YeneTube
117K subscribers
31.6K photos
485 videos
79 files
3.91K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
Forwarded from YeneTube
💥💥ዘመኑ የሚፈልገውን የቴክኖሎጂ ባለሙያ ሆነው በቀላሉ ከቤት ሆነው የሚሰሩበትን የሶሻል ሚድያ ማስታወቂና አሰራር ስልጠና እንዲሁም መሰረታዊ የኮምፒውተር ኘሮግራሚንግ በቤቶ ሆነው በ 2 ወር ብቻ የተፈላጊ ሙያ ባለቤት ይሁኑ!

- ስልጠናው ቨርቹዋል ስለሆነ በየትኛውም ቦታ ሆነው መማር ይችላሉ!

- ስልጠናውን ሲወስዱ በተግባር የታገዘ ልምምድ እንዲሁም ሲጨርሱ የስራ እድል እናመቻቻለን!

- ስልጠናውን ሲጨርሱ ሰርተፊኬት ያገኛሉ!

- ከተለያዩ ውጭ ሀገር መግዛት የሚችሉበት እንዲሁም የሶሻል ሚድያ ማስታወቂያ መስራት የሚችሉበት የራሳቹን የቨርቹዋል ማስተር ካርድ ያገኛሉ!

- የተለያዩ ኘሮጀክቶችን በመስራት ልምድ ይቀስማሉ!

- የተለያዩ ኦላይን ኮርሶችን በነፃ በቤቶ የሚማሩበት እድል እንሰጣለን!

🎓 ለአዳዲስ ተመራቂ ተማራዎች ልዩ ቅናሽ አዘጋጅተናል!

ለተጨማሪ መረጃ 0954742475 ይደውሉ
ወይንም በቴሌግራም @Bekalu_gebremariam ያዋሩን
Forwarded from Setu
"ትልቅሰው ሪል እስቴት "
በመሃል ካዛንችስ እንደራሴ እጅግ ዘመናዊ አፓርትመንቶችን በማስተዋቂያ ዋጋ መሸጥ ጀምረናል ።
ትልቅ ሰው ሪል እስቴት
🌹 የኔክሰስ ሆቴል
🌹 የግራንድ ሆቴል
🌹 የኢግል ፓክ ኢንዱስትሪያል እና
🌹 የስካይ ፔትሮሊየም እህት ኩባንያ ነው
👉ባለ 2 መኝታ
👉ባለ 3 መኝታ
👉የሚገርም ማራኪ እይታ ያላቸው !!!
👉ግንባታቸው 90% የደረሰ !!!
👉ማስረከቢያ ጊዜ ከ6 ወር -1 አመት
👉ከአማራጭ አከፋፈል ጋር
✍️100% በ1 አመት በ"4"ዙር
✍️50/50 ከባንክ ጋር ከ5-20 አመት
🙏🙏🙏🙏🙏
ለበለጠ መረጃ
@setu1988
+251936606665
Forwarded from YeneTube
🌼 🎁የአዲስ አመት ገጸበረከት ከ ቴዲ አበራ ላንጋኖ ፈርኒቸር የ15% ቅናሽ  ጋር እና ከልዩ ልዩ ስጦታዎች ጋር ይዞላችሁ ከተፍ ብሏል 🌼🎁🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼


  🌼🎁ቴዲ አበራ ላንጋኖ ፈርኒቸር ሀዋሳ 🌼🎁እጅግ ውብና ማራኪ የ2016  የፋሽን ጥግ  የሆኑ  የፈርኒቸር ውጤቶች አቅርበንሎታል 🤗
ስለሆነም ከወዲሁ ለበአሉ ከመቼውም ጊዜ  በላቀ ልዩ ዝግጅት አድርገን ለውድ ደንበኞቻችን እነሆ ብለናል  🙏
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼
 
