YeneTube
117K subscribers
31.6K photos
485 videos
79 files
3.91K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
የሙስሊሙ ማኀበረሰብ በሸገር ከተማ እየተፈፀመ ያለውን መስጂድ የማፍረስ ሒደት በመቃወም በአዲስ አበባ የተቃውሞ ሰልፍ አካኼደ።
@Yenetube @Fikerassefa
የሸገር ከተማን መስጂድ ፈረሳ በመቃወም በአዲስ አበባ የተቃውሞ ሰልፍ ተካሄደ!

በአዲሱ የሸገር ከተማ አስተዳደር እየተፈጸመ የሚገኘውን መስጂድ የማፍረስ ተግባር በመቃወም ሙስሊሙ ማኀበረሰብ በአዲስ አበባ አንዋር መስጂድ የተቃውሞ ሰልፍ አካሂዷል።የሰልፉ ዋነኛ ዓላማም በአዲሱ የሸገር ከተማ አስተዳደር እየተከናወኑ የሚገኙ የመስጂድ ፈረሳዎች በአስቸኳይ እንዲቆም ማሳሰብ መሆኑ ታውቋል።ይህንንም ተከትሎ የአዲስ አበባ ፖሊስ በአንዋር መስጂድ ላይ የተቃውሞ እያደረገ ያለውን ህዝበ ሙስሊም እንዲበተን ማድረጉም ተነግሯል።

የኦሮሚያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ግንቦት 15/2015 በሰጠው መግለጫ፤ በከተማ አስተዳደሩ እየተካሄደ ያለውን የመስጂድ ፈረሳ ያወገዘ ሲሆን፤ ዛሬ ግንቦት 18/2015 በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ ኹሉም መስጂዶች የጁምዓ ኹጥባ መልዕክት በከተማ አስተዳደሩ እየተከናወነ የሚገኘውን የመስጂድ ፈረሳው የተመለከተ እንዲሆን ማሳሰቡን መዘገባችን ይታወሳል።

ምክር ቤቱ በአዲሱ የሸገር ሲቲ ከተማ አስተዳደር ከረመዳን 1 ጀምሮ የፈረሱ መስጂዶች ቁጥር 19 መድረሳቸውን ያስታወቀ ሲሆን፤ እነዚህ የፈረሱት መስጂዶች በከተማ አስተዳደሩ ሥር በሚገኙት በቡራዩ መልካ ኖኖ፣ በኮዬ ፈጬ፣ በሰበታ፣ በፉሪ፣ በአጃምባና ሌሎችም አካባቢዎች እንደሆነ ገልጾ ነበር፡፡በተመሳሳይ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጻፈው ደብዳቤ፤ በሸገር ከተማ እያፈረሱ ስላሉ መስጂዶች አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጥ መጠየቁም ይታወሳል።

[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
የህወሓት ታጣቂ ሃይሎች የመጀመሪያው ዙር የተሃድሶና መልሶ የማቋቋም መርሐ ግብር ተጀመረ!

የህወሓት ታጣቂ ሃይሎች የመጀመሪያው ዙር የተሃድሶና መልሶ የማቋቋም መርሐ ግብር ዛሬ ከመቀሌ ከተማ በቅርብ ርቀት በምትገኘው ኩሐ በይፋ ተጀምሯል።በማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ተወካይ ብርጋዴር ጀነራል ደርቤ መኩሪያ እንደገለጹት÷ በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት በኢትዮጵያ አንጻራዊ ሰላም ሰፍኗል።

“ታጣቂዎች በዚህ ሰላም ተጠቅማችሁ የራሳችሁን ህይወት መቀየርና፥ በክልሉ ብሎም በኢትዮጵያ ልማት መሳተፍ፤ የተፈጠረውን ሰላምም ዘላቂ ለማድረግ መስራት ይኖርባችኋል” ብለዋል።

