YeneTube
117K subscribers
31.6K photos
485 videos
79 files
3.91K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
Forwarded from YeneTube
"ትልቅሰው ሪል እስቴት "
በመሃል ካዛንችስ እንደራሴ እጅግ ዘመናዊ አፓርትመንቶችን በማስተዋቂያ ዋጋ መሸጥ ጀምረናል ።
ትልቅ ሰው ሪል እስቴት
🌹 የኔክሰስ ሆቴል
🌹 የግራንድ ሆቴል
🌹 የኢግል ፓክ ኢንዱስትሪያል እና
🌹 የስካይ ፔትሮሊየም እህት ኩባንያ ነው
👉ባለ 2 መኝታ
👉ባለ 3 መኝታ
👉የሚገርም ማራኪ እይታ ያላቸው !!!
👉ግንባታቸው 90% የደረሰ !!!
👉ማስረከቢያ ጊዜ ከ6 ወር -1 አመት
👉ከአማራጭ አከፋፈል ጋር
✍️100% በ1 አመት በ"4"ዙር
✍️50/50 ከባንክ ጋር ከ5-20 አመት
🙏🙏🙏🙏🙏
ለበለጠ መረጃ
@setu1988
+251936606665
👍1
ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር የሚያገናኛትን የባቡር መስመር ልትዘረጋ መሆኑ ተገለጸ!

ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር የሚያገናኛትን የባቡር መስመር በ13 ነጥብ 8 ቢሊዮን ዶላር ልትዘረጋ መሆኑን አስታውቃለች፡፡

ኬንያ የምትዘረጋው ይህ ፈጣን የባቡር መስመር በኤሌክትሪክ የሚሰራ ሲሆን፤ መነሻውን ከህንድ ውቅያኖስ ላሙ ወደብ በማድረግ ኢትዮጵያን እና ደቡብ ሱዳንን እንደሚያገናኝ ብሉምበርግ ዘግቧል።

በዓይነቱ ልዩ ነው የተባለው ይህ የባቡር መስመር በፈረንጆቹ 2025 ሥራ እንደሚጀመር እና 3 ሺሕ ከሎ ሜትር ወይም 1 ሺሕ 864 ማይል እንደሚረዝም ታውቋል፡፡

የባቡር መስመሩ መነሻውን ከህንድ ውቅያኖስ አድርጎ፣ በኬንያዋ ማዕከላዊ ከተማ ኦሲዮሎን በኩል፣ ናይሮቢን እና አዲስ አበባን በማገናኘት የመጨረሻም መዳረሻውን ደቡብ ሱዳን ጁባ እንደሚያደርግ ተነግሯል፡፡

ይህ ፈጣን የባቡር መስመር “ኢትዮጵያ በአሰብ እና ምጽዋ እንዲሁም ጅቡቲ ወደቦች ላይ ያላትን ጥገኝነት የሚቀንስ ነው” የተባለ ሲሆን፤ ሌሎች በርካታ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች እንዳሉትም ተገልጿል፡፡

በዚሁ ፈጣን የባቡር መስመር ዝርጋታ አማካኝነት ደቡብ ሱዳን ኹለተኛ ወደብ እንደሚኖራትም ተመላክቷል።

የባቡር መስመር ዝርጋታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠጥ በሚጀምርበት ወቅት፣ ከላሞ ወደብ ወደ ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት ውል የፈጸመው ላፕሴት፣ በዓመት ከ29 ሚሊዮን ቶን በላይ ጭነት እና 700 ሺሕ ተጓዦችን እንደሚያመላልስ አስታውቋል። 

🖋Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
1👍1
የቻይና መንግስት በሰጠው የነፃ ትምህርት እድል አሸናፊ ለሆኑ ተማሪዎች ሽኝት ተደረገ።