   ከ ምናቀርባቸው እቃዎች በጥቂቱ፡-
🌼የሌዘር እና የጨርቅ ሶፋዎች

🌼 የአዋቂ እና የህጻን ልጅ አልጋዎች በተለያዩ መጠን እና ዲዛይን

 🌼 ቁ/ሳጥኖች በተለያዩ ዲዛይን

🌼 የምግብ ጠረጴዛዎች በተለያየ ዲዛይን፡-በ6ወንበር,በ8ወንበር፣በ4ወንበር

🌼የሶፋ ጠረጴዛዎች በተለያዩ መጠንና ዲዛይን

 🌼 ዘመናዊ ኪችኖች

🌼  የጫማ ሸልፍ በተለያዩ መጠንና ዲዛይን፡፡
       
                ልዩነታችን
ከጊዜ በኃላ ማሳደስ ቢፈልጉ እንደ አዲስ አድርገን ማደሳችን፣

ከኛ የገዙትን ዕቃዎችን ከረጅም ጊዜ በኀላ  ከአነስተኛ የገንዘብ ጭማሪ ጋር በአዲስ እቃ መለወጣችን ከሌሎች ልዩ ያደርገናል

መጓጓዣና ጫኝ እስከ ቤትዎ ድረስ ከኛው መሆኑ፣
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
በማንኛውም በዓላት ወቅት 15% የዋጋ ቅናሽ የምናደርግ መሆናችን፣
አድራሻችን፡-ሀዋሳ ከአረብ ሰፈር ወደ እርሻ ጣቢያ በሚወስደው መንገድ ከራስ ጤና ሆቴል ፊትለፊት ከንግድ ባንክ አንደኛ ህንጳ ለይ እንገኛለን

በስልክ ቁጥሮቻችን ፡
0924711168 /0912340763 ሀሎ ይበሉን

ለበለጠ መረጃ የቴሌግራም ገጳችንን ይጎብኙ    
: 👇👇👇👇
https://tttttt.me/tedyaberalanganofurniturehawassa
"በየመን ድንበር በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በሳውዲ ዓረቢያ ጦር ተገድለዋል" - ሂዩውማን ራይትስ ዎች

ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብቶች ተከራካሪ ድርጅት ሂዩውማን ራይትስ ዎች << በየመን ድንበር በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በሳውዲ ዓረቢያ ጦር መገደላቸውን >> አጋልጧል።

መቀመጫውን ዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ፣ ኒውዮርክ ያደረገው የሰብዓዊ መብቶች ተከራከሪው ድርጅት ሂዩውማን ራይት ዎች ነሐሴ 15 ቀን 2015 ዓ.ም ባወጣው የምርመራ ሪፖርት <<  የሳውዲ አረቢያ የጸጥታ ሃይሎች በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች ከየመን ለመሻገር ሲሞክሩ መገደላቸውን >> አስታውቋል።

የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቱ ከምስክሮች ጋር ባደረገው ቃለ መጠይቅ፣ በሳተላይት ምስልና በቪዲዮ የታገዘው ሪፖርት ይፋ ባደረገበት ወቅትም <<  ግድያው ሰፊና ስልታዊ መሆኑን >> አስታውቋል፡፡

ሪፖርቱ << የሳዑዲ ጦር፤ ድንበር ጠባቂዎችንና ምን አልባትም ሌሎች ልዩ ክፍሎችን ጨምሮ በቅርብ ዓመታት ውስጥ በመቶዎች ወይንም በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን መግደላቸውንና በህይወት የተረፉትንም ለእስር፣ ለእንግልት፣ አስገድዶ መድፈርና ሌሎች ኢ ሰብዓዊ ድርጊቶችን ፈፅመዋል >> ሲል ወንጅሏል።

ጉዳዩን አስመልክቶም የሳውዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፣ የሳዑዲ የተለያዩ ተቋማት፣ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴርና የሰብአዊ መብት ኮሚሽንን አስተያየት እንዲሰጡ ቢጠይቅም ምላሽ አለማግኘቱን ሂውማን ራይት ዎች ገልጿል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
1👍1
ማይክ ሀመር በኢትዮጵያ ጉዳይ ለመምከር ወደ አውሮፓ ማቅናታቸውን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታወቀ!