መንግስት ከልማት አጋሮች ጋር በመተባበር ወደ መደበኛ ህይወታችሁ እስክትመለሱ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ያሉት ምክትል ኮሚሽነሩ፥ ለተሀድሶ የገቡት እስከሚቋቋሙ ድረስ ተገቢው ዕገዛ የሚደረግ መሆኑን ተናግረዋል።የህወሓት ታጣቂ ሀይሎች ተወካይ ብርጋዴር ጀነራል ምግበይ ሀይለ በበኩላቸው፥ “እናንተ የተሀድሶ መርሐ ግብርን አጠናቃችሁ ወደ ህብረተሰቡ ስትመለሱ የልማትና የሰላም ሀይል መሆን አለባችሁ” ብለዋል።

@YeneTube @FikerAssefa
👍1
የማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ጣቢያ እግድ መነሳቱን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን አስታወቀ

@YeneTube @FikerAssefa
ከጁምዓ ሶላት በኋላ በመርካቶ አካባቢ በተፈጠረ ረብሻና ግርግር የሰው ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ!

ዛሬ ረፋድ ላይ በአዲስ አበባ ከተማ አንዋር መስጂድ የጁምዓ ሶላት ከተጠናቀቀ በኋላ በሌሎች አካባቢዎች መስጂዶች ፈርሰዋል በሚል ምክንያት በመርካቶ ዙሪያ በተፈጠረ ረብሻና ግርግር የሁለት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።ፖሊስ ባወጣው መግለጫ በተፈጠረው ረብሻና ግርግር ህግ በማስከበር መደበኛ ሥራ ላይ በነበሩ የፖሊስ አባላት ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት መድረሱንም አስታውቋል።

በተለይም በተለምዶ ጋዝ ተራ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ተፈጥሮ በነበረ ግርግር ሁለት ግለሰቦች ጉዳት ደርሶባቸው ለህክምና ሆስፒታል ከተላኩ በኋላ ሕይወታቸው ማለፉንም ነው የገለጸው።በተጨማሪም አራት ግለሰቦች ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን ህግን ለማስከበር በተሰማሩ 37 የፖሊስ አመራርና አባላት እንዲሁም 15 የሚሆኑ የተለያዩ የፖሊስ አጋዥ ሀይሎች ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸው ለህክምና መላካቸውንም ገልጿል።

ረብሻውን ባስነሱት አካላት በተጨማሪ ንብረትነታቸው የአዲስ አበባ ከተማ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅት በሆኑ ሁለት አውቶቡሶች ላይ ጉዳት መድረሱንም በመግለጫው አመላክቷል።መነሻውን አንዋር መስጂድ ያደረገው ረብሻ በጋዝ ተራ፣ ቆርቆሮ ተራ፣ ሰባተኛ አካባቢ፣ አመዴ እና በተለያዩ አካባቢ ለማዛመት የተሞከረ ቢሆንም በፀጥታ አካሉ ጥረት ረብሻው ሳይስፋፋ መቆጣጠር ተችሏልም ነው ያለው።

[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa
ከሀዋሳከአዳማከሻሸመኔ አስቸኳይ ፖስታ ወደ አዲስ አበባ ያሉበት ድረስ በ 300 ብር ብቻ።

እንዲሁም

Online የገዙትን ልብስ፣ጫማ የተለያዩ እቃዎችን ከአዲስ አበባ እቃው ያለበት ድረስ በመምጣት እንቀበሎታለን። እንዲሁም ሀዋሳአዳማሻሸመኔያሉበት ድረስ እናደርሳለን።

የየኔቲዩብ እህት ድርጅት አዲስ ኤክሰረስ
T.me/Addisexpressdelivery
መርጌታ ጥበቡ የባህል ህክምና መስጫ ማዕከል በቲክቶክ መቷል።

