የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ወደ ጦርነት የገቡ አካላትን ለማስታረቅ ጠየቀች!
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ወደ ጦርነት የገቡ አካላትን ማስታረቅ እንደምትፈልግ ገለጸች፡፡ቤተ ክርስቲያኒቷ ከግንቦት 9 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ስታካሂድ የነበረውን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ማህበራዊና መንፈሳዊ ውሳኔዎችን በማሳለፍ አጠናቃለች፡፡
የጉባኤውን መጠናቀቅ ተከትሎም ቤተ ክርስቲያኒቷ ውሳኔዎቿን የተመለከተ መግለጫን አውጥታለች፡፡በመግለጫው በኢትዮጵያ በጦርነት ውስጥ ያሉ ወገኖች ወደ ሰላም እና እርቅ እንዲመጡ ማስታረቅ እንደምትፈልግ አስታውቃለች፡፡
ምልዓተ ጉባኤው በአሁኑ ደረጃ በኢትዮጵያ ባለው የሰላም እጦት ላይ በሰፊው መወያየቱን ገልጻ በቀጣይ ጦርነትና የእርስ በርስ ግጭት ተወግዶ አጠቃላይ ሰላም በሚሰፍንበት መልኩ ተነጋግሮ ችግሩን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መፍታት እንዲቻል፣ የአስታራቂነት ሚናዋን መጫወት እንድትችል ለማድረግ ለፌዴራል መንግሥት ጥያቄ አቅርቤያለሁ ብላለች፡፡
ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ: https://am.al-ain.com/article/eotc-request-to-mediate-waging-parties-in-ethiopia
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ወደ ጦርነት የገቡ አካላትን ማስታረቅ እንደምትፈልግ ገለጸች፡፡ቤተ ክርስቲያኒቷ ከግንቦት 9 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ስታካሂድ የነበረውን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ማህበራዊና መንፈሳዊ ውሳኔዎችን በማሳለፍ አጠናቃለች፡፡
የጉባኤውን መጠናቀቅ ተከትሎም ቤተ ክርስቲያኒቷ ውሳኔዎቿን የተመለከተ መግለጫን አውጥታለች፡፡በመግለጫው በኢትዮጵያ በጦርነት ውስጥ ያሉ ወገኖች ወደ ሰላም እና እርቅ እንዲመጡ ማስታረቅ እንደምትፈልግ አስታውቃለች፡፡
ምልዓተ ጉባኤው በአሁኑ ደረጃ በኢትዮጵያ ባለው የሰላም እጦት ላይ በሰፊው መወያየቱን ገልጻ በቀጣይ ጦርነትና የእርስ በርስ ግጭት ተወግዶ አጠቃላይ ሰላም በሚሰፍንበት መልኩ ተነጋግሮ ችግሩን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መፍታት እንዲቻል፣ የአስታራቂነት ሚናዋን መጫወት እንድትችል ለማድረግ ለፌዴራል መንግሥት ጥያቄ አቅርቤያለሁ ብላለች፡፡
ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ: https://am.al-ain.com/article/eotc-request-to-mediate-waging-parties-in-ethiopia
@YeneTube @FikerAssefa
የሚኒስትሮች ምክር ቤት የ2015 በጀት 786 ነጥብ 61 ቢሊዮን ብር እንዲሆን ወሰነ፡፡
በጀቱ በአስር ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ የተቀመጡ ግቦችን ለማስፈጸም ያለመ ነው፡፡ በተጨማሪም የሀገር ደህንነትን ለማስጠበቅ፣ የተፈናቀሉ ዜጎችን ከመርዳትና የወደሙ መሰረተ ልማቶችን እና አገልግሎቶችን መልሶ ማቋቋምን ታሳቢ ያደረገ ነው፡፡
ከ2014 በጀት ዓመት በጀት ጋር ሲነጻጸር የብር 111.94 ቢሊዮን ወይም የ16.59 በመቶ እድገት አሳይቷል፡፡ ምክር ቤቱም የፌዴራል መንግሥት የ2015 በጀትን ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡የ2014 ዓ.ም በጀት 561 ቢሊየን ብር እንደነበር ይታወሳል፡፡መረጃዉ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ነዉ፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
በጀቱ በአስር ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ የተቀመጡ ግቦችን ለማስፈጸም ያለመ ነው፡፡ በተጨማሪም የሀገር ደህንነትን ለማስጠበቅ፣ የተፈናቀሉ ዜጎችን ከመርዳትና የወደሙ መሰረተ ልማቶችን እና አገልግሎቶችን መልሶ ማቋቋምን ታሳቢ ያደረገ ነው፡፡
ከ2014 በጀት ዓመት በጀት ጋር ሲነጻጸር የብር 111.94 ቢሊዮን ወይም የ16.59 በመቶ እድገት አሳይቷል፡፡ ምክር ቤቱም የፌዴራል መንግሥት የ2015 በጀትን ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡የ2014 ዓ.ም በጀት 561 ቢሊየን ብር እንደነበር ይታወሳል፡፡መረጃዉ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ነዉ፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የተለያዩ ሹመቶችን ሰጡ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በዛሬው እለት የተለያዩ ሹመቶች ሰጥተዋል።
በዚሁ መሰረት፥
1. አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን - የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ሚኒስትር
2. አቶ ካሊድ አብዱራህማን - በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የፕሮጀክቶች ክትትል
3. አቶ ወንድሙ ሴታ - የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ
4. አቶ ሄኖስ ወርቁ - የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሹመዋል።
በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚከተሉትን ሸመቶች የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲያጸድቅላቸው ጠይቀዋል፦
1. ወ/ሮ መሰረት ዳምጤ - የፌደራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ዋና ኦዲተር
2. አቶ አበራ ታደሰ - የፌደራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ምክትል ዋና ኦዲተር ሆነው ተሹመዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በዛሬው እለት የተለያዩ ሹመቶች ሰጥተዋል።
በዚሁ መሰረት፥
1. አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን - የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ሚኒስትር
2. አቶ ካሊድ አብዱራህማን - በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የፕሮጀክቶች ክትትል
3. አቶ ወንድሙ ሴታ - የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ
4. አቶ ሄኖስ ወርቁ - የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሹመዋል።
በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚከተሉትን ሸመቶች የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲያጸድቅላቸው ጠይቀዋል፦
1. ወ/ሮ መሰረት ዳምጤ - የፌደራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ዋና ኦዲተር
2. አቶ አበራ ታደሰ - የፌደራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ምክትል ዋና ኦዲተር ሆነው ተሹመዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
ደንበኞች ግብራቸውን ኦንላይን እንዲከፍሉ ከባንኮች ጋር ስምምነት ላይ ተደረሰ!
