YeneTube
116K subscribers
31.6K photos
485 videos
79 files
3.91K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
ዘመኑን የዋጁ ዝንጥ ፣ ጥንቅቅ ብለው የተሰሩ ፈርኒቸሮችን እነሆ ከ #ላንጋኖ_ፈርኒቸር

ላንጋኖ  ፈርኒቸር
ዘመናዊነትና ውበትን የተላበሱ የሀገር ወስጥ የፈርኒቸር ምርቶቻችን፡-
✔️ ለዜርና የጨርቅ ሶፋዎች

✔️ የአዋቂ እና የህጻን ልጅ አልጋዎች በተለያዩ መጠን እና ዲዛይን

✔️  ቁ/ሳጥኖች በተለያዩ ዲዛይን

✔️ የምግብ ጠረጴዛዎች በተለያየ ዲዛይን፡-በ6ወንበር,በ8ወንበር፣በ4ወንበር

✔️ የሶፋ ጠረጴዛዎች በተለያዩ መጠንና ዲዛይን

✔️  ዘመናዊ ኪችኖች

✔️  የጫማ ሸልፍ በተለያዩ መጠንና ዲዛይን…..ወዘተ ሲሆን በእርስዎ ፍላት መሰረት የሚቀርቡ አዳዲስ ዲዛይኖችን ተቀብለን እናዘጋጃለን፡፡
       
       ልዩነታችን
♦️ ከጊዜ በኃላ ማሳደስ ቢፈልጉ እንደ አዲስ አድርገን መሳደሳችን፣

♦️ ያዘዙትን ፈርኒቸር በቁርጥ ቀጠሮ ቀን እናቀርባን፣

♦️ ከኛ የገዙትን ዕቃዎችን ከረጅም ጊዜ በኃላ በአዲስ መለወጥ ሲፈልጉ እንቀበላለን

♦️ መጓጓዣና ጫኝ እስከ ቤትዎ ድረስ ከኛው መሆኑ፣

♦️ ከደንበኞች ለሚቀርቡ ቅሬታዎች አፋጣኝ ምላሽ መስጠታችን

♦️ በማንኛውም በዓላት ወቅት 5% የዋጋ ቅናሽ የሚናደርግ መሆናችን፣

♦️ አዲስ ደንበኛ በርሶዎ በኩል ሲመጣ ማበረታች አዘጋጅተናል
ስለሆነም ለዘላቂ ተጠቃሚነት እና እርካታ የሀገር ውስጥ ፈርኒቸር ምርቶችን ከእኛ ይግዙ፡፡

🛑አድራሻችን፡-ሀዋሳ
ከሳሙኤል ገበያ አዳራሽ ተሻግሮ / ዋንዛ አደባባይ ሳይደርሱ

በሰልክ ቁጥሮቻችን ፡0916581884 /0907212223/0944221511

ይደውሉልን,ይጎበኙን!       
ላንጋኖ ፈርኒቸር
በሀዋሳ የአበራ ላንጋኖ ፈርኒቸር እህት ድርጅት
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ 30/2015 በመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች ይሰጣል!

የ2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ማጠቃለያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ 30/2015 ድረስ የመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ግንቦት 09/2015 ተፈርሞ፤ ለኹሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች፣ ለኹሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ለኹሉም የክልል ትምህርት ቢሮዎች የተሰራጨ ደብዳቤ ፈተናው በተጠቀሱት ቀናት እንደሚሰጥ አመላክቷል፡፡በዚህም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ከሐምሌ 15 ቀን 2015 ጀምሮ ብሔራዊ ፈተናውን የመስጠት ሥራ ላይ ብቻ ትኩረት እዲያደርጉ የትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ ማስቀመጡ ተገልጿል።

በተጨማሪም በ2015 የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ በግልና በመንግሥት ተቋማት የሚገኙ እጩ ምሩቃን እና ባለፉት ዓመታት የህግ መውጫ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያላስመዘገቡት ተማሪዎች በመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች የመፈተኛ ማዕከላት ውስጥ ፈተናው ከሐምሌ 3 እስከ 13 ባሉት ቀናት ተሰጥቶ እንዲጠናቀቅ ሚኒስቴሩ በደብዳቤው አሳስቧል።

ሚኒስቴሩ አክሎም፤ በ2014 የ12ኛ ክፍል አጠናቀው ፈተና በመውሰድ በልዩ ሁኔታ የሬሜዲያል ኘሮግራም ተጠቃሚ ለሆኑ ተማሪዎች ለአንድ ሴሚስተር የተሰጠው ትምህርት በማዕከል የጋራ ፈተና ተዘጋጅቶ ለተቋማት እንዲላክ፣ ተቋማት ፈተናውን የማስተዳደር ውጤት የመግለጽና በ2016 ፍሬሽማን ፕሮግራም ለመከታተል ብቁ ሆነው የተገኙት (ማለትም በተቋማት የውስጥ ፈተና 50 ከመቶ፣ በማዕከል የተዘጋጀው ፈተና 50 ከመቶ) ተደምሮ በድምሩ 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡቱን እንዲያሳወቁ፣ ይህ አጠቃላይ ሂደት እስከ ሰኔ 30/2015 ድረስ እንዲጠናቀቅ አሳስቧል።