የባህል መድሀኒት ከአባቶቻችን ባገኘነው ትምህርትና ጥበቡ እንዲሁም ከተለያዩ የአፍሪካ እና የአረብ ሀገራት በምናመጣቸው መድለኒቾች ፍቱን ህክምናወችን
እንሰጣለን ።
👉ለኪንታሮት በሽታ ታማሚው ባለበት ከቤቱ ወስዶ በመቀባት ሌላ ገላ ሳይነካ ሳያቆስል ስራ ሳያስቆም ዘላቂ ፈውስ ይሰጣል
👉በሌሊት ለሚሸና
👉ለነገረ በትን
👉ለደም ግፊት
👉ለስኳር ህመም መቀነሻ
👉ለሁሉም ቁርጥማት
👉ለዲስክ መንሸራተት ዘላቂ ፈውስ
👉ለፊት ማድያት
👉ለሳል በሽታ
👉ለግርማሞገስ ለህዝብ መስተፋቅር
👉ለማህጸን እንፌክሽን
👉ለአእምሮ ጭንቀት
👉ለወገብ ህመም
👉ለነርብ
👉ጋኔን አጋንንት የሰውጅ ለያዘው
👉የሚጥል በሽታ

👉ለበለጠ መረጃ አድራሻ ባህርዳር ቀበሌ 11ዲያስፖራ በኮብሉ መጨረሻ ንግድ ባንኩ ላይ።

    ቅርንጫፍ አዲስ አበባ ሳሪስ አደይ አበባ

👉እኒህን እና ሌሎች አገልልግሎቶችን ለማግኔት
                   👎ይደውሉ
👉☎️0917040506
          0912718883

    ቻናሉን ይቀላቀሉ👇
https://tttttt.me/mergatah

👉ቻናሉን በመቀላቀል ሊንኳን በመጫን ጤናወ በቤትወ የባህል ህክምና የእጽዋት የህቡ ስም የጠልሰም ጥቅሞችን ይጋሩ ይፈወሱ

tiktok.com/@u0917040506_0912718883
ዘመኑን የዋጁ ዝንጥ ፣ ጥንቅቅ ብለው የተሰሩ ፈርኒቸሮችን እነሆ ከ #ላንጋኖ_ፈርኒቸር

ላንጋኖ  ፈርኒቸር
ዘመናዊነትና ውበትን የተላበሱ የሀገር ወስጥ የፈርኒቸር ምርቶቻችን፡-
✔️ ለዜርና የጨርቅ ሶፋዎች

✔️ የአዋቂ እና የህጻን ልጅ አልጋዎች በተለያዩ መጠን እና ዲዛይን

✔️  ቁ/ሳጥኖች በተለያዩ ዲዛይን

✔️ የምግብ ጠረጴዛዎች በተለያየ ዲዛይን፡-በ6ወንበር,በ8ወንበር፣በ4ወንበር

✔️ የሶፋ ጠረጴዛዎች በተለያዩ መጠንና ዲዛይን

✔️  ዘመናዊ ኪችኖች

✔️  የጫማ ሸልፍ በተለያዩ መጠንና ዲዛይን…..ወዘተ ሲሆን በእርስዎ ፍላት መሰረት የሚቀርቡ አዳዲስ ዲዛይኖችን ተቀብለን እናዘጋጃለን፡፡
       
       ልዩነታችን
♦️ ከጊዜ በኃላ ማሳደስ ቢፈልጉ እንደ አዲስ አድርገን መሳደሳችን፣

♦️ ያዘዙትን ፈርኒቸር በቁርጥ ቀጠሮ ቀን እናቀርባን፣

♦️ ከኛ የገዙትን ዕቃዎችን ከረጅም ጊዜ በኃላ በአዲስ መለወጥ ሲፈልጉ እንቀበላለን

♦️ መጓጓዣና ጫኝ እስከ ቤትዎ ድረስ ከኛው መሆኑ፣

♦️ ከደንበኞች ለሚቀርቡ ቅሬታዎች አፋጣኝ ምላሽ መስጠታችን

♦️ በማንኛውም በዓላት ወቅት 5% የዋጋ ቅናሽ የሚናደርግ መሆናችን፣

♦️ አዲስ ደንበኛ በርሶዎ በኩል ሲመጣ ማበረታች አዘጋጅተናል
ስለሆነም ለዘላቂ ተጠቃሚነት እና እርካታ የሀገር ውስጥ ፈርኒቸር ምርቶችን ከእኛ ይግዙ፡፡