የገቢዎች ሚኒስቴር ደንበኞች ግብራቸውን በኦንላይን እንዲከፍሉ ለማስቻል ከኦሮሚያ፤ ወጋገን እና ዘመን ባንክ ጋር ስምምነት ተፈራርሟል ተብሏል።ስምምነቱ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የታክስ አሰባሰቡን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ እና ደንበኛውም በኦንላይን በየትኛውም ጊዜ እና ቦታ ሆኖ ግብሩን መክፈል ያስችለዋል ነው የተባለው።
የገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ክፍያ በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ ለማሰባሰብ በሚያደርገው ጥረት ንግድ ባንክን ጨምሮ ከአራት ባንኮች ጋር እየሠራ መሆኑንም ተመላክቷል።
በሚኒስቴሩ የታክስ ኦፕሬሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ መሠረት መስቀሌ፤ የታክስ አስተዳደር ሥርዓቱን ዓለም በደረሰበት ቴክኖሎጂ በመደገፍ የአገልግሎት አሰጣጡ ግልጽ፤ ቀልጣፋ እና ተደራሽ በሆነ መንገድ መስጠት ዋናው የተቋሙ ተልእኮ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አያይዘውም የግብር ሥርዓቱን ይበልጥ ለማዘመን ሌሎች ባንኮችም ወደ ሥርዓቱ እንዲገቡ ጥሪ ማቅረባቸው ተዘግቧል።
ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ: https://addismaleda.com/archives/27774
@YeneTube @FikerAssefa
የገቢዎች ሚኒስቴር ደንበኞች ግብራቸውን በኦንላይን እንዲከፍሉ ለማስቻል ከኦሮሚያ፤ ወጋገን እና ዘመን ባንክ ጋር ስምምነት ተፈራርሟል ተብሏል።ስምምነቱ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የታክስ አሰባሰቡን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ እና ደንበኛውም በኦንላይን በየትኛውም ጊዜ እና ቦታ ሆኖ ግብሩን መክፈል ያስችለዋል ነው የተባለው።
የገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ክፍያ በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ ለማሰባሰብ በሚያደርገው ጥረት ንግድ ባንክን ጨምሮ ከአራት ባንኮች ጋር እየሠራ መሆኑንም ተመላክቷል።
በሚኒስቴሩ የታክስ ኦፕሬሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ መሠረት መስቀሌ፤ የታክስ አስተዳደር ሥርዓቱን ዓለም በደረሰበት ቴክኖሎጂ በመደገፍ የአገልግሎት አሰጣጡ ግልጽ፤ ቀልጣፋ እና ተደራሽ በሆነ መንገድ መስጠት ዋናው የተቋሙ ተልእኮ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አያይዘውም የግብር ሥርዓቱን ይበልጥ ለማዘመን ሌሎች ባንኮችም ወደ ሥርዓቱ እንዲገቡ ጥሪ ማቅረባቸው ተዘግቧል።
ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ: https://addismaleda.com/archives/27774
@YeneTube @FikerAssefa
አሜሪካ ሶማሊያ ውስጥ የአልሻባብ ታጣቂዎችን ኢላማ ያደረገ የአየር ጥቃት ፈጽማ በቡድኑ ላይ ጉዳት ማድረሷን የሶማሊያ መንግሥት አስታወቀ።
ከሶማሊያ የማስታወቂያ ሚኒስቴር የወጣ መግለጫ እንዳመለከተው “ከአገሪቱ መንግሥት ጋር በመቀናጀት” ትናንት አርብ በተፈጸመው የአየር ጥቃት አምስት የአልሻባብ ታጣቂዎች ተገድለዋል።
የሶማሊያ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት የአየር ጥቃቱን በተመለከተ በትዊተር ላይ ባወጣው መግለጫ፣ እርምጃው የአልሻባብ ታጣቂዎች ከኪስማዮ ከተማ ደቡብ ምዕራብ በሚገኝ አካባቢ ያለ የሶማሊያ መንግሥት ኃይሎች ላይ ጥቃት ከፈጸሙ በኋላ ነው።
ይህ ጥቃት የተፈፀመው አሜሪካ ወታደሮቿን ወደ ሶማሊያ መልሳ ለማስፈር ከወሰነች ከሳምንታት በኋላ ነው። ፕሬዝዳንት ባይደን 500 የሚሆኑ የልዩ ተልዕኮ ወታደሮቻቸው ወደ ሶማሊያ እንዲሰማሩ የወሰኑት በሶማሊያ ከተካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ በኋላ ነበር።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
ከሶማሊያ የማስታወቂያ ሚኒስቴር የወጣ መግለጫ እንዳመለከተው “ከአገሪቱ መንግሥት ጋር በመቀናጀት” ትናንት አርብ በተፈጸመው የአየር ጥቃት አምስት የአልሻባብ ታጣቂዎች ተገድለዋል።
የሶማሊያ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት የአየር ጥቃቱን በተመለከተ በትዊተር ላይ ባወጣው መግለጫ፣ እርምጃው የአልሻባብ ታጣቂዎች ከኪስማዮ ከተማ ደቡብ ምዕራብ በሚገኝ አካባቢ ያለ የሶማሊያ መንግሥት ኃይሎች ላይ ጥቃት ከፈጸሙ በኋላ ነው።
ይህ ጥቃት የተፈፀመው አሜሪካ ወታደሮቿን ወደ ሶማሊያ መልሳ ለማስፈር ከወሰነች ከሳምንታት በኋላ ነው። ፕሬዝዳንት ባይደን 500 የሚሆኑ የልዩ ተልዕኮ ወታደሮቻቸው ወደ ሶማሊያ እንዲሰማሩ የወሰኑት በሶማሊያ ከተካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ በኋላ ነበር።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
ራይድ የትራንስፖርት አገልግሎት በስሩ ያሉ ከ40ሺ በላይ የሚልቁ አሽከርካሪዎች መኪናዎቻቸውን በኤሌክትሪክ ሃይል ወደሚሰራ መኪና እንዲቀይሩ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።
የራይድ መስራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወ/ት ሳምራዊት ፍቅሩ ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት፤ ድርጅታቸው በስሩ አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ ከ40ሺ በላይ የሚሆኑ አሽከርካሪዎች ከባንክና ከመኪና አምራች ኩባንያዎች ጋር በማስተሳሰር መኪናዎቻቸውን ዘመናዊና በኤሌክትሪክ ሃይል ወደሚሰራ ተሽከርካሪ ለመቀየር እየሰራ ነው።
እንደዋና ሥራ አስፈፃሚዋ ገለፃ፤ የተሽከርካሪዎቹ መቀየር ከጊዜ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የነዳጅና የተሽከሪካሪ መለዋወጫ ወጪን በመቀነስ ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል። በተለይም አገሪቱ ለነዳጅና ለተሽከርካሪ መለዋወጭ የምታወጣው የውጭ ምንዛሬ በመታደግ ለሌላ የልማት ሥራ እንድታውለው ለማድረግ የጎላ ሚና አለው። በተጨማሪም በከተሞች የሚስተዋለውን ከፍተኛ የበካይ ጋዝ ልቀትን ለመከላከል ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል።
ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከነዳጁ ባሻገር መለዋወጫዎችን ከውጭ በበርካታ ቢሊዮን ዶላር በማውጣት እያስመጣች በመሆኑ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እንዲባባስ ምክንያት እንደሆነ ዋና ስራ አስፈፃሚዋ አስረድተዋል። ይህም ሀገሪቱ ለዘመናት የኢኮኖሚ ጥገኛ እንድትሆን ያደረጋት መሆንኑም አብራርተዋል። ‹‹በመሆኑም ጥገኝነታችንን እየቀነስን ለመምጣት ከውጭ የሚመጣውን እዚሁ የሚተካበትን መንገድ መፍጠር አለብን። አንደኛው ደግሞ በነዳጅ ከሚነዳው መኪና ወደ ኤሌክትሪክ መኪና መሸጋገር አዋጭ ነው›› ብለዋል።
ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ: https://www.press.et/?p=74326
@YeneTube @FikerAssefa
የራይድ መስራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወ/ት ሳምራዊት ፍቅሩ ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት፤ ድርጅታቸው በስሩ አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ ከ40ሺ በላይ የሚሆኑ አሽከርካሪዎች ከባንክና ከመኪና አምራች ኩባንያዎች ጋር በማስተሳሰር መኪናዎቻቸውን ዘመናዊና በኤሌክትሪክ ሃይል ወደሚሰራ ተሽከርካሪ ለመቀየር እየሰራ ነው።
እንደዋና ሥራ አስፈፃሚዋ ገለፃ፤ የተሽከርካሪዎቹ መቀየር ከጊዜ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የነዳጅና የተሽከሪካሪ መለዋወጫ ወጪን በመቀነስ ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል። በተለይም አገሪቱ ለነዳጅና ለተሽከርካሪ መለዋወጭ የምታወጣው የውጭ ምንዛሬ በመታደግ ለሌላ የልማት ሥራ እንድታውለው ለማድረግ የጎላ ሚና አለው። በተጨማሪም በከተሞች የሚስተዋለውን ከፍተኛ የበካይ ጋዝ ልቀትን ለመከላከል ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል።
ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከነዳጁ ባሻገር መለዋወጫዎችን ከውጭ በበርካታ ቢሊዮን ዶላር በማውጣት እያስመጣች በመሆኑ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እንዲባባስ ምክንያት እንደሆነ ዋና ስራ አስፈፃሚዋ አስረድተዋል። ይህም ሀገሪቱ ለዘመናት የኢኮኖሚ ጥገኛ እንድትሆን ያደረጋት መሆንኑም አብራርተዋል። ‹‹በመሆኑም ጥገኝነታችንን እየቀነስን ለመምጣት ከውጭ የሚመጣውን እዚሁ የሚተካበትን መንገድ መፍጠር አለብን። አንደኛው ደግሞ በነዳጅ ከሚነዳው መኪና ወደ ኤሌክትሪክ መኪና መሸጋገር አዋጭ ነው›› ብለዋል።
ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ: https://www.press.et/?p=74326
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ የትምህርት ሥነ ሥርዓት /ካሪኩለም/ መስማት ለተሰናቸው ተማሪዎች አካታች አለመሆኑ ጫና እየፈጠረባቸው እንደሆነ ተነገረ፡፡
መስማት የተሳናቸው ተማሪዎች የሚገጥሟቸውን ችግሮች ለመቀነስ ROOTS & wings በመባል የሚጠራ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ከአልፋ መስማት የተሰናቸው ልዩ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ጋር በመተባበር ችግሮቻቸውን ለመቀነስ ፣ጥራት ያለው ትምህርት መስማት ለተሰናቸው ሴት ተማሪዎች በሚል ሀሳብ ሥራ መጀመራቸው ይፋ አድርገዋል፡፡
ሴት መስማት የተሳናቸው ተማሪዎች ከወንዶች የበለጠ ፍላጎቶች ስለሚያስፈልጓቸው ሴቶችን ላይ የበለጠ ትኩረት አድርገን የትምህርት ሥርዓት መፍጠር ላይ እንሰራለን ያሉት የ ROOTS & wings መስራቾች መካካል አንዷ የሆኑት ዶ/ር ሰርካለም ግርማ ናቸው፡፡
መስማት በተሳናቸው ተማሪዎች ላይ የተጠኑ ጥናቶች በተለይም የመማሪያ መሳሪያዎች ፈፅሞ ለተማሪዎች እንደማይመቹ ፣ ወላጆች ጋር ያላቸው የመግባቢያ ቋንቋ ችግር ፣ ለተማሪዎቹ ለመግለፅ የሚያዳግቱ ቋንቋዎች መኖራቸውን የጠቀሱት ዶ/ር ሰርካለም ግርማ እነዚህን ችግሮች ለመፍታት ROOTS & wings በተቻለ አቅም ይሰራል ብለዋል፡፡
የድርጅቱ ከፍተኛ ትምህርት አማካሪ ዶ/ር ስለሺ ይትባረክ አልፋ መስማት የተሰናቸው ልዩ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ድርጅታቸው ሲሰራ የተማሪ የመማሪያ መፅሐፍቶችን ወደ ምልክት ቋንቋ መቀየር ፣ ለመምህራኖች እና ለወላጆች ሥልጠና መስጠት ፣ለሴት ተማሪዎች ክበባት ማቋቋም ፣ግንዛቤ የመፍጠሪያ መድረኮች መጀመር እና መሰል ሥራዎችን እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል፡፡በተመሳሳይ ሥራቸው አንድ ት/ቤት ውስጥ ተወስኖ የሚቀር እንዳልሆነ ለወደፊት የተለያዩ ት/ቤቶች ጋር እንደሚሰሩ ተሰምቷል፡፡
Via Sheger FM
@YeneTube @FikerAssefa
መስማት የተሳናቸው ተማሪዎች የሚገጥሟቸውን ችግሮች ለመቀነስ ROOTS & wings በመባል የሚጠራ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ከአልፋ መስማት የተሰናቸው ልዩ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ጋር በመተባበር ችግሮቻቸውን ለመቀነስ ፣ጥራት ያለው ትምህርት መስማት ለተሰናቸው ሴት ተማሪዎች በሚል ሀሳብ ሥራ መጀመራቸው ይፋ አድርገዋል፡፡
ሴት መስማት የተሳናቸው ተማሪዎች ከወንዶች የበለጠ ፍላጎቶች ስለሚያስፈልጓቸው ሴቶችን ላይ የበለጠ ትኩረት አድርገን የትምህርት ሥርዓት መፍጠር ላይ እንሰራለን ያሉት የ ROOTS & wings መስራቾች መካካል አንዷ የሆኑት ዶ/ር ሰርካለም ግርማ ናቸው፡፡
መስማት በተሳናቸው ተማሪዎች ላይ የተጠኑ ጥናቶች በተለይም የመማሪያ መሳሪያዎች ፈፅሞ ለተማሪዎች እንደማይመቹ ፣ ወላጆች ጋር ያላቸው የመግባቢያ ቋንቋ ችግር ፣ ለተማሪዎቹ ለመግለፅ የሚያዳግቱ ቋንቋዎች መኖራቸውን የጠቀሱት ዶ/ር ሰርካለም ግርማ እነዚህን ችግሮች ለመፍታት ROOTS & wings በተቻለ አቅም ይሰራል ብለዋል፡፡
የድርጅቱ ከፍተኛ ትምህርት አማካሪ ዶ/ር ስለሺ ይትባረክ አልፋ መስማት የተሰናቸው ልዩ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ድርጅታቸው ሲሰራ የተማሪ የመማሪያ መፅሐፍቶችን ወደ ምልክት ቋንቋ መቀየር ፣ ለመምህራኖች እና ለወላጆች ሥልጠና መስጠት ፣ለሴት ተማሪዎች ክበባት ማቋቋም ፣ግንዛቤ የመፍጠሪያ መድረኮች መጀመር እና መሰል ሥራዎችን እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል፡፡በተመሳሳይ ሥራቸው አንድ ት/ቤት ውስጥ ተወስኖ የሚቀር እንዳልሆነ ለወደፊት የተለያዩ ት/ቤቶች ጋር እንደሚሰሩ ተሰምቷል፡፡