የአሜሪካ የምስራቅ አፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሀመር ከነሐሴ 13 ጀምሮ እስከ 19/2015 ድረስ ወደ አውሮፓ በማቅናት፤ ከኅብረቱ አገራት ጋር በኢትዮጵያ ወቅትዊ ጉዳዮችና በህዳሴ ግድብ ዙሪያ እንደሚመክሩ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታውቋል።

የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ በድረገጹ ባሰፈረው መረጃ፤ ማይክ ሀመር በስዊድን ስቶኮልም እና በቤልጂየም ብራስልስ በሚኖራቸው ቆይታ፤ በአውሮፓ ኅብረት የኢትዮጵያ እና ሱዳን ተዎካዮች ጋር ተገናኝተው እንደሚመክሩ አስታውቋል፡፡

በዚህም በቅድሚያ በስቶኮም ዓለም አቀፍ የውሃ ተቋም በተዘጋጀው የዓለም የውሃ ሳምንት መድረክ ላይ እንደሚሳተፉ የተገለጸ ሲሆን፤ በመድረኩ ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ እንደሚመክሩ ተመላክቷል።

እንዲሁም ልዩ መልዕክተኛው በቤልጂየም ብራስልስ በሚኖራቸዉ ቆይታ፤ ከአውሮፓ ኅብረት የኢትዮጵያ ተዎካዮች ጋር ተገናኝተው ኅብረቱ እና አሜሪካ በኢትዮጵያ በአማራ እና በኦሮምያ ክልል የተፈጠረውን ቀውስ በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት እና ሰላማዊ ሰዎችን በመጠበቅ ዙሪያ ምክክር ያደርጋሉ ተብሏል፡፡

በተጨማሪም አምባሳደሩ ከአዉሮፓ ኅብረት ባለስልጣናት ጋር በጋራ በፕሪቶሪያ የተፈረመዉ የሰላም ስምምነት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ በሚደረግበት ሁኔታ፣ ፍትሕ እና ተጠያቂነትን በማስፈን ዙሪያም ከኢትዮጵያ አመራሮች ጋር እንደሚወያዩ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ በመግለጫው አስታውቋል፡፡

[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
ከኢትዮጵያ አጠቃላይ የቆዳ ስፋት ግማሽ ያህሉ መሬት በተፈጥሯዊና በሰው ሰራሽ ምክንያቶች የተጎዳ እንደሆነ ተገለጸ፡፡

ከኢትዮጵያ አጠቃላይ የቆዳ ስፋት ማለትም 54 ሚሊየን ሄክታር የሚሆነው መሬት ለምነቱ የተጎዳ እንደሆነ ጥናቶች አመላክተዋል ሲሉ የተናገሩት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የቴክኒክ ኮሚቴ አስተባባሪ ዶክተር አደፍርስ ወርቁ ናቸው፡፡

ለግጦሽ እና ለእርሻ የሚያገለግለው ይህ አፈር በበርካታ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ምክንያቶች ለምነቱን እንደሚያጣም ጠቁመዋል፡፡አስተባባሪው ይህን የተናገሩት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት በተዘጋጀው አዲስ ወግ የውይይት መድረክ ላይ ነው ሲሆን ከዚህ በተጨማሪም በየዓመቱ 92 ሺ ሄክታር ደን እንደሚጨፈጨፍ ገልጸዋል፡፡

አክለውም ኢትዮጵያ በአፈር መከላትና በአፈር መታጠብ በአንድ ዓመት ብቻ 4.3 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር እንደምታጣም ነው የተናገሩት፡፡ዘላቂ የመከላከል ስራዎች ካልተሰሩ በ20 ዓመት ውስጥ ይህ አሃዝ ወደ 228 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ሊያድግ እንደሚችል በጥናቶች ተገምቷል ብለዋል፡፡

[Ahadu]
@YeneTube @FikerAssefa
በሲዳማ በሙስና ተሳትፈዋል የተባሉ 25 አመራሮችና ባለሞያዎች ታሠሩ!

የሲዳማ ክልላዊ መንግሥት በሙስናና ብልሹ አሠራር ላይ ተሳትፈዋል ያላቸውን 25 አመራርና ባለሞያዎችን ይዞ አሠረ ፤ ክልሉ 10 ከፍተኛ አመራሮችንም ከኃላፊነት አነሳ፡፡የክልሉ መንግሥት ይህን ያስታወቀው ላለፉት ዐሥር ቀናት በሀዋሳ ከተማ ሲያከሄድ የቆየውን የ2015 ዓ.ም የፓርቲና የመንግስት ሥራዎች አፈፃፀም የግምገማ መድረክ ዛሬ ባጠናቀቀበት ወቅት ነው፡፡

በግምገማ መድረኩ ማብቂያ ላይ የማጠቃለያ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ “መድረኩ በሲዳማ ክልል የልማት ሥራዎችን ተደራሽ በማድረግ ረገድ አደናቃፊ ሁኔታዎችን በመታገል ህዝብን የሚጎዱ ተግባራትን አንጥሮ ለማውጣት ትግል የተካሄደበት ነው“ ብለዋል።

በግምገማው በሙስናና በብልሹ አሠራር ላይ ተሳትፈው የተገኙ 25 አመራሮችና ባለሙያዎች በህግ ቁጥጥር ስር ሲውሉ ሌሎች 10 ከፍተኛ አመራሮች ደግሞ ከኃላፊነት እንዲነሱ መደረጉን ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም ከአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት ጋር በተያያዘ ዝርፊያ ፈጽመዋል በተባሉ 97 ሰዎች ላይ ታሳታፊዎችን የመለየትና ተጠያቂ የማድረግ ሥራዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኙ ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቅሰዋል፡፡

ሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ሌብነትና ብልሹ አሠራር መታየቱንና ግምገማው እየተካሄደ ባለበት ወቅት ከተጠያቂነት ለማምለጥ መድረኩን አቋርጠው በመውጣት የሸሹ ሥለመኖራቸውም ርዕሰ መስተዳድሩ መናገራቸውን የክልል መንግሥት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አስታውቋል፡፡

ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ከኃላፊነታቸው ተነስተዋል ሥለተባሉት ዐሥሩ ከፍተኛ አመራር ማንነትም ሆነ የግምገማ መድረኩን አቋርጠው ሸሽተዋል ያሏቸው አመራር በሥም አልጠቀሱም፡፡ያም ሆኖ የሲዳማ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብርሃም ማርሻሎ ባለፈው ዓርብ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረ/ፕ ፀጋዬ ቱኬ ከኃላፊነታቸው መነሳታቸውን መግለጻቸው ይታወቃል፡፡

ከንቲባ ፀጋዬ በመድረኩ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት ሲገባቸው ስብሰባውን ረግጠው መውጣታቸውን በመግለጫቸው የጠቀሱት አቶ አብረሃም ከንቲባው ባሳዩት የሥራ ድክመት ከኃላፊነታቸው እና ከፓርቲ አባልነት እንዲነሱና በህግ እንዲጠየቁ መወሰኑን ተናግረው ነበር፡፡

Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
Betስኬት ለስፖርታዊ ውርርዶች የሚጠቅሙ መረጃዎችን ይዞ ወደናንተ መጥቷል።

ስፖርታዊ ውርርድ(ቤቲንግ) መጫወት ሚያዘወትሩ ከሆነ ይህ ዌብሳይት ጨዋታዎችን ከቁጥራዊ መረጃዎች በመነሳት በጥልቀት በመተንተን የትኛውን ቡድን ወይም Possibility መምረጥ እንዳለብዎ ስራዎን እናቀልሎታለን፤ ትንተናዎቻችንን ሊንኩን በመጫን በነጻ ያንብቡ።

ወደፊትን መገመት ከባድ ቢሆንም እኛ ግን ለእርሶ ለማቅለል ተግተን እንሰራልን!

ለዛሬ የመረጥንላችሁ ጨዋታዎች:
👇👇👇

https://www.betsket.com/አርሴናል፣-ቶሪኖንና-ሁራካንን-የተመለከ/
👍1
ሶማሊያ ቲክቶክ እና ቴሌግራምን አገደች!

ምሥራቅ አፍሪካዊቷ አገር ሶማሊያ ቲክቶክ እና ቴሌግራም የተባሉትን ማኅበራዊ ሚዲያዎችን እንዲሁም 1ኤክስቤት (1XBet) የተባለውን የስፖርት ውርርድ ገጽን እንዲዘጉ አዘዘች።በወጣቶች ዘንድ ሰፊ ተጠቃሚ የላቸው ቲክቶክ እና ቴሌግራም የአሸባሪዎች መረጃ ማስተላለፊያ ሆነዋል ብሏል የሶማሊያ መንግሥት።

መተግበሪያዎቹ “አሸባሪ ድርጅቶች እና ቡድኖች አሰቃቂ የሆኑ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን እንዲሁም ፎቶግራፎችን በማሰራጨት ሕብረተሰቡን ለማሳሳት ጥቅም ላይ ውለዋል” ብሏል የአገሪቱ መንግሥት ባወጣው መግለጫ።የሶማሊያ የኮሚዩኒኬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ በአገሪቱ ያሉ የኢንተርኔት አግልግሎት አቅራቢዎች እስከ ሐሙስ ነሐሴ 18/2015 ዓ.ም. ድረስ ትዕዛዙን ተግባራዊ የማያደርጉ ከሆነ ቅጣት ይጠብቃቸዋል።

ቲክቶክ እና ቴሌግራምን እንዲሁም የስፖርት ውርርድ ገጹን የመዝጋት ውሳኔ የተሰማው የሶማሊያ መንግሥት አልሸባብን ለማጥፋት ዘመቻ ከጀመረች በኋላ ነው።የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በርካታ የሶማሊያ አካባቢዎችን ተቆጣጥሮ የሚገኘውን ጸንፈኛውን እስላማዊ ቡድን አል-ሸባብን በአምስት ወራት ውስጥ አጠፋለሁ ብለው ነበር።

በቅርቡ በሶማሊያ መዲና ሞቃዲሹ ኢንተርኔት እና ማኅበራዊ ሚዲያን በተመለከተ በተካሄደ ኮንፈረንስ ላይ ማኅበራዊ ሚዲያዎች እና ኢንተርኔት በአጠቃላይ በተለይ በወጣቱ ላይ “ሕይወት እስከ ማሳጣት” የሚደርስ ጉዳት እያደረሰ ነው የሚል ሃሳብ በስፋት ተንጸባርቆ ነበር።

Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
የአማራ ክልል መንግስት በአስር ዞኖች እና አንድ የከተማ አስተዳደር ስር ባሉ አካባቢዎች የሚገኙ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ገንዘብ እንዳይንቀሳቀስ አገደ!

የክልሉ መንግስት ይህን ትዕዛዝ ያስተላለፈው፤ በአስሩ ዞኖች እና በደብረ ታቦር ከተማ የሚገኙ የመንግስት መስሪያ ቤቶች የሚጠቀሙባቸው “ደረሰኞች እና ቼኮች በመዘረፋቸው” መሆኑን ገልጿል።የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ እገዳው ተግባራዊ እንዲደረግ፤ የክልሉ “የመንግስት ሀብት ለሚንቀሳቀስባቸው” ባንኮች ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ ዕለት ነሐሴ 9፤ 2015 በጻፈው ደብዳቤ ማሳወቁን የቢሮው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ደሳለኝ አለምነህ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።

እግዱ ከተጣለባቸው አስር ዞኖች መካከል፤ በስራቸው ያሉ ሁሉም መዋቅሮች ላይ  እርምጃው ተግባራዊ የሚደረግባቸው አራቱ ናቸው።የገንዘብ እንቅስቃሴ እገዳው ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ የሚደረገው በምዕራብ ጎጃም፣ ምስራቅ ጎጃም፣ ሰሜን ጎጃም እና ደቡብ ጎንደር ዞኖች እንደሆነ በአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አደራጀው ካሴ ተጽፎ ለባንኮች የተሰራጨው ደብዳቤ ያመለክታል። “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” በተመለከተችው በዚሁ የደብዳቤ ክፍል ላይ እገዳው ተግባራዊ የሚደረግበት ብቸኛ የከተማ አስተዳደር ደብረታቦር ነው። 

የክልሉ መንግስት እገዳ “በተመረጡ አካባቢዎቻቸው” ብቻ ተፈጻሚ የሚሆንባቸው፤ የማዕከላዊ ጎንደር፣ ምዕራብ ጎንደር፣ ሰሜን ሸዋ፣ ሰሜን ወሎ፣ ደቡብ ወሎ ዞኖች እንዲሁም የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር መሆናቸው በደብዳቤው ላይ ሰፍሯል። የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ይህንን ትዕዛዝ በዞኖች ላይ ከማስተላለፉ አራት ቀናት አስቀድሞ የብሔራዊ ባንክ ለሁሉም የሀገሪቱ ባንኮች በጻፈው ደብዳቤ፤ የክልሉ መንግስት በሚያስተዳድራቸው የባንክ ሂሳቦች ስር ያለ ገንዘብ የሚንቀሳቀስበት መንገድ ላይ ገደብ ጥሎ ነበር።

በዚህ ገደብ መሰረት፤ የአማራ ክልል የአስተዳደር ጉዳዮች ክላስተር አስተባባሪ የሆኑት ዶ/ር ሰማ ጥሩነህ እና የክልሉ ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ጥላሁን መሐሪ “በጋራ ፈርመው ትዕዛዝ ካልሰጡ በስተቀር” የክልሉን መስሪያ ቤቶች ገንዘብ ማንቀሳቀስ እንደማይቻል የብሔራዊ ባንክ ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር። የብሔራዊ ባንክ ይህንን ገደብ ያስቀመጠው፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን እንዲያስፈጽም የተቋቋመው ጠቅላይ መመሪያ ዕዝ ያቀረበውን ጥያቄ ተከትሎ ነው። 

ጠቅላይ መምሪያ ዕዙ ለብሔራዊ ባንክ ያቀረበው ጥያቄ፤ የአማራ ክልል መንግስት የባንክ ሂሳቦች “ላልተፈለገ ዓላማ ማስፈጸሚያ እንዳይውሉ እና እንዳይመዘበሩ የጥንቃቄ እርምጃ” እንዲወሰድ የሚያሳስብ ነበር። በዚህ ጥያቄ መሰረት ነሐሴ 5፤ 2015 የተላለፈው የብሔራዊ ባንክ ገደብ ተግባራዊ ሆኖ የቆየው ለአራት ቀናት ብቻ ነው። የብሔራዊ ባንክ ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ በጻፈው ሌላ ደብዳቤ፤ ከአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መመሪያ ዕዝ በቀረበ ጥያቄ ትዕዛዙ መሻሩን አስታውቋል። 

የገደቡ መነሳት የአማራ ክልል መንግስት የባንክ ሂሳቦች፤ በመደበኛው የአስተዳደር ስርዓት እንዲንቀሳቀሱ አድርጓል። ብሔራዊ ባንክ በአማራ ክልል ያለው የገንዘብ ዝውውር ወደ መደበኛ ስርዓቱ እንዲመለስ የተደረገው፤ “የክልሉ ሰላም እና ጸጥታ ተረጋግቶ እየተመለሰ ስለሚገኝ” እንደሆነ በባለፈው ሳምንቱ ደብዳቤው ላይ ጠቅሷል። ሆኖም ይህ ገደብ በተነሳበት ዕለት፤ የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ለባንኮች ሌላ የእግድ ትዕዛዝ አስተላልፏል።

በደብዳቤዉ የተላለፈው ይህ እግድ በአስር ዞኖች እና አንድ የከተማ አስተዳደር ስር ያሉ አካባቢዎችን የሚመለከት እንደሆነ የክልሉ ገንዘብ ቢሮ በደብዳቤው ላይ ዘርዝሯል። “ወረዳዎች ላይ፣ ዞኖች ላይ፣ አሁን በክልሉ በተፈጠረው ጸጥታ ምክንያት አንዳንድ ችግሮች ስላሉ፣ ቼኮች ደረሰኞች የጠፉበት ሁኔታ ስላለ፤ እነሱ እስከሚጣሩ ድረስ ዞኖች የሰጡንን መረጃ መሰረት በማድረግ የባንክ አካውንቶቹ እንዲታገዱ [ተደርጓል]” ሲሉ የክልሉ ገንዘብ ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።

ቢሮው ይህንን እርምጃ የወሰደው “የመንግስት ሀብት ለብልሽት እንዳይዳረግ፣ እንዳይባክን በማሰብ” መሆኑን የሚናገሩት አቶ ደሳለኝ፤ ይህ እግድ የሚቆየው “ዝርፊያ ተፈጸመ” በተባለባቸው አካባቢዎች የሚደረገው ማጣራት እስከሚጠናቀቅ ድረስ እንደሆነ አክለዋል። የማጣራት ስራው ተጠናቅቆ በአካባቢዎቹ የባንክ ሂሳቦች ውስጥ ያለው ገንዘብ እስከሚለቀቅ ድረስ ግን “የስራ ማንቀሳቀሻ እንቅስቃሴዎች የሚቆሙበት ሁኔታ ይፈጠራል” ሲሉ እግዱ ለጊዜው የሚያስከትለው ችግር እንደሚኖር ኃላፊው አምነዋል። 

እገዳው በመንግስት ስራ ላይ መስተጓጎል ሊፈጥር ቢችልም ፤ የመንግስት ሰራተኞች የደመወዝ ክፍያ ግን “እንደማይቋረጥ” አቶ ደሳለኝ ለዜና ወኪሉ መናገራቸውን ዳጉ ጆርናል ከዘገባዉ ተመልክቷል። በዚህ ረገድ ችግር የማይፈጠረው ፤ የመንግስት ሰራተኞች ደመወዝ “በአካውንታቸው [በቀጥታ] የሚገባ” በመሆኑ ምክንያት እንደሆነ አስረድተዋል። 

የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ የገንዘብ እንቅስቃሴ እግድ መጣሉን ቢያረጋገጥም ትዕዛዙ ከተላለፈባቸው አካባቢዎች አንዱ የሆነው የምስራቅ ጎጃም ዞን፤ ይህ አይነቱ ክልከላ እስካሁን በይፋ እንዳልደረሰው ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስታውቋል። የገንዘብ እንቅስቃሴ ላይ ስለተጣለ እግድ “መረጃ” እንዳልደረሳቸው እና እስካሁንም ስለጉዳዩ “አለመስማታቸውን” የሚናገሩት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አያሌው፤ “አሁን ስራ ስለጀመርን፤ የዞን አስተዳደር [ገንዘብ] እናንቀሳቅሳለን” ብለዋል። 

Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
💥💥ዘመኑ የሚፈልገውን የቴክኖሎጂ ባለሙያ ሆነው በቀላሉ ከቤት ሆነው የሚሰሩበትን የሶሻል ሚድያ ማስታወቂና አሰራር ስልጠና እንዲሁም መሰረታዊ የኮምፒውተር ኘሮግራሚንግ በቤቶ ሆነው በ 2 ወር ብቻ የተፈላጊ ሙያ ባለቤት ይሁኑ!

- ስልጠናው ቨርቹዋል ስለሆነ በየትኛውም ቦታ ሆነው መማር ይችላሉ!

- ስልጠናውን ሲወስዱ በተግባር የታገዘ ልምምድ እንዲሁም ሲጨርሱ የስራ እድል እናመቻቻለን!

- ስልጠናውን ሲጨርሱ ሰርተፊኬት ያገኛሉ!

- ከተለያዩ ውጭ ሀገር መግዛት የሚችሉበት እንዲሁም የሶሻል ሚድያ ማስታወቂያ መስራት የሚችሉበት የራሳቹን የቨርቹዋል ማስተር ካርድ ያገኛሉ!

- የተለያዩ ኘሮጀክቶችን በመስራት ልምድ ይቀስማሉ!

- የተለያዩ ኦላይን ኮርሶችን በነፃ በቤቶ የሚማሩበት እድል እንሰጣለን!

🎓 ለአዳዲስ ተመራቂ ተማራዎች ልዩ ቅናሽ አዘጋጅተናል!

ለተጨማሪ መረጃ 0954742475 ይደውሉ
ወይንም በቴሌግራም @Bekalu_gebremariam ያዋሩን
"ትልቅሰው ሪል እስቴት "
በመሃል ካዛንችስ እንደራሴ እጅግ ዘመናዊ አፓርትመንቶችን በማስተዋቂያ ዋጋ መሸጥ ጀምረናል ።
ትልቅ ሰው ሪል እስቴት
🌹 የኔክሰስ ሆቴል
🌹 የግራንድ ሆቴል
🌹 የኢግል ፓክ ኢንዱስትሪያል እና
🌹 የስካይ ፔትሮሊየም እህት ኩባንያ ነው
👉ባለ 2 መኝታ
👉ባለ 3 መኝታ
👉የሚገርም ማራኪ እይታ ያላቸው !!!
👉ግንባታቸው 90% የደረሰ !!!
👉ማስረከቢያ ጊዜ ከ6 ወር -1 አመት
👉ከአማራጭ አከፋፈል ጋር
✍️100% በ1 አመት በ"4"ዙር
✍️50/50 ከባንክ ጋር ከ5-20 አመት
🙏🙏🙏🙏🙏
ለበለጠ መረጃ
@setu1988
+251936606665