@YeneTube @FikerAssefa
“ፖሊሲያችን፥ የግዛት አንድነቷ የተጠበቀ ሉዓላዊት ኢትዮጵያን መደገፍ ነው” - አምባሳደር ማይክ ሐመር

የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር፣ ከትላንት በስቲያ፣ በዩናይትድ ስቴትስ ካሊፎርኒያ ግዛት በሎስ አንጀለስ ከተማ ውስጥ ከሚኖሩ፣ የዐማራ ማኅበረሰብ ተወላጅ ትውልደ ኢትዮጵያውያን አሜሪካውያን ጋራ ተገናኝተው፣ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ፖለቲካዊ ጉዳዮች እና በተለይ በዐማራ ማኅበረሰብ ላይ ይፈጸማሉ በተባሉ ጥቃቶች ዙሪያ ተወያይተዋል።

ሰኞ ግንቦት 7 ቀን 2015 ዓ.ም ሎሰ አንጀለስ ውስጥ የዐማራ ማኅበረሰብ ተወላጅ ትውልደ ኢትዮጵያውያን አሜሪካውያን ጋራ ተገናኝተው፣ የተወያዩት አምባሳደር ማይክ ሐመር፣ በደቡብ አፍሪካ የተፈረመው የሰላም ስምምነት ይዘት እና አፈጻጸም፣ በዐማራ ክልል እና ከዐማራ ክልል ውጪ በሚኖሩ የዐማራ ማኅበረሰብ አባላት ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችንና ሌሎች የአሜሪካን ፖሊሲ የሚመለከቱ ጥያቄዎች የቀረቡላቸው ሲኾን፣ በኢትዮጵያ፣ ልዩ ልዩ ማኅበረሰቦች ያሉባቸውን ችግሮች እንደሚረዱና አሜሪካ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚፈጸምን ማንኛውም የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ተቃውማ እንደምትናገር አመልክተዋል።

"ዐዲስ አበባ በሚገኘው ኤምባሲያችንም ኾነ፣ እኔም አጋጣሚውን በአገኘኹበት ጊዜ፣ ከዐማራ የፖለቲካ አመራሮች ጋራ ተገናኝተን ተወያይተናል። ልክ የኦሮሞ፣ የትግራይ እና ሌሎች ማኅበረሰቦችን እንደምንሰማው፣ የዐማራ ማኅበረሰብም ያለበትን ስጋት እናውቃለን። በእውነት ይህ ወቅት፣ ለኢትዮጵያውያን ፈታኝ ነው፤ ይገባኛል። ኾኖም፣ አንድ ፖሊሲ አለን። ሉዓላዊት የኾነች ኢትዮጵያን፣ የግዛት አንድነቷን በጠበቀ መልኩ የመደጋፍ እና እነዚኽን ግጭቶች እንደምን በሰላማዊ መንገድ መፍታት እንደሚቻል የመሥራት ፖሊሲ አለን፡፡”

አምባሳደር ሐመር አክለውም፣ በኢትዮጵያ የሚታዩት ወቅታዊ ችግሮች እንዲፈቱ፣ በአሜሪካ የሚኖረው ትውልደ ኢትዮጵያዊ ማኅበረሰብ፣ ትልቅ ሚና እንዳለው ያስገነዘቡ ሲኾን፣ ዩናይትድ ስቴትስ በኢትዮጵያ ሰላም እንዲሰፍን የሚያስችሉ መፍትሔዎችን ለመደገፍ ዝግጁ እንደኾነችም ጠቁመዋል።

“በጣም አስቸጋሪ ለኾኑ ጉዳዮች፣ ሰላማዊ መፍትሔ ለማግኘት እየሞከርን ነው። የአፍሪካ ኅብረት፣ ኢትዮጵያ እና የኢትዮጵያ ሕዝቦች፥ አገሪቱ ወደፊት እንድትራመድ፣ አስፈላጊ መፍትሔዎችን ለማምጣት እና ግጭትን ለማቆም የተደረሰውን ስምምነት ተግባራዊ ለማድረግ እየሞከሩ ባሉበት ወቅት፣ ዩናይትድ ስቴትስ ድጋፏን ለመቀጠል ተዘጋጅታለች።"

በውይይቱ ላይ የተሳተፉ የዐማራ ማኅበረሰብ አባላት፣ በዐማራ ተወላጆች ላይ ተፈጽመዋል ያሏቸውን የጋዜጠኞች፣ የመብት አቀንቃኞች እና የፖለቲከኞች እስራት፣ የኢንተርኔት መታገድ እና በታጠቁ አካላት የሚደርሱባቸውን ጥቃቶች አንሥተው ጥያቄ አቅርበዋል። ከተወያዮቹ መካከል አንዱ የኾኑት ዶር. ጌታቸው አበበ፣ ስለነበረው ውይይት የተሰማቸውን ነግረውናል።

ውይይቱን ያሰናዳው የሎስ አንጀለስ ዐማራ ማኅበረሰብ ፕሬዚዳንት ወይዘሮ ቤተ ልሔም ሙሉጌታ አየለ በበኩላቸው፣ የማኅበረሰቡ አባላት፥ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰላም እንዲሰፍን፣ በዐማራ ኅብረተሰብ ላይ ይደርሳል ያሉት ጥቃት መቆም እንዳለበት ገልጸው፣ ለአምባሳደር ሐመር ያስተላለፉት መልዕክት መደመጡ ተስፋ እንደሰጣቸው አመልክተዋል።

“በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ሁሉም ሰዎች፣ በአንድነት እና በዴሞክራሲ መንገድ እንዲኖሩ ነው የምንፈልገው፤” ያሉት ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ አቶ አሰፋ ድረስ በበኩላቸው፣ አምባሳደር ሐመር፣ በውይይቱ የተነሡ ሐሳቦችን በተግባር ላይ እንደሚያውሏቸው ያላቸውን ተስፋ ተናግረዋል።

"የዩናይትድ ስቴትስ ፍላጎት፣ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ደኅንነት ነው፤” ያሉት ሐመር፣ በሰላም፣ በትምህርት እና በጤና የመኖር ዕድል ለማግኘት እንደሚፈልጉ የሰው ልጆች ሁሉ፣ የሁሉም ኢትዮጵያውያን ሕዝቦች ሰብአዊ ደኅንነት የአሜሪካ ትኩረት መኾኑን አስምረውበታል።

በሎስ አንጀለስ ከሚኖሩ የዐማራ ማኅበረሰብ ተወላጆች በተጨማሪ፣ ከኦሮሞ፣ ከትግራይ እና ከሶማሌ ማኅበረሰብ ጋራም እንደሚገናኙ ያስታወቁት ሐመር፣ ሁሉም ማኅበረሰቦች የየራሳቸው ስጋት እንዳለባቸው ሁሉ፣ የሚጋሯቸው የጋራ ችግሮችም በመኖራቸው፣ አብረው መሥራት እንደሚችሉም አስገንዝበዋል።

[VoA]
@YeneTube @FikerAssefa
1
በኢትዮጵያ በየቀኑ በአማካይ 27 እናቶች ከወሊድ ጋር በተያያዘ ህይወታቸዉን እንደሚያጡ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ!

በኢትዮጵያ በየእለቱ ከወሊድ ጋር በተያያዘ 27 እናቶች ህይወታቸዉ እንደሚያልፍ በጤና ሚኒስቴር የእናቶች ፣ህጻናትና ወጣቶች ጤና አገልግሎት መሪ ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ ብሩክ ሀይሉ ለብስራት ራዲዮ ተናግረዋል። በየአመቱም 10 ሺህ ገደማ እናቶች በ እርግዝና ወቅት በሚያጋጥሙ የተለያዩ የጤና እክሎች ህይወታቸዉ ያልፋል ብለዋል።

ለሚመዘገቡት የሞት ቁጥሮች ከወሊድ በኋላ የሚከሰት ከፍተኛ የሆነ ደም መፍሰስ ፣ በእርግዝና ግዜ የሚከሰት የደም ግፊትና ኢንፌክሽን ዋነኛ ምክንያቶች መሆናቸዉን አቶ ብሩክ ጠቁመዋል። ቅድመ እርግዝና እና ቅድመ ወሊድ ክትትል የሚያደርጉ እናቶች ቁጥር አናሳ መሆኑም ለሚሰተዉ ሞት ሌላኛዉ ምክኒያት እንደሆነ ገልጸዋል።በተመሳሳይ እ.ኤ.አ በ 2020 በተሰራ ጥናት በኢትዮጵያ ከ 100 ሺህ ወሊዶች ዉስጥ 2 መቶ 67 እናቶች በእኚሁ ምክኒያቶች ህይወታቸዉ ይቀጠፋል ብለዋል።

በአለም ጤና ድርጅት በአመቱ በተሰራ ሌላ ጥናት በአለማቀፍ ደረጃ በየእለቱ 8 መቶ እናቶች ከወሊድ ጋር በተያያዘ ህይወታቸዉ የሚያልፍ ሲሆን ይህም በየ 2 ደቂቃዉ የአንድ እናት ህይወት ያልፋል እንደማለትም ነዉ።ከነዚህ ዉስጥ 87 በመቶ የሆነዉ ከሰሀራ በታች እና በደቡብ እስያ ባሉ ሀገራት ይመዘገባል ያሉ ሲሆን 95 በመቶ የሚሆነዉ ደግሞ በዝቅተኛ እና መካከለኛ ሀገራት ነዉ ብለዋል።

[ዳጉ ጆርናል]
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ አንድ እቁላል ከ14 ብር እስከ 16 ብር እየተሸጠ ነው፡፡

-‹‹ለእንቁላል ጣይ ዶሮ መኖ በኩንታል ከ 3 ሺህ 680 እስከ 4 ሺህ ብር ወጪ እያስደረገን ነው››--- የኢትዮጵያ ዶሮ አርቢዎች እና አቀናባሪዎች ማህበር

በመኖ መወደድ እና ከዚህ ቀደም ተከስቶ በነበረው ወረርሺኝ ምክንያት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዶሮዎች መሞታቸው አብዛኛው ዶሮ አርቢ አባላትን ዘርፉ ውስጥ እንዳይቆዩ እያደረጋቸው መሆኑ ተገልጧል፡፡