Via Sheger FM
@YeneTube @FikerAssefa
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ሩሲያ ዶንባስ የተሰኘ ሮኬት ወደ አለም አቀፉ የጠፈር ጣቢያ አመጠቀች
ሩሲያ ትናንት አርብ ዶንባስ የተሰኘ ሮኬት ወደ አለም አቀፉ የጠፈር ጣቢያ አስወንጭፋለች ፡፡
ስያሜው በዩክሬን ዶንባስ ግዛት ውስጥ ለሚገኙ ተገንጣይ ሪፐብሊካኖች (የዶኔትስክ እና የሉሃንስክ ህዝባዊ ሪፐብሊኮች) ክብር ለመስጠት በማሰብ የተሰጠ ነው፡፡
የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት 100 ቀናትን አስቆጥሯል፡፡
@Yenetube @Fikerassefa
ሩሲያ ትናንት አርብ ዶንባስ የተሰኘ ሮኬት ወደ አለም አቀፉ የጠፈር ጣቢያ አስወንጭፋለች ፡፡
ስያሜው በዩክሬን ዶንባስ ግዛት ውስጥ ለሚገኙ ተገንጣይ ሪፐብሊካኖች (የዶኔትስክ እና የሉሃንስክ ህዝባዊ ሪፐብሊኮች) ክብር ለመስጠት በማሰብ የተሰጠ ነው፡፡
የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት 100 ቀናትን አስቆጥሯል፡፡
@Yenetube @Fikerassefa
የመንግስትን የሰላም ጥሪ የተቀበሉ እና ስልጠና የወሰዱ ኃይሎች በተለያየ የልማት ስራ ላይ መሰማራት መጀመራቸውን የመተከል ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጋሹ ዱጋዝ ገልፀዋል።
ፅንፈኛ አመለካከት ይዘው ሲዋጉ የነበሩት ታጣቂ ኃይሎች የመተከል ዞን የተቀናጀ ኮማንድ ፖስት እና የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባከናወኑት የፀጥታ ስራ አብዛኞቹ የመንግስትን ጥሪ የተቀበሉና ስልጠና የወሰዱ አባላት በእርሻ በማዕድን ዘርፍ እና ቀደም ሲል በነበሩት የስራ መስክ ላይ ተሰማርተዋል።
ከ 4 እና 5 ወራት በፊት የነበረው የፀጥታ ችግር በመቀረፉ አሁን ላይ የመተከል ዞን ፊቷን ወደልማት ማዞር ጀምራለች ያሉት አስተዳዳሪው አቶ ጋሹ በእርሻ ስራ ለመሰማራት ለተደራጁ አባላት በቅድሚያ 6 የእርሻ ትራክተሮች መንግስት 30 ከመቶ ቅድመ ክፍያን በመሸፈን ለርክክብ ዝግጁ ሆነዋል ብለዋል።
ትራክተሮቹ በሁሉም የመተከል ዞን ወረዳዎች የሚታደሉ ሲሆን 11ተጨማሪ ትራክተሮችም በግዥ ሒደት ላይ እንዳሉ ገልፀዋል።
የተሃድሶ ስልጠና ከወሰዱት ተመላሽ ታጣቂዎች መካከል 17 በማዕድን ስራ 92 በንግድ ስራ ወደነበሩበት የመንግስት ስራ የተመለሱ 43 እንዲሁም 493 አባላት ደግሞ በፀጥታ ስራ ላይ ተሰማርተዋል።
ወደፀጥታ ስራ እየተሰማሩ ላሉት በቂ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን የገለፁት ደግሞ በመተከል ዞን የተቀናጀ ኮማንድ ፖስት የዳንጉር ወረዳ ኮማንድ ፖስት ሰብሳቢ ሻለቃ ደምስ ዳኜ ናቸው።
አሁን ላይ የፀጥታ ስራው በአካባቢው የፀጥታ ኃይሎች ጭምር እየተከናወነ በመሆኑ ዜጎችን ወደቀያቸው የመመለስ ስራም ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
ፅንፈኛ አመለካከት ይዘው ሲዋጉ የነበሩት ታጣቂ ኃይሎች የመተከል ዞን የተቀናጀ ኮማንድ ፖስት እና የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባከናወኑት የፀጥታ ስራ አብዛኞቹ የመንግስትን ጥሪ የተቀበሉና ስልጠና የወሰዱ አባላት በእርሻ በማዕድን ዘርፍ እና ቀደም ሲል በነበሩት የስራ መስክ ላይ ተሰማርተዋል።
ከ 4 እና 5 ወራት በፊት የነበረው የፀጥታ ችግር በመቀረፉ አሁን ላይ የመተከል ዞን ፊቷን ወደልማት ማዞር ጀምራለች ያሉት አስተዳዳሪው አቶ ጋሹ በእርሻ ስራ ለመሰማራት ለተደራጁ አባላት በቅድሚያ 6 የእርሻ ትራክተሮች መንግስት 30 ከመቶ ቅድመ ክፍያን በመሸፈን ለርክክብ ዝግጁ ሆነዋል ብለዋል።
ትራክተሮቹ በሁሉም የመተከል ዞን ወረዳዎች የሚታደሉ ሲሆን 11ተጨማሪ ትራክተሮችም በግዥ ሒደት ላይ እንዳሉ ገልፀዋል።
የተሃድሶ ስልጠና ከወሰዱት ተመላሽ ታጣቂዎች መካከል 17 በማዕድን ስራ 92 በንግድ ስራ ወደነበሩበት የመንግስት ስራ የተመለሱ 43 እንዲሁም 493 አባላት ደግሞ በፀጥታ ስራ ላይ ተሰማርተዋል።
ወደፀጥታ ስራ እየተሰማሩ ላሉት በቂ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን የገለፁት ደግሞ በመተከል ዞን የተቀናጀ ኮማንድ ፖስት የዳንጉር ወረዳ ኮማንድ ፖስት ሰብሳቢ ሻለቃ ደምስ ዳኜ ናቸው።
አሁን ላይ የፀጥታ ስራው በአካባቢው የፀጥታ ኃይሎች ጭምር እየተከናወነ በመሆኑ ዜጎችን ወደቀያቸው የመመለስ ስራም ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
አቶ ደመቀ ህወሓት ለጥፋት ዓላማ ሊጠቀምባቸው የሚችሉ ቁሳቁሶች እንዳያልፉ ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳሰቡ!
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ለጥፋት ዓላማ ሊጠቀምባቸው የሚችሉ ቁሳቁሶች ለህወሓት እንዳይተላለፉ አሳሰቡ፡፡አቶ ደመቀ በአፋር ክልል ሰርዶ ኬላ ተገኝተው የሰብዓዊ ድጋፎችን ትግራይ ክልል ለማድረስ የሚደረጉ ጥረቶችን ከሌሎች የፌዴራል እና የክልሉ ባለስልጣናት ጋር በመሆን ጎብኝተዋል፡፡አቶ ደመቀ የአፋር ህዝብ በህወሓት ወረራ ምክንያት ከ1 ሚሊየን በላይ ተፈናቃዮችን ይዞ መንግስት ለትግራይ ህዝብ ሰብዓዊ እርዳታ ለማቅረብ እያደረገ ለሚገኘው ጥረት ያሳየውን ቀና ትብብር አድንቀዋል፡፡
በየደረጃው ያሉትን የክልሉን ነዋሪዎች ያመሰገኑም ሲሆን ሰብዓዊ እርዳታዎችን በሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች ወደተጎዱ ወገኖች ለማድረስ መንግስት በትኩረት እየሰራ መሆኑንም አብራርተዋል፤ ከዚህም ውስጥ ለትግራይ ክልል ነዋሪዎች የሚደረገው ድጋፍ አንዱ መሆኑን በመጠቆም፡፡በሰርዶ ኬላ ተገቢው የፍተሻና ተያያዥ ቁጥጥር ከተደረገበት በኋላ በቀን እስከ 200 ኮንቮይ ተሽከርካሪዎች ሰብዓዊ እርዳታ ጭነው ወደ ትግራይ እንደሚያቀኑም ተናግረዋል አቶ ደመቀ፡፡ይሁንና በተደረገዉ ፍተሻ ለሽብር ቡድኑ የጥፋት አላማ ማስፈጸሚያ ሊውሉ የሚችሉ ከተፈቀደው የነዳጅ መጠን በላይ ተጨማሪ ነዳጅና አንዳንድ ያልተፈቀዱ ቁሳቁሶች ለማሳለፍ ሙከራዎች አንዳሉ መገንዘባቸውን ነው የተናገሩት፡፡
https://am.al-ain.com/article/demeke-mekonnen-warned-to-be-careful-not-to-pass-on-materials-that-could-be-used-by-tplf
@YeneTube @FikerAssefa
