነካ በመሆኑ ፣ በሚያዋርድ እና ቤተክርስቲያንን በሚያናንቅ መልኩ የተፈጸመ በመሆኑ በግለሰቡ እና በተባባሪዎቹም ላይ ጭምር ፖሊስ ተገቢውን ምርመራ በማድረግ ክስ እንዲመሠርት ለአቃቤ ሕግም እንዲልክ ›› ጠይቃለች።
Via Asham
@YeneTube @FikerAssefa
የፌደራል ፖሊስ የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ ጄይላን አብዲ ‹‹ በመታወቂያ ስሙ ያሬድ ዘላለም በቅፅል ስሙ ደግሞ ልጅ ያሬድ በሚል የሚታወቀው ግለሰብ ላይ የማድረገውን ምርመራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ›› ለአሻም ነግረዋታል፡፡ከሰሞኑ ‹‹ ልጅ ያሬድ ›› በሚል ቅፅል ስም የሚጠራዉ የቀድሞ ኮሜዲያን ያሬድ ዘላለም በተረጋገጥ የፌስቡክ ገፁ ‹‹ የአንድ ትልቅ የእምነት ተቋምን ክብር በሚያጎድፍ መልኩ ባስተላለፈዉ ጸያፍና ማንንም ብሄር በማይወክል መልዕክት ምክንያት የፌደራል ፖሊስ ነሐሴ 26 ቀን 2015 ዓ.ም በቁጥጥር ስር እንዳዋለው ›› የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊው ተናግረዋል፡፡
‹‹ ግለሰቡ ተሰውሯራል፣ጠፍቷል እያሉ ያልተጣራና ትክክለኛ ያልሆነ መረጃ የሚነዙና ኅብረተሰቡ ላይ ዉዥንብር የሚነዙ ›› ያሏቸው ‹‹ አካላት ከድርጊታቸዉ እንዲቆጠቡም ›› አሳስበዋል፡፡
ጄይላን ሲቀጥሉ ‹‹ ይህን ከኢትጵያዊነት ያፈነገጠ ተግባር የፈጸመዉ ልጅ ያሬድ( ያሬድ ዘላለም) የተባለ ግለሰብ ከ3ቀናት በፊት የፌደራል ፖሊስ በቁጥጥሩ ስር አውሎት እንደሚገኝ ›› ጠቅሰው ‹‹ ህብረተሰቡ ግንዛቤ እንዲኖረው እንወዳለን ›› ሲሉ አክለዋል፡፡
‹‹ ግለሰቡ በማህበራዊ ሚዲያ ወጥቶ የአንድ ብሄር ተወካይ በሚመስል መልኩ ያስተላለፈው ግብረገብነት የጎደለው፣ የተወደደና የተከበረ የእምነት ተቋም ላይ ያስተላለፈው ጸያፍ ቃላቶች ታላቁን የኦሮሞ ህዝብም ሆነ የአማራን ህዝብ የሚወክል አይደልም ›› ሲሉም ነቅፈዋል፡፡
‹‹ ማንም ደግሞ ለዚህ ግለሰብ የሠጠዉ የእምነትም ሆነ የብሔር ውክልና የለም ›› በማለት ፌደራል ፖሊስ የጀመረውን ምርመራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቁዋል፡፡
‹‹ ሌሎችም ከእንዲህ ዓይነት ከኢትጵያዊነት ከወረደና የእምነት ተቋማትን በመሳደብ ህዝብን ለቁጣ የምታነሳሱና፣ አንድን ብሄረሰብ ከሌላዉ ለማጋጨት በተለያየ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች የምትቀሳቀሱ ከድርጊታቸዉ እንዲታቀቡ ›› አሳስበዋል፡፡
በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ‹‹ ልጅ ያሬድ የተባለውን ግለሰብ እና ተባባሪዎቹ ላይ ክስ እንዲመሠረት የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮን ›› ጠይቃለች፡፡
‹‹ በግለሰቡ እና ተባባሪዎቹ ድፍረት የተሞላበት ድርጊት በርካታ ኦርቶዶክሳዊያንም ኢትዮጵያውያንም ላይ ከፍተኛ ቁጣን በመቀስቀሱን እና ከፍትህ አደባባይ ፍርድን ስለሚጠብቁ ፖሊስን ለማገዝ ይሔን አቤቱታ አቅርቤያለሁ ›› ብላለች።
ቤተ ክርስቲያኗ አክላም ‹‹ የተከሳሹ ድርጊት በዋናነት የቤተ ክርስቲያኗን መልካም ስም የሚያጎድፍ ድርጊት፤ ለቤተ ክርስቲያን ያለውን ጥላቻ በመግለጽ ሰዎችን ለአመጽ እና ብጥብጥ የሚያነሳሳ፤ የቤተክርስቲያንን የአምልኮ ቦታ ያራከሰ ፤ የምዕመናኑን ስሜት የሚነካ በመሆኑ ፣ በሚያዋርድ እና ቤተክርስቲያንን በሚያናንቅ መልኩ የተፈጸመ በመሆኑ በግለሰቡ እና በተባባሪዎቹም ላይ ጭምር ፖሊስ ተገቢውን ምርመራ በማድረግ ክስ እንዲመሠርት ለአቃቤ ሕግም እንዲልክ ›› ጠይቃለች።
Via Asham
@YeneTube @FikerAssefa
👍186❤23👎11🔥1
በመቀሌ በሰላማዊ ሰልፍ ቅስቀሳ ላይ የነበሩ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ታሰሩ!
በመቐለ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ቅስቀሳ ላይ የነበሩ 6 የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ጨምሮ ሌሎች በፖሊስ ተይዘው ታሰሩ። "ኪዳን ለስር ነቀል ለውጥ" በሚል መሪ ቃል በመቐለ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያካሂዱ ሲገልፁ የቆዩት በትግራይ በተቃዋሚነት የሚንቀሳቀሱ ሳልሳይ ወያነ ትግራይ፣ የትግራይ ነፃነት ፓርቲ እና ባይቶና የተባሉ የፖለቲካ ድርጅቶች፥ ህወሓት ሰልፍ ለማደናቀፍ እየሰራ ነው በማለት ከሰዋል። ከሰልፉ ጋር በተገናኘ የመቐለ ከተማ አስተዳደር ለፖርቲዎቹ በላከው ደብዳቤ ፀጥታ የሚያስከብርበት አቅም እንደሌለው የገለፀ ቢሆንም ተቃዋሚዎቹ ግን በትግራይ ያሉ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማሕበራዊ ችግሮች የሚንፀባረቁበት ሰልፍ በመጪው ሐሙስ ጳጉሜ 2 ቀን 2015 ዓመተምህረት በሮማናት አደባባይ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል።
በትግራይ ያሉ ፖለቲካዊ፣ ማሕበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ለማንፀባረቅ እንዲሁም ዓለም በትግራይ ያለው ሁኔታ እንዲረዳ የተለያዩ መፈክሮች በመያዝ ሰልፍ ለማድረግ ዝግጅት ላይ ያሉት ሶስት ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች ፥ በትግራይ ያለው 'ህወሓት መር አስተዳደር' ሕጋዊ መብት የሆነው ሰላማዊ ሰልፍ እንዳይካሄድ የተለያዩ እንቅፋቶች እየፈጠረ ነው በማለት ከሰዋል።
የፊታችን ጳጉሜ 2 ቀን 2015 ዓመተምህረት ይካሄዳል የተባለው የተቃውሞ ሰልፍ ለህዝብ ለማስተዋወቅ በመቐለ ከተማ ጎዳናዎች በመኪና እየተዘዋወሩ ይሰሩ የነበሩ ስድስ አባላቶቻቸው ጨምሮ ሌሎች መታሰራቸው የገለፁት ሳልሳይ ወያነ ትግራይ፣ የታላቋ ትግራይ ብሔራዊ ሸንጎ ባይቶና እና የትግራይ ነፃነት ፓርቲ ፥ የገዢው ሐይል አፈና እና ማደናቀፍ ቢቀጥልም ሰልፊ እንደሚደረግ ገልፀዋል።
"ኪዳን ለስር ነቀል ለውጥ" በሚል የተሰባሰቡት እነዚህ ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች በትግራይ የሚታይ ፖለቲካዊ ውድቀት፣ ሕገወጥነት፣ በሴቶች ላይ የሚደርስ ፆታዊ አመፅ፣ ዓይን ያወጣ ያሉት በመንግስት መዋቅር የሚደገፍ ዝርፍያና ማጭበርበር እንዲሁም ሌሎች ያልተገቡ ተግባራት እንደሚቃወሙ የገለፁ ሲሆን በትግራይ ስርነቀል ለውጥ ለማምጣት እንደሚታገሉም ዛሬ በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል። የትግራይ ነፃነት ፓርቲ ኮምኒኬሽን ሐላፊ አቶ ገብረስላሴ ካሕሳይ፥ ሰልፉ ለማስቀረት ህወሓት ሕገወጥ ተግባራት በመከወን ላይ በማለት ይከሳሉ።
ዛሬ በመቐለ ሮማናት አደባባይ አካባቢ እንደታዘብነው፥ የተለያዩ የሰልፊ መፈክሮች እያስተዋወቀ ሲንቀሳቀስ የነበረ ተሽከርካሪ፥ የደንብ አስከባሪ እና ሲቪል ልብስ በለበሱ ታጣቂ እንዲቆም ተደርጎ፥ ተሽከርካሪው እዛው ከነበሩ ስዎች ጋር ወደ ቀዳማይ ወያነ ክፍለከተማ ፖሊስ ጣብያ ተወስደዋል። ከተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ እንደተረዳነውም ስድስት የፖለቲካ ድርጅቶቹ አባላት ጨምሮ ሌሎች የቴክኒክ ስራ ይከውኑ የነበሩ ግለሰቦች ታስረዋል። ህወሓት ሰልፊ ለማደናቀፍ እየሰራ ነው ያሉት የባይቶና ከፍተኛ አመራር አቶ ዮሴፍ በርሃ በበኩላቸው ሰልፊችን ሰላማዊ ነው፣ አስተዳደሩ ግን ከዓመፅ ተግባራት ጋር እያስተሳሰረው ይገኛል በማለት ወቅሰዋል። አቶ ዮሴፍ "ከጠላት የተላከ ሐይል የለም። ዓመፅ እየጠራ ያለ ሐይል የለም።
ትግላችን፣ ሰላማዊ ሰልፋችን ወደ ዓመፅ እንዳይሄዱ አግዙን ነው እያልን እየጠየቅን ያለነው። ፀጥታ አናግዝም ስላሉ የሚቀር ሰላማዊ ሰልፍ ግን የለም። እነሱ እጃቸው ከሰበሰቡልን የትግራይ ህዝብ አመፀኛ አይደለም። እኛም ሰላማዊ ሰልፍ እንጂ ዓመፅ አይደለም የምናደርገው። ግልፅ መሆን ያለበት ይህ ሰልፍ ለውጥ ፈላጊ የትግራይ ልጆች የጠሩት ሰላማዊ ሰልፍ መሆኑ ነው" ብለዋል።
ይህ የትግራይ ነፃነት ፓርቲ፣ ባይቶናና ሳልሳይ ወያነ ትግራይ የጠሩት "ኪዳን ለስር ነቀል ለውጥ" የሚል መፈክር ያለው የተቃውሞ ሰልፍ፥ በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ ሌሎች ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶችም ድጋፍ ተችሮታል። ዓረና ትግራይ ባወጣው መግለጫ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ የማንም ፍቃድ የማያስፈልገው የህዝብ መብት ነው ያለ ሲሆን ከግጭት የፀዳ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሁሉም የበኩሉ ይወጣ ብሏል። ዓሲምባ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲም እንዲሁ የተቃውሞው አካል እንደሚሆን በፖርቲው ከፍተኛ አመራር አቶ መሐሪ ገብራይ በኩል ገልጿል።«የትግራይ ነፃነት ፓርቲ» በህወሓት ላይ ያቀረበው ክስ የመቐለ ከተማ አስተዳደር ሰልፉ አስመልክቶ ለተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶቹ በላከው ደብዳቤ ሰልፊ የሚደረግበት ቀን ከበዓል ጋር የተቀራረበ በመሆኑ እና በቂ የፀጥታ ሐይል ባለመኖሩ ድጋፍ ለማድረግ እንደማይችል ገልፆ ነበር።
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
በመቐለ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ቅስቀሳ ላይ የነበሩ 6 የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ጨምሮ ሌሎች በፖሊስ ተይዘው ታሰሩ። "ኪዳን ለስር ነቀል ለውጥ" በሚል መሪ ቃል በመቐለ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያካሂዱ ሲገልፁ የቆዩት በትግራይ በተቃዋሚነት የሚንቀሳቀሱ ሳልሳይ ወያነ ትግራይ፣ የትግራይ ነፃነት ፓርቲ እና ባይቶና የተባሉ የፖለቲካ ድርጅቶች፥ ህወሓት ሰልፍ ለማደናቀፍ እየሰራ ነው በማለት ከሰዋል። ከሰልፉ ጋር በተገናኘ የመቐለ ከተማ አስተዳደር ለፖርቲዎቹ በላከው ደብዳቤ ፀጥታ የሚያስከብርበት አቅም እንደሌለው የገለፀ ቢሆንም ተቃዋሚዎቹ ግን በትግራይ ያሉ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማሕበራዊ ችግሮች የሚንፀባረቁበት ሰልፍ በመጪው ሐሙስ ጳጉሜ 2 ቀን 2015 ዓመተምህረት በሮማናት አደባባይ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል።
በትግራይ ያሉ ፖለቲካዊ፣ ማሕበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ለማንፀባረቅ እንዲሁም ዓለም በትግራይ ያለው ሁኔታ እንዲረዳ የተለያዩ መፈክሮች በመያዝ ሰልፍ ለማድረግ ዝግጅት ላይ ያሉት ሶስት ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች ፥ በትግራይ ያለው 'ህወሓት መር አስተዳደር' ሕጋዊ መብት የሆነው ሰላማዊ ሰልፍ እንዳይካሄድ የተለያዩ እንቅፋቶች እየፈጠረ ነው በማለት ከሰዋል።
የፊታችን ጳጉሜ 2 ቀን 2015 ዓመተምህረት ይካሄዳል የተባለው የተቃውሞ ሰልፍ ለህዝብ ለማስተዋወቅ በመቐለ ከተማ ጎዳናዎች በመኪና እየተዘዋወሩ ይሰሩ የነበሩ ስድስ አባላቶቻቸው ጨምሮ ሌሎች መታሰራቸው የገለፁት ሳልሳይ ወያነ ትግራይ፣ የታላቋ ትግራይ ብሔራዊ ሸንጎ ባይቶና እና የትግራይ ነፃነት ፓርቲ ፥ የገዢው ሐይል አፈና እና ማደናቀፍ ቢቀጥልም ሰልፊ እንደሚደረግ ገልፀዋል።
"ኪዳን ለስር ነቀል ለውጥ" በሚል የተሰባሰቡት እነዚህ ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች በትግራይ የሚታይ ፖለቲካዊ ውድቀት፣ ሕገወጥነት፣ በሴቶች ላይ የሚደርስ ፆታዊ አመፅ፣ ዓይን ያወጣ ያሉት በመንግስት መዋቅር የሚደገፍ ዝርፍያና ማጭበርበር እንዲሁም ሌሎች ያልተገቡ ተግባራት እንደሚቃወሙ የገለፁ ሲሆን በትግራይ ስርነቀል ለውጥ ለማምጣት እንደሚታገሉም ዛሬ በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል። የትግራይ ነፃነት ፓርቲ ኮምኒኬሽን ሐላፊ አቶ ገብረስላሴ ካሕሳይ፥ ሰልፉ ለማስቀረት ህወሓት ሕገወጥ ተግባራት በመከወን ላይ በማለት ይከሳሉ።
ዛሬ በመቐለ ሮማናት አደባባይ አካባቢ እንደታዘብነው፥ የተለያዩ የሰልፊ መፈክሮች እያስተዋወቀ ሲንቀሳቀስ የነበረ ተሽከርካሪ፥ የደንብ አስከባሪ እና ሲቪል ልብስ በለበሱ ታጣቂ እንዲቆም ተደርጎ፥ ተሽከርካሪው እዛው ከነበሩ ስዎች ጋር ወደ ቀዳማይ ወያነ ክፍለከተማ ፖሊስ ጣብያ ተወስደዋል። ከተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ እንደተረዳነውም ስድስት የፖለቲካ ድርጅቶቹ አባላት ጨምሮ ሌሎች የቴክኒክ ስራ ይከውኑ የነበሩ ግለሰቦች ታስረዋል። ህወሓት ሰልፊ ለማደናቀፍ እየሰራ ነው ያሉት የባይቶና ከፍተኛ አመራር አቶ ዮሴፍ በርሃ በበኩላቸው ሰልፊችን ሰላማዊ ነው፣ አስተዳደሩ ግን ከዓመፅ ተግባራት ጋር እያስተሳሰረው ይገኛል በማለት ወቅሰዋል። አቶ ዮሴፍ "ከጠላት የተላከ ሐይል የለም። ዓመፅ እየጠራ ያለ ሐይል የለም።
ትግላችን፣ ሰላማዊ ሰልፋችን ወደ ዓመፅ እንዳይሄዱ አግዙን ነው እያልን እየጠየቅን ያለነው። ፀጥታ አናግዝም ስላሉ የሚቀር ሰላማዊ ሰልፍ ግን የለም። እነሱ እጃቸው ከሰበሰቡልን የትግራይ ህዝብ አመፀኛ አይደለም። እኛም ሰላማዊ ሰልፍ እንጂ ዓመፅ አይደለም የምናደርገው። ግልፅ መሆን ያለበት ይህ ሰልፍ ለውጥ ፈላጊ የትግራይ ልጆች የጠሩት ሰላማዊ ሰልፍ መሆኑ ነው" ብለዋል።
ይህ የትግራይ ነፃነት ፓርቲ፣ ባይቶናና ሳልሳይ ወያነ ትግራይ የጠሩት "ኪዳን ለስር ነቀል ለውጥ" የሚል መፈክር ያለው የተቃውሞ ሰልፍ፥ በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ ሌሎች ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶችም ድጋፍ ተችሮታል። ዓረና ትግራይ ባወጣው መግለጫ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ የማንም ፍቃድ የማያስፈልገው የህዝብ መብት ነው ያለ ሲሆን ከግጭት የፀዳ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሁሉም የበኩሉ ይወጣ ብሏል። ዓሲምባ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲም እንዲሁ የተቃውሞው አካል እንደሚሆን በፖርቲው ከፍተኛ አመራር አቶ መሐሪ ገብራይ በኩል ገልጿል።«የትግራይ ነፃነት ፓርቲ» በህወሓት ላይ ያቀረበው ክስ የመቐለ ከተማ አስተዳደር ሰልፉ አስመልክቶ ለተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶቹ በላከው ደብዳቤ ሰልፊ የሚደረግበት ቀን ከበዓል ጋር የተቀራረበ በመሆኑ እና በቂ የፀጥታ ሐይል ባለመኖሩ ድጋፍ ለማድረግ እንደማይችል ገልፆ ነበር።
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
👍36👎6❤5
Facebook, Twitter, Instagram እና በመሳሳሉት የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ድርጅትዎን ፤ አገልግሎትዎን እና ምርትዎን ማስተዋወቅ ፈልገዋል? እንግዲያውስ መፍትሄው እኛ ጋር ነው።
በማንኛውም Social Media Boost ለማድረግ ካሰቡ ይደውሉልን፤ በተመጣጣኝ ዋጋ ታማኝና ቀልጣፋ አገልግሎት እንሰጣለን::
ከዚህም በተጨማሪ የቴሌግራም ፕሪሚየም ጨምሮ ለተለያዩ ኢንተርናሽናል አገልግሎቶች ክፍያዎችን መፈጸም ካስፈለግዎ ከስር በተቀመጡ አድራሻዎች ያናግሩን።
Telegram: @adsommar
📞0929334267
በማንኛውም Social Media Boost ለማድረግ ካሰቡ ይደውሉልን፤ በተመጣጣኝ ዋጋ ታማኝና ቀልጣፋ አገልግሎት እንሰጣለን::
ከዚህም በተጨማሪ የቴሌግራም ፕሪሚየም ጨምሮ ለተለያዩ ኢንተርናሽናል አገልግሎቶች ክፍያዎችን መፈጸም ካስፈለግዎ ከስር በተቀመጡ አድራሻዎች ያናግሩን።
Telegram: @adsommar
📞0929334267
👍7❤1
የዋግነር ቡድን በእንግሊዝ ሽብርተኛ ድርጅት ተብሎ ሊፈረጅ ነው!
የሩሲያው ዋግነር ታጣቂ ቡድን በእንግሊዝ ሽብርተኛ ድርጅት ተብሎ ሊፈረጅ ነው።በእንግሊዝ የቡድኑ አባል ወይም ደጋፊ መሆንን ህገወጥ የሚያደርግ ረቂቂ ህግ በዛሬው እለት በፖርላማ ይቀርባል።በዚህ ረቂቅ ህግ እስከ 14 አመታት እስራት የሚያስቀጡ አንቀጾች እንደተካተቱበት ስካይ ኒውስ ዘግቧል።በዚሁ ረቂቅ ህግ መሰረት የዋግነር ንብረቶች የአሸባሪ ድርጅት ንብረቶች ተብለው እንደሚመዘገቡ እና እንደሚወረሱ ተገልጿል።
በፕሪጎዥን ሲመራ የነበረው ይህ ቡድን ባለፈው ወር በአውሮፕላን አደጋ ህይወቱን እስካጣበት ጊዜ ድረስ ሩሲያ በዩክሬን ላይ እያካሄደችው ባለው ጦርነት ጉልህ ሚና ተጫውቷል።ቡድኑ ከዩክሬን በተጨማሪ በሶሪያ፣ በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ በሱዳን እና በሊቢያ እንደሚንቀሳቀስ ይነገራል።
እንግሊዝ ፍረጃው ለማድረግ ያሰበችው የቡድኑ ተፈጥሮአዊ ባህሪይ፣ የቡድኑ እንቅስቃሴ እንዲሁም በውጭ በሚኖሩ የእንግሊዝ ዜጎች ላይ የደቀነውን አደጋ ከግምት በማስገባት መሆኑን ገልጻለች።ዋግነር ከወራት በፊት በሩሲያ መንግስት ላይ አመጽ ከፍቶ የነበረ ቢሆንም በቤላሩስ አደራዳሪነት አመጹ ቆሙ፣ የቡድኑ መሪም ወደ ቤላሩስ እንዲሄድ ተደርጎ ነበር።
Via Al ain
@YeneTube @FikerAssefa
የሩሲያው ዋግነር ታጣቂ ቡድን በእንግሊዝ ሽብርተኛ ድርጅት ተብሎ ሊፈረጅ ነው።በእንግሊዝ የቡድኑ አባል ወይም ደጋፊ መሆንን ህገወጥ የሚያደርግ ረቂቂ ህግ በዛሬው እለት በፖርላማ ይቀርባል።በዚህ ረቂቅ ህግ እስከ 14 አመታት እስራት የሚያስቀጡ አንቀጾች እንደተካተቱበት ስካይ ኒውስ ዘግቧል።በዚሁ ረቂቅ ህግ መሰረት የዋግነር ንብረቶች የአሸባሪ ድርጅት ንብረቶች ተብለው እንደሚመዘገቡ እና እንደሚወረሱ ተገልጿል።
በፕሪጎዥን ሲመራ የነበረው ይህ ቡድን ባለፈው ወር በአውሮፕላን አደጋ ህይወቱን እስካጣበት ጊዜ ድረስ ሩሲያ በዩክሬን ላይ እያካሄደችው ባለው ጦርነት ጉልህ ሚና ተጫውቷል።ቡድኑ ከዩክሬን በተጨማሪ በሶሪያ፣ በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ በሱዳን እና በሊቢያ እንደሚንቀሳቀስ ይነገራል።
እንግሊዝ ፍረጃው ለማድረግ ያሰበችው የቡድኑ ተፈጥሮአዊ ባህሪይ፣ የቡድኑ እንቅስቃሴ እንዲሁም በውጭ በሚኖሩ የእንግሊዝ ዜጎች ላይ የደቀነውን አደጋ ከግምት በማስገባት መሆኑን ገልጻለች።ዋግነር ከወራት በፊት በሩሲያ መንግስት ላይ አመጽ ከፍቶ የነበረ ቢሆንም በቤላሩስ አደራዳሪነት አመጹ ቆሙ፣ የቡድኑ መሪም ወደ ቤላሩስ እንዲሄድ ተደርጎ ነበር።
Via Al ain
@YeneTube @FikerAssefa
👍47👎6❤5
በኢንዶኔዥያ ሙሽራው በሰርጉ ቀን በመቅረቱ ሙሽሪትን የሙሽራው አባት ኃላፊነቱን ወስዶ አገባ
በኢንዶኔዥያ አንዲት ሙሽሪትን በህይወቷ ውስጥ በጣም ደስተኛ በሚያደርጋት ቀን ባለቤቷ መጥፋቱን ተከትሎ ይህ ደስታ ወደ አዋራጅ ቅዠት ተለውጧል።
በኢንዶኔዥያ መገናኛ ብዙሃን እንደተዘገበው ከሆነ ኤስኤ ብቻ የተባለችው ወጣቷ በደቡብ ሃልማሄራ ጂኮታሞ መንደር ነዋሪ ስትሆን ሲሆን ከሙሽራው ጋር የረጅም ጊዜ ግንኙነት እንዳላት ተነግሯል። ነገር ግን በነሀሴ 29 በሠርጋቸው ቀን ሙሽራው በመቅረቱ ለእንግዶች ስለ ሰርጉ መሰረዝ ለመናገር እጅግ አዳጋች ያደርገዋል።
ይህው ችግም በሁለቱም ቤተሰቦች ይሆናል ተብሎ የማይታሰብ የነበረ ሲሆን ፣ ለሠርጉ ዝግጅት ገንዘብ የተከፈለ ሲሆን ለጥሎሽ ተገቢው በሙሉ በመደረጉ የሙሽራው አባት ሙሽሪትን በማግባት የስዎች ጥያቄ ዝም ለማሰኘት ሞክሯል።በኢንዶኔዥያ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በተሰራጨ ምስል መሰረት የሙሽሪት እና የሙሽራዋ አባቶች በአስደናቂው የሰርግ ስነስርአት ላይ አንድ ላይ ዘና ብለው ሲጫወቱ ታይ
በሰርጉ ላይ ለመታደም አስቀድመው እንግዶቹ ተገኝተዋል። የሙሽራው ቤተሰቦች ልጃቸው እንደጠፋ እና ሊገኝ እንደማይችል በማሳወቃቸው የሙሽራዋ ወንድም ዊስቶ አህመድ ለጋዜጠኞች እንደተናገረው አባታችን ሙሽሪትን አግብቷል ሲል አረጋግጧል።
የሙሽራዋ ቤተሰብ በሙሽራው መጥፋቱ በጣም ያዘኑ ቢሆንም፣ ለሠርግ ዝግጅት ወደ 25 ሚሊዮን ሩፒያ ወይም 1,700 ዶላር ያወጡት ወጪ ሌላኛው ጭንቀታቸው ሆኗል። ዝግጅቱ ቢሰረዝ ገንዘቡን መተካት የወንዱ ሙሽራ ቤተሰብ ውጪ በመሆነ የሙሽራው አባት ማግባቱን መርጠዋል።
ይህ ያልተለመደ ሰርግ በኢንዶኔዥያ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ የተደበላለቀ አስተያየት የተሰጠበት ሲሆን የወጣቷን ሙሽራ እጣ ፈንታ በርካቶች አሳዛኝ ብለውታል።አንድ አስተያየት ሰጪ የአባቴ ሚስት የቀድሞ የሴት ጓደኛዬ ናት " ሲሉ በጉዳዩ ላይ ያጋራው መልዕክት አነጋጋሪ ሆኗል።
ይህው ጋብቻ ህጋዊ በመሆኑ ለሙሽራው እንጀራ እናቱ ሆናለች። በቀሪው ሕይወቷ ውስጥ በማትፈልገው የትዳር "ወጥመድ" ውስጥ መግባቷ የሚያስቆጭ ያሉም በርካቶች ናቸው።
@Yenetube @Fikerassefa
በኢንዶኔዥያ አንዲት ሙሽሪትን በህይወቷ ውስጥ በጣም ደስተኛ በሚያደርጋት ቀን ባለቤቷ መጥፋቱን ተከትሎ ይህ ደስታ ወደ አዋራጅ ቅዠት ተለውጧል።
በኢንዶኔዥያ መገናኛ ብዙሃን እንደተዘገበው ከሆነ ኤስኤ ብቻ የተባለችው ወጣቷ በደቡብ ሃልማሄራ ጂኮታሞ መንደር ነዋሪ ስትሆን ሲሆን ከሙሽራው ጋር የረጅም ጊዜ ግንኙነት እንዳላት ተነግሯል። ነገር ግን በነሀሴ 29 በሠርጋቸው ቀን ሙሽራው በመቅረቱ ለእንግዶች ስለ ሰርጉ መሰረዝ ለመናገር እጅግ አዳጋች ያደርገዋል።
ይህው ችግም በሁለቱም ቤተሰቦች ይሆናል ተብሎ የማይታሰብ የነበረ ሲሆን ፣ ለሠርጉ ዝግጅት ገንዘብ የተከፈለ ሲሆን ለጥሎሽ ተገቢው በሙሉ በመደረጉ የሙሽራው አባት ሙሽሪትን በማግባት የስዎች ጥያቄ ዝም ለማሰኘት ሞክሯል።በኢንዶኔዥያ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በተሰራጨ ምስል መሰረት የሙሽሪት እና የሙሽራዋ አባቶች በአስደናቂው የሰርግ ስነስርአት ላይ አንድ ላይ ዘና ብለው ሲጫወቱ ታይ
በሰርጉ ላይ ለመታደም አስቀድመው እንግዶቹ ተገኝተዋል። የሙሽራው ቤተሰቦች ልጃቸው እንደጠፋ እና ሊገኝ እንደማይችል በማሳወቃቸው የሙሽራዋ ወንድም ዊስቶ አህመድ ለጋዜጠኞች እንደተናገረው አባታችን ሙሽሪትን አግብቷል ሲል አረጋግጧል።
የሙሽራዋ ቤተሰብ በሙሽራው መጥፋቱ በጣም ያዘኑ ቢሆንም፣ ለሠርግ ዝግጅት ወደ 25 ሚሊዮን ሩፒያ ወይም 1,700 ዶላር ያወጡት ወጪ ሌላኛው ጭንቀታቸው ሆኗል። ዝግጅቱ ቢሰረዝ ገንዘቡን መተካት የወንዱ ሙሽራ ቤተሰብ ውጪ በመሆነ የሙሽራው አባት ማግባቱን መርጠዋል።
ይህ ያልተለመደ ሰርግ በኢንዶኔዥያ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ የተደበላለቀ አስተያየት የተሰጠበት ሲሆን የወጣቷን ሙሽራ እጣ ፈንታ በርካቶች አሳዛኝ ብለውታል።አንድ አስተያየት ሰጪ የአባቴ ሚስት የቀድሞ የሴት ጓደኛዬ ናት " ሲሉ በጉዳዩ ላይ ያጋራው መልዕክት አነጋጋሪ ሆኗል።
ይህው ጋብቻ ህጋዊ በመሆኑ ለሙሽራው እንጀራ እናቱ ሆናለች። በቀሪው ሕይወቷ ውስጥ በማትፈልገው የትዳር "ወጥመድ" ውስጥ መግባቷ የሚያስቆጭ ያሉም በርካቶች ናቸው።
@Yenetube @Fikerassefa
👍35👎6❤5
የዓረና ፓርቲ ሊቀ መንበር ዓምዶም ገብረስላሴን ጨምሮ ዛሬ ብቻ ከ20 በላይ ሰዎች ታሰሩ!
በትግራይ ክልል 'ጥምረት ለስር ነቀል ለውጥ” በሚል የተሰባሰቡ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በዛሬ እለት ከጠሩት ሠላማዊ ሰልፍ ጋር ተያይዞ ከጠዋት ጀምሮ ይህ ዘገባ እስከወጣበት ሰዓት ድረስ ቢያንስ ከ20 የሚበልጡ ሰዎች ታስረዋል ተባለ።
የሠልፉ አስተባባሪ ኮሚቴ አባል እና የውድብ ናፃነት ትግራይ (ውናት) ምክትል ሊቀ መንበር አለምሰገድ አረጋይ ለአዲስ ዘይቤ እንደገለፁት “ሰልፉን የሚያስተባብሩ ከተፎካካሪ ፓርቲዎቹ የተውጣጡ የኮሚቴ አባላቶች በሙሉ ከሁለት አስተባባሪዎች በስተቀር ታስረዋል”።
እንደ መረጃ ምንጮቹ ከሆነ ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ ብቻ ከፖለቲካ ፓርቲዎች አመራርና አባላት ብቻ ዓምዶምን ጨምሮ 13 ሰዎች የታሰሩ ሲሆን፣ ስድስት የቀድሞ የትግራይ ሠራዊት (ቲዲኤፍ) ሰዎች፣ አራት ለሰላማዊ ሰልፍ የወጡ ንፁሃን ሰዎች በአጠቃላይ ከ20 በላይ ሰዎች ለእስር ተዳርገዋል።
ሰላማዊ ሰልፉ የተጠራበት ሮማናት አደባባይ አካባቢ “ከሰልፈኞች ቁጥር ያለተናነሰ የፀጥታ ኃይል” መኖሩ የተገለፀ ሲሆን አሁንም በሰልፈኞች እና በፀጥታ ኃይሎች መካከል ግብግብ ቀጥሏል።
Via Addis Zeybe
@YeneTube @FikerAssefa
በትግራይ ክልል 'ጥምረት ለስር ነቀል ለውጥ” በሚል የተሰባሰቡ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በዛሬ እለት ከጠሩት ሠላማዊ ሰልፍ ጋር ተያይዞ ከጠዋት ጀምሮ ይህ ዘገባ እስከወጣበት ሰዓት ድረስ ቢያንስ ከ20 የሚበልጡ ሰዎች ታስረዋል ተባለ።
የሠልፉ አስተባባሪ ኮሚቴ አባል እና የውድብ ናፃነት ትግራይ (ውናት) ምክትል ሊቀ መንበር አለምሰገድ አረጋይ ለአዲስ ዘይቤ እንደገለፁት “ሰልፉን የሚያስተባብሩ ከተፎካካሪ ፓርቲዎቹ የተውጣጡ የኮሚቴ አባላቶች በሙሉ ከሁለት አስተባባሪዎች በስተቀር ታስረዋል”።
እንደ መረጃ ምንጮቹ ከሆነ ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ ብቻ ከፖለቲካ ፓርቲዎች አመራርና አባላት ብቻ ዓምዶምን ጨምሮ 13 ሰዎች የታሰሩ ሲሆን፣ ስድስት የቀድሞ የትግራይ ሠራዊት (ቲዲኤፍ) ሰዎች፣ አራት ለሰላማዊ ሰልፍ የወጡ ንፁሃን ሰዎች በአጠቃላይ ከ20 በላይ ሰዎች ለእስር ተዳርገዋል።
ሰላማዊ ሰልፉ የተጠራበት ሮማናት አደባባይ አካባቢ “ከሰልፈኞች ቁጥር ያለተናነሰ የፀጥታ ኃይል” መኖሩ የተገለፀ ሲሆን አሁንም በሰልፈኞች እና በፀጥታ ኃይሎች መካከል ግብግብ ቀጥሏል።
Via Addis Zeybe
@YeneTube @FikerAssefa
👍25👎2❤1
ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብቶች ባለሙያ ቡድን ኮሚሽን በኢትዮጵያ የሥራ ጊዜው በአንድ ዓመት እንዲራዘም 63 ድርጅቶች ጠየቁ፡፡
ሁለቱ የሰብዓዊ መብቶች ተከራካሪ ድርጅቶች ሂዩውማን ራይትስ ዎችና አምነስቲ ኢንተርናሽናልን ጨምሮ 63 ድርጅቶች ከቀናት በኋላ የሚጠናቀቀው የኮሚሸኑ የሥራ ጊዜ እስከ መስከረም 2024 እ.አ.አ. ወይም አንድ ዓመት እንዲራዘም ለተባባሩት መንግስታት ድርጅት 54ኛው የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ ባለኩት ደብዳቤ ጠይቀዋል፡፡
እነዚህ የሲቪልና የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች እንደሚሉት በኢትዮጵያ ያለው የከፋ የሰብኣዊ መብቶች አያያዝ፣ የኮሚሽኑን የሥራ ጊዜ እንዲራዘም የሚያስገድድ ነው፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት የኮሚሽኑን ሥራ ደጋግሞ ለማደናቀፍ ቢሞክርም፣ ይህ የባለሙያዎች ቡድን እጅግ ጠቃሚ ስራዎችን መስራቱን ደብዳቤው አመልክቷል፡፡ መንግስት በኮሚሽኑ ላይ እንቅፋት ሆኗል ሲል ከተጠቀሳቸው ጉዳዮች መካከል ‹‹ ባለሙያዎቹ በአዲስ አበባ እንጂ በሌሎች ግጭት ባለባቸው አካባቢዎች እንዳይሄድ፣ ለኮሚሽኑ በጀት እንዳይመደብና ስራው ሙሉ በሙሉ እንዲቀለበስ ደጋግሞ መሞከር ›› የሚሉት ይገኙበታል፡፡
እነዚህ ፈተናዎች ቢኖሩም ‹‹ ኮሚሽኑ በወርሃ መስከረም 2022 እ.አ.አ. ይፋ ባደረገው የመጀመሪያ ዙር ሪፖርት የሰሜን ኢትዮጵያ ሁሉም ተፋላሚ ሀይላት የጦር ወንጀል መፈፀማቸውን ሊያሳምን የሚችል ማስረጃዎችን አጋልጧል ›› ብሏል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ሁለቱ የሰብዓዊ መብቶች ተከራካሪ ድርጅቶች ሂዩውማን ራይትስ ዎችና አምነስቲ ኢንተርናሽናልን ጨምሮ 63 ድርጅቶች ከቀናት በኋላ የሚጠናቀቀው የኮሚሸኑ የሥራ ጊዜ እስከ መስከረም 2024 እ.አ.አ. ወይም አንድ ዓመት እንዲራዘም ለተባባሩት መንግስታት ድርጅት 54ኛው የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ ባለኩት ደብዳቤ ጠይቀዋል፡፡
እነዚህ የሲቪልና የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች እንደሚሉት በኢትዮጵያ ያለው የከፋ የሰብኣዊ መብቶች አያያዝ፣ የኮሚሽኑን የሥራ ጊዜ እንዲራዘም የሚያስገድድ ነው፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት የኮሚሽኑን ሥራ ደጋግሞ ለማደናቀፍ ቢሞክርም፣ ይህ የባለሙያዎች ቡድን እጅግ ጠቃሚ ስራዎችን መስራቱን ደብዳቤው አመልክቷል፡፡ መንግስት በኮሚሽኑ ላይ እንቅፋት ሆኗል ሲል ከተጠቀሳቸው ጉዳዮች መካከል ‹‹ ባለሙያዎቹ በአዲስ አበባ እንጂ በሌሎች ግጭት ባለባቸው አካባቢዎች እንዳይሄድ፣ ለኮሚሽኑ በጀት እንዳይመደብና ስራው ሙሉ በሙሉ እንዲቀለበስ ደጋግሞ መሞከር ›› የሚሉት ይገኙበታል፡፡
እነዚህ ፈተናዎች ቢኖሩም ‹‹ ኮሚሽኑ በወርሃ መስከረም 2022 እ.አ.አ. ይፋ ባደረገው የመጀመሪያ ዙር ሪፖርት የሰሜን ኢትዮጵያ ሁሉም ተፋላሚ ሀይላት የጦር ወንጀል መፈፀማቸውን ሊያሳምን የሚችል ማስረጃዎችን አጋልጧል ›› ብሏል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
👍35❤3
"ግጭቶች ሳይፈጠሩ ቀድመን ወደ ውይይት መምጣት አለብን፣ እሣት ማጥፋት ላይ መጠመድ የለብንም" ሲሉ የመብቶችና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል /ካርድ/ ዋና ዳይሬክተር አቶ በፍቃዱ ሀይሉ ተናገሩ፡፡
የነበሩ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ ለምፍታት፣ እየመጡ ያሉ የሚታዩ ግጭቶችን ቀድሞ ለመከላከልና መልስ እንዲያገኙ ለማድረግ እና በሰላማዊ መንገድ የተፈቱ ግጭቶችን ዛላቂ ለማድረግ ሁሉን አካታች የውይይት መድረክ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡በሀገራችን እስካሁን ድረስ እየተደረጉ ያሉት ሙከራዎች እሣት የማጥፋት ሁኔታዎቸ ናቸው ያሉት ዋና ዳይሬከተሩ የውይይት መድረኮች ግጭቶች ሳይፈጠሩ ቀድመው መከናወን አለባቸው ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ በተለያዩ አቅጣጫዎች ግጭቶች ሲመጡ ቀድመው ይታያሉ ስለዚህም እነዚህን ግጭቶች ለመከላከል የሚያስችል የውይይት መድረክ ያስፈልጋል ሲሉ ተደምጠዋል፡፡
በባለፈው ዓመት በተመሳሳይ በትግራይ የነበረው ጦርነት እንዲቆም ጥሪ አቅርበን ከመንግስት ከፍተኛ ውግዘትን ብናስተናግድም ከተወሰኑ ወራት ባኃላ የፕሪቶሪያው ውይይት ተካሂዷል ብለዋል አቶ በፍቃዱ ሀይሉ፡፡በመሆኑም መንግስት አሁንም ሁሉን አቀፍ የሆነና ዘላቂ የሆነ መድረክ አዘጋጅቶ ያሉበትን ችግሮች በውይይት መፍታት ያስፈልገዋል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
የነበሩ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ ለምፍታት፣ እየመጡ ያሉ የሚታዩ ግጭቶችን ቀድሞ ለመከላከልና መልስ እንዲያገኙ ለማድረግ እና በሰላማዊ መንገድ የተፈቱ ግጭቶችን ዛላቂ ለማድረግ ሁሉን አካታች የውይይት መድረክ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡በሀገራችን እስካሁን ድረስ እየተደረጉ ያሉት ሙከራዎች እሣት የማጥፋት ሁኔታዎቸ ናቸው ያሉት ዋና ዳይሬከተሩ የውይይት መድረኮች ግጭቶች ሳይፈጠሩ ቀድመው መከናወን አለባቸው ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ በተለያዩ አቅጣጫዎች ግጭቶች ሲመጡ ቀድመው ይታያሉ ስለዚህም እነዚህን ግጭቶች ለመከላከል የሚያስችል የውይይት መድረክ ያስፈልጋል ሲሉ ተደምጠዋል፡፡
በባለፈው ዓመት በተመሳሳይ በትግራይ የነበረው ጦርነት እንዲቆም ጥሪ አቅርበን ከመንግስት ከፍተኛ ውግዘትን ብናስተናግድም ከተወሰኑ ወራት ባኃላ የፕሪቶሪያው ውይይት ተካሂዷል ብለዋል አቶ በፍቃዱ ሀይሉ፡፡በመሆኑም መንግስት አሁንም ሁሉን አቀፍ የሆነና ዘላቂ የሆነ መድረክ አዘጋጅቶ ያሉበትን ችግሮች በውይይት መፍታት ያስፈልገዋል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
👍23❤1