ይህን ያለው የኢትዮጵያ ዶሮ አርቢዎች እና አቀናባሪዎች ማህበር ነው፡፡የማህበሩ ምክትል ሃላፊ አቶ ቴዎድሮስ ካሳሁን ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደተናገሩት፣የመኖው መወደድ የእንቁላል ዋጋ ከዚህም በላይ ከፍ እንዲል ሊያደርገው እንደሚችል ስጋታቸውን ገልፀዋል።

ሬዲዮ ጣቢያው ባደረገው ቅኝት በአማካይ የ1 እንቁላል ዋጋ ከ 14 ብር አስከ 16 ብር እየተሸጠ ይገኛል፡፡አንድ እንቁላል ጣይ ዶሮ ከምታስገኘው ገቢ 75 ከመቶዋ ወጪዋ መሆኑን አቶ ቴዎድሮስ ተናግረዋል።

አቶ ቴዎድሮስ ጨምረውም ቀደም ሲል " ዶሮ እና የዶሮ ውጤቶችን ያለ ስጋት መጠቀም ይቻላል " የሚል ትዕዛዝ አስከተሰጥበት ቀን ድረስ በነበረው ጊዜ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዶሮዎች መቀበራቸውን እና ብዙ አርቢዎችም ላይ ኪሳራ ማስከተሉን ተናግረዋል።

በማህበሩ ውስጥ በአሁኑ ሰዓት 125 አርቢ አባላት መኖራቸውንም ተሰምቷል። ዘርፉ በባንክ በብድር ቢደገፍ ፣ እውቀቱ እና ማምረቻ ቦታው ለወጣቶች በመስጠት ቢታገዝ ፣ ገበሬው ደግሞ በማርባቱ ሂደት በብዛት ቢቀላቀል መሻሻል ሊኖረው ይችላልም ብለዋል፡፡

Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
የዩኒቨርሲቲ እጩ ተመራቂዎች መውጫ ፈተና ከፊታችን ሐምሌ 3 ቀን ጀምሮ ይሰጣል!

የዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች መውጫ ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 13 ቀን 2015 ዓ.ም እንደሚሰጥ የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።የ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ በግልና በመንግስት ተቋማት የሚገኙ እጩ ምሩቃን በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የመፈተኛ ማዕከላት ፈተናውን እንደሚወስዱ ተገልጿል።

በ2014 ዓ.ም የሕግ መውጫ ፈተና ተፈትነው ማለፊያ ነጥብ ያላስመዘገቡ ተማሪዎችም በዚሁ ጊዜ ፈተናውን የመንግስት ዩኒቨርሲቲ የመፈተኛ ማዕከላት ውስጥ መውሰድ ይችላሉ ተብሏል።ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተናን ለመሥጠት የተለያዩ ዝግጅቶችን ሲያደርግ መቆየቱንም የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል።

@YeneTube @FikerAssefa
የኮሌራ ወረርሽኝ በኢትዮጵያ አራት ክልሎች የተዛመተ ሲሆን፤ በደቡብ ክልል 18 ሰዎች በበሽታው ሞተዋል።

የኮሌራ ወረርሽኝ በኢትዮጵያ አራት ክልሎች መዛመቱን የጤና ሚኒስቴር ሲገልጽ፣ በደቡብ ክልል ልዩ ልዩ ዞኖች እና ወረዳዎች ደግሞ፣ 18 ሰዎችን ለኅልፈት መዳረጋቸውንና 919 ሰዎች በበሽታው መያዛቸውን፣ የክልሉ ጤና ቢሮ አስታውቋል።ወረርሽኙ በበረታባቸው የክልሉ ዞኖች፣ ትላንት እና ዛሬ ክትባት መስጠት መጀመሩን፣ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዲሬክተር አቶ ማሙሽ ሑሴን ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ፣ የኮሌራ ወረርሽኝ፣ በአራት ክልሎች መዛመቱን ያስታወቀው የጤና ሚኒስቴር፣ ወረርሽኙን ለመከላከል፣ ለ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ዜጎች ክትባት እንደሚሰጥ አመልክቷል፡፡በኢትዮጵያ አራት ክልሎች ተዛምቶ ጉዳት እያደረሰ የሚገኘው የኮሌራ ወረርሽኝ፣ በዐዲስ መልክ በተከሠተባቸው የደቡብ ክልል አምስት ዞኖች እና ሦስት ልዩ ወረዳዎች፣ ሰዎችን ለኅልፈተ ሕይወት እና ለሕመም መዳረጉን፣ የደቡብ ክልል የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡

የኢንስቲትዩቱ ዲሬክተር አቶ ማሙሽ ሑሴን፣ ለአሜሪካ ድምፅ ሲናገሩ፣ በደቡብ ክልል እንደ ዐዲስ በተስፋፋው የኮሌራ ወረርሽኝ የ18 ሰዎች ሕይወታቸው ማለፉንና 919 ሰዎች ደግሞ በበሽታው መያዛቸውን አስረድተዋል።በክልሉ፣ ለተከታታይ አምስት ቀናት ይሰጣል የተባለውን የኮሌራ ክትባት ዘመቻ፣ ትላንት ማክሰኞ፣ ግንቦት 8 ቀን 2015 ዓ.ም.፣ በደቡብ ኦሞ ዞን ያስጀመሩት የጤና ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ፣ ወረርሽኙ፥ በአገር አቀፍ ደረጃ በአራት ክልሎች መከሠቱን አረጋግጠዋል።

ዕድሜያቸው፣ ከአንድ ዓመት በላይ ለኾኑ 1ነጥብ5 ሚሊዮን ዜጎች፣ የኮሌራ ክትባት እንደሚሰጥ፣ ሚኒስትር ዴኤታው ማስታወቃቸውን፣ የክልሉ መንግሥት ቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል።የክትባት ዘመቻው፣ በደቡብ ኦሞ ዞን በናፀማይ ወረዳ የተጀመረ ሲኾን፣ ወረርሽኙ በባሰባቸው በጋሞ ዞን ማላጋርዳ ወረዳም፣ በዛሬ ዕለት መሰጠት መጀመሩን፣ በጋሞ ዞን ጤና መምሪያ የጤና እና ጤና ነክ ድንገተኛ አደጋዎች ቅኝት ዳይሬክቶሬት ዲሬክተር አቶ ታረቀኝ መርዕድ ገልጸዋል።

በጋሞ ዞን፣ እስከ ትላንትናው ዕለት ድረስ፣ ከ400 በላይ የሕመምተኞች ቁጥር መመዝገቡን የጠቀሱት ዲሬክተሩ፣ ወደ ጤና ተቋም ከመድረሳቸው በፊት አምስት ሰዎች ሕይወታቸው ማለፉንና በአጠቃላይ ስምንት ሰዎች መሞታቸውን አስታውቀዋል።

በሌላ በኩል፣ ባለፈው ሳምንት፣ በቡርጂ እና በአማሮ ልዩ ወረዳዎች በተዛመተው በዚኹ የኮሌራ ወረርሽኝ፣ ሰባት ሰዎች ለኅልፈተ ሕይወት መዳረጋቸውን መዘግባችን የሚታወስ ሲኾን፣ ለወረርሽኙ ጉዳት መባባስ፣ በልዩ ወረዳዎቹ ወሳኝ መሠረተ ልማቶች ባለመዘርጋታቸው እንደኾነ፣ የአማሮ ልዩ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽሕፈት ቤት የበሽታ መከላከል እና ጤና ማጎልበት ዋና የሥራ ሒደት የማኅበረሰብ ተግባቦት እና የጤና ኤክስቴንሽን አስተባባሪ አቶ አክሊሉ ካሌብ አመልክተዋል።

በጋሞ ዞን ጤና መምሪያ የጤና እና ጤና ነክ ድንገተኛ አደጋዎች ቅኝት ዳይሬክቶሬት ዲሬክተር አቶ ታረቀኝ መርዕድም፣ የአቶ አክሊሉን አስተያየት ያጠናክራሉ፡፡የኮሌራ ወረርሽኙ፣ በዐዲስ መልክ የተከሠተባቸው የደቡብ ክልል አካባቢዎች፥ የጋሞ፣ የጎፋ፣ የደቡብ ኦሞ፣ የኮንሶ እና የጌዲኦ ዞኖች፣ እንዲሁም የአሌ፣ የአማሮ እና የቡርጂ ልዩ ወረዳዎች ናቸው።

[VoA]
@YeneTube @FikerAssefa
Are you the one?

👉  Learning Management System Developers
👉  Tech Startups & Incubators
👉  Digital Solution Providers
👉  Music Streaming Service Providers
👉  Coding Learning Centers
👉  Digital Library Service Providers
👉  Social Media Training Centers
👉  Student Tutorial Service Providers
👉  Professional Toastmaster's Clubs
👉  Student Club Association
👉  Online Education Service Providers
👉  Digital Theology Service Platforms
👉  Distance Education Learning Centers
👉  Short-term Training Service Institutes

When Yes:
Don't miss a chance to exhibit at the

Edition
5th

Event
Back to School Africa
Festival, 2023.

When
May 19 - 21/2023

Dates
Friday, Saturday, & Sunday

Duration
9am - 7pm

Visit event website👇!  
www.backtoschoolafrica.com 

Follow us on👇
Facebook and LinkedIn

Contact us
 
    ☎️ :   +251 974 08 2036
              +251 974 08 2037

With Support of
FDRE Ministry of Education

     Sponsors
Oracle Academy
Study in Japan
BUKU Digital Platform
DSTV Ethiopia
መርጌታ ጥበቡ የባህል ህክምና መስጫ ማዕከል በቲክቶክ መቷል።

የባህል መድሀኒት ከአባቶቻችን ባገኘነው ትምህርትና ጥበቡ እንዲሁም ከተለያዩ የአፍሪካ እና የአረብ ሀገራት በምናመጣቸው መድለኒቾች ፍቱን ህክምናወችን
እንሰጣለን ።
👉ለኪንታሮት በሽታ ታማሚው ባለበት ከቤቱ ወስዶ በመቀባት ሌላ ገላ ሳይነካ ሳያቆስል ስራ ሳያስቆም ዘላቂ ፈውስ ይሰጣል
👉በሌሊት ለሚሸና
👉ለነገረ በትን
👉ለደም ግፊት
👉ለስኳር ህመም መቀነሻ
👉ለሁሉም ቁርጥማት
👉ለዲስክ መንሸራተት ዘላቂ ፈውስ
👉ለፊት ማድያት
👉ለሳል በሽታ
👉ለግርማሞገስ ለህዝብ መስተፋቅር
👉ለማህጸን እንፌክሽን
👉ለአእምሮ ጭንቀት
👉ለወገብ ህመም
👉ለነርብ
👉ጋኔን አጋንንት የሰውጅ ለያዘው
👉የሚጥል በሽታ

👉ለበለጠ መረጃ አድራሻ ባህርዳር ቀበሌ 11ዲያስፖራ በኮብሉ መጨረሻ ንግድ ባንኩ ላይ።

    ቅርንጫፍ አዲስ አበባ ሳሪስ አደይ አበባ

👉እኒህን እና ሌሎች አገልልግሎቶችን ለማግኔት
                   👎ይደውሉ
👉☎️0917040506
          0912718883

    ቻናሉን ይቀላቀሉ👇
https://tttttt.me/mergatah

👉ቻናሉን በመቀላቀል ሊንኳን በመጫን ጤናወ በቤትወ የባህል ህክምና የእጽዋት የህቡ ስም የጠልሰም ጥቅሞችን ይጋሩ ይፈወሱ

tiktok.com/@u0917040506_0912718883
አዲስ ነገር ከነዳጅ!!ስልፍ ቀረ‼️

በአንዳንድ የነዳጅ ማደያዎች ላይ የሚስተዋሉ ሠልፎች ፤ ኤሌክትሮኒክ የነዳጅ ግብይት ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ በአሽከርካሪዎች እንዲሁም በነዳጅ ማድያዎች በኩል ግብይት ለመፈፀም ቅድመ ዝግጅት ባለመደረጉ ብዙ ሰዓታትን በሰልፍ ላይ እንደሚያጠፉ የከተማዋ አሽከርካሪዎች ገልጸዋል።

ይህንንም ተግዳሮት ከግምት ውስጥ በማስገባት ነዳጅ በተሰኝው መተግበሪያ ላይ በነዳጅ ማደያዎች ያለውን ሰልፍ ለመቅረፍ አሽከርካሪዎች በመጅመሪያ

ነዳጅ መተግበሪያን በመክፈት
STANDBY ሚለውን ይምረጡ❗️

የመዘገቡትን መኪና ይምረጡ

ሚቀዱትን መጠንና ነዳጅ አይነት ያስግቡ፦

🚀ወድያውኑ ስታንድ ባይ ኮድ ይሰጦታል❗️
አሽከርካሪው የሚደርሰውን ኮድ ለነዳጅ ቀጂው በሚሰጥበት ወቅት መተግበሪያው ላይ የሚመጣለትን  ሙሉ መረጃ በማረጋገጥ ግብይቱን በቀላሉ ማጠናቀቅ ይችላል።

ይህም የነዳጅ ቀጂው ሙሉ መረጃ አስገብቶ ግብይት እስኪፈጠር ደረስ ያለውን ጊዜ በመቆጠብ ከአላስፈላጊ ሰልፍ እና መንገላታት የነዳጅ ግብይቱን እንደሚያሳልጥ ተነግሯል።

በነዳጅ አፕ ይጠቀሙ ግዚዎትን ይቆጥቡ።

አሁኑኑ ከ PLAY STORE እና APP STORE ያውርዱ፣ ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሂሳብ አካውንትዎ ጋር ያስተሳስሩ!

For Android: https://play.google.com/store/apps/details?id=com.eaglelionsystems.nedaj


For iOS:
https://apps.apple.com/us/app/nedaj/id1639807926

#Nedaj #nedajapp
ዘመኑን የዋጁ ዝንጥ ፣ ጥንቅቅ ብለው የተሰሩ ፈርኒቸሮችን እነሆ ከ #ላንጋኖ_ፈርኒቸር

ላንጋኖ  ፈርኒቸር
ዘመናዊነትና ውበትን የተላበሱ የሀገር ወስጥ የፈርኒቸር ምርቶቻችን፡-
✔️ ለዜርና የጨርቅ ሶፋዎች

✔️ የአዋቂ እና የህጻን ልጅ አልጋዎች በተለያዩ መጠን እና ዲዛይን

✔️  ቁ/ሳጥኖች በተለያዩ ዲዛይን

✔️ የምግብ ጠረጴዛዎች በተለያየ ዲዛይን፡-በ6ወንበር,በ8ወንበር፣በ4ወንበር

✔️ የሶፋ ጠረጴዛዎች በተለያዩ መጠንና ዲዛይን

✔️  ዘመናዊ ኪችኖች

✔️  የጫማ ሸልፍ በተለያዩ መጠንና ዲዛይን…..ወዘተ ሲሆን በእርስዎ ፍላት መሰረት የሚቀርቡ አዳዲስ ዲዛይኖችን ተቀብለን እናዘጋጃለን፡፡
       
       ልዩነታችን
♦️ ከጊዜ በኃላ ማሳደስ ቢፈልጉ እንደ አዲስ አድርገን መሳደሳችን፣

♦️ ያዘዙትን ፈርኒቸር በቁርጥ ቀጠሮ ቀን እናቀርባን፣

♦️ ከኛ የገዙትን ዕቃዎችን ከረጅም ጊዜ በኃላ በአዲስ መለወጥ ሲፈልጉ እንቀበላለን

♦️ መጓጓዣና ጫኝ እስከ ቤትዎ ድረስ ከኛው መሆኑ፣

♦️ ከደንበኞች ለሚቀርቡ ቅሬታዎች አፋጣኝ ምላሽ መስጠታችን

♦️ በማንኛውም በዓላት ወቅት 5% የዋጋ ቅናሽ የሚናደርግ መሆናችን፣

♦️ አዲስ ደንበኛ በርሶዎ በኩል ሲመጣ ማበረታች አዘጋጅተናል
ስለሆነም ለዘላቂ ተጠቃሚነት እና እርካታ የሀገር ውስጥ ፈርኒቸር ምርቶችን ከእኛ ይግዙ፡፡

🛑አድራሻችን፡-ሀዋሳ
ከሳሙኤል ገበያ አዳራሽ ተሻግሮ / ዋንዛ አደባባይ ሳይደርሱ

በሰልክ ቁጥሮቻችን ፡0916581884 /0907212223/0944221511

ይደውሉልን,ይጎበኙን!       
ላንጋኖ ፈርኒቸር
በሀዋሳ የአበራ ላንጋኖ ፈርኒቸር እህት ድርጅት
👎1
የሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ፈተና ማጠናቀቂያ ጊዜ ተገለፀ።

በ2014ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ወስደው በልዩ ሁኔታ በሪሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ የሆኑ ተማሪዎች ፈተናና ተዘጋጅቶ እንዲላክና አጠቃላይ ሂደቱ  እስከ ሰኔ 30/2015ዓ.ም ድረስ እንዲጠናቀቅ በትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ ተቀምጧል።ፈተናውም በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው በተሰጠው ትምህርት መሠረት ከማዕከል በጋራ ተዘጋጅቶ ለተቋማት እንዲላክ ተብሏል።

በዚህም መሰረት በሴሚስተሩ በተሰጠው ትምህርት የተቋማት የውስጥ ፈተና ውጤት 50 ከመቶ እንዲሁም በማዕከል የተዘጋጀው ፈተና ውጤት 50 ከመቶ  ይይዛል ተብሏል።ተማሪዎችም በ2016 ዓ.ም ትምህርታቸውን ለመከታተል ብቁ ሆነው ለመገኘት የሁለቱ ድምር አማካይ 50 ከመቶና በላይ ውጤት ማስመዝገብ ይጠበቅባቸዋልም ተብሏል።

ዩኒቨርሲቲዎችም ፈተናውን በማስተዳደርና ውጤት በመግለጽ በ2016 የፍሬሽማን ፕሮግራም ለመከታተል ብቁ የሆኑ ተማሪዎችን  ለይተው እስከ ሰኔ 30/2015ዓም እንዲያጠናቅቁ ተገልጿል።ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን ስራ በማጠናቀቅ የ2016 የትምህርት ካሌንደር የተስተካከለ እንዲሆን ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

@YeneTube @FikerAssefa
በፋኖና በመከላከያ መካከል በተደረገ ውጊያ በትንሹ የአምስት ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተገለጸ!

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሸዋሮቢት ዙሪያ ራሳ ተብሎ ከሚጠራ ስፍራ ረቡዕ ግንቦት 92015 በፋኖ እና በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት መካከል በተደረገ የተኩስ ልውውጥ በትንሹ የአምስት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የአካባቢው ነዋሪዎች ለአዲስ ማለዳ ገለጹ።በሸዋሮቢት ዙሪያ እና አካባቢዋ በተደረገው በዚህ ውጊያ ንፁሃን ዜጎች የሞት ሰለባ ሁነዋል የተባለ ሲሆን፤ ሰላማዊ ሰዎች አካባቢያቸውን ለቀው መሄዳቸው ነው የተገለጸው፡፡

በዚህ በአገር መከላከያ ሰራዊት እና በፋኖ መካከል በተከፈተው ጦርነት ሌሎች የሸኔ አባላት እና የአካባቢው ነዋሪዎችም ተሳትፈዋል የሚሉት ነዋሪዎቹ፤ በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን እና በሰሜን ሸዋ ዞን መካከል በሚገኙ አካባቢዎች ላይ ከፍተኛ ውጥረት መንገሱን ተናግረዋል።

በአካባቢው ሲካሄድ በነበረው የተኩስ ልውውጥ የከባድ መሳሪያ ድምፅ ይሰማ እንደነበርም ነው ለማወቅ የተቻለው፡፡በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን እና በሰሜን ሸዋ ዞን አካባቢዎች በሚከሰቱ ግጭቶች በየወቅቱ የሰው ሕይወት እየጠፋ፣ ቤት እየተቃጠለ፣ ሃብት ንብረት እየወደመ የቀጠለ ቢሆንም፣ የፌደራል መንግሥቱ በዘላቂነት ሊያስቆመው ባልመቻሉ በርካታ ነዋሪዎች አካባቢያቸውን ለቀው እንዲሰደዱ እንዳስገደዳቸው ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡

በዚህ ዓመት ብቻ ከሦስት ጊዜ በላይ በአካባቢው ጦርነት ተካሂዶበታል የሚሉት የራሳ እና ግድም ነዋሪዎች፤ በአካባቢው ሰላም ያስከብራሉ ተብለው የተመደቡ የአገር መከላከያ ሰራዊት የንፁሃንን ሕይወት ከመጥፋት አልታደጉም ብለዋል።

Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የተሳታፊዎች ልየታን ለመጀመር ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታወቀ፡፡

የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ወደ አራት ክልሎች እና አንድ ከተማ አስተዳደር በመሄድ ለሀገራዊ ምክክሩ ተሳታፊዎችን የመለየት ስራ እንደሚሰራ ተናግረዋል።

በዚህም በጋምቤላ፣ ሲዳማ፣ ሀረሪ፣ ደቡብ ምዕራብ ክልሎች እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ላይ የተሳታፊዎች ልየታው እንደሚጀመር አንስተዋል፡፡ከወረዳ እስከ ዞን ከተሞች በሚደረገው ልየታ የተመረጡ ተሳታፊዎችም ወደ ክልሉ በመሄድ ተወካዮቻቸውን እንደሚመርጡም ተነስቷል።

ሂደቱን የመታዘብ ሚና እንዲኖራቸው የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች፣ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤትን ጨምሮ በአጠቃላይ ሰባት ተባባሪ ተቋማት ስለመመረጣቸው የተነሳ ሲሆን 11ዱም ኮሚሽነሮች ወደየአካባቢዎቹ በመሄድ የልየታ ስራውን እንደሚከታተሉ ተገልጿል፡፡ተወካዮች ከተለዩ በኋላ የመወያያ አጀንዳ የማሰባሰቡ ስራ እንደሚቀጥል የተነሳ ሲሆን ሁሉም ኢትዮጵያዊ በአጀንዳ የማሰባሰቡ ስራ እንደሚሳተፍም ተጠቁሟል፡፡

[Walta]
@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወደ ፕሪምየር ሊግ ማደጉን አረጋገጠ!

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለት ጨዋታ እየቀረው ወደ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ማደጉን አረጋገጠ፡፡የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ምድብ ሀ የ25ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከትናንት ጀምሮ እየተካሄዱ ሲሆን ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ቤንች ማጂ ቡና ዛሬ ከአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ጋር ባደረገው ጨዋታ 2 ለ 1 በመሸነፉ መሪው ንግድ ባንክ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ማደጉን ማረጋገጥ ችሏል፡፡በዚህም ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ2016 የውድድር ዓመት ማደጉን ከወዲሁ አረጋግጧል ነው የተባለው።

@YeneTube @FikerAssefa
የኤክሳይዝ ታክስ አዋጅ ላይ ማሻሻያ መደረጉን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታውቋል።

የኤክሳይዝ ታክስ አዋጅ ቁጥር 1186/2012 ከየካቲት 5/2012 ጀምሮ ሥራ ላይ የዋለ ሲሆን፤ ይህ አዋጅ የታክሱን መሰረት በማስፋት እና የታክሱን አስተዳደር ስርዓት በመቀየር ከፍተኛ ጠቀሜታን ማስገኘቱን ሚኒስቴሩ ገልጿል።የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሚያዚያ 19/2015 ባካሄደው 15ኛ መደበኛ ጉባኤው በአዋጁ ላይ የቀረቡ ማሻሻያዎችን ታሳቢ በማድረግ የአዋጁ ማሻሻያ መድረጉንም ሚኒስቴሩ አስታውሷል።

የአዋጁ ማሻሻያ ታሳቢ ያደረገው ተደራራቢ የኤክሳይዝ ታክስ የተጣለባቸው ምርቶች ላይ ማሻሻያ ለማድረግ፣ በቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት ላይ የኤክሳይዝ ታክስ እንዲከፈል ለማድረግ፣ የኤክሳይዝ ታክስ ተጥሎባቸው የነበሩት አንዳንድ ምርቶች ላይ ታክሱን ለማንሳት መሆናቸው ተገልጿል።እንዲሁም በአስተዳደር ምክንያት የተደረጉ ማስተካከያዎችን እና የማሻሻያውን ዋና ዋና ምክንያቶችን ከመረመረ በኋላ የኤክሳይዝ ታክስ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1287/2015 እንዲጸድቅ ማድረጉን ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

በመሆኑም ገቢዎች ሚኒስቴር የአዋጁ ማሻሻያ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፀደቀበት ጊዜ ጀምሮ በሥራ ላይ እንዲውል እንዲደረግ እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላት፤ የንግዱ ማህበረሰብ ሁሉ እንዲያውቁት መመሪያ ሰጥቷል።

👆የተደረገው የኤክሳይዝ ታክስ አዋጅ ማሻሻያ ከላይ ተያይዟል

@YeneTube @FikerAssefa