በ2015 በጀት ዓመት ለአዲስ አበባ ከተማ የመንግሥት ሠራተኞች ሁለት ነጥብ ስምንት ቢሊዮን ብር የቤት ኪራይ ድጎማ መደረጉን የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የቢሮው ኃላፊ ወይዘሮ ሂክማ ከይረዲን የበጀት ዓመቱን የሥራ እንቅስቃሴ አስመልክተው ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ከቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር ጋር ተያይዞ ከሠራተኞች ጥያቄ ሲነሳ እንደነበር ጠቅሰዋል። የከተማ አስተዳደሩ አመራር ውይይት አድርጎ አቅም በፈቀደ መጠን ሁለት ነጥብ ስምንት ቢሊዮን ብር የቤት ኪራይ ድጎማ መደረጉን ገልጸዋል። ይህም ሠራተኞች ያላቸውን የክፍያ ምጣኔ ታሳቢ ያደረገና እስከ አንድ ሺህ 500ብር እንደሆነ ጠቁመው፤ ይህ አሁን ያለውን መሠረታዊ የቤት ኪራይ ክፍያ ጥያቄ የሚፈታ ባይሆንም በተወሰነ ደረጃ ችግሩን ማቃለል ያስቻለ ነው ብለዋል።
ከኑሮ ውድነቱ ጋር ተያይዞ ሠራተኛው የሚያነሳቸው ጥያቄዎች እንዳሉ የገለጹት ኃላፊዋ፤ በሁሉም የመንግሥት መስሪያ ቤት ካፍቴሪያዎች ላይ የሚከፈሉ ክፍያዎችን በተወሰነ መጠን መንግሥት መደጎም መቻል እንዳለበት ታምኖ በ2015 መመሪያ ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ እንደተገባ አስታውቀዋል።ይህም ሁሉንም ሠራተኛ ታሳቢ የደረገና በአንድ ሠራተኛ የ20 ብር ድጎማ እንደሆነ ገልጸዋል። በሂደቱ መንግሥት ከ20 ብሩ ድጎማ ባሻገር ለካፍቴሪያ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችንና መሰረተ ልማቶችን የማሟላት ሥራ እንደሚፈጽምም ጠቁመዋል።
ሙሉውን ለማንበብ: https://press.et/?p=106158
@YeneTube @FikerAssefa
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የቢሮው ኃላፊ ወይዘሮ ሂክማ ከይረዲን የበጀት ዓመቱን የሥራ እንቅስቃሴ አስመልክተው ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ከቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር ጋር ተያይዞ ከሠራተኞች ጥያቄ ሲነሳ እንደነበር ጠቅሰዋል። የከተማ አስተዳደሩ አመራር ውይይት አድርጎ አቅም በፈቀደ መጠን ሁለት ነጥብ ስምንት ቢሊዮን ብር የቤት ኪራይ ድጎማ መደረጉን ገልጸዋል። ይህም ሠራተኞች ያላቸውን የክፍያ ምጣኔ ታሳቢ ያደረገና እስከ አንድ ሺህ 500ብር እንደሆነ ጠቁመው፤ ይህ አሁን ያለውን መሠረታዊ የቤት ኪራይ ክፍያ ጥያቄ የሚፈታ ባይሆንም በተወሰነ ደረጃ ችግሩን ማቃለል ያስቻለ ነው ብለዋል።
ከኑሮ ውድነቱ ጋር ተያይዞ ሠራተኛው የሚያነሳቸው ጥያቄዎች እንዳሉ የገለጹት ኃላፊዋ፤ በሁሉም የመንግሥት መስሪያ ቤት ካፍቴሪያዎች ላይ የሚከፈሉ ክፍያዎችን በተወሰነ መጠን መንግሥት መደጎም መቻል እንዳለበት ታምኖ በ2015 መመሪያ ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ እንደተገባ አስታውቀዋል።ይህም ሁሉንም ሠራተኛ ታሳቢ የደረገና በአንድ ሠራተኛ የ20 ብር ድጎማ እንደሆነ ገልጸዋል። በሂደቱ መንግሥት ከ20 ብሩ ድጎማ ባሻገር ለካፍቴሪያ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችንና መሰረተ ልማቶችን የማሟላት ሥራ እንደሚፈጽምም ጠቁመዋል።
ሙሉውን ለማንበብ: https://press.et/?p=106158
@YeneTube @FikerAssefa
❤1
ሐሙስ ሐምሌ 27 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በተደረገ ውጊያ ወደ ላሊበላ የሚደረግ የአየር በረራ መቋረጡን የላሊበላ ኤርፖርት ሠራተኞች ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል፡፡
በተጨማሪም በጎንደር ከተማ ከትናንት ጀምሮ በመንግሥት የጸጥታ አካላትና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል እየተደረገ ባለው ውጊያ ምክንያት በዛሬው ዕለት ወደ ጎንደር የሚደረግ የአየር በረራ አለመኖሩን አዲስ ማለዳ አረጋግጣለች።
ዛሬ ረፋድ ላይም በጎንደር አየር ማረፊያ አቅራቢያ የተኩስ ልውውጥ እየተደረገ መሆኑን ነው መረዳት የተቻለው።
የላሊበላ አየር ማረፊያ ሠራተኞች ወደ ላሊበላ በቀን ከሚደረጉ ኹለት በረራዎች የመጀመሪያው ማክሰኞ ሐምሌ 25/2015 ጠዋት ላይ መደረጉን ገልጸው፤ “ተጨማሪ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ላሊበላ አየር ማረፊያ ሊገቡ ነው” የሚል ወሬ የሰሙ የፋኖ ታጣቂዎች ወደ ሥፍራው አቅንተው ጥበቃ ላይ ከነበሩ የፌዴራል ፖሊስ አባላት ጋር የተኩስ ልውውጥ ሲያደርጉ እንደነበር ጠቅሰዋል።
ይህን ተከትሎም በኹለተኛው በረራ ከቀኑ 6 ሰዓት ከ50 ላይ ላሊበላ ኤርፖርት ማረፍ የነበረበት የመንገደኞች አውሮፕላን ካለው የጸጥታ ስጋት አንጻር ሳያርፍ መመለሱን ገልጸዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
በተጨማሪም በጎንደር ከተማ ከትናንት ጀምሮ በመንግሥት የጸጥታ አካላትና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል እየተደረገ ባለው ውጊያ ምክንያት በዛሬው ዕለት ወደ ጎንደር የሚደረግ የአየር በረራ አለመኖሩን አዲስ ማለዳ አረጋግጣለች።
ዛሬ ረፋድ ላይም በጎንደር አየር ማረፊያ አቅራቢያ የተኩስ ልውውጥ እየተደረገ መሆኑን ነው መረዳት የተቻለው።
የላሊበላ አየር ማረፊያ ሠራተኞች ወደ ላሊበላ በቀን ከሚደረጉ ኹለት በረራዎች የመጀመሪያው ማክሰኞ ሐምሌ 25/2015 ጠዋት ላይ መደረጉን ገልጸው፤ “ተጨማሪ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ላሊበላ አየር ማረፊያ ሊገቡ ነው” የሚል ወሬ የሰሙ የፋኖ ታጣቂዎች ወደ ሥፍራው አቅንተው ጥበቃ ላይ ከነበሩ የፌዴራል ፖሊስ አባላት ጋር የተኩስ ልውውጥ ሲያደርጉ እንደነበር ጠቅሰዋል።
ይህን ተከትሎም በኹለተኛው በረራ ከቀኑ 6 ሰዓት ከ50 ላይ ላሊበላ ኤርፖርት ማረፍ የነበረበት የመንገደኞች አውሮፕላን ካለው የጸጥታ ስጋት አንጻር ሳያርፍ መመለሱን ገልጸዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
‹‹ መንግስት የታገቱት ያሉበትን ያሳውቀን ›› የታጋች ቤተሰቦች
‹‹ ባለፈው ሰኞ የታገቱ 62 ሰዎችን ለማስለቀቅ ከፍተኛ ጥረት እያደረግሁ ነው ›› - የፌደራል ፖሊስ
ባለፈው ሰኞ ሐምሌ 24 ቀን 2015 ዓ.ም ከባህርዳር ወደ አዲስ አበባ ለመምጣት ጉዞ የጀመረ ‹‹ ታታ ›› የሕዝብ ማመላለሻ ተሸከርካሪ ውስጥ የነበሩ ተሳፋሪዎች በታጣቂዎች እገታ እንደተፈፀመባቸው › አሻም ከቤተሰቦቻቸው ለመረዳት ችላለች፡፡
‹‹ ታናሽ ወንድሜ ነዉ፤ ዘመድ ለመጠየቅ ነበር ባህርዳር የመጣው፡፡ ስራዉ አዲስ አበባ አንድ የግል ት/ቤት ዉስጥ ጥበቃ ነዉ፡፡ ቤተሰቦቻችን በህይወት የሉም፡፡መንግስት ወንድሞቻችንን ያሉበትን ሁኔታ ያሣዉቀን ›› ሲል አንድ የታጋች ቤተሰብ በአሻም በኩል አቤቱታውን አሰምቷል፡፡
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ጀይላን አብዲ ‹‹ባለፈው ሰኞ የተጋቱት ሰዎች ቁጥር 65 ቢሆንም አሽከርካሪውን ጨምሮ አንድ እናት ልጇ አምልጠው አዲስ አበባ መግባታቸውን›› ለአሻም ነግረዋታል፡፡
በዚህም የታገቾች ቁጥር 63 መሆናቸውን አመልክተው ከአመለጡት ሰዎች በደረሳቸው ጥቆማ መሠረት የታገቱትን ለማስቀቅ ጥረት እያደረጉ መሆኑን ›› ገልፀዋል፡፡የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊው እንደሚሉት ‹‹ በኦሮሚያ ክልል ገብረ ጉረቻ ደብረፅጌ አከባቢ ተደጋጋሚ ዕገታ እንደሚፈፀም ›› ጠቅሰዋል፡፡ይህን ለመከላከል ሕብረተሰቡ ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ አቀርበዋል፡፡
[Asham]
@YeneTube @FikerAssefa
‹‹ ባለፈው ሰኞ የታገቱ 62 ሰዎችን ለማስለቀቅ ከፍተኛ ጥረት እያደረግሁ ነው ›› - የፌደራል ፖሊስ
ባለፈው ሰኞ ሐምሌ 24 ቀን 2015 ዓ.ም ከባህርዳር ወደ አዲስ አበባ ለመምጣት ጉዞ የጀመረ ‹‹ ታታ ›› የሕዝብ ማመላለሻ ተሸከርካሪ ውስጥ የነበሩ ተሳፋሪዎች በታጣቂዎች እገታ እንደተፈፀመባቸው › አሻም ከቤተሰቦቻቸው ለመረዳት ችላለች፡፡
‹‹ ታናሽ ወንድሜ ነዉ፤ ዘመድ ለመጠየቅ ነበር ባህርዳር የመጣው፡፡ ስራዉ አዲስ አበባ አንድ የግል ት/ቤት ዉስጥ ጥበቃ ነዉ፡፡ ቤተሰቦቻችን በህይወት የሉም፡፡መንግስት ወንድሞቻችንን ያሉበትን ሁኔታ ያሣዉቀን ›› ሲል አንድ የታጋች ቤተሰብ በአሻም በኩል አቤቱታውን አሰምቷል፡፡
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ጀይላን አብዲ ‹‹ባለፈው ሰኞ የተጋቱት ሰዎች ቁጥር 65 ቢሆንም አሽከርካሪውን ጨምሮ አንድ እናት ልጇ አምልጠው አዲስ አበባ መግባታቸውን›› ለአሻም ነግረዋታል፡፡
በዚህም የታገቾች ቁጥር 63 መሆናቸውን አመልክተው ከአመለጡት ሰዎች በደረሳቸው ጥቆማ መሠረት የታገቱትን ለማስቀቅ ጥረት እያደረጉ መሆኑን ›› ገልፀዋል፡፡የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊው እንደሚሉት ‹‹ በኦሮሚያ ክልል ገብረ ጉረቻ ደብረፅጌ አከባቢ ተደጋጋሚ ዕገታ እንደሚፈፀም ›› ጠቅሰዋል፡፡ይህን ለመከላከል ሕብረተሰቡ ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ አቀርበዋል፡፡
[Asham]
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራ ክልል የፌደራል መንግስት አስፈላጊውን የህግ ማዕቀፍ እንዲተገብር የክልሉ መንግስት ጠየቀ!
በአማራ ክልል ያጋጠመውን የፀጥታ መደፍረስ በመደበኛ የህግ ማስከበር ሥርዓት ለመቆጣጠር አዳጋች ሆኖ በመገኘቱ የፌደራል መንግስት አስፈላጊውን የህግ ማዕቀፍ እንዲተገብር የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ጠየቀ።
በአማራ ክልል የተከሰተው የሰላም መደፍረስ በክልሉ ከፍተኛ ሰብአዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ እያደረሰ መሆኑን የክልሉ መንግስት አስታውቋል።
የተከሰተውን የፀጥታ ችግር በቁጥጥር ስር ለማዋል እስካሁን በክልሉና በፌደራል የፀጥታ ኃይሎች በኩል በርካታ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸው ይታወቃል።
ሆኖም በክልሉ ያለው የፀጥታ መደፍረስና ጥቃት በንፁሃን ዜጎች ላይ እያደረሰ ያለውን ጉዳት በአስቸኳይ ለማስቆም የፌደራል መንግስት ከመደበኛው የህግ ማስከበር ሥርዓት ባሻገር በኢፌዴሪ ህገ መንግስት መሰረት አስፈላጊውን የህግ ማዕቀፍ በአፋጣኝ እንዲተገበር ነው የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የጠየቀው።
ክልሉ ወደ ቀደመ መረጋጋቱ እንዲመለስ ዜጎች ሰላማቸው ተመልሶ አርሶአደሩ ወደ እርሻው ክልሉም ወደ ልማት ስራዎች ፊቱን እንዲያዞር ለማድረግ መንግስት ያለበትን ኃላፊነት በአግባቡ ሊወጣ ይገባልም በሚል የፌደራል መንግስትን ጠይቋል።
[Walta]
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራ ክልል ያጋጠመውን የፀጥታ መደፍረስ በመደበኛ የህግ ማስከበር ሥርዓት ለመቆጣጠር አዳጋች ሆኖ በመገኘቱ የፌደራል መንግስት አስፈላጊውን የህግ ማዕቀፍ እንዲተገብር የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ጠየቀ።
በአማራ ክልል የተከሰተው የሰላም መደፍረስ በክልሉ ከፍተኛ ሰብአዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ እያደረሰ መሆኑን የክልሉ መንግስት አስታውቋል።
የተከሰተውን የፀጥታ ችግር በቁጥጥር ስር ለማዋል እስካሁን በክልሉና በፌደራል የፀጥታ ኃይሎች በኩል በርካታ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸው ይታወቃል።
ሆኖም በክልሉ ያለው የፀጥታ መደፍረስና ጥቃት በንፁሃን ዜጎች ላይ እያደረሰ ያለውን ጉዳት በአስቸኳይ ለማስቆም የፌደራል መንግስት ከመደበኛው የህግ ማስከበር ሥርዓት ባሻገር በኢፌዴሪ ህገ መንግስት መሰረት አስፈላጊውን የህግ ማዕቀፍ በአፋጣኝ እንዲተገበር ነው የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የጠየቀው።
ክልሉ ወደ ቀደመ መረጋጋቱ እንዲመለስ ዜጎች ሰላማቸው ተመልሶ አርሶአደሩ ወደ እርሻው ክልሉም ወደ ልማት ስራዎች ፊቱን እንዲያዞር ለማድረግ መንግስት ያለበትን ኃላፊነት በአግባቡ ሊወጣ ይገባልም በሚል የፌደራል መንግስትን ጠይቋል።
[Walta]
@YeneTube @FikerAssefa
ቅዱስ ሲኖዶስ በየትኛውም የሀገራችን ክፍል እየተደረጉ ባሉ ግጭቶች ተሳታፊ የሆኑ ወገኖቻችን ካለፈው የጦርነት ውጤት በመማር የተፈጠረውን ችግር በጥበብና በማስተዋል እንዲሁም በሰለጠነ አካሄድና በሰላማዊ መንገድ ተወያይተው እንዲፈቱ ጥሪ አቀረበ!
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ ሐምሌ 27 ቀን 2015 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ወቅታዊ ሀገራዊ ሰላምን በተመለከተ አጀንዳ በመቅረጽ በጉዳዩ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ መግለጫ ሰጥቷል ፤ በመግለጫውም በአሁኑ ወቅት በሀገራችን በተለያዩ ቦታዎች እየተከሰተ ባለው የሰላም መደፍረስና የእርስ በርስ ግጭቶች ምክንያት የበርካታ ወገኖቻችን ውድ ሕይወት እያለፈ እና በርካታ የሀገርና የሕዝብ ሀብትና ንብረት እየወደመ በመሆኑ ቤተ ክርስቲያናችን የተሰማትን ጥልቅ ሐዘን ትገልጻለች ብሏል።
ሰላም ለሰው ልጆች ብቻ ሳይሆን ለሁሉም ፍጡራን መሠረታዊ ጉዳይ ነው፡፡ ሰላም ከሌለ ቀድሶ ማቁረብ፣ ነግዶ ማትረፍ፣ አርሶ ማምረት፣ ተምሮ ማስተማር ወልዶ ማሳደግ፣ ወጥቶ መግባት፣ አገር መምራትና ማስተዳደር አይቻልም ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ በጥቅሉ ሰላም ሲጠፋ አብረው የሚጠፉ መልካም እሴቶቻችን ብዙ ናቸው፡፡ በቅርብ ጊዜ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረው ጦርነት የበርካታ ወገኖቻችንን ሕይወት የቀጠፈ ከመሆኑም በላይ ከሞት የተረፉት ወገኖቻችንም ለስደትና ለረሀብ የዳረገ፣ ለአካልና ለእእምሮ ስብራት ያጋለጠ ከመሆኑም በተጨማሪ በርካታ አድባራትና ገዳማትን እንዲሁም አብያተ ክርስቲያናትን ያፈረሰ እና መተኪያ የሌላቸውን ውድ ቅርሶቻችንን ያወደመ እጅግ በጣም አስከፊ ተግባር መሆኑ ይታወሳል።
በመሆኑም፡-
በሀገራችን በኢትዮጵያ የተከሰተው የእርስ በርስ ጦርነትና ግጭት ተወግዶ ሰላምና አንድነት እንዲሰፍን ከሁሉም በላይ እግዚአብሔርን በጾምና በጸሎት ልንማጸን ይገባል ሲል የገለጸ ሲሆን በሀገራችን በኢትዮጵያ አሁን ያለው የሰላም እጦትና የእርስ በርስ ግጭት ወደፊት ሊያስከትል የሚችለው ችግር ከፍተኛ መሆኑን በመገንዘብ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ለአገራዊ ሰላም የበኩላቸውን ጥረት እንድታደርጉ ቅዱስ ሲኖዶስ መልእክቱን አስተላልፏል።
ቅዱስ ሲኖዶስ በመጨረሻም በየትኛውም የሀገራችን ክፍል እየተደረጉ ባሉ ግጭቶች ተሳታፊ የሆኑ ወገኖቻችን ካለፈው የጦርነት ውጤት በመማር የተፈጠረውን ችግር በጥበብና በማስተዋል እንዲሁም በሰለጠነ አካሄድና በሰላማዊ መንገድ ተወያይተው እንዲፈቱ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሰላም ጥሪዋን ከአደራ ጋር ታስተላልፋለች ሲል መልዕክቱን ማስተላለፉ ተገልጿል።
ሐምሌ 27 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ ሐምሌ 27 ቀን 2015 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ወቅታዊ ሀገራዊ ሰላምን በተመለከተ አጀንዳ በመቅረጽ በጉዳዩ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ መግለጫ ሰጥቷል ፤ በመግለጫውም በአሁኑ ወቅት በሀገራችን በተለያዩ ቦታዎች እየተከሰተ ባለው የሰላም መደፍረስና የእርስ በርስ ግጭቶች ምክንያት የበርካታ ወገኖቻችን ውድ ሕይወት እያለፈ እና በርካታ የሀገርና የሕዝብ ሀብትና ንብረት እየወደመ በመሆኑ ቤተ ክርስቲያናችን የተሰማትን ጥልቅ ሐዘን ትገልጻለች ብሏል።
ሰላም ለሰው ልጆች ብቻ ሳይሆን ለሁሉም ፍጡራን መሠረታዊ ጉዳይ ነው፡፡ ሰላም ከሌለ ቀድሶ ማቁረብ፣ ነግዶ ማትረፍ፣ አርሶ ማምረት፣ ተምሮ ማስተማር ወልዶ ማሳደግ፣ ወጥቶ መግባት፣ አገር መምራትና ማስተዳደር አይቻልም ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ በጥቅሉ ሰላም ሲጠፋ አብረው የሚጠፉ መልካም እሴቶቻችን ብዙ ናቸው፡፡ በቅርብ ጊዜ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረው ጦርነት የበርካታ ወገኖቻችንን ሕይወት የቀጠፈ ከመሆኑም በላይ ከሞት የተረፉት ወገኖቻችንም ለስደትና ለረሀብ የዳረገ፣ ለአካልና ለእእምሮ ስብራት ያጋለጠ ከመሆኑም በተጨማሪ በርካታ አድባራትና ገዳማትን እንዲሁም አብያተ ክርስቲያናትን ያፈረሰ እና መተኪያ የሌላቸውን ውድ ቅርሶቻችንን ያወደመ እጅግ በጣም አስከፊ ተግባር መሆኑ ይታወሳል።
በመሆኑም፡-
በሀገራችን በኢትዮጵያ የተከሰተው የእርስ በርስ ጦርነትና ግጭት ተወግዶ ሰላምና አንድነት እንዲሰፍን ከሁሉም በላይ እግዚአብሔርን በጾምና በጸሎት ልንማጸን ይገባል ሲል የገለጸ ሲሆን በሀገራችን በኢትዮጵያ አሁን ያለው የሰላም እጦትና የእርስ በርስ ግጭት ወደፊት ሊያስከትል የሚችለው ችግር ከፍተኛ መሆኑን በመገንዘብ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ለአገራዊ ሰላም የበኩላቸውን ጥረት እንድታደርጉ ቅዱስ ሲኖዶስ መልእክቱን አስተላልፏል።
ቅዱስ ሲኖዶስ በመጨረሻም በየትኛውም የሀገራችን ክፍል እየተደረጉ ባሉ ግጭቶች ተሳታፊ የሆኑ ወገኖቻችን ካለፈው የጦርነት ውጤት በመማር የተፈጠረውን ችግር በጥበብና በማስተዋል እንዲሁም በሰለጠነ አካሄድና በሰላማዊ መንገድ ተወያይተው እንዲፈቱ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሰላም ጥሪዋን ከአደራ ጋር ታስተላልፋለች ሲል መልዕክቱን ማስተላለፉ ተገልጿል።
ሐምሌ 27 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
በቅዱስ ሲኖዶሱ የተወገዙ የትግራይ ክልል አባቶች ውሳኔውን እንደሚቃወሙና ዳግም እንዲያጤነው ጠየቁ!
በትግራይ ክልል የሚገኙ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶች እና ሓላፊዎች፣ በአክሱም ከተፈጸመው የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ እና ሹመት እንዲሁም፣ ‘መንበረ ሰላማ ከፍተኛ ቤተ ክህነት’ በሚል ከሚያደርጉት ክልላዊ እንቅስቃሴ ጋራ በተያያዘ፣ ትላንት፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተላለፈባቸውን ውግዘት፣ “ከንቱ ውግዘት ነው” ሲሉ እንደማይቀበሉት ገለጹ፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ፣ ሐምሌ 16 እና 23 ቀን 2015 ዓ.ም. በአክሱም የተፈጸመውን ሕገ ወጥ የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት የሰጡ እና የተቀበሉ፣ እንዲሁም ‘መንበረ ሰላማ’ በሚል በክርስቲያናዊ ትውፊት የማይታወቅ እንቅስቃሴ ያመነጩ እና ያስተባበሩ፥ አራት ሿሚ ሊቃነ ጳጳሳትን፣ ዘጠኝ ተሿሚ መነኰሳትንና ሁለት ሌሎች ግለሰቦችን፥ ከማዕርገ ክህነታቸው በመሻር፣ ከቤተ ክርስቲያን አገልግሎት እና አባልነት በመለየት ማውገዙን፣ በትላንትናው መግለጫው አስታውቋል፡፡
ለቅዱስ ሲኖዶሱ የውግዘት መግለጫ መልስ የሰጡት፣ በክልሉ የሚገኙ አባቶች፣ ውግዘቱ፥ የትግራይን ሕዝብ ያለአባት ለማስቀረት የተላለፈ እና በጦርነት ጊዜ የተፈጸመው በደል ቅጥያ ነው፤ ብለዋል።
Via VoA
@YeneTube @FikerAssefa
በትግራይ ክልል የሚገኙ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶች እና ሓላፊዎች፣ በአክሱም ከተፈጸመው የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ እና ሹመት እንዲሁም፣ ‘መንበረ ሰላማ ከፍተኛ ቤተ ክህነት’ በሚል ከሚያደርጉት ክልላዊ እንቅስቃሴ ጋራ በተያያዘ፣ ትላንት፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተላለፈባቸውን ውግዘት፣ “ከንቱ ውግዘት ነው” ሲሉ እንደማይቀበሉት ገለጹ፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ፣ ሐምሌ 16 እና 23 ቀን 2015 ዓ.ም. በአክሱም የተፈጸመውን ሕገ ወጥ የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት የሰጡ እና የተቀበሉ፣ እንዲሁም ‘መንበረ ሰላማ’ በሚል በክርስቲያናዊ ትውፊት የማይታወቅ እንቅስቃሴ ያመነጩ እና ያስተባበሩ፥ አራት ሿሚ ሊቃነ ጳጳሳትን፣ ዘጠኝ ተሿሚ መነኰሳትንና ሁለት ሌሎች ግለሰቦችን፥ ከማዕርገ ክህነታቸው በመሻር፣ ከቤተ ክርስቲያን አገልግሎት እና አባልነት በመለየት ማውገዙን፣ በትላንትናው መግለጫው አስታውቋል፡፡
ለቅዱስ ሲኖዶሱ የውግዘት መግለጫ መልስ የሰጡት፣ በክልሉ የሚገኙ አባቶች፣ ውግዘቱ፥ የትግራይን ሕዝብ ያለአባት ለማስቀረት የተላለፈ እና በጦርነት ጊዜ የተፈጸመው በደል ቅጥያ ነው፤ ብለዋል።
Via VoA
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
✅✅✅ "Do or Die..!" ✅✅✅
የተዋጣለት የሺያጪ ቻናል ፈልገዋል..!!!
ቤት ...❓
መሬት...❓
መካዝን...❓
ኢንዳስትሪ...❓
ኢንቨስትመንት...❓
ሪል ስቴት ..❓
ለትርፍ የሚሆኑ ለ 2 ..3..የሚከፈሉ ቦታዎችን ፈልገዋል ..❓❓❓
አዲስ አበባ ውስጥ የግዙፍ የግዢ እና የሽያጪ ቻናላችን ነው
..የምትወዱትን ሰው የሆነ ፍጥረት ወደ ቻናሉ ቤተሰብ በማደረግ መረጃን በቤትዎ ያስገቡ ..
መረጃን በቀላሉ እንዲያገኙ በማደረግ ሀላፊነታችሁን ተወጡ..!!!
+251937736408
https://tttttt.me/shger21
Inbox @FikreabAmanu
ለበለጠ መረጃ.. ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://tttttt.me/+U2S2JyiWsfAzNzc0
የተዋጣለት የሺያጪ ቻናል ፈልገዋል..!!!
ቤት ...❓
መሬት...❓
መካዝን...❓
ኢንዳስትሪ...❓
ኢንቨስትመንት...❓
ሪል ስቴት ..❓
ለትርፍ የሚሆኑ ለ 2 ..3..የሚከፈሉ ቦታዎችን ፈልገዋል ..❓❓❓
አዲስ አበባ ውስጥ የግዙፍ የግዢ እና የሽያጪ ቻናላችን ነው
..የምትወዱትን ሰው የሆነ ፍጥረት ወደ ቻናሉ ቤተሰብ በማደረግ መረጃን በቤትዎ ያስገቡ ..
መረጃን በቀላሉ እንዲያገኙ በማደረግ ሀላፊነታችሁን ተወጡ..!!!
+251937736408
https://tttttt.me/shger21
Inbox @FikreabAmanu
ለበለጠ መረጃ.. ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://tttttt.me/+U2S2JyiWsfAzNzc0
"ትልቅሰው ሪል እስቴት "
በመሃል ካዛንችስ እንደራሴ እጅግ ዘመናዊ አፓርትመንቶችን በማስተዋቂያ ዋጋ መሸጥ ጀምረናል ።
ትልቅ ሰው ሪል እስቴት
🌹 የኔክሰስ ሆቴል
🌹 የግራንድ ሆቴል
🌹 የኢግል ፓክ ኢንዱስትሪያል እና
🌹 የስካይ ፔትሮሊየም እህት ኩባንያ ነው
👉ባለ 2 መኝታ
👉ባለ 3 መኝታ
👉የሚገርም ማራኪ እይታ ያላቸው !!!
👉ግንባታቸው 90% የደረሰ !!!
👉ማስረከቢያ ጊዜ ከ6 ወር -1 አመት
👉ከአማራጭ አከፋፈል ጋር
✍️100% በ1 አመት በ"4"ዙር
✍️50/50 ከባንክ ጋር ከ5-20 አመት
🙏🙏🙏🙏🙏
ለበለጠ መረጃ
@setu1988
+251936606665
በመሃል ካዛንችስ እንደራሴ እጅግ ዘመናዊ አፓርትመንቶችን በማስተዋቂያ ዋጋ መሸጥ ጀምረናል ።
ትልቅ ሰው ሪል እስቴት
🌹 የኔክሰስ ሆቴል
🌹 የግራንድ ሆቴል
🌹 የኢግል ፓክ ኢንዱስትሪያል እና
🌹 የስካይ ፔትሮሊየም እህት ኩባንያ ነው
👉ባለ 2 መኝታ
👉ባለ 3 መኝታ
👉የሚገርም ማራኪ እይታ ያላቸው !!!
👉ግንባታቸው 90% የደረሰ !!!
👉ማስረከቢያ ጊዜ ከ6 ወር -1 አመት
👉ከአማራጭ አከፋፈል ጋር
✍️100% በ1 አመት በ"4"ዙር
✍️50/50 ከባንክ ጋር ከ5-20 አመት
🙏🙏🙏🙏🙏
ለበለጠ መረጃ
@setu1988
+251936606665
🔥🔥አስቸኳይ ክፍት የስራ ቅጥር💥💥
🔴በሁሉም ስራ ዘርፎች ሰራተኞችን በብዛት እንፈልጋለን።
🔥ቀጥታ ወደ ስራ ቦታ እንልካለን።
📞 ስልክ:- 09 78 88 18 19
09 77 64 18 19
💥ጉዳይ አስፈፃሚ/smart phone ያለው/
🔹የት/ደረጃ:10
🔹የስራ ልምድ: 0አመት ጀምሮ
🔹ደሞዝ:5000+ የቀን አበል
💥ካሸር አሰልጥኖ
🔹የት/ት ደረጃ= 12/ዲፕሎማ
🔹ልምድ= 0 አመት
🔹ደሞዝ= 5,500
💥ባርማን/ባሬስታ
🔹የት/ት ደረጃ= መፃፍ ማንበብ
🔹ልምድ= ያለው
🔹ደሞዝ=በስምምነት
💥ሪሴፕሽን ለገስት ሀውስ/ለሆቴሎች
🔹የት/ደረጃ:10ኛ- ከዚያ በላይ
🔹የስራ ልምድ: 0 አመት ጀምሮ
🔹ደሞዝ፡ 4,500
💥ቤቲንግ ቤት ካሸር (በፈረቃ)
🔹የት/ት ደረጃ= 10ኛ በላይ
🔹የስራ ልምድ=0
🔹ደሞዝ=5000
💥 ሼፍ/ዋና እና ረዳት/
🔹የት/ት ደረጃ= 10ኛ በላይ
🔹የስራ ልምድ=ያለው
🔹ደሞዝ=6000-10,000
▶ለበለጠ መረጃ
🏘አድራሻ: አ.አ 22 ጎላጎል ሲደርሱ ወደ ቦሌ በሚወስደው መንገድ ወረድ ብለው ሎተስ ህንፃ ግራውንድ ላይ ቢ.ቁ 006
👇👇https://tttttt.me/JobsAtHewan
🔴በሁሉም ስራ ዘርፎች ሰራተኞችን በብዛት እንፈልጋለን።
🔥ቀጥታ ወደ ስራ ቦታ እንልካለን።
📞 ስልክ:- 09 78 88 18 19
09 77 64 18 19
💥ጉዳይ አስፈፃሚ/smart phone ያለው/
🔹የት/ደረጃ:10
🔹የስራ ልምድ: 0አመት ጀምሮ
🔹ደሞዝ:5000+ የቀን አበል
💥ካሸር አሰልጥኖ
🔹የት/ት ደረጃ= 12/ዲፕሎማ
🔹ልምድ= 0 አመት
🔹ደሞዝ= 5,500
💥ባርማን/ባሬስታ
🔹የት/ት ደረጃ= መፃፍ ማንበብ
🔹ልምድ= ያለው
🔹ደሞዝ=በስምምነት
💥ሪሴፕሽን ለገስት ሀውስ/ለሆቴሎች
🔹የት/ደረጃ:10ኛ- ከዚያ በላይ
🔹የስራ ልምድ: 0 አመት ጀምሮ
🔹ደሞዝ፡ 4,500
💥ቤቲንግ ቤት ካሸር (በፈረቃ)
🔹የት/ት ደረጃ= 10ኛ በላይ
🔹የስራ ልምድ=0
🔹ደሞዝ=5000
💥 ሼፍ/ዋና እና ረዳት/
🔹የት/ት ደረጃ= 10ኛ በላይ
🔹የስራ ልምድ=ያለው
🔹ደሞዝ=6000-10,000
▶ለበለጠ መረጃ
🏘አድራሻ: አ.አ 22 ጎላጎል ሲደርሱ ወደ ቦሌ በሚወስደው መንገድ ወረድ ብለው ሎተስ ህንፃ ግራውንድ ላይ ቢ.ቁ 006
👇👇https://tttttt.me/JobsAtHewan
👍1
በአማራ ክልል ላይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲታወጅ ተወሰነ!
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 23ኛ መደበኛ ስብሰባ የሕዝብን ሠላምና ደህንነት ለማስጠበቅ በአማራ ክልል ላይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲታወጅ በሙሉ ድምጽ ወሰነ።
የክልሉ መንግስትም በአማራ ክልል ያጋጠመው የፀጥታ መደፍረስ፣ በክልሉ ሰብዓዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት እያስከተለ የሚገኝ መሆኑን በመግለጽ፣ ሁኔታውን በመደበኛው የህግ ማስከበር ሥርዓት ለመቆጣጠር አዳጋች ሆኖ በመገኘቱ፣ የፌደራል መንግስት አስፈላጊውን የህግ ማዕቀፍ በኢፌድሪ ህገ መንግስት መሰረት እንዲደነግግ እና ተገቢውን እርምጃ እንዲወስድ ጥያቄ ማቅረቡን አስታውሷል፡፡
በመሆኑም መደበኛ የህግ ስርዓትን መሰረት አድርጎ ይህን ፈር የለቀቀ እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር አዳጋች ሁኔታ በመፈጠሩ፣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በህገመንግስቱ የተጣለበትን ሃላፊነት ለመወጣት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጅ ስላለበት፣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 6/2015 እንዲታወጅ በሙሉ ድምጽ መወሰኑን አስታውቋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 23ኛ መደበኛ ስብሰባ የሕዝብን ሠላምና ደህንነት ለማስጠበቅ በአማራ ክልል ላይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲታወጅ በሙሉ ድምጽ ወሰነ።
የክልሉ መንግስትም በአማራ ክልል ያጋጠመው የፀጥታ መደፍረስ፣ በክልሉ ሰብዓዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት እያስከተለ የሚገኝ መሆኑን በመግለጽ፣ ሁኔታውን በመደበኛው የህግ ማስከበር ሥርዓት ለመቆጣጠር አዳጋች ሆኖ በመገኘቱ፣ የፌደራል መንግስት አስፈላጊውን የህግ ማዕቀፍ በኢፌድሪ ህገ መንግስት መሰረት እንዲደነግግ እና ተገቢውን እርምጃ እንዲወስድ ጥያቄ ማቅረቡን አስታውሷል፡፡
በመሆኑም መደበኛ የህግ ስርዓትን መሰረት አድርጎ ይህን ፈር የለቀቀ እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር አዳጋች ሁኔታ በመፈጠሩ፣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በህገመንግስቱ የተጣለበትን ሃላፊነት ለመወጣት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጅ ስላለበት፣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 6/2015 እንዲታወጅ በሙሉ ድምጽ መወሰኑን አስታውቋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ ሆነ!
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 23ኛው መደበኛ ስብሰባ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን የራስ ገዝ ማቋቋሚያ ደንብ ላይ ተወያይቶ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ እንዲሆን ወስኗል።
ውሳኔው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአካዳሚክ ነጻነት እንዲረጋገጥ፣ ከፖለቲካዊም ሆነ አስተዳደራዊ ጣልቃ ገብነት ነጻ ሆነው የመማር ማስተማር እና የምርምር ሥራዎችን በላቀ መልኩ መፈጸም እንደሚያስችላቸው የታመነበት በመሆኑ እንደሆነ ተገልጿል።
በዚሁ መሰረትም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ሆኖ አካዳሚያዊ እና አስተዳደራዊ ነፃነቱ ተጠብቆ መንቀሳቅስ እንዲችል፣ በትምህርት ዘርፍ ለተጀመረው የሪፎርም እንቅስቃሴ ፈር ቀዳጅ ሆኖ እንዲወጣ እድል ይፈጥርለታል ተብሏል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ ስርዓትን በቀዳሚነት ተግባራዊ እንደሚያደርግና ለሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችም ተምሳሌት እንደሚሆን ይጠበቃል።
@YeneTube @FikerAssefa
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 23ኛው መደበኛ ስብሰባ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን የራስ ገዝ ማቋቋሚያ ደንብ ላይ ተወያይቶ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ እንዲሆን ወስኗል።
ውሳኔው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአካዳሚክ ነጻነት እንዲረጋገጥ፣ ከፖለቲካዊም ሆነ አስተዳደራዊ ጣልቃ ገብነት ነጻ ሆነው የመማር ማስተማር እና የምርምር ሥራዎችን በላቀ መልኩ መፈጸም እንደሚያስችላቸው የታመነበት በመሆኑ እንደሆነ ተገልጿል።
በዚሁ መሰረትም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ሆኖ አካዳሚያዊ እና አስተዳደራዊ ነፃነቱ ተጠብቆ መንቀሳቅስ እንዲችል፣ በትምህርት ዘርፍ ለተጀመረው የሪፎርም እንቅስቃሴ ፈር ቀዳጅ ሆኖ እንዲወጣ እድል ይፈጥርለታል ተብሏል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ ስርዓትን በቀዳሚነት ተግባራዊ እንደሚያደርግና ለሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችም ተምሳሌት እንደሚሆን ይጠበቃል።
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
የኢቢሲ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ እና የኮርፓሬት ዘርፍ ኃላፊ የነበሩት አቶ ዓባይነህ ሙሉጌታ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ እና የኮርፓሬት ዘርፍ ኃላፊ የነበሩት አቶ ዓባይነህ ሙሉጌታ ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው በዛሬው ዕለት (ሐምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም) በ37 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ እና የኮርፓሬት ዘርፍ ኃላፊ የነበሩት አቶ ዓባይነህ ሙሉጌታ ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው በዛሬው ዕለት (ሐምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም) በ37 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
👍1
#ሰበር_ዜና
የተወካዮች ምክር ቤት አባሉ አቶ ክርስቲያን ታደለ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለፀ
የአብን ፓርቲ አባልና ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባሉ አቶ ክርስቲያን ታደለ ሃምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም በፌደራል ፖሊስ አማካይነት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የሚያመላክቱ መረጃዎች በማህበራዊ ትስስር ገፆች በስፋት እየተዘዋወሩ ይገኛሉ።
የፓርቲው አባል እና በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ክርስቲያን ታደለ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ያስተላለፏቸው መልዕክቶች ለእስራቸው ምክንያት ሳይሆን እንዳልቀረ ተገምቷል።
አባሉ ምንም እንኳን ያለ መከሰስ መብት ቢኖራቸውም በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ አማካይነት በቁጥጥር ስር ሳይውሉ እንዳልቀረ ተጠቁሟል።
ያም ሆኖ ግን አቶ ክርስቲያን ታደለ ታስረዋል መባሉን ተከትሎ ከፓርቲያቸው አብን ሆነ እስሩን ፈፅሟል ከተባለው የመንግስት አካል በኩል የተሰጠ ምላሽ እና ማብራሪያ በይፋ አልወጣም።
Via ዳጉ_ጆርናል
@Yenetube @Fikerassefa
የተወካዮች ምክር ቤት አባሉ አቶ ክርስቲያን ታደለ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለፀ
የአብን ፓርቲ አባልና ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባሉ አቶ ክርስቲያን ታደለ ሃምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም በፌደራል ፖሊስ አማካይነት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የሚያመላክቱ መረጃዎች በማህበራዊ ትስስር ገፆች በስፋት እየተዘዋወሩ ይገኛሉ።
የፓርቲው አባል እና በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ክርስቲያን ታደለ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ያስተላለፏቸው መልዕክቶች ለእስራቸው ምክንያት ሳይሆን እንዳልቀረ ተገምቷል።
አባሉ ምንም እንኳን ያለ መከሰስ መብት ቢኖራቸውም በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ አማካይነት በቁጥጥር ስር ሳይውሉ እንዳልቀረ ተጠቁሟል።
ያም ሆኖ ግን አቶ ክርስቲያን ታደለ ታስረዋል መባሉን ተከትሎ ከፓርቲያቸው አብን ሆነ እስሩን ፈፅሟል ከተባለው የመንግስት አካል በኩል የተሰጠ ምላሽ እና ማብራሪያ በይፋ አልወጣም።
Via ዳጉ_ጆርናል
@Yenetube @Fikerassefa
👍3
Forwarded from YeneTube
✅✅✅ "Do or Die..!" ✅✅✅
የተዋጣለት የሺያጪ ቻናል ፈልገዋል..!!!
ቤት ...❓
መሬት...❓
መካዝን...❓
ኢንዳስትሪ...❓
ኢንቨስትመንት...❓
ሪል ስቴት ..❓
ለትርፍ የሚሆኑ ለ 2 ..3..የሚከፈሉ ቦታዎችን ፈልገዋል ..❓❓❓
አዲስ አበባ ውስጥ የግዙፍ የግዢ እና የሽያጪ ቻናላችን ነው
..የምትወዱትን ሰው የሆነ ፍጥረት ወደ ቻናሉ ቤተሰብ በማደረግ መረጃን በቤትዎ ያስገቡ ..
መረጃን በቀላሉ እንዲያገኙ በማደረግ ሀላፊነታችሁን ተወጡ..!!!
+251937736408
https://tttttt.me/shger21
Inbox @FikreabAmanu
ለበለጠ መረጃ.. ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://tttttt.me/+U2S2JyiWsfAzNzc0
የተዋጣለት የሺያጪ ቻናል ፈልገዋል..!!!
ቤት ...❓
መሬት...❓
መካዝን...❓
ኢንዳስትሪ...❓
ኢንቨስትመንት...❓
ሪል ስቴት ..❓
ለትርፍ የሚሆኑ ለ 2 ..3..የሚከፈሉ ቦታዎችን ፈልገዋል ..❓❓❓
አዲስ አበባ ውስጥ የግዙፍ የግዢ እና የሽያጪ ቻናላችን ነው
..የምትወዱትን ሰው የሆነ ፍጥረት ወደ ቻናሉ ቤተሰብ በማደረግ መረጃን በቤትዎ ያስገቡ ..
መረጃን በቀላሉ እንዲያገኙ በማደረግ ሀላፊነታችሁን ተወጡ..!!!
+251937736408
https://tttttt.me/shger21
Inbox @FikreabAmanu
ለበለጠ መረጃ.. ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://tttttt.me/+U2S2JyiWsfAzNzc0
❤1👍1
Forwarded from YeneTube
"ትልቅሰው ሪል እስቴት "
በመሃል ካዛንችስ እንደራሴ እጅግ ዘመናዊ አፓርትመንቶችን በማስተዋቂያ ዋጋ መሸጥ ጀምረናል ።
ትልቅ ሰው ሪል እስቴት
🌹 የኔክሰስ ሆቴል
🌹 የግራንድ ሆቴል
🌹 የኢግል ፓክ ኢንዱስትሪያል እና
🌹 የስካይ ፔትሮሊየም እህት ኩባንያ ነው
👉ባለ 2 መኝታ
👉ባለ 3 መኝታ
👉የሚገርም ማራኪ እይታ ያላቸው !!!
👉ግንባታቸው 90% የደረሰ !!!
👉ማስረከቢያ ጊዜ ከ6 ወር -1 አመት
👉ከአማራጭ አከፋፈል ጋር
✍️100% በ1 አመት በ"4"ዙር
✍️50/50 ከባንክ ጋር ከ5-20 አመት
🙏🙏🙏🙏🙏
ለበለጠ መረጃ
@setu1988
+251936606665
በመሃል ካዛንችስ እንደራሴ እጅግ ዘመናዊ አፓርትመንቶችን በማስተዋቂያ ዋጋ መሸጥ ጀምረናል ።
ትልቅ ሰው ሪል እስቴት
🌹 የኔክሰስ ሆቴል
🌹 የግራንድ ሆቴል
🌹 የኢግል ፓክ ኢንዱስትሪያል እና
🌹 የስካይ ፔትሮሊየም እህት ኩባንያ ነው
👉ባለ 2 መኝታ
👉ባለ 3 መኝታ
👉የሚገርም ማራኪ እይታ ያላቸው !!!
👉ግንባታቸው 90% የደረሰ !!!
👉ማስረከቢያ ጊዜ ከ6 ወር -1 አመት
👉ከአማራጭ አከፋፈል ጋር
✍️100% በ1 አመት በ"4"ዙር
✍️50/50 ከባንክ ጋር ከ5-20 አመት
🙏🙏🙏🙏🙏
ለበለጠ መረጃ
@setu1988
+251936606665
❤1