የቻይና መንግስት  በሰጠው የነጻ የትምህርት እድል አሸናፊ ለሆኑ 26 ተማሪዎች አዲስ አበባ በሚገኘው የቻይና ኢምባሲ  ትናንት ሽኝት ተደርጓል።በሽኝት መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት በኢትዮጵያ የቻይና አምባስደር ዣዎ ዚዩአን  ሀገራቸው በኢትዮጵያ የሚደረገውን የእውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግርን  በዘላቂነት እንደምትደግፍ ገልጸዋል።

አምባሳደሩ አያይዘውም በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያና ቻይና መካከል ያለው ሁሉን አቀፍ ስትራቴጂካዊ ትብብር  የጋራ በሆኑ ጉዳዮች በዘላቂነት ለመስራት እንደሚያስችል አብራርተዋል።በትምህርት ሚንስቴር የከፍተኛ ትምህርት አለማቀፋዊነትና ስኮላርሺፕ ዴስክ ሀላፊ ዶ/ር ኢዶሳ ተርፋሳ በበኩላቸው  በኢትዮጵያ የሰለጠነ የሰው ሀይል ግንባታ ሂደት ውስጥ የቻይና መንግስት እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ተማሪዎች ተጨባጭ እውቀት በመቅሰምና ወደ ሀገራቸው በመመለስ በእውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር  ግምባታ የበኩላቸውን አስተዋጾ እንዲያደርጉም አሳስበዋል።በተደረገው የሽኝት መርሃ ግብር ላይ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የስራ ሀላፊዎችና ቀደም ሲል በቻይና ትምህርታቸውን ተከታትለው የተመለሱ ምሁራን ልምዳቸውን አካፍለዋል።

@YeneTube @FikerAssefa
👍1
የአማራ ክልል ምክር ቤት የተለያዩ ሹመቶችን አጸደቀ!

ለአንድ ቀን በባሕር ዳር ሲካሄድ የቆየው የአማራ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን፣ 1ኛ አስቸኳይ ጉባዔ የተለያዩ ሹመቶችን በማጽደቅ ተጠናቋል፡፡

የቀድሞውን ርእሰ መሥተዳደር ዶክተር ይልቃል ከፋለን የመልቀቂያ ጥያቄ ተቀብሎ የአቶ አረጋ ከበደን ርእሰ መሥተዳድርነት ሹመት ያጸደቀው ምክር ቤቱ በአዲሱ ርእሰ መሥተዳድር በእጩነት የቀረቡትን የተለያዩ ሹመቶች ተወያይቶ አጽዷል፡፡

በዚሁ መሠረት፤

1.አቶ አብዱ ሁሴን የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር
2.ዶክተር አህመዲን መሐመድ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የከተማ እና መሰረተ ልማት ቢሮ ኅላፊ
3.ዶክተር ድረስ ሳህሉ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የገጠር ዘርፍ አስተባባሪ እና የግብርና ቢሮ ኅላፊ
4.ዶክተር ሙሉነሽ ደሴ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማእረግ የማሕበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኅላፊ
5.አቶ ደሳለኝ ጣሰው በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የአስተዳደር ጉዳዮች አስተባባሪ እና የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ኅላፊ
6.ዶክተር ጋሻው አወቀ የአማራ ክልል መንገድ ቢሮ ኅላፊ
7.አቶ ብርሃኑ ጎሽም የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ኅላፊ
8.ዶክተር መንገሻ ፈንታው የአማራ ክልል ኮምዩኒኬሽን ቢሮ ኅላፊ
9.ዶክተር ስቡህ ገበያው የአማራ ክልል ሥራ እና ስልጠና ቢሮ ኅላፊ
10.አቶ ክብረት አህመድ የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኅላፊ
11.አቶ አብዱልከሪም መንግሥቱ የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ኅላፊ
12. ዶክተር ደመቀ ቦሩ የአማራ ክልል ፕላን እና ልማት ቢሮ ኅላፊ ሆነው ተሹመዋል።

ከላይ የተጠቀሱት ተሿሚዎች በእጩነት የቀረቡ ሲሆን ሌሎቹ ተቋማት ባሉበት እንደሚቀጥሉ ርእሰ መሥተዳድሩ መግለጻቸውን አሚኮ ዘግቧል። የምክር ቤት አባላቱ በእጩ ተሿሚዎች ላይ ሰፊ ውይይት እና ምክክር ካደረጉ በኋላ ሹመታቸውን አጽድቀዋል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
👍21
Betስኬት ለስፖርታዊ ውርርዶች የሚጠቅሙ መረጃዎችን ይዞ ወደናንተ መጥቷል።

ስፖርታዊ ውርርድ(ቤቲንግ) መጫወት ሚያዘወትሩ ከሆነ ይህ ዌብሳይት ጨዋታዎችን ከቁጥራዊ መረጃዎች በመነሳት በጥልቀት በመተንተን የትኛውን ቡድን ወይም Possibility መምረጥ እንዳለብዎ ስራዎን እናቀልሎታለን፤ ትንተናዎቻችንን ሊንኩን በመጫን በነጻ ያንብቡ።

ወደፊትን መገመት ከባድ ቢሆንም እኛ ግን ለእርሶ ለማቅለል ተግተን እንሰራልን!

ለዛሬ የመረጥንላችሁ ጨዋታዎች:
👇👇👇

https://www.betsket.com/ቼልሲ፤-ሪያል-ማድሪድንና-አርጀንቲኒዮስ/
1
ሩሲያ 42 የዩክሬን ድሮኖችን መትታ መጣሏን አስታወቀች!

ሩሲያ ከዩክሬን የተላኩ በርካታ ሰው አልባ አውሮፕላኖች (ድሮኖች) መደምሰሳቸውን ዛሬ ዓርብ አስታወቀች፡፡የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር እንዳመለከተው 42ቱ ድሮኖች የተደመሰሱት ክሬይሚያ ላይ ነው፡፡

ከእነዚህ ዘጠኙ በአየር መከላከያ ተመተው የወደቁ ሲሆን 33ቱ ደግሞ በኤሌክትሮኒክ የጦር መሳሪያዎች መውደማቸውን ሚኒስቴሩ አስታውቋል፡፡በጥቃቱ በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት መኖሩ አልተገለጸም፡፡

በሌላ በኩል የዩናይትድ ስቴትስ የመከላከያ ሚኒስቴር (ፔንታገን) ኤፍ 16 የተባሉ ተዋጊ ጀቶችን የሚያበሩ እና የሚጠግኑ ዩክሬናውያንን እንደሚያሰለጥን ትናንት ሐሙስ አስታውቋል፡፡

ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ በአሪዞና ክፍለ ግዛት ይሰጣል የተባለው ሥልጠና "የዩክሬንን የረዥም ጊዜ መከላከያን ለማዳበር እና ለማጠናከር የሚደረገውን ዓለም አቀፍ ጥረት ለመደገፍ የሚሰጥ ነው" ሲሉ የፔንታገን ቃል አቀባይ የአየር ኃይሉ ብርጊዴየር ጄኔራል ፓት ራይደር ተናግረዋል።ይህ በእንዲህ እንዳለ ኖርዌይ የኤፍ 16 ተዋጊ ጀቶችን ለዩክሬን እየሰጠች መሆኑን ትናንት ሐሙስ ኪቭን የጎበኙት የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ጆናስ ጋህር ስቶሬ ተናግረዋል፡፡

የተዋጊ ጀቶቹ ብዛት ባይገለጽም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምናልባት ከአስር ያልበለጡ ሊሆኑ እንደሚችሉ አመልክተዋል፡፡ዩክሬን ከሩሲያ ጋር ለምታካሂደው ውጊያ ተዋጊ ጀቶችን በመለገስ ከኔዘርላንድ እና ዴንማርክ ቀጥሎ ኖርዌይ ሶስተኛዋ የአውሮፓ አገር መሆኗ ተነግሯል፡፡

[VoA]
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
"ትልቅሰው ሪል እስቴት "
በመሃል ካዛንችስ እንደራሴ እጅግ ዘመናዊ አፓርትመንቶችን በማስተዋቂያ ዋጋ መሸጥ ጀምረናል ።
ትልቅ ሰው ሪል እስቴት
🌹 የኔክሰስ ሆቴል
🌹 የግራንድ ሆቴል
🌹 የኢግል ፓክ ኢንዱስትሪያል እና
🌹 የስካይ ፔትሮሊየም እህት ኩባንያ ነው
👉ባለ 2 መኝታ
👉ባለ 3 መኝታ
👉የሚገርም ማራኪ እይታ ያላቸው !!!
👉ግንባታቸው 90% የደረሰ !!!
👉ማስረከቢያ ጊዜ ከ6 ወር -1 አመት
👉ከአማራጭ አከፋፈል ጋር
✍️100% በ1 አመት በ"4"ዙር
✍️50/50 ከባንክ ጋር ከ5-20 አመት
🙏🙏🙏🙏🙏
ለበለጠ መረጃ
@setu1988
+251936606665
1👍1
ኢትዮጵያ በሴቶች ማራቶን ውድድር የወርቅ እና የብር ሜዳሊያ አገኘች!

በ19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሴቶች ማራቶን ውድድር አትሌት አማኔ በሪሶ የወርቅ እና አትሌት ጎይቲቶም ገብረስላሴ የብር ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ አስገኝተዋል።

እንኳን ደስ አለን!

@YeneTube @FikerAssefa
ኡጋንዳ "የሞቱ ምዕራባውያን" ልብስ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ እግድ ጣለች!

የኡጋንዳው ፕሬዝደንት ዮሪ ሙሰቨኒ የሀገር ውስጥ የጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪዎችን እድገት ያቀጭጫሉ ያሏቸውን "የሞቱ ምዕራባውያን" ልብሶች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ እገዳ ጥለዋል።ኡጋንዳ ከፍተኛ መጠን ያለው ያገለገለ ልብስ ስታስገባ የቆየች ሲሆን የዋጋ ቅናሽ ስላላቸው በተወሰኑ በተጠቃሚዎች ዘንድ ተመራጭ ናቸው።

ነገርግን የሀገር ውስጥ የጨርቃጨርቅ ድርጅቶች ያገለገሉ ልብሶች ገበያው ላይ መብዛት የሀገሪቱን የጥጥ እና የጨርቃጨርቅ እንዱስትሪ እድገት ይገታዋል የሚል ቅሬታ እያቀረቡ ሲያቀርቡ ቆይተዋል።ፕሬዝደንት ሙሰቨኒ"እነዚህ ለሞቱ ሰዎች የሚሆኑ ናቸው። ነጭ ሰው በሚሞትበት ጊዜ፣ ልብሶቹን ይሰበስቡና ወደ አፍሪካ ይልኳቸዋል" ሲሉ ተናግረዋል።

የእንግሊዙ ግበረሰናይ ድርጅት ኦክስፋም እንደገለጸው ከሆነ የእርዳታ ድርጅቶች ከሜሪካ እና አውሮፖ ከሚሰበስቡት 70 በመቶ የሚሆነው ልብስ ወደ አፍሪካ ይላካል።ሮይተርስ ከሞቱ ሰዎች የሚመጣው ልብስ ምን ያህል ድርሻ እንዳለው ማረጋገጥ እንደማይችል ገልጿል።"አዲስ ምርት የሚያመርቱ ሰዎች እዚህ አሉን ነገረግን ገበያውን ሰብረው መግባት አልቻሉም" ብለዋል ሙሰቨኒ።

ኡጋንዳ ከፍተኛ የጥጥ አምራች ሀገር ብትሆንም አብዛኛው ምርት በተወሰኑ ደረጃ እሴት ተጨምሮበት ወደ ውጭ የሚላክ ነው። ኡጋንዳ አባል የሆነችበት የምስራቅ አፍሪካ ቡድን ያገለገሉ ልብሶች እንዳይገቡ በፈረንጆቹ 2016 ተስማምተው ነበር። ነገርግን አስካሁን ተግባራዊ ያደረገችው ሩዋንዳ ነች።

Via Al ain
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
የዛሬ ከሰአት በኋላ ጨዋታዎች:-

ማንችስተር ዩናይትድ፤ ፍሬይቡርግን እና ብሬንትፎርድን የተመለከቱ የቤቲንግ መረጃዎች እና ግምቶች በቤትስኬት

ሊንኩን በመጫን በነጻ ያንብቡ👇👇

https://www.betsket.com/ማንችስተር-ዩናይትድ፤-ፍሬይቡርግን-እና/


ምሽት በሚደረጉ ጨዋታዎችም እንመለሳለን። ሁል ጊዜ የሚለቀቁ መረጃዎችን በአንድ ላይ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ።👉 @betskett
ጀንቦሮ ሪል እስቴት በ370 ሚሊዮን ብር ያስገነባቸውን ቤቶች በዛሬው ዕለት አስመረቀ!

ጀንቦሮ ሪል ስቴት በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ቡልቡላ ሁለተኛውን የሪልስቴት ኘሮጀክት ነው ያስመረቀው።በዛሬው ዕለት የተመረቀው ሁለተኛው ኘሮጀክት 72 መኖሪያዎችን የሚይዝ በ1200 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ ነው ተብሏል።

ለባለቤቶቹ የተላለፉት እነዚህ ቤቶች 6 መቶ70 ሚሊዮን ብር ወጪ ተደርጎባቸዋል ነው የተባለው።ለህንፃው አገልግሎት የሚሰጡ የከርሰ ምድር ውሃ፣ሊፍት፣የደህንነት ካሜራዎችና ጀነሬተር እንደተገጠመለትም ተሰምቷል።

በቀጣይ በሳርቤት ሳይት 5ሺህ ካሬ ላይ ያረፈ ግዙፍ የመኖሪያ መንደር እንደሚገነባም ገልጿል።በመጪው አምስት አመታት ውስጥ 5000 አፖርትመንቶችን ፣ ቪላዎችን እና የንግድ ስቆችን ለቤት ገዥዎች በጥራት ሰርቶ ለማጠናቀቅ ዕቅድ እንዳለው አስታውቋል።

Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
"በመኖሪያ ቤቶች ኪራይ ላይ የተደረገ ምንም ዓይነት ጭማሪ የለም"- የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን

በመኖሪያ ቤቶች ኪራይ ላይ የተደረገ ምንም ዓይነት ጭማሪ የለም ሲል የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን አስታወቀ።በአንዳንድ የማኅበራዊ ትሥሥር ገጾች በመኖሪያ ቤቶች ኪራይ ላይ ጭማሪ ተደርጓል በሚል እየተሠራጨ ያለው መረጃ የተሳሳተ እና ከእውነታ የራቀ መሆኑን ኮርፖሬሽኑ ገልጿል።

ኮርፖሬሽኑ በአዲስ አበባ እና በድሬደዋ ከተማ የሚገኙ የፌዴራል መንግሥት ይዞታዎችን እና ቤቶችን እያስተዳደረ እንደሚገኝ አስታውቋል።በአሁኑ ሰዓት ኮርፖሬሽኑ 20 ሺህ የሚጠጉ የመኖሪያ እና የንግድ ቤት ደንበኞች እንዳሉት እና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ባካሄደው የተቋም ግንባታ ለደንበኞቹ ፈጣን እና ዘመናዊ አገልግሎት እያቀረበ እንደሚገኝም አመልክቷል።

ኮርፖሬሽኑ ባቋቋማቸው የነዋሪች ማኅበራት እና በዘረጋው የመረጃ ሥርዓት መሠረት ከተከራይ ደንበኞቹ ጋርም በቅርበት እየሠራ መሆኑን ጠቁሟል።ይሁንና ከሰሞኑ በአንዳንድ የማኅበራዊ ሚዲያ መገናኛ አውታሮች የኮርፖሬሽኑን ሎጎ እና ስም በመጠቀም ኮርፖሬሽኑ በመኖሪያ ቤቶች ላይ ኪራይ ጭማሪ እንዳደረገ ተደርጎ ሐሰተኛ ዜና መውጣቱን ማረጋገጥ መቻሉን ነው ኮርፖሬሽኑ ያስታወቀው።

ኮርፖሬሽኑ የኪራይ ማሻሻያ ማድረግ ሲያስፈልገው ሳይንሳዊ የጥናት ውጤቶችን መሠረት አድርጎ እና ከተከራይ ደንበኞች ጋር አስፈላጊውን ውይይት እና መተማመን ሲፈጠር ብቻ ማሻሻያ ሊያደረግ እንደሚችል እየታወቀ በማኅበራዊ ሚዲያ የኮርፖሬሽኑን ሎጎ እና ስም በመጠቀም የወጣው መረጃ የተሳሳተ መሆኑን እና በአሁኑ ሰዓት ምንም ዓይነት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ማሻሻያ አለማድረጉን አመልክቷል።

በመኖሪያ ቤቶች ላይ የኪራይ ማሻሻያ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝም በነዋሪዎች ማኅበራት እና በተዘረጋው የመረጃ ሥርዓት መሠረት ለተከራይ ደንበኞች እንደሚያሳውቅ ገልጿል።ተከራይ ደንበኞች ትክክለኛ መረጃ ማግኘት ከፈለጉ በቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች በኩል እንደሚያገኙ እና ከሐሰተኛ መረጃ ራሳቸውን እንዲጠብቁ ኮርፖሬሽኑ ማሳሰቡን ኢዜአ ዘግቧል።

@YeneTube @FikerAssefa
👍31
አርባምንጭ አቅራቢያ የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች 18 ሰዎች ሳይገድሉ እንዳልቀረ ተገለጸ!

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን አርባምንጭ ከተማ አቅራቢያ 18 ሰዎች በፀጥታ አባላት መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ ፡፡ ከሥፍራው የሚወጡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት የግድያ ድርጊቱ የተፈጸመው በጋሞ ዞን አስተዳደር አርባምንጭ ከተማ አቅራቢያ ነው ፡፡

የተኩስ ልውውጡ የተጀመረው የጋሞ ዞን አስተዳደርና የአርባ ምንጭ ከተማ ፖሊስ አባላት ወደ ቀበሌው መግባታቸውን ተከትሎ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል ፡፡ የግጭቱና የግድያው መንስኤ በአርባ ምንጭ ወረዳ ዙሪያ ሥር ሲተዳደር የቆየውና ሻራ የተባለው ቀበሌ ወደ አርባ ምንጭ ከተማ ይካለል በሚል በተነሳ አለመግባባት መሆኑን ነው የአይን እማኞች የገለጹት፡፡

ዶቼ ቬለ DW በግጭቱ ጉዳት ደርሶባቸው በአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ይገኛሉ ሥለተባሉት ተጎጂዎች ሁኔታ ለመጠየቅ የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ወንደሰን ወርቁ ጋር ደውሏል ፡፡ ይሁንእንጂ ሜዲካል ዳይሬክተሩ ከደቂቃዎች በኋላ ደውሉልኝ ባሉት መሠረት ቢደወልላቸውም ሥልካቸው በመዘጋቱ ምላሻቸውን ማካተት አልተቻለም ፡፡ ያም ሆኖ የሆሰፒታሉ ባልደረባ ነኝ ያሉ አንድ የህክምና ባለሙያ 12 ሰዎች መሞታቸውና ሌሎች በጥይት ተመተው የመጡ 15 ሰዎችን ማየታቸውን ለዶቼ ቬለ አረጋግጠዋል ፡፡

ዶቼ ቬለ DW ለተጨማሪ አስተያየት የጋሞ ዞን ፖሊስንም ሆነ የዞኑ መንግሥት ኮሚኒዩኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ጋር ቢደውልም የሥራ ሃላፊዎቹ ጥሪ ባለመመለሳቸው አስተያየታቸውን ማካተት አልተቻለም ፡፡ ያምሆኖ የዞኑ መንግሥት ኮሚኒዩኬሽን ጉዳዮች መምሪያ በሻራ ቀበሌ ተከሰተ በተባለው ጉዳይ ዙሪያ በተረጋገጠ የፌስ ቡክ ገጹ መግለጫ አውጥቷል ፡፡ መምሪያው በዚሁ መግለጫው በቀበሌው ህገ መንግስታዊ ስርዓትን ለማፍረስና የአካባቢውን ሰላምና ፀጥታ ለማደፍረስ ታጥቆ ሲንቀሳቀስ ነበር ባለው ኃይል ላይ የተሳካ የኦፕሬሽን ሥራ መከናወኑን ገልጿል፡፡በተካሄደው ኦፕሬሽንም ድምፅ አልባ የሆኑ ስለታማ መሣሪያዎችን ጨምሮ ክላሽ፣ ሽጉጥና በርካታ የግልና የቡድን ጦር መሣሪያዎች በቁጥጥር ስር መዋሉን መምሪያው አስታውቋል፡፡

Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
ልዑል ገ/ስላሴ በወንዶች ማራቶን 3ኛ በመውጣት የነሃስ ሜዳልያን ለሀገራችን ኢትዮጵያ አስገኝቷል!

ውድድሩን ዩጋንዳ በበላይነት ስታጠናቅቅ ትውልደ ኢትዮጵያዊው ለእስራኤል የሚሮጠው ማሩ ተፈሪ ሁለተኛ ሆኗል።

@YeneTube @FikerAssefa
Forwarded from YeneTube
Facebook, Twitter, Instagram እና በመሳሳሉት የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ድርጅትዎን ፤ አገልግሎትዎን እና ምርትዎን ማስተዋወቅ ፈልገዋል? እንግዲያውስ መፍትሄው እኛ ጋር ነው።

በማንኛውም Social Media  Boost ለማድረግ ካሰቡ ይደውሉልን፤ በተመጣጣኝ ዋጋ ታማኝና ቀልጣፋ አገልግሎት እንሰጣለን::

ከዚህም በተጨማሪ የቴሌግራም ፕሪሚየም ጨምሮ ለተለያዩ ኢንተርናሽናል አገልግሎቶች ክፍያዎችን መፈጸም ካስፈለግዎ ከስር በተቀመጡ አድራሻዎች ያናግሩን።

Telegram: @adsommar
📞0929334267
👍3
Forwarded from YeneTube
"ትልቅሰው ሪል እስቴት "
በመሃል ካዛንችስ እንደራሴ እጅግ ዘመናዊ አፓርትመንቶችን በማስተዋቂያ ዋጋ መሸጥ ጀምረናል ።
ትልቅ ሰው ሪል እስቴት
🌹 የኔክሰስ ሆቴል
🌹 የግራንድ ሆቴል
🌹 የኢግል ፓክ ኢንዱስትሪያል እና
🌹 የስካይ ፔትሮሊየም እህት ኩባንያ ነው
👉ባለ 2 መኝታ
👉ባለ 3 መኝታ
👉የሚገርም ማራኪ እይታ ያላቸው !!!
👉ግንባታቸው 90% የደረሰ !!!
👉ማስረከቢያ ጊዜ ከ6 ወር -1 አመት
👉ከአማራጭ አከፋፈል ጋር
✍️100% በ1 አመት በ"4"ዙር
✍️50/50 ከባንክ ጋር ከ5-20 አመት
🙏🙏🙏🙏🙏
ለበለጠ መረጃ
@setu1988
+251936606665
👍1