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ለጥፋት ዓላማ ሊጠቀምባቸው የሚችሉ ቁሳቁሶች ለህወሓት እንዳይተላለፉ አሳሰቡ፡፡አቶ ደመቀ በአፋር ክልል ሰርዶ ኬላ ተገኝተው የሰብዓዊ ድጋፎችን ትግራይ ክልል ለማድረስ የሚደረጉ ጥረቶችን ከሌሎች የፌዴራል እና የክልሉ ባለስልጣናት ጋር በመሆን ጎብኝተዋል፡፡አቶ ደመቀ የአፋር ህዝብ በህወሓት ወረራ ምክንያት ከ1 ሚሊየን በላይ ተፈናቃዮችን ይዞ መንግስት ለትግራይ ህዝብ ሰብዓዊ እርዳታ ለማቅረብ እያደረገ ለሚገኘው ጥረት ያሳየውን ቀና ትብብር አድንቀዋል፡፡
በየደረጃው ያሉትን የክልሉን ነዋሪዎች ያመሰገኑም ሲሆን ሰብዓዊ እርዳታዎችን በሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች ወደተጎዱ ወገኖች ለማድረስ መንግስት በትኩረት እየሰራ መሆኑንም አብራርተዋል፤ ከዚህም ውስጥ ለትግራይ ክልል ነዋሪዎች የሚደረገው ድጋፍ አንዱ መሆኑን በመጠቆም፡፡በሰርዶ ኬላ ተገቢው የፍተሻና ተያያዥ ቁጥጥር ከተደረገበት በኋላ በቀን እስከ 200 ኮንቮይ ተሽከርካሪዎች ሰብዓዊ እርዳታ ጭነው ወደ ትግራይ እንደሚያቀኑም ተናግረዋል አቶ ደመቀ፡፡ይሁንና በተደረገዉ ፍተሻ ለሽብር ቡድኑ የጥፋት አላማ ማስፈጸሚያ ሊውሉ የሚችሉ ከተፈቀደው የነዳጅ መጠን በላይ ተጨማሪ ነዳጅና አንዳንድ ያልተፈቀዱ ቁሳቁሶች ለማሳለፍ ሙከራዎች አንዳሉ መገንዘባቸውን ነው የተናገሩት፡፡
https://am.al-ain.com/article/demeke-mekonnen-warned-to-be-careful-not-to-pass-on-materials-that-could-be-used-by-tplf
@YeneTube @FikerAssefa
አቶ ጃዋር መሐመድ በእስር ላይ በቆዩባቸው ጊዜያት ለሳቸው እና አብረዋቸው ለታሰሩ ሰዎች ከእስር እንዲለቀቁ ደጋፊዎቻቸው አድርገዋል ላሉት ጥረት ዛሬ ምስጋና አቀረቡ።
የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ አቶ ጃዋር መሐመድ ምስጋናውን ያቀረቡት ዛሬ በጀርመን ኑርንበርግ ከተማ አቅራቢያ በተዘጋጀ ህዝባዊ ስብሰባ ላይ በአካል ተገኝተው ነው። ይህ የጉዟቸው አንደኛው አላማ ሲሆን ሌላኛዋ አላማ በብዙ ውጥንቅጥ ውስጥ የምትገኘው ኢትዮጵያ ላይ ሰላም እንዲሰፍን ለማስቻል በሚደረግ ጥረት ውስጥ ደጋፊዎቻቸው የበኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱ ለማሳሰብ ነው ተብሏል። ጉብኝታቸው አውሮፓ እና ሰሜን አሜሪካን የሚያካልል ሲሆን በቀጣይ ደግሞ ፈረንሳይ፣ ኔዘርላንድስ እና ቤልጄም ከመሳሰሉ የአውሮፓ ሀገራት ከደጋፊዎቻቸው ጋር ከተገናኙ በኋላ ወደ ሰሜን አሜሪካ እንደሚያቀኑ ዶይቸ ቬለ ዘግቧል።አቶ ጃዋር መሐመድ የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያን ተከትሎ ለሁለት ዓመት ገደማ ያህል በእስር ላይ መቆየታቸው ይታወሳል።
@YeneTube @FikerAssefa
የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ አቶ ጃዋር መሐመድ ምስጋናውን ያቀረቡት ዛሬ በጀርመን ኑርንበርግ ከተማ አቅራቢያ በተዘጋጀ ህዝባዊ ስብሰባ ላይ በአካል ተገኝተው ነው። ይህ የጉዟቸው አንደኛው አላማ ሲሆን ሌላኛዋ አላማ በብዙ ውጥንቅጥ ውስጥ የምትገኘው ኢትዮጵያ ላይ ሰላም እንዲሰፍን ለማስቻል በሚደረግ ጥረት ውስጥ ደጋፊዎቻቸው የበኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱ ለማሳሰብ ነው ተብሏል። ጉብኝታቸው አውሮፓ እና ሰሜን አሜሪካን የሚያካልል ሲሆን በቀጣይ ደግሞ ፈረንሳይ፣ ኔዘርላንድስ እና ቤልጄም ከመሳሰሉ የአውሮፓ ሀገራት ከደጋፊዎቻቸው ጋር ከተገናኙ በኋላ ወደ ሰሜን አሜሪካ እንደሚያቀኑ ዶይቸ ቬለ ዘግቧል።አቶ ጃዋር መሐመድ የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያን ተከትሎ ለሁለት ዓመት ገደማ ያህል በእስር ላይ መቆየታቸው ይታወሳል።
@YeneTube @FikerAssefa
በምስራቅ ሐረርጌ ዞን በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ14 ሰዎች ህይወት አለፈ!
በምስራቅ ሐረርጌ ዞን ቀርሳ ወረዳ ከቀኑ 8፡30 አካባቢ የጭነት አይሱዙ ተሽከርካሪ ባደረሰው አደጋ የ14 ሰዎች ህይወት ወዲያውኑ ማለፉን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ፡፡የዞኑ ፖሊስ መምሪያ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዲቪዥን ኃላፊ ኢንስፔክተር ቶሎሳ ጐሹ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደተናገሩት ፥ አደጋው የደረሰው ተሽከርካሪው ከድሬዳዋ ወደ አዲስ አበባ ሲሚንቶ ጭኖ እየተጓዘ ባለበት ወቅት ቀርሳ ከተማ ሲደርስ ፍሬን አልታዘዝ ብሎት ወደ ገበያ በመሄድ ላይ የነበሩ መንገደኞችን በመግጨቱ መሆኑንም ተናግረዋል።
በዚህም 8 ወንዶችና 6 ሴቶች ህይወታቸው አልፏል።በአደጋው ህይወታቸው ካለፈው በተጨማሪ ሁለት ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው ለከፍተኛ ህክምና ወደ ድሬዳዋ ከተማ ተልከዋል።የአደጋው መንስኤ ከፍጥነት ወሠን በላይ ማሽከርከርና ፍሬ ለመያዝ አለመቻል መሆኑንም ገልጸዋል።ተሽከርካሪው በእግረኞች ላይ ጉዳት ካደረሰ በኋላ መገልበጡን የገለፁት ኢኒስፔክተር ቶሎሳ አሽከርካሪው ጉዳት ደርሶበት በቁጥጥር ስር መዋሉን ጠቁመዋል።
[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa
በምስራቅ ሐረርጌ ዞን ቀርሳ ወረዳ ከቀኑ 8፡30 አካባቢ የጭነት አይሱዙ ተሽከርካሪ ባደረሰው አደጋ የ14 ሰዎች ህይወት ወዲያውኑ ማለፉን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ፡፡የዞኑ ፖሊስ መምሪያ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዲቪዥን ኃላፊ ኢንስፔክተር ቶሎሳ ጐሹ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደተናገሩት ፥ አደጋው የደረሰው ተሽከርካሪው ከድሬዳዋ ወደ አዲስ አበባ ሲሚንቶ ጭኖ እየተጓዘ ባለበት ወቅት ቀርሳ ከተማ ሲደርስ ፍሬን አልታዘዝ ብሎት ወደ ገበያ በመሄድ ላይ የነበሩ መንገደኞችን በመግጨቱ መሆኑንም ተናግረዋል።
በዚህም 8 ወንዶችና 6 ሴቶች ህይወታቸው አልፏል።በአደጋው ህይወታቸው ካለፈው በተጨማሪ ሁለት ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው ለከፍተኛ ህክምና ወደ ድሬዳዋ ከተማ ተልከዋል።የአደጋው መንስኤ ከፍጥነት ወሠን በላይ ማሽከርከርና ፍሬ ለመያዝ አለመቻል መሆኑንም ገልጸዋል።ተሽከርካሪው በእግረኞች ላይ ጉዳት ካደረሰ በኋላ መገልበጡን የገለፁት ኢኒስፔክተር ቶሎሳ አሽከርካሪው ጉዳት ደርሶበት በቁጥጥር ስር መዋሉን ጠቁመዋል።
[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በሰሜናዊ ኬንያ የዋጅር አውራጃ ፖሊስ ጣቢያ የታሰሩ ዘጠኝ ኢትዮጵያዊያን ፍልሰተኞችን በአካል መጌብኘቱንና ፍልሰተኞቹ በምን አኳኋን እንደታሰሩ ቃላቸውን መቀበሉን በድረገጹ ገልጧል።
ፍልሰተኞቹ በሕገወጥ ሰው አዘዋዋሪዎች አማካኝነት ወደ ኬንያ በሕገወጥ መንገድ በመግባት የታሰሩ ሲሆኑ፣ ሁሉም እድሜያቸው ከ18 በታች እንደሆነ እና አራቱ ሴቶች እንደሆኑ ኮሚሽኑ ጠቅሷል። በእስር ቤቱ ሌሎች ከ18 ዓመት በላይ የሚሆናቸው 18 ሕገወጥ ፍልሰተኛ ኢትዮጵያዊያን ታስረው እንደሚገኙ ማረጋገጠንም ኮሚሽኑ ገልጧል። ኮሚሽኑ ከጎረቤት አገራት አቻ ተቋማት ጋር በመተባበር፣ ፍልሰት መደበኛ፣ ሥርዓት ያለውና ደኅንነቱ የተጠበቀ እንዲሆን እየሰራሁ ነው ብሏል።
@YeneTube @FikerAssefa
ፍልሰተኞቹ በሕገወጥ ሰው አዘዋዋሪዎች አማካኝነት ወደ ኬንያ በሕገወጥ መንገድ በመግባት የታሰሩ ሲሆኑ፣ ሁሉም እድሜያቸው ከ18 በታች እንደሆነ እና አራቱ ሴቶች እንደሆኑ ኮሚሽኑ ጠቅሷል። በእስር ቤቱ ሌሎች ከ18 ዓመት በላይ የሚሆናቸው 18 ሕገወጥ ፍልሰተኛ ኢትዮጵያዊያን ታስረው እንደሚገኙ ማረጋገጠንም ኮሚሽኑ ገልጧል። ኮሚሽኑ ከጎረቤት አገራት አቻ ተቋማት ጋር በመተባበር፣ ፍልሰት መደበኛ፣ ሥርዓት ያለውና ደኅንነቱ የተጠበቀ እንዲሆን እየሰራሁ ነው ብሏል።
@YeneTube @FikerAssefa
የተቃዋሚ ፓርቲዎች የምክክር ቤት (caucus) ተቋቋመ።
በሀገራዊ የምክክር መድረክ አካሄድ ላይ መሰረታዊ ቅሬታ አለን ያሉ 10 የሚደርሱ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች
"እውነተኛ የዴሞክራሲ ስርአትን የሚያስገኝ ሀገራዊ ውይይት አማራጭን ለማቅረብ የሚያስችል የምክክር ቤት (Caucus) አቋቁመናል" ሲሉ በዛሬው ዕለት ባወጡት መግለጫ አሳውቀዋል።
ሀገራዊ ምክክር በምን መልኩ ይካሄድ በሚለው ላይ ክርክሮች እየተደረጉ ባለበት ወቅት " መንግስት ሂደቱን የሚቆጣጠር ረቂቅ ህግ በማዘጋጀት በአንድ ፓርቲ የበላይነት ባለው ፓርላማ በኩል የፖለቲካ ፓርቲዎችን ጥያቄ እና የግብአት ሀሳብ ችላ በማለት እንዲፀድቅ ማድረጉን ያስታወሰው የፓርቲዎቹ መግለጫ የኮሚሽነሮቹን ምርጫም "የተድበሰበሰ" ነበር ሲል ኮንኗል።
በትጥቅ እየተፋለሙ የሚገኙ አካላትን ወደ ምክክሩ ለመጋበዝ የተቀመጠ ድንጋጌ አለመኖሩን የነቀፈው የምክክር ቤቱ መግለጫ "አማራጭ" በተባለው አዲስ የምክክር ቤት (Caucus) በኩልም
ለመንግስት በርከት ያሉ ምክረሀሳቦችንም አቅርቧል።
በምክረሀሳቦቹም ላይ:-
-አፋጣኝ እና አለም አቀፍ ተቋማት የሚቆጣጠሩት የተኩስ ማቆም በሁሉም የኢትዮጵያ ክፍሎች ላይ እንዲደረግ
-የምክክር ኮሚሽኑ በድጋሜ እንዲቋቋም እና ኮሚሽነሮቹም ገለልተኛ በሆነ መንገድ እንዲመረጡ
- የውይይት አጀንዳዎቹ ሁሉንም ባሳተፈ መልኩ እንዲቀረፁ እንዲሁም
-ውይይቶቹ አለም አቀፍ ታዛቢ በተገኘበት እንዲደረጉ
አሳስቧል።
የምክክር ቤቱን የመሰረቱት ፓርቲዎችም
1- መድረክ
2- ህብር ኢትዮጵያ
3- የአፋር ህዝብ ፓርቲ
4- የአፋር ፍትህ እና ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ
5- የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ)
6- የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ
7-የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር
8- የዎላይታ ብሄራዊ ንቅናቄ
9- ዓረና ትግራይ
10- የዶንጋ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት
መሆናቸው ተገልፃል።
ስለ ምክክር ቤቱ ለሚዲያችን አስተያየታቸውን የሰጡት የአፋር ህዝብ ፓርቲ መሪ እና የምክክር ቤቱ ሊቀመንበር ሆነው የተመረጡት አቶ ሙሳ አደም "ፓርቲዎቹ በተለያየ ጉዳይ ላይ የተለያየ አቋም ቢኖራቸውም ሀገራዊ ምክክሩ በሀቀኛ መንገድ መከናወን አለበት የሚለው ላይ ግን የማያወላዳ የጋራ አቋም አላቸው፤ አማራጭ የምክክር ቤት ለማቋቋም የወሰነውም ለዚህ ነው"
ብለዋል።
[Ubuntu News]
@YeneTube @FikerAssefa
በሀገራዊ የምክክር መድረክ አካሄድ ላይ መሰረታዊ ቅሬታ አለን ያሉ 10 የሚደርሱ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች
"እውነተኛ የዴሞክራሲ ስርአትን የሚያስገኝ ሀገራዊ ውይይት አማራጭን ለማቅረብ የሚያስችል የምክክር ቤት (Caucus) አቋቁመናል" ሲሉ በዛሬው ዕለት ባወጡት መግለጫ አሳውቀዋል።
ሀገራዊ ምክክር በምን መልኩ ይካሄድ በሚለው ላይ ክርክሮች እየተደረጉ ባለበት ወቅት " መንግስት ሂደቱን የሚቆጣጠር ረቂቅ ህግ በማዘጋጀት በአንድ ፓርቲ የበላይነት ባለው ፓርላማ በኩል የፖለቲካ ፓርቲዎችን ጥያቄ እና የግብአት ሀሳብ ችላ በማለት እንዲፀድቅ ማድረጉን ያስታወሰው የፓርቲዎቹ መግለጫ የኮሚሽነሮቹን ምርጫም "የተድበሰበሰ" ነበር ሲል ኮንኗል።
በትጥቅ እየተፋለሙ የሚገኙ አካላትን ወደ ምክክሩ ለመጋበዝ የተቀመጠ ድንጋጌ አለመኖሩን የነቀፈው የምክክር ቤቱ መግለጫ "አማራጭ" በተባለው አዲስ የምክክር ቤት (Caucus) በኩልም
ለመንግስት በርከት ያሉ ምክረሀሳቦችንም አቅርቧል።
በምክረሀሳቦቹም ላይ:-
-አፋጣኝ እና አለም አቀፍ ተቋማት የሚቆጣጠሩት የተኩስ ማቆም በሁሉም የኢትዮጵያ ክፍሎች ላይ እንዲደረግ
-የምክክር ኮሚሽኑ በድጋሜ እንዲቋቋም እና ኮሚሽነሮቹም ገለልተኛ በሆነ መንገድ እንዲመረጡ
- የውይይት አጀንዳዎቹ ሁሉንም ባሳተፈ መልኩ እንዲቀረፁ እንዲሁም
-ውይይቶቹ አለም አቀፍ ታዛቢ በተገኘበት እንዲደረጉ
አሳስቧል።
የምክክር ቤቱን የመሰረቱት ፓርቲዎችም
1- መድረክ
2- ህብር ኢትዮጵያ
3- የአፋር ህዝብ ፓርቲ
4- የአፋር ፍትህ እና ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ
5- የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ)
6- የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ
7-የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር
8- የዎላይታ ብሄራዊ ንቅናቄ
9- ዓረና ትግራይ
10- የዶንጋ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት
መሆናቸው ተገልፃል።
ስለ ምክክር ቤቱ ለሚዲያችን አስተያየታቸውን የሰጡት የአፋር ህዝብ ፓርቲ መሪ እና የምክክር ቤቱ ሊቀመንበር ሆነው የተመረጡት አቶ ሙሳ አደም "ፓርቲዎቹ በተለያየ ጉዳይ ላይ የተለያየ አቋም ቢኖራቸውም ሀገራዊ ምክክሩ በሀቀኛ መንገድ መከናወን አለበት የሚለው ላይ ግን የማያወላዳ የጋራ አቋም አላቸው፤ አማራጭ የምክክር ቤት ለማቋቋም የወሰነውም ለዚህ ነው"
ብለዋል።
[Ubuntu News]
@YeneTube @FikerAssefa
የታለመ የነዳጅ ድጎማ ተጠቃሚ ተሸከርካሪዎች መለያ ይፋ ሆነ!
የታለመ የነዳጅ ድጎማ ተጠቃሚ የሚሆኑ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ተሸከርካሪዎች የድጎማው ተጠቃሚ መሆናቸውን የሚገልፅ መለያ ይፋ መሆኑን የትራንስፓርት እና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር አስታወቀ።
መለያው ሁለት አይነት ሲሆን ለመደበኛ ሀገር አቋራጭ የህዝብ ትራንስፖርት ተሸከርካሪዎች እና በክልል ለሚገኙ ተሸከርካሪዎች የሚያገለግል ነው።
መለያው ተሸከርካሪዎቹ የታለመ የነዳጅ ድጎማ ተጠቃሚ መሆናቸውን ለነዳጅ ማደያዎችና ለሚመለከታቸው ሌሎች አካላት መረጃ የሚሠጥ ነው።
Via EBC
@YeneTube @FikerAssefa
የታለመ የነዳጅ ድጎማ ተጠቃሚ የሚሆኑ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ተሸከርካሪዎች የድጎማው ተጠቃሚ መሆናቸውን የሚገልፅ መለያ ይፋ መሆኑን የትራንስፓርት እና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር አስታወቀ።
መለያው ሁለት አይነት ሲሆን ለመደበኛ ሀገር አቋራጭ የህዝብ ትራንስፖርት ተሸከርካሪዎች እና በክልል ለሚገኙ ተሸከርካሪዎች የሚያገለግል ነው።
መለያው ተሸከርካሪዎቹ የታለመ የነዳጅ ድጎማ ተጠቃሚ መሆናቸውን ለነዳጅ ማደያዎችና ለሚመለከታቸው ሌሎች አካላት መረጃ የሚሠጥ ነው።
Via EBC
@YeneTube @FikerAssefa
YeneTube
የታለመ የነዳጅ ድጎማ ተጠቃሚ ተሸከርካሪዎች መለያ ይፋ ሆነ! የታለመ የነዳጅ ድጎማ ተጠቃሚ የሚሆኑ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ተሸከርካሪዎች የድጎማው ተጠቃሚ መሆናቸውን የሚገልፅ መለያ ይፋ መሆኑን የትራንስፓርት እና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር አስታወቀ። መለያው ሁለት አይነት ሲሆን ለመደበኛ ሀገር አቋራጭ የህዝብ ትራንስፖርት ተሸከርካሪዎች እና በክልል ለሚገኙ ተሸከርካሪዎች የሚያገለግል ነው። መለያው…
ሙሉ ሰማያዊ ቀለም ያለው መለያ ለሀገር አቋራጭ የህዝብ ትራንስፖርት ተሸከርካሪዎች የሚያገለግል ሲሆን በነጭ መደብ የተዘጋጀው መለያ ደግሞ በክልል ለሚገኙ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎ ሰጪ ተሸከርካሪዎች የሚያገለግል ነው፡፡
በቅርቡ ተግባራዊ ለመሆን በዝግጅት ላይ የሚገኘው የታለመ የነዳጅ ድጎማ ስርዓት ተጠቃሚ የሚሆኑ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ተሸከርካሪዎችን የመለየትና መረጃ የማጥራት ስራ እየተከናወነበት እንደሚገኝ ይታወቃል።
@YeneTube @FikerAssefa
በቅርቡ ተግባራዊ ለመሆን በዝግጅት ላይ የሚገኘው የታለመ የነዳጅ ድጎማ ስርዓት ተጠቃሚ የሚሆኑ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ተሸከርካሪዎችን የመለየትና መረጃ የማጥራት ስራ እየተከናወነበት እንደሚገኝ ይታወቃል።
@YeneTube @FikerAssefa
የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ አራት የማጣሪያ ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከ ማላዊ ጋር አቻዉ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 2 - 1 በሆነ ውጤት ተሸንፏል ።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ከሽንፈት ያልታደገችውን ግብ አቡበከር ናስር ማስቆጠር ችሏል ። የማላዊውን የማሸነፊያ ሁለት ግቦች ጋባዲንሆ ምህንጎ አስቆጥሯል።
የዛሬውን ውጤት ተከትሎ ዋልያዎቹ ያለ ምንም ነጥብ ምድብ አራት ላይ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል።
ሀሙስ ምሽት 1:00 በማላዊ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከግብፅ ብሄራዊ ቡድን ጋር የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለተኛ የማጣሪያ ጨዋታቸውን የሚያከናውኑ ይሆናል።
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ከሽንፈት ያልታደገችውን ግብ አቡበከር ናስር ማስቆጠር ችሏል ። የማላዊውን የማሸነፊያ ሁለት ግቦች ጋባዲንሆ ምህንጎ አስቆጥሯል።
የዛሬውን ውጤት ተከትሎ ዋልያዎቹ ያለ ምንም ነጥብ ምድብ አራት ላይ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል።
ሀሙስ ምሽት 1:00 በማላዊ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከግብፅ ብሄራዊ ቡድን ጋር የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለተኛ የማጣሪያ ጨዋታቸውን የሚያከናውኑ ይሆናል።
@YeneTube @FikerAssefa
ሩሲያ ከአውሮፓ ህብረት ለዩክሬን የተለገሱ የጦር መሳሪያዎችን አወደምኩ አለች!
ሩሲያ ከአውሮፓ ህብረት ለዩክሬን የተለገሱ የጦር መሳሪያዎችን ማውደሟን አስታወቀች።ዩክሬን የሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ጦር ወይም ኔቶን እቀላቀላለሁ ማለቷን ተከትሎ ከሩሲያ ጋር ይፋዊ ጦርነት ከጀመረች 102 ቀናት ሆኖታል።
በዚህ ጦርነት ምክንያት ከ6 ሚሊየን በላይ ዩክሬናዊያን ዜጎች መኖሪያ ቤታቸውን ለቀው ሲሰደዱ 20 በመቶ የዩክሬን ክፍልም በሩሲያ ጦር ቁጥጥር ስር ወድቋል።
ጦርነቱን ተከትሎም አውሮፓ ህብረት፣አሜሪካ እና ሌሎች ሀገራት በሩሲያ ላይ ከስድስት ሺህ በላይ ማዕቀቦች የተጣሉባት ሲሆን፤ ሩሲያም የአጸፋ እርምጃ በመውሰድ ላይ ትገኛለች።ምዕራባዊያን ሀገራት ለዩክሬን የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን በመለገስ ላይ ሲሆኑ፤ ሩሲያም የተለገሱትን የጦር መሳሪያዎች በማውደም ላይ መሆኗን ገልጻለች።
ከሰሞኑ ከአውሮፓ ሀገራት ለዩክሬን የተለገሱ የጦር ተሽከርካሪዎችን እና ሌሎች የጦር መሳሪያዎችን ማውደሟን የሀገሪቱ ዜና ወኪል ታስ ዘግቧል።
የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አሜሪካ እና ሌሎች ምዕራባዊያን ሀገራት ለዩክሬን የጦር መሳሪያ እንዳይለግሱ አሳስበው ልገሳቸውን ከቀጠሉ ግን እርምጃ መውሰዴን እንደሚቀጥሉ አስጠንቅቀዋል።
ሩሲያ “ዚርኮን” የተባለ አዲስ ሃይፐርሶኒክ ክሩዝ ሚሳዔል ሞከረች
በተለይም ምእራባዊያን ሀገራት ረጅም ርቀት ተወንጫፍ ሚሳኤሎችን እንዳይለግሱ የተናገሩት ፕሬዝዳንት ፑቲን ሩሲያ ደህንነቷን ለመጠበቅ ስትል እርምጃ ትወስዳለች ብለዋል።
አሜሪካ፣ ስፔን እና ሌሎች የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት ለዩክሬን ሚሳኤሎች እና ሌሎች የጦር መሳሪያዎችን ለግሰዋል ተብሏል።
እንደ ሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር መግለጫ ከሆነ ምዕራባዊያን ለዩክሬን የጦር መሳሪያ በመለገስ ጦርነቱን የማራዘም እቅድ እንዳላቸው ተገልጿል።
Via Alain
@Yenetube @Fikerassefa
ሩሲያ ከአውሮፓ ህብረት ለዩክሬን የተለገሱ የጦር መሳሪያዎችን ማውደሟን አስታወቀች።ዩክሬን የሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ጦር ወይም ኔቶን እቀላቀላለሁ ማለቷን ተከትሎ ከሩሲያ ጋር ይፋዊ ጦርነት ከጀመረች 102 ቀናት ሆኖታል።
በዚህ ጦርነት ምክንያት ከ6 ሚሊየን በላይ ዩክሬናዊያን ዜጎች መኖሪያ ቤታቸውን ለቀው ሲሰደዱ 20 በመቶ የዩክሬን ክፍልም በሩሲያ ጦር ቁጥጥር ስር ወድቋል።
ጦርነቱን ተከትሎም አውሮፓ ህብረት፣አሜሪካ እና ሌሎች ሀገራት በሩሲያ ላይ ከስድስት ሺህ በላይ ማዕቀቦች የተጣሉባት ሲሆን፤ ሩሲያም የአጸፋ እርምጃ በመውሰድ ላይ ትገኛለች።ምዕራባዊያን ሀገራት ለዩክሬን የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን በመለገስ ላይ ሲሆኑ፤ ሩሲያም የተለገሱትን የጦር መሳሪያዎች በማውደም ላይ መሆኗን ገልጻለች።
ከሰሞኑ ከአውሮፓ ሀገራት ለዩክሬን የተለገሱ የጦር ተሽከርካሪዎችን እና ሌሎች የጦር መሳሪያዎችን ማውደሟን የሀገሪቱ ዜና ወኪል ታስ ዘግቧል።
የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አሜሪካ እና ሌሎች ምዕራባዊያን ሀገራት ለዩክሬን የጦር መሳሪያ እንዳይለግሱ አሳስበው ልገሳቸውን ከቀጠሉ ግን እርምጃ መውሰዴን እንደሚቀጥሉ አስጠንቅቀዋል።
ሩሲያ “ዚርኮን” የተባለ አዲስ ሃይፐርሶኒክ ክሩዝ ሚሳዔል ሞከረች
በተለይም ምእራባዊያን ሀገራት ረጅም ርቀት ተወንጫፍ ሚሳኤሎችን እንዳይለግሱ የተናገሩት ፕሬዝዳንት ፑቲን ሩሲያ ደህንነቷን ለመጠበቅ ስትል እርምጃ ትወስዳለች ብለዋል።
አሜሪካ፣ ስፔን እና ሌሎች የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት ለዩክሬን ሚሳኤሎች እና ሌሎች የጦር መሳሪያዎችን ለግሰዋል ተብሏል።
እንደ ሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር መግለጫ ከሆነ ምዕራባዊያን ለዩክሬን የጦር መሳሪያ በመለገስ ጦርነቱን የማራዘም እቅድ እንዳላቸው ተገልጿል።
Via Alain
@Yenetube @Fikerassefa
ሦስተኛው ዙር የህዳሴው ግድብ ሙሌት በሐምሌ ወር እንደሚጀመር ታወቀ!
የሁለተኛው ተርባይን ፍተሻ ተጀምሯል
ለመጀመሪያ ጊዜ ኃይል ማመንጨት ከጀመረ ሦስት ወራት ያለፉት የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሦስተኛ ዙር ሙሌት፣ ከመጪው ሐምሌ ወር አንስቶ መከናወን እንደሚጀምር ታወቀ፡፡ከክረምቱ መግባት ጋር ተያይዞ ወደ ግድቡ የሚፈሰው የውኃ መጠን ከሰኔ አጋማሽ ጀምሮ ከፍ እያለ ከሄደ በኋላ ወደ ግድቡ የሚገባውን ውኃ በመያዝ፣ በሐምሌ ወር ሙሌቱ እንደሚጀመር ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የህዳሴ ግድብ ከፍተኛ ኃላፊ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡
በዚህ ዓመት ወደ ግድቡ እንዲገባ የሚጠበቀውን የውኃ መጠን ለመያዝ የግድቡን ቁመት የመጨመር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው፣ የውኃ ሙሌቱ ሲጀመር የግድቡ ቁመት በሚፈለገው መጠን እንደሚደርስ አስረድተዋል፡፡ከክረምቱ መግባት በኋላ ባሉት ወራት የሚኖረው የውኃ መጠን የሚለያይና እየጨመረ የሚሄድ በመሆኑ፣ ከፍተኛው የውኃ መጠን የሚታየው በነሐሴ ወር ነው ብለዋል፡፡ በዚህም መሠረት ከሐምሌ ጀምሮ የሚፈለገው የውኃ መጠን ተይዞ፣ በነሐሴ ወር ውኃው በግድቡ ላይ ይፈሳል ሲሉ እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡
Via Reporter
@YeneTube @FikerAssefa
የሁለተኛው ተርባይን ፍተሻ ተጀምሯል
ለመጀመሪያ ጊዜ ኃይል ማመንጨት ከጀመረ ሦስት ወራት ያለፉት የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሦስተኛ ዙር ሙሌት፣ ከመጪው ሐምሌ ወር አንስቶ መከናወን እንደሚጀምር ታወቀ፡፡ከክረምቱ መግባት ጋር ተያይዞ ወደ ግድቡ የሚፈሰው የውኃ መጠን ከሰኔ አጋማሽ ጀምሮ ከፍ እያለ ከሄደ በኋላ ወደ ግድቡ የሚገባውን ውኃ በመያዝ፣ በሐምሌ ወር ሙሌቱ እንደሚጀመር ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የህዳሴ ግድብ ከፍተኛ ኃላፊ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡
በዚህ ዓመት ወደ ግድቡ እንዲገባ የሚጠበቀውን የውኃ መጠን ለመያዝ የግድቡን ቁመት የመጨመር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው፣ የውኃ ሙሌቱ ሲጀመር የግድቡ ቁመት በሚፈለገው መጠን እንደሚደርስ አስረድተዋል፡፡ከክረምቱ መግባት በኋላ ባሉት ወራት የሚኖረው የውኃ መጠን የሚለያይና እየጨመረ የሚሄድ በመሆኑ፣ ከፍተኛው የውኃ መጠን የሚታየው በነሐሴ ወር ነው ብለዋል፡፡ በዚህም መሠረት ከሐምሌ ጀምሮ የሚፈለገው የውኃ መጠን ተይዞ፣ በነሐሴ ወር ውኃው በግድቡ ላይ ይፈሳል ሲሉ እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡
Via Reporter
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ በትላንትናው እለት በደረሰ የጎርፍ አደጋ በዘጠኝ መኖሪያ ቤቶች ውድመት ደርሷል!
በአዲስ አበባ በጎርፍ አደጋ ከአንድ ነጥብ ሶስት ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት መውደሙንም የእሳት አደጋ ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል፡፡ጎርፉ በሁለት አካባቢዎች ከፍተኛ ውድመት አድርሷል።
የመጀመሪያው የጎርፍ አደጋ የደረሰው በዲስ አበባ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ላዩ ቦታው አየር ጤና አካባቢ ከቀኑ10፡30 ነው። ሁለተኛው አደጋ በኮልፌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 በተለምዶ ስልጤ ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከቀኑ 11 ሰዓት ከ20 ላይ መሆኑን የኮሚሽነ የህዝብ ግንኙነት ባላሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።
በደረሱት የጎርፍ አደጋዎች ዘጠኝ መኖሪያ ቤቶች ጉዳት ሲደርስባቸው አንድ ነጥብ ሶስት ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ውድማል። የድንገተኛ የጎርፍ አደጋ ቡድን በስፍራው በመድረስ ከመኖሪያ ቤቶቹ በፓንፕ ውሃ የማውጣት ስራ የሰራ ሲሆን ባደረገውም ርብርብ ከሰባት ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ማትረፍ መቻሉን አቶ ንጋቱ ጨምረው ተናግረዋል።
በአዲስ አበባ በመጪው የክረምት ወራት 148 ቦታዎች ለጎርፍ ተጋላጭ መሆናቸውን ያሳወቀው ኮሚሽኑ ችግሮች እንዳይፈጠር እየተሰራ መሆኑን ብስራት ሬዲዮ መዘገቡ ይታወሳል፡፡
[ዳጉ ጆርናል]
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ በጎርፍ አደጋ ከአንድ ነጥብ ሶስት ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት መውደሙንም የእሳት አደጋ ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል፡፡ጎርፉ በሁለት አካባቢዎች ከፍተኛ ውድመት አድርሷል።
የመጀመሪያው የጎርፍ አደጋ የደረሰው በዲስ አበባ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ላዩ ቦታው አየር ጤና አካባቢ ከቀኑ10፡30 ነው። ሁለተኛው አደጋ በኮልፌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 በተለምዶ ስልጤ ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከቀኑ 11 ሰዓት ከ20 ላይ መሆኑን የኮሚሽነ የህዝብ ግንኙነት ባላሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።
በደረሱት የጎርፍ አደጋዎች ዘጠኝ መኖሪያ ቤቶች ጉዳት ሲደርስባቸው አንድ ነጥብ ሶስት ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ውድማል። የድንገተኛ የጎርፍ አደጋ ቡድን በስፍራው በመድረስ ከመኖሪያ ቤቶቹ በፓንፕ ውሃ የማውጣት ስራ የሰራ ሲሆን ባደረገውም ርብርብ ከሰባት ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ማትረፍ መቻሉን አቶ ንጋቱ ጨምረው ተናግረዋል።
በአዲስ አበባ በመጪው የክረምት ወራት 148 ቦታዎች ለጎርፍ ተጋላጭ መሆናቸውን ያሳወቀው ኮሚሽኑ ችግሮች እንዳይፈጠር እየተሰራ መሆኑን ብስራት ሬዲዮ መዘገቡ ይታወሳል፡፡
[ዳጉ ጆርናል]
@YeneTube @FikerAssefa