🛑አድራሻችን፡-ሀዋሳ
ከሳሙኤል ገበያ አዳራሽ ተሻግሮ / ዋንዛ አደባባይ ሳይደርሱ

በሰልክ ቁጥሮቻችን ፡0916581884 /0907212223/0944221511

ይደውሉልን,ይጎበኙን!       
ላንጋኖ ፈርኒቸር
በሀዋሳ የአበራ ላንጋኖ ፈርኒቸር እህት ድርጅት
🔥🔥አስቸኳይ ክፍት የስራ ቅጥር💥💥

🌕ድርጅታችን ከታች በተዘረዘሩ የስራ ዘርፎች ሰራተኞችን በብዛት ይፈልጋል። 

🔥ቀጥታ ወደ ስራ ቦታ እንልካለን።

💥NGO በማንኛውም

     🔹የት/ደረጃ:ዲፕሎማ/ድግሪ
     🔹የስራ ልምድ: 0 ዓመት
     🔹ደሞዝ: 18,500+

💥ሹፌር በሁሉም

     🔹የት/ደረጃ:መፃፍ ማንበብ
     🔹የስራ ልምድ: 0 አመት ጀምሮ
     🔹ደሞዝ:13,500+

💥ስልክ ኦፕሬተር

     🔹የት/ደረጃ: 10 ጀምሮ
     🔹የስራ ልምድ: 0አመት ጀምሮ
     🔹ደሞዝ: 6500

💥ጉዳይ አስፈፃሚ

     🔹የት/ደረጃ:10
     🔹የስራ ልምድ: 0አመት ጀምሮ
     🔹ደሞዝ:7000

💥ባንክ ቤት ፅዳት ተላላኪ

    🔹የት/ደረጃ:10ኛ- ከዚያ በላይ
     🔹የስራ ልምድ: 0አመት ጀምሮ
     🔹ደሞዝ፡4500

💥አካውንታንት

🔹የት/ት ደረጃ= ድግሪ/ድፕሎማ
🔹 ልምድ = 0-2 አመት
🔹ደሞዝ=8500

💥ካሸር አሰልጥኖ

🔹የት/ት ደረጃ= 12/ዲፕሎማ
🔹ልምድ= 0 አመት
🔹ደሞዝ= 5,500

💥ባርማን/ባሬስታ

🔹የት/ት ደረጃ= መፃፍ ማንበብ
🔹ልምድ= ያለው
🔹ደሞዝ=በስምምነት

💥 ዌተር የጧት እና የከሰዓት

     🔹የት/ደረጃ: 10 ከዚያ በላይ
     🔹የስራ ልምድ: 0አመት ጀምሮ
     🔹ደሞዝ: 3500


💥ሪሴፕሽን ለገስት ሀውስ/ለሆቴሎች

     🔹የት/ደረጃ:10ኛ- ከዚያ በላይ
     🔹የስራ ልምድ: 0 አመት ጀምሮ    
     🔹ደሞዝ፡ 4,000

💥ቤቲንግ ቤት ካሸር (በፈረቃ)

🔹የት/ት ደረጃ= 10ኛ በላይ
🔹የስራ ልምድ=0
🔹ደሞዝ=5000

ለበለጠ መረጃ
🏘አድራሻ: አ.አ 22 ጎላጎል ሲደርሱ ወደ ቦሌ በሚወስደው መንገድ ወረድ ብለው ሎተስ ህንፃ ግራውንድ ላይ ቢ.ቁ 006

👇👇https://tttttt.me/JobsAtHewan
በቱኒዚያ ፍልሰተኞች አሻጋሪው በቁጥጥር ሥር ዋለ!

ፍልሰተኞችን በሜዲትሬንያን ባህር ላይ የሚያሻግር ሕገ ወጥ ቡድን አደራጅ ነው በሚል የተጠረጠረን ግለሠብ በቁጥጥር ሥር ማድረጓን ቱኒዚያ ትናንት አስታውቃለች፡፡ከጣልያን ላምፔዱሳ ደሴት 130 ኪ. ሜ. ርቀት ላይ የምትገኘው ቱኒዚያ፣ ወደ አውሮፓ መሻገር ለሚሹ ፍልሰተኞች ተመራጭ አቋራጭ ነች፡፡

ግለሰቡ 24 በሚሆኑ ክሶች ተከሶ፣ በሌለበት የ79 ዓመት እስራት ተፈርዶበት ነበር።ከአገሪቱ ወደ አውሮፓ ለሚደረገው ሕገ ወጥ ጉዙ ዋና አስተባባሪ እንደነበር የቱኒዚያ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር አስታውቀዋል።

ባለፈው መስከረም ባህር ላይ ለሰመጡት 20 የሚሆኑ ቱኒዚያውያን ዕልፈትም ተጠያቂ መሆኑን የአገሪቱ የባህር ድንበር ጠባቂ ኃይል አስታውቋል።የአውሮፓ ኅብረት የድንበር ቁጥጥር ድርጅት እንደሚለው፣ በሜዲትሬንያን በኩል ወደ አውሮፓ የሚደረገው ጉዞ በ300 እጥፍ ማደጉንና፣ 42 ሺሕ 200 ፍልሰተኞች መግባታቸውን አስታውቋል።

Via VoA
@YeneTube @FikerAssefa
ዘመን ባንክ በ1 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ ያስገነባውን ባለ 36 ወለል የዋና መስሪያ ቤት ህንጻ በዛሬው ዕለት አስመርቋል፡፡

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የብሄራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ እና የባንኩ ቦርድ ሊቀመንበር ኤርሚያስ እሸቱን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

የባንኩ ቦርድ ሊቀመንበር ኤርሚያስ እሸቱ በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ዘመን ባንክ ባደረገው ስኬታማ ጉዞ የአገልግሎት አድማሱን በማስፋትና የማዕከላቱን ቁጥር በመጨመር ተደራሽነቱን እያሰፋ ይገኛል ብለዋል፡፡የተመረቀው ባለ 36 ወለል ህንጻ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገበት ጠቁመው ለባንኩ ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል፡፡

የባንኩ ዋና መስሪያ ቤት ህንጻ ለከተማዋ ልዩ ውበት የሚያጎናጽፍ ከመሆኑ ባሻገር ባንኩ የደረሰበትን ከፍታ የሚገልጽ መሆኑንም ጠቁመዋል።የባንኩ ዋና መስሪያ ቤት ህንጻ እጅግ ውብ ተደርጎ እንደተገነባና በርካታ አገልግሎቶች እንደሚሰጥም ተናግረዋል።እስከ 5ኛ ወለል ድረስ መኪና ማቆሚያ ያለው ይህ ህንጻ ከምድር በታች 3 ወለሎችም አሉትም ነው የተባለው።

የህንጻው ወደ ስራ መግባት ባንኩ ለዋና መስሪያቤት ህንጻ ኪራይ በዓመት ሲያወጣ የነበረውን ከ40 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚያስቀር መሆኑም ተገልጿል።ዘመን ባንክ ከ15 ዓመታት በፊት በ87 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር ካፒታል የተመሠረተና በአሁኑ ወቅት በ100 ቅርንጫፎች 35 ቢሊየን ብር ተቀማጭ ገንዘብ እንዳለውም ተገልጸዋል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa