YeneTube
117K subscribers
31.6K photos
485 videos
79 files
3.9K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
ዩክሬን ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዲሚትሮ ኩሌባ ትናንት አዲስ አበባ ውስጥ ከጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ፣ ከአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ እና ከአፍሪካ ኅብረት የወቅቱ ሊቀመንበር የኮሞሮሱ ፕሬዚዳንት አዛሊ አሱማኒ ጋር ተወያይተዋል።

ኩሌባ፣ የአፍሪካ አገራት በዩክሬንና ሩሲያ ጦርነት ላይ ገለልተኛ አቋም ከመያዝ እንዲቆጠቡ በሰጡት መግለጫ መጠየቃቸውን የአገር ውስጥ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። አገራቸው ከአፍሪካዊያን ጋር ላላት ግንኙነት ትኩረት ሳትሰጥ መቆየቷ ስህተት እንደነበርም ኩሌባ ጠቁመዋል ተብሏል።

@YeneTube @FikerAssefa
ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ለማምለጥ በተደረገ ሙከራ፤ ቢያንስ አምስት ታራሚዎች ቆስለው መያዛቸውን የዓይን እማኞች ተናገሩ!

በአዲስ አበባ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት የሚገኙ የተወሰኑ ታራሚዎች ትላንት ለሊት ለማምለጥ ባደረጉት ሙከራ፤ አንድ እስረኛ ሲገደል ቢያንስ አምስቱ መቁሰላቸውን እና አንዱ ሳያይዝ መቅረቱን የአይን እማኞች እና የአካባቢ ነዋሪዎች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። ከቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል የማምለጥ ሙከራ መደረጉን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ያረጋገጠው የፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ግን ያመለጠ እስረኛ “የለም” ብሏል።

ከአስር ዓመት እና ከዚያ በላይ የተፈረደባቸው እስረኞችን ከሚያስተናግደው ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት የማምለጥ ሙከራ የተደረገው፤ ለዛሬ አጥቢያ ትላንት ረቡዕ ግንቦት 16፤ 2015 ለሊት አስር ሰዓት ገደማ መሆኑን “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ያነጋገረቻቸው አንድ የአይን እማኝ እና አምስት የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል። የማምለጥ ሙከራውን ያደረጉት እስረኞች ብዛት 11 መሆኑን ከማረሚያ ቤት ፖሊሶች መስማታቸውን ነዋሪዎቹ አክለዋል።

እንደ ነዋሪዎቹ ገለጻ እስረኞቹ ከማረሚያ ቤቱ አምልጠው መውጣታቸውን ተከትሎ፤ በትንሹ ለአንድ ሰዓት ያህል የቆየ ተኩስ በአካባቢው ሲሰማ ቆይቷል። ድርጊቱ በተፈጸመበት ሰዓት በስራ ምክንያት በአካባቢው እንደነበሩ የተናገሩ አንድ የዓይን እማኝ በበኩላቸው፤ ተኩሱ ይበልጥ ጎልቶ ይሰማ የነበረው በማረሚያ ቤቱ መግቢያ ላይ ባለው አስፓልት መንገድ ላይ እና ተሻግሮ ባሉት አካባቢዎች እንደነበር አስረድተዋል።

Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
🔥🔥አስቸኳይ ክፍት የስራ ቅጥር💥💥

🌕ድርጅታችን ከታች በተዘረዘሩ የስራ ዘርፎች ሰራተኞችን በብዛት ይፈልጋል። 

🔥ቀጥታ ወደ ስራ ቦታ እንልካለን።

💥NGO በማንኛውም

     🔹የት/ደረጃ:ዲፕሎማ/ድግሪ
     🔹የስራ ልምድ: 0 ዓመት
     🔹ደሞዝ: 18,500+

💥ሹፌር በሁሉም

     🔹የት/ደረጃ:መፃፍ ማንበብ
     🔹የስራ ልምድ: 0 አመት ጀምሮ
     🔹ደሞዝ:13,500+

💥ስልክ ኦፕሬተር

     🔹የት/ደረጃ: 10 ጀምሮ
     🔹የስራ ልምድ: 0አመት ጀምሮ
     🔹ደሞዝ: 6500

💥ጉዳይ አስፈፃሚ

     🔹የት/ደረጃ:10
     🔹የስራ ልምድ: 0አመት ጀምሮ
     🔹ደሞዝ:7000

💥ባንክ ቤት ፅዳት ተላላኪ

    🔹የት/ደረጃ:10ኛ- ከዚያ በላይ
     🔹የስራ ልምድ: 0አመት ጀምሮ
     🔹ደሞዝ፡4500

💥አካውንታንት

🔹የት/ት ደረጃ= ድግሪ/ድፕሎማ
🔹 ልምድ = 0-2 አመት
🔹ደሞዝ=8500

💥ካሸር አሰልጥኖ

🔹የት/ት ደረጃ= 12/ዲፕሎማ
🔹ልምድ= 0 አመት
🔹ደሞዝ= 5,500

💥ባርማን/ባሬስታ

🔹የት/ት ደረጃ= መፃፍ ማንበብ
🔹ልምድ= ያለው
🔹ደሞዝ=በስምምነት

💥 ዌተር የጧት እና የከሰዓት

     🔹የት/ደረጃ: 10 ከዚያ በላይ
     🔹የስራ ልምድ: 0አመት ጀምሮ
     🔹ደሞዝ: 3500


💥ሪሴፕሽን ለገስት ሀውስ/ለሆቴሎች

     🔹የት/ደረጃ:10ኛ- ከዚያ በላይ
     🔹የስራ ልምድ: 0 አመት ጀምሮ    
     🔹ደሞዝ፡ 4,000

💥ቤቲንግ ቤት ካሸር (በፈረቃ)

🔹የት/ት ደረጃ= 10ኛ በላይ
🔹የስራ ልምድ=0
🔹ደሞዝ=5000

ለበለጠ መረጃ
🏘አድራሻ: አ.አ 22 ጎላጎል ሲደርሱ ወደ ቦሌ በሚወስደው መንገድ ወረድ ብለው ሎተስ ህንፃ ግራውንድ ላይ ቢ.ቁ 006

👇👇https://tttttt.me/JobsAtHewan
መርጌታ ጥበቡ የባህል ህክምና መስጫ ማዕከል በቲክቶክ መቷል።

የባህል መድሀኒት ከአባቶቻችን ባገኘነው ትምህርትና ጥበቡ እንዲሁም ከተለያዩ የአፍሪካ እና የአረብ ሀገራት በምናመጣቸው መድለኒቾች ፍቱን ህክምናወችን
እንሰጣለን ።
👉ለኪንታሮት በሽታ ታማሚው ባለበት ከቤቱ ወስዶ በመቀባት ሌላ ገላ ሳይነካ ሳያቆስል ስራ ሳያስቆም ዘላቂ ፈውስ ይሰጣል
👉በሌሊት ለሚሸና
👉ለነገረ በትን
👉ለደም ግፊት
👉ለስኳር ህመም መቀነሻ
👉ለሁሉም ቁርጥማት
👉ለዲስክ መንሸራተት ዘላቂ ፈውስ
👉ለፊት ማድያት
👉ለሳል በሽታ
👉ለግርማሞገስ ለህዝብ መስተፋቅር
👉ለማህጸን እንፌክሽን
👉ለአእምሮ ጭንቀት
👉ለወገብ ህመም
👉ለነርብ
👉ጋኔን አጋንንት የሰውጅ ለያዘው
👉የሚጥል በሽታ

👉ለበለጠ መረጃ አድራሻ ባህርዳር ቀበሌ 11ዲያስፖራ በኮብሉ መጨረሻ ንግድ ባንኩ ላይ።

    ቅርንጫፍ አዲስ አበባ ሳሪስ አደይ አበባ

👉እኒህን እና ሌሎች አገልልግሎቶችን ለማግኔት
                   👎ይደውሉ
👉☎️0917040506
          0912718883

    ቻናሉን ይቀላቀሉ👇
https://tttttt.me/mergatah

👉ቻናሉን በመቀላቀል ሊንኳን በመጫን ጤናወ በቤትወ የባህል ህክምና የእጽዋት የህቡ ስም የጠልሰም ጥቅሞችን ይጋሩ ይፈወሱ

tiktok.com/@u0917040506_0912718883
ዘመኑን የዋጁ ዝንጥ ፣ ጥንቅቅ ብለው የተሰሩ ፈርኒቸሮችን እነሆ ከ #ላንጋኖ_ፈርኒቸር

ላንጋኖ  ፈርኒቸር
ዘመናዊነትና ውበትን የተላበሱ የሀገር ወስጥ የፈርኒቸር ምርቶቻችን፡-
✔️ ለዜርና የጨርቅ ሶፋዎች

✔️ የአዋቂ እና የህጻን ልጅ አልጋዎች በተለያዩ መጠን እና ዲዛይን

✔️  ቁ/ሳጥኖች በተለያዩ ዲዛይን

✔️ የምግብ ጠረጴዛዎች በተለያየ ዲዛይን፡-በ6ወንበር,በ8ወንበር፣በ4ወንበር

✔️ የሶፋ ጠረጴዛዎች በተለያዩ መጠንና ዲዛይን

✔️  ዘመናዊ ኪችኖች

✔️  የጫማ ሸልፍ በተለያዩ መጠንና ዲዛይን…..ወዘተ ሲሆን በእርስዎ ፍላት መሰረት የሚቀርቡ አዳዲስ ዲዛይኖችን ተቀብለን እናዘጋጃለን፡፡
       
       ልዩነታችን
♦️ ከጊዜ በኃላ ማሳደስ ቢፈልጉ እንደ አዲስ አድርገን መሳደሳችን፣

♦️ ያዘዙትን ፈርኒቸር በቁርጥ ቀጠሮ ቀን እናቀርባን፣

♦️ ከኛ የገዙትን ዕቃዎችን ከረጅም ጊዜ በኃላ በአዲስ መለወጥ ሲፈልጉ እንቀበላለን

♦️ መጓጓዣና ጫኝ እስከ ቤትዎ ድረስ ከኛው መሆኑ፣

♦️ ከደንበኞች ለሚቀርቡ ቅሬታዎች አፋጣኝ ምላሽ መስጠታችን

♦️ በማንኛውም በዓላት ወቅት 5% የዋጋ ቅናሽ የሚናደርግ መሆናችን፣

♦️ አዲስ ደንበኛ በርሶዎ በኩል ሲመጣ ማበረታች አዘጋጅተናል
ስለሆነም ለዘላቂ ተጠቃሚነት እና እርካታ የሀገር ውስጥ ፈርኒቸር ምርቶችን ከእኛ ይግዙ፡፡

🛑አድራሻችን፡-ሀዋሳ
ከሳሙኤል ገበያ አዳራሽ ተሻግሮ / ዋንዛ አደባባይ ሳይደርሱ

በሰልክ ቁጥሮቻችን ፡0916581884 /0907212223/0944221511

ይደውሉልን,ይጎበኙን!       
ላንጋኖ ፈርኒቸር
በሀዋሳ የአበራ ላንጋኖ ፈርኒቸር እህት ድርጅት
መንግስት በኢንተርኔት ሚዲያዎች እየመጣበት ያለዉን ተቃዉሞ ለመመከት በሚመስል መልኩ ለፋና ብሮድካስቲንግ እና ለዋልታ ዳጎስ ያለ የገንዘብ ድጋፍ እያደረገ ነው ተባለ!

በፓርቲ ንብረትነት ለሚታወቁት ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እና ለዋልታ ሚድያ እና ኮሚኒኬሽን ኮርፖሬት ባልተለመደ መልኩ የፌደራሉ መንግስት  በርካታ መጠን ያለው ገንዘብ ድጎማ እያደረገላቸው መሆኑን ዋዜማ ያገኘችው መረጃ ያመለክታል።

የሚድያ ተቋማቱ ገንዘቡን ስራቸውን ለማስፋፊያ እንዲሁም ለሰራኞቻቸው ደሞዝ ጭማሪ እና ማሻሻያዎችን ለመተግበር ይጠሙበታል ተብሏል። ሁለቱ ሚድያዎች በኢህአዴግ ጊዜ ከአራቱ እህት ድርጅቶች የቦርድ አባላት የሚሾሙላቸው ፣ እንዲሁም አመታዊ ትርፋቸውን በኢህአዴግ እህት ድርጅቶች ከሚተዳደሩ ኩባንያዎች ጋር የሚከፋፈሉት ነው። ገንዘብ ሲያስፈልጋቸውም ከባንኮች ይበደሩ ይሆናል እንጂ በቀጥታ በፌደራሉ መንግስት በኩል አይሰጣቸውም ነበር።

ዋዜማ ከምንጮቿ እንደሰማችው ዋልታ ሚድያ እና ኮሚኒኬሽን ኮርፖሬት እስከ ሁለት ቢሊየን ብር ከመንግስት እንደሚያገኝ እንደሚያገኝ ታሳቢ አድርጎ ዕቅድ አውጥቷል። የገንዘቡን መጠን ፣ እንዲሁም ገንዘቡ የሚሰጠው በብድር ይሁን በልግስና ከተቋሙ አመራሮች ለማረጋገጥ ያደረግነው ጥረት አልተሳካም። ይሁንና የሚዲያ ተቋሙ አመራሮች ገንዘቡን ለማግኘት ከገንዘብ ሚኒስቴር ሰዎች ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶችን ሲያደርጉ እንደነበር ተረድተናል። 

ዋልታ ሚድያ እና ኮሚኒኬሽን ኮርፖሬት የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የቅርብ ሰው እንደሆኑ በሚነገርላቸው እና “ሰውዬው” የሚለውን መጽሀፍ በጻፉት መሀመድ ሀሰን በዋና ስራ አስፈፃሚነት እየመሩት ይገኛሉ።

ተቋሙን ሰፋፊ የፕሮግራም ማሻሻያዎችን ለማድረግ ፣ የህንፃና እና ስቱዲዮ ግንባታዎችን ለማከናወን እየተዘጋጀ መሆኑን ሰምተናል። እንዲሁም ለሰራተኞች የደሞዝ እና ጥቅማ ጥቅም ማስተካከያ ባለፉት ቀናት አድርጓል።ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በበኩሉ ድጎማን ለመቀበል  ሰሞኑን ከገንዘብ ሚኒስቴር ምላሽ እየተጠባበቀ ይገኛል።

እነዚህ መገናኛ ብዙሀን ከመንግስት ለመጀመሪያ ጊዜ ድጎማ ያገኙት በኮቪድ ወረርሽኝ ወቅት በሰላም ሚኒስቴር በኩል ገንዘብ ፈሰስ በተደረገላቸው ወቅት ነበር። በውጪ ሀገራትና በሀገር ቤት በመንግስት ላይ ተቃውሞና ትችት የሚያቀርቡ የኢንተርኔት ሚዲያዎች መበራከታቸው እንዲሁም በመንግስት ላይ የተደራጀ የተቃውሞ ዘመቻዎች መጀመራቸው መንግስት በሙሉ አቅሙ ተቃውሞውን ለመመከት አስቦ ሚዲያዎች ላይ ትኩረት አድርጓል ብለው እንደሚገምቱ አንድ የፋና ብሮድካስት የስራ ሀላፊ ነግረውናል። 

ዋልታም ሆነ ፋና የኢህአዴግ መክሰምን ተከትሎ ብልፅግና ሲመሰረት በየኢህአዴግ አባል ድርጅቶች መካከል በነበረው አለመግባባት እንድም እንዲፈርሱ አልያም ባለቤትነቱ ለሌላ አካል እንዲተላለፍ የሚሉ አማራጮች ቀርበው ነበር። በወቅቱ የብልፅግና ሊቀመንበር በሚዲያ ተቋማቱ ዕጣ ፈንታ ላይ ጥናት እንዲደረግና እንዲቀርብ አዘዙ።

ጥናቱ የሚዲያ ተቋማቱ ወደ ሕዝብ ንብረትነት ቢዛወሩ የተሻለ መሆኑን አልያ ግን ከመዘጋት ውጪ አማራጭ እንደሌላቸው ምክረ ሀሳብ አቀረበ። ይሁንና “የፖለቲካ ፍላጎት” እንዳለው የሚነገርለት “ቡድን” አጀንዳውን አደፋፍኖ ተቋማቱን በበላይነት መቆጣጠር ችሏል ይላሉ ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁና በሂደቱ የተሳተፉ ምንጮች።

[ዋዜማ]
@YeneTube @FikerAssefa
በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት በትግራይ ክልል ከ2 ሺሕ 100 በላይ መምህራን እና 1 ሺሕ 700 ተማሪዎች መሞታቸው ተገለጸ!

በሰሜን ኢትዮጵያ ለኹለት ዓመት በቆየው ጦርነት ምክንያት በትግራይ ክልል ብቻ፤ 2 ሺሕ 146 መምህራን እና 1 ሺሕ 700 ተማሪዎች መሞታቸውን የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም አስታውቋል፡፡ተቋሙ በክልሉ በርካታ ትምህርት ቤቶች ላይ መጠነ ሰፊ ውድመት መድረሱን ገልጾ፤ በጦርነቱ በትምህርት ዘርፉ ላይ የደረሰውን የጉዳት መጠን በገንዘብ ተመን በተመለከተ የሚካሄደው ጥናት አለመጠናቀቁን ጠቅሷል፡፡

የተማሪዎችና የመማሪያ ክፍል ጥምርታን በተመለከተም፤ ከጦርነቱ በፊት በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በአንድ መማሪያ ክፍል ውስጥ በአማካኝ 39 ተማሪዎች ይማሩ የነበረ ሲሆን፣ ከጦርነቱ በኋላ አንድ መማሪያ ክፍል ለ434 ተማሪዎች ሆኗል ነው የተባለው፡፡በኹለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲሁ ከጦርነቱ በፊት ለ43 ተማሪዎች መማሪያ የነበረ አንድ ክፍል ከጦርነቱ በኋላ ለ365 ተማሪዎች መማሪያ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

ሆኖም ጉዳት የደረሰባቸው የትምህርት ተቋማቱን መልሶ ለማቋቋም ከፍተኛ፣ መካከለኛ እና ዝቅተኛ ጉዳት የደረሰባቸውን በመለየት፣ ጥገና ለማድረግ የአጭር እና የረዥም ጊዜ እቅድ መዘጋጀቱ ተገልጿል፡፡በሌላ በኩል በአጠቃላይ በክልሉ የጤና ሴክተር ላይ ከ65 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ የሚተመን ጉዳት መድረሱን ነው ተቋሙ ያስገነዘበው፡፡

በጦርነቱ ጉዳት የደረሰባቸው የጤና ተቋማት ተለይተው ለጤና ሚኒስቴር እና ለክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ቢቀርብም በጀት ተፈቅዶ እስካሁን የተሰራው ስራ የሚፈለገውን ያህል አይደለም ተብሏል፡፡የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ጉዳት የደረሰባቸው አገልግሎት ሰጭ ተቋማትን መልሶ ለማቋቋም እና ተፈናቃዮች ያሉባቸውን የመጠለያና የምግብ ችግሮች ለማቃለል የብዙ ባለድርሻ አካላትን አስተዋጾ የሚጠይቅ ስለሆነ ሁሉም ድጋፍ ሊያደርግ ይገባል ሲል አሳስቧል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
👍1
የዳያስፖራ አባላት የገንዘብ፣ ጉዞ እና መዋእለ ንዋይ እቀባ ዘመቻ በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ጀምረዋል።

ውጭ ሃገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የሲቪል ማኅበራት «ግፈኛ አገዛዝ» ያሉት መንግሥት ላይ የገንዘብ ተጽእኖ ለማሳደር ዘመቻ ጀምረዋል። ማኅበራቱ ዘመቻቸው፦ ኢትዮጵያ ውስጥ በገዢው ብልጽግና መንግሥት ይፈጸማል ያሉትን ኢ-ፍትኃዊነትና ዘረኝነት በመቃወም፤ ትኩረቱ ፍትሕ ላይ ያተኮረ መሆኑንም ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያን የዳያስፖራው ማኅበረሰብም ወደ ሀገር ቤት የሚልከውን ገንዘብ በባንኮች እንዳይጠቀም ጥሪ አስተላልፈዋል። ሰዎች ወደ ኢትዮጵያ የሚያደረጓቸውን ጎዞዎች እንዲያቋርጡ እና መዋእለ ንዋይ ፍሰት (ኢንቨስትመንት) ለማደርግ የሚደረጉ ሂደቶች በአጠቃላይም መቋረጥ አለበት ብለዋል።

ከሰሞኑ የኢትዮጵያ ገንዘብ ሚንሥትር አህመድ ሽዴ ባቀረቡት ዘገባ፦ የፌድራል መንግሥት የበጀት ጉድለት እንደገጠመው ይፋ አድርገዋል።የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በሀገሪቱ ኤኮኖሚ ላይ 28 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ኪሳራ ማድረሱን ዐሳውቀዋል ። ሚንስትሩ ጉድለት ያሉትን ለመሸፈንም ከአገር ውስጥ 194.6 ቢሊዮን ብር በብድር መንግስት መውሰዱን ገልጸዋል። «ብድሩም የተገኘው ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ቀጥታ ብድር፣ ከትሬዠሪ ቦንድ እንዲሁም ከትሬዠሪ ቢል ነው።ካሉት የፋይናንስ ተቋማት 194.6 ቢሊዮን ብር የበጀት ጉድለቱን ለመሸፈን ሬይዝ ተደርጓል»ም ብለዋል ። መንግስት ከፍተኛ የገንዘብ ችግር እንደገጠመው፤ የኑሮ ውድነቱም በከፍተኛ ደረጃ ማኅበረሰቡን እንዳማረረው የሚወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
የአፍሪካ ኅብረት በትግራይ ክልል ተዋጊዎችን ማሰናበት እና መልሶ ማዋሐድ በአፋጣኝ እንዲተገበር አሳሰበ!

በፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት መሠረት፣ “የትግራይ ተዋጊዎች ኃይል” የተባለውን ታጣቂ አደረጃጀት የማፍረስ ሒደት እና ተዋጊዎችን ወደ ሰላማዊ ኑሮ መልሶ የማዋሐድ፣ እንዲሁም ተፈናቃዮችን ወደ ቀዬአቸው የመመለስ ሥራዎች፣ በአስቸኳይ ሊተገበሩ እንደሚገባ፣ የአፍሪካ ኅብረት አሳሰበ፡፡አህጉራዊ ኅብረቱ፣ በፌዴራል መንግሥቱ እና በህወሓት መካከል፣ ባለፈው ጥቅምት ወር በፕሪቶርያ የተደረሰውን የሰላም ስምምነት ትግበራ ሒደት መገምገሙን፣ በአወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡በጉዳዩ ላይ፣ የትግራይ ክልል የኮምዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤትንና የፖለቲካ ሳይንስ ምሁርን አስተያየት ጠይቀናል፡፡

በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ መንግሥት በእና በህወሓት መካከል፣ ባለፈው ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም. በደቡብ አፍሪካ-ፕሪቶርያ የተደረሰውን የሰላም ስምምነት ትግበራ ሒደት የሚከታተለው እና የሚቆጣጠረው የአፍሪካ ኅብረት ቡድን፣ ትላንት ረቡዕ፣ ግንቦት 16 ቀን 2015 ዓ.ም.፣ ከኢትዮጵያ መንግሥት፣ ከህወሓት እንዲሁም ከኢጋድ ተወካዮች ጋራ በመኾን፣ አፈጻጸሙን መገምገሙን፣ የአፍሪካ ኅብረት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል::በዘላቂነት ተኩስ የማቆም ስምምነቱ መሠረት፣ የትግራይ ተዋጊዎች ከባድ ትጥቆችን እንደፈቱ፣ ቀላል እና መካከለኛ ትጥቆችን ደግሞ በማስረከብ ሒደት ላይ እንዳሉ መግለጫው አመልክቷል፡፡

በትግራይ ክልል፥ ያልተገደበ ሰብአዊ ርዳታ እንዲገባ ማመቻቸት፣ መሠረታዊ አገልግሎቶች ማለትም የጤና፣ የትራንስፖርት፣ የንግድ እንቅስቃሴ መጀመር እና የትምህርት ቤቶች በአብዛኛው የክልሉ አከባቢዎች ዳግም መከፈት የሚሉት፣ በጋራ ግምገማው በአዎንታዊነት መጠቀሳቸውን መግለጫው ጠቅሷል፡፡በሌላ በኩል፣ በጦርነቱ ወቅት፣ በትግራይ ክልል የነበረውን የተዋጊዎች አደረጃጀት ማፍረስ እና ወደ ሰላማዊ ኑሮ መልሶ የማደራጀት ሥራው፣ በአፋጣኝ መተግበር እንዳለበት የጋራ ግምገማው ማሳሰቡን መግለጫው አመልክቷል፡፡

ነገ ዐርብ፣ ግንቦት 18 ቀን 2015 ዓ.ም.፣ የሰላም ስምምነቱ ፈራሚ የኾነው ህወሓት፥ የተዋጊዎቹን፣ የመካከለኛ እና ቀላል የጦር መሣርያዎች፣ ለኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እንደሚያስረክብና ተዋጊዎቹን የማሰናበት ሥራ ደግሞ በይፋ እንደሚጀመር ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡የሰላማዊ ዜጎችን ደኅንነት በመጠበቅ ረገድ፣ ተፈናቃዮችን ወደ ቀዬአቸው የመመለሱ ሥራም እንዲተገበር፣ የአፍሪካ ኅብረት በመግለጫው አሳስቧል፡፡

የትግራይ ክልል ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ሓላፊ አቶ ረዳኢ ሓለፎም፣ በሰላም ስምምነቱ መሠረት፣ ተፈናቃዮች ወደ ቀዬአቸው ከመመለሳቸው አስቀድሞ፣ የውጭ ወታደሮች እና የኢትዮጵያ መከላከያ ያልኾኑ ኃይሎች፣ ከክልሉ መውጣት ይገባቸዋል፤ ብለዋል፡፡

የአፍሪካ ኅብረት ያወጣውን መግለጫ አስመልክቶ ማብራርያ የሰጡን፣ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር አቶ ገብረ መድኅን ገብረ ሚካኤል፣ የትጥቅ መፍታቱ እና ተዋጊዎችን በትኖ ወደ ቀድሞ ሕይወት የመመለሱ ሥራ፣ ከሌሎች አገሮች ተሞክሮ አኳያ፣ ጊዜ የሚወስድ ተግባር እንደኾነ ጠቅሰው፣ በፕሪቶርያው ስምምነት አተገባበር ግን፣ “ሒደቱ እየተቀላጠፈ ነው፤” በማለት ተናግረዋል፡፡

የአፍሪካ ኅብረት ባወጣው መግለጫ፣ በአብዛኛው የክልሉ አካባቢዎች፣ መሠረታዊ ሕዝባዊ አገልግሎቶች ተጀምሯል፤ የተባለው፣ “የተጋነነ አገላለጽ ነው፤ ገና ብዙ መሥራት ያስፈልገዋል፤” ብለዋል፣ አቶ ገብረ መድኅን፡፡የፖለቲካ ሳይንስ መምህሩ፣ የሰላም ስምምነት ሂደቱ እንዳይደናቀፍ ፣ በትኩረት ሊሠሩ ይገባል ያሏቸውንም ጉዳዮች አንሥተዋል፡

የፕሪቶርያውን የሰላም ስምምነት ትግበራ የሚከታተለውና የሚቆጣጠረው ቡድን፣ ሥራው፥ እስከ ታኅሣሥ 2023 እንዲቀጥልም፣ በትላንትናው ዕለት መወሰኑን፣ የኅብረቱ መግለጫ አስታውቋል፡፡በመጨረሻም፣ የኢትዮጵያ መንግሥት እና ህወሓት፣ “ለኣፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ” በሚለው አህጉራዊ መርሕ መሠረት፣ ጉዳዩ እልባት እንዲያገኝ እያሳዩ ለሚገኙት ተነሣሽነት እና ትብብር፣ ኅብረቱ በመግለጫው አመስግኗል፡፡

Via VoA
@YeneTube @FikerAssefa
የሙስሊሙ ማኀበረሰብ በሸገር ከተማ እየተፈፀመ ያለውን መስጂድ የማፍረስ ሒደት በመቃወም በአዲስ አበባ የተቃውሞ ሰልፍ አካኼደ።
@Yenetube @Fikerassefa
የሸገር ከተማን መስጂድ ፈረሳ በመቃወም በአዲስ አበባ የተቃውሞ ሰልፍ ተካሄደ!

በአዲሱ የሸገር ከተማ አስተዳደር እየተፈጸመ የሚገኘውን መስጂድ የማፍረስ ተግባር በመቃወም ሙስሊሙ ማኀበረሰብ በአዲስ አበባ አንዋር መስጂድ የተቃውሞ ሰልፍ አካሂዷል።የሰልፉ ዋነኛ ዓላማም በአዲሱ የሸገር ከተማ አስተዳደር እየተከናወኑ የሚገኙ የመስጂድ ፈረሳዎች በአስቸኳይ እንዲቆም ማሳሰብ መሆኑ ታውቋል።ይህንንም ተከትሎ የአዲስ አበባ ፖሊስ በአንዋር መስጂድ ላይ የተቃውሞ እያደረገ ያለውን ህዝበ ሙስሊም እንዲበተን ማድረጉም ተነግሯል።

የኦሮሚያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ግንቦት 15/2015 በሰጠው መግለጫ፤ በከተማ አስተዳደሩ እየተካሄደ ያለውን የመስጂድ ፈረሳ ያወገዘ ሲሆን፤ ዛሬ ግንቦት 18/2015 በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ ኹሉም መስጂዶች የጁምዓ ኹጥባ መልዕክት በከተማ አስተዳደሩ እየተከናወነ የሚገኘውን የመስጂድ ፈረሳው የተመለከተ እንዲሆን ማሳሰቡን መዘገባችን ይታወሳል።

ምክር ቤቱ በአዲሱ የሸገር ሲቲ ከተማ አስተዳደር ከረመዳን 1 ጀምሮ የፈረሱ መስጂዶች ቁጥር 19 መድረሳቸውን ያስታወቀ ሲሆን፤ እነዚህ የፈረሱት መስጂዶች በከተማ አስተዳደሩ ሥር በሚገኙት በቡራዩ መልካ ኖኖ፣ በኮዬ ፈጬ፣ በሰበታ፣ በፉሪ፣ በአጃምባና ሌሎችም አካባቢዎች እንደሆነ ገልጾ ነበር፡፡በተመሳሳይ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጻፈው ደብዳቤ፤ በሸገር ከተማ እያፈረሱ ስላሉ መስጂዶች አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጥ መጠየቁም ይታወሳል